Journalist Abdlwehab Bilall

Journalist Abdlwehab Bilall Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Journalist Abdlwehab Bilall, Media/News Company, Philadelphia, PA.

ሰውየው እኮ ግግም ብለው ባለ አደራውን፣ እሱ ነው ያገኘኝ አሉ ።መልዕክተኛው ደሞ በስልክ ደውሎ እኔ ነኝ ያገኘውሆት እኔ ነኝ የሰጠሁዎት እያላቸው አንተ አደለህም ባለ አደራው ነው አሉ። በዛ...
11/03/2025

ሰውየው እኮ ግግም ብለው ባለ አደራውን፣ እሱ ነው ያገኘኝ አሉ ።
መልዕክተኛው ደሞ በስልክ ደውሎ እኔ ነኝ ያገኘውሆት እኔ ነኝ የሰጠሁዎት እያላቸው አንተ አደለህም ባለ አደራው ነው አሉ።
በዛ ላይ ረዥም ጠይም ነው ብለው ነበር፣ ባላ አደራው አጭር ነው
ሰውዬው የሆነ ነገር ተምታቶባቸዋል

በሰውዲ እና በግብፅ የሚመራው ቡድን በወታደራዊ ሜዳ ያጣውን ድል በፕሮፖጋንዳ ለማግኘት እየጣረ ይገኛል ።በሰሞኑ በሱዳን እጅግ እስትራቴጂካዊ የሆነችውን ዳርፉርን አልቡርሃን ለቆ ወጥቷል ። ላ...
11/01/2025

በሰውዲ እና በግብፅ የሚመራው ቡድን በወታደራዊ ሜዳ ያጣውን ድል በፕሮፖጋንዳ ለማግኘት እየጣረ ይገኛል ።

በሰሞኑ በሱዳን እጅግ እስትራቴጂካዊ የሆነችውን ዳርፉርን
አልቡርሃን ለቆ ወጥቷል ። ላለፉት ሁለት አመታት የአልቡርሃን ሀይል ከግብፅ እና ከሳውዲ ጋር በመሆን ያልፈፀመው ወንጀል የለም ። በሱዳን ውስጥ ሞተ ከተባለው 120 ሺህ ሰው ከግማሽ በላዩ የሞተው ዳርፉር ውስጥ ነው ።

ተቀርጾ ቪዲዮው ባይወጣም አልቡርሃን ያልፈፀመው በደል የለም ። በሰሞኑ ዳርፉር ላይ የተፈፀመውን ወንጀል ለፖለቲካ ትርፍ ያቀናበረው አልቡርሃን እንደሆነ ነው የሚነገረው ።
ሰውዲ እና ግብፅ ያለቸውን መሳሪያ ሁሉ ሰጥተውን ማሸነፍ ሲያቀተው በRSF ውስጥ የራሱን ሰዎች አስገብቶ ሲቪሎችን እየገደሉ ቪዲዮ እንዲቀርፁ አድርጎ የፖለቲካ ጫና ለመፍጠር እንደ ሰራ ሀምዳን ዳጋሎ ተናግረዋል ።

አቡ ሉሉ የተሰኘው ግለሰብ በቁጥጥር ስር አውሎ እርምጃ ወስዷል ። በተቃራኒው አልቡርሃን በዳርፉር ለጨፈጨፋቸው ሰዎች እስካሁን ለጠያቂ የሆነ የለም ።

አልቡርሃን በተደጋጋሚ በአለም አቀፉ ማህበረሰብ የቀረበውን የትኩስ አቁም ስምምነት ውድቅ በማድረግ ሀገሩን የግብፁ አንባገነን አልሲሲ መጫወቻ ነው ያደረጋት ።
ጦርነት የቀሰቀሰው ስልጣኑን ለሲቪል መንግሰት ለማሸጋገር ፈቃደኛ ባለመሆኑ ነው ።

የእኛ ሀገር የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች ተረጋጉ በሱዳን እየሆነ ያለው ነገር አሳዛኝ ነው የዚህ ውጤት ግን ሽማግሌ ው ለሲቪል አስተዳደር ስልጣን አልሰጥም ያለው አል ቡርሃን እንጂ ሀሚቲ አይደለ...
10/31/2025

የእኛ ሀገር የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች ተረጋጉ

በሱዳን እየሆነ ያለው ነገር አሳዛኝ ነው የዚህ ውጤት ግን ሽማግሌ ው ለሲቪል አስተዳደር ስልጣን አልሰጥም ያለው አል ቡርሃን እንጂ ሀሚቲ አይደለም ።

ሀገርህ ኢትዮጵያ ውስጥ በየ አከባቢው ለሚገደለው ሰው ሳታዝን ለሱዳኖች አዛኝ መሆንህ የአዞ እንብ ያስመስለዋል ። በቅርብ ወራት እንኳን ስንት ሲቪሎች ተገደሉ ።

የሀገርህን ግድያ እንኳን በሰብዓዊነት ማውገዝ አልቻልክም ። በዘር በሀይማኖት ወግነህ የምታወራውም የኔ የምትለው ሰው ሲገደል ነው ። ሌላ ሲገደል ጥሩ ከሆንከ ዝም ትላለህ አብዛኞቹ የውጭ ሀገራት የሰብአዊ መብት ተሟጋቾች ግን ገዳይን ይከላከላሉ ።

ታዲያ ለራስህ ወንድም ያላዘንከ ለሌላ ሀገር ሰው አዘንኩ ብትል እምባህ የአዞ እንባ አይደለም ?

እኔን ከግብፅ አምባገነን ሲሲ ጋር ሆኖ ሊያጠፋኝ የሚያሴረውን ሽማግሌ አልቡርሃንን በቅርቡ ጀግናው ሀምዳን ዳጋሎ አንቆ ከቤተመንግስት ያስወጣዋል ።

የአልቡርሃን ለቅሶ ምንም አያመጣም

RSF በቅርቡ 🇸🇩 ካርቱም

ህንሸ አላህ

ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጅ ኡመር ኢድሪስ ያረፉበትን የመካነ መቃብር ስፍራ በአዲስ አበባ መጅሊሱ እውቅና መሰጠቱ ተገለፀ!የአዲስአበባ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጅ ኡመር ኢድ...
10/30/2025

ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጅ ኡመር ኢድሪስ ያረፉበትን የመካነ መቃብር ስፍራ በአዲስ አበባ መጅሊሱ እውቅና መሰጠቱ ተገለፀ!

የአዲስአበባ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጅ ኡመር ኢድሪስ የተቀበሩበትን ቦታ እና ከዚህ ጋር የሚያያዙ ጉዳዮችን አስመልክቶ በዛሬው ዕለት መግለጫ አውጥቷል።

- የመግለጫው ሙሉ ይዘት እንደሚከተለው ቀርቧል፦

ከአዲስ አበባ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ም/ቤት የተሰጠ መግለጫ።

የአባታችን የክቡር ዶ/ር ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር እድሪስ ሞት በሁላችንም ዘንድ ከፍተኛ የሐዘን ድባብ ፈጥሮብን መቆየቱ ይታወቃል። ተቀዳሚ ሙፍቲ እስከ ሕልፈተ ሕይወታቸው ድረስ በብዙ መልኩ ኢስላምንና ሙስሊሞችን ሲያገለግሉ የኖሩ አባት ነበሩ። በተለይ ለአዲስ አበባ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ደግሞ ተቋሙን በመሪነት ከአስር ዓመታት በላይ የመሩና አሻራቸውን ያስቀመጡ መሪያችን እንደመሆናቸው ኃዘናችን ጥልቅ መሆኑን ከዚህ በፊት ባወጠናቸው ተከታታይ መግለጫዎች መግለጻችን ይታወሳል።

አሁን በድጋሚ አላህ (ሱ.ወ) ምህረቱን እንዲለግሳቸዉና ጀነተል ፊርደዉስን ማረፊያቸዉ ያደርግላቸዉ ዘንድ አላህን እንማጸነዋለን። በማስከተልም ከሰሞኑ ከታዩ ሁነቶች ጋር በተያያዘ በቀጣይ ነጥቦች ላይ የምክር ቤቱን አቋም እንደሚከተለው ለመግለጽ እንወዳለን።

1. ለሕዝበ ሙስሊሙ አንድነት የመስራት ታሪክ ያላቸው ሙፍቲ ሞት ሕዝባችን በሀዘን ዉስጥ በነበረበት ሁኔታ ከቀብር ስፍራቸው ጋር ተያይዞ አላስፈላጊ የሆኑ ንትርኮች መነሳታቸው አሳዝኖናል። መሰል ዉዝግቦች ስሜትና ቡድንተኝነት ሲታከልባቸው ሙፍቲ ሲለፉለት የነበረውን አንድነትን ከማስጠበቅ በተቃራኒ ሕዝባችንን ወዳልሆነ ንትርክ፣ ጭቅጭቅ እና ክፍፍል የሚያመራ አደገኛ ነገር ነው።

2. ተቀዳሚ ሙፍቲ የተቀበሩበት ቦታ ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፕላንና ልማት ኮሚሽን በደብዳቤ ቁጥር አ/አ/ፕ/ል/ኮ02/910/2013 በቀን 05/10/13 በተፃፈ ደብዳቤ ከቅይጥ መኖሪያነት ወደ መካነ መቃብርነት የተቀየረ መሆኑን ለማረጋገጥ ችለናል፡፡ ስለሆነም ስፍራውን በአዲስ አበባ ውስጥ እንደሚገኙት የሕዝበ ሙስሊሙ መካነ መቃብሮች በመቁጠር በአስራ ሁለተኛ መካነ መቃብርነት እውቅና ሰጥተነዋል።

በመሆኑም የመቃብር ስፍራውም ተጨማሪ የማስፋሪያ ጥያቄ ለመንግስት ከማቃረባችን በተጨማሪ እንደሌሎቹ መካነ መቃብሮች ማንኛውም ሙስሊም ሲሞት የሚቀበርበት በመሆኑ ለመካነ መቃብሩ አስፈላጊውን ጥበቃ፣ ድጋፍ እና ክትትል በመጅሊሱ በኩል እንደሚደረግለት ማሳወቅ እንወዳለን። ስለሆነም ከአሁን በኋላ ከመካነ መቃብሩ ጋር በተያያዘ የሚደረጉ ማንኛውም ዓይነት አጀንዳዎች ሊቆሙ እንደሚገባ አናሳስባለን።

3. ከዚህ በኋላ የተለያዩ አጅንዳዎችን ምክንያት በማድረግ በሕዝባችን መካካል ክፍፍልን የሚፈጥሩና የሚያባብሱ እንዲሁም ሰላምን የሚያደፈርሱ ንትርኮች፣ ጭቅጭቆች እና ውግዘቶች እንዲቆሙ እናሳስባለን። ዉይይትን፥ መማማርንና መተሳሰብን ዓላማ ያላደረጉ መልዕክቶች በማህበራዊ ሚዲያም ሆነ በማንኛውም መድረክ እንዳይተላለፉ ጥሪ እናደርጋለን።

4. ለየትኛውም ሃይማኖታዊ አለመግባባቶች መፍትሄ ፍለጋው መንገዱ አላህ እንደነገረን መመለሻችን ቁርኣንና የነብያችን (ሰ.ዐ.ወ.) ፈለግ(ሱና) ዋቢ በማደረግ ሊሆን ይገባል። በዚህ ረገድ አርዓያዎቻችን መልዕክተኛው (ሰ.ዐ.ወ.) እና ሰሀቦቻቸው(ረ.ዐ.) ናቸው። ዑለሞችና ዱዓቶች የሕዝባችንን የዲን ግንዛቤና እውቀትን ለማስፋት የምታደርጓቸው አስተምህሮቶች፥ ዳዕዋዎች፥ በመልካም የማዘዝና ከመጥፎ የመከልከል ጥረቶች ከስሜት በራቀ፤ በእውቀት፣ በጥበብና በለዘብታ ቃል የተላበሰ መሆኑን ባረጋገጠ መልኩ ሊቀጥል እንደሚገባ እናሳስባለን።

5. አንዳንድ አካላት የተፈጠረውን ሁኔታ ሲጠብቁት እንደነበረ መልካም አጋጣሚ በማየት የራሳቸውን ድብቅ ፍላጎትና ዓላማን ለማሳካት ሕዝቡን የሚያሳዝኑ ድርጊቶችንና ንግግሮችን በማድረግ የሕዝባችንን ሐዘን አባብሰዋል። ምክር ቤቱ በምርጫ የተጣለበትን ታላቅ አደራ ለመወጣት በቁርጠኝነት የሚንቀሳቀስ ሲሆን በዚህ ረገድ ማንኛውንም የሕዝባችንን አንድነትና ጥቅሞችን የሚጎዱ አካላትንና አካሄዶችን ፈጽሞ እንደማይታገስ በጥብቅ ለማሳሰብ አንወዳለን።

6. በመጨረሻ በተከበሩ አባታችን ህልፈት ከፍተኛ ሀዘን ላይ ከሚገኙት ቤተሰቦቻቸው ጋር በመነጋገር ተቀዳሚ ሙፍቲ ሀጂ ዑመር እድሪስ የሚዘከሩበትና መልካም ሥራዎቻቸው ቀጣይነት እንዲኖራቸው የምናደርግበት ተቋም ጉዳይ ጥናት እየተደረገበት መሆኑን እየገለፅን ሙፍቲ ሐጂ ዑመርን ጨምሮ ሕዝበ ሙስሊሙን በማስተማርና አንድነቱ የተጠበቀ እንዲሆን ጥረት ሲያደርጉ የነበሩና በሞት የተለዩንን እንደነ ሐጅ ሙሐመድ ሳኒ ሐቢብ፥ ሐጅ ሙሐመድ ራፊዕ፥ ሐጅ ዘይኑ ሙቅና፥ ሐጅ ሙሳ ኪኪያና ሌሎችም ታላላቅ ዓሊሞቻችንንና ዱዓቶቻችን አላህ ጀነተል ፊርደውስን እንዲለግሳቸው አላህን እንማጸነዋለን።

ሕዝበ ሙስሊሙም የእነርሱን መልካም አርዓያነትን በመከተል ኢስላማዊ እውቀት እንዲሰራጭና የሕዝበ ሙስሊሙ አንድነት እንዲጠናከር የየበኩሉን ሚና እንዲወጣ ጥሪ እናደርጋለን።

አላህ ሃይማኖታችንን፥ሀገራችንና ሕዝባችንን ከክፉዎች ተልኮል ይጠብቀልን።

የአዲስ አበባ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት

10/30/2025

መለስ ዜናዊ የጀነት ነው 😂😂😂

10/30/2025

በዚህ ሀሳብ ይስማማሉ

የስልጣን እና የጥቅም ፀብኢትዮጵያ ውስጥ በሙስሊሙ ማህበረሰብ መካከል ያለው የአስተምህሮ ልዩነት አይደለም ። ጥቃቅን ልዩነቶች ናቸው በእነዚህ ልዩነቶች በዚህ ልክ ጠላት መሆን አይቻልም ። አ...
10/29/2025

የስልጣን እና የጥቅም ፀብ

ኢትዮጵያ ውስጥ በሙስሊሙ ማህበረሰብ መካከል ያለው የአስተምህሮ ልዩነት አይደለም ። ጥቃቅን ልዩነቶች ናቸው በእነዚህ ልዩነቶች በዚህ ልክ ጠላት መሆን አይቻልም ።

አንድ ቤት ወስጥ ብናይ አባት የሱፊያ ነው ልጁ ሰለፊያ ነው ። ወንድም እና እህቶች መካከል ይሄ ልዩነት አብዛኛው ቤት ላይ አለ ።
ይህ ሊዩነት የሙስሊሙ መሪዎች እርስበርስ የሚፈራረጁበትን ያክል የከረረ ፀብ የሚፈጥር አይደለም ።

ህዝበ ሙስሊሙ ሊገነዘበው የሚገባው ፀቡ የመጅሊስ የስልጣን ወንበር እና የጥቅም እንደሆነ ነው ።
አንዱ ከመጅሊስ ተገፍቻለሁ ብሎ የሚያስብ አካል መጅሊስ ለመግባት የሆኑ ጥቅሞችን ለመጠቀም ነው ። ሌላው እሱ እንዳይመጣበት ነው ።

በኡስታዝ ያሲን እና በሀሰን ታጁ መካከል የተነሳው ሀይማኖታዊ አስተምህሮ ወደ ፀብ የሚያመራም አልነበረም ። እንዳ አለም ማድረግ የነበረባቸው ጉዳዩ ይቻላል አይቻልም የሚለውን በቁርአን እና በሀዲስ ማመሳከር እና ያንን መናገር ነበር የነበረባቸው ዘለፋ ሳይሆን ።
ግን እነሱ እርስበርስ የጦርነት ዛቻ ነው ያሰሙት ይህም የግል ፀባቸውን ገላጭ ነው ።

10/28/2025

አጨቃጫቂው የሙፍቲ ቀብር

የስልጥኛ መዝሙር ቋንቋ መግባቢያ ነው በየትኛውም ቋንቋ የተኛውም ሀይማኖት ቢሰብክ ቢዘምር ምንም ችግር የለውም ይሁን እንጂ የቋንቋውን ተናጋሪ ህዝብ ሀይማኖት የሚነኩ አለባበሶችን መልበስ ወይ...
10/28/2025

የስልጥኛ መዝሙር

ቋንቋ መግባቢያ ነው በየትኛውም ቋንቋ የተኛውም ሀይማኖት ቢሰብክ ቢዘምር ምንም ችግር የለውም
ይሁን እንጂ የቋንቋውን ተናጋሪ ህዝብ ሀይማኖት የሚነኩ አለባበሶችን መልበስ ወይህ የሀይማኖቱን መለኮታዊ ተግባራትን ለሌ አላማ ማዋል ግጭት ቀስቃሽ ህገወጥ ተግባር ነው ።

እስላማዊ አለባበስን ተጠቅሞ የሌላ እምነት ሰበካ ማድረግ ሀይማኖቱን ማንቋሸሽ ወይም በሀይማኖቱ መቀለድ መሳለቅ ሲሆን ወንጀልም ነው ።

ሀገራዊ አብሮ የመኖር የመቻቻል እሴቶችን በመሸርሸር
ለሀይማኖት ግጭት በር ከፋች ነውና ሁሉም በራሱ የሀይማኖት ድንበር እንዲቆም ማድረግ የመንግስት ሀላፊነት ነው ።

በስልጥኛ መዝሙር መስራት ከተፈለገ አለባበሱ ና ውስጡ ላይ የያዘው መልእክት ከእስልምና እምነት ውጪ የሆነ በግልጽ የራሳቸውን ሀይማኖት ገላጭ ሆኖ ነው መሰራት ያለበት ።

እስላማዊ አስመስሎ በመስራት ማጭበርበር ሃይማኖቱን የሚቀይር ግን በፍጹም አይኖርም ።

የ92 አመቱ የካሜሮን ፕሬዘዳንት ምርጫ ማሸነፋቸው ተገለፀ ። በዚህ ምክንያት በተፈጠረ ግጭት 4 ሰዎች ሞተዋል ።
10/27/2025

የ92 አመቱ የካሜሮን ፕሬዘዳንት ምርጫ ማሸነፋቸው ተገለፀ ። በዚህ ምክንያት በተፈጠረ ግጭት 4 ሰዎች ሞተዋል ።

የሀበሻ ሴቶች ከኛ አልፈው ቻይናዊያንን አቃጥለው እየደፉ ነውይህ ወንድማችን በመኪና ሊገባ ነበር ወይፍቅ 💔💔
10/27/2025

የሀበሻ ሴቶች ከኛ አልፈው ቻይናዊያንን አቃጥለው እየደፉ ነው
ይህ ወንድማችን በመኪና ሊገባ ነበር ወይፍቅ 💔💔

ይህ ፖሊስ ጣቢያ የሀገሪቱን ባንዲራ ገልብጦ ሰቅሏል
10/27/2025

ይህ ፖሊስ ጣቢያ የሀገሪቱን ባንዲራ ገልብጦ ሰቅሏል

Address

Philadelphia, PA

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Journalist Abdlwehab Bilall posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share