
08/02/2025
ፓስፖርቱን የምናሳድስበት ጊዜ የለንም በማለት "ልጃቸውን" ኤርፖርት የጣሉት ጥንዶች ተይዘዋል
ጥንዶቹ የሽርሸር ጊዜያቸውን አጠናቀው ወደ ሃገራቸው ለመመለስ ባርሴሎና ኤርፖት ተገኝተዋል፡፡ የ10 ዓመት ዕደሜ ያለው ልጃቸውም አብሯቸው ነው፡፡ የጉዞ ሰነዱን ሲመለከቱት ጊዜው ያለፈበት ሆኖ ያገኙታል ይላል "ፎክስ ኒውስ፡፡"
እናም እንደ ዘበት አውላላው ሜዳ ላይ ጥለውት ሊጓዙ ይፈርዱበታል፡፡ በረራችን ያመልጠናል ያሉት ጥንዶቹ ህጻኑን በኤርፖርቱ የመንገደኞች ማቆያ ጥለውት ይሳፈራሉ፡፡
አፍታም ሳይቆይ አንዲት ሊሊያን የተባላች ጠርጠራ የኤርፖርቱ ተርሚናል ሰራተኛ የግለሰቦቹን ድርጊት የሚያወግዝ ተንቀሳቃሽ ምስል በማህበራዊ ሚዲያ ትለቃለች፡፡
ኤርፖርቱም መረጃ ይደርሰውና ለፖሊስ ጥቆማ በመስጠቱ ወላጆቹ በቁጥጥር ስር ይውላሉ፡፡
"ልጀቸውን" ዘመድ መጥቶ እንዲወስደው ተናግረው ነበር ህጻኑን ጥለውት የተሳፈሩት ትላለች ሊሊያ፡፡
ይሁን ልጁን መጥቶ ያነያሳው ወዳጀ ዘመድ አለመኖሩን የተገነዘበው የኤርፖርቱ አስተናባሪ በደረሰው ጥቆማ ምክንያት ነገሩ ይጋለጣል፡፡ ህጻኑም ወላጆቹ ጥለውት መሳፈራቸወን ይናራል፡፡
" የልጃቸው የጉዞ ሰነድ ስለተቃጠለ ብቻ ወላጆች እንዴት ልጃቸውን አውላላው ሜዳ ላይ ጥለው ይሄዳሉ ?
ልጁን መጥተው እንዲያነሱት ተነግሯቸዋል የተባሉት ዘመዶችም ኤርፖርት መጥተው ልጁን ለመውሰድ እንዴት አራት ሰዓት ያህል ይወስድባቸዋል?" ስትል ትናገራለች ሊሊያን፡፡
በመጨረሻም ፖሊስ የህፃኑን "ወላጆች በቁጥጥር ስር አውሏቸዋል ሲል “ Fox News “ ዛሬ አስነብቧል፡፡