EthioInfo

EthioInfo EthioInfo Media brings, social, economic, political and cultural issues to its audience.

ደቡብ አፍሪካ የሚኖረው ኢትዮጵያዊ ሀዘን ላይ ነው 😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭ደቡብ አፍሪካ ተወልደው ያደጉ ልጆቻችን እህትማማቾቹ ዲቦራ መንግስቴ ኦፕራ መንግስቴ ምንነቱ ባልታወቀ ሁኔታ የተማሪ ...
10/28/2025

ደቡብ አፍሪካ የሚኖረው ኢትዮጵያዊ ሀዘን ላይ ነው
😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭
ደቡብ አፍሪካ ተወልደው ያደጉ ልጆቻችን
እህትማማቾቹ
ዲቦራ መንግስቴ
ኦፕራ መንግስቴ

ምንነቱ ባልታወቀ ሁኔታ የተማሪ አኮሚዴሽን ውስጥ ባለ ክፍላቸው ሞተው ተገኝተዋል

ጥቁር ቀን ደቡብ አፍሪካ ለሚኖር ኢትዮጵያዊ

ቤተሰብ ጆሀንስበርግ ኪስንግተን ባለ የሀዘን መቀመጫ ስፍራ ላይ ተቀምጦል

ከቤተሰብ ተጨማሪ መረጃ ስናገኝ እናሳውቃለን

አምላክ መጽናናትን ለቤተሰብ ለወዳጅ ለዘመድ እንዲሁም ደቡብ አፍሪካ ለሚኖረው ወገናችን ይስጥ

አርቲስት ፍሬህይወት ባህሩ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየች አርቲስትና ኮሜዲያን ፍሬሕይወት ባህሩ ባጋጠማት ድንገተኛ ህመም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይታለች፡፡‎አርቲስቷ የቀለጠው መንደር፣ ፎርፌ፣ ረመ...
10/02/2025

አርቲስት ፍሬህይወት ባህሩ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየች

አርቲስትና ኮሜዲያን ፍሬሕይወት ባህሩ ባጋጠማት ድንገተኛ ህመም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይታለች፡፡

‎አርቲስቷ የቀለጠው መንደር፣ ፎርፌ፣ ረመጥ፣ ነቃሽ እና ሌሎች በርካታ በሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት በተሰሩ ቴአትሮች ላይ ተውናለች ።

‎አርቲስት ፍሬህይወት በሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት በውዝዋዜ እና ዳንስ ተቀጥረው ችሎታቸውን በመድረክ ካሳዩት ከያኒያን መካከል አንዷ ነበረች።

በሀገር ፍቅር ቴአትር ለበርካታ ዓመታት በሙያዋ ያገለገለችው አርቲስቷ፤ በበርካታ ፊልሞች፣ የቴሌቪዥን ድራማ እና የሙዚቃ ክሊፖች ላይ በትወና መሳተፏን የሀገር ፍቅር ቴአትር መረጃ አመልክቷል።

Via EthioFm
መስከረም 22/2018 ዓ.ም

ፅጌ በሳይክል ታሪክ ሰራች 👏ፅጌ ካህሳይ ኪሮስ በታዳጊዎች የጎዳና ላይ ውድድር ሰባተኛ ሆና በመውጣት ኢትዮጵያ በመንገድ ብስክሌት የአለም ሻምፒዮናዎች አስመዝግባ የማታውቀውን ትልቅ ውጤት በማ...
09/27/2025

ፅጌ በሳይክል ታሪክ ሰራች 👏

ፅጌ ካህሳይ ኪሮስ በታዳጊዎች የጎዳና ላይ ውድድር ሰባተኛ ሆና በመውጣት ኢትዮጵያ በመንገድ ብስክሌት የአለም ሻምፒዮናዎች አስመዝግባ የማታውቀውን ትልቅ ውጤት በማስመዝገብ ታሪክ ሰራች!

የመስቀል ደመራ በዓል የ2018 የመስቀል ደመራ በዓል በአዲስ አበባ መስቀል አደባባይ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨ...
09/26/2025

የመስቀል ደመራ በዓል

የ2018 የመስቀል ደመራ በዓል በአዲስ አበባ መስቀል አደባባይ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ጨምሮ በርካታ ሊቃነ ጳጳሳት እንዲሁም የኢፌድሪ ባህል እና ስፖርት ሚኒስቴር ክብርት ወይዘሮ ሸዊት ሻንካ ፣ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ክብርት ወይዘሮ አዳነች አበቤ ጨምሮ ሌሎች በርካታ እንግዶች በተገኙበት መከበር ጀምሯል።

" የኢትዮጵያን ህዝብ ከልብ ይቅርታ እንጠይቃለን “ " የተገኘው ውጤት ኢትዮጵያን የማይገልፅ ነው “ “ አትሌቶች ሀገራዊ ስሜት የላቸውም "            ስለሺ ስህን የኢትዮጵያ አትሌቲክ...
09/26/2025

" የኢትዮጵያን ህዝብ ከልብ ይቅርታ እንጠይቃለን “

" የተገኘው ውጤት ኢትዮጵያን የማይገልፅ ነው “

“ አትሌቶች ሀገራዊ ስሜት የላቸውም "
ስለሺ ስህን

የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን በቶኪዮው የአለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ዙሪያ በአሁኑ ሰዓት ጋዜጣዊ መግለጫ በመስጠት ላይ ይገኛል።

በጋዜጣዊ መግለጫው የተገኙት የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት ስለሺ ስህን በተገኘው ውጤት ማዘናቸውን ገልጸዋል።

“ በተገኘው ውጤት ፌዴሬሽኑ እንዲሁም ልዑክ ቡድኑ በጣም አዝኗል “ ሲሉ ስለሺ ስህን ተናግረዋል።

የተገኘው ውጤት “ ኢትዮጵያን የማይገልጽ “ ነው ሲሉ የገለፁት ፕሬዝዳንት ስለሺ ስህን “ ህዝቡን ከልብ ይቅርታ እንጠይቃለን “ ብለዋል።

በቶኪዮ ለማስመዝገብ ታቅዶ ስለነበረው እቅድ ያነሱት ስለሺ ስህን “ ሶስት ወርቅ ፤ አራት ብር ፤ አራት ነሐስ አቅድን ነበር “ ብለዋል።

በሌላ በኩል ፕሬዚዳንቱ ስለነበሩ ክፍተቶች አንስተው ያብራሩ ሲሆን “ አብሮ ለመስራት ፍላጎት አልነበረም “ ሲሉ አሳውቀዋል።

“ አትሌቶች አብራችሁ ልምምድ ስሩ በቡድን ስሩ ሲባሉ በአፍ እሺ እሺ ብለው ነገርግን አይተገብሩትም ፍላጎት የላቸውም “ ሲሉ ገልጸዋል።

በተጨማሪም “ ሀገራዊ ስሜት የለም “ ያሉት ስለሺ ስህን “ አትሌቶች ሀገራዊ ስሜት የላቸውም ለውጤቱ ተፅዕኖ አሳድሯል ወደፊት በስፋት ይሰራበታል “ ብለዋል።

የአርቲስት ሀና መርሐፅድቅ አባት የሆኑት መልአከ ፀሐይ መምህር አባ መርሐፅድቅ ጥሩነህ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል።የእኚህ ታላቅ መምህር የቀብር ሥነ-ሥርዓትም ተፈጽሟል። ለወዳጅ ዘመዶቻቸው...
09/26/2025

የአርቲስት ሀና መርሐፅድቅ አባት የሆኑት መልአከ ፀሐይ መምህር አባ መርሐፅድቅ ጥሩነህ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል።

የእኚህ ታላቅ መምህር የቀብር ሥነ-ሥርዓትም ተፈጽሟል።

ለወዳጅ ዘመዶቻቸውና ለቤተሰባቸው በተለይም ለልጃቸው አርቲስት ሀና መርሐፅድቅ መጽናናትን እንመኛለን።

ነብስ ይማር

ለ11 ዓመታት ካንሰርን የታገለችዉ የ14 ዓመቷ ዙዛ በምድር ላይ ከኖረችባቸው 14 ዓመታት 11ዱን ዓመታት ያሳለፈችው የካንሰር በሽታን በመታገል ነበር።  ሶስት ጊዜም የመቅኔ ተከላ ተደርጎላታ...
09/25/2025

ለ11 ዓመታት ካንሰርን የታገለችዉ የ14 ዓመቷ ዙዛ

በምድር ላይ ከኖረችባቸው 14 ዓመታት 11ዱን ዓመታት ያሳለፈችው የካንሰር በሽታን በመታገል ነበር።

ሶስት ጊዜም የመቅኔ ተከላ ተደርጎላታል።

ዙዛ ከካንሰር ጋር የምታደርገውን ትግል እና የቀን ውሎዋን በማኅበራዊ ሚዲያዎች በማጋራት በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ተከታዮችንም አፍርታ ነበር።

ይሁንና ዙዛ በተወለደች በ14 ዓመቷ ሕይወቷ ማለፉን ቤተሰቦቿ አሳውቀዋል፤ በርካቶችም ሀዘናቸውን እየገለፁ መሆኑን ኒውዮርክ ታይምስ ዘግቧል።

ዙዛ አስከሞተችበት ዕለት ድረስ ለብዙዎች ያጋጠሟትን ፈተናዎች እያሳየች እንደ እርሷ በተለያየ በሽታ ለሚሰቃዩ ሰዎች ተስፋ ሰጪ ቪድዮዎች ትሰራ ነበር።

ለተሽከርካሪ ዝግ የሚሆኑ መንገዶች ይፋ ተደረጉ ነገ መስከረም 16 ቀን 2018 ዓ.ም በመስቀል አደባባይ በሚከበረው የመስቀል ደመራ በዓል ምክንያት የትራፊክ መጨናነቅ እንዳይፈጠር የተወሰኑ መ...
09/25/2025

ለተሽከርካሪ ዝግ የሚሆኑ መንገዶች ይፋ ተደረጉ

ነገ መስከረም 16 ቀን 2018 ዓ.ም በመስቀል አደባባይ በሚከበረው የመስቀል ደመራ በዓል ምክንያት የትራፊክ መጨናነቅ እንዳይፈጠር የተወሰኑ መንገዶች ለተሽከርካሪ ዝግ ስለሚሆኑ አሽከርካሪዎች አማራጭ መንገዶችን እንዲጠቀሙ የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አሳስቧል፡፡

የ2018 ዓ.ም የመስቀል ደመራ በዓል በሠላም እንዲከበር የፀጥታና ደህንነት የጋራ ግብረ ኃይል ዝግጅቱን አጠናቆ ወደ ስራ መግባቱን ያስታወሰው ጠቅላይ መምሪያው፤ ነገ ከረፋዱ 4:00 ሠዓት ጀምሮ እስከ መርሀ ግብሩ ፍፃሜ ድረስ ለተሽከርካሪዎች ዝግ የሚደረጉ መንገዶችን ይፋ አድርጓል፡፡

በዚህም መሠረት፦
• ከቅዱስ ኡራኤል አደባባይ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ቅዱስ ኡራኤል አደባባይ፣

• ከቦሌ አቅጣጫ ወደ መስቀል አደባባይ ለሚመጡ ተሽከርካሪዎች ኦሎምፒያ አደባባይ ላይና ታች እንዲሁም ግራና ቀኝ፣

• ከመስቀል ፍላወር ወደ ኦሎምፒያ የሚወስደው መንገድ ጋዜቦ አደባባይ፣

• ከአጎና ሲኒማ ወደ መስቀል አደባባይ ለከባድ ተሽከርካሪ አጎና ሲኒማ አጠገብ እንዲሁም ለቀላል ተሽከርካሪ ጥላሁን አደባባይ (አራተኛ ክፍለ ጦር)፣

• ከለገሀር መብራት ወደ መስቀል አደባባይ ለገሀር መብራት፣

• ከቴሌ ማቋረጫ ወደ ስታድዮም ለሚጓዙ ቴሌ ማቋረጫ፣

• ከራስ ሆቴል ወደ ስታድየም ለሚመጡ ተሽከርካሪዎች ራስ ሆቴል፣

• ከሐራምቤ መብራት ወይም ከአምባሳደር ሲኒማ ወደ መስቀል አደባባይ ሃራምቤ መብራት፣

• ከብሔራዊ ቤተ መንግስት ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ብሔራዊ ቤተ መንግስት አጠገብ፣

• ከዛንቺስ ሼል ወደ ባምቢስ የሚወስደው መንገድ ከዛንቺስ ሼል አጠገብ፣ እንዲሁም

• ከጁፒተር ሆቴል ወደ ECA የሚወሰደው መንገድ ባምቢስ ሳልኮት ሕንጻ አጠገብ እስከ መርሀ ግብሩ ፍፃሜ ድረስ መንገድ የሚዘጋ መሆኑን አስታውቋል፡፡

በተጨማሪም በተገለጹት መስመሮች ላይ ተሽከርካሪዎችን ለአጭርም ይሁን ለረዥም ጊዜ ማቆም የተከለከለ መሆኑ የተገለጸ ሲሆን፤ አሽከርካሪዎች አማራጭ መንገዶችን በመጠቀም አስፈላጊውን ትብብር እንዲያደርጉ የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ጥሪውን አቅርቧል።

ሕብረተሰቡ ለፀጥታ ስጋት የሆኑ አጠራጣሪ ነገሮች ሲያጋጥሙት በ011-1-11-01-11 እንዲሁም በ991 ነፃ የስልክ መስመር ጥቆማ በመስጠትና አስፈላጊውን ትብብር በማድረግ የበኩሉን ድርሻ እንዲወጣም ጥሪ አስተላልፏል፡፡

5 ልጆችን በአንድ ጊዜ የወለደችው እናት  በኦሮሚያ ክልል የነቀምቴ ከተማ ነዋሪ የሆነችው ወ/ሮ አስቴር ተረፈ የተባለች እናት በወለጋ ዩኒቨርሲቲ ጠቅላላ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል 5 ልጆችን በአ...
09/25/2025

5 ልጆችን በአንድ ጊዜ የወለደችው እናት

በኦሮሚያ ክልል የነቀምቴ ከተማ ነዋሪ የሆነችው ወ/ሮ አስቴር ተረፈ የተባለች እናት በወለጋ ዩኒቨርሲቲ ጠቅላላ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል 5 ልጆችን በአንድ ጊዜ ወልዳለች።

ወ/ሮ አስቴር 3 ወንድ እና 2 ሴት እንደወለደች እና የሕፃናቱ የጤና ሁኔታ በጥሩ ደረጃ ላይ እንደሚገኝ ሆስፒታሉ አስታውቋል።

ከአምስት ዓመት በፊት አንድ ልጅ የወለደችው ይህች እናት ከዚያ በኋላ ልጅ ሳትወልድ የቆየች ቢሆንም አሁን ላይ 5 ልጆችን በአንድ ጊዜ መገላገል መቻሏ ተገልጿል።

(EBC)

ፓስፖርቱን  የምናሳድስበት  ጊዜ የለንም  በማለት     "ልጃቸውን"  ኤርፖርት የጣሉት ጥንዶች ተይዘዋልጥንዶቹ የሽርሸር ጊዜያቸውን አጠናቀው ወደ   ሃገራቸው  ለመመለስ ባርሴሎና ኤርፖት ተ...
08/02/2025

ፓስፖርቱን የምናሳድስበት ጊዜ የለንም በማለት "ልጃቸውን" ኤርፖርት የጣሉት ጥንዶች ተይዘዋል

ጥንዶቹ የሽርሸር ጊዜያቸውን አጠናቀው ወደ ሃገራቸው ለመመለስ ባርሴሎና ኤርፖት ተገኝተዋል፡፡ የ10 ዓመት ዕደሜ ያለው ልጃቸውም አብሯቸው ነው፡፡ የጉዞ ሰነዱን ሲመለከቱት ጊዜው ያለፈበት ሆኖ ያገኙታል ይላል "ፎክስ ኒውስ፡፡"

እናም እንደ ዘበት አውላላው ሜዳ ላይ ጥለውት ሊጓዙ ይፈርዱበታል፡፡ በረራችን ያመልጠናል ያሉት ጥንዶቹ ህጻኑን በኤርፖርቱ የመንገደኞች ማቆያ ጥለውት ይሳፈራሉ፡፡

አፍታም ሳይቆይ አንዲት ሊሊያን የተባላች ጠርጠራ የኤርፖርቱ ተርሚናል ሰራተኛ የግለሰቦቹን ድርጊት የሚያወግዝ ተንቀሳቃሽ ምስል በማህበራዊ ሚዲያ ትለቃለች፡፡

ኤርፖርቱም መረጃ ይደርሰውና ለፖሊስ ጥቆማ በመስጠቱ ወላጆቹ በቁጥጥር ስር ይውላሉ፡፡


"ልጀቸውን" ዘመድ መጥቶ እንዲወስደው ተናግረው ነበር ህጻኑን ጥለውት የተሳፈሩት ትላለች ሊሊያ፡፡

ይሁን ልጁን መጥቶ ያነያሳው ወዳጀ ዘመድ አለመኖሩን የተገነዘበው የኤርፖርቱ አስተናባሪ በደረሰው ጥቆማ ምክንያት ነገሩ ይጋለጣል፡፡ ህጻኑም ወላጆቹ ጥለውት መሳፈራቸወን ይናራል፡፡
" የልጃቸው የጉዞ ሰነድ ስለተቃጠለ ብቻ ወላጆች እንዴት ልጃቸውን አውላላው ሜዳ ላይ ጥለው ይሄዳሉ ?

ልጁን መጥተው እንዲያነሱት ተነግሯቸዋል የተባሉት ዘመዶችም ኤርፖርት መጥተው ልጁን ለመውሰድ እንዴት አራት ሰዓት ያህል ይወስድባቸዋል?" ስትል ትናገራለች ሊሊያን፡፡

በመጨረሻም ፖሊስ የህፃኑን "ወላጆች በቁጥጥር ስር አውሏቸዋል ሲል “ Fox News “ ዛሬ አስነብቧል፡፡

የበዛው የኢትዮጲያውያን በአሜሪካ የጎዳና ኑሮ ምክንያቱ ምን ይሆን?Land of opportunity የት ገባ?
08/02/2025

የበዛው የኢትዮጲያውያን በአሜሪካ የጎዳና ኑሮ
ምክንያቱ ምን ይሆን?
Land of opportunity የት ገባ?

Address

San Diego, CA

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when EthioInfo posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to EthioInfo:

Share