EthioInfo

EthioInfo EthioInfo Media brings, social, economic, political and cultural issues to its audience.

በዓመት ከ2 ሚ. ብር በላይ የሚያገኙ ቲክቶከርናዩቲዩበሮች   ግብር እንደሚከፍሉ ተገለጸ*ከ2 ሚ. ብር በታች  ገቢ ማግኘታቸው ከገቢ ግብር ነጻ አያደርጋቸውምእንደ ቲክቶክ እና ዩቲዩብ ካሉ የ...
12/30/2025

በዓመት ከ2 ሚ. ብር በላይ የሚያገኙ ቲክቶከርና
ዩቲዩበሮች ግብር እንደሚከፍሉ ተገለጸ

*ከ2 ሚ. ብር በታች ገቢ ማግኘታቸው ከገቢ ግብር ነጻ አያደርጋቸውም

እንደ ቲክቶክ እና ዩቲዩብ ካሉ የማኅበራዊ ሚዲያ መድረኮች በዓመት ከሁለት ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ የሚያገኙ የዲጂታል ይዘት ፈጣሪዎች፤ እንቅስቃሴያቸው "በንግድ ሥራነት" ተቆጥሮ ግብር እንዲከፍሉ የሚያደርግ ረቂቅ ሕግ ተዘጋጀ።

የገንዘብ ሚኒስቴር ያዘጋጀው ረቂቅ ደንብ፤ የዲጂታል ይዘት ፈጣሪዎች "ማስታወቂያዎች እና ስፖንሰርሺፖችን" ጨምሮ በተለያዩ መንገዶች ያገኙትን "ሁሉንም የገቢ መጠን" የሚያሳይ "የሂሳብ መዝገብ" እንዲይዙ ያስገድዳል።

ኢትዮጵያ ውስጥ ጥቂት ለማይባሉ ወጣቶች የገቢ ምንጭ በሆነው የዲጂታል ይዘት ፈጠራ የሚገኝ ገቢ ላይ ታክስ የሚጣልበት ሁኔታ በዝርዝር የተቀመጠው የገንዘብ ሚኒስቴር ባዘጋጀው የገቢ ግብር ረቂቅ ደንብ ነው።

የዲጂታል ይዘት ፈጣሪዎች ለመጀመሪያ ጊዜ የገቢ ግብር ከፋይ ዝርዝር ውስጥ የገቡት ባለፈው ዓመት ሐምሌ 2017 ዓ.ም. በጸደቀው "የገቢ ግብር አዋጅ" ነው። አዲሱ ረቂቅ ሕግ፤ በአዋጁ ላይ የተቀመጡ ድንጋጌዎችን የተመለከቱ ዝርዝር ጉዳዮችን የያዘ ነው። ከአምስት ወራት በፊት የጸደቀው አዋጅ፤ ከዲጂታል ይዘት ፈጠራ ገቢ የሚያገኝ "አንድ ግለሰብ ወይም ድርጅቶች" ግብር መክፈል እንዳለባቸው ደንግጓል።

'የዲጂታል ይዘት ፈጣሪ' በሚባለው ዝርዝር ውስጥ እንደ ዩትዩብ እና ቲክቶክ ያሉ "የቪዲዮ ማጋሪያ አገልግሎቶችን" እንዲሁም እንደ ፌስቡክ ያሉ "የማኅበራዊ ሚዲያ መድረኮችን" ተጠቅመው ገቢ የሚያገኙ ግለሰቦች ተጠቅሰዋል።

"የድምጽ ማስተላለፊያ (ፖድካስት)" እና "የቀጥታ ሥርጭት መድረኮች" ላይ ገንዘብ የሚሠሩ አካላትም እዚህ ውስጥ እንደሚካተቱ አዋጁ ያስረዳል።

ግብሩ የሚከፈለው እነዚህ ግለሰቦች ወይም ድርጅቶች "በኦንላይን መድረኮች ላይ የዲጂታል ይዘትን በመፍጠር እና በማሠራጨት" ከሚያገኙት "ማንኛውም ገቢ" ላይ እንደሆነም ተጠቅሷል። ይህ ገቢ "በጥሬ ገንዘብ ወይም በዓይነት የሚገኝ" ሊሆን እንደሚችልም ያስገነዝባል።

"ማስታወቂያዎች እና ስፖንሰርሺፖች" እንዲሁም "የገንዘብ ስጦታዎች እና የብዙኃን የገንዘብ ማሰባሰብ" ግብር ከሚከፈልባቸው የገቢ ምንጮች መካከል ተጠቅሰዋል።

ይዘት ፈጣሪዎች "በማስተዋወቂያ እንቅስቃሴ ምትክ" ከሚያገኟቸው "ዕቃዎች ወይም አገልግሎቶች" እንዲሁም ከሚፈጽሟቸው "የምርት ስም ስምምነቶች እና ድጋፎች" ግብር እንዲከፍሉ በአዋጁ ግዴታ ተጥሎባቸዋል።

ግብር የሚከፍሉት ከምን ያህል ገቢ ጀምሮ የሚያገኙ ይዘት ፈጣሪዎች እንደሆነ የተገለጸው ደግሞ አሁን በተዘጋጀው የገቢ ግብር ረቂቅ ደንብ ነው። ከዲጂታል ይዘት ፈጠራ የሚገኝ ገንዘብ "የንግድ ሥራ ገቢ" እንደሆነ ተቆጥሮ ግብር እንዲጣልበት የሚያደርጉ ሦስት ሁኔታዎች ረቂቁ ላይ ተቀምጠዋል።

የመጀመሪያው ሁኔታ ከይዘት ፈጣሪዎቹ ዓመታዊ ገቢ ጋር የተያያዘ ነው። የይዘት ፈጣሪው "ዓመታዊ ጠቅላላ ገቢ ከሁለት ሚሊዮን ብር በላይ ከሆነ" ተግባሩ እንደ 'ንግድ ሥራ ገቢ' ተቆጥሮ ግብር ይከፈልበታል።

"በፈጠራ ሥራ ላይ የተሰማራው ግብር ከፋይ በድርጅት መልክ የተቋቋመ" ከሆነም የንግድ ሥራ ገቢ ግብር እንዲከፍል ይገደዳል። ይዘት ፈጣሪዎች በዚህ ምድብ ውስጥ እንዲካተቱ የሚያደርገው ሌላኛው ሁኔታ ደግሞ "ግብር ከፋዩ የሂሳብ መዝገብ የመያዝ ግዴታ ያለበት ወይም ተቀናሽ ወጪ ያለው ከሆነ" የሚል ነው።

ይዘት ፈጣሪዎች በዓመት ከሁለት ሚሊዮን ብር በታች የሆነ ገቢ ማግኘታቸው ወይም እንደ ድርጅት አለመቋቋማቸው ግን ከገቢ ግብር ነጻ አያደርጋቸውም። እነዚህን ሁኔታዎች የማያሟሉ ከሆነ "ሌሎች ገቢዎች" በሚለው ምድብ ውስጥ ገብተው "ከጠቅላላ ገቢያቸው 15 በመቶውን" የመክፈል ግዴታ እንደሚኖርባቸው ባለፈው ዓመት ለጸደቀው አዋጅ የተዘጋጀው ማብራሪያ ላይ ተገልጿል።

"የንግድ ሥራ ገቢ ግብር" የሚለው ምድብ ውስጥ የሚገቡ ይዘት ፈጣሪዎች ከገቢ መረጃ እና መዝገቦች ጋር የተያያዙ ግዴታዎች በአዲሱ ረቂቅ ሕግ ይጣልባቸዋል።
ቢቢሲ -

ታዋቂው እንግሊዛዊ ቦክሰኛ አንቶኒ ጃሽዋ የ2 ሰዎችን ህይወት ከቀጠፈው አስከፊ የመኪና አደጋ ተረፈ
12/29/2025

ታዋቂው እንግሊዛዊ ቦክሰኛ አንቶኒ ጃሽዋ የ2 ሰዎችን ህይወት ከቀጠፈው አስከፊ የመኪና አደጋ ተረፈ

አዶናይ ብርሃነ ሀ/ሚካኤል በቁጥጥር ስር ዋለ‎AMN ታህሳስ 1/2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ አዶናይ ብርሃነ ሀ/ሚካኤል የተባለ ተጠርጣሪን በቁጥጥር ሥር አውሎ ምርመራ እያጣራ መሆኑ...
12/10/2025

አዶናይ ብርሃነ ሀ/ሚካኤል በቁጥጥር ስር ዋለ

‎AMN ታህሳስ 1/2018 ዓ.ም

የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ አዶናይ ብርሃነ ሀ/ሚካኤል የተባለ ተጠርጣሪን በቁጥጥር ሥር አውሎ ምርመራ እያጣራ መሆኑን ገልጿል።

አዶናይ ብርሃነ ሀ/ሚካኤል በቁጥጥር ሥር ሊውል የቻለው ‎ከኢትዮጵያ ሕዝብ ባህል እና መልካም ሥነ-ምግባር በተቃራኒ በሕዝብ ዘንድ ተቀባይነት የሌለው አስነዋሪ አለባበስ ለብሰው በአደባባይ እና በቴሌቪዥን ቀጥታ ስርጭት የታዩት አምስት ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር በዋሉበት የወንጀል ጉዳይ ጋር በተያያዘ መሆኑን የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ አስታውቋል።

ዕውቅና እና ገንዘብ ለማግኘት ብቻ በማሰብ ሚዲያዎችን ኃላፊነት በጎደለው አኳሃን እየተጠቀሙ በተለይ ወጣቱ ትውልድ በመልካም ሥነ ምግባር ተቀርጾ ሀገርን የሚጠቅሙ ተግባራትን እንዳያከናውንና በተቃራኒው በትውልዱ ላይ ርካሽ ባህል ለመጫን የሚደረገው ተግባር ለመከላከል የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ የጀመረውን ምርመራ አጠናክሮ እንደሚቀጥል የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ለኤኤምኤን በላከዉ መረጃ ያስታውቃል።

11/28/2025

ኢትዮ ኢንፎ ዩቲዩብ ቻናል ላይ ይጠብቁን።

የማህበራዊ ሚዲያ ማጭበርበሮች በጋራ እንከላከል
11/26/2025

የማህበራዊ ሚዲያ ማጭበርበሮች በጋራ እንከላከል

Enjoy the videos and music you love, upload original content, and share it all with friends, family, and the world on YouTube.

ደቡብ አፍሪካ የሚኖረው ኢትዮጵያዊ ሀዘን ላይ ነው 😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭ደቡብ አፍሪካ ተወልደው ያደጉ ልጆቻችን እህትማማቾቹ ዲቦራ መንግስቴ ኦፕራ መንግስቴ ምንነቱ ባልታወቀ ሁኔታ የተማሪ ...
10/28/2025

ደቡብ አፍሪካ የሚኖረው ኢትዮጵያዊ ሀዘን ላይ ነው
😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭😭
ደቡብ አፍሪካ ተወልደው ያደጉ ልጆቻችን
እህትማማቾቹ
ዲቦራ መንግስቴ
ኦፕራ መንግስቴ

ምንነቱ ባልታወቀ ሁኔታ የተማሪ አኮሚዴሽን ውስጥ ባለ ክፍላቸው ሞተው ተገኝተዋል

ጥቁር ቀን ደቡብ አፍሪካ ለሚኖር ኢትዮጵያዊ

ቤተሰብ ጆሀንስበርግ ኪስንግተን ባለ የሀዘን መቀመጫ ስፍራ ላይ ተቀምጦል

ከቤተሰብ ተጨማሪ መረጃ ስናገኝ እናሳውቃለን

አምላክ መጽናናትን ለቤተሰብ ለወዳጅ ለዘመድ እንዲሁም ደቡብ አፍሪካ ለሚኖረው ወገናችን ይስጥ

አርቲስት ፍሬህይወት ባህሩ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየች አርቲስትና ኮሜዲያን ፍሬሕይወት ባህሩ ባጋጠማት ድንገተኛ ህመም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይታለች፡፡‎አርቲስቷ የቀለጠው መንደር፣ ፎርፌ፣ ረመ...
10/02/2025

አርቲስት ፍሬህይወት ባህሩ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየች

አርቲስትና ኮሜዲያን ፍሬሕይወት ባህሩ ባጋጠማት ድንገተኛ ህመም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይታለች፡፡

‎አርቲስቷ የቀለጠው መንደር፣ ፎርፌ፣ ረመጥ፣ ነቃሽ እና ሌሎች በርካታ በሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት በተሰሩ ቴአትሮች ላይ ተውናለች ።

‎አርቲስት ፍሬህይወት በሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት በውዝዋዜ እና ዳንስ ተቀጥረው ችሎታቸውን በመድረክ ካሳዩት ከያኒያን መካከል አንዷ ነበረች።

በሀገር ፍቅር ቴአትር ለበርካታ ዓመታት በሙያዋ ያገለገለችው አርቲስቷ፤ በበርካታ ፊልሞች፣ የቴሌቪዥን ድራማ እና የሙዚቃ ክሊፖች ላይ በትወና መሳተፏን የሀገር ፍቅር ቴአትር መረጃ አመልክቷል።

Via EthioFm
መስከረም 22/2018 ዓ.ም

ፅጌ በሳይክል ታሪክ ሰራች 👏ፅጌ ካህሳይ ኪሮስ በታዳጊዎች የጎዳና ላይ ውድድር ሰባተኛ ሆና በመውጣት ኢትዮጵያ በመንገድ ብስክሌት የአለም ሻምፒዮናዎች አስመዝግባ የማታውቀውን ትልቅ ውጤት በማ...
09/27/2025

ፅጌ በሳይክል ታሪክ ሰራች 👏

ፅጌ ካህሳይ ኪሮስ በታዳጊዎች የጎዳና ላይ ውድድር ሰባተኛ ሆና በመውጣት ኢትዮጵያ በመንገድ ብስክሌት የአለም ሻምፒዮናዎች አስመዝግባ የማታውቀውን ትልቅ ውጤት በማስመዝገብ ታሪክ ሰራች!

የመስቀል ደመራ በዓል የ2018 የመስቀል ደመራ በዓል በአዲስ አበባ መስቀል አደባባይ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨ...
09/26/2025

የመስቀል ደመራ በዓል

የ2018 የመስቀል ደመራ በዓል በአዲስ አበባ መስቀል አደባባይ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ጨምሮ በርካታ ሊቃነ ጳጳሳት እንዲሁም የኢፌድሪ ባህል እና ስፖርት ሚኒስቴር ክብርት ወይዘሮ ሸዊት ሻንካ ፣ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ክብርት ወይዘሮ አዳነች አበቤ ጨምሮ ሌሎች በርካታ እንግዶች በተገኙበት መከበር ጀምሯል።

" የኢትዮጵያን ህዝብ ከልብ ይቅርታ እንጠይቃለን “ " የተገኘው ውጤት ኢትዮጵያን የማይገልፅ ነው “ “ አትሌቶች ሀገራዊ ስሜት የላቸውም "            ስለሺ ስህን የኢትዮጵያ አትሌቲክ...
09/26/2025

" የኢትዮጵያን ህዝብ ከልብ ይቅርታ እንጠይቃለን “

" የተገኘው ውጤት ኢትዮጵያን የማይገልፅ ነው “

“ አትሌቶች ሀገራዊ ስሜት የላቸውም "
ስለሺ ስህን

የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን በቶኪዮው የአለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ዙሪያ በአሁኑ ሰዓት ጋዜጣዊ መግለጫ በመስጠት ላይ ይገኛል።

በጋዜጣዊ መግለጫው የተገኙት የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት ስለሺ ስህን በተገኘው ውጤት ማዘናቸውን ገልጸዋል።

“ በተገኘው ውጤት ፌዴሬሽኑ እንዲሁም ልዑክ ቡድኑ በጣም አዝኗል “ ሲሉ ስለሺ ስህን ተናግረዋል።

የተገኘው ውጤት “ ኢትዮጵያን የማይገልጽ “ ነው ሲሉ የገለፁት ፕሬዝዳንት ስለሺ ስህን “ ህዝቡን ከልብ ይቅርታ እንጠይቃለን “ ብለዋል።

በቶኪዮ ለማስመዝገብ ታቅዶ ስለነበረው እቅድ ያነሱት ስለሺ ስህን “ ሶስት ወርቅ ፤ አራት ብር ፤ አራት ነሐስ አቅድን ነበር “ ብለዋል።

በሌላ በኩል ፕሬዚዳንቱ ስለነበሩ ክፍተቶች አንስተው ያብራሩ ሲሆን “ አብሮ ለመስራት ፍላጎት አልነበረም “ ሲሉ አሳውቀዋል።

“ አትሌቶች አብራችሁ ልምምድ ስሩ በቡድን ስሩ ሲባሉ በአፍ እሺ እሺ ብለው ነገርግን አይተገብሩትም ፍላጎት የላቸውም “ ሲሉ ገልጸዋል።

በተጨማሪም “ ሀገራዊ ስሜት የለም “ ያሉት ስለሺ ስህን “ አትሌቶች ሀገራዊ ስሜት የላቸውም ለውጤቱ ተፅዕኖ አሳድሯል ወደፊት በስፋት ይሰራበታል “ ብለዋል።

የአርቲስት ሀና መርሐፅድቅ አባት የሆኑት መልአከ ፀሐይ መምህር አባ መርሐፅድቅ ጥሩነህ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል።የእኚህ ታላቅ መምህር የቀብር ሥነ-ሥርዓትም ተፈጽሟል። ለወዳጅ ዘመዶቻቸው...
09/26/2025

የአርቲስት ሀና መርሐፅድቅ አባት የሆኑት መልአከ ፀሐይ መምህር አባ መርሐፅድቅ ጥሩነህ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል።

የእኚህ ታላቅ መምህር የቀብር ሥነ-ሥርዓትም ተፈጽሟል።

ለወዳጅ ዘመዶቻቸውና ለቤተሰባቸው በተለይም ለልጃቸው አርቲስት ሀና መርሐፅድቅ መጽናናትን እንመኛለን።

ነብስ ይማር

Address

San Diego, CA

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when EthioInfo posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to EthioInfo:

Share