EthioInfo

EthioInfo EthioInfo Media brings, social, economic, political and cultural issues to its audience.

ፓስፖርቱን  የምናሳድስበት  ጊዜ የለንም  በማለት     "ልጃቸውን"  ኤርፖርት የጣሉት ጥንዶች ተይዘዋልጥንዶቹ የሽርሸር ጊዜያቸውን አጠናቀው ወደ   ሃገራቸው  ለመመለስ ባርሴሎና ኤርፖት ተ...
08/02/2025

ፓስፖርቱን የምናሳድስበት ጊዜ የለንም በማለት "ልጃቸውን" ኤርፖርት የጣሉት ጥንዶች ተይዘዋል

ጥንዶቹ የሽርሸር ጊዜያቸውን አጠናቀው ወደ ሃገራቸው ለመመለስ ባርሴሎና ኤርፖት ተገኝተዋል፡፡ የ10 ዓመት ዕደሜ ያለው ልጃቸውም አብሯቸው ነው፡፡ የጉዞ ሰነዱን ሲመለከቱት ጊዜው ያለፈበት ሆኖ ያገኙታል ይላል "ፎክስ ኒውስ፡፡"

እናም እንደ ዘበት አውላላው ሜዳ ላይ ጥለውት ሊጓዙ ይፈርዱበታል፡፡ በረራችን ያመልጠናል ያሉት ጥንዶቹ ህጻኑን በኤርፖርቱ የመንገደኞች ማቆያ ጥለውት ይሳፈራሉ፡፡

አፍታም ሳይቆይ አንዲት ሊሊያን የተባላች ጠርጠራ የኤርፖርቱ ተርሚናል ሰራተኛ የግለሰቦቹን ድርጊት የሚያወግዝ ተንቀሳቃሽ ምስል በማህበራዊ ሚዲያ ትለቃለች፡፡

ኤርፖርቱም መረጃ ይደርሰውና ለፖሊስ ጥቆማ በመስጠቱ ወላጆቹ በቁጥጥር ስር ይውላሉ፡፡


"ልጀቸውን" ዘመድ መጥቶ እንዲወስደው ተናግረው ነበር ህጻኑን ጥለውት የተሳፈሩት ትላለች ሊሊያ፡፡

ይሁን ልጁን መጥቶ ያነያሳው ወዳጀ ዘመድ አለመኖሩን የተገነዘበው የኤርፖርቱ አስተናባሪ በደረሰው ጥቆማ ምክንያት ነገሩ ይጋለጣል፡፡ ህጻኑም ወላጆቹ ጥለውት መሳፈራቸወን ይናራል፡፡
" የልጃቸው የጉዞ ሰነድ ስለተቃጠለ ብቻ ወላጆች እንዴት ልጃቸውን አውላላው ሜዳ ላይ ጥለው ይሄዳሉ ?

ልጁን መጥተው እንዲያነሱት ተነግሯቸዋል የተባሉት ዘመዶችም ኤርፖርት መጥተው ልጁን ለመውሰድ እንዴት አራት ሰዓት ያህል ይወስድባቸዋል?" ስትል ትናገራለች ሊሊያን፡፡

በመጨረሻም ፖሊስ የህፃኑን "ወላጆች በቁጥጥር ስር አውሏቸዋል ሲል “ Fox News “ ዛሬ አስነብቧል፡፡

የበዛው የኢትዮጲያውያን በአሜሪካ የጎዳና ኑሮ ምክንያቱ ምን ይሆን?Land of opportunity የት ገባ?
08/02/2025

የበዛው የኢትዮጲያውያን በአሜሪካ የጎዳና ኑሮ
ምክንያቱ ምን ይሆን?
Land of opportunity የት ገባ?

ሴት አጋቾች!የ5 ዓመት ህፃን ልጅ አግተው 1 ሚሊዮን ብር የጠየቁ ግለሰቦች በእስራት ተቀጡ።በደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር በተድላ ጓሉ ክፍለ ከተማ ዐ7 ቀበሌ ልዩ ቦታው ሀቢታት እየተባለ ...
08/01/2025

ሴት አጋቾች!

የ5 ዓመት ህፃን ልጅ አግተው 1 ሚሊዮን ብር የጠየቁ ግለሰቦች በእስራት ተቀጡ።

በደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር በተድላ ጓሉ ክፍለ ከተማ ዐ7 ቀበሌ ልዩ ቦታው ሀቢታት እየተባለ በሚጠራው አካባቢ

* 1ኛ ተከሳሽ ናርዶስ ወይም ህይወት አዘነ
* 2ኛ ተከሳሽ ወርቅነሽ ወይም ትግስት ከልካይ የተባሉ ግለሰቦች

ጥር 29 ቀን 2017 ዓ/ም ከቀኑ 5 ሰዓት የ5 ዓመት ልጅ ከመኖሪያ ቤቱ ወስደው አግተው በማስቀመጥ ለቤተሰቦቹ 1 ሚሊዮን ብር ካልከፈሉ ህጻኑን ማግኘት እንደማይችሉ ይነግሯቸዋል።

በዚህም ቤተሰቦቹ ጉዳዩን ወደ ፖሊስ በመውሰድ ፖሊስ ባደረገው ያልተቋረጠ ክትትል ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር በማዋል አስፈላጊውን ምርመራ ያጣራ ሲሆን ተጠርጣሪ ግለሰቦቹ ሁለት ስም እና ከዚያ በላይ በመጠቀም ለወንጀል መፈጸሚያነት ሲገለገሉ እንደነበርም ታውቋል።

ፖሊስ አስፈላጊውን ምርመራ በማጣራት መዝገቡን ለዓቃቢ ህግ በመላክ ክስ ለመመስረት ችሏል።

የምስራቅ ጎጃም ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሐምሌ 23 ቀን 2017 ዓ/ም በዋለው ችሎት ተከሳሾች 1ኛ ናርዶስ ወይም ህይወት አዘነ 2ኛ ወርቅነሽ ወይም ትግስት ከልካይ ጥፋተኛ መሆናቸው በሰው ማስረጃ በመረጋገጡ እያንዳንዳቸው በ9 አመት እስራት መቀጣታቸውን የ2ኛ ፖሊስ ጣቢያ የታክቲክ ወንጀል ምርመራ ተወካይ ክፍል ሀላፊ ዋና ሳጅን ሱሌይማን ሰይድ ገልጸዋል።

አንዳንድ ግለሰቦች ወቅታዊ ሁኔታውን እንደምቹ ሁኔታ በመጠቀም በአቋራጭ ለመበልጸግ እና ሀብት ለማካበት በማሰብ የእገታ ወንጀል እንደሚፈጽሙ ገልጸው ከቅርብ ግዜ ወዲህ በጣቢያም ሆነ በከተማ አስተዳደር ደረጃ ወንጀል የሚፈጽሙ ተጠርጣሪዎችን አድኖ በመያዝ በህግ እንዲጠየቁ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰዋል።

አክለውም ህብረተሰቡ በእገታ ወንጀል እና መሠል ወንጀሎች የሚሳተፉ እና የሚጠረጠሩ ግለሰቦችን በሚመለከትበት ግዜ በአካባቢው ለሚገኙ የጸጥታ ሀይሎች ጥቆማ መስጠት እንደሚገባ መናገራቸውን ብስራት ሬዲዮ ከደብረ ማርቆስ ከተማ ፖሊስ መምሪያ ያገኘው መረጃ ያስረዳል።

በግ ሰርቆ የሸጠው መምህር በእስራት ተቀጣበምስራቅ ወለጋ ቦናያ ቦሼ ወረዳ በግ ሰርቆ የሸጠው መምህር በእስራት ተቀጣ። ጳውሎስ መኮንን የተባለ መምህር ሰኔ 24/2017 በቢሎ ከተማ ሰብሰብ ብ...
07/31/2025

በግ ሰርቆ የሸጠው መምህር በእስራት ተቀጣ

በምስራቅ ወለጋ ቦናያ ቦሼ ወረዳ በግ ሰርቆ የሸጠው መምህር በእስራት ተቀጣ። ጳውሎስ መኮንን የተባለ መምህር ሰኔ 24/2017 በቢሎ ከተማ ሰብሰብ ብለው ሳር ከሚግጡበት ቦታ የአቶ ኡስማን ከድሮ በግ በመስረቅ 6ሺህ ብር የተገመተችውን በ4500 ብር ሸጧል።

የቦናያ ወረዳ ፍርድ ቤትም በተከሳሽ ላይ የአንድ አመት ከስምንት ወር እስራት አስተላልፏል።

FastMereja

የጊዮኬሬሽ ቲሸርት ሽያጭ ክብረ ወሰን ሰብሯልከስፖርቲንግ ሊዝበን አርሰናልን የተቀላቀለው ቪክቶር ጊዮኬሬሽ መለያው እጅግ ተፈላጊ መሆኑን ዘ አትሌቲከስ ዘግቧል፡፡የ14 ቁጥር ለባሹ ስዊድናዊ አ...
07/29/2025

የጊዮኬሬሽ ቲሸርት ሽያጭ ክብረ ወሰን ሰብሯል

ከስፖርቲንግ ሊዝበን አርሰናልን የተቀላቀለው ቪክቶር ጊዮኬሬሽ መለያው እጅግ ተፈላጊ መሆኑን ዘ አትሌቲከስ ዘግቧል፡፡

የ14 ቁጥር ለባሹ ስዊድናዊ አጥቂ መለያ ሽያጭ የአርሰናል አዲስ ክብረ ወሰን ሆኖም ተመዝግቧል፡፡

ከተጫዋቹ መፈረም በኋላ አርሰናል የ27 አመቱን አጥቂ ስም በየትኛውም የክለቡ ቲሸርት ላይ በነጻ እንደሚያትም አሳውቋል፡፡

ከጊዮኬሬሽ በፊት የቡካዮ ሳካ፣ ማርቲን ኦዴጋርድ እና ደክለን ራይስ መለያ በብዙ የተሸጠ ሲሆን ባለፈው ዓመት ዋናውን ቡድን ከተቀላቀለ በኋላ ክስተት የሆነው የሊዩስ ስኬሊ ቲሸርትም ተፈላጊ መሆኑ ይፋ ሆኗል፡፡

ለቅድመ ውድድር ዝግጅት በሆንግ ጎንግ የሚገኘው አርሰናል 3ኛ የአቋም መለኪያ ጨዋታውን ሀሙስ ከቶተንሀም ሆትስፐር ጋር ያደርጋል፡፡

በጥቅሉ 75 ሚሊየን ብር አሸናፊዎች
07/29/2025

በጥቅሉ 75 ሚሊየን ብር አሸናፊዎች

ሲንግሏ የ50,000,000 ብር አሸናፊ የሽቱ :- የ50 ሚሊዮን ብሩን ሎተሪ ትኬት ጥዬው ነበር ከ2 ቀን በኃላ ግን ድጋሚ አገኘውት እንዴ ይሄ ነገር ምንድን ነው አልፋታ አለኝ ብዬ በማህበራ...
07/28/2025

ሲንግሏ የ50,000,000 ብር አሸናፊ

የሽቱ :- የ50 ሚሊዮን ብሩን ሎተሪ ትኬት ጥዬው ነበር ከ2 ቀን በኃላ ግን ድጋሚ አገኘውት

እንዴ ይሄ ነገር ምንድን ነው አልፋታ አለኝ ብዬ በማህበራዊ ሚዲያ የተለቀቀውን የ50 ሚሊዮን እጣ የወጣበትን ሳያ 50 ሚሊዮን ብር ደርሶኛል::

ሰይፉ ጥያቄ : አግብተሻል ?
የሽቱ :- አይ አላገባውም ገና ነኝ Single ነኝ

በጃር ንጹህ የመጠጥ ውሃ የሚያቀርቡ ፋብሪካዎች አስፈላጊውን የማጠቢያ ማሽን እንደሚጠቀሙ የኢትዮጵያ ምግብና መድሃኒት ባለስልጣን አስታወቀበኢትዮጵያ በንጹህ የመጠጥ ውሃ አቅርቦት ዘርፍ የተሰማ...
07/28/2025

በጃር ንጹህ የመጠጥ ውሃ የሚያቀርቡ ፋብሪካዎች አስፈላጊውን የማጠቢያ ማሽን እንደሚጠቀሙ የኢትዮጵያ ምግብና መድሃኒት ባለስልጣን አስታወቀ

በኢትዮጵያ በንጹህ የመጠጥ ውሃ አቅርቦት ዘርፍ የተሰማሩ ፋብሪካዎች አስፈላጊውን የማጠቢያ ማሽን ማሟላታቸውን በማረጋገጥ ፈቃድ እንደተሰጣቸው የኢትዮጵያ ምግብና መድሐኒት ባለስልጣን ለመናኸሪያ ሬዲዮ አረጋግጧል።

በ20 ሊትር የውሃ ማቅረቢያ ጃር ላይ የሚደረገው ሙሌት በየጊዜው የኬሚካል እጥበት የሚያስፈልገው በመሆኑ፤ በምግብና መድሃኒት ባለስልጣን ፍቃድ ያገኙ ፋብሪካዎች ለዚያ የሚያገለግሉ ማሽኖችን እንደሚጠቀሙ በባለስልጣኑ የምግብ አምራቾች ተቆጣጣሪ አቶ አዲስ አለቤ ገልጸዋል።

ገና ማምረት ሳይጀመሩ በፊት የማጠቢያ ማሽን ማሟላታቸው ፍቃድ ለማውጣት ዋናው መስፈርት ሆኖ እንደሚቀርብ ያስታወቁት ተቆጣጣሪው፤ በየሶስት ወራት በሚደረግ የቁጥጥር ስራ፣ በማሽን በመታገዝ የተጣራ ውሃ ሙሌት ማከናወናቸውን ተቋሙ እንደሚከታተል ተናግረዋል።

በመዲናዋ አብዛኛው ማህበረሰብ የጃር ውሃ ተጠቃሚ መሆኑን በመረዳት በህገ-ወጥ መንገድ በቤታቸው በማሽን እና ኬሚካል እቃውን ሳያጥቡ ያልተጣራ ውሃ የሚያከፋፍሉ ሊኖሩ እንደሚችሉ አያይዘው ገልጸዋል፡፡

ተጠቃሚዎች የጃር ውሃ ሲገዙ የደረጃዎች ኢንስቲትዩት አርማ ያለበት መሆኑን ማረጋገጥ እንዳለባቸው የተናገሩት አቶ አዲስ፣ የሚያጠራጥር ነገር ሲያስተውሉ በነጻ የስልክ መስመር 8482 ላይ በመደወል ጥቆማ እንዲሰጡ መልዕክት አስተላልፈዋል።

(መናኸሪያ ሬዲዮ)

በጨረቃ ላይ ውኃየቻይና ሳይንቲስቶች የጨረቃን አፈር በመጠቀም ከ50 ኪሎ ግራም በላይ ውኃ ማምረት መቻላቸውን ይፋ አደረጉ። ይህ ታላቅ ሳይንሳዊ ግኝት፣ ለወደፊት የሰው ልጅ በጨረቃ ላይ ዘላቂ...
07/28/2025

በጨረቃ ላይ ውኃ

የቻይና ሳይንቲስቶች የጨረቃን አፈር በመጠቀም ከ50 ኪሎ ግራም በላይ ውኃ ማምረት መቻላቸውን ይፋ አደረጉ።

ይህ ታላቅ ሳይንሳዊ ግኝት፣ ለወደፊት የሰው ልጅ በጨረቃ ላይ ዘላቂ መኖሪያ ለመመስረትና የጠፈር ጉዞዎችን ለማስፋት ከፍተኛ አስተዋጽኦ የሚያበረክት እንደሆነ ተመላክቷል።

የግኝቱ ዝርዝርና ሳይንሳዊ ዳራ ግኝቱ የተረጋገጠው ቻይና በ2020 ዓ.ም በቻንግኤ-5 የጠፈር መንኮራኩር አማካኝነት ከጨረቃ ይዛው በመጣችው የአፈር ናሙና (Lunar Regolith) ላይ በተደረገ ጥናት ነው።

ተመራማሪዎቹ የጨረቃን አፈር በከፍተኛ ሙቀት በማሞቅ፣ በውስጡ የተከማቸውን የውኃ ሞለኪውሎች በመልቀቅ ውኃ ማግኘት ችለዋል። ከዚህም በመነሳት፣ አንድ ቶን የጨረቃ አፈር ከ50 ኪሎ ግራም በላይ ውሃ የመስጠት አቅም እንዳለው ደርሰውበታል፤ ይህም ወደ 50 ለሚጠጉ ሰዎች የአንድ ቀን የመጠጥ ውኃ ፍላጎትን ሊያሟላ ይችላል ነው የተባለው።

የውሃው ምንጭ የፀሐይ ንፋስ በጨረቃ ላይ ከሚያስቀምጠው ሃይድሮጂን ጋር በጨረቃ አፈር ውስጥ የሚገኙ ማዕድናት በሚያደርጉት ኬሚካላዊ ምላሽ እንደሆነም ሳይንቲስቶቹ አስረድተዋል።

ይህ ግኝት ለጠፈር ምርምር ወሳኝ ምዕራፍ ተደርጎ ተወስዷል። ቀደም ሲል የጠፈር ተመራማሪዎች የሚያስፈልጋቸውን ውኃ በሙሉ ከምድር የማጓጓዝ ከባድና ውድ ተግባር ይፈጽሙ ነበር የተባለ ሲሆን፤ አሁን ግን በጨረቃ ላይ ውሃን ማምረት መቻሉ፣ የጨረቃን መሠረት ለመገንባትና ለረጅም ጊዜ በጨረቃ ላይ ለመቆየት ለሚደረገው ጥረት ትልቅ እገዛ ያደርጋል ተብሏል።

ከዚህም ባሻገር፣ ከውኃ ኦክስጅንና ሃይድሮጂን በመለየት ለሮኬት ነዳጅነት የመጠቀም ዕድልንም ይከፍታል ተብሏል።

የቻይና የጠፈር ኤጀንሲ (CNSA) ይህንን አዲስ ዘዴ በጨረቃ ላይ ለሚያደርጋቸው ቀጣይ ተልዕኮዎች ተግባራዊ ለማድረግ እቅድ እንዳለው የገለጸ ሲሆን፣ ግኝቱ የሰው ልጅ ወደ ጨረቃና ወደ ሌሎች ፕላኔቶች ለሚያደርገው ጉዞ ትልቅ ተስፋን ሰንቋል ነው የተባለው። (መናኸሪያ ሬዲዮ)

‎“ ፌዴሬሽኑ በአሜሪካ ጉዞ ምንም አይነት ወጪ አያወጣም “‎‎" 31 የቡድን አባላት ወደ አሜሪካ ያቀናሉ " አቶ ባህሩ ጥላሁን ‎‎ዋልያዎቹ ወደ አሜሪካ የሚያደርጉትን ጉዞ አስመልክቶ የኢትዮ...
07/28/2025

‎“ ፌዴሬሽኑ በአሜሪካ ጉዞ ምንም አይነት ወጪ አያወጣም “

‎" 31 የቡድን አባላት ወደ አሜሪካ ያቀናሉ " አቶ ባህሩ ጥላሁን

‎ዋልያዎቹ ወደ አሜሪካ የሚያደርጉትን ጉዞ አስመልክቶ የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን በአሁኑ ሰዓት መግለጫ እየሰጠ ይገኛል።

‎በመግለጫው አስተያየታቸውን የሰጡት የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ባህሩ ጥላሁን ስለ ጉዞው አብራርተዋል።

‎15 የቡድኑ አባላት አዲስ ቪዛ ያስፈልጋቸው እንደነበር የገለፁት አቶ ባህሩ ጥላሁን 7 አግኝተዋል እንዲሁም 8 ደግሞ ተከልክለዋል ብለዋል።

‎አቶ ባህሩ ጥላሁን አያይዘውም ቪዛው ያልተፈቀደው ከኤምባሲው ፖሊሲ ጋር የተያያዘ ነው ብለዋል።

‎በሌላ በኩል :-

‎- ቪዛ ከጠየቁ 6 የስራ አስፈፃሚ አባላት መካከል 3 አግኝተዋል።

‎- ከአሰልጣኝ አባላት 4 ጠይቀው 2 ሲያገኙ 2 አላገኙም “ ሲሉ አቶ ባህሩ ጥላሁን ተናግረዋል።

‎ይህንንም ተከትሎ 35 አባላት ይዞ ለመሄድ ስምምነት የነበረው ብሔራዊ ቡድኑ 31 አባላት በመያዝ ነገ ምሽት ወደ አሜሪካ እንደሚያቀና ተገልጿል።

‎[ ምንጮ - Tikvah Sport ]

በቻይና ኢትዮጵያዊቷ ጋዜጠኛ ተሸለመች                                    ዘገባ ዕዝራ እጅጉ ጋዜጠኛ ሰላም ተሾመ ከሰሞኑ በቻይና በተካሄደው የ"Road and Belt jou...
07/28/2025

በቻይና ኢትዮጵያዊቷ ጋዜጠኛ ተሸለመች

ዘገባ ዕዝራ እጅጉ

ጋዜጠኛ ሰላም ተሾመ ከሰሞኑ በቻይና በተካሄደው የ"Road and Belt journalist forum" ላይ ኢትዮጵያን ወክላ ተገኝታ ነበር።

ይህ ፎረም ለ 7ቀናት የቆየ ሲሆን ጋዜጠኛ ሰላም በዕለቱ ባደረገችው ከመንገድ ጋር የተያያዘ ንግግር ከፍተኛ አድናቆትን አትርፋለች፡፡ ጋዜጠኛዋ ሀሳቦችን በቁጥር ከመግለፅ ይልቅ ሰው ላይ ትኩረትን ያደረገ ሀሣብ በማቅረቧ በፎረሙ ተሳታፊዎች ዘንድ ለመደነቅ ችላለች፡፡

ጋዜጠኛ ሰላም ለተወዳጅ ሚድያ እንደተናገረችው ይህ ሥራዋ የአገሯን ስም እንድታስጠራ ያስቻላት መሆኑን ተሸላሚም እንዳደረጋት ገልፃለች።

"The Belt and Road Journalists Forum" በየዓመቱ የሚደረግ የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች እንዲሁም የመገናኛ ብዙኃን ላይ የሚያገለግሉ የሙያ ማህበራት
የሚሳተፉበት ጉባዔ ነው፡፡

ጉባዔው በ All China Journalists Association የሚዘጋጅ ሲሆን ዘንድሮ ለ ሰባተኛ ጊዜ በቻይና ጃንጉ ተደርጎል።

ከ 50 ሀገራት የተወጣጡ 100 ባለሙያዎች ተሳትፈውበታል። በመድረኩ
ላይ ከቤልት ኤንድ ሮድ ጋር እና ከጋዜጠኝነት ሙያ ጋር በተገናኘ ልምዳቸውን በንግግር ከገለጹ 8 ዓለም አቀፍ ጋዜጠኞች መካከል ሰላም ተሾመ አንዷ ነበረች።

በንግግሯም፣ ከቁጥራዊ ዘገባ ይልቅ የሰዎችን ሕይወት ተስፋዎችን እና ለውጦች እንዲሁም ፈተናዎችን በዘገባችን ማሳየት ይገባናል ብላለች።

ሙያቸውን በተመለከተ ንግግር ያደረጉት የኢትዮጵያ፣ቻይና፣ሰርቢያ ብራዚል እና የካምቦዲያ ጋዜጠኞች የ 2025 Belt and Road Journalists Forum የሚዲያ አምባሳደር ተደርገው እውቅና
ተሰጥቷቸዋል።

በዚህ ጉባዔ ላይ በኢትዮጵያ አርታኢያን ማህበር ፕሮዲዩስ የተደረገ አጭር ዘጋቢ ፊልም ምርጥ 10 ውስጥ በመግባት እውቅና አግኝቷል።ለአጭር ዘገባ ፊልሙ ውድድር 100 በላይ ፊልሞች ቀርበው ነበር።

ሰላም ተሾመ፣ ላለፉት 12 ዓመታት በተለያዩ ሚዲያዎች ከሪፖርተርነት እስከ ዋና አዘጋጅነት ሠርታለች፡፡ በዛሚ፣ፋና፣ኤል ቲቪ በሪፖርተርነት በአሀዱ ቴሌቪዥን ዜና ክፍል፣በዋዜማ ሬዲዮ በዋና አዘጋጅነት በያ ቲቪ በምክትል ሥራ አስኪያጅ እና አማካሪነት በአዲስ ዋልታ ቴሌቪዥን የዲጂታል ክፍል ዳይሬክተር
አሁን ደግሞ በፋና ቴሌቪዥን የመዝናኛ ክፍል ዋናአዘጋጅነት እና በፋና ማሰልጠኛ ደግሞ አሰልጣኝ ሆና እያገለገለች ትገኛለች።

ሰላም ተሾመ፣የመጀመሪያ እና ሁለተኛ ዲግሪዋን ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በጆርናሊዝም እና ኮምዩኒኬሽን አግኝታለች።ከ IMS,DW Akademie, CFI እንዲሁም Code for Africa ሥልጠናዎችን በመውሰድ ሰርቲፋይ ሆናለች።

Address

San Diego, CA

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when EthioInfo posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to EthioInfo:

Share