ዋግ ኸምራ

ዋግ ኸምራ Advocate of Wag Himira

ኢትዮጵያ ዉስጥ ስልጣን ላይ ባሉ ግለሰቦች ላይ የጥላቻ ዘመቻ በማድረግም ይሁን ስልጣን እንዲለቁ በማድረግ ለዉጥ እንደማይመጣ ከታወቀ ቆይቷል፡፡ ነገር ግን ዛሬም ግለሰቦችን እየመረጡ የሚተቹ ...
07/08/2025

ኢትዮጵያ ዉስጥ ስልጣን ላይ ባሉ ግለሰቦች ላይ የጥላቻ ዘመቻ በማድረግም ይሁን ስልጣን እንዲለቁ በማድረግ ለዉጥ እንደማይመጣ ከታወቀ ቆይቷል፡፡ ነገር ግን ዛሬም ግለሰቦችን እየመረጡ የሚተቹ ፖለቲከኞች ሞልተዋል፡፡
የየሰፈራችን ሰዎች ስልጣኑን እንዲይዙት በመመኜት የሚመጣ የስርዓትና የዲሞክራሲ ለዉጥ የለም፡፡ የሚገኝ ግላዊ ጥቅምና ስልጣን ግን ሊኖር ይችላል፡፡ ከዚህ ጥቅም ተቋዳሽ የሆነ የፌስቡክ መንጋም ሊኖር ይችላል፡፡
ለማንኛዉም ለ30 ዓመታት ዶላር ሲያጠራቅም የነበረዉና አሁን እያጠራቀመ ያለዉ ቡድን የሚያደርጉትን የጦርነት ግብግብ ከህዝባችን ሜዳ ቢያወጡት ምንኛ ደስ ባለን ነበር!!

Eshetu

ፖለቲካ ውስጥ ስልጣን ለብቻ ለመቆጣጠር ስም ማጥፋት ያለ እና የተለመደ አካሄድ ነው። ከሌላው ብቻ ተመርጣችሁ እናንተ ላይ ዘመቻ የተደረገው በምክንያት ነው። አካዳሚካሊ ጥሩ ናችሁ፣ የመጣችሁበ...
07/08/2025

ፖለቲካ ውስጥ ስልጣን ለብቻ ለመቆጣጠር ስም ማጥፋት ያለ እና የተለመደ አካሄድ ነው። ከሌላው ብቻ ተመርጣችሁ እናንተ ላይ ዘመቻ የተደረገው በምክንያት ነው። አካዳሚካሊ ጥሩ ናችሁ፣ የመጣችሁበት አካባቢ የተለየ ስለሆነ፣ ያ ክልል ውስጥ ስልጣኑም፣ ሃብቱም በእኛ ቁጥጥር ስር መሆን አለበት ብሎ የሚዶልት ሃይል አለ።

አማራ አማራ የሚሉት ለሽፋን ነው። ይሄ ቡድን ከራሱ ጥቅም ውጪ ሌሎችን ማየት መስማት አይፈልግም። በተደጋጋሚ በማስረጃ ተፈትሸው ወድቀዋል፤ ሙስሊም ስለሆንን የሚል ግምት እንዳትይዙ፣ ወሎዬ የሆነ ግለሰብ ሁሉ ኦሮሞ እያደረጉ መፈረጅ ከተጀመረ ቆይቷል።

ያ ክልል መዋቅሩ ብልሹ እና ቆሻሻ ነው። እንደ አዲስ መደራጀት አለበት የምንለው በምክንያት ነው። በጣም ቀፋፊ ክልል ነው። ከላይ እስከታች በመጥፎ ሁኔታ የተደራጀ ስብስብ ነው። ፖለቲካ ላይ ምንም አይነት ይሉንታ የሚባል ነገር የለም።

የሌሎችን መብት አለመንካት እንጂ የመጣችሁበት አካባቢ ማህበረሰብ የኢኮኖሚ ጥቅም እና ስልጣን ተካፋይ ማድረግ ትክክል ነው። በእናንተ ላይ ስም ማጥፋት ዘመቻ ያደረገው ልጅ ከኪሱ መዞት እንዳይመስላችሁ፤ ተልኮ ነው። በደንብ ታቅዶበት የሚሰራ ፕሮፓጋንዳ ነው።

- ያ ክልል ስልጣን ክፍፍል ፍጹም ልክ አይደለም
- የሃብት ስርጭቱም ፍጹም ልክ አይደለም
- የስራ ክፍፍሉም በፍጹም የህዝቡን ስብጥር የሚወክል

አይደለም እናም ወንድሞች ቆራጥ መሆን ይገባል። ማንንም እንዳትለማመጡ፣ ወሎዬን ሁሉ ኦሮሞ እያሉ መፈረጅ እና ስም ማጥፋት አዲስ ፕሮፓጋንዳ አይደለችም። እውቀት እና አቅም ያላችሁ ግለሰቦች ስለሆናችሁ ለስልጣን ስለምታሰጉ ነው እናም ሁሉም የራሱ አካባቢ ማስተዳደር እና በእኩል መወከል አለበት።

የሃብት ክፍፍሉም በስርዓት መከፋፈል አለበት። መላቀቅ የለም። የክልሉ በጀት ሰባራ ሳንቲም ሳይቀር ለሁሉም እኩል መካፈል አለበት።

አይዞን አለን 💪💪

Ashagre Getachew

" ቡድኑ ትግራይን ለማተራመስና ኢትዮጵያን ለመውጋት ከኤርትራ መንግስት እየሰራ ጋር ነው " - ስምረት ፓርቲየኢፌዴሪ መንግስት ከኢትዮጵያ የፓለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባ የተሰረዘው '  #ህወሓት ...
07/07/2025

" ቡድኑ ትግራይን ለማተራመስና ኢትዮጵያን ለመውጋት ከኤርትራ መንግስት እየሰራ ጋር ነው " - ስምረት ፓርቲ

የኢፌዴሪ መንግስት ከኢትዮጵያ የፓለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባ የተሰረዘው ' #ህወሓት ' ላይ ህጋዊ እርምጃ መውሰድ እንጂ ማስታመም አይገባውም አለ ዴሞክራሲያዊ ስምረት ትግራይ (ስምረት) ፓርቲ።

በቀድሞ የህወሓት ምክትል ሊቀ-መንበርና የትግል ጓደኞቻቸው በቅርቡ ከብሄራዊ የምርጫ ቦርድ የቅድመ እውቅና ምዝገባ የተሰጠው ስምረት " ለህግ የማይገዛ ወመኔ " ሲል የገለፀው ህወሓት ትግራይን ለማተራመስና ኢትዮጵያ ለመውጋት ከኤርትራ መንግስት እየሰራ ነው " ሲል ከሶታል።

" ኋላ ቀር ቡድን " በማለት በገለፀው ህወሓት ምክንያት የትግራይ ህዝብ መልሶ ወደ ጦርነት እንዳይገባ የፌደራል መንግስት ሃላፊነቱ እንዲወጣ አሳስቧል።

" ከአሁን በኋላ በትግራይ ላይ የሚፈፀሙ ጥፋቶች ብቸኛው ተጠያቂ ከዓለም አቀፍና አገራዊ ህጎች የተቃረነው ወመኔው ኋላ ቀር ቡድን እና መሰሎቹ መሆናቸው የኢትዮጵያ መንግስት መገንዘብ አለበት " ሲልም ስምረት ፓርቲ ገልጿል።

" የሃይማኖት አባቶች ፣ የአገር ሽማግሌዎች ፣ ወጣቶች በአገር ውስጥና በመላ ዓለም የሚገኙ ትግራዎት ቡድኑ በስልጣን የሚቆይባቸው እያንዳንዱ ቀናት በህዝብ ላይ አስከፊ መከራና ስቃይ የሚያስከትሉ መሆናቸው በመረዳት ትግላችሁ አጠናክሩ " ሲል ጥሪ አቅርቧል።

ፓርቲው ለታጠቀው ሰራዊት ባስተላለፈው ጥሪ " ሌት ተቀን የጦርነት ነጋሪት ከሚጎስመው ኋላ ቀር ቡድን ራሳችሁን በማራቅ ከሰላም ፈላጊ ህዝብ ጎን ተሰለፉ " ብሏል።

" ከአሁን በኋላ በትግራይ ህዝብ ላይ የሚፈፀም ወንጅልም ይሁን የሚቀሰቀስ ጦርነት በዝምታ ማየት በህዝብ ላይ የሚያስከትለው ከባድ አደጋ መዘንጋት ነው " ያለው ስምረት ፓርቲ " አደጋውን አስቀድሞ ለማስቀረት ሁሉም የሚመለከታቸው አካላት ሚናቸው ከወዲሁ እንዲወጡ " በማለት ለአገር አቀፍና ዓለምአቀፍ ተቋማት ጥሪውን አቅርቧል።

07/06/2025

I got over 18,000 reactions on my posts last week! Thanks everyone for your support! 🎉

ሁለቱ ወንድማማቾች!          Reposted.የእርሻ መሬት ወርሰው በጋራ የሚሰሩ ሁለት ወንድማማቾች ነበሩ፡፡ አንድኛው ትዳር መስርቶ ትልቅ ቤተሰብ ሲኖረው ሁለተኛው ግን ብቻውን ነበር የ...
07/06/2025

ሁለቱ ወንድማማቾች!
Reposted.

የእርሻ መሬት ወርሰው በጋራ የሚሰሩ ሁለት ወንድማማቾች ነበሩ፡፡ አንድኛው ትዳር መስርቶ ትልቅ ቤተሰብ ሲኖረው ሁለተኛው ግን ብቻውን ነበር የሚኖረው፡፡

ከዕለታት አንድ ቀን ወንድማማቾቹ ከቤተሰባቸው የወረሱትን ሀብትና ንብረት በመከፋፈል በየግላቸው ለመስራት ይስማማሉ፡፡ ከዚያም ያለውንም ሀብት እኩል ተከፋፍለው የየግላቸውን ኑሮ ይጀምራሉ፡፡

ወድያውኑ ግን ብቻውን የሚኖረው ወንድሙ ከራሱ ጋር መነጋገር ይጀምራል “ያለውን ሀብትና ትርፍ እኩል መከፋፈላችን አግባብ አልነበረም፡፡ እኔ ብቻየን ነው የምኖረው የሚያስፈልገኝ ነገር በጣም ትንሽ ነው፡፡ እርሱ ግን ብዙ የቤተሰብ ሀላፊነት አለበት” በማለት ያስባል፡፡
እናም በጎተራው ካለው እህል አንድ ጆንያ የሚሆነውን ሁል ግዜ ማታ ማታ እየተደበቀ ወንድሙ ጎተራ ውስጥ ማስገባት ይጀምራል፡፡

በተመሳሳይ ግዜ ሚስትና ልጆች ያሉት ወንድምም በተመሳሳይ ሁኔታ ያስባል “ይህንን ሀብት እኩል መካፈል አልነበረብንም፡፡ እኔኮ ትዳር አለኝ፡፡ ሚስቴና ልጆቼ ሁል ግዜ ከጎኔ በመሆናቸው ወደፊት በደንብ ይንከባከቡኛል፡፡ወንድሜ ግን ብቸኛ ነው፡፡ ወደፊት አጠገቡ ሆኖ የሚንከባከበው እንኳ የለውም” ሲል ያስባል፡፡

እርሱም እንደዚያኛው ወንድሙ በጎተራ ካለው እህል አንድ ጆንያ የሚሆነውን ሁል ግዜ ማታ ማታ እየተደበቀ ወንድሙ ጎተራ ውስጥ ማስገባት ይጀምራል፡፡ ወንድማማቾቹ በዚህ ሁኔታ ለብዙ ግዜ ኖሩ፡፡

ከብዙ ግዜ ብኋላ ግን ሁለቱንም አንድ ነገር ያስገርማቸው ጀመር፡፡ በጎተራቸው ውስጥ ያለው እህል መጠን እየቀነሰ አለመሄዱ ግራ ያጋባቸዋል፡፡ ሁለቱም የገጠማቸውን ያልተለመደ ነገር ለመመርመር በየግላቸው
እየጣሩ ሳለ ከእለታት አንድ ቀን ሌሊት ላይ የተለመደውን ተግባራቸውን ለመፈጸም እህል የተሞላበት ከረጢት እንደተሸከሙ በድንገት ተገናኙ ። ምንም አይነት ቃላት ሳይለዋወጡ ሸክማቸውን መሬት ላይ በመጣል በፍቅር ተቃቅፈው አለቀሱ።

የመተሳሰብ ፍቅር በአይምሮህ አስበህ በአንደበትህ የምታወጣው ቃል ሳይሆን፣ በልብህ የሚንፈራገጥ የማይወለድ ፅንስ ነው!!

የአንድ አባት ልጆች ነን!!

@ የአብወይ ልጅ

07/06/2025

ማህተሙ ምን ይላል? "በወሎ ጠቅላይ ግዛት ፣ የኮረም ሰቆጣ ማዘጋጃ ቤት " ይላል፡፡ ከታደልክ "ሀ" ብለህ በማስረጃ ፣ እምቢ ካልክ "ዋ" ብለህ በሳንጃ ሀቋን ትማራለህ!!!

ባለቤትሽ (የፍቅር ጓድሽ) እንዳይተውሽ ማድረግ ካሉብሽ ጥንቃቄዎች ውስጥ፦፩) ወንዶች በማይከበሩበት ቦታ መቆየት     አይፈልጉም።     ይህ ኩራት ወይም እብሪተኝነት አይደለም።     የክብ...
06/29/2025

ባለቤትሽ (የፍቅር ጓድሽ) እንዳይተውሽ ማድረግ ካሉብሽ ጥንቃቄዎች ውስጥ፦

፩) ወንዶች በማይከበሩበት ቦታ መቆየት
አይፈልጉም።
ይህ ኩራት ወይም እብሪተኝነት አይደለም።
የክብራቸውና የማንነታቸው ጉዳይ ነው። እንደ
አክብሮት ማጣት ወንዶችን የሚያናድዳቸው
ነገር የለም። ራሳቸው ለራሳቸው ካልሆኑ
ማንም እንደማይመጣላቸው ስለሚያውቁ
እራሳቸውንም ሌላውንም ያስከብራሉ።

ስለዚህ በቀልድ መሀልም ቢሆን ክብሩን
ከመንካት ተቆጠቢ። ወንድ በክብሩና በማንነቱ
ጉዳይ ስሜታዊ ነው።

፪) ወዳጅ ዘመዶቹን አክብሪ።
ልክ እንደ ራሱ የወዳጅ ዘመዱን ክብር
ስለምፈልግ ጠብቂለት። እንዳትወጃቸው
የሚያደርግሽ ምክንያት ብታገኝ እንኳን
ክብራቸውን አትቀንሽ።

፫) ሙያተኛ ሁኝ።
ሌላው ቢቀር በምግብ አሰራር ከየትኛዋም ሴት
ያነሰች አትሁኝ። ያልቻልሽውን ተማሪ፤ ጠይቂ።
ያቀረበልሽን ጨምረሽ እንጅ አጉድለሽ
አትስጭ። አጣፍጠሽ ስሪ። በዚህ ምክንያት
የሚኮራብሽ እንጅ የሚሸማቀቅብሽ አትሁኝ።

፬) ምስጢር ጠባቂ ሁኝ።
ከእሱና ከቤተሰባችሁ ጋር ያለው ጉዳይ
ገመናችሁ ስለሆነ ለማንም አትንገሪ።
ምስጢሩን ስትጠብቂ የበለጠ ትታመኛለሽ።
ጉድለት ካለበት ሁለታችሁ ጨርሱት።

፭) ሀሜተኛ አትሁኝ።
ስትገናኙ ስለራሳችሁ፣ ስለስራችሁ ካልሆነ
በስተቀር ማንንም እያነሳሽ አትሚ። ሀሜት
የሀጢአት ስር መሆኗንም አስቢ።

፮) ንጽህናሽንና ውበትሽን ጠብቂ።
የራስሽንና የቤትሽን ንጽህና እንዲሁም
ውበትሽን ጠብቂ። ወንድ ዝርክርክ ያለ ነገር
አይወድም።

፯) አባካኝ አትሁኝ።
እሱ ደክሞ አንቺ ደክመሽ የምታገኙትን
በአግባቡ ተጠቀሙ። ከመጠን በላይ ስታወጭ
ልፋቱን እንደናቅሽበት ሊያስብ ይችላል።

፰) ቅናት ካለብሽ ቀንሽ።
መውደድሽ ቅናት ሊያመጣብሽ ቢችልም ከልክ
እንዳያልፍ ተጠንቀቂ። ቅናት ጥርጣሬ
ያመጣል። ጥርጣሬ ደግሞ ጭቅጭቅና ጥል
ያስከትላል። በማንኛውም ሁኔታ ውስጥ
አብረሽው መሆንሽን ብቻ አሳይው።
እንዳመንሽው ሲያይ የበለጠ ይታመንሻል።

፱) ኃላፊነት አትፍሪ።
ቤተሰብን በመምራት፣ በማህበራዊ ግንኙነት
የሚመጣውን ኃላፊነት በመቀበልና
በመወጣትና መሰል ጉዳዮች ላይ ከእሱ ጋር
እየተናበብሽ ፈጽሚ። ጀግናው ያደርግሻል።

፲) ቤቱ ሰላሙ ነውና ሰላሙን እንዲያገኝ እርጅው።
በቤቱ ማረፍ፣ መረጋጋት፣ ሰላም ማግኘት፣
ራሱን ማዳመጥ ከቤተሰቡ ጋር ማሳለፍ
ይፈልጋል። አብዛኛው ወንድ እርጋታና
ብልሃት እንጅ ጫጫታ፣ ክርክር፣
ጭቅጭቅና ግርግር አይፈልግም።

፲፩) በወሬ አትሸበሪ።
አንቺንና እሱን ወይም ቤተሰባችሁን
የሚመለከት ወሬ ከተለያየ ቦታ ሊደርስሽ
ይችላል። ወዲያው ሰምተሽ ለብቻሽ
አትወስኝ። ወሬ ብዙ ቤት አፍርሷልና
መጀመሪያ ከእሱ ጋር ተወያዩበት።

፲፪) በሚያደርገው ጥረትና ልፋት ሁሉ ከጎኑ ሁኝ።
ድጋፍሽ በተግባር ጭምር ይሁ። ፍላጎቱን
አክብሪ፤ ገደቡን አትለፊ፤ አትፈታተኝው።

==========================

Among the precautions you should take to prevent your husband (lover) from leaving you:

1) Men don't want to be in a place where they are not respected.
This is not pride or arrogance.
It is a matter of their honor and identity. Nothing annoys them like this lack of respect.
They know that, if they are not for themselves, no one will come and protect them. So, they try to protect themselves and others.

So, avoid touching his honor
even in the midst of a joke. A man is sensitive about his honor and identity.

2) Respect his friends and relatives.
Like his one, he wants the honor of his friends and relatives to be respected. Even if you find a reason to dislike them, don't diminish their honor.

3) Be a professional.
At least, don't be less than any woman
in cooking. Ask for what you can't do.
Don't give him less than what he offered to you. Cook it sweet. Make him proud of you.

4) Be a keeper of secrets.
Since the matter with him and your family is private, don't tell anyone.
He will trust you more when you keep the secret. If there is a problem, first, both of you should discuss it.

5) Don't be a gossiper.
Discuss about yourself and your works instead of others. Remember that gossip is the root of sin.

6) Maintain your cleanliness and beauty.
Maintain the cleanliness of yourself and your home, as well as
your beauty. A man
doesn't like dirty things.

7) Don't be wasteful.
Use your things properly. If you spend too much, he may think that you are disrespecting his efforts.

8) Although your love may make you jealous, be careful not to overdo it. Jealousy brings suspicion. Suspicion also brings arguments and hostility. In any situation, just show that you are with your man. When he sees that you trust him, he will trust you more.

9) Don't be afraid of responsibility.
Be consistent with him in managing the family, accepting and fulfilling responsibilities that come with social relationships, and similar issues. The, he will make you his hero.

10) Help him find peace.
In his house, he wants to rest, be calm, find peace, and spend time with his family. Most men don't want much noise, arguments, and chaos, but calmness and intelligence.

11) Don't be terrified by rumors.
Rumors about you, him, or your families may come from different directions. Don't immediately take them for granted. They have destroyed many families.
Talk to your man him first.

12) Be by his side in all his efforts and endeavors.
Be your support in action as well.
Respect his desires; don't exceed his limits; don't challenge him excessively.

ይህ በምስሉ የምንመለከተው "ተገኘ ታደሰ" የተባለ በ1950ዎቹ በዋግ አውራጃ በጣም የታወቀና የተወደደ አዝማሪ ነበር። እርሱ ባለበት ደስታው ብቻ ሳይሆን ሀዘኑም ይደምቅ ነበር (ታላላቅና የታ...
06/25/2025

ይህ በምስሉ የምንመለከተው "ተገኘ ታደሰ" የተባለ በ1950ዎቹ በዋግ አውራጃ በጣም የታወቀና የተወደደ አዝማሪ ነበር። እርሱ ባለበት ደስታው ብቻ ሳይሆን ሀዘኑም ይደምቅ ነበር (ታላላቅና የታወቁ ሰዎች ሲሞቱና ሲታሰቡ አዝማሪዎች ያንጎራጉሩ ነበር)። ተገኘ ታደሰ የሌለባቸው መንግሥታዊ፣ ባህላዊና ሃይማኖታዊ በዓላት አይደምቁም ነበር። ተገኘ ታደሰን የህይወት ታሪክ ሪፖርተር ላይ January 29 ቀን 2023 በሰፊው ጽፌያለሁ። ፍላጎቱ ያላችሁ ሪፖርተር ገጽ "ተገኘ ታደሰ" ብላችሁ በመግባት ለማንበብ ትችላላችሁ። ሆኖም ፎቶግራፉ አልነበረኝም። ዕድሜ ለAl በ1957 ከተቀረጸ ፊልም የተወሰደ ሥዕል ከብሩክ ሙላቱ ገጽ ወስጄና ከብዙ ሰዎች መካከል አውጥቼ እንዲህ አቀረብኩት። ሥዕሉ የእርሱ መሆኑን አረጋግጣለሁ። የዋግ ኽምራ ዞን አስተዳደር ከሚዩኒኬሽንና ባህል ቢሮዎች በትልቁ አሳትማችሁ ሙዝየሙ ውስጥ እንደሚያስቀምጡት ተስፋ አደርጋለሁ።

በጋሽ .5

Address

San Diego, CA
93145

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ዋግ ኸምራ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to ዋግ ኸምራ:

Share