10/06/2025
የእገታ መረጃ ከወደ ራያ👇
የሰቆጣ የተፈራ ሃይሉ ሆስፒታል አምቡላንስ በጁንታው ታግታል። ይህም ከሰቆጣ ሪፈር የተባለ በሽተኛ አድርሶ ሲመለስ ዋጃ ላይ በጁንታው ታግታል።
የፕሪቶሪያውን ስምምነት ጥሶ በጉልበት ወደ ራያ የገባው የህወሀት ታጣቂ በአብክመ በሰሜን ወሎ ዞን ዋጃ ከተማ ከወደ ሰቆጣ የሚመጣውን የሰቆጣ አምቡላንስና ሾፌሮችን አገተ ።
ዘራፊው ቡድን ዋጃ ልዩ ስሙ ማዶ ከተማ ላይ ኬላ የሰራ ሲሆን በአከባቢው የሚያልፈውን የሰቆጣ ከተማ የመንግስት አምቡላንስን ማገታቸውን ከአከባቢ ነዋሪዎች ማረጋገጥ ችለናል ።
በነዚህ ሰዎች ላይ የከፋ ጉዳት ከመድረሱ በፊት የዋግኽምራ ዞን ሰቆጣ አስተዳደርና የአማራ በሄራዊ ክልላዊ መንግስት አስተዳደር ጣልቃ ገብቶ በአስቸኳይ ሊያስለቅቋቸው ይገባል ።