
07/12/2025
ጂኤች አልያንስ ስማርት ባዛር በፍራንቻይዝ ንግድ ሲሰተም እስከ ጥር 30 ድረስ ትርፍ እንጂ ኪሳራ የሌላቸው ሀምሳ ሚኒ ማርቶች ሥራ እንደሚጀምሩ ገለጸ
ጂኤች አልያንስ ስማርት ባዛር /GH Alliance Smart Bazaar/ ከባለድርሻ አካላት ጋር 3ኛ ዙር ውይይቱን ዛሬ ቅዳሜ ሐምሌ 5 ቀን 2017 ዓ.ም በዳዓማት ሆቴል አካሂዷል።
ጂኤች እስከ አሁን በአዲስ አበባና በክልል ከተሞች ከሁለት መቶ በላይ ሰዎች (አባላት) የመዘገበ ሲሆን እስከ ጥር 30 ቀን 2018 ዓ.ም 50 ሚኒ ማርቶች ስራ እንደሚጀምሩ በዛሬው መድረክ ገልጿል።
በመድረኩ የጂኤች አልያንስ አባላት ባቀረቧቸው ጥያቄዎች ላይ ውይይት ተካሂዷል። የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ ዳይሬክተር አቶ መከተ አዳፍሬ ፣ ከዳሸን ባንክ የማርኬቲንግ ባለሙያ አቶ አክሊሉ ፍስሐ እና የኦሮሚያ ህብረት ስራ ባንክ ተወካይ በመድረኩ ተገኝተዋል።
"Together, We Grow Faster" በሚል መሪ ቃል የተቋቋመው ጂኤች አልያንስ ስማርት ባዛር በሀገር ውስጥ ፍትሃዊ የንግድ ስርዓት እንዲሰፍን የሚያደርግ ሲሆን ለብዙዎች የስራ ዕድል የሚፈጥር ነው። ከዚህም ባሻገር የአምራቾች እና ሸማቾች ግንኙነት በቴክኖሎጂ የተደገፈ ዘመናዊ፣ ቀልጣፋ፣ ምቹና አስተማማኝ እንዲሆን የሚሰራ ተቋም መሆኑን በመድረኩ ተገልጿል። የሚከፈቱት ሚኒ ማርቶች ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ከሚያገኙት ድጋፍ በተጨማሪ በጂኤች የፍራንቻይዝ ሲስተም በርካታ ጥቅማጥቅሞችን የሚያገኙ በመሆናቸው ትርፍ እንጂ ኪሳራ እንደማያስተናግዱ በመድረኩ ላይ ተብራርቷል።