Sodere Sodere is Ethiopian film streaming service, website, application and online store. Sodere Media produces and owns the largest Ethiopian movies library.

Sodere is an Ethiopian movie producer, studio, website, application and entertainment website.

12/29/2025

የኢትዮ ግሪን ሞቢሊቲ(ግሪን ሞቢሊቲ) 2025” ሳምንት በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል እየተከናወነ ይገኛል። ኢግዚቢሽን በአፍሪካ ኮንቬንሽን ሴንተር ከታህሣስ 18 እስከ ታህሣስ 23 ቀን 2018 ዓ.ም ይደረጋል።

ግሪን ሞቢሊቲ 2025 ኢግዚቢሽን በአፍሪካ ኮንቬንሽን ተከፈተ።  አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 18፣ 2018  የኢትዮጵያ ብልጽግና የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ልማትን ታሳቢ ያደረገ እንዲሆን እየተሰራ ነው አ...
12/27/2025

ግሪን ሞቢሊቲ 2025 ኢግዚቢሽን በአፍሪካ ኮንቬንሽን ተከፈተ።

አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 18፣ 2018 የኢትዮጵያ ብልጽግና የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ልማትን ታሳቢ ያደረገ እንዲሆን እየተሰራ ነው አሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ።

በኢትዮጵያ ብክለት ቀናሽ እንቅስቃሴ 2025 ኤግዚቢሽን እና ፎረም ተጀምሯል፡፡

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በወቅቱ እንዳሉት÷ የተባበሩት መንግስታት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤን (ኮፕ2032) እንድታዘጋጅ የተመረጠችው ኢትዮጵያ ሰፋፊ የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታ ስራዎችን እያከናወነች ነው።

በኢትዮጵያ የተሟላ ለውጥ እና ብልጽግናን ለማምጣት ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ገልጸው÷ ይህ ዘላቂ ልማት እና ለውጥ አረንጓዴ ኢኮኖሚን ታሳቢ ያደረገ እንዲሆን ለማድረግ እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡

የአየር ንብረት መለዋወጥ የከተሞች መጨናነቅ እና ዝቅተኛ የኃይል አቅርቦት የልማት ፈተናዎች መሆናቸውን ጠቅሰው÷ ኢትዮጵያ ችግሮቹን በመረዳት መፍትሄ ለመስጠት ከጠረጴዛ ተኮር ወደ ተግባር ተኮር ስራ መሸጋገሯን አብራርተዋል፡፡

በነዳጅ ላይ ያለውን ጥገኝነት ለመቀነስ እንዲሁም የልማት ስራዎችን ከፀሐይ፣ ከሃይድሮ ኤሌክትሪክ እና ከነፋስ ኃይል ልማት ጋር ለማስተሳሰር እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

ስለአረንጓዴ ልማት የምንጨነቀው ለቀጣይ ትውልድ ስለምናስብ ነው ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ÷ ኢትዮጵያ ለአረንጓዴ ልማት የሰጠችው ትኩረት ከራሷ አልፎ ለዓለም የሚተርፍ መሆኑን አስገንዝበዋል፡፡

በአረንጓዴ አሻራ እና በታዳሽ ኃይል ልማት ላይ ውጤቶች የተገኙት በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና በሕዝቡ ቆራጥ ስራ መሆኑን አስረድተዋል።

መንግሥት በዘርፉ የጀመራቸውን ተግባራት አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠው፤ በኢትዮጵያ ብክለት ቀናሽ እንቅስቃሴ 2025 ኤግዚቢሽን እና ፎረም የኢትዮጵያን ብክለት ቅነሳ መርሐ ግብር ያግዛል ብለዋል።

ኢትዮጵያ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ኢኮኖሚ እየገነባች እንደሆነ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ።

የኢትዮጵያ ብክለት ቀናሽ እንቅስቃሴ (ግሪን ሞቢሊቲ) 2025 ዐውደ ርዕይና ጉባኤ በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል ተከፍቷል።

አፍሪካ ለአየር ንብረት ለውጥ ያላት አስተዋጽኦ አነስተኛ ቢሆንም ከፍተኛ ተጎጂ እንደሆነችም ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ተናግረዋል።

ተፈጥሮን መጠበቅ እና መንከባከብ የተሻለ ነገን ለትውልድ ለማሻገር ያስችላል ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ነገር ግን ተፈጥሮ ሲጎዳ የሰው ልጅ ከፍተኛና ዘርፈ ብዙ ችግርን ይጋፈጣል ብለዋል።

ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥን ለመከላከል በአረንጓዴ አሻራ ትልቅ ለውጥ ማስመዝገቧን አንስተዋል። ኢትዮጵያ ታዳሽ ኃይልን መሠረት ያደረገ ኢኮኖሚ በመገንባት እና የአየር ንብረት ለውጥን ለመከላከል የሚያስችል ተጨባጭ ሥራ በመሥራቷ ዓለም አቀፍ ዕውቅና አግኝታበታለች ተብሏል።

የአየር ንብረት ለውጥን ለመከላከል የሚያስችል ሥራ በትራንስፖርት ዘርፉ በትኩረት እየተሠራ መሆኑን ያነሱት ደግሞ የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስትሩ ዓለሙ ስሜ (ዶ/ር) ናቸው።

በዘርፉ የአየር ብክለትን ለማስቀረት በተሠራ ሥራ የባቡር አገልግሎት ታዳሽ የኃይል ምንጭ እንዲጠቀም የተደረገበት እና የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች በዘርፉ መሰማራት ትልቅ እርምጃ እንደሆነም ሚኒስትሩ አንስተዋል።

እንዲሁም አሮጌ መኪና ወደ ሀገር ውስጥ እንዳይገባ የተደረገበት አሠራር ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ብክለትን ለማስቀረት ያላትን ቁርጠኝነት ያሳያል ብለዋል።

በኢትዮጵያ እስከ አውሮፓውያኑ 2030 ድረስ ታዳሽ ኃይል የሚጠቀሙ ከ500 ሺህ በላይ ተሽከርካሪዎች አገልግሎት እንዲሰጡ እየተሠራ መሆኑም ተገልጿል። ኢትዮጵያ በአረንጓዴ ልማት ላይ የተመሠረተ ስኬታማ የብልፅግና ጉዞ ላይ ትገኛለች ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ

ኢትዮጵያ በአረንጓዴ ልማት ላይ የተመሠረተ ስኬታማ የብልፅግና ጉዞ ላይ እንደምትገኝ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ።

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሁለተኛውን ሀገራዊ “የብክለት ቀናሽ እንቅስቃሴ(ግሪን ሞቢሊቲ) 2025” ሳምንት ዛሬ በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል በይፋ ከፍተዋል።

በመክፈቻ ንግግራቸውም የኢትዮጵያ የብልፅግና ጉዞ ዋነኛ መሠረቱ አረንጓዴ ልማት መሆኑን አጽንኦት ሰጥተው ገልጸዋል።

ኢትዮጵያ በአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር ያስመዘገበችውን ድል በአረንጓዴ ትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ዘርፍ ለመድገም እየሰራች መሆኑን አስታውቀዋል።

በዚህም ለበካይ ጋዝ የካርቦን ልቀት ቅነሳ እና ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር የኢኮኖሚ ሥርዓት ለመገንባት በቁርጠኝነት እየተሠራ መሆኑን ተናግረዋል።

የሰው ልጅ ከተፈጥሮ ጋር የነበረውን ቅራኔ መፍታት የሚችለው ብክለትን በሚቀንሱ ቴክኖሎጂዎች ጉዞውን ሲመራ ብቻ መሆኑን አስረድተዋል።
ዓለም አቀፍ የአየር ንብረት ውይይቶች ከንግግር ባለፈ ወደ ተግባር መሸጋገር እንዳለባቸውም ነው ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ የተናገሩት።

ኢትዮጵያ ውጤትና ተግባር ተኮር የመፍትሔ አካሄድን እየተከተለች መሆኗን በማንሳት፤ ብክለት ቀናሽ የአረንጓዴ እንቅስቃሴና የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች መስፋፋት የዚሁ ተግባራዊ ምላሽ ዋነኛው ማሳያ መሆኑን ገልጸዋል።

በአረንጓዴ ዐሻራ፣ ወንዞችን ከብክለት በማፅዳት፣ የፌስታል ምርቶችን አጠቃቀም በመገደብና በታዳሽ ኃይል የሚንቀሳቀሱ ተሽከርካሪዎችን በማስፋፋት ረገድ ትልቅ ሥራ መከናወኑን ጠቅሰዋል።

ታዳሽ ኃይል የሚጠቀሙ ተሽከርካሪዎችን ከንጹሕ የኢነርጂ መሠረተ ልማት በተለይ ከሃይድሮ ኤሌክትሪክ፣ ከፀሐይና ከነፋስ ኃይል ጋር ማቀናጀት፣ የካርቦን መጠንንና የኃይል ወጪዎችን ለመቀነስ ወሳኝ መሆኑንም ጠቁመዋል።
በዘላቂ ትራንስፖርት ላይ ያተኮሩ ውጥኖች የካርቦን ልቀትን ለመግታት ብቻ ሳይሆን፣ ኢትዮጵያን በአፍሪካ በአረንጓዴ ኢንዱስትሪያላዊነት አፈጻጸም ግንባር ቀደም እንደሚያደርጋት አንስተዋል።

አውደ ርዕዩ የኢትዮጵያን ብክለት ቀናሽ አብዮት የሚያበረታቱ ቴክኖሎጂዎች ማሳያ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡

በተጨማሪም ፖሊሲ አውጪዎች፣ ባለሀብቶችና ዜጎች በጋራ እየተገነባ ስላለው ዘላቂና ዘመናዊ የትራንስፖርት አገልግሎት ግንዛቤና ልምድ እንዲኖራቸው ያስችላል ብለዋል።

የኢትዮጵያ የብልፅግና ጉዞ በአረንጓዴ ልማት ላይ የተመሠረተ እንዲሆን መንግሥት አበክሮ እየሠራ መሆኑን በማንሳት፤ ለስኬቱ ሁሉም የኅብረተሰብ ክፍል ተግባራዊ ምላሽ እንዲሰጥ ጥሪ አቅርበዋል።
መንግሥት ለዚህ ዓላማ ስኬታማነት ሁሌም የመሪነት ሚናውን አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል።

ኢትዮፒካር (ETIOPIKAR) የአፍሪካ የአመራርና የተቋማት ሽልማትን ማሸነፉን ተከትሎ ልዩ የበዓል ቅናሽ ይፋ አደረገ።  ተሽከርካሪዎች አስመጪነትና በኤክስፖርት ዘርፍ የተሰማራው ኢትዮፒካር፣...
12/26/2025

ኢትዮፒካር (ETIOPIKAR) የአፍሪካ የአመራርና የተቋማት ሽልማትን ማሸነፉን ተከትሎ ልዩ የበዓል ቅናሽ ይፋ አደረገ።

ተሽከርካሪዎች አስመጪነትና በኤክስፖርት ዘርፍ የተሰማራው ኢትዮፒካር፣ በ20ኛው "ግራንድ አፍሪካ የአመራርና የተቋማት ሽልማት" ላይ በምርጥ ተቋማዊ አፈፃፀም ሽልማት ተሸላሚ ሆኗል።

ኩባንያው ይህንን ስኬት በማስመልከትም ለደንበኞቹ እስከ ጥምቀት በዓል የሚቆይ ልዩ የዋጋ ቅናሽ እና የብድር አመቻች መርሃ-ግብር ይፋ አድርጓል።

ባለፈው ሳምንት በአድዋ መታሰቢያ ሙዚየም "ትጉኃንን እንሸልማለን" በሚል መሪ ቃል በተካሄደው የሽልማት ስነ-ስርዓት ላይ፣ ተቋሙ በሦስት የተለያዩ ዘርፎች እውቅናን አግኝቷል።

በዚሁ መሰረት የድርጅቱ መስራችና ባለቤት አቶ ሳሙኤል አዲስአለም በከፍተኛ አመራር ዘርፍ ሲሸለሙ፣ አቶ ኤፍሬም ታደለና አቶ ሴና ጌትነት በመካከለኛ አመራር ዘርፍ የላቀ አፈፃፀም ላሳዩ መሪዎች የሚሰጠውን ሽልማት ተቀብለዋል።

ኩባንያው የተገኘውን እውቅና ለደንበኞቹ ለማካፈል ባዘጋጀው መርሃ-ግብር፤ ከገና እስከ ጥምቀት በዓል ድረስ በኤሌክትሪክ መኪኖች ሽያጭ ላይ ከፍተኛ ቅናሽ ማድረጉን ገልጿል።

በተለይም መኪና መግዛት ለሚፈልጉ ግለሰቦች እና ድርጅቶች 50 በመቶ የቅድመ ክፍያ በመክፈል፣ ቀሪውን 50 በመቶ ከተለያዩ ባንኮች እና የፋይናንስ ተቋማት ጋር በመተባበር በሚመቻች ብድር መውሰድ የሚችሉበትን አሰራር መዘርጋቱን አስታውቋል።

በፈረንጆቹ 2013 ዓ.ም. የቀድሞ የባንክ ባለሙያ በሆኑት በአቶ ሳሙኤል አዲስአለም የተመሰረተው "ሳሙኤል አዲስአለም አስመጪ እና ላኪ"፤ በአሁኑ ወቅት በዩናይትድ አረብ ኤምሬትስ እና በአዲስ አበባ ቅርንጫፎቹን በመክፈት በስፋት እየተንቀሳቀሰ ይገኛል።

ተቋሙ በኢትዮፒካር (ETIOPIKAR) መለያ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን ወደ ሀገር ውስጥ ከማስገባት ባለፈ፣ በቡና፣ በቅባት እህሎች እና በፍየል ስጋ ኤክስፖርት ዘርፍ በመሰማራት ለሀገር የውጭ ምንዛሬ ግኝት የድርሻውን እየተወጣ እንደሚገኝ ተገልጿል።

ይህ ልዩ የሽያጭ እና የብድር ዕድል ደንበኞች ዘመናዊ እና ለአካባቢ ጥበቃ ተስማሚ የሆኑ የኤሌክትሪክ መኪኖችን በቀላሉ እንዲያገኙ ዓላማ ያደረገ መሆኑን ኩባንያው አክሎ ገልጿል።

#ሶደሬ አዲስ

አካፑልኮ ቤይ ተከታታይ ድራማ ላይ ማክስ ሆኖ ከሚተውነው አሽ አዳምስ ጋር ቆይታ አድርገናል
12/21/2025

አካፑልኮ ቤይ ተከታታይ ድራማ ላይ ማክስ ሆኖ ከሚተውነው አሽ አዳምስ ጋር ቆይታ አድርገናል

Interview with Ash Adams Acapulco bay series drama actor Max Houser

የደራሽነት ጥሪ፡ ለአርቲስት ወንደሰን ልጅ እና ቤተሰብ! 🇪🇹ሁላችንም እንደሰማነውና በሚዲያ እንደተከታተልነው፣ ተወዳጁ አርቲስት ወንደሰን በሞት መለየቱ ቤተሰቡን ለከባድ ሃዘንና ፈተና ዳርጓል...
12/21/2025

የደራሽነት ጥሪ፡

ለአርቲስት ወንደሰን ልጅ እና ቤተሰብ! 🇪🇹

ሁላችንም እንደሰማነውና በሚዲያ እንደተከታተልነው፣ ተወዳጁ አርቲስት ወንደሰን በሞት መለየቱ ቤተሰቡን ለከባድ ሃዘንና ፈተና ዳርጓል።

በተለይም በቅርቡ በሚዲያ ቀርባ ያየናት ልጁ የደረሰባት የስነ-ልቦና ስብራት (Trauma) ሁላችንንም “ዝም አንልም” የሚያሰኝ ነው።

የአርቲስት ልጅ የሁላችንም ልጅ ናት! የዚችን ህጻን እንባ ለማበስ እና የወደፊት ህይወቷን ለመታደግ፣ በባለቤቱ ሙሉ ፍቃድ እና በአርቲስት ዳንኤል አማካኝነት ይህ የGoFundMe የገቢ ማሰባሰቢያ ተከፍቷል።

ከታች ያለውን ሊንክ በመጫን አቅም የፈቀደውን በመለገስ።

* በማጋራት (Share)፦
ይህ መረጃ ለብዙዎች እንዲደርስ ፖስቱን ለወዳጅ ዘመድዎ ሼር በማድረግ።

የGoFundMe ሊንኩ👇👇👇

https://gofund.me/6a6d81ba1

ዛሬ የምናደርገው ትንሽ ድጋፍ ለዚች ህጻን ትልቅ ተስፋ እና መጽናኛ ይሆናል። ሰብአዊነታችንን የምናሳይበት ወቅት አሁን ነው።

ፈጣሪ መልካም ስራችሁን ይባርክ።
የሟቹን ነፍስ በአጸደ ገነት ያኑርልን።

🙏🙏🙏

12/17/2025
"ይህቺ ምድር የፈተና ዓለም ናት" ኡስታዝ አቡበከር አህመድ | USTAZ ABUBAKER AHMED
12/15/2025

"ይህቺ ምድር የፈተና ዓለም ናት" ኡስታዝ አቡበከር አህመድ | USTAZ ABUBAKER AHMED

"ይህቺ ምድር የፈተና ዓለም ናት" ኡስታዝ አቡበከር አህመድ | USTAZ ABUBAKER AHMED Subscribe to our channel Amharic Tube and enjoy Ethiopian daily news, Ethiopian movies, Ethiop...

ልክ እንዳየሁሽ ሙሉ ፊልም
12/15/2025

ልክ እንዳየሁሽ ሙሉ ፊልም

ልክ እንዳየሁሽ ሙሉ ፊልም Lik Endayehush full Ethiopian movie 2023

የኮሜዲያን ወንድወሰን አውራሪስ ቤተሰብ ድጋፍ ይሻሉ፡ ባለቤቱና ልጃቸው አስቸጋሪ ሁኔታ ላይ ናቸውአዲስ አበባ — የቅርብ ጊዜ አሟሟቱ የኢትዮጵያን አርቲስት ማህበረሰብ ያሳዘነው ተወዳጁ ኮሜዲያ...
12/15/2025

የኮሜዲያን ወንድወሰን አውራሪስ ቤተሰብ ድጋፍ ይሻሉ፡ ባለቤቱና ልጃቸው አስቸጋሪ ሁኔታ ላይ ናቸው

አዲስ አበባ — የቅርብ ጊዜ አሟሟቱ የኢትዮጵያን አርቲስት ማህበረሰብ ያሳዘነው ተወዳጁ ኮሜዲያን ወንድወሰን አውራሪስ ባለቤት ወ/ሮ በቴልሄም ህሉፍ እና ልጃቸው፣ ከሟቹ ሞት በኋላ አስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ እንደሚገኙ የገለፁበት ቃለ-ምልልስ በሰይፉ ሾው ላይ ቀርቧል።

ወ/ሮ በቴልሄም በሰጡት ቃለ-ምልልስ መሰረት፣ ኮሜዲያኑ ከተቀበረ ማግስት ከባልደረባዋ ቤተሰቦች ጋር በተፈጠረ አለመግባባት ምክንያት የመኖሪያ ቦታቸውን ለመልቀቅ መገደዳቸውን ተናግረዋል።

* ስልክ እና ንብረት:
ሟቹ ኮሜዲያን ወንድወሰን ይጠቀምበት የነበረው ስልክ የቀብር ዕለት እንደተወሰደባቸውና፣ ለልጃቸውም ምንም አይነት ንብረት ትቶ ያለፈው ነገር እንደሌለ ገልጸዋል።

* የአሁኑ ሁኔታ:
እናትና ልጃቸው ለአሁኑ የሟቹ ጓደኞች ባዘጋጁላቸው ጊዜያዊ መጠለያ ውስጥ እንደሚገኙ ተገልጿል።

ወ/ሮ በቴልሄም፣ በዚህ አሳዛኝ ወቅት ከደረሰባቸው መፈናቀል ጋር ተያይዞ ልጃቸው ከፍተኛ የስሜት መረበሽ ውስጥ መሆኗን ገልጸዋል፤ ይህም በልጅቱ ላይ ከአባቷ ሞት ባልተናነሰ የስነ-ልቦና ጉዳት እንደጣለባት አስረድተዋል። የደረሰባቸው ሁኔታ ኢትዮጵያዊ ባህልን የሚፈታተን እንደሆነ ተመልክቷል።

እናትና ልጃቸው ይህን አስቸጋሪ ጊዜ እንዲያልፉ ለመርዳት የኢትዮጵያ ሕዝብ ዘርጋፊ እጅ እንዲያደርግላቸው ጥሪ ቀርቧል። ሰብዓዊነትን መሠረት ባደረገ መልኩ ድጋፍ ለማድረግ የሚሹ አካላት ከታች በተዘረዘሩት መረጃዎች መጠቀም ይችላሉ።

#ሸር በማድረግ ይህ የዕርዳታ ጥሪ ለብዙ ደጋግ ኢትዮጵያውያን እንዲደርስ ያግዙ።

የእርዳታ ማሰባሰቢያ መረጃ:

Betelhem Hiluf የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ (CBE) 1000024737385

ስልክ 0910219309

Via Seifu on EBS

Address

312 Arizona Avenue
Santa Monica, CA
90401

Telephone

+13105709291

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Sodere posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Our Story

Sodere is an Ethiopian news and entertainment website. Sodere Media streams Ethiopian movies legally through SodereOnDemand website. Sodere has started as a blog on October 2010 and became a news and entertainment site in January 2011. As of Dec 4, 2016, sodere.com has close to 42,000 highly engaged email subscribers. There were more than 10.1 million visitors in 2015. Half of our members has invited more than 20 of their friends to read news and become a member of Sodere. 40% of our users visit the website twice daily. Sodere has it's own social features integrated in the website. Every member can submit articles, blogs and videos. Members also can post activity, communicate and send messages to each other. Membership, blog posts, article and videos submission are all moderated and approved by moderators. As of April 2013 Sodere team has launched SodereTube.com exclusively for videos and had 1.6 million visitors in 2013.