Sodere Sodere is Ethiopian film streaming service, website, application and online store. Sodere Media produces and owns the largest Ethiopian movies library.

Sodere is an Ethiopian movie producer, studio, website, application and entertainment website.

ፒኤስጂ የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ዋንጫን በድጋሚ አሸነፈ
05/30/2026

ፒኤስጂ የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ዋንጫን በድጋሚ አሸነፈ

"የፍቅር ግርማ" ምሽት!አንጋፋ የኪነጥበብ ምሽት!እባክዎ ሸር በማድረግ ተባበሩን!57ኛው የባህል ማዕከል የኪነጥበብ ምሽት ረቡዕ ግንቦት 26፥2018 ዓ.ም ይካሄዳል።በዕለቱም  ተወዳጇ ድምጻዊ...
05/30/2026

"የፍቅር ግርማ" ምሽት!

አንጋፋ የኪነጥበብ ምሽት!

እባክዎ ሸር በማድረግ ተባበሩን!

57ኛው የባህል ማዕከል የኪነጥበብ ምሽት ረቡዕ ግንቦት 26፥2018 ዓ.ም ይካሄዳል።
በዕለቱም ተወዳጇ ድምጻዊ ፀደንያ ገብረማርቆስ የክብር እንግዳችን ሆና በመካከላችን በመገኘት ሙያዊ ልምዷን ታካፍለናለች።

እንዲሁም ግጥሞች ፣ ወግ ፣ ሙዚቃና ሞኖሎግ ለእናንተ ውድ ታዳሚዎቻችንን በባህል ማዕከል አዳራሽ ከቀኑ በ 11: 30 ጀምሮ ተሰናድቶ ይጠብቃችኃል።

#ማስታወሻ :— ፕሮግራሙ ላይ ለመታደም የምትፈልጉ በአሁን ሰዓት የዩኒቨርስቲው ተማሪ ያልሆናችሁ የስነ-ጽሑፍ አፍቃሪያን መግቢያው በ5ተኛ በር በኩል ነው።

አርቲስት ሰላማዊት ደስታ ከዚህ ዓለም ድካም አረፈችአርቲስት ሰላማዊት ደስታ ባደረባት ህመም ምክንያት በህክምና ስትረዳ ቆይታ ግንቦት 21/2018 ዓ.ም ከዚህ ዓለም ድካም አርፋለች።የአርቲስት...
05/30/2026

አርቲስት ሰላማዊት ደስታ ከዚህ ዓለም ድካም አረፈች

አርቲስት ሰላማዊት ደስታ ባደረባት ህመም ምክንያት በህክምና ስትረዳ ቆይታ ግንቦት 21/2018 ዓ.ም ከዚህ ዓለም ድካም አርፋለች።

የአርቲስት ሰላማዊት ደስታ የሽኝት ፕሮግራም በሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ዛሬ ግንቦት 22/2018 ዓ.ም ከረፋዱ 4:00 ሰዓት ቤተሰቦቿ፣ ዘመዶቿ፣ ጓደኞቿና የሙያ አጋሮቿ በተገኙበት የሚከናወን ሲሆን የቀብር ስነስርአቱ ከቀኑ 7:00 ሰዓት በማህደረ ስብሃት ቅድስት ልደታ ለማርያም እና ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን ይፈፀማል።

Sodere Media ለቤተሰቦቿ፣ ዘመድ ወዳጆቿ፣ ጓደኞቿና የስራ ባልደረቦቿ ፈጣሪ ልባዊ መፅናናትን እንዲሰጥ ይመኛል።

እንኳን ለ1447ኛው የዒድ አል አድሐ (አረፋ) በዓል  በሰላም አደረሳችሁ! ☪መልካም በዓል ☪ Sodere Media
05/27/2026

እንኳን ለ1447ኛው የዒድ አል አድሐ (አረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ! ☪

መልካም በዓል ☪

Sodere Media

👉 ዛሬ የኢትዮጵያ አባቶች ቀን ነውኢትዮጵያዊ ታሪክና መልክ ይዞ በየአመቱ ግንቦት 15 የሚከበረው የኢትዮጵያ አባቶች ቀን የዘንድሮው ዛሬ ይከበራል፤ የአፍሪካ አባቶች ቀንንም በአዲስ አበባ ለ...
05/23/2026

👉 ዛሬ የኢትዮጵያ አባቶች ቀን ነው

ኢትዮጵያዊ ታሪክና መልክ ይዞ በየአመቱ ግንቦት 15 የሚከበረው የኢትዮጵያ አባቶች ቀን የዘንድሮው ዛሬ ይከበራል፤

የአፍሪካ አባቶች ቀንንም በአዲስ አበባ ለማክበር ዝግጅት እየተደረገ ነው።

ኢትዮጵያዊው የአባቶች ቀን

ሌላው አለም በደፈናው የአባቶች ቀን ብሎ ዕለት መርጦ የሚያከብረውን የአባቶች ቀን ክብረ በዓል ኢትዮጵያዊ መልክ በመስጠት በየአመቱ ግንቦት 15 በመላ ኢትዮጵያ እንዲከበር እያደረገ የሚገኘው የኢትዮጵያ አባቶች ቀን በጎ አድራጎት ድርጅት ዘንድሮም ለ18'ኛ ጊዜ ይሄንኑ ዕለት ዛሬ ግንቦት 15 ቀን 2018 ዓ.ም ተከብሮ እንደሚውል አስታውቋል።

ታሪካዊው ግንቦት 15

ይህ ግንቦት 15 የተመረጠበት ዋነኛ ምክንያት የአፍሪካ ኩራት ከሆነው ከአድዋ ድል ታሪክ ጋር የተገናኘ ሲሆን በአድዋ ጦርነት የተሳተፉ ጀግኖች አባቶቻችን ድል አድርገው ወደ መናገሻ ከተማ አዲስ አበባ የተመለሱበት ዕለት መሆኑን መነሻ በማድረግም ነው።

እስካሁን እነማን ተመሰገኑ?

የዚህ ሀሳብ አመንጪና ባለቤት የሆነው የኢትዮጵያ አባቶች ቀን በጎ አድራጎት ድርጅት መስራችና ዋና ስራ አስኪያጅ እዮብ አርጋው፤ ባለፉት 17 አመታት የቀድሞው የኢፌዲሪ ፕሬዝደንት ግርማ ወልደ ጊዮርጊስ፣ ጄኔራል ጃገማ ኬሎ፣ ፕሮፌሰር አብይ ፎርድ እና የጋሞ የሃገር ሽማግሌዎችን ከመሳሰሉ ታላላቅ አባቶች የግለሰቦችን ቤትና የድርጅቶችን ቅፅር በጥበቃ ሰራተኝነት እያገለገሉ የሚገኙና በአነስተኛ ገቢ የቤተሰባቸውን ጉሮሮ ለመድፈን እስከሚተጉ አባቶች ድረስ እግራቸውን በማጠብ፣ ጋቢ በማልበስና ጉልበታቸው በመሳም የማመስገንና ዕውቅና የመስጠት ተግባር መከናወኑን ገልጿል።

የአፍሪካ አባቶች ቀን

ዘንድሮ ይህን የኢትዮጵያ አባቶች ቀን በአፍሪካ ደረጃ ለማክበር ዝግጅት እየተከናወነ መሆኑንና ከአፍሪካ ህብረት ጋር በመተባበር ከ54'ቱም የአፍሪካ ሀገራት የሚጋበዙ አባቶችን በአዲስ አበባ በማሰባሰብ በልዩ ሁኔታ እንደሚከበር አቶ እዮብ አርጋው አስታውቋል።

1 ኪሎ ሜትር ጋቢ

ከዚህም በተጨማሪ በአፍሪካ ድንቃ ድንቅ መዝገብ ላይ መመዝገብ የሚችል 1ኪሎ ሜትር የሚረዝም ጋቢ ሽመና እንደሚከናወን እና ለዚህም የሚረዳ ዝግጅት እየተከናወነ መሆኑን ያነሱት አቶ እዮብ ማንኛውም ኢትዮጵያዊ በሽመናው መሳተፍ እንደሚችልም ጠቁመዋል።

ጥሪ ለልጆች

ሁሉም ኢትዮጵያዊ ልጆች ዛሬ ግንቦት 15 የኢትዮጵያ አባቶች ቀን መሆኑን አውቀው ባመቻቸው ሁኔታ ለአባቶቻቸው ምስጋና በማቅረብ እና ተገቢውን ክብር በመስጠት እንዲያከብሩ ጥሪ አቅርቧል።

እንኳን ደስ አላችሁ!!!በዛሬዉ  ዕለት ጥራታቸዉን እና ደረጃቸዉን የጠበቁ  ባለ 40  fit  11  ኮንቴነር የፊኒሽንግ  እቃወችን  ገቢ  ያደረግን ሲሆን    እነዚህ  እቃወች  ከ1 ዓመት...
05/21/2026

እንኳን ደስ አላችሁ!!!

በዛሬዉ ዕለት ጥራታቸዉን እና ደረጃቸዉን የጠበቁ ባለ 40 fit 11 ኮንቴነር የፊኒሽንግ እቃወችን ገቢ ያደረግን ሲሆን እነዚህ እቃወች ከ1 ዓመት በፊት የታዘዙ ናቸዉ፡፡
 Win loader (4)
 Concrete mixing plant
 Tower crain
 Concrete line pump (1unit)
 Construction lift (2)
 Concrete boom pump
 Concrete truck mixer (5)
 Generator (2 set)
 Excavator እንዲሁም ለሁሉም ማሽኖች የሚያስፈልጉ spare parts (የመለዋወጫ እቃወችን ) ቻይና ዉስጥ ከሚገኘዉ ከ XMG Construction machinery አምራች ድርጅት በቀጥታ የተገዙ ሲሆን እነዚህ ማሽኖች ህንፃዉን ለመገንባት ፣ ግብዓቶችን ለማምረት እንዲሁም ለማጣራት የሚያገለግሉ Full Set Concrete ማሽኖች ናቸዉ፡፡
በአጠቃላይ ከ XMG ማሽነሪ ድርጅት ባለ 40 fit 24 ኮንቴነር የፊኒሽንግ እቃወችን ግዥ ፈፅመናል፡፡

የ XMG Staff ሰራተኞች ፣ መካኒኮች ፣ ጥሪያችንን አክብራችሁ የተገኛችሁ የሚዲያ አካላት እንዲሁም መላዉ የኢትዮጵያ ህዝብ ስላደረጋችሁልን ፣ ወደ ፊትም ስለምታደርጉልን ድጋፍ በተገልጋዮቻችን ስም ከልብ እናመሰግናለን!!
ሰዉን ለመርዳት ሰዉ መሆን በቂ ነዉ!!
መቄዶንያ

#ሶደሬአዲስ

Arsenal 2025/26 champions
05/19/2026

Arsenal 2025/26 champions

"ትዝታ" ምሽት!አንጋፋ የኪነጥበብ ምሽት!እባክዎ ሸር በማድረግ ተባበሩን!56ኛው የባህል ማዕከል የኪነጥበብ ምሽት ረቡዕ ግንቦት 12፥2018 ዓ.ም ይካሄዳል።በዕለቱም  ተወዳጁ ተዋናይ እንግዳ...
05/17/2026

"ትዝታ" ምሽት!

አንጋፋ የኪነጥበብ ምሽት!

እባክዎ ሸር በማድረግ ተባበሩን!

56ኛው የባህል ማዕከል የኪነጥበብ ምሽት ረቡዕ ግንቦት 12፥2018 ዓ.ም ይካሄዳል።
በዕለቱም ተወዳጁ ተዋናይ እንግዳሰው ሀብቴ የክብር እንግዳችን ሆኖ በመካከላችን በመገኘት ሙያዊ ልምዱን ያካፍለናል።

እንዲሁም ግጥሞች ፣ ወግ ፣ ሙዚቃና ሞኖሎግ ለእናንተ ውድ ታዳሚዎቻችንን በባህል ማዕከል አዳራሽ ከቀኑ በ 11: 30 ጀምሮ ተሰናድቶ ይጠብቃችኃል።

#ማስታወሻ :— ፕሮግራሙ ላይ ለመታደም የምትፈልጉ በአሁን ሰዓት የዩኒቨርስቲው ተማሪ ያልሆናችሁ የስነ-ጽሑፍ አፍቃሪያን መግቢያው በ5ተኛ በር በኩል ነው።

"የኔ ዜማ" ምሽት!አንጋፋ የኪነጥበብ ምሽት!እባክዎ ሸር በማድረግ ተባበሩን!55ኛው የባህል ማዕከል የኪነጥበብ ምሽት ረቡዕ ግንቦት 05፥2018 ዓ.ም ይካሄዳል።በዕለቱም አንዱ ኮከብ፤ ተወዳጁ...
05/09/2026

"የኔ ዜማ" ምሽት!

አንጋፋ የኪነጥበብ ምሽት!

እባክዎ ሸር በማድረግ ተባበሩን!

55ኛው የባህል ማዕከል የኪነጥበብ ምሽት ረቡዕ ግንቦት 05፥2018 ዓ.ም ይካሄዳል።
በዕለቱም አንዱ ኮከብ፤ ተወዳጁ ድምጻዊ ዳዊት ፅጌ የክብር እንግዳችን ሆኖ በመካከላችን በመገኘት ሙያዊ ልምዱን ያካፍለናል።

እንዲሁም ግጥሞች ፣ ወግ ፣ ሙዚቃና ሞኖሎግ ለእናንተ ውድ ታዳሚዎቻችንን በባህል ማዕከል አዳራሽ ከቀኑ በ 11: 30 ጀምሮ ተሰናድቶ ይጠብቃችኃል።

#ማስታወሻ :— ፕሮግራሙ ላይ ለመታደም የምትፈልጉ በአሁን ሰዓት የዩኒቨርስቲው ተማሪ ያልሆናችሁ የስነ-ጽሑፍ አፍቃሪያን መግቢያው በ5ተኛ በር በኩል ነው።

Address

312 Arizona Avenue
Santa Monica, CA
90401

Telephone

+13105709291

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Sodere posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share