Sodere Sodere is Ethiopian film streaming service, website, application and online store. Sodere Media produces and owns the largest Ethiopian movies library.

Sodere is an Ethiopian movie producer, studio, website, application and entertainment website.

ጂኤች አልያንስ ስማርት ባዛር በፍራንቻይዝ ንግድ ሲሰተም እስከ ጥር 30 ድረስ ትርፍ እንጂ ኪሳራ የሌላቸው ሀምሳ ሚኒ ማርቶች ሥራ እንደሚጀምሩ ገለጸጂኤች አልያንስ ስማርት ባዛር /GH All...
07/12/2025

ጂኤች አልያንስ ስማርት ባዛር በፍራንቻይዝ ንግድ ሲሰተም እስከ ጥር 30 ድረስ ትርፍ እንጂ ኪሳራ የሌላቸው ሀምሳ ሚኒ ማርቶች ሥራ እንደሚጀምሩ ገለጸ

ጂኤች አልያንስ ስማርት ባዛር /GH Alliance Smart Bazaar/ ከባለድርሻ አካላት ጋር 3ኛ ዙር ውይይቱን ዛሬ ቅዳሜ ሐምሌ 5 ቀን 2017 ዓ.ም በዳዓማት ሆቴል አካሂዷል።

ጂኤች እስከ አሁን በአዲስ አበባና በክልል ከተሞች ከሁለት መቶ በላይ ሰዎች (አባላት) የመዘገበ ሲሆን እስከ ጥር 30 ቀን 2018 ዓ.ም 50 ሚኒ ማርቶች ስራ እንደሚጀምሩ በዛሬው መድረክ ገልጿል።

በመድረኩ የጂኤች አልያንስ አባላት ባቀረቧቸው ጥያቄዎች ላይ ውይይት ተካሂዷል። የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ ዳይሬክተር አቶ መከተ አዳፍሬ ፣ ከዳሸን ባንክ የማርኬቲንግ ባለሙያ አቶ አክሊሉ ፍስሐ እና የኦሮሚያ ህብረት ስራ ባንክ ተወካይ በመድረኩ ተገኝተዋል።

"Together, We Grow Faster" በሚል መሪ ቃል የተቋቋመው ጂኤች አልያንስ ስማርት ባዛር በሀገር ውስጥ ፍትሃዊ የንግድ ስርዓት እንዲሰፍን የሚያደርግ ሲሆን ለብዙዎች የስራ ዕድል የሚፈጥር ነው። ከዚህም ባሻገር የአምራቾች እና ሸማቾች ግንኙነት በቴክኖሎጂ የተደገፈ ዘመናዊ፣ ቀልጣፋ፣ ምቹና አስተማማኝ እንዲሆን የሚሰራ ተቋም መሆኑን በመድረኩ ተገልጿል። የሚከፈቱት ሚኒ ማርቶች ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ከሚያገኙት ድጋፍ በተጨማሪ በጂኤች የፍራንቻይዝ ሲስተም በርካታ ጥቅማጥቅሞችን የሚያገኙ በመሆናቸው ትርፍ እንጂ ኪሳራ እንደማያስተናግዱ በመድረኩ ላይ ተብራርቷል።

ትምህርት ቤቶች የፋይናንስ አሰራራቸውን እንዲያዘምኑ የሚያስችል "እናት መላ" የተሰኘ ስርዓት መዘርጋቱን እናት ባንክ አስታውቋል።* "እናት መላ" ለወላጆችም ቀላል ዘዴን ይዟል ብሏል።እናት ባ...
07/09/2025

ትምህርት ቤቶች የፋይናንስ አሰራራቸውን እንዲያዘምኑ የሚያስችል "እናት መላ" የተሰኘ ስርዓት መዘርጋቱን እናት ባንክ አስታውቋል።

* "እናት መላ" ለወላጆችም ቀላል ዘዴን ይዟል ብሏል።

እናት ባንክ ትምህርት ቤቶች ዘርፈ ብዙ አገልግሎቶችን የሚያገኙበትን "እናት መላ" የትምህርት ቤት ክፍያ ሥርዓትን (UNICASH) በተመለከተ ከተለያዩ ትምህርት ቤቶች ለተውጣጡ የሥራ ሃላፊዎችና ተወካዮች የግንዛቤ ማስጨበጫ ሰጥቷል።

"እናት መላ" የትምህርት ቤት ክፍያ ሥርዓት ተማሪዎችን ለመመዝገብ፣ የጉዞ፣ የመጽሐፍ ግዢና የትምህርት ክፍያን በቀላሉ ለመፈጸም ያስችላል፡፡ በተጨማሪም የተማሪዎችን መረጃ ለማስተዳደር፣ የፋይናንስ ሪፖርት ለማዘጋጀት እና ከተማሪ ወላጆች ጋር ያለውን ግንኙነትን ለማሳለጥ ፋይዳው የጎላ ነው።

የእናት ባንክ ኦፕሬሽን ዘርፍ ም/ፕሬዝዳንት ወ/ሮ ትዕግስት አባተ የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን የባንኩ የዲጂታል ባንኪንግ ዳይሬክተር አቶ እስጢፋኖስ ስሜ በበኩላቸው እናት መላ የተሰኘ የትምህርት ቤት ክፍያና የተማሪ የመረጃ አስተዳደር ሥርዓት ባለፉት ሶስት አመታት ለትምህርት ቤቶች በማቅረብ አበረታች ውጤት መገኘቱን ተናግረዋል ።ይህም ትምህርት ቤቶች አሰራራቸውን እንዲያዘምኑ ማስቻሉን አስረድተዋል።

እናት ባንክ የ"እናት መላ" የትምህርት ቤት ክፍያ ሥርዓትን በስፋት ተደራሽ ለማድረግ ከትምህርት ቤቶች ጋር ያለውን ትብብር አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታወቀ።* ለትምህርት ቤቶች አመራርና ሰራተ...
07/07/2025

እናት ባንክ የ"እናት መላ" የትምህርት ቤት ክፍያ ሥርዓትን በስፋት ተደራሽ ለማድረግ ከትምህርት ቤቶች ጋር ያለውን ትብብር አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታወቀ።

* ለትምህርት ቤቶች አመራርና ሰራተኞች ለቤትና ለመኪና መግዣ
የሚውል አዲስ የብድር አገልግሎት መጀመሩን ይፋ አድርጓል።

እናት ባንክ ትምህርት ቤቶች ዘርፈ ብዙ አገልግሎቶችን የሚያገኙበትን "እናት መላ" የትምህርት ቤት ክፍያ ሥራዓትን (UNICASH) በተመለከተ ከተለያዩ ትምህርት ቤቶች ለተውጣጡ የሥራ ሃላፊዎችና ተወካዮች የግንዛቤ ማስጨበጫ ሰጥቷል።

"እናት መላ" የትምህርት ቤት ክፍያ ሥርዓት ተማሪዎችን ለመመዝገብ፣ የጉዞ፣ የመጽሐፍ ግዢና የትምህርት ክፍያን በቀላሉ ለመፈጸም ያስችላል፡፡ በተጨማሪም የተማሪዎችን መረጃ ለማስተዳደር፣ የፋይናንስ ሪፖርት ለማዘጋጀት እና ከተማሪ ወላጆች ጋር ያለውን ግንኙነትን ለማሳለጥ ፋይዳው የጎላ ነው።

የእናት ባንክ ኦፕሬሽን ዘርፍ ም/ፕሬዝዳንት ወ/ሮ ትዕግስት አባተ የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን የባንኩ የዲጂታል ባንኪንግ ዳይሬክተር አቶ እስጢፋኖስ ስሜ በበኩላቸው እናት መላ የተሰኘ የትምህርት ቤት ክፍያና የተማሪ የመረጃ አስተዳደር ሥርዓት ባለፉት ሶስት አመታት ለትምህርት ቤቶች በማቅረብ አበረታች ውጤት መገኘቱን ተናግረዋል ።ይህም ትምህርት ቤቶች አሰራራቸውን እንዲያዘምኑ ማስቻሉን አስረድተዋል።
በሌላ በኩል

እናት ባንክ ለትምህርት ቤቶች አመራርና ሰራተኞች ለቤትና ለመኪና መግዣ የብድር አገልግሎት እንደሚያመቻች ገልጿል።
እናት ባንክ ለግል የትምህርት ተቋማት ከፍተኛ ኃላፊዎች፣ መምህራን እና ሌሎች ሰራተኞች የተዘጋጀ አዲስ የብድር አግልግሎት መጀመሩን ይፋ አድርጓል። የተሟላ፣ ቀልጣፋ እና ምቹ የባንክ አገልግሎት ለሁሉም ማህበረሰብ ማቅረብ አንዱ የባንኩ ስልታዊ እቅድ በመሆኑ ይህ የብድር አገልግሎት በትምህርቱ ዘርፍ ያሉ ባለሙያዎችን ለመደገፍ እና ተጠቃሚ ለማድረግ የተዘጋጀ ስለመሆኑ ባንኩ አስታውቋል፡፡
ለዚህም ሁለት የብድር አይነቶችን ስለማዘጋጀቱ ጠቁሟል፤ እነዚህም:-
1- የአጭር ጊዜ ብድር (የግል ብድር)፦
2- የደመወዝ ቅድመ ክፍያ ብድር 3-የመኪና ብድር
4.የቤት መግዣ ብድር
ይህን የብድር አገልግሎት ማግኘት፤ ተመጣጣኝ የወለድ መጠን አነስተኛ የመያዣ መስፈርት፣ የመክፈያ አቅምን መሰረት በማድረግ የክፍያ ጊዜ አማራጮች፤ ከሚያስገኛቸው ልዩ ጥቅሞች መካከል ተጠቃሽ ናቸው።

Tombolla Lottery Winners July 6, 2025 - ቶምቦላ ሎተሪ ሰኔ 2017 አሸናፊዎች ->
07/06/2025

Tombolla Lottery Winners July 6, 2025 - ቶምቦላ ሎተሪ ሰኔ 2017 አሸናፊዎች ->

Tombolla Lottery Draw 2025 (ሰኔ 29 ፤ 2017) winners list which has prizes such as 3 and 2-bedroom Apartments, Volkswagen ID.6 & BYD SUV car, Cash Prizes, Smart TVs, Laptops & Smartphones

ድርሹ ዳና አሸነፈችበሁለተኛው ዓለም አቀፍ የሴቶች ፖርላመንት ላይ በሚዲያው ዘርፍ በራሷ ብርታት ላመጣቸውም ውጤት እና እናትነት ፈተና  ሳይገድባት  ለሰኬት በምታደርገው ትግል ይገባሻል በሚል...
07/01/2025

ድርሹ ዳና አሸነፈች

በሁለተኛው ዓለም አቀፍ የሴቶች ፖርላመንት ላይ በሚዲያው ዘርፍ በራሷ ብርታት ላመጣቸውም ውጤት እና እናትነት ፈተና ሳይገድባት ለሰኬት በምታደርገው ትግል ይገባሻል በሚል አለም አቀፍ ተቋም ይህንን አዋርድ ሸልሟታል።
በቀጣይ በሀገሯ ላይ ላለው የሴቶች ማንኛውም ድጋፍ ላይ አለም አቀፍ ተቋሙ እንደሚደግፏትም ገልፆል።

ካቦድ “ካቦድ ሪል እስቴት ኤከስፖ 2025- "ቤት ለገዢው ሱቅ ለነጋዴው” በሚል መሪ ቃል ከሰኔ 27 እስከ 29 2017ዓ.ም በሳይንስና ቴክኖሎጂ ሙዚየም ደማቅና ውጤታማ ኤክስፖ አዘጋጀ:: ካ...
06/20/2025

ካቦድ “ካቦድ ሪል እስቴት ኤከስፖ 2025- "ቤት ለገዢው ሱቅ ለነጋዴው” በሚል መሪ ቃል ከሰኔ 27 እስከ 29 2017ዓ.ም በሳይንስና ቴክኖሎጂ ሙዚየም ደማቅና ውጤታማ ኤክስፖ አዘጋጀ::

ካቦድ ማርኬቲንግ ሶሉሽን ላለፉት 20 ዓመታት በሸያጭናበገበያ ጥናት ላይ በዘርፉ በሰለጠኑና የካበተ ልምድ ባላቸውባለሙያዎች የተመሰረተና የሪል እስቴት ሻጮችን የማማከር፣ ቢሮ ማደራጀት፣ በዘርፉ የሰው ኃይል በማሰልጠን ውጤታማሥራዎች እንዲሰሩ በማስቻል በርካታ ሥራዎችን በመሥራትታዋቂና ተመራጭ ለመሆን የቻለ ድርጅት ነው፡፡ ከዚህም ጋርበተያያዘ ለሪል እስቴት ገንቢዎች ወይም አልሚዎች በኃላፊነትናበታማኝነት ውጤታማ የሽያጭ አጋር በመሆን ቤት ገዢዎችታማኝ ከሆኑ በሥራቸው ከሚታወቁ አልሚዎች ጋር በማገናኘትበርካታ ውጤታማ ሥራዎችን በመሥራት የተመሰከረለትድርጅት ነው፡፡
ከዚህም ሌላ ለሽያጭ ባለሙያዎች፣ የሥራ ዕድልንበማመቻቸትና ስልጠናዎችን በመስጠት ተጠቃሚ እንዲሆኑከማድረግ ባለፈ ዘርፉን በማሳደግ ጥሩ የሥራ ቦታዎችንበመፍጠርና የሥራ ፍላጐት እንዲጨምር ከማድረግም ሌላ ነፃስልጠናዎችን በተለይም ለወጣት ዜጐች የሥራ ዕድልከመፍጠር አንፃርና በኃላፊነት በመሥራት ለዘርፉምአስተዋጽዎ በማድረግ ይታወቃል፡፡
ከዚህም ጋር በተያያዘ የካቦድ ማርኬቲንግ ሶሉሽን እናእህት ኩባንያው የሆነው ዶክስ ቢዝነስ ትሬዲንግ ኃላፊነቱየተወሰነ የግል ማኀበር /ዶክስ ኤቨንትስ/ በከተማችንከሚካሄደው የሪል እስቴት ኤክስፖዎች እጅግ በዓይነቱ ለየት ያለኤክስፖ አዘጋጅቷል፡፡ በዚህም ኤክስፖ ላይ የተመረጡ የሪልእስቴት አልሚዎች ዋና ባለቤትና ኃላፊዎች የሚገኙበትናለመኖሪያ ቤትና የንግድ ሱቅ ፈላጊ ሕብረተሰብ ትልቅ የንግድልውውጦች ኢንቨስትመንት መድረክ የሚሆን “ካቦድ ሪልእስቴት ኤክስፖ 2025” “ቤት ለገዢው ሱቅ ለነጋዴው” በሚል መሪ ቃል ከሰኔ 27 እስከ 29 2017ዓ.ም በሳይንስናቴክኖሎጂ ሙዚየም ደማቅና ውጤታማ ኤክስፖአዘጋጅቷል፡፡ ከዚህም ሌላ ለቤት ፈላጊ ኀብረተሰብእንዲሁም የከተማችንን ገጽታ እየቀየረ በሚገኘውየኮሪደር ልማትና መንገዶች ዙሪያና ዳር በአፋጣኝእየተገነቡ ያሉ የንግድ ቦታዎችን ለነጋዴዎች ያቀርባል፡፡ በዚህም ኤክስፖ ላይ በርካታ ጐብኚዎች፣ የኤክስፖተጠቃሚዎች፣ ተሳታፊዎችና ታላላቅ የመንግስትየሥራ ኃላፊዎች በኤክስፖ ላይ ይገኛሉ፡፡
የዚህ ኤክስፖ አስፈላጊነት በዋናነት:-
➢ መንግስት ለትልልቅ ሪል እስቴት አልሚዎች የከተማዋንእድገት የሚያፋጥኑ መሬትን እየሰጠና አብሮ እያለማመሆኑ የሚታይበት ነው፡፡
➢ የሪል እስቴት አልሚዎች ትክክለኛ ገፅታቸው እንዲታይማድረግ ነው፡፡
➢ ቤት ፈላጊዎች ከቤት አልሚዎች ጋር በተመቻቸ መድረክእንዲገናኙ ማድረግ ነው፡፡
➢ አልሚዎች ለገበያ ያቀረቧቸውን ኢንቨስትመንትአማራጮች ከሀገር ውስጥ አልፎ በውጭ አገር ለሚገኙትውልደ ኢትዮጵያውያን /ዲያስፖራዎችን/ ሥራዎቻቸውንእንዲያውቁላቸው የሚደረግበት መድረክ ነው፡፡
➢ በሪል እስቴት ዘርፎች ግንዛቤ አስጨባጭ ውይይቶችንእንዲካሄድ ማድረግ፣
➢ በዚህ ኤክስፖ ላይ ሪል እስቴት ያቀረቧቸውን አስደናቂአማራጮች ለሕብረተሰቡ ለማቅረብ በካቦድ ማርኬቲንግሶሉሽንና በዶክስ ኢንቨንትስ እህት ኩባንያ አስተማማኝየማማከር አገልግሎት የሚሰጥበት መድረክ ነው፡፡
➢ በከተማችን ውስጥ የመኖሪያ ቤት እጥረት ምን ያህልከባድ እንደሆነ የሚታወቅ ሲሆን በረጅም ጊዜ አከፋፈልናጥራት ያላቸውን መኖሪያ ቤቶች ለማህበረሰቡ ለማቅረብየተለያዩ አማራጮችን በመጠቀም ገዢዎቹን ከአልሚዎቹጋር ያገናኛል፡፡

በመጨረሻም እነዚህ ዓይነት የሪል እስቴት ኤስፖዎችየማማከርና የማሰልጠን እንዲሁም በከተማችን የሚገኘውንየመኖሪያ ቤት እጥረት መቅረፍ በሚቻልበት ሁኔታ ሚኒስቴርመ/ቤቶች፣ ባለድርሻ አካላት በየዘርፉ ያሉ የመንግስትተቋማትና ሚዲያዎች ድጋፍና አጋርነታቸውን እንዲያሳዩይጠበቃል፡፡

እናት ባንክ በኢትዮጵያ የባንክ ዘርፍ በሴቶች አካታች የባንክ አገልግሎት የምዘና መስፈርት ብቸኛና ቀዳሚ ባንክ በመባል ተሸለመች።የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ከዓለም ባንክ የሥርዓተ-ፆታ ፈጠራ ጋ...
06/20/2025

እናት ባንክ በኢትዮጵያ የባንክ ዘርፍ በሴቶች አካታች የባንክ አገልግሎት የምዘና መስፈርት ብቸኛና ቀዳሚ ባንክ በመባል ተሸለመች።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ከዓለም ባንክ የሥርዓተ-ፆታ ፈጠራ ጋር በመተባበር ባካሄዱት የ2025 የባንኮች የስርዓተ ፆታ አካታችነት ምዘና መስፈርት መሰረት እናት ባንክ የተሻለ ስራ በመስራቷ ከ30 የኢትዮጵያ ባንኮች የመጀመሪያና ብቸኛ ባንክ መሆኗ ተገልጿል።

ለሴቶች የተለየ የባንክ አገልግሎት ማቅረብ፣ በፈጠራ የተደገፈ የባንክ አሠራር መዘርጋት ብሎም ቀልጣፋ አገልግሎት መስጠት በኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ የባንኮች ሁሉን አካታችነት የባንክ አገለግሎት መስፈርቶች ሲሆኑ እናት ባንክም እነዚህን መስፈርቶች በማሟላቷ ቀዳሚ ባንክ መባል ችላለች።

በእነዚህና መሰል ምክንያቶች እናት ባንክ ሴቶችን በኢኮኖሚ ተጠቃሚ የሚያደርግ አካታች የባንክ አገልግሎት አሰራር ዘርግታ በመስራቷና ሌሎች ሴቶችን በንግዱ ዘርፍ ተጠቃሚ የሚያድርጉ ተግባራትን በማከናወኗ በተቀመጠው መለኪያ ቀዳሚ ደረጃ ላይ ተመዝግባለች።

በዚህም የእናት ባንክ ደንበኞችን፣ የቦርድ አባላቶችን፣ ባለ አክሲዮኖችን፣ አደራጆችን ብሎም ከፍተኛ አመራሮችን እና ሠራተኞች ባንኳ አመስግናለች።

06/18/2025

"እኔ"

ለኢትዮጵያ ብቸኛውን እና ውዱን መሳሪያ አግኝተኛል | ወላጆች ልጃቸው በህክምና ቢሞ.ት እሬ.ሳውን አያገኙም "
06/17/2025

ለኢትዮጵያ ብቸኛውን እና ውዱን መሳሪያ አግኝተኛል | ወላጆች ልጃቸው በህክምና ቢሞ.ት እሬ.ሳውን አያገኙም "

ለኢትዮጵያ ብቸኛውን እና ውዱን መሳሪያ አግኝተኛል | ወላጆች ልጃቸው በህክምና ቢሞ.ት እሬ.ሳውን አያገኙም Hiwote Tadese | Ethiopia Subscribe to our channel Amharic Tube and enjoy Ethiopian dai...

06/17/2025

ሞቢሊቲ ኢ ከእህት ኩባንያው ድጋፍ ማይክሮ ፈይናንስ ጋር በመተባበር ለ5ኛ ዙር የኤሌትሪክ መኪናዎችን ርክክብ አደረገ።

06/16/2025

ጋዜጠኛዋ የልደት ቀኗን ምክንያት በማድረግ ለኢትዮጵያ ብቸኛ የሆነውን የልብ ህክምና ማሽን ለልብ ማዕከል አስረከበች

"እኔ" የተሰኝው መፅሐፍ  ተመረቀ!!************************************የቀድሞ የሸገር ሬዲዮ ጋዜጠኛ የነበረችውና በአሁኑ ወቅት ነዋሪነቷን አሜሪካን ሐገር ያደረገችው የ...
06/15/2025

"እኔ" የተሰኝው መፅሐፍ ተመረቀ!!
************************************

የቀድሞ የሸገር ሬዲዮ ጋዜጠኛ የነበረችውና በአሁኑ ወቅት ነዋሪነቷን አሜሪካን ሐገር ያደረገችው የጤና ባለሙያዋ የሚስጢረ አደራው "እኔ" የተሰኝው መጽሐፍ በዋሊያስ መፅሐፍት አዳራሽ ሰኔ 07/10/17 ዓ.ም የተለያዩ እንግዶች በተገኙበት ተመርቋል::

📸 Tekle Markon

Address

Santa Monica, CA

Telephone

+13105709291

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Sodere posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Our Story

Sodere is an Ethiopian news and entertainment website. Sodere Media streams Ethiopian movies legally through SodereOnDemand website. Sodere has started as a blog on October 2010 and became a news and entertainment site in January 2011. As of Dec 4, 2016, sodere.com has close to 42,000 highly engaged email subscribers. There were more than 10.1 million visitors in 2015. Half of our members has invited more than 20 of their friends to read news and become a member of Sodere. 40% of our users visit the website twice daily. Sodere has it's own social features integrated in the website. Every member can submit articles, blogs and videos. Members also can post activity, communicate and send messages to each other. Membership, blog posts, article and videos submission are all moderated and approved by moderators. As of April 2013 Sodere team has launched SodereTube.com exclusively for videos and had 1.6 million visitors in 2013.