Sodere Sodere is Ethiopian film streaming service, website, application and online store. Sodere Media produces and owns the largest Ethiopian movies library.

Sodere is an Ethiopian movie producer, studio, website, application and entertainment website.

ኦሜጋ ብድርና ቁጠባ ህብረት ስራ ማህበር ከሚዲያ እና ኪነ ጥበብ ባለሙያዎች ጋር ተፈራረመ።   |ኦሜጋ ብድርና ቁጠባ ህብረት ስራ ማህበር ከሚዲያ እና ኪነ ጥበብ ባለሙያዎች ጋር ዛሬ ሕዳር 1...
11/21/2025

ኦሜጋ ብድርና ቁጠባ ህብረት ስራ ማህበር ከሚዲያ እና ኪነ ጥበብ ባለሙያዎች ጋር ተፈራረመ።

|ኦሜጋ ብድርና ቁጠባ ህብረት ስራ ማህበር ከሚዲያ እና ኪነ ጥበብ ባለሙያዎች ጋር ዛሬ ሕዳር 12 ቀን 2018 ዓ.ም የስምምነት ፊርማ አድርጓል።

የሚዲያ እና ኪነ ጥበብ ባለሙያዎች ባለሙያዎቹ ለሚሰሯቸው ሙያዊ ስራዎች የፋይናንስ አቅም ተግዳሮት እንዳይሆንባቸው እና ከስራቸው እንዳያስተጓጉላቸው በልዩ ሁኔታ የብድር አቅርቦት ለማመቻቸት መዘጋጀቱ ተነግሯል።

በዛሬው ዕለት ከቦሌ ክፍለ ከተማ እና ከክፍለ ከተማው ወረዳ 12 የህብረት ስራ ኮሚሽን ፅህፈት ቤት ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች በተገኙበት ስራውን በይፋ የጀመረው ኦሜጋ ብድርና ቁጠባ ህብረት ስራ ማህበር ለሁሉም ኢትዮጵያዊ አስተማማኝ የፋይናንስ አጋር ለመሆን መዘጋጀቱን ገልጿል።

በተጨማሪም የወረዳው ጋር በመሆን ለ10 ሴቶች ከወለድ ነጻ ብድር መመቻቸቱ ተነግሯል።

ኦሜጋ ብድርና ቁጠባ ህብረት ስራ ማህበር ብድር ፈላጊዎች የአጭር ጊዜ አነስተኛ ወለድ ያለው የብድርፐ አገልግሎት፣ በቡድን ለሚመጡ ብድር ፈላጊዎች ልዩ የወለድ ቅናሽ፣ ወላጆች ለታዳጊ ተማሪ ልጆቻቸው የት/ቤት ክፍያ ብድር፣ ለከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ዝግጅት የሚሆን ብድር፣ ለጤና አገልግሎት የሚውል ብድር፣ ለተለያዩ የውጭ ጉዞዎች የሚሆን ብድር እና ለሴቶች ስራ ማስጀመሪያ የሚሆን ከወለድ ነፃ የብድር አገልግሎት ማህበሩ ይዟቸው ከመጡ ብድሮች መካከል ይጠቀሳሉ ተብሏል።

ኦሜጋ ብድርና ቁጠባ ህብረት ስራ ማህበር በ2017 ዓ.ም በህብረት ስራ ማህበር አዋጅ ቁጥር 985/09 በህጋዊ መንገድ የተቋቋመው ማህበር ነው፡፡

የበቃ ፍቅር ፊልም ምረቃ
11/18/2025

የበቃ ፍቅር ፊልም ምረቃ

Subscribe to Etege Entertainment | And Turn ON Notifications To Stay Updated With All New Uploads!🔔Unauthorized use, Distribution And Re-Upload of This Cont...

በስንታየሁ ታዬ Sintayehu Taye  (ፋቡላ) የተዘጋጀው "መልቲ" አዲስ ኮሜዲ ቴአትር በቀይ ምንጣፍ ስነ ስርዓት በድምቀት ተመርቋል።በአዶት ሲኒማ በተመረቀው ትያትር ታላላቅ የኪነ ጥበብ...
11/17/2025

በስንታየሁ ታዬ Sintayehu Taye (ፋቡላ) የተዘጋጀው "መልቲ" አዲስ ኮሜዲ ቴአትር በቀይ ምንጣፍ ስነ ስርዓት በድምቀት ተመርቋል።

በአዶት ሲኒማ በተመረቀው ትያትር ታላላቅ የኪነ ጥበብ ባለሙያዎች፣ ትያትር አፍቃሪያን፣ እና በርካታ ተመልካቾች ተገኝተዋል።

በከፍተኛ የተመልካች ሳቅ የታጀበው የ"መልቲ" ትያትር የመጀመሪያ የምርቃት መድረክ በብዙዎች ዘንድ አድናቆትን ማግኘት ችሏል።

የዕለቱ የክብር እንግዳ የኢፌድሪ የቴክኒክና ሙያ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ብሩክ ከድር (ዶ/ር) ትያትሩ እንዲሳካ ላደረጉ የምስክር ወረቀት ሰጥተዋል።

ትያትሩ ዘወትር አርብ በ11:30 በአዶት ሲኒማ በቋሚነት መታየት ይጀምራል።

11/16/2025

"መልቲ"
ዛሬ ህዳር 7 ብስራተ ገብርኤል በሚገኘው አዶት ሲኒማ ምሽት 11:00 ላይ በቀይ ምንጣፍ ይመረቃል።


#መልቲቴአትር
#ቴአትር
#ፊልም
#አዲስ
Abel Melti
Surafel Bisrat
Selamawit Kassaye
Tewodros Shewangizaw
Amore Amore
Cassiopiea Daniel
Mitiku Bekele
Sintayehu Taye
Bella Entertainment
ኤልሻዳይ ከበደ

አንጋፋ የኪነ-ጥበብ ምሽት ...!  | 34ኛው የባህል ማዕከል የኪነጥበብ ምሽት ረቡዕ ህዳር 10፥2018 ዓ.ም ይጀምራል። በዕለቱም ታዋቂው ኮሜዲያን እሸቱ መለሰ የክብር እንግዳችን ሆኖ በመ...
11/15/2025

አንጋፋ የኪነ-ጥበብ ምሽት ...!

| 34ኛው የባህል ማዕከል የኪነጥበብ ምሽት ረቡዕ ህዳር 10፥2018 ዓ.ም ይጀምራል። በዕለቱም ታዋቂው ኮሜዲያን እሸቱ መለሰ የክብር እንግዳችን ሆኖ በመካከላችን በመገኘት ሙያዊ ልምዱን ያካፍላል።

እንዲሁም ግጥሞች ፣ ወግ ፣ ሙዚቃና ሞኖሎግ ተሰናድቶ እናንተ ውድ ታዳሚዎቻችንን በባህል ማዕከል አዳራሽ ከቀኑ በ 11: 30 ጀምሮ ይጠብቃችኃል።

#ማስታወሻ :— ፕሮግራሙ ላይ ለመታደም የምትፈልጉ በአሁን ሰዓት የዩኒቨርስቲው ተማሪ ያልሆናችሁ የስነ-ጽሑፍ አፍቃሪያን መግቢያው በ5ተኛ በር በኩል ነው።

እባክዎ ሸር በማድረግ ተባበሩን!

ታማኝ በየነ ስለ ጌትነት እንየው ምን አለ? | የልብ ወዳጆቹ ምስክርነት | የጌትነት በእንባ የተሞላው ንግግሩ |Getenet Eneyew Atta ሙሉውን ቪዲዬ ለመመልከት ከታች ያለውን ሊንክ ...
11/13/2025

ታማኝ በየነ ስለ ጌትነት እንየው ምን አለ? | የልብ ወዳጆቹ ምስክርነት | የጌትነት በእንባ የተሞላው ንግግሩ |Getenet Eneyew Atta

ሙሉውን ቪዲዬ ለመመልከት ከታች ያለውን ሊንክ ይጫኑ
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👍👍👍

ታማኝ በየነ ስለ ጌትነት እንየው ምን አለ? | የልብ ወዳጆቹ ምስክርነት | የጌትነት በእንባ የተሞላው ንግግሩ |Getenet Eneyew Atta| Ethiopia Subscribe to our channel Amharic Tube and enjoy Ethiop...

“የሥርዓተ ፆታ ቦንድ' (Gender Bond)”ሴቶችን የፋይናንስ ተጠቃሚነት ለማሳደግ በልዩ ሁኔታ የተመሠረተው እናት ባንክ፣ በኢትዮጵያ የፋይናንስ ኢንዱስትሪ ውስጥ የመጀመሪያውን በግል ዘርፍ...
11/13/2025

“የሥርዓተ ፆታ ቦንድ' (Gender Bond)”

ሴቶችን የፋይናንስ ተጠቃሚነት ለማሳደግ በልዩ ሁኔታ የተመሠረተው እናት ባንክ፣ በኢትዮጵያ የፋይናንስ ኢንዱስትሪ ውስጥ የመጀመሪያውን በግል ዘርፍ የሚወጣ 'የሥርዓተ ፆታ ቦንድ' (Gender Bond) ለገበያ ለማቅረብ ጥናት መጀመሩን አስታውቋል።

ይህንን አዲስ የገንዘብ ማሰባሰቢያ መሣሪያ ለመጠቀም የሚያስችለውን ጥናት ከትራንዛክሽን አማካሪው አይ ካፒታል ኢንስቲትዩት ኃ.የተ.የግ.ማ. ጋር በመተባበር እየሰራ መሆኑን ገልጿል።

የቦንዱ ዋና ዓላማ እስካሁን ድረስ በፋይናንስ እጥረት ምክንያት ተገቢውን አገልግሎት ያላገኙትን በሴቶች ባለቤትነት የተያዙ ወይም በሴቶች የሚመሩ ድርጅቶች፣ ሴት ሥራ ፈጣሪዎችና አርሶ አደሮችን በአመቺ ብድር ተደራሽ ማድረግ ነው።

ይህ እርምጃ ባንኩ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በአካታችነት (Financial Inclusion) የያዘውን ዕቅድ ለመደገፍ ትልቅ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው ታምኖበታል።

የእናት ባንክ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኤርሚያስ አንዳርጌ እንደገለጹት፣ ባንኩ በኢትዮጵያ የካፒታል ገበያ ቁልፍ ተጫዋች ለመሆን የሚያስችሉ ዝግጅቶችን እያደረገ ሲሆን፣ ባለስልጣኑ ባስቀመጠው የጊዜ ገደብ ውስጥ በህዝብ የተያዙ አክሲዮኖችን መዝግቦ ለማጠናቀቅ ከአይ ካፒታል ኢንስቲትዩት ጋር በመስራት ላይ ይገኛል።

ባንኩ፣ ከ11 ባለራዕይ ሴቶች በመቋቋሙ ላለፉት 12 ዓመታት አሳይቷል በተባለዉ ዕድገት ተከትሎ፣ የባንኩ ባለአክሲዮኖች ቁጥር 27 ሺህ 136 የደረሰ ሲሆን ከዚህም ውስጥ 60 በመቶ የሚሆኑት ሴቶች መሆናቸውን አስታውቋል።

ባንኩ በዛሬዉ ዕለት በሰጠዉ መግለጫ ፤ በቅርቡም የብሔራዊ ባንክን የብር 5 ቢሊዮን የተከፈለ ካፒታል መስፈርት ለመሙላት ተዘጋጅቻለሁ ብሏል።

እናት ባንክ የሥርዓተ ፆታ ቦንዱን አስመልክቶ የሚያስፈልጉ ጥናቶችን በአስቸኳይ በማጠናቀቅ ለብሔራዊ ባንክና ለካፒታል ገበያ ባለስልጣን እንደሚያቀርብና ዝርዝር መረጃውን እና የሽያጭ መጀመሪያ ቀኑን ፈቃድ እንዳገኘ ይፋ እንደሚያደርግ አስታውቋል።

11/12/2025

Now Hiring – Join Yoo Production!
Established in 2006, Yoo Production specializes in social media management, documentary filming, and video documentation.

We’re looking for creative and passionate people to join our team!

🎬 Open Positions:
1️⃣ Content Creator – for social media & documentary projects
2️⃣ Video Editor – experienced in editing for social media & film
3️⃣ Cameraman / Videographer – skilled in camera, lighting, and sound

✅ Requirements:
• Creative and reliable
• Team player
• Experience in video, photography, or content creation

📩 How to Apply:
Send your CV or portfolio to [email protected]
Or contact us on WhatsApp: +1 202 263 9084

11/12/2025

"መልቲ" የተሰኘ አዲስ ትያትር ለዕይታ ሊበቃ ነው

“መልቲ” ትያትር በአዲስ መልክ ለዕይታ ሊበቃ ነው።  በዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ላይ ታሪኩን ማጠንጠኛ ያደረገው መልቲ ትያትር ከአመታት በፊት በአዲስ አበባ ቴአተርና ባህል አዳራሽ-ማዘጋጃ ቤት ለ...
11/12/2025

“መልቲ” ትያትር በአዲስ መልክ ለዕይታ ሊበቃ ነው።

በዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ላይ ታሪኩን ማጠንጠኛ ያደረገው መልቲ ትያትር ከአመታት በፊት በአዲስ አበባ ቴአተርና ባህል አዳራሽ-ማዘጋጃ ቤት ለዕይታ በቅቶ የነበረ ትያትር ነው።

ትያትሩ ዘመኑን በሚመጥንና በአዳዲስ ሀሳቦች ዳግም እንደተዘጋጀ ዛሬ ሕዳር 03 ቀን 2018 ዓ.ም በተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ ተነግሯል።

ምትኩ በቀለ፣ ኤልሻዳይ ከበደ፣ ሱራፌል ብስራት፣ ቴዎድሮስ ሸዋንግዛው፣ አቤል ሰለሞን እና ሰላማዊት ካሳዬ በትወና የተሳተፉ ሲሆን በመልቲ የትያትር ቡድን ተደርሶ በስንታየሁ ታዬ (ፋቡላ) ተዘጋጅቷል።

የኮሜዲ ዘውግ ያለው “መልቲ” ቴአትር የትያትር ወዳጆችን እርካታ ለመሙላት በማሰብ ከፍ ባለ ሙያዊ ጥንቃቄ ለአንድ አመት ያህል በተዋንያን መረጣ፣ አልባሳትና መሰል ሙያዊ ዝግጅቶች ላይ መቆየቱ ተነግሯል።

ህዳር 7 ቀን 2018 ዓ.ም ጥሪ የተደረገላቸው ታላላቅ የኪነ ጥበብ ባለሙያዎች፣ የትያትርና ፊልም መምህራን ብሎም የተመረጡ እንግዶች በተገኙበት በቀይ ምንጣፍ ስነ-ስርዓት ይመረቃል።

ከምርቃቱ በኋላም ዘወትር አርብ በ12:00 ሰዓት ብስራተ ገብርኤል በሚገኘው አዶት ሲኒማ መታየት ይጀምራል።

የትያትር ተመልካቾች የቴአትር ቤት መግቢያ ትኬታቸውን በእናት ባንክ የዲጂታል ባንኪንግ ሲስተም መቁረጥ የሚያስችላቸውን አሰራር በዕለቱ ይፋ ሆኗል።

በዚህ አሰራር መሰረት ትያትር ተመልካቾች የመግቢያ ትኬታቸውን በእናት ባንክ ዲጂታል ባንኪንግ አማካኝነት በቀላሉ መቁረጥ የሚችሉ ይሆናል።

ይህንን አሰራር ለመጀመሪያ ጊዜ አዶት ሲኒማ ከእናት ባንክ እና ከመልቲ የትያትር ቡድን ጋር የመግባቢያ ስምምነት ፊርማ በመፈራረም ያስጀመሩ ሲሆን በቀጣይ በሌሎች ትያትር እና ሲኒማ ቤቶች አሰራሩ ተግባራዊ እንደሚደረግ ተገልጿል።

11/11/2025

ታክ ቢዝነስ ግሩፕ የኤሌክትሪክ መኪና ቻርጅ መሞያ ጣቢያዎችን ለመገንባት ከቻይና ኩባንያ ጋር ተፈራረመ

11/11/2025

ለሎሬት ጌትነት እንየው የተበረከቱ ሽልማቶችና ማዕረግ

ከአቢሲኒያ ባንክ የ5 ሚሊዮን ብር ስጦታ

በባህዳር ከተማ አዲስ በሚከፈተው የአቢሲኒያ ባንክ አዲስ ቅርንጫፍ በጌትነት እንየው ስም ይሰየማል

ከአቢሲኒያ ባንክ የጌትነት እንየው የስራ ዘመናትና ስራዎቹን የሚያስታውስ ሰዕል ተበርክቶለታል።

ከሃበሻ ቢራ የ2025 BYD መኪና ስጦታ

ከብሔራዊ ቲያትር ቤት የካባ ሽልማት ተበርክቶለታል

በደራሲ ኃይሉ ፀጋዬ ቀስቃሽነት በኪነጥበቡ ቤተሰብ ይሁንታና በአኢትዮዽያ ህዝብ ስም ከዛሬ ጀምሮ የሎሬትነት ማዕረግ ተሰጥቶታል

የዚህ ፕሮግራም ዋና አዘጋጅ ተስፋ የኪነ-ጥበብ ኢንተርፕራይዝ ተፈራ ወርቁ፣ የአርቲስቱ የቅርብ ወዳጀች እና ቤተሰቦቹ በጋራ በመሆን ነው።

Address

312 Arizona Avenue
Santa Monica, CA
90401

Telephone

+13105709291

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Sodere posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Our Story

Sodere is an Ethiopian news and entertainment website. Sodere Media streams Ethiopian movies legally through SodereOnDemand website. Sodere has started as a blog on October 2010 and became a news and entertainment site in January 2011. As of Dec 4, 2016, sodere.com has close to 42,000 highly engaged email subscribers. There were more than 10.1 million visitors in 2015. Half of our members has invited more than 20 of their friends to read news and become a member of Sodere. 40% of our users visit the website twice daily. Sodere has it's own social features integrated in the website. Every member can submit articles, blogs and videos. Members also can post activity, communicate and send messages to each other. Membership, blog posts, article and videos submission are all moderated and approved by moderators. As of April 2013 Sodere team has launched SodereTube.com exclusively for videos and had 1.6 million visitors in 2013.