AmharicTube

AmharicTube Amharic Tube Ethiopian movies, press conference and news
(1)

ኦሜጋ ብድርና ቁጠባ ህብረት ስራ ማህበር ከሚዲያ እና ኪነ ጥበብ ባለሙያዎች ጋር ተፈራረመ።ኦሜጋ ብድርና ቁጠባ ህብረት ስራ ማህበር ከሚዲያ እና ኪነ ጥበብ ባለሙያዎች ጋር ዛሬ ሕዳር 12 ቀን...
11/21/2025

ኦሜጋ ብድርና ቁጠባ ህብረት ስራ ማህበር ከሚዲያ እና ኪነ ጥበብ ባለሙያዎች ጋር ተፈራረመ።

ኦሜጋ ብድርና ቁጠባ ህብረት ስራ ማህበር ከሚዲያ እና ኪነ ጥበብ ባለሙያዎች ጋር ዛሬ ሕዳር 12 ቀን 2018 ዓ.ም የስምምነት ፊርማ አድርጓል።

የሚዲያ እና ኪነ ጥበብ ባለሙያዎች ባለሙያዎቹ ለሚሰሯቸው ሙያዊ ስራዎች የፋይናንስ አቅም ተግዳሮት እንዳይሆንባቸው እና ከስራቸው እንዳያስተጓጉላቸው በልዩ ሁኔታ የብድር አቅርቦት ለማመቻቸት መዘጋጀቱ ተነግሯል።

በዛሬው ዕለት ከቦሌ ክፍለ ከተማ እና ከክፍለ ከተማው ወረዳ 12 የህብረት ስራ ኮሚሽን ፅህፈት ቤት ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች በተገኙበት ስራውን በይፋ የጀመረው ኦሜጋ ብድርና ቁጠባ ህብረት ስራ ማህበር ለሁሉም ኢትዮጵያዊ አስተማማኝ የፋይናንስ አጋር ለመሆን መዘጋጀቱን ገልጿል።

በተጨማሪም የወረዳው ጋር በመሆን ለ10 ሴቶች ከወለድ ነጻ ብድር መመቻቸቱ ተነግሯል።

ኦሜጋ ብድርና ቁጠባ ህብረት ስራ ማህበር ብድር ፈላጊዎች የአጭር ጊዜ አነስተኛ ወለድ ያለው የብድርፐ አገልግሎት፣ በቡድን ለሚመጡ ብድር ፈላጊዎች ልዩ የወለድ ቅናሽ፣ ወላጆች ለታዳጊ ተማሪ ልጆቻቸው የት/ቤት ክፍያ ብድር፣ ለከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ዝግጅት የሚሆን ብድር፣ ለጤና አገልግሎት የሚውል ብድር፣ ለተለያዩ የውጭ ጉዞዎች የሚሆን ብድር እና ለሴቶች ስራ ማስጀመሪያ የሚሆን ከወለድ ነፃ የብድር አገልግሎት ማህበሩ ይዟቸው ከመጡ ብድሮች መካከል ይጠቀሳሉ ተብሏል።

ኦሜጋ ብድርና ቁጠባ ህብረት ስራ ማህበር በ2017 ዓ.ም በህብረት ስራ ማህበር አዋጅ ቁጥር 985/09 በህጋዊ መንገድ የተቋቋመው ማህበር ነው፡፡

እንጀራ በሸቀጣሸቀጦች ሱቅ መሸጥ ተከለከለየተለያዩ ሸቀጣሸቀጦች በሚሸጡባቸው ሱቆች ውስጥ እንጀራ መሸጥ መከልከሉን የአዲስ አበባ  ምግብና መድሃኒት ባለስልጣን በተለይ ለኤ ኤም ኤን ኤፍ ኤም ...
11/17/2025

እንጀራ በሸቀጣሸቀጦች ሱቅ መሸጥ ተከለከለ

የተለያዩ ሸቀጣሸቀጦች በሚሸጡባቸው ሱቆች ውስጥ እንጀራ መሸጥ መከልከሉን የአዲስ አበባ ምግብና መድሃኒት ባለስልጣን በተለይ ለኤ ኤም ኤን ኤፍ ኤም 96.3 ሬዲዮ አሳውቋል።

የባለስልጣኑ ምክትል ሥራ አስኪያጅ አቶ እንጋ እርቀታ፣ የተለያዩ መርዛማ ነገሮች ሳሙና እና ለጤና ጠንቅ የሆኑ ሸቀጦች በሚሸጡባቸው ሱቆች በቀጥታ ለምግብነት የሚውሉትን እንጀራ እና ዳቦን መሸጥ ልክ ባለመሆኑ ለመከልከል መገደዳቸውን ተናግረዋል።

እንጀራ እና ዳቦ መሸጥ ያለባቸው በምግብ ቤቶች፣ በዳቦ ቤተች እና በባልትና ወይም ለዚሁ መሻጫነት በተፈቀደ ቦታ ብቻ መሆኑንም አስረድተዋል።

ሕብረተሰቡ ለጤናው ጠንቅ መሆኑን ተገንዝቦ ተባባሪ እንዲሆንና ጥቆማም እንዲሰጥ የጠየቁት ምክትል ሥራ አስኪያጁ፣ ያልተፈቀደላቸው ነጋዴዎችም ሲሸጡ ከተገኙ አስፈላጊው የእርምት እርምጃ እንደሚወሰድባቸው አስገንዝበዋል።

VIA AMN

በ  #አማራ ክልል የኦፓል ማዕድን ዋሻ የተናደባቸው ማዕድን አውጭዎች አፅም ተገኝቶ ስርዓተ ቀበራቸው ተፈፀመበአማራ ክልል ደቡብ ወሎ ዞን ደላንታ ወረዳ ባሳለፍነው ዓመት ጥር 30 ቀን 2016...
11/17/2025

በ #አማራ ክልል የኦፓል ማዕድን ዋሻ የተናደባቸው ማዕድን አውጭዎች አፅም ተገኝቶ ስርዓተ ቀበራቸው ተፈፀመ

በአማራ ክልል ደቡብ ወሎ ዞን ደላንታ ወረዳ ባሳለፍነው ዓመት ጥር 30 ቀን 2016 ዓ.ም ኦፓል በማውጣት ላይ ሳሉ ዋሻ ተንዶባቸው ህይወታቸው ያለፈ ስመንት ወጣቶች አፅም ተገኝቶ ስርዓተ ቀበራቸው መፈጸሙ ተገልጿል።

በደላንታ ወረዳ በተለምዶ ቆቅ ውኃ እየተባለ በሚጠራ አካባቢ ጥር 30 ቀን 2016 ዓ.ም ሌሊት የኦፓል ማዕድን በቁፋሮ ለማውጣት ሲሞክሩ የነበሩ በርካታ ወጣቶች የቆፈሩት አለት ተንዶ ህወታቸውን ማትረፍ እና አጽማቸውን ማውጣት ሳይቻል ቆይቷል።

የቦታው መልክአ ምድር ምቹ በመሆኑ አጽማቸውን ለማውጣት አስቸጋሪ ማድረጉን የወረዳው አስዳዳሪ በወቅቱ አስታውቋል። የደቡብ ወሎ ዞን ኮሙኒኬሽን ባሳለፍነው ሳምንት ባወጣው መግለጫ፣ የወጣቶቹን ሕይወት ለመታደግ መንግስት የተለያዩ ጥረቶችን ቢያደርግም ወጣቶቹን ከተዳፈኑበት ማውጣት ሳይቻል ቀርቶ ነበር ሲል አስታውሷል።

ይሁን እንጂ ባሳለፍነው ሳምንት ህዳር 4 ቀን 2018 ዓ/ም በአካባቢው ኦፖል በማውጣት ላይ የነበሩ ወጣቶች አፅማቸው ማግኘታቸውን ኮሙኒኬሽኑ አስታውቋል።

ይህንንም ተከትሎ የወረዳው አስተዳደሪ እና ሌሎች ኃላፊዎች በተገኙበት ህዳር 4 ቀን ከማለዳው 12:00 ጀምሮ የአፀም ማውጣት ስራው ተጀምሮ የ8 ወጣቶች አፅም ወጥቶ ወዳጅ ዘመዶቻቸው በተገኙበት በወገልጤና ርዕሰ አድባራት ሐመረኖህ ቅድስት ኪዳነምህረት ቤተክርስቲያን የፍትሃተ ፀሎት ተደርጎ ስርዓተ ቀብራቸው ተፈፅሟል ተብሏል።

ላለፉት 13 አመታት የኦፓል ማዕድን ቁፋሮ ሲደረግበት የቆየው ዋሻ ከ750 ሜትር በላይ ርዝመት ያለው ሲሆን በደረሰበት የመናድ አደጋ በውስጡ የቀሩ ሰዎችን ለማውጣት በወቅቱ ከ80 ሜትር በላይ ቁፋሮ መደረጉ ይታወሳል።

በነዳጅ ምርቶች ላይ የተጣለዉ አጠቃላይ የ30 በመቶ ግብር በቀጣይ ወር ተግባራዊ እንደሚሆን ተገለፀ የኢትዮጵያ መንግሥት ለረጅም ጊዜ የዘለቀውን የነዳጅ ድጎማ ቀስ በቀስ ለማስወገድ ከሚወስዳቸ...
11/17/2025

በነዳጅ ምርቶች ላይ የተጣለዉ አጠቃላይ የ30 በመቶ ግብር በቀጣይ ወር ተግባራዊ እንደሚሆን ተገለፀ

የኢትዮጵያ መንግሥት ለረጅም ጊዜ የዘለቀውን የነዳጅ ድጎማ ቀስ በቀስ ለማስወገድ ከሚወስዳቸው ሰፋፊ የኢኮኖሚ ማሻሻያዎች አንዱ የሆነው አዲስ የግብር አወቃቀር ከሚቀጥለው ወር ጀምሮ ተግባራዊ ሊሆን ነው።

ይህ አዲስ እርምጃ በነዳጅ ምርቶች ላይ 15 በመቶ ተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) እና 15 በመቶ ኤክሳይዝ ቀረጥን ያካተተ አጠቃላይ 30 በመቶ ታክስ መጣል ሲሆን፤ የኢትዮጵያ ነዳጅ አቅራቢ ድርጅት ከአንድ ወር በኋላ ታክሱን መሰብሰብ ይጀምራል።

በአዲሱ መመሪያ መሠረት፣ ነዳጅ አቅራቢ ድርጅቱ የተሰበሰበውን ግብር በሙሉ ለገቢዎች ሚኒስቴር ማስገባት ግዴታው ሲሆን፤ መንግሥት በዚህም እስከ ታኅሣሥ 2018 ዓ.ም ድረስ ለቤንዚንና ናፍጣ መሸጫ ዋጋዎች ሁሉንም ህጋዊ የግብር መጠን ጨምሮ ሙሉ ወጪን የመሸፈን ግብ ላይ ለመድረስ አቅዷል።

የገንዘብ ሚኒስቴር ከአዲሱ በጀት ዓመት ጀምሮ በነዳጅ ምርቶች ላይ አጠቃላይ 30 በመቶ ግብር ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ ሊያደርግ ማቀዱን ከሁለት ወራት በፊት መዘገቡን አስታዉሶ ካፒታል አስነብቧል፡፡

በስንታየሁ ታዬ Sintayehu Taye  (ፋቡላ) የተዘጋጀው "መልቲ" አዲስ ኮሜዲ ቴአትር በቀይ ምንጣፍ ስነ ስርዓት በድምቀት ተመርቋል።በአዶት ሲኒማ በተመረቀው ትያትር ታላላቅ የኪነ ጥበብ...
11/17/2025

በስንታየሁ ታዬ Sintayehu Taye (ፋቡላ) የተዘጋጀው "መልቲ" አዲስ ኮሜዲ ቴአትር በቀይ ምንጣፍ ስነ ስርዓት በድምቀት ተመርቋል።

በአዶት ሲኒማ በተመረቀው ትያትር ታላላቅ የኪነ ጥበብ ባለሙያዎች፣ ትያትር አፍቃሪያን፣ እና በርካታ ተመልካቾች ተገኝተዋል።

በከፍተኛ የተመልካች ሳቅ የታጀበው የ"መልቲ" ትያትር የመጀመሪያ የምርቃት መድረክ በብዙዎች ዘንድ አድናቆትን ማግኘት ችሏል።

የዕለቱ የክብር እንግዳ የኢፌድሪ የቴክኒክና ሙያ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ብሩክ ከድር (ዶ/ር) ትያትሩ እንዲሳካ ላደረጉ የምስክር ወረቀት ሰጥተዋል።

ትያትሩ ዘወትር አርብ በ11:30 በአዶት ሲኒማ በቋሚነት መታየት ይጀምራል።

የድምፃዊ በረከት መንግስተዓብ ስርዓተ ቀብር ፕሬዚዳንት ኢሳያስ በተገኙበት ተፈፀመ።Via: Eritrean Media Network
11/16/2025

የድምፃዊ በረከት መንግስተዓብ ስርዓተ ቀብር ፕሬዚዳንት ኢሳያስ በተገኙበት ተፈፀመ።

Via: Eritrean Media Network

11/16/2025

"መልቲ"
ዛሬ ህዳር 7 ብስራተ ገብርኤል በሚገኘው አዶት ሲኒማ ምሽት 11:00 ላይ በቀይ ምንጣፍ ይመረቃል።


#መልቲቴአትር
#ቴአትር
#ፊልም
#አዲስ
Abel Melti
Surafel Bisrat
Selamawit Kassaye
Tewodros Shewangizaw
Amore Amore
Cassiopiea Daniel
Mitiku Bekele
Sintayehu Taye
Bella Entertainment
ኤልሻዳይ ከበደ

" የበሽታዉ መንስኤ ማርበርግ ቫይረስ (Marburg Virus) መሆኑን መለየት ተችሏል " - ጤና ሚኒስቴር የጤና ሚኒስቴር በደቡበ ኢትዮጵያ ክልል በጅንካ ከተማ የሄሞራጅከ ፊቨር (Viral ...
11/15/2025

" የበሽታዉ መንስኤ ማርበርግ ቫይረስ (Marburg Virus) መሆኑን መለየት ተችሏል " - ጤና ሚኒስቴር

የጤና ሚኒስቴር በደቡበ ኢትዮጵያ ክልል በጅንካ ከተማ የሄሞራጅከ ፊቨር (Viral Hemorragic Fever) በሽታ መከሰቱን እና የበሽታዉን ምንነት በማረጋገጥ ላይ መሆኑን መግለጹ ይታወቃል፡፡

ሚኒስትሩ በዛሬው ዕለት ባወጣው መግለጫ የበሽታዉ መንስኤ ማርበርግ ቫይረስ (Marburg Virus) መሆኑን መለየት ተችሏል ብሏል።

የዘረመል ምርመራው የተከናወነው በኢትዮጵያ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ብሄራዊ ሪፈረንስ ላብራቶሪ ነው።

መግለጫው "በዚህም የዘረመል ምርመራ በአሁኑ ሰዓት ኢትዮጵያ ውስጥ የተገኘዉ ቫይረስ ሌሎች ምስራቅ አፍሪካ ሃገራት ላይ ከዚህ በፊት ከተከሰቱት ጋር ተመሳሳይ ዝርያ ያለዉ መሆኑ ታዉቋል" ነው ያለው።

በተጨማሪም በዛሬው እለትም አዲስ የበሽታውን ምልክት ያሳየ ወይም በቫይረሱ የተጠረጠረ ሰው ያልተገኘ መሆኑን ሚኒስትሩ ያሳወቀ ሲሆን በአሁኑ ሰዓት የተለያዩ የሙያ ስብጥር ያካተተ ከፍተኛ ፈጣን ምላሽ ሰጭ ቡድን ወደ ከልሉ በመላከ በሽታዉን የመከላከል እና የመቆጣጠር ስራዎች እየተሰሩ ይገኛሉ ብሏል።

ከነዚህም ውስጥ :-

° የማህበረሰብ አቀፍ የቅኝት ስራዎች፣

° በቫይረሱ የተያዙ ሰዎችን ለይቶ ማከም፣

° የማህበረሰብ ግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎች እና ከተጠረጠሩ ሰዎች ጋር ንክኪ ያላቸዉን ሰዎች የመለየት ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ተገልጿል።

በሃገር አቀፍ እንዲሁም በክልል ደረጃ የሕብረተሰብ ጤና አደጋዎች የክስተት አስተዳደር ስርዓት (Incident Management System) ተቋሞ የፈጣን ምላሽ ስራዎችን በማስተባበር ላይ ይገኛል ተብሏል።

ጤና ሚኒስቴር:-

➢ ከጤና ሚኒስቴር እና ከኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የሚተላለፉ መረጃዎችንና የጥንቃቄ መልዕክቶችን መከታተልና መተግበር፣

➢ የበሽታው ምልከት የሆኑትን በአፍ፣አፍንጫ እና ሌሎች የሰውነት ክፍሎች የመድማት፣ትኩሳት፣ማስቀመጥ እና ማስመለስ ምልከት ሲኖር ወደ ህክምና ተቋማት መሄድና በወቅቱ የላቦራቶሪ ምርመራ ማድረግ፣

➢ ምልክት ከታየበት ማንኛዉም ሰዉ ጋር ንክኪ በሚኖርበት ግዜ ራስን የመከላከያ ዘዴዎችን መጠቀም፣

➢ ሁልጊዜ እጅን በውሃና ሳሙና መታጠብ ወይም በሳኒታይዘር ማጽዳት እንደሚያስፈልግ አሳስቧል።

ማንኛውም ጤና ተቋም ለታካሚዎች ልየታ ልዩ ትኩርት በመስጠት የማርበርግ በሽታ (Marburg viral disease) መሰል በሸታ መለየት፣ ማከም እና በአፋጣኝ ሪፖርት ማድረግ እንደሚያስፈልግም በመግለጫው ጠቁሟል።

ታማኝ በየነ ስለ ጌትነት እንየው ምን አለ? | የልብ ወዳጆቹ ምስክርነት | የጌትነት በእንባ የተሞላው ንግግሩ |Getenet Eneyew Atta
11/13/2025

ታማኝ በየነ ስለ ጌትነት እንየው ምን አለ? | የልብ ወዳጆቹ ምስክርነት | የጌትነት በእንባ የተሞላው ንግግሩ |Getenet Eneyew Atta

ታማኝ በየነ ስለ ጌትነት እንየው ምን አለ? | የልብ ወዳጆቹ ምስክርነት | የጌትነት በእንባ የተሞላው ንግግሩ |Getenet Eneyew Atta| Ethiopia Subscribe to our channel Amharic Tube and enjoy Ethiop...

በዛሬው ዕለት የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ ሹመታቸው የጸደቀላቸው አቶ ጥራቱ በየነ፤ በከተማይቱ ያሉ የሰላም እና ጸጥታ ተቋማትን “ማጠናከር” እንዲሁም አረንጓዴ ቦታዎች እና መሰረተ ልማትን “ማስፋፋ...
11/12/2025

በዛሬው ዕለት የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ ሹመታቸው የጸደቀላቸው አቶ ጥራቱ በየነ፤ በከተማይቱ ያሉ የሰላም እና ጸጥታ ተቋማትን “ማጠናከር” እንዲሁም አረንጓዴ ቦታዎች እና መሰረተ ልማትን “ማስፋፋት” የትኩረት አቅጣጫቸው እንደሆነ ገለጹ።

አዲሱ ከንቲባ ሳምንቱን ሙሉ ለ24 ሰዓት ስራዎችን የማከናወን ባህልን ወደ ሀዋሳ ከተማ በማምጣት ተግባራዊ ማድረግ እንደሚፈልጉም አስታውቀዋል።

አቶ ጥራቱ የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ ሆነው የተሾሙት፤ ዛሬ ረቡዕ ህዳር 3፤ 2018 በተካሄደ የከተማይቱ ምክር ቤት አስቸኳይ ጉባኤ ላይ ነው።

የአዲሱ ከንቲባ ሹመት እንዲጸድቅ ለምክር ቤቱ ያቀረቡት፤ የሲዳማ ክልል የብልጽግና ፓርቲ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አብርሃም ማርሻሎ ናቸው።

ምክር ቤቱ ለሁለተኛ ጊዜ የሀዋሳ ከተማን በከንቲባነት ለመምራት በዕጩነት የቀረበሉትን የአቶ ጥራቱን ሹመት ያጸደቀው በሙሉ ድምጽ መሆኑን ምንጮች ገልጸዋል።

አዲሱ ከንቲባ ሹመታቸው መጽደቁን ተከትሎ ለምክር ቤቱ አባላት ባደረጉት ንግግር፤ የሀዋሳ ከተማን በሀገር አቀፍ እና በአህጉር ደረጃ “ተመራጭ የመኖሪያ፣ የቱሪዝም እና የኮንፍረንስ ከተማ ለማድረግ” “ከፍ ያለ ራዕይ” መሰነቃቸውን ተናግረዋል።

በ  #ጅንካ ከተማ ምንነቱ በመረጋገጥ ላይ ያለ ሄሞራጂክ ፊቨር በሽታ ተከሰተ፤ ስምንት ሰዎች በበሽታው ተጠርጥረዋል ተብሏል በደቡበ ኢትዮጵያ ክልል በጅንካ ከተማ ምንነቱ በመረጋገጥ ላይ ያለ ...
11/12/2025

በ #ጅንካ ከተማ ምንነቱ በመረጋገጥ ላይ ያለ ሄሞራጂክ ፊቨር በሽታ ተከሰተ፤ ስምንት ሰዎች በበሽታው ተጠርጥረዋል ተብሏል

በደቡበ ኢትዮጵያ ክልል በጅንካ ከተማ ምንነቱ በመረጋገጥ ላይ ያለ የሄሞራጂክ ፊቨር (Hemorrhagic Fever) በሽታ መከሰቱን የጤና ሚኒስቴርና የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት አስታወቁ።

የጤና ሚኒስቴርና የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት በጋራ ባወጡት መግለጫ፣ እስካሁን ድረስ ስምንት ሰዎች በበሽታው እንደተጠረጠሩ ገልፀዋል።

መግለጫው፣ ከከልሉ ጤና ቢሮ ጋር በመሆን በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የተመዘገበውን ይህንን የበሽታ መንስኤ ለማወቅ እና ተጨማሪ ስርጭትን ለመግታት እንዲሁም ለመቆጣጠር ፈጣን ምላሽ ሰጪ ቡድን ወደቦታው በመላክ የመስክ ግምገማዎች እና የላብራቶሪ ምርመራዎችን እያከናወነ መሆኑን ገልጿል።

በተጨማሪም የማህበረሰብ ቅኝት፣ የንከኪ ልየታ፣የቤት ለቤት ልየታ እንዲሁም የህክምና አገልግሎት አሰጣጥን እያጠናከረ ይገኛል ብሏል።

በመሆኑም መላዉ ሕብረተሰባችንና የሚመለከታቸዉ የባለድርሻ አካላት ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ሌላ ተጨማሪ መግለጫ እስከሚሰጥ ድረስ፤ ለመከላከል የሚከተሉትን ምከረ-ሃሳቦች እና ጥንቃቄዎች ተግባራዊ እንዲያደርጉ አስስቧል።

በአፍ፣አፍንጫ እና ሌሎች የሰውነት ከፍሎች የመድማት፣ትኩሳት፣ማስቀመጥ እና ማስመለስ ምልክት ሲኖር ወደ ህክምና ተቋማት መሄድና በወቅቱ የላቦራቶሪ ምርመራ ማድረግ እንደሚገባም አስገንዝቧል።

በተጨማሪም፣ ምልክት ከታየበት ማንኛዉም ሰዉ ጋር ንክኪ በሚኖርበት ጊዜ ራስን የመከላከያ ዘዴዎችን መጠቀም፣ ሁልጊዜ እጅን በሳኒታይዘር ወይም በውሃና በሳሙና በመታጠብ ማጽዳት አስፈላጊ ነው ተብሏል።

11/12/2025

Address

Santa Monica, CA
90403

Opening Hours

Monday 9am - 6pm
Tuesday 9am - 6pm
Wednesday 9am - 6pm
Thursday 9am - 6pm
Friday 9am - 6pm

Telephone

+13105709291

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when AmharicTube posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to AmharicTube:

Share