AmharicTube

AmharicTube Amharic Tube Ethiopian movies, press conference and news
(1)

ኢትዮፒካር (ETIOPIKAR) የአፍሪካ የአመራርና የተቋማት ሽልማትን ማሸነፉን ተከትሎ ልዩ የበዓል ቅናሽ ይፋ አደረገ።በኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች አስመጪነትና በኤክስፖርት ዘርፍ የተሰማራው ኢ...
12/26/2025

ኢትዮፒካር (ETIOPIKAR) የአፍሪካ የአመራርና የተቋማት ሽልማትን ማሸነፉን ተከትሎ ልዩ የበዓል ቅናሽ ይፋ አደረገ።

በኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች አስመጪነትና በኤክስፖርት ዘርፍ የተሰማራው ኢትዮፒካር፣ በ20ኛው "ግራንድ አፍሪካ የአመራርና የተቋማት ሽልማት" ላይ በምርጥ ተቋማዊ አፈፃፀም ሽልማት ተሸላሚ ሆኗል።

ኩባንያው ይህንን ስኬት በማስመልከትም ለደንበኞቹ እስከ ጥምቀት በዓል የሚቆይ ልዩ የዋጋ ቅናሽ እና የብድር አመቻች መርሃ-ግብር ይፋ አድርጓል።

ባለፈው ሳምንት በአድዋ መታሰቢያ ሙዚየም "ትጉኃንን እንሸልማለን" በሚል መሪ ቃል በተካሄደው የሽልማት ስነ-ስርዓት ላይ፣ ተቋሙ በሦስት የተለያዩ ዘርፎች እውቅናን አግኝቷል።

በዚሁ መሰረት የድርጅቱ መስራችና ባለቤት አቶ ሳሙኤል አዲስአለም በከፍተኛ አመራር ዘርፍ ሲሸለሙ፣ አቶ ኤፍሬም ታደለና አቶ ሴና ጌትነት በመካከለኛ አመራር ዘርፍ የላቀ አፈፃፀም ላሳዩ መሪዎች የሚሰጠውን ሽልማት ተቀብለዋል።

ኩባንያው የተገኘውን እውቅና ለደንበኞቹ ለማካፈል ባዘጋጀው መርሃ-ግብር፤ ከገና እስከ ጥምቀት በዓል ድረስ በኤሌክትሪክ መኪኖች ሽያጭ ላይ ከፍተኛ ቅናሽ ማድረጉን ገልጿል።

በተለይም መኪና መግዛት ለሚፈልጉ ግለሰቦች እና ድርጅቶች 50 በመቶ የቅድመ ክፍያ በመክፈል፣ ቀሪውን 50 በመቶ ከተለያዩ ባንኮች እና የፋይናንስ ተቋማት ጋር በመተባበር በሚመቻች ብድር መውሰድ የሚችሉበትን አሰራር መዘርጋቱን አስታውቋል።

በፈረንጆቹ 2013 ዓ.ም. የቀድሞ የባንክ ባለሙያ በሆኑት በአቶ ሳሙኤል አዲስአለም የተመሰረተው "ሳሙኤል አዲስአለም አስመጪ እና ላኪ"፤ በአሁኑ ወቅት በዩናይትድ አረብ ኤምሬትስ እና በአዲስ አበባ ቅርንጫፎቹን በመክፈት በስፋት እየተንቀሳቀሰ ይገኛል።

ተቋሙ በኢትዮፒካር (ETIOPIKAR) መለያ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን ወደ ሀገር ውስጥ ከማስገባት ባለፈ፣ በቡና፣ በቅባት እህሎች እና በፍየል ስጋ ኤክስፖርት ዘርፍ በመሰማራት ለሀገር የውጭ ምንዛሬ ግኝት የድርሻውን እየተወጣ እንደሚገኝ ተገልጿል።

ይህ ልዩ የሽያጭ እና የብድር ዕድል ደንበኞች ዘመናዊ እና ለአካባቢ ጥበቃ ተስማሚ የሆኑ የኤሌክትሪክ መኪኖችን በቀላሉ እንዲያገኙ ዓላማ ያደረገ መሆኑን ኩባንያው አክሎ ገልጿል።

ዛሬ በጣም ነው የተሸወድኩት" ተሸውጄ አላቅም " | ውቅሮ ነው የመጣሁት | አርቲስት ኪሮስ ሃ/ስላሴ ሙሉውን ቪዲዬ ለመመልከት ከታች ያለውን ሊንክ ይጫኑ👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👍👍
12/26/2025

ዛሬ በጣም ነው የተሸወድኩት" ተሸውጄ አላቅም " | ውቅሮ ነው የመጣሁት | አርቲስት ኪሮስ ሃ/ስላሴ
ሙሉውን ቪዲዬ ለመመልከት ከታች ያለውን ሊንክ ይጫኑ
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👍👍

"ዛሬ በጣም ነው የተሸወድኩት" ተሸውጄ አላቅም " | ከውቅሮ ነው የመጣሁት | አርቲስት ኪሮስ ሃ/ስላሴ Subscribe to our channel Amharic Tube and enjoy Ethiopian daily news, Ethiopian movies, ...

" የማህበራዊ ሚዲያ ' አንቂ ነን ' ባዮችን አልታገስም " - የአዲስ አበባ ፖሊስየአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያም የማህበራዊ ሚዲያን በመጠቀም ሙያዊ ክብርን የሚያዋርዱ፣ ከህብረተሰቡ ባ...
12/17/2025

" የማህበራዊ ሚዲያ ' አንቂ ነን ' ባዮችን አልታገስም " - የአዲስ አበባ ፖሊስ

የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያም የማህበራዊ ሚዲያን በመጠቀም ሙያዊ ክብርን የሚያዋርዱ፣ ከህብረተሰቡ ባህል፣ እምነትና ሞራል ተቃራኒ የሆኑ መልዕክቶችን ሲያስተላልፉ የነበሩ " የማህበራዊ ሚዲያ አንቂ ወይም ይዘት ፈጣሪዎች ነን " (Social Media Influencers and Content Creators) የሚሉ አራት ግለሰቦችን በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ እያጣራ ይገኛል፡፡

የመጀመሪያዎቹ ተጠርጣሪዎች ዛሀራ መሀመድና ፈቲያ ኤልያስ የተባሉ ነዋሪነታቸው በቦሌ ክ/ከተማ ወረዳ 12 ልዩ ቦታው ቦሌ ቡልቡላ ሲሆን የቲክቶክ ፕላትፎርምን በመጠቀም የሀገሪቱን ባህል፣ ወግ፣ እምነትና ሞራል በማይመጥን መልኩ "Illuminant" ወይም " የሠይጣን ማህበርተኞች አባላት ነን እኛን ምሰሉ፤ በርካታ ገንዘብ ታገኛላችሁ" የሚሉ መልዕክቶችን ሲያስተላልፉ በቁጥጥር ስር ውለዋል፡፡

ሦስተኛው ተጠርጣሪ ደግሞ ለታ ደረጄ ተረፋ የተባለ ነዋሪነቱ በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክ/ከተማ ወረዳ 04 ልዩ ቦታው ጀሞ ሦስት የሆነ " የተከበረውን የመምህርነት ሙያና የመምህራንን ክብር በሚያንቋሽሽ መልኩ" ተንቀሳቃሽ ምስሎችን እየሰራ በቲክቶክ ፕላትፎርም ሲያሰራጭ በቁጥጥር ስር ሊውል ችሏል።

ተጠርጣሪው በሚለቃቸው ተንቀሳቃሽ ምስሎች የተማሪ የደንብ ልብስ ለብሶ የመማሪያ ወንበሮች ላይ ቆሞ መጨፈር፣ በመምህራን ላይ የማሾፍ፣ ከተማሪ ኪስ ገንዘብ የመስረቅና የመሳሰሉ ይዘቶችንም ይሰራ እንደነበር ፖሊስ አረጋግጧል፡፡

አራተኛው ተጠርጣሪ ኤዶም ሚሊዮን ሲሆን ነዋሪነቱ በቂርቆስ ክ/ከተማ ወረዳ 10 ልዩ ቦታው ካምቦሎጆ እንዲሁም የሽመልስ ሀብቴ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪ ሲሆን እርሱም የቲክቶክ ፕላትፎርምን በመጠቀም ከወገቡ በላይ ልብሱን በማውለቅና ራቁቱን በመሆን "ሰግጥ ፈምስ" በማለት በየመንገዱ ህብረተሰቡን የማስደንገጥ፣ ራቁቱን ምግብ በትሪ በመያዝ ህብረተሰቡን ካላጎረስኳችሁ የማለትና የማስደንገጥ ይዘቶችን ሲሰራ በቁጥጥር ስር ውሏል፡፡

ፖሊስ በቁጥጥር ስር በዋሉ ግለሰቦች ወይም " የማህበራዊ ሚዲያ አንቂ ወይም ይዘት ፈጣሪዎች ነን" (Social Media Influencers and Content Creators) በሚሉ ግለሰቦች ላይ ተገቢውን የወንጀል ምርመራ ስራ የጀመረ ሲሆን በቀጣይም ተመሳሳይ ድርጊት ውስጥ የሚገቡ የማህበራዊ ሚዲያ "አንቂ ነን" ባዮችን እንደማይታገስም የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ያሳስባል፡፡

"ይህቺ ምድር የፈተና ዓለም ናት" ኡስታዝ አቡበከር አህመድ | USTAZ ABUBAKER AHMED
12/15/2025

"ይህቺ ምድር የፈተና ዓለም ናት" ኡስታዝ አቡበከር አህመድ | USTAZ ABUBAKER AHMED

"ይህቺ ምድር የፈተና ዓለም ናት" ኡስታዝ አቡበከር አህመድ | USTAZ ABUBAKER AHMED Subscribe to our channel Amharic Tube and enjoy Ethiopian daily news, Ethiopian movies, Ethiop...

12/13/2025

ከዛሬ ጀምሮ
“ወደ ማዶ”
ኮሜዲ ቴአትር
በዱባይ December 13th Crown plaza Hotel
በሻርጃ. December 14th Expo center
በአቡድሃቢ. December 21 Folklore and Theater Society

መድረክ ላይ መቅረብ ይጀምራል።

" ከሁለትኛ ክፍል ጀምሮ የተ.ደ.ፈ.ረው ህፃን " አሳዛኙ ታሪክ | Ethiopia
12/12/2025

" ከሁለትኛ ክፍል ጀምሮ የተ.ደ.ፈ.ረው ህፃን " አሳዛኙ ታሪክ | Ethiopia

" ከሁለትኛ ክፍል ጀምሮ የተ.ደ.ፈ.ረው ህፃን " አሳዛኙ ታሪክ | Ethiopia Subscribe to our channel Amharic Tube and enjoy Ethiopian daily news, Ethiopian movies, Ethiopian dr...

ሜሮን መብራህቱ የተባለች ወጣትን የገደለው ወንጀለኛ በእድሜ ልክ ፅኑ እስራት ተቀጣ።የፍርድ ውሳኔው ከሦስት ዓመት በላይ ጊዜ ፈጅቷል።የ23 ዓመቷ ሜሮን መብራህቱ የካቲት 18 /2015 ዓ.ም ...
12/11/2025

ሜሮን መብራህቱ የተባለች ወጣትን የገደለው ወንጀለኛ በእድሜ ልክ ፅኑ እስራት ተቀጣ።

የፍርድ ውሳኔው ከሦስት ዓመት በላይ ጊዜ ፈጅቷል።

የ23 ዓመቷ ሜሮን መብራህቱ የካቲት 18 /2015 ዓ.ም በመቐለ የአውቶቡስ መናሃሪያ አከባቢ ነው በባጃጅ ተገድላ ተጥላ የተገኘችው።

በግድያው ተጠርጥሮ ክስ የተመሰረተበት በላይ ፀጋይ የተባለ ግለሰብ ነው።

ጉዳዩን የያዘው የመቐለ ማእከላዊ ፍርድ በወጣት ሜሮን መብራህቱ ግድያ የተከሰሰውን ግለሰብ ወንጀለኛነቱን አረጋግጦ ዛሬ ሀሙስ ታህሳስ 2/2018 ዓ.ም የፍርድ ውሳኔ ሰጥቷል።

ወንጀለኛው ግለሰብ ግድያውን ጨለማን ተገን በማድረግ መፈፀሙ የተገለጸ ሲሆን ይህ የጭካኔ ድርጊቱ አልበቃ ብሎት የፈጸመውን እኩይ ተግባሩን ለመደበቅ ጥረት ማድረጉ የፍርድ ቅጣቱን ከባድ አድርጎታል።

ፍርድ ቤቱ ግለሰቡን በእድሜ ልክ ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ወስኗል።

ይህ የፍርድ ውሳኔ የተላለፈው ከሦስት ዓመት በላይ ጊዜ ከወሰደ በኋላ ነው።

" አምስቱ ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር በዋሉበት የወንጀል ጉዳይ ጋር በተያያዘ ነው በቁጥጥር ስር ያዋልኩት " - ፖሊስየኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ አዶናይ ብርሃነ ሀ/ሚካኤል የተባለ ተጠርጣሪን በ...
12/10/2025

" አምስቱ ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር በዋሉበት የወንጀል ጉዳይ ጋር በተያያዘ ነው በቁጥጥር ስር ያዋልኩት " - ፖሊስ

የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ አዶናይ ብርሃነ ሀ/ሚካኤል የተባለ ተጠርጣሪን በቁጥጥር ሥር አውሎ ምርመራ እያጣራ መሆኑን ገልጿል።

" አዶናይ ብርሃነ ሀ/ሚካኤል በቁጥጥር ሥር ሊውል የቻለው ‎ከኢትዮጵያ ሕዝብ ባህል እና መልካም ሥነ-ምግባር በተቃራኒ በሕዝብ ዘንድ ተቀባይነት የሌለው አስነዋሪ አለባበስ ለብሰው በአደባባይ እና በቴሌቪዥን ቀጥታ ስርጭት የታዩት አምስት ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር በዋሉበት የወንጀል ጉዳይ ጋር በተያያዘ ነው " ሲል ፖሊስ አስታውቋል።

" ዕውቅና እና ገንዘብ ለማግኘት ብቻ በማሰብ ሚዲያዎችን ኃላፊነት በጎደለው አኳሃን እየተጠቀሙ በተለይ ወጣቱ ትውልድ በመልካም ሥነ ምግባር ተቀርጾ ሀገርን የሚጠቅሙ ተግባራትን እንዳያከናውንና በተቃራኒው በትውልዱ ላይ ርካሽ ባህል ለመጫን የሚደረገው ተግባር ለመከላከል የጀመርኩትን ምርመራ አጠናክሬ እቀጥላለሁ " ሲል ፖሊስ አስታውቋል።

“አዲስ_አበባ ለተከራዮች በጣም ውድ ከተማ”  በ2025 ለተከራዮች በጣም ውድ ከሆኑ 10 የ  #አፍሪካ ከተሞች መካከል አንዷ ሆነችአዲስ አበባ በ2025 ዓ.ም. ማብቂያ ላይ ከፍተኛ የቤት ኪራ...
12/10/2025

“አዲስ_አበባ ለተከራዮች በጣም ውድ ከተማ”

በ2025 ለተከራዮች በጣም ውድ ከሆኑ 10 የ #አፍሪካ ከተሞች መካከል አንዷ ሆነች

አዲስ አበባ በ2025 ዓ.ም. ማብቂያ ላይ ከፍተኛ የቤት ኪራይ ከሚያስከፍሉ አስር የአፍሪካ ከተሞች መካከል መመደቧን ቢዝነስ ኢንሳይደር ዓለም አቀፍ የኦንላይን ዳታቤዝ የሆነውን የኑምቤኦ (Numbeo) መረጃን ዋቢ በማድረግ ዘግቧል።

ቢዝነስ ኢንሳይደር አፍሪካ በዘገባው የአዲስ አበባ ከተማ የኪራይ መረጃ ጠቋሚ 22 ሆኖ የተመዘገበ ሲሆን በዓለም አቀፍ ደረጃ 202ኛ ላይ ተቀምጣለች። በዚህም ለመኖሪያ ቤት ተከራዮች በአህጉሪቱ በጣም ውድ ከሆኑ ከተሞች መካከል አንዷ እንድትሆን አድርጓታል ብሏል።

ከአዲስ አበባ በመቀጠል የደቡብ አፍሪካዋ ኬፕ ታውን ከተማ የኪራይ መረጃ ጠቋሚ 21 (ዓለም አቀፍ ደረጃ 218) ሆኖ ሲመዘገብ ኪጋሊ ደግሞ በ16 የኪራይ መረጃ ጠቋሚ (ዓለም አቀፍ ደረጃ 264) ተቀምጣለች።

ቢዝነስ ኢንሳይደር እንደዘገበው ከሆነ፣ በዚህ ዓመት የቤት ኪራይ ዋጋ መጨመር በአፍሪካ ከተሞች ለሚኖሩ ነዋሪዎች ዋና ፈተና ሆኗል። ከፍተኛ የመኖሪያ ቤት ወጪዎች ግለሰቦችን እና ቤተሰቦችን ራቅ ወዳለ የከተማ ዳርቻዎች እንዘዋወሩ እያስገደደ መሆኑን የገለጸው ዘገባው፣ ይህም የትራንስፖርት ወጪን መጨመር፣ የጉዞ ጊዜን ማርዘም እና ምርታማነትን መቀነስ ያስከትላል ብሏል። በተለይም ዝቅተኛና መካከለኛ ገቢ ያላቸው ቤተሰቦች በእጅጉ ተጎድተዋል ሲልም አክሏል።

በተመሳሳይ የንግድ ቤቶች ኪራይ መጨመርም በአነስተኛና መካከለኛ ንግዶች ላይ ከፍተኛ ጫና አሳድሯል ተብሏል።

Addisstandard

ወላጆች ንቁ ልጆቻችሁን ጠብቁ "ያለሽ መስሎሻ ተበልተሸ አልቀሻል" ሊቀ ትጉሃን ደረጀ ነጋሽ ሙሉውን ቪዲዬ ለመመልከት ከታች ያለውን ሊንክ ይጫኑ👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👍👍👍
12/10/2025

ወላጆች ንቁ ልጆቻችሁን ጠብቁ "ያለሽ መስሎሻ ተበልተሸ አልቀሻል" ሊቀ ትጉሃን ደረጀ ነጋሽ
ሙሉውን ቪዲዬ ለመመልከት ከታች ያለውን ሊንክ ይጫኑ
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👍👍👍

ወላጆች ንቁ ልጆቻችሁን ጠብቁ "ያለሽ መስሎሻ ተበልተሸ አልቀሻል" ሊቀ ትጉሃን ደረጀ ነጋሽ | Ethiopia Subscribe to our channel Amharic Tube and enjoy Ethiopian daily news, Ethiopian movies...

🟡ለውድ ተመልካቾቻችን እና ተከታታዮቻችን፡-🏷ከአሻም ሚዲያ ትሬዲንግ አክሲዮን ማህበር በወቅታዊ ጉዳይ ላይ የተሰጠ  መግለጫድርጅታችን አሻም ሚዲያ ትሬዲንግ አክሲዮን ማህበር ጋዜጠኛ ሶፎንያስ ...
12/09/2025

🟡ለውድ ተመልካቾቻችን እና ተከታታዮቻችን፡-

🏷ከአሻም ሚዲያ ትሬዲንግ አክሲዮን ማህበር በወቅታዊ ጉዳይ ላይ የተሰጠ መግለጫ

ድርጅታችን አሻም ሚዲያ ትሬዲንግ አክሲዮን ማህበር ጋዜጠኛ ሶፎንያስ ዋሲሁን በኮንትራት ውል በዜና አቅራቢነት እንዲሁም በቅርቡ በጣቢያችን ‹‹ሶፊ ሾው›› ሲል በሰየመው የመዝናኛ ዝግጅቱ በአሻም የቴሌቪዥን እና በዩትዩብ ገፅ እያዘጋጀ ሲያቀርብ እንደነበረ ይታወቃል፡፡

ይህ በሆነበት ከትላንት ሕዳር 29 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በተለያዩ የማህበራዊ ሚድያ አማራጮች ስለ ጋዜጠኛው ከኢትዮጵያዊነት ባሕል፣ ወግ እንዲሁም ሃይማኖት ያፈነገጠ ተግባር ሲፈጽም የሚያሣይ መረጃ በድምጽ፣ በጽሁፍና በተንቀሳቃሽ ምስል ጭምር ሲዘዋወር ተመልክተናል፡፡

አሻም ይህንኑ በማህበራዊ ሚዲያ ስለ ጋዜጠኛው የተሰራጨውን መረጃ ተከትላ ስለ ተሰራጨበት መረጃ ሶፎኒያስን ማብራሪያ እንዲሰጥበት ጠይቃለች፡፡ በዚህም ሶፎኒያስ የሚል አጭር ምላሽ ከመስጠት ውጭ ተጨማሪ ያለው ነገር የለም።
ስለሆነም አሻም ሚድያ ትሬዲንግ አ.ማ. የኢትዮጵያን ባህል እና ወግ እንዲሁም የህብረተሰቡን እሴት እና ሃይማኖት ያከበረ የምትመራበት ኤዲቶሪያል አላት፡፡ ይሁን እንጂ ጋዜጠኛው የሚዲያውን ኤዲቶሪያልም ሆነ የማህበረሰቡን እምነት ፣ እሴት፣ ወግ፣ ባህልና ሃይማኖት የሚጻረር ተግባር ተሰራጭቶበት በመመልከቷ እጅጉን እያዘነች ድርጊቱ የሚዲያ ተቋሟን የማይወክል ይልቁንም በጽኑ የምታወግዘው መሆኑን ለውድ ተመልካቾቻችን እና ተከታታዮቻችን ለመግለጽ እንወዳለን፡፡

ከዚህም በተጨማሪ አሻም ሚዲያ ትሬዲን አክሲዮን ማህበር ጋዜጠኛ ሶፎኒያስ ዋሲሁን በፈጸመው ከባድ የማህበረሰባዊ እሴት እና ኤዲቶሪያል ጥሰት ጭምር የነበራትን የስራ ውል ከዛሬ ሕዳር 30 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ማቋረጡዋን ለመግለጽ ትወዳለች፡፡

አሻም ለሁላችን!

"ሰብዓዊ መብት አሁን ላይ ያለ አይመስለኝም " ኮሜዲያን አዝመራው ሙሉሰው
12/08/2025

"ሰብዓዊ መብት አሁን ላይ ያለ አይመስለኝም " ኮሜዲያን አዝመራው ሙሉሰው

"ሰብዓዊ መብት አሁን ላይ ያለ አይመስለኝም " ኮሜዲያን አዝመራው ሙሉሰው | New Comedy | Comedian | Azmeraw Mulusew Ethiopia Subscribe to our channel Amharic Tube and enjoy Ethiopian ...

Address

Santa Monica, CA
90403

Opening Hours

Monday 9am - 6pm
Tuesday 9am - 6pm
Wednesday 9am - 6pm
Thursday 9am - 6pm
Friday 9am - 6pm

Telephone

+13105709291

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when AmharicTube posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to AmharicTube:

Share