06/16/2026
ፈረንሳይ ሴኔጋልን 3 ለ 1 አሸነፈች
************
በዓለም ዋንጫ የምድብ የመጀመሪያ ጨዋታ ፈረንሳይ ሴኔጋልን በማሸነፍ ጉዟዋን ጀምራለች። በኒው ጄርሲ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ኬሊያን ምባፔ ሁለት ግቦችን ሲያስቆጥር፣ ብራድሊ ባርኮላ አንድ ግብ አስቆጥሯል።
ኢብራሂም ምባየ የሴኔጋልን አንድ ግብ ያሰቆጠረ ተጫዋች ነው።
ሴኔጋል በመጀመሪያው 45 ደቂቃ የግብ ዕድሎችን በመፍጠርም ይሆን ጨዋታውን በመቆጣጠር የተሻለች ብትሆንም በ2ኛው ግማሽ በተወሰደባት ብልጫ ተሸንፋለች።
በጨዋታው ሁለት ግቦችን ያስቆጠርው ኬሊያን ምባፔ በ58 ግቦች የፈረንሳይ ብሔራዊ ቢድን የምንጊዜም ከፍተኛ ግብ አስቀጣሪነት ክብረ ወሰንን ከኦሊቬ ጅሩ ተረክቧል።
@ሀገሬ ቲቪ