AmharicTube

AmharicTube Amharic Tube Ethiopian movies, press conference and news
(1)

ፈረንሳይ ሴኔጋልን 3 ለ 1 አሸነፈች************በዓለም ዋንጫ የምድብ የመጀመሪያ ጨዋታ ፈረንሳይ ሴኔጋልን በማሸነፍ ጉዟዋን ጀምራለች።  በኒው ጄርሲ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ኬሊያን...
06/16/2026

ፈረንሳይ ሴኔጋልን 3 ለ 1 አሸነፈች
************

በዓለም ዋንጫ የምድብ የመጀመሪያ ጨዋታ ፈረንሳይ ሴኔጋልን በማሸነፍ ጉዟዋን ጀምራለች። በኒው ጄርሲ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ኬሊያን ምባፔ ሁለት ግቦችን ሲያስቆጥር፣ ብራድሊ ባርኮላ አንድ ግብ አስቆጥሯል።

ኢብራሂም ምባየ የሴኔጋልን አንድ ግብ ያሰቆጠረ ተጫዋች ነው።

ሴኔጋል በመጀመሪያው 45 ደቂቃ የግብ ዕድሎችን በመፍጠርም ይሆን ጨዋታውን በመቆጣጠር የተሻለች ብትሆንም በ2ኛው ግማሽ በተወሰደባት ብልጫ ተሸንፋለች።

በጨዋታው ሁለት ግቦችን ያስቆጠርው ኬሊያን ምባፔ በ58 ግቦች የፈረንሳይ ብሔራዊ ቢድን የምንጊዜም ከፍተኛ ግብ አስቀጣሪነት ክብረ ወሰንን ከኦሊቬ ጅሩ ተረክቧል።

@ሀገሬ ቲቪ

🔶ሰበር: አሜሪካ እና ኢራን ስምምነት ፈፀሙ አሜሪካ እና ኢራን ጦርነቱን ማስቆም የሚያስችል ስምምነት ላይ መድረሳቸው ታውቋል።አሸማጋይዋ ፓኪስታን እንደገለጸችው ስምምነቱ የፊታችን አርብ በስዊ...
06/15/2026

🔶ሰበር: አሜሪካ እና ኢራን ስምምነት ፈፀሙ

አሜሪካ እና ኢራን ጦርነቱን ማስቆም የሚያስችል ስምምነት ላይ መድረሳቸው ታውቋል።

አሸማጋይዋ ፓኪስታን እንደገለጸችው ስምምነቱ የፊታችን አርብ በስዊዘርላንድ ይፈረማል።

የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ከስምምነቱ በኋላ የሆርሙዝ የባህር ሰርጥ እንደሚከፈት አስታውቀዋል።

የኢራን ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በበኩላቸው ስምምነት መደረሱን ሲገልጹ፥ ስማቸው ያልተጠቀሰ ከፍተኛ የጦር መኮንን ደግሞ ስምምነቱን ለኢራን ድል ብለውታል።

ሊባኖስን ጨምሮ በየትኛው ግንባር ምንም አይነት ግጭትም ሆነ ጦርነትን ማስቆም፣ ተጨማሪ ጠብ አጫሪ ድርጊቶችን ማስወገድ፣ የአሜሪካን ጦር ከስፍራው ማስወጣት፣ የባህር ላይ መዕቀቡን ማንሳት፣ ኢራን ላይ የተጣለውን ማዕቀብ ማንሳት እና የኢራን መልሶ ግንባታ ዕቅዶች በስምምነቱ ተካተዋል ተብሏል።

ከስምምነቱ በኋላ ዓለም አቀፍ የአክሲዮን ገበያ ጭማሪ ማሳየቱም ታውቋል።

ከደሴ ወደ አዲስ አበባ ሲጓዝ በነበረ ተሽከርካሪ ላይ በደረሰ አደጋ የ28 ሰዎች ሕይወት አለፈከደሴ ወደ አዲስ አበባ ሲጓዝ በነበረ ተሽከርካሪ ላይ በደረሰ አደጋ የ28 ሰዎች ሕይወት ማለፉን ...
06/15/2026

ከደሴ ወደ አዲስ አበባ ሲጓዝ በነበረ ተሽከርካሪ ላይ በደረሰ አደጋ የ28 ሰዎች ሕይወት አለፈ

ከደሴ ወደ አዲስ አበባ ሲጓዝ በነበረ ተሽከርካሪ ላይ በደረሰ አደጋ የ28 ሰዎች ሕይወት ማለፉን ፖሊስ አስታውቋል።

አደጋው የደረሰው በዛሬው ዕለት ከደሴ እና ኮምቦልቻ ከተሞች መካከል በሚገኘው የሐረጎ መንገድ ላይ መሆኑም ነው የተገለጸው፡፡

በአደጋው ከሞቱት ሰዎች በተጨማሪም በርካታ ሰዎች ላይ ቀላልና ከባድ ጉዳት እንደደረሰባቸው ፖሊስ ገልጿል፡፡

የሕዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪው በግምት 100 ሜትር ጥልቀት ወዳለው ገደል ውስጥ መግባቱን አሚኮ ዘግቧል፡፡

በሕይወት የተረፉትን ወደ ሕክምና ቦታ ለማድረስ ርብርብ እየተደረገ ሲሆን፥ የአደጋው ምክንያት በመጣራት ላይ ይገኛል፡፡

ሰኔ 08/2018 ዓ.ም

ጥርስን እንደገና የሚያሳድገው መድሃኒት‼️ሳይንቲስቶች የሰው ልጆች በተፈጥሮ የጠፉ ጥርሶችን እንደገና እንዲያሳድጉ የሚያስችል መድሃኒት ፈጠሩ‼️በህክምና ምርምር ኢንስቲትዩት ኪታኖ ሆስፒታል በ...
06/14/2026

ጥርስን እንደገና የሚያሳድገው መድሃኒት‼️

ሳይንቲስቶች የሰው ልጆች በተፈጥሮ የጠፉ ጥርሶችን እንደገና እንዲያሳድጉ የሚያስችል መድሃኒት ፈጠሩ‼️

በህክምና ምርምር ኢንስቲትዩት ኪታኖ ሆስፒታል በዶ/ር ካትሱ ታካሃሺ የሚመራው የጃፓን ተመራማሪዎች የጥርስን ተፈጥሯዊ እድገት የሚያነቃቃ ፈር ቀዳጅ የሆነ መድሃኒት ፈጥረዋል። መድሃኒቱ የሚሠራው የጥርስን እድገት የሚከላከለውን ዩኤስኤግ-1 የተባለውን ፕሮቲን በመግታት ነው።

ይህ መድሃኒት በአይጦች ላይ ሙከራ ተደርጎ አዲስ-ጥርሶችን በተሳካ ሁኔታ በማሳደጉ የምርምር ቡድኑ አሁን ይህን ለውጥ የሚያመጣ ህክምና በአስር አመታት ውስጥ ወደ ገበያ ለማውጣት በሰዎች ላይ ክሊኒካዊ ሙከራዎችን ለመጀመር በዝግጅት ላይ ነው።

ኧረ ፋታ ስጡን?!   መንግስት ግን" ምን ሁኑ ?" ሊለን ነው :: አጀንዳ እየደራረበና እያፋጠነ በመስጠት የሚያወዛግበን !?   የነዳጅ ዋጋ ጭማሪው ወር አላስቆጠረም ::   በዚህ ምክንያት...
06/13/2026

ኧረ ፋታ ስጡን?!

መንግስት ግን" ምን ሁኑ ?" ሊለን ነው :: አጀንዳ እየደራረበና እያፋጠነ በመስጠት የሚያወዛግበን !?

የነዳጅ ዋጋ ጭማሪው ወር አላስቆጠረም :: በዚህ ምክንያት ጣሪያ የነካው የኑሮ ውድነት ናላውን ያዞረው ዜጋ ግራ በተጋባበት ስዐት መንጃ ፍቃድ እንደ አዲስ ትፈተናላችሁ አለና ክፍያ ያሳሰበውን ምድረ አሽከርካሪ አንጫጫው ::

ከኑሮ ውድነት ጋር በተያያዘ በጭንቀት የተሞላው ውክቢያ ሳይረግብ አስደንጋጭ የአዲስ ታርጋ ዋጋ ክፍያ አጀንዳ ተከተለ :: ምን ጉድ ነው !?

ዜጋው በእንዲህ ያለ ውክቢያ ግራ ሲጋባ : መንግስት ለዜጎች አሳቢ መስሎ " የመኖሪያ ቤት ኪራይ ዋጋን እኔ ነኝ የምወስነው" እያለን ነው ::

ሀሳቡ ባልከፋ :: ግን እሱ በየጊዜው የሚጨምረው የነዳጅ ዋጋና እሱን ተከትሎ የሚግተለተለው የኑሮ ውድነት ቤት እያከራየ የሚተዳደረውን ዜጋ እይመለከተውም ይሆን ?!

እንዲህ ማሰቡ ካልቀር ህዝቡም እንዲተሳሰብ እሱ የሚዘውረውን የጭማሪ ማርሽ ለምሳሌ በቤትና በይዞታ ላይ የሚጨመረውን የግብር ልክና መልክ ለምን አያየውም !? ( ልብ አድርጉ ገና የፕሮፐርቲ ታክስ ሊመጣ መሆኑም አይዘነጋም )::

ሌላው ቀርቶ እስከ ቅርብ ጊዜ የፈለከውን ይህል ጊዜ ቆመህ ለሰፈር ወጣቶች አስር በር ብቻ የምትከፍልበት ፓርኪንግ መንግስት ጣልቃ ሲገባበት በትንሹ 40 ብር ደርሷል :: አንድ ደቂቃ እንኳ ብታሳልፍ ደግሞ ተጨማሪ የምትከፍለው በመነሻው ዋጋ ልክ ነው :: መኪና መጠቀም የማይቻል በት ደረጃ እየተደረሰ መስሏል::

እንዲህ እንዲህ እያልን መካከለኛና ዝቅተኛ ገቢ ያለው ዜጋ የሚብከነከንበትን ብዙ ጉዳይ ማንሳት ይቻላል :: ግራ ገባን እኮ ጎበዝ !?
እባካችሁ ፉታ ስጡን?!

( ጋዜጠኛና የህግ ባለሙያ ሳሙኤል ፍቅሬ)

የቻይንኛ ቋንቋ ትምህርት በኢትዮጵያ የትምህርት ስርዓት ውስጥ ሊካተት ነው፡፡የቻይንኛ ቋንቋ ትምህርትን በቀጣይ አምስት ዓመታት በኢትዮጵያ ለማስተማር የሚያስችል የሁለትዮሽ ስምምነት ተፈፅሟል።...
06/12/2026

የቻይንኛ ቋንቋ ትምህርት በኢትዮጵያ የትምህርት ስርዓት ውስጥ ሊካተት ነው፡፡

የቻይንኛ ቋንቋ ትምህርትን በቀጣይ አምስት ዓመታት በኢትዮጵያ ለማስተማር የሚያስችል የሁለትዮሽ ስምምነት ተፈፅሟል።

የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ክንደያ ገብረሕይወት (ፕ/ር) እና በኢትዮጵያ የቻይና አምባሳደር ቺን ሃይ ስምምነቱን ተፈራርመዋል።

ስምምነቱ በሁለቱ አገራት መካከል እያደገ የሚገኘውን የባህል፣ የትምህርት እና የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ትብብር የበለጠ ለማጠናከር ያስችላል ተብሏል፡፡

የአማርኛ ቋንቋ ትምህርት በቻይና ዩኒቨርሲቲዎች እየተሰጠ መሆኑ የተገለፀ ሲሆን፤ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የኮንፊሽየስ ኢንስቲትዩት የቻይንኛ ቋንቋ ትምህርት ከሰርተፊኬት ስልጠና ጀምሮ እስከ 2ኛ ዲግሪ ፕሮግራም እንደሚያስተምር ይታወቃል፡፡

አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የቻይንኛ ቋንቋ ትምህርትን በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለማስፋፋት ከአዲስ አበባ እና ከኦሮሚያ ትምህርት ቢሮዎች ጋር በቅርቡ ስምምነት መፈፀሙ ይታወሳል።

አሜሪካ ሄዶ መውለድ ሊያከትም ነው፡ ከ200 በላይ ቪዛዎች ተሰርዘዋልየአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር  በምዕራብና ሰሜን አፍሪካ የሚንቀሳቀሱና «የወሊድ ቱሪዝም»  ላይ የተሰማሩ ህገ-ወጥ መረቦ...
06/11/2026

አሜሪካ ሄዶ መውለድ ሊያከትም ነው፡
ከ200 በላይ ቪዛዎች ተሰርዘዋል

የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በምዕራብና ሰሜን አፍሪካ የሚንቀሳቀሱና «የወሊድ ቱሪዝም» ላይ የተሰማሩ ህገ-ወጥ መረቦችን ማፍረሱን አስታወቀ። ሚኒስቴሩ ከ200 በላይ የውጭ ሀገር ዜጎችን በሀሰተኛ ሰነዶች በመጠቀምና የቪዛ «አስተላላፊዎችን» በማገዝ የአሜሪካን ቪዛ አግኝተዋል ሲል ከሷል። በኤክስ ማህበራዊ ገጹ ላይ ባወጣቸው ተከታታይ መግለጫዎች፣ ዋናው የጉዞ ዓላማቸው አሜሪካ ውስጥ በመውለድ ለልጆቻቸው የአሜሪካን ዜግነት በነፃ ለማግኘት የነበሩ ሰዎችን ቪዛ ሙሉ በሙሉ መሰረዙንና ይህ እርምጃ ሰፊው የቁጥጥር ዘመቻ አካል መሆኑን ገልጿል።

ይህንን መሰል ህገ-ወጥ ተግባራትን ለመለየትና ሙሉ በሙሉ ለማስቆም ከየሀገራቱ የአካባቢ ባለስልጣናት ጋር በቅንጅት እየሰራ መሆኑን የገለጸው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ ሆኖም ግን ጉዳዩ የሚመለከታቸውን የአፍሪካ ሀገራት ስም እስካሁን ይፋ አላደረገም። ይህ የአሜሪካ ጠንካራ እርምጃ በተለይም ወደ ሀገሪቱ ለመጓዝ የሚያስቡ ነፍሰጡር እናቶች ላይ የሚደረገውን የቪዛ ማጣሪያ ሂደት ይበልጥ እንደሚያጠብቀው ተገምቷል።

#የአሜሪካቪዛ #አስቸኳይመረጃ #የአፍሪካዜና #የቪዛክልከላ

አዲሱ ሰሌዳ እስከ 56,000 ብር ዋጋ ተቆርጦለታል የሚለው መረጃ እያነጋገረ ነው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አሽከርካሪና ተሽከርካሪ ፈቃድና ቁጥጥር ባለስልጣን ዛሬ መግለጫ እየሰጠ ነው።...
06/11/2026

አዲሱ ሰሌዳ እስከ 56,000 ብር ዋጋ ተቆርጦለታል የሚለው መረጃ እያነጋገረ ነው

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አሽከርካሪና ተሽከርካሪ ፈቃድና ቁጥጥር ባለስልጣን ዛሬ መግለጫ እየሰጠ ነው።ከመግለጫው ቀድሞ የወጣው ሰነድ ብዙዎችን እያነጋገረ ነው።

አዲስ የተሽከርካሪ ሰሌዳ (ታርጋ) መሸጫ ዋጋ እስከ 56000 ብር ዋጋ ተቆርጦለታል ይላል ሰነዱ። የቀረቡት ዋጋዎች የፊትና የኋላ ሰሌዳዎችን እንዲሁም ቫትን (VAT) ያካተቱ መሆናቸውም ተጠቁሟል።

አነጋጋሪ ነው በተባለው ሰነድ ለግል መገልገያ (የቤት)፣ ለንግድ፣ ለዲፕሎማት፣ ለዕርዳታ ድርጅቶች፣ ለዓለም አቀፍ ተቋማት እና ለልዩ ተንቀሳቃሽ ተሽከርካሪዎች፦
📌በነዳጅ የሚሰሩ ከሆነ፦ 56,000 ብር
📌 በኤሌክትሪክ እና በተፈጥሮ ጋዝ የሚሰሩ ከሆነ፦ 44,500 ብር
ለድንበር ተሻጋሪ የጭነት ትራንስፖርት ተሽከርካሪዎች፦
📌 በነዳጅ የሚሰሩ ከሆነ፦ 28,500 ብር
📌 በኤሌክትሪክ እና በተፈጥሮ ጋዝ የሚሰሩ ከሆነ፦ 15,200 ብር
ለሕዝብ ታክሲ ትራንስፖርት ተሽከርካሪዎች፦
📌 በነዳጅ የሚሰሩ ከሆነ፦ 11,700 ብር
📌በኤሌክትሪክ እና በተፈጥሮ ጋዝ የሚሰሩ ከሆነ፦ 9,400 ብር
ለከተማና የሀገር አቋራጭ አውቶቡስ፣ ለመንግሥት፣ ለአካል ጉዳተኛ (PD) እና ለባለሦስት እግር (ባጃጅ) ተሽከርካሪዎች፦
📌በነዳጅ የሚሰሩ ከሆነ፦ 9,400 ብር
📌 በኤሌክትሪክ እና በተፈጥሮ ጋዝ የሚሰሩ ከሆነ፦ 7,100 ብር
ለባለሁለት እግር (ሞተርሳይክል) ተሽከርካሪዎች፦
📌 በነዳጅ የሚሰሩ ከሆነ፦ 4,700 ብር
📌 በኤሌክትሪክ እና በተፈጥሮ ጋዝ የሚሰሩ ከሆነ፦ 3,550 ብር መሆኑን ከመግለጫው ቀድሞ የወጣው ሰነድ ያስረዳል።የመግለጫው ሙሉ ይዘት ከቆይታ በኋላ ይቀርባል

አሜሪካ በኢራን ላይ በከባድ ቦንቦች የታገዘ ድብደባ ማድረሷን ተከትሎ ኢራን የሆርሙዝ ወሽመጥ ሙሉ ለሙሉ መዝጋቷን አስታወቀችበአሜሪካ እና በኢራን መካከል ያለው ወታደራዊ ግጭት በከፍተኛ ሁኔታ...
06/11/2026

አሜሪካ በኢራን ላይ በከባድ ቦንቦች የታገዘ ድብደባ ማድረሷን ተከትሎ ኢራን የሆርሙዝ ወሽመጥ ሙሉ ለሙሉ መዝጋቷን አስታወቀች

በአሜሪካ እና በኢራን መካከል ያለው ወታደራዊ ግጭት በከፍተኛ ሁኔታ ማገርሸቱን ተከትሎ፣ የኢራን ወታደራዊ ዕዝ የዓለም የነዳጅ አቅርቦት ቁልፍ መተላለፊያ በሆነው የሆርሙዝ ወሽመጥ ላይ የነዳጅ ጫኝ መርከቦችንና የንግድ ትራፊክን ሙሉ በሙሉ መዝጋቱን አስታወቀ።

ኢራን ይህን አስቸኳይ እርምጃ የወሰደችው የአሜሪካ መከላከያ ሚኒስትር ፒት ሄግዝ አሜሪካ በኢራን ቁልፍ ተቋማት ላይ ጠንካራ የአየር ድብደባ ማድረሷን በይፋ ከገለጹ በኋላ ሲሆን አሁን ላይ ምንም ዓይነት መርከብ ቦታው ማለፍ አይችልም ብላለች። የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ትራምፕ ኢራን ስምምነቱን የማትቀበል ከሆነ በነገው ዕለት አይታው የማታውቀው ጥቃት እንፈፅማለን ሲሉ ዝተዋል።

የአሜሪካ መከላከያ ሚኒስትር ፒት ሄግዝ በፍሎሪዳ ከሚገኘው የአሜሪካ ማዕከላዊ ዕዝ ዋና መሥሪያ ቤት በሰጡት መግለጫ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ያስተላለፉትን ትዕዛዝ መሠረት በማድረግ የአሜሪካ ጦር በኢራን ውስጥ በሚገኙ ቁልፍ ወታደራዊ እና የስትራቴጂክ ተቋማት ላይ የቦምብ ድብደባ አካሂደናል ሲሉ አስታውቀዋል። ሚኒስትሩ ይህንን እርምጃ “ኢራን በቀጣናው በምታሳየው መተናኮስ እና በሰላም ድርድሩ ላይ በወሰደችው ግትር አቋም” ምክንያት የመጣ መሆኑን በመግለፅ ጥቃቱ በተሳካ ሁኔታ መከናወኑንና የኢራንን ወታደራዊ አቅም ለማዳከም የታለመ ነው ሲሉ ተናግረዋል።

ይህንን የአሜሪካን ድብደባ ተከትሎ የኢራን ኻታም አል-አንቢያ የተሰኘው ከፍተኛ ጥምር ጦር እዝ አስቸኳይ መግለጫ ያወጣ ሲሆን የሆርሙዝ ወሽመጥ ለማንኛውም ዓይነት የባህር ላይ ትራፊክ በተለይም ለነዳጅ ጫኝ እና ለንግድ መርከቦች ሙሉ በሙሉ ዝግ መሆኑን አስታውቋል።

እዙ አክሎም ትዕዛዙን ጥሶ ለመሻገር በሚሞክር በማንኛውም መርከብ ላይ ጦሩ ወታደራዊ እርምጃ ይወስዳል ሲል አስጠንቅቋል። የኢራን መንግስታዊ ሚዲያዎች በሆርሙዝ አቅራቢያ በነበሩ የአሜሪካ የጦር መርከቦች ላይ የ ሚሳኤልና የድሮን ጥቃት መሰንዘሩን የዘገቡ ቢሆንም የአሜሪካ ወታደራዊ ባለሥልጣናት ግን የተመታ መርከብ የለም በማለት አስተባብለዋል።

አሁን ላይ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለፍጆታ የሚውለው የድንጋይ ከሰልና የነዳጅ አቅርቦት አንድ አምስተኛው የሚሻገርበት የሆርሙዝ ወሽመጥ መዘጋት በዓለም የነዳጅ ገበያ ላይ ወዲያውኑ ከፍተኛ ጭማሪ አስከትሏል ሲል ለሮይተርስ ዘግቧል።

እንደ አዲስ የተከሰተው ይህ ወታደራዊ ግጭት ባለፈው ሚያዝያ ወር ላይ በሁለቱ ወገኖች መካከል ተደርሶ የነበረውን ደካማ የተኩስ አቁም ስምምነት ሙሉ በሙሉ ያፈረሰ ሲሆን የመካከለኛው ምስራቅ ቀጣና በሙሉ ወደ ከፋ የጦርነት ቀውስ ሊከተው እንደሚችል ዓለም አቀፍ ተንታኞች ስጋታቸውን እየገለጹ ይገኛሉ።

Maleda

አስቸኳይ የአፋልጉኝ እና የትብብር ጥሪ! * በአጎቷ የተጠለፈች ህፃን ሳምራዊት  * አባቷ እንግሊዝ ነው ያለው * የገዛ ወንድሜ ልጄን ይዞብኝ ጠፋ* አሁን 2 ሚሊዮን አምጣ እያለኝ ነው.......
06/10/2026

አስቸኳይ የአፋልጉኝ እና የትብብር ጥሪ!

* በአጎቷ የተጠለፈች ህፃን ሳምራዊት
* አባቷ እንግሊዝ ነው ያለው
* የገዛ ወንድሜ ልጄን ይዞብኝ ጠፋ
* አሁን 2 ሚሊዮን አምጣ እያለኝ ነው......

"ይህችን ጨቅላ ህጻን በፍጥነት ወደ እናቷ እቅፍ ለመመለስ ሁላችንም በጋራ እንፈልጋት፤ እባካችሁ መረጃው ለሁሉም እንዲደርስ ሼር (Share) በማድረግ ተባበሩን!"

በአንድ ግቢ ውስጥ (እሱ ፎቅ ላይ እሷ ምድር ቤት) በሚኖሩበት ወቅት፣ በደረሰ ከፍተኛ የደህንነት እክል የሕጻኗ እናት ንብረቶቿን (ወርቅ፣ ጥሬ ገንዘብ እና በባንክ አካውንት የነበረውን ጨምሮ) እና ስልኳን ተነጥቃለች።

ከሁሉም በላይ ግን እጅግ የምታሳዝነው የ 1 ዓመት ከ 9 ወር ልጇ ተወስዳባት አሁን ያለችበትን አቅጣጫ ለማወቅ ከፍተኛ ፍለጋ ላይ እንገኛለን።

የሕጻኗ እና ወቅታዊ መረጃ

የሕጻኗ ስም፦ ሳምራዊት ብሩክ
ዕድሜ፦ 1 ዓመት ከ 9 ወር
የመነሻ ቦታ፦ በሱሉልታ ሚዛን አካባቢ ከእናቷ ዘንድ ተወስዳ የተሰወረች ሲሆን፣

በቅርብ ሰዓት የተገኘው የጂፒኤስ መረጃ እና ጥቆማ እንደሚያመለክተው በደብረማርቆስ እና በደጀን አካባቢ እንደሚገኙ ሰፊ ፍንጭ ተገኝቷል።

አብረው ያሉ ግለሰቦች ከህጻኗ ጋር አብረው የተሰወሩት እና የምንፈልጋቸው ግለሰቦች፦

1. ስለሺ ለማ (አጎት)
2. እሌኒ ቢያዝ

የሕጻኗ አባት በዩናይትድ ኪንግደም (UK) የሚኖር መሆኑ ይታወቃል

ይህችን ህጻን ወይም ከላይ የተጠቀሱትን ግለሰቦች በደብረማርቆስ፣ በደጀንም ሆነ በማንኛውም አካባቢ ያየ፣ ወይም ያለችበትን ትክክለኛ አቅጣጫ የሚያውቅ ደግ ሰው ካለ ሰብአዊነትን በማስቀደም በአስቸኳይ

በሚከተሉት የፈላጊዎች (ሳራ ለማ እና ነብዩ ለማ) ስልክ ቁጥሮች በመደወል ያሳውቁን። ወይም በአቅራቢያችሁ ለሚገኝ የሕግ አካል/ፖሊስ በአካል በመሄድ ይጠቁሙ።
የመገናኛ ስልክ ቁጥሮች፦

* 0911179632 ሳራ ለማ
* 0911179633 ነብዩ ለማ

የሕጻኗን ደህንነት ለመታደግ እና የናፈቃትን የእናት እቅፍ እንድታገኝ እባካችሁ ይህንን መልዕክት ለሁሉም እንዲደርስ ሼር (Share) ያድርጉት!

@አባቷ ብሩክ ከUk

Address

Santa Monica, CA
90403

Opening Hours

Monday 9am - 6pm
Tuesday 9am - 6pm
Wednesday 9am - 6pm
Thursday 9am - 6pm
Friday 9am - 6pm

Telephone

+13105709291

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when AmharicTube posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to AmharicTube:

Share