AmharicTube

AmharicTube Amharic Tube Ethiopian movies, press conference and news

09/08/2026
በኢትዮጵያ ከ46 በመቶ በላይ የሚሆኑ ወጣቶች በሱስ ተጠቂ መሆናቸው ተነገረ::በኢትዮጵያ የወጣቶች የሱስ ተጠቃሚነት በከፍተኛ ደረጃ ላይ መድረሱን በቅርቡ የተደረገ አንድ ሀገራዊ ጥናት አመላክ...
09/07/2026

በኢትዮጵያ ከ46 በመቶ በላይ የሚሆኑ ወጣቶች በሱስ ተጠቂ መሆናቸው ተነገረ::

በኢትዮጵያ የወጣቶች የሱስ ተጠቃሚነት በከፍተኛ ደረጃ ላይ መድረሱን በቅርቡ የተደረገ አንድ ሀገራዊ ጥናት አመላክቷል።

በጥናቱ መሰረት ከ15 እስከ 24 በሚሆን የዕድሜ ክልል ዉስጥ የሚገኙ ወጣቶች የሱስ ተጠቂ መሆናቸዉ ተረጋግጧል ሲሉ በቅዱስ ጳዉሎስ ሆስፒታል የአእምሮ ህክምና ስፔሻሊስት የሆኑት ዶክተር አስካለማሪያም ቢክስ ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል ።

እንደ ዶክተር አስካለማሪያም ገለፃ በወጣቶች ዘንድ የአልኮል ተጠቃሚነት ሱስ ከፍተኛዉን ድርሻ ይይዛል ። ሲጓራ እና ጫትን ጨምሮ ለማስታገሻነት በጥንቃቄ የሚወሰዱ መድኃኒቶችን ወጣቶች ለሱስ እንደሚጠቀሙበት ተገልጿል ።

ወጣቶች ራሳቸዉን ከሱስ ለመጠበቅ እርስ በእርስ መረዳዳት ፣ጊዜያቸዉን ትርጉም ባላቸዉ ነገሮች ላይ ማሳለፍ ፣ስፖርት መስራት እና በሌሎች የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ላይ መሳተፍ እንዳለባቸዉ ተነግሯል።የሱስ ተጠቂነት የሚያስከትለው ጫና ቀላል አለመሆኑን የሚያስረዱት ስፔሻሊስቷ ተጋላጭ የሆኑ ሰዎች ለራሳቸዉ ቅድሚያ በመስጠት ህክምና ማድረግ እንዳለባቸዉ አስገንዝበዋል ።

ሱስ በአካል እንዲሁም በአእምሮ ላይ የሚያሳድረዉን ተፅዕኖ ሁሉም የማህበረሰብ ክፍል ተገንዝቦ ከመፈረጅ ይልቅ በዙሪያው ያሉ የሱስ ተጠቂዎች የህክምና አገልግሎት እንዲያገኙ ማድረግ ይኖርበታል ተብሏል ።

የአሜሪካ የግሪን ካርድ ሎተሪ ዕድለኞች የፍርድ ቤት ድል እና አዲስ እገዳየአሜሪካ ፌዴራል ፍርድ ቤት በኢትዮጵያና በሌሎች አፍሪካ ሀገራት የዲቪ ሎተሪ ዕድለኞች ላይ ተጥሎ የነበረውን ገደብ ው...
09/06/2026

የአሜሪካ የግሪን ካርድ ሎተሪ ዕድለኞች የፍርድ ቤት ድል እና አዲስ እገዳ

የአሜሪካ ፌዴራል ፍርድ ቤት በኢትዮጵያና በሌሎች አፍሪካ ሀገራት የዲቪ ሎተሪ ዕድለኞች ላይ ተጥሎ የነበረውን ገደብ ውድቅ በማድረግ ውሳኔ አሳለፈ።

በካሊፎርኒያ የፌዴራል ፍርድ ቤት ዳኛ ኤድዋርድ ዳቪላ የቪዛ ሂደቱን አግደው የነበሩ መመሪያዎችን በጊዜያዊነት እንዲቆሙ ወስነዋል።

ይህ ውሳኔ በዲቪ-2026 ፕሮግራም ከተመዘገቡት ከ53 ሺህ በላይ አፍሪካውያን መካከል ከ3 ሺህ በላይ የሚሆኑ ኢትዮጵያውያንን ጨምሮ 41 ሺህ የሚጠጉ አመልካቾች ተስፋ የፈነጠቀ ነው።

ሆኖም ይህን ፍትህ ተከትሎ የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት ከጸጥታ ስጋት ጋር በተያያዘ የቪዛ አሰጣጡን በድጋሚ ማገዱ አዳዲስ ስጋቶችን ፈጥሯል። አመልካቾች ሰነዶችን ማቅረብ እና ቃለ መጠይቅ ማድረግ ቢችሉም፣ መስከረም 20 ቀን 2018 ዓ.ም ከመጠናቀቁ በፊት ቪዛ ካልተሰጣቸው እድሉ ሊባክን ይችላል የሚል ስጋት አለ። የፍርድ ቤቱ ውሳኔ ህጋዊ እንቅፋቶችን ያስወገደ ቢሆንም፣ አዲሱ እገዳ ዕድለኞቹን ባለበት እንዲቆሙ አድርጓል።

በአዲስ ከተማ «ሸማ ተራ» ተከስቶ የነበረው የእሳት አደጋ በቁጥጥር ስር ውሏልበአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 «ሸማ ተራ» አካባቢ ተከስቶ  የነበረው ድንገተኛ የእሳት አደጋ ሙሉ በሙሉ በ...
09/05/2026

በአዲስ ከተማ «ሸማ ተራ» ተከስቶ የነበረው
የእሳት አደጋ በቁጥጥር ስር ውሏል

በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 «ሸማ ተራ» አካባቢ ተከስቶ የነበረው ድንገተኛ የእሳት አደጋ ሙሉ በሙሉ በቁጥጥር ስር መዋሉ ተገለጸ። የክፍለ ከተማው ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ወ/ሮ እቴማር ጌታቸው እንደገለጹት፤ አደጋውን በፍጥነት ለማጥፋት የእሳት አደጋ ሠራተኞችና የአካባቢው ነዋሪዎች ትልቅ ትብብር አድርገዋል።

በአሁኑ ወቅት የአደጋው መንስኤና የደረሰው የጉዳት መጠን እየተጣራ እንደሚገኝ የተገለፀ ሲሆን፣ የተደረገው ፈጣን ርብርብ አደጋው ወደ ሌሎች አካባቢዎች እንዳይስፋፋ አድርጓል።

ኢትዮጵያ በ83 ቢ. ብር ወጪ 16 ግዙፍ መርከቦችን ልትገዛ ነውኢትዮጵያ የውጪና የገቢ ምርቶቿን የሎጂስቲክስ አቅርቦት ለማቀላጠፍ በ83 ነጥብ 1 ቢሊዮን ብር ወጪ 16 አዳዲስ መርከቦችን ለመ...
09/05/2026

ኢትዮጵያ በ83 ቢ. ብር ወጪ 16
ግዙፍ መርከቦችን ልትገዛ ነው

ኢትዮጵያ የውጪና የገቢ ምርቶቿን የሎጂስቲክስ አቅርቦት ለማቀላጠፍ በ83 ነጥብ 1 ቢሊዮን ብር ወጪ 16 አዳዲስ መርከቦችን ለመግዛት አቅዳለች። በቀጣይ አምስት ዓመታት ውስጥ የሚከናወነው ይህ የግዥ እቅድ አሁን ካሉት 10 መርከቦች በተጨማሪ የሚከናወን ሲሆን፣ ቀደም ሲል ከነበሩት ከ25 ሺህ እስከ 28 ሺህ ቶን አቅም በበለጠ ከ50 ሺህ እስከ 63 ሺህ ቶን የመሸከም አቅም ያላቸው ግዙፍ መርከቦችን የሚያካትት ነው።

የኢትዮጵያ ባሕር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ እንደገለጸው፣ በአሁኑ ወቅት ከስድስት መርከቦች በላይ ሕጋዊ የግዥ ሥርዓት በሂደት ላይ ይገኛል። አዲሶቹ መርከቦች ስትራቴጂክ ግብዓቶችን በብቃት በማስገባትና ወደ ውጭ የሚላኩ ምርቶችን በወቅቱ በመላክ የሀገሪቱን የንግድ እንቅስቃሴ ውጤታማ ለማድረግ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ይኖራቸዋል።


AmharicTube

    ጨምሮ በአንዳንድ የ  #ኢትዮጵያ አካባቢዎች ላይ ጥላው የነበረውን ልዩ የጉዞ ማስጠንቀቂያ አነሳች የደቡብ ኮሪያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አርብ ዕለት ባወጣው መግለጫ፣ በኢትዮጵያ ያለውን ...
09/05/2026

ጨምሮ በአንዳንድ የ #ኢትዮጵያ አካባቢዎች ላይ ጥላው የነበረውን ልዩ የጉዞ ማስጠንቀቂያ አነሳች

የደቡብ ኮሪያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አርብ ዕለት ባወጣው መግለጫ፣ በኢትዮጵያ ያለውን የጤና ሁኔታ እና የኢቦላ ቫይረስ በሽታ አለመኖሩን በተመለከተ ግምገማ በማድረግ አዲስ አበባን ጨምሮ በአንዳንድ የሀገሪቱ አካባቢዎች ላይ ተጥሎ የነበረውን የጉዞ ማስጠንቀቂያ ማንሳቱን አስታወቀ።

ሚኒስቴሩ በመስከረም ወር ያበቃሉ ተብለው የታቀዱትን ልዩ የጉዞ ማስጠንቀቂያ ማራዘም በሚያስፈልግበት ሁኔታ ላይ ክለሳ ማድረጉን የገለጸ ሲሆን፣ በኢትዮጵያ፣ ታይላንድ፣ ቱርክ እና አዘርባጃን ውስጥ የሚገኙ የተወሰኑ አካባቢዎችን ሁኔታ በመገምገም ማዕቀቦቹን ለማንሳት መወሰኑን አስረድቷል።

ኢትዮጵያን በተመለከተ የተላለፈው ይህ ውሳኔ፣ የደቡብ ኮሪያ ባለሥልጣናት በሀገሪቱ ውስጥ እስካሁን የተረጋገጠ የኢቦላ ቫይረስ በሽታ አለመኖሩን ከረጋገጡ በኋላ የተሰጠ ነው።

በኢቦላ ስርጭት ስጋት ምክንያት አዲስ አበባን ጨምሮ በበርካታ አካባቢዎች ላይ ግንቦት 19 ቀን 2018 ዓ.ም. ተጥሎ የነበረው ልዩ የጉዞ ማስጠንቀቂያ የተነሳ ሲሆን፣ ለአካባቢዎቹ የተሰጠው የጉዞ ስጋት ደረጃ ወደ ደረጃ 2 ዝቅ እንዲል ተደርጓል። ይህም መንገደኞች አስፈላጊውን ጥንቃቄ እንዲያደርጉ የሚያስጣነቅቅ ነው።

አዲስ ስታንዳርድ

2ቱ የትራፊክ የቁጥጥር ባለሙያዎች ለጊዜው ከስራ እንዲታገዱ መደረጉ ተገለፀ::የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ባለስልጣን በከተማዋ የመንገድ ተጠቃሚዎችን ደህንነት ለማስጠበቅና የትራፊክ እንቅ...
09/02/2026

2ቱ የትራፊክ የቁጥጥር ባለሙያዎች ለጊዜው ከስራ እንዲታገዱ መደረጉ ተገለፀ::

የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ባለስልጣን በከተማዋ የመንገድ ተጠቃሚዎችን ደህንነት ለማስጠበቅና የትራፊክ እንቅስቃሴን ለማስፈጸም በሚያከናውናቸው የመስክ ቁጥጥር ስራዎች ወቅት ከመንገድ ተጠቃሚዎች ጋር አለመግባባቶች እንደሚከሰቱ ገልጿል።

በዛሬው ዕለት (ነሀሴ 27 ቀን 2018 ዓ.ም) በማህበራዊ ትስስር ገፆች ላይ ሲሰራጭ የዋለውን ምስል አስመልክቶ ተቋሙ ባወጣው መረጃ የሚከተሉትን ዋና ዋና ነጥቦች አብራርቷል፦

• የቁጥጥር ባለሙያዎች ደንብ የተላለፈን አሽከርካሪ የመንጃ ፈቃድ በሚጠይቁበት ወቅት "አልሰጥም" በማለት ስራ ማስተጓጎል፣ ስድብ፣ ዛቻ ወይም ሃይል መጠቀም በህግ የሚያስጠይቅ ተግባር መሆኑ ተመልክቷል።

• ተቋሙ በምስሉ ላይ የታየውን አለመግባባት ግራና ቀኝ ያለውን አካል ሚዛናዊ በሆነ መንገድ በማጣራት ላይ እንደሚገኝና እስከዚያው ድረስ በክስተቱ ላይ የተሳተፉት ሁለቱ የቁጥጥር ባለሙያዎች ለጊዜው ከስራ እንዲታገዱ ማድረጉን አስታውቋል።

ህብረተሰቡ የችግሩን የማጣራት ሂደት በስክነት እንዲከታተልና ትክክለኛ ካልሆኑ መረጃዎች እንዲቆጠብ ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ጥሪ አቅርቧል።

Via የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት
AmharicTube

በአዲስ አበባ ጎዳናዎች የታየውና ማህበራዊ ሚዲያውን ያነጋገረው ድንገተኛ ክስተት! አዲስ አበባ — በዋና ከተማዋ አዲስ አበባ በመንገድ ትራንስፖርት ተቆጣጣሪዎች እና በአሽከርካሪዎች መካከል ያ...
09/02/2026

በአዲስ አበባ ጎዳናዎች የታየውና ማህበራዊ ሚዲያውን ያነጋገረው ድንገተኛ ክስተት!

አዲስ አበባ — በዋና ከተማዋ አዲስ አበባ በመንገድ ትራንስፖርት ተቆጣጣሪዎች እና በአሽከርካሪዎች መካከል ያለው ፍጥጫ ወደ አካላዊ ግብግብ (MMA Fight) እየተቀየረ መምጣቱን የሚያሳዩ ተንቀሳቃሽ ምስሎች በማህበራዊ ሚዲያ ላይ ትልቅ መነጋገሪያ ሆነዋል።

አንድ አሽከርካሪ ከተቆጣጣሪዎች ጋር በገባው አለመግባባት የትራፊክ ቅጣትን እና የመኪና ታርጋ መፈታትን በመቃወም ቀጥታ ወደ ድብድብ የገባበት ይህ ትዕይንት፣ በርካታ አሽከርካሪዎች አሁን ላይ በተጣለው የትራፊክ ቅጣት መጠን መማረራቸውንና ጥብቅ ቁጥጥሩ የወለደው ብስጭት እንደሆነ ብዙዎች ይገልፃሉ። የህዝቡ አስተያየት በሁለት ተከፍሏል፦

በርካታ የማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች በአሁኑ ወቅት የሚጣሉት ቅጣቶች ከልክ ያለፉና አሽከርካሪውን ላስፈላጊ እንግልት የሚዳርጉ በመሆናቸው አሽከርካሪው የወሰደው ምላሽ የሚጠበቅ ነው በማለት ደግፈውታል።

በሌላ በኩል ደግሞ በርካቶች አጋጣሚው ምንም ያህል የሚያበሳጭ ቢሆንም፣ የህግ የበላይነትና ስርዓት መከበር እንዳለበት በመጥቀስ አለመግባባቶች በውይይትና በህጋዊ መንገድ እንጂ በጉልበት መፈታት የለባቸውም ሲሉ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።

ይህ ክስተት በአሽከርካሪዎች እና በትራንስፖርት ተቆጣጣሪዎች መካከል ያለውን ግንኙነት እንደገና ማየትና የቅጣት አሰራሮችን በስርዓት መፈተሽ አስፈላጊ መሆኑን ማሳያ ነው ተብሏል። እርስዎ በዚህ ጉዳይ ላይ ምን አስተያየት አለዎት? ህጉ ይከበር ወይስ አሰራሩ ?

ጉርሻ page
AmharicTube

ሰማይ ላይ የተጻፈ ስማችን!ከሰሞኑ ጣሊያን በነበረን የትያትር ሥልጠና “I am from a place where…” የሚል የጌም መልክ ያለውና ወደዋነው ጉዳይ የሚያንደረድር አንድ ጨዋታ እንጫወት...
08/31/2026

ሰማይ ላይ የተጻፈ ስማችን!

ከሰሞኑ ጣሊያን በነበረን የትያትር ሥልጠና “I am from a place where…” የሚል የጌም መልክ ያለውና ወደዋነው ጉዳይ የሚያንደረድር አንድ ጨዋታ እንጫወት ነበር።

አጨዋወቱ ቀላል ነው። በክብ ተቀምጠን አንድ ሰው መሀል ይቆማል። “I am from a place where…” ብሎ ከመጣበት ማኅበረሰብ፣ ባህል ወይም የኑሮ ልምድ ጋር የሚያያዝ አንድ ነገር ይናገራል። የተናገረውን ሐሳብ የሚጋሩ ሰዎች ከወንበራቸው ተነስተው ቦታ ይቀያየራሉ።

ቦታ ያጣው ደግሞ መሀል ቆሞ የራሱን “I am from a place where…” ይናገራል፤ ጨዋታውም በዚሁ መልኩ ይቀጥላል።
አብዛኛውን ጊዜ የሚያነሷቸው ጉዳዮች ከእኔ ልምድ ጋር የማይገጥሙ፣ እኔም የማልጋራቸው ስለነበሩ ከመቀመጫዬ አልተነሳሁም። ዝም ብዬ የሚሉትን እከታተል ነበር። ድንገት አንዷ አሜሪካዊት፣ “የመጣሁት በነጭና በጥቁር መካከል ኢፍትሐዊነት ካለበት ቦታ ነው” አለች። ብዙዎቹ ተነሱ። እኔም አሰብኩ። በአገሬ የነጭና የጥቁር መከፋፈል በዚያው መልክ ባይኖርም፣ እኔ ጥቁር ነኝ። ስለጥቁር ማንነትና መብት የተነሳ ጉዳይ ነውና “እኔ ታዲያ እዚህ ተቀምጬ ምን እሠራለሁ?” ብዬ ከመቀመጫዬ ተነሳሁ።
ስለጉዳዩ እያሰብኩ ስለነበር ዘወር ስል ቦታዬ ተይዟል! መሀል ቆሜ “ምን ልበላቸው?” እያልኩ ማሰብ ጀመርኩ። ሁሉም ዓይን ዓይኔን ሲመለከተኝ፦
“I am from a place where our airline is part of our identity.”
“የመጣሁት እንደ ዓይናችን ብሌን የምናየው አየር መንገዳችን የማንነታችን አካል ከሆነበት አገር ነው።” እንደማለት ነው።
ዙሪያዬን አየሁ።
የሚነሳ አጣሁ!
አንድም የጨዋታው ተሳታፊ ከመቀመጫው አልተነሳም። ግራ ገባኝ። እኔም እዚያው መሀል ቆሜ ቀረሁ። ምንም እንኳ የጨዋታው ሕግ መጠየቅን ባይፈቅድም፣ አለመነሳታቸው ቆረቆረኝ። የመጣው ይምጣ ብዬ፦
“ለምን አልተነሳችሁም?” አልኳቸው።
መልሳቸው የተለያየ ነበር። ለአንዳንዶቹ አየር መንገድ በዋናነት የመጓጓዣ አገልግሎት የሚሰጥ ተቋም ነው። አንዳንዶቹማ “የእኛ” የሚሉት ተወዳዳሪ ብሔራዊ አየር መንገድ እንኳ የላቸውም። ለሌሎቹ ደግሞ የሀገራቸው መለያ ቢሆንም፣ እስከ “የማንነቴ አካል ነው” የሚያስብል ግንኙነት ከአየር መንገዳቸው ጋር አልነበራቸውም።
ምናልባት “የመጣሁት ሽማግሌዎች ከሚከበሩበት ቦታ ነው” ብዬ ቢሆን ኖሮ ከወንበራቸው የሚነሱ ይኖሩ ነበር። “የመጣሁት ቤተሰብ ትልቅ ቦታ ከሚሰጠው ማኅበረሰብ ነው” ብል፣ ወይም “የመጣሁት እንግዳ በክብር ከሚቀበልበት ቦታ ነው” ብል፣ ከተለያዩ ሀገራት የመጡ ሰዎች ሐሳቡን ሊጋሩኝ ይችሉ ነበር። እነዚህ በብዙ ማኅበረሰቦች የሚጋሩ እሴቶች ናቸውና።
አየር መንገድን ከማንነት ጋር ሳገናኝ ግን ሐሳቡን የሚጋራኝ አጣሁ።
እዚህ ላይ አንድ ጥያቄ ውስጤ ቀረ።
እንዴት ነው አንድ የንግድና የመጓጓዣ ተቋም ከተራ ተቋምነት አልፎ የሕዝብ የጋራ ማንነትና ኩራት አካል የሚሆነው?....መልሱ “የሀገራችንን ባንዲራ ይዞ ስለሚበር” ብቻ አይደለም። እንዲያውም ይህ ለኢትዮጵያ አየር መንገድ ብቻ የተሰጠ ልዩ ነገር አይደለም። በዓለም ላይ ብዙ flag carriers የሀገራቸውን ባንዲራ፣ ብሔራዊ ቀለማት ወይም ሌሎች የሀገር ምልክቶች በአውሮፕላኖቻቸው ላይ ይዘው ይበራሉ።
ታዲያ የእኛን ልዩ የሚያደርገው ምንድን ነው?....
ለእኔ ልዩነቱ ባንዲራውን መሸከሙብቻ አይደለም። ያንን ባንዲራና “Ethiopian” የሚለውን ስም ከተቋማዊ ቀጣይነት፣ ከውድድርና ከስኬት ጋር ማያያዝ መቻሉ ነው። የኢትዮጵያን ስም ይዞ ለዓመታት ተወዳድሯል። በውድድሩ ውስጥ ብቻ አልቆየም፤ አድጓል፣ መዳረሻዎቹን አስፍቷል፣ በዓለም አቀፍ የአቪዬሽን ገበያ ውስጥም ተወዳዳሪ ተቋም ሆኗል። በሀገራችን የተለያዩ ዘመናት፣ መንግሥታትና ፈተናዎች ሲፈራረቁ፣ እሱ ግን ትውልድ ተሻግሮ “Ethiopian” የሚለውን ስም ይዞ ቀጥሏል። ምናልባት የማንነት ጉዳዩ የሚጀምረውም እዚህ ላይ ነው። ማንነት በስም፣ በባንዲራና በቀለም ብቻ አይገነባም፤ በታሪክ፣ በቀጣይነት፣ በስኬትና በጋራ ትውስታም ይገነባል።
ስለዚህ በሌላ ሀገር አየር ማረፊያ አረንጓዴ፣ ቢጫና ቀዩን ጭራ ከሩቅ ስናይ፣ የምናየው ቀለም ብቻ አይደለም። ከዚያ ቀለም ጀርባ ያለውን ስም፣ ታሪክ፣ ቀጣይነትና ስኬትም ነው። በዚህም አየር መንገዳችን ከተራ የመጓጓዣ ተቋምነት አልፎ የጋራ ትውስታችንና ኩራታችን አካል ሆኗል። በብዙ ኢትዮጵያውያን ልብ ውስጥ ያገኘው ቦታም ከዚህ የመጣ ነው።
ከጨዋታው በኋላም ለሥልጠናው ከተለያዩ ሀገራት ለመጡት የትያትር ባለሙያዎች ደረቴን ነፍቼ ነገርኳቸው፤ አየር መንገዳችን ከA ወደ B የሚያደርሰን የመጓጓዣ ተቋም ብቻ አይደለም። “Ethiopian” የሚለውን የሀገሬን ስም ይዞ ብቻ ሳይሆን የአፍሪካ መልክ በሰማይ ላይ የሚዞር፣ ታሪካችንን ሰማይ ላይ ያተመ ስማችን ነው፡፡ መቸስ ከዚህ በኋላ የኢትዮዽያን አየር መንገድ ሲያዩ እንደ ቀላላ አየር መንገድ እንደማይወስዱት ተስፋ አለኝ፡፡
አዎ፣ እኔ ሁሌም እንዲህ እላለሁ፦
“I am from a place where our airline is part of our identity.”
የመጣሁት አየር መንገዳችን የማንነታችን አካል ከሆነበት አገር ነው።
ደህና አምሹ!

@የጉዞ ማስታወሻ
ተስፋዬ እሸቱ (ረዳት ፕሮፌሰር)
AmharicTube

የገቢዎች ሚኒስቴር የኤክሳይዝ ታክስ ከፋይ የሆኑ የማምረቻ ተቋማት፣ በተለይም የቢራና የታሸጉ መጠጦች ፋብሪካዎች ውስጥ ከፍተኛ ጥራት ያላቸው የክትትል ካሜራዎችን መግጠም መጀመሩ ካፒታል ጋዜጣ...
08/31/2026

የገቢዎች ሚኒስቴር የኤክሳይዝ ታክስ ከፋይ የሆኑ የማምረቻ ተቋማት፣ በተለይም የቢራና የታሸጉ መጠጦች ፋብሪካዎች ውስጥ ከፍተኛ ጥራት ያላቸው የክትትል ካሜራዎችን መግጠም መጀመሩ ካፒታል ጋዜጣ ዘገበ።

እንደ ጋዜጣው ዘገባ መንግሥት ለዲጂታል የክትትል ሥርዓቱ ወደ 300 ሚሊዮን ብር የሚገመት በጀት መድቧል።

ካሜራዎቹ የምርት መስመሮችን፣ የማሸጊያ ክፍሎችን፣ መጋዘኖችን፣ የጭነት መውጫዎችንና የምርት መጓጓዣን በቅጽበት ለመከታተል እንደሚውሉ ተገልጿል።


AmharicTube

Address

Santa Monica, CA
90403

Opening Hours

Monday 9am - 6pm
Tuesday 9am - 6pm
Wednesday 9am - 6pm
Thursday 9am - 6pm
Friday 9am - 6pm

Telephone

+13105709291

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when AmharicTube posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to AmharicTube:

Shortcuts

Share