AmharicTube

AmharicTube Amharic Tube Ethiopian movies, press conference and news

“ወደ ማዶ”በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ በ30 የአለም ሀገራት መድረኮች የሚታይ ወደ ማዶ" አለም አቀፍ የትያትር ጉዞ ሊጀመር ነውበኢትዮጵያ የትያትር ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ በ30 የአለም ሀገራት...
07/25/2025

“ወደ ማዶ”

በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ በ30 የአለም ሀገራት መድረኮች የሚታይ ወደ ማዶ" አለም አቀፍ የትያትር ጉዞ ሊጀመር ነው

በኢትዮጵያ የትያትር ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ በ30 የአለም ሀገራት መድረኮች የሚታይ ወደ ማዶ" አለም አቀፍ የትያትር ጉዞ ሊጀመር እንደሆነ የትያትሩ አዘጋጆቹ በዛሬው እለት በሰጡት መግለጫ አስታውቀዋል፡፡

አንጋፋ ተዋንያን የሚተውኑበት ይህ "ወደ ማዶ" የተሰኘው ትያትር በውጭ ሃገር መድረክ እንደሚመረቅም ተገልጿል፡፡

ይህን እስካሁን ባልተለመደ መልኩ በ30 አለም አቀፍ መድረኮች የሚታይ ትያትርን ፕሮዲውስ ያደረገው ዋካ ፕሮሞሽንና ኢቨንት ነው፡፡

"ወደ ማዶ" የተሰኘው እና ኮሜዲ ዘውግ ያለው ትያትር ን ለመስራት ብዙ አመታትን የፈጀ ሲሆን በትወና ብቃቷ ከፍተኛ የተመልካች ፍቅርና አድናቆት ያላት ሃረገወይን አሰፋን ጨምሮ ሸዋፈራው ደሳለኝ እና የኋላእሸት ዘሪሁን ይተውኑበታል፡፡

በቴዎድሮስ ተ/አረጋይ ተደርሶ በሴም አማኑኤል የተዘጋጀው "ወደ ማዶ" ትያትር ማህበራዊ ጉዳዮችን እያነሳ የሚሄድ፤ ሲሆን በሕይወታችን የሚገጥሙን ችግሮች ለማውጣት የሚደረግን ትንቅንቅ የሚያሳይ ነው፡፡

ወደ ማዶ" አለም አቀፍ የትያትር ጉዞ ለሚቀጥሉት ሦስት ዓመታት ትውልደ ኢትዮጵያውያን በሚገኙባቸው በአፍሪካ፣ በመካከለኛው ምስራቅ፣ በአውሮፓና በሰሜን አሜሪካ አህጉራት በሚገኙ ሀገራት እንዲሁም በኢትዮጵያ ከ30 በላይ መድረኮች ይታያል ተብሏል፡፡

የትያትሩ ይፋዊ የመክፈቻ መርሃ ግብር ታላላቅ የኪነ ጥበብ ባለሙያዎች፣ የጥበብ ወዳጅ ኢትዮጵያውያን በተገኙበት በነሐሴ ወር በአፍሪካ የተለያዩ ሃገራት ይደረጋል፡፡

በተጨማሪም እስካሁን ባልተለመደ መልኩ ትያትሩ በሚታይባቸው ሀገራትና መድረኮች ከትያትሩ ጎን ለጎን ለ"የኢትዮጵያ የልብ ህሙማን ህፃናት መርጃ ማዕከል" የገቢ ማሰባሰቢያ እንደሚካሄድም ተነግሯል፡፡ ይህንንም በጎ አላማ ለማሳካት ከማዕከሉ ጋር የመግባቢያ ስምምነት ተፈርሟል፡፡

ትያትሩን ፕሮዲውስ ያደረገው ዋካ ፕሮሞሽንና ኤቨንት በኪነ ጥበቡ ሰፊ እንቅስቃሴዎችን በማድረግ የረጅም ጊዜ ልምድ የካበተ ሲሆን ትያትርና ፊልሞችን ጨምሮ የተለያዩ ሁነቶችን በማዘጋጀት ይታወቃል፡፡

07/11/2025

Enat Bank - The Only Transformational Bank by National Bank of Ethiopia Based on Ethiopia's Women's financial inclusion scorecard initiative.

07/11/2025
“የብራድ አንባሳደሮቸ አርቲስት ይገረም ደጀኔ ወንድም ካሊድ ናስርና ፕሮሞተር አብርሃም ግዛው የመኪና ሽልማት”ፊንቴክ ኢንቨስትመንት 250 መኪኖችን ለደንበኞች አስረከበ!!****ፊንቴክ ኢንቨስ...
06/25/2025

“የብራድ አንባሳደሮቸ አርቲስት ይገረም ደጀኔ ወንድም ካሊድ ናስርና ፕሮሞተር አብርሃም ግዛው የመኪና ሽልማት”

ፊንቴክ ኢንቨስትመንት 250 መኪኖችን ለደንበኞች አስረከበ!!
****
ፊንቴክ ኢንቨስትመንት ኃ/የተ/የግል ማህበር ለ250 ደንበኞች የኤሌክትሪክ የቢዋይዲ መኪኖችን ዛሬ ሰኔ 18/2017 ዓ.ም በመስቀል አደባባይ በተከናወነ ዝግጅት ለደንበኞች አስረከበ!

ይህ መርሐ ግብር 20 ሺህ ኤሌክትሪክ መኪኖችን የመገጣጠም እና የማቅረብ ፕሮጀክት አካል እንደሆነ ነው የተገለጸው።

ከዚህኛው መርሐ በፊት በ3 ዙር 250 ያህል መኪኖችን ያስረከበ ሲሆን ይሄኛው ለ4ኛ ጊዜ ያስረከባቸው እንደሆነ ሲገለፀ በዚሁም ጊዜ ለድርጅቱ ብራንድ አምባሳደር ለሆነው ጋዜጠኛና ፕሮሞተር አብርሃም ግዛው የብራድ አንባሳደሮቸ አርቲስት ይገረም ደጀኔ ወንድም ካሊድ ናስር የመኪና ሽልማት ፊንቴክ ኢንቨስትመንት 250 መኪኖችን ለደንበኞች አስረከበ!!
****

ከዚህኛው መርሐ በፊት በ3 ዙር 250 ያህል መኪኖችን ያስረከበ ሲሆን ይሄኛው ለ4ኛ ጊዜ ያስረከባቸው እንደሆነ ሲገለፀ በዚሁም ጊዜ ለድርጅቱ ብራንድ አምባሳደር ለሆነው ጋዜጠኛና ፕሮሞተር አብርሃም ግዛው የብራድ አንባሳደሮቸ አርቲስት ይገረም ደጀኔ ወንድም ካሊድ ናስር የመኪና ሽልማት የኢ.ፊ.ዲ.ሪ ትራንስፖርትና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዲኤታ ክብር አቶ በርሆ ሃሰን እና የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዉጭ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አንባሳደር ዲና ሙፍቲ እጅ ተበርክቶላቸዋል:: ።

ፊንቴክ ኢንቨስትመንት በየ120 ኪሎ ሜትሩ የኤሌክትሪክ ቻርጅ ማድረጊያ መሙያ ጣቢያዎችን ለመገንባት ማቀዱ በዝግጅት ስነስርዓቱ ላይ ተብራርቷል።

ፊንቴክ ኢንቨስትመንት ከቢዋይዲ ኩባንያ “Ocean Network" የኤለክትሪክ መኪኖችን ገዝቶ ከ950 ሺህ ብር ቅድመ ክፍያ ጀምሮ በ5 ዓመት የሚከፈል ከወለድ ነፃ የ50% (የሃምሳ ከመቶ) የብድር አገልግሎት አዘጋጅቶ ከ8 ዓመት ዋስትና ጋር በማቅረብ እንቅስቃሴ ላይ የነበረ ሲሆን ድርጅቱ ቀደም ሲል በኦሮሚያ ባህል ማእከል፣ በስካይ ላይት ሆቴል እና በወዳጅነት ፓርክ እስከ 250 የኤለክትሪክ መኪኖች ለደንበኞች አስረክቧል ተብሏል።

ፊንቴክ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን ማቅረቡ ኢትዮጵያ ለምትከተለው አረንጓዴ ኢኮኖሚ አጋዥ ይሆናል ተብሏል።

የምግብ ቤቶች አዋርድ ሊካሄድ ነው!በአዲስ አበባ ውስጥ ያሉ ምርጥ ምግብ ቤቶች በ10 በተለያዩ ምድቦች እውቅና ለመስጠት እና ለመሸለም ያለመ የbeU 2024 ምግብ ቤቶች ሽልማት ተዘጋጀ።የምር...
06/20/2025

የምግብ ቤቶች አዋርድ ሊካሄድ ነው!

በአዲስ አበባ ውስጥ ያሉ ምርጥ ምግብ ቤቶች በ10 በተለያዩ ምድቦች እውቅና ለመስጠት እና ለመሸለም ያለመ የbeU 2024 ምግብ ቤቶች ሽልማት ተዘጋጀ።

የምርጫ ሂደቱ የ2024 በተደረገ የደንበኞች እና ተጠቃሚዎች የመረጃ ጥናት፣ የትዕዛዝ ብዛት እና ጥራት፣ የደንበኞች አስተያየቶች፣ ከ5 ኮኮብ የተሰጣቸው የደንበኞች rating እንዲሁም በbeU ውስጥ ባሉ ሰራተኞች በስራቸው በአፈፃፀምና ባመጡት ተፅዕኖ የተሞላ ነጥበ መሆኑ ተገልጿል።

ሽልማት የሚሰጥባቸው ዘርፎች

1. በbeU app ዘንድ ከፍተኛ ኮኮብ ያገኘ ምግብ ቤት
2. በደንበኞች ዘንድ ተወዳጅ
3. የምርጦች ምርጥ
4. አስደማሚ የምግብ አይነቶችን የሚያዘጋጅ ቤት
5. በጣም ፈጣን Delivery
6. ጥራት ያለው አስተሻሸግ
7. ለጤና ተመራጭ
8. ምርጥ ሀገርኛ ጣዕም
9. ምርጥ አለማቀፋዊ ጣዕም
10. ያልታወቀባቸው ግን በጣም ገራሚ ምግብ ቤቶች

በአስሩም ዘርፍ ሁለት ሁለት ተሸላሚ ይኖራል።

የሽልማቱ ስነ ስርዓቱ ሰኔ 21/2017 ዓ.ም በሳፋየር አዲስ ሆቴል የሚካሄድ ይሆናል።

ከ1,200 ምግቦች ቤቶች ጋር አብሮ የሚሰራው BeU Delivery ከ3 ሚሊዮን በላይ ትዕዛዞችን አጠናቋን፣ 3000 ብስክሌተኞች እና ሞተረኞች አሉት።

ቢዩ ዴሊቨሪ ከቅሩንፉድ ዲጂታልስ በጋራ በመሆን ያዘጋጁት የመጀመሪያው የbeU ምግብ ቤቶች ሽልማት ነው።

📸 Sisay Guzaye

ለኢትዮጵያ ብቸኛውን እና ውዱን መሳሪያ አግኝተኛል | ወላጆች ልጃቸው በህክምና ቢሞ.ት እሬ.ሳውን አያገኙም Hiwote Tadese | Ethiopia
06/17/2025

ለኢትዮጵያ ብቸኛውን እና ውዱን መሳሪያ አግኝተኛል | ወላጆች ልጃቸው በህክምና ቢሞ.ት እሬ.ሳውን አያገኙም Hiwote Tadese | Ethiopia

ለኢትዮጵያ ብቸኛውን እና ውዱን መሳሪያ አግኝተኛል | ወላጆች ልጃቸው በህክምና ቢሞ.ት እሬ.ሳውን አያገኙም Hiwote Tadese | Ethiopia Subscribe to our channel Amharic Tube and enjoy Ethiopian dai...

ሰቨን ቢራ የ2025 ሞንዴ ሰሌክሽን ዓለም አቀፍ የጥራት ተሸላሚ ሆነየ2025 ሞንዴ ሰሌክሽን ዩናይትድ ቢቬሬጅ አክሲዮን ማህበር በሰቨን የቢራ ምርት ጥራት የወርቅ ተሸላሚ መሆኑን አስታውቋል።...
06/15/2025

ሰቨን ቢራ የ2025 ሞንዴ ሰሌክሽን ዓለም አቀፍ የጥራት ተሸላሚ ሆነ

የ2025 ሞንዴ ሰሌክሽን ዩናይትድ ቢቬሬጅ አክሲዮን ማህበር በሰቨን የቢራ ምርት ጥራት የወርቅ ተሸላሚ መሆኑን አስታውቋል። ተቋሙ ሽልማቱን በማስመልከት በሰጠው መግለጫ አለማቀፋዊ እውቅናን ያገኘንበት እንዲሁም የስራችንን ወጤት ያየንበት በመሆኑ ሽልማቱ ከሜዳሊያም በላይ ነው ሲል አስታውቋል። ሽልማቱ ዩናይትድ ቢቬሬጅ ለጥራት፣ ለደንበኞቹ ፍላጎት፣ እንዲሁም ታዓማኒነት እንደሚሰራ ምስክር መሆን የሚችል ሽልማት ነውም ተብሏል።

ኩባንያው " የተባበሩት ቢቬሬጅ አክስዮን ማህበር ለጥራት፣ ወጥነት ላለው ምርት እንዲሁም የደንበኞቹን እምነት ለመጠበቅ ዘወትር የሚተጋ በመሆኑ በሞንዴ ሰሌክሽን እውቅና ማግኘት መቻሉ ትልቅ ክብር ነው" ያለ ሲሆን "ይህ ሽልማት የመላው ቡድናችንን ትጋት እና ጥረት የሚያረጋግጥ ሲሆን ጥራትን ያስቀደመ የስኬት ማማ ላይ እንደሚቀመጥ ማሳያ ነው" ሲልም አክሏል።

ሞንዴ ሰሌክሽን የጥራት ሽልማት ብቻ አይደለም በዓለም አቀፍ ደረጃ እውቅና ያለው ማህተም ነው። ተጠቃሚዎች ከፍተኛውን ዓለም አቀፍ የጥራት ደረጃዎችን የሚያሟላ ምርት እንደመረጡ የሚያረጋግጥ የጥራት ምልክት ነው። ሞንዴ ሰሌክሽን ከሌሎች የሽልማት ዘርፎች ለየት ባለ መልኩ የራሱን መመሪያዎች በማዘጋጀት በተደራጀ መልኩ አለም ዓቀፍ በሆኑ እና የረጅም ጊዜ ልምድ ባላቸው ገለልተኛ ዳኞች አሸናፊው የሚለይበት መሆኑ ልዩ ያደርገዋል።

የሞንዴ ሰሌክሽን ከሽልማትነት ባለፈ ከፍተኛ የጥራት መመዘኛዎች በማሟላት የተመረጡ ምርቶች ቡድን አንድ አካል መሆን መቻልም ነው። ይህም ተጠቃሚዎች በገለልተኛ አካል የተገመገመ እና በጥራቱ የላቀ ምርት በቀላሉ ለማግኘት ያስችላቸዋል ተብሏል። ይህ ስኬት ከተጠቃሚዎች እምነት ባሻገር ዩናይትድ ቢቬሬጅ አክሲዮን ማህበርም በዓለም አቀፍም ሆነ በሀገር ውስጥ ያለውን ገበያ ያጠናክራል በተጨማሪም ለአዳዲስ ስራዎች ፤ ተደራሽነቶች ፤ አጋርነቶች እንዲሁም ስኬቶች መንገድ ይከፍታል ተብሎለታል።

ሰቨን ቢራ ይኽን ሽልማት ማሸነፉ ዩናይትድ ቤቬሬጅ ለተዓማኒነቱ እና ለምርት ጥራቱ ተግቶ እንደሚሰራ ማረጋገጫ ነውም ተብሏል።

"እኔ" የተሰኝው መፅሐፍ  ተመረቀ!!************************************የቀድሞ የሸገር ሬዲዮ ጋዜጠኛ የነበረችውና በአሁኑ ወቅት ነዋሪነቷን አሜሪካን ሐገር ያደረገችው የ...
06/15/2025

"እኔ" የተሰኝው መፅሐፍ ተመረቀ!!
************************************

የቀድሞ የሸገር ሬዲዮ ጋዜጠኛ የነበረችውና በአሁኑ ወቅት ነዋሪነቷን አሜሪካን ሐገር ያደረገችው የጤና ባለሙያዋ የሚስጢረ አደራው "እኔ" የተሰኝው መጽሐፍ በዋሊያስ መፅሐፍት አዳራሽ ሰኔ 07/10/17 ዓ.ም የተለያዩ እንግዶች በተገኙበት ተመርቋል::

📸 Tekle Markon

ሞቢሊቲ ኢ ከድጋፍ ማይክሮ ፋይናንስ ጋር በመተባበር ለ 5ኛ ጊዜ የመኪና ርክክብ አከናወነሞቢሊቲ  ኢ በእህት ኩባንያው ድጋፍ ማይክሮ ፋይናንስ ቆጥበው ሲጠባበቁ የነበሩ ለብድር ብቁ የሆኑ ደን...
06/14/2025

ሞቢሊቲ ኢ ከድጋፍ ማይክሮ ፋይናንስ ጋር በመተባበር ለ 5ኛ ጊዜ የመኪና ርክክብ አከናወነ

ሞቢሊቲ ኢ በእህት ኩባንያው ድጋፍ ማይክሮ ፋይናንስ ቆጥበው ሲጠባበቁ የነበሩ ለብድር ብቁ የሆኑ ደንበኞችን የ አምስተኛ ዙር የ ቢዋዲ መኪኖችን ርክክብ ዛሬ ሰኔ 7/2017 ዓ.ም
አድርጓል።

ሞቢሊቲኢ ከ ቢዋይዲ ሲጉል፣ ቢዋይዲ ኢ2፣ ቢዋይዲ ዩአን አፕ፣ ቢዋይዲ ዩአን ፕላስ እና ቢዋይዲ ሶንግ ፕላስ መኪኖችን በ 50% ቅድመ ከፍያ ብቻ ቀሪውን ከድጋፍ ማይክሮ ፋይናንስ ጋር በመተባበር በ 16 ነጥብ 5 በመቶ ወለድ ለደንበኞች ማቅረቡ ታውቋል።

በዚህም መሰረት ከ ሞቢሊቲ ኢ ጋር የመኪና ግዢ ፈጽመው ሲጠባበቁ ከነበሩት ውስጥ ለ 50 ደንበኞች የቁልፍ ማስረከብ ስነስርአት በ ዛሬው እለት አከናውኗል።

ሞቢሊቲ ኢ በ 4 ዓመት የብድር ክፍያ መመለሻ ጊዜ ያቀረበውን ለአጭር ጊዜ የሚቆይ ልዩ ቅናሽ ሪፌንቲ በሚገኘው ዋናው ሾውሩም እንዲሁም መስቀል ፍላወር እና ሃዋሳ ፒያሳ ሩት ገበያ በሚገኙት ቅርንጫፎች አመቻችቶ ተጨማሪ ዙር መኪኖችን ለማስረከብ ዝግጅቱን ማጠናቀቁ ተገልጷል።

ሞቢሊቲኢ በቀጣይም የተለያዩ የኤሌክትሪክ መኪናዎችን ከ ድጋፍ ማይከሮ ፋይናንስ ጋር ለማቅረብ ዝግጅቱን የጨረሰ ሲሆን፤ እስካሁን ከድርጅቱ ጋር አብረው የሰሩትን አካላት አመስግኗል።

"ማህበራዊ ሚዲያን ለበጎ አላማ" በሚል መሪ ቃል የምትታወቀው ህይወት ታደሰ ለኢትዮጵያ ብቸኛ የሆነውን የልብ ህክምና ማሽን ለልብ ህሙማን መርጃ ማዕከል አስረከበች።ነዋሪቷን በሰሜን አሜሪካ ያ...
06/12/2025

"ማህበራዊ ሚዲያን ለበጎ አላማ" በሚል መሪ ቃል የምትታወቀው ህይወት ታደሰ ለኢትዮጵያ ብቸኛ የሆነውን የልብ ህክምና ማሽን ለልብ ህሙማን መርጃ ማዕከል አስረከበች።

ነዋሪቷን በሰሜን አሜሪካ ያደረገችውና በተለይም ከአራት አመታት ወዲህ "ማህበራዊ ሚዲያን ለበጎ አላማ" በሚል መሪ ቃል የምትታወቀው ጋዜጠኛ ህይወት ታደሰ የልደት ቀኗን ምክንያት በማድረግ ላለፉት አምስት አመታት ስታደርግ የቆየችውን የበጎ አድራጎት ተግባር ዘንድሮም አከናውናለች።

ህይወት በተለይም በርካታ የልብ ታማሚ ህፃናት ህክምና አግኝቶ ለመዳን ተስፋ ለሚጥሉበት ለኢትዮጵያ የልብ ህሙማን መርጃ ማዕከል ድጋፍ በማሰባሰብ በየጊዜው የምትልክ ሲሆን፤ ዘንድሮ በአይነቱ እና አገልግሎቱ እጅግ የተለየ ለማዕከሉም ይሁን ለሃገሪቱ ብቸኛ የሆነ የህክምና ማሽን ነው ያስረከበችው።

ስድስድ ሚሊየን ብር ግምት ያለው ይህ የህምክና ማሽን
በቀላሉ የማይገኝ ለማዕከሉ ግን እጅግ ጠቃሚና የብዙዎችን ህይወት የሚታደግ ስለመሆኑም ህይወት ታደሰ ከአሜሪካን ሃገር ባስተላለፈችው መልዕክት ጠቁማለች።

ህይወት ታደሰ ይሄንን የበጎ አድራጎት ስራ ለማጠናከር "ላይፍ ፎር አፍሪካ" የተሰኘ ግብረ ሰናይ ድርጅት በአሜሪካን ሃገር ያቋቋመች ሲሆን፤ በዚህም ድርጅት አማካኝነት በምታከናውናቸው ቅን ተግባራት በአሜሪካን ሃገር ለሃገር ብሎም ለማህበረሰብ በጎ የሰሩ ሰዎች የሚሸለሙበት "ቤስት ሰርቪስ አዋርድ " እጩ ሆና እስከመቅረብ ደርሳለች።

"በማህበራዊ ትስስር ገፆች (ሶሻል ሚዲያ) ልባቸው ተሰብሮ ወረፋ እየተጠባበቁ ለሚገኙ ምስኪን ህፃናት ህይወታቸው እንዳያልፍ በርካታ ተከታይ ያለን ታዋቂ ሰዎች በተከታዮቻችን ልክ ፈጥነን ልንደርስላቸው ይገባል" ስትልም መልዕክት አስተላልፋለች።

ህይወት ታደሰ ከዚህ ቀደም ለማዕከሉ ከ50 ሚሊየን ብር በላይ የሚገመት፤ ለልብ ቀዶ ህክምና፣ በደም ስር ውስጥ ለሚደረግ ህክምና የሚያገለግሉ መሳሪያዎችን፣ አላቂ እቃዎችና መድሃኒቶችን ብሎም በርካታ ጠቃሚ ድጋፎችን ለማዕከሉ አድርጋለች።

ማዕከሉ ከተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች የሚላኩ ታካሚዎችን የሚያስተናግድ በመሆኑ አሁን ላይ ከ7000 በላይ ህፃናት የቀዶ ህክምና ለማግኘት በመጠባበቅ ላይ ይገኛሉ።

"ማህበራዊ ሚድያን ለበጎ ዓላማ" በመጠቀም ይህንን የህክምና መሳሪያ ለማዕከሉ ያስረከበችው ጋዜጠኛ ህይወት ታደሰ እና በመላው ዓለም የሚገኙ ለጋስ ኢትዮጵያውያንን ማዕከሉ አመስግኗል።

አንዷለም ጎሳ ከእስር ተፈታ
06/10/2025

አንዷለም ጎሳ ከእስር ተፈታ

አንዷለም ጎሳ ከእስር ተፈታ

በእጮኛው ሞዴል ቀነኒ አዱኛ ሞት ተጠርጥሮ እስር ቤት የቆየው ድምጻዊ አንዱዓለም ጎሳ ሶስት ወራት ከተጠጋ ጊዜ በኋላ ከእስር ቤት መውጣቱን ፋስት መረጃ አስነብቧል።

በሌላ በኩል ደግሞ የህግ ባለሙያው አበባየው ጌታ "ከአርቲስት አንዷለም ጎሳ ጠበቃ ጋር በስልክ ባደረኩት ንግግር አርቲስቱ ከእስር የመፈታቱ ዜና እውነት መሆኑን አረጋግጦልኛል።" ሲል አስታውቋል።

Via ዳጉ_ጆርናል

Address

Santa Monica, CA

Opening Hours

Monday 9am - 6pm
Tuesday 9am - 6pm
Wednesday 9am - 6pm
Thursday 9am - 6pm
Friday 9am - 6pm

Telephone

+13105709291

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when AmharicTube posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to AmharicTube:

Share