11/21/2025
ኦሜጋ ብድርና ቁጠባ ህብረት ስራ ማህበር ከሚዲያ እና ኪነ ጥበብ ባለሙያዎች ጋር ተፈራረመ።
ኦሜጋ ብድርና ቁጠባ ህብረት ስራ ማህበር ከሚዲያ እና ኪነ ጥበብ ባለሙያዎች ጋር ዛሬ ሕዳር 12 ቀን 2018 ዓ.ም የስምምነት ፊርማ አድርጓል።
የሚዲያ እና ኪነ ጥበብ ባለሙያዎች ባለሙያዎቹ ለሚሰሯቸው ሙያዊ ስራዎች የፋይናንስ አቅም ተግዳሮት እንዳይሆንባቸው እና ከስራቸው እንዳያስተጓጉላቸው በልዩ ሁኔታ የብድር አቅርቦት ለማመቻቸት መዘጋጀቱ ተነግሯል።
በዛሬው ዕለት ከቦሌ ክፍለ ከተማ እና ከክፍለ ከተማው ወረዳ 12 የህብረት ስራ ኮሚሽን ፅህፈት ቤት ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች በተገኙበት ስራውን በይፋ የጀመረው ኦሜጋ ብድርና ቁጠባ ህብረት ስራ ማህበር ለሁሉም ኢትዮጵያዊ አስተማማኝ የፋይናንስ አጋር ለመሆን መዘጋጀቱን ገልጿል።
በተጨማሪም የወረዳው ጋር በመሆን ለ10 ሴቶች ከወለድ ነጻ ብድር መመቻቸቱ ተነግሯል።
ኦሜጋ ብድርና ቁጠባ ህብረት ስራ ማህበር ብድር ፈላጊዎች የአጭር ጊዜ አነስተኛ ወለድ ያለው የብድርፐ አገልግሎት፣ በቡድን ለሚመጡ ብድር ፈላጊዎች ልዩ የወለድ ቅናሽ፣ ወላጆች ለታዳጊ ተማሪ ልጆቻቸው የት/ቤት ክፍያ ብድር፣ ለከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ዝግጅት የሚሆን ብድር፣ ለጤና አገልግሎት የሚውል ብድር፣ ለተለያዩ የውጭ ጉዞዎች የሚሆን ብድር እና ለሴቶች ስራ ማስጀመሪያ የሚሆን ከወለድ ነፃ የብድር አገልግሎት ማህበሩ ይዟቸው ከመጡ ብድሮች መካከል ይጠቀሳሉ ተብሏል።
ኦሜጋ ብድርና ቁጠባ ህብረት ስራ ማህበር በ2017 ዓ.ም በህብረት ስራ ማህበር አዋጅ ቁጥር 985/09 በህጋዊ መንገድ የተቋቋመው ማህበር ነው፡፡