12/26/2025
ኢትዮፒካር (ETIOPIKAR) የአፍሪካ የአመራርና የተቋማት ሽልማትን ማሸነፉን ተከትሎ ልዩ የበዓል ቅናሽ ይፋ አደረገ።
በኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች አስመጪነትና በኤክስፖርት ዘርፍ የተሰማራው ኢትዮፒካር፣ በ20ኛው "ግራንድ አፍሪካ የአመራርና የተቋማት ሽልማት" ላይ በምርጥ ተቋማዊ አፈፃፀም ሽልማት ተሸላሚ ሆኗል።
ኩባንያው ይህንን ስኬት በማስመልከትም ለደንበኞቹ እስከ ጥምቀት በዓል የሚቆይ ልዩ የዋጋ ቅናሽ እና የብድር አመቻች መርሃ-ግብር ይፋ አድርጓል።
ባለፈው ሳምንት በአድዋ መታሰቢያ ሙዚየም "ትጉኃንን እንሸልማለን" በሚል መሪ ቃል በተካሄደው የሽልማት ስነ-ስርዓት ላይ፣ ተቋሙ በሦስት የተለያዩ ዘርፎች እውቅናን አግኝቷል።
በዚሁ መሰረት የድርጅቱ መስራችና ባለቤት አቶ ሳሙኤል አዲስአለም በከፍተኛ አመራር ዘርፍ ሲሸለሙ፣ አቶ ኤፍሬም ታደለና አቶ ሴና ጌትነት በመካከለኛ አመራር ዘርፍ የላቀ አፈፃፀም ላሳዩ መሪዎች የሚሰጠውን ሽልማት ተቀብለዋል።
ኩባንያው የተገኘውን እውቅና ለደንበኞቹ ለማካፈል ባዘጋጀው መርሃ-ግብር፤ ከገና እስከ ጥምቀት በዓል ድረስ በኤሌክትሪክ መኪኖች ሽያጭ ላይ ከፍተኛ ቅናሽ ማድረጉን ገልጿል።
በተለይም መኪና መግዛት ለሚፈልጉ ግለሰቦች እና ድርጅቶች 50 በመቶ የቅድመ ክፍያ በመክፈል፣ ቀሪውን 50 በመቶ ከተለያዩ ባንኮች እና የፋይናንስ ተቋማት ጋር በመተባበር በሚመቻች ብድር መውሰድ የሚችሉበትን አሰራር መዘርጋቱን አስታውቋል።
በፈረንጆቹ 2013 ዓ.ም. የቀድሞ የባንክ ባለሙያ በሆኑት በአቶ ሳሙኤል አዲስአለም የተመሰረተው "ሳሙኤል አዲስአለም አስመጪ እና ላኪ"፤ በአሁኑ ወቅት በዩናይትድ አረብ ኤምሬትስ እና በአዲስ አበባ ቅርንጫፎቹን በመክፈት በስፋት እየተንቀሳቀሰ ይገኛል።
ተቋሙ በኢትዮፒካር (ETIOPIKAR) መለያ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን ወደ ሀገር ውስጥ ከማስገባት ባለፈ፣ በቡና፣ በቅባት እህሎች እና በፍየል ስጋ ኤክስፖርት ዘርፍ በመሰማራት ለሀገር የውጭ ምንዛሬ ግኝት የድርሻውን እየተወጣ እንደሚገኝ ተገልጿል።
ይህ ልዩ የሽያጭ እና የብድር ዕድል ደንበኞች ዘመናዊ እና ለአካባቢ ጥበቃ ተስማሚ የሆኑ የኤሌክትሪክ መኪኖችን በቀላሉ እንዲያገኙ ዓላማ ያደረገ መሆኑን ኩባንያው አክሎ ገልጿል።