EthioTimes

EthioTimes EthioTimes is a source of credible news and entertaining TV and radio productions.

በ28 ዓመት ታሪክ ከፍተኛውን ውጤት ላስመዘገበችው ተማሪ ቤተ መጻሕፍት በስሟ ተሰየመ‼️ በአዊ ብሔረሰብ አስተዳደር እንጅባራ ከተማ የሚገኘው አገው ምድር ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት፣ በ28 ዓመት ...
08/22/2026

በ28 ዓመት ታሪክ ከፍተኛውን ውጤት ላስመዘገበችው ተማሪ ቤተ መጻሕፍት በስሟ ተሰየመ‼️

በአዊ ብሔረሰብ አስተዳደር እንጅባራ ከተማ የሚገኘው አገው ምድር ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት፣ በ28 ዓመት ታሪኩ ከፍተኛውን የትምህርት ውጤት ላስመዘገበችው ተማሪ ህዳሴ ዘመኑ ልዩ እውቅና ሰጥቷል።

ተማሪ ህዳሴ በ11ኛ ክፍል 99.67% በማምጣት በትምህርት ቤቱ ታሪክ ከፍተኛውን ውጤት መመዝገብ ችላለች። ይህንን የላቀ ስኬቷን ለማክበርም ትምህርት ቤቱ ቤተ መጻሕፍቱን “ህዳሴ ቤተ መጻሕፍት” በማለት በስሟ ሰይሞላታል።

ህዳሴ የተሰጣት እውቅና ለቀጣይ ጥረቷ ትልቅ መነሳሳት እንደሆነ ገልጻ፣ በወደፊት በሶፍትዌር ቴክኖሎጂ ዘርፍ ተሰማርታ ሀገሯን ለማገልገል ትልቅ ራዕይ እንዳላት ገልጻለች።

በዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ሀገራዊ ፈተናም ከትምህርት ቤቱ በተፈጥሮ ሳይንስ ዘርፍ ከፍተኛ ውጤቶች ተመዝግበዋል፤ በሴቶች 583/600 እና በወንዶች 591.6/600 በማምጣት ትምህርት ቤቱ ከፍተኛ ውጤት ካስመዘገቡ ተቋማት መካከል ሆኗል።

ምንጭ- ጌጡ ተመስገን

ጀነራል ባጫ ደበሌ ከኬንያ ተሸኙ‼️ጀነራል ባጫ ደበሌ በኬንያ ናይሮቢ የነበራቸውን ስራ አጠናቀው ዛሬ ተሸኝተዋል።በተያያዘ መረጃ፣ ጀነራሉ በከፍተኛ አማካሪነት ሊሾሙ እንደሚችሉ መሰረት ሚዲያ ...
08/22/2026

ጀነራል ባጫ ደበሌ ከኬንያ ተሸኙ‼️

ጀነራል ባጫ ደበሌ በኬንያ ናይሮቢ የነበራቸውን ስራ አጠናቀው ዛሬ ተሸኝተዋል።

በተያያዘ መረጃ፣ ጀነራሉ በከፍተኛ አማካሪነት ሊሾሙ እንደሚችሉ መሰረት ሚዲያ ዘግቧል።

"ከሃገሬ አልሸሸሁም ፡ ምን ጊዜም አልሸሽም" ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ
08/22/2026

"ከሃገሬ አልሸሸሁም ፡ ምን ጊዜም አልሸሽም" ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ

"ክርስቶስ 'ጠላቶቻችሁን ውደዱ' ብሎን ሳለ ፣ እኛ ግን ወዳጆቻችንን እንኳ ብንጠላ በፈጣሪ ፊት ምን መልስ ይኖረን ይሆን?" — ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
08/22/2026

"ክርስቶስ 'ጠላቶቻችሁን ውደዱ' ብሎን ሳለ ፣ እኛ ግን ወዳጆቻችንን እንኳ ብንጠላ በፈጣሪ ፊት ምን መልስ ይኖረን ይሆን?" — ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ

በአዲስ አበባ መገናኛ ብቻውን ለተቃውሞ አደባባይ የወጣው ግለሰብ በቁጥጥር ስር ዋለ‼️ዛሬ ቅዳሜ ነሐሴ 16 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ መገናኛ አካባቢ የጠቅላይ ሚኒስትሩን ስም የጠቀሰ ...
08/22/2026

በአዲስ አበባ መገናኛ ብቻውን ለተቃውሞ አደባባይ የወጣው ግለሰብ በቁጥጥር ስር ዋለ‼️

ዛሬ ቅዳሜ ነሐሴ 16 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ መገናኛ አካባቢ የጠቅላይ ሚኒስትሩን ስም የጠቀሰ መፈክር በመያዝ ብቻውን አደባባይ ወጥቶ ተቃውሞ ሲያሰማ የነበረ ግለሰብ በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋሉ ታውቋል።

📌 ክስተቱ የተፈጠረዉዛሬ ረፋድ 4:00 ላይ ከፍተኛ የሕዝብና የትራፊክ እንቅስቃሴ በሚታይበት የመገናኛ አካባቢ ነው። ግለሰቡ አስቀድሞ ያዘጋጀውንና የጠቅላይ ሚኒስትሩን ስም የያዘውን መፈክር መገናኛ ብረት ላይ አስደግፎ፣ እሱ ከጎኑ በመቆም ድምፁን ሲያሰማ እንደነበር የአይን እማኞች ገልጸዋል።

👉 የፖሊስ እርምጃ፦ ተቃውሞውን ማሰማት በጀመረ በጥቂት ደቂቃዎች ውስጥ በአካባቢው በነበሩ የፖሊስ አባላት በቁጥጥር ስር ውሎ ወደ ፖሊስ ጣቢያ መወሰዱን እማኞቹ ጨምረው አስረድተዋል።

ስለ ሁኔታውና ግለሰቡ በአሁኑ ወቅት ስለሚገኝበት ሁኔታ ከሚመለከተው የፖሊስ አካል እስካሁን የተሰጠ ይፋዊ ማብራሪያ የለም።

ምንጭ- ዋሱ መሀመድ

#አዲስአበባ #መገናኛ #ሰበርዜና #ወቅታዊመረጃ #የኢትዮጵያፖለቲካ #አዲስአበባፖሊስ #ኢትዮጵያ #ዜና

🇪🇹 ኢትዮጵያውያን ስንተባበር ምን ያህል እንደምንደርስ ያሳየ ውጤት‼️ 🇪🇹በሚስ ወርልድ የቁንጅና ውድድር ኢትዮጵያን ወክላ የምትወዳደረው ሞዴል ሩት፣ በኢትዮጵያዉያን ርብርብ በተገኘላት ድምፅ...
08/22/2026

🇪🇹 ኢትዮጵያውያን ስንተባበር ምን ያህል እንደምንደርስ ያሳየ ውጤት‼️ 🇪🇹

በሚስ ወርልድ የቁንጅና ውድድር ኢትዮጵያን ወክላ የምትወዳደረው ሞዴል ሩት፣ በኢትዮጵያዉያን ርብርብ በተገኘላት ድምፅ ከ8ኛ ደረጃ ወደ 2ኛ ደረጃ ከፍ ብላለች።

🔥 24 ሰዓታት ሳይሞላ 97,127 ድምፅ በማግኘት ቦትስዋናን፣ ሶማሊያንና ሌሎች ተወዳዳሪዎችን ቀድማለች።

🥇 አሁንም እገዛችን ስለሚያስፈልጋት ኮመንት ላይ በተቀመጠው ሊንክ በመግባት ድምፅ እንስጣት።

📖  "ራሔል ጓል መቐለ" አዲስ መጽሐፍ ለንባብ በቃ‼️ ደራሲ አረጋዊ ዕፁብ (ቃዳዊ) አዲስ መፅሀፍ ይዞ ብቅ ብሏል። "ራሔል ጓል መቐለ" የተሰኘው አዲስ መጽሐፍ፣ በብሔራዊ ቤተ-መጻሕፍትና ቤ...
08/22/2026

📖 "ራሔል ጓል መቐለ" አዲስ መጽሐፍ ለንባብ በቃ‼️

ደራሲ አረጋዊ ዕፁብ (ቃዳዊ) አዲስ መፅሀፍ ይዞ ብቅ ብሏል። "ራሔል ጓል መቐለ" የተሰኘው አዲስ መጽሐፍ፣ በብሔራዊ ቤተ-መጻሕፍትና ቤተ-መዛግብት ኤጀንሲ (ወመዘክር) አዳራሽ በተሰጠ ደማቅ ጋዜጣዊ መግለጫ በይፋ ለንባብ መብቃቱ ተበስሯል።

1️⃣ በእውነተኛ ታሪክ ላይ የተመሰረተ፦

ይህ መጽሐፍ በእውነተኛ የሕይወት ገጠመኞችና ወቅታዊ ፈተናዎች ላይ ተመስርቶ፣ የወጣቶችን ሕይወት በጥልቀት የሚያወሳ ስራ ነው።

2️⃣ በሦስት ዋና ዋና ክፍሎች የተዋቀረ፦
ደራሲው ታሪኩን፣ ጥንካሬንና ታሪካዊ ክስተቶችን በሦስት ዋና ዋና ክፍሎች ስልታዊ በሆነ መንገድ አዋቅሮ አቅርቦታል።

መጽሐፉ ይበልጥ ልዩ የሚሆነው በአማርኛ፣ ትግርኛ እና እንግሊዝኛ ቋንቋዎች ተተርጉሞ መቅረቡ ነው። በሦስቱም ቋንቋዎች ከ150 እስከ 152 ገጾች ያሉት ሆኖ ተዘጋጅቷል።

መጽሐፉ በማንኩሳ አታሚና አሳታሚ ድርጅት ከፍተኛ ጥራቱን ጠብቆ ታትሟል።

ዋጋ- 450 ብር
👉 በአሁኑ ወቅት በዋናነት በጃዕፋር መጻሕፍት መደብር (በሁሉም ቅርንጫፎች) በገበያ ላይ ይገኛል።

በውጭ አገር ለምትኖሩ ወገኖቻችን በቅርቡ በአማዞን (Amazon) ላይ እንደሚጫን ተገልጿል።

#ራሔልጓልመቐለ #አዲስመጽሐፍ #አረጋዊዕፁብ #የመጽሐፍምረቃ #የኢትዮጵያሥነጽሑፍ #አሸንዳ #ማንኩሳአሳታሚ #የፍቅርታሪክ #እውነተኛታሪክ #መጽሐፍ

"እንጦጦ ኪዳነምህረት በየወሩ አልቀርም‼️""እኔ በሰከንድ ውስጥ በሚሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ እንዳገኘሁት ሁሉ፣ በተመሳሳይ በሰከንድ ውስጥ ብዙ ሚሊዮኖችን የሚያወጣ ውድ ሀብት አጥቻለሁ።ነገር ...
08/22/2026

"እንጦጦ ኪዳነምህረት በየወሩ አልቀርም‼️"

"እኔ በሰከንድ ውስጥ በሚሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ እንዳገኘሁት ሁሉ፣ በተመሳሳይ በሰከንድ ውስጥ ብዙ ሚሊዮኖችን የሚያወጣ ውድ ሀብት አጥቻለሁ።

ነገር ግን ኪዳነምህረት ከእኔ ጋር በመሆኗ ሁሌም አሸናፊ ነኝ!" ሻለቃ አትሌት ኃይሌ ገብረስላሴ

🎶 ሽሽግ ቸኮል — የማይረሳው የኢትዮጵያ ሙዚቃ ድምፅ‼️የወሎዋ ፈርጥ ሽሽግ ቸኮል በባህላዊና በአዝማሪ ሙዚቃ ታሪክ ውስጥ ስሟን ያስመዘገበች አንጋፋ አርቲስት ናት። በተለይም ከወሎ የባህል ሙ...
08/22/2026

🎶 ሽሽግ ቸኮል — የማይረሳው የኢትዮጵያ ሙዚቃ ድምፅ‼️

የወሎዋ ፈርጥ ሽሽግ ቸኮል በባህላዊና በአዝማሪ ሙዚቃ ታሪክ ውስጥ ስሟን ያስመዘገበች አንጋፋ አርቲስት ናት። በተለይም ከወሎ የባህል ሙዚቃ ትውፊት ጋር በተያያዘ ከተጠቀሱ ታዋቂ አዝማሪዎች መካከል ስሟ ይገኛል።

🎤 ሽሽግ ቸኮል ከአሰፋ አባተ፣ ንጋቷ ከልካይ፣ ካሳ ተሰማ እና ጌታመሳይ አበበ ጋር በኢትዮጵያ የቆየ የሙዚቃ ቅርስ ውስጥ ስሟ ይነሳል።

🎵 በድምፅ አቀራረቧ ፣ በባህላዊ ዜማዎቿና በአዝማሪ ግጥሞቿ የተለየ ትዝታ ያስቀመጠች ሲሆን፣ ከጌታመሳይ አበበ ጋር የተያያዙ የቆዩ የሙዚቃ ስራዎችም ዛሬም በተለያዩ በየሙዚቃ ስብስቦች ይገኛሉ።

ተወዳጁ አርቲስት ቴዲ አፍሮ በትዝታ

"አራት መቶ ፍቅር መሸከም ፈርተሽ፤
ይኸዉ ለዘልዓለም አፈር ተጫነሽ" ሲልም ተቀኝቶላታል።

ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ ደግሞ በቲክቶክ ትሬንድ ብዙዎች ከተቀባበሉት የሙዚቃ ግጥም ስንኝ ዉስጥ የሽሽግ ቸኮል

“መሔዴ ነው እንጅ ትንሽ ያበረደኝ፣
ኗሪ ሰው በሆንኩኝ እንዴት በነደደኝ።” የሚለዉ ይገኝበታል።

🇪🇹 ሽሽግ ቸኮል የአንድ ዘመን ድምፃዊት ብቻ ሳትሆን፣ የኢትዮጵያ የባህል ሙዚቃ ትውስታ አካል ናት።

💬 እርስዎ የሽሽግ ቸኮልን የትኛውን ሙዚቃ ያስታውሳሉ?

መካኖች ልጅ ያገኙበት የኪዳነምህረት ቤተክርስቲያን‼️እንኳን አደረሳችሁ‼️ይህ ቤተክርስቲያን በሰሜን ጎንደር ዞን ደባርቅ ወረዳ ኪኖ ቀበሌ የሚገኘዉ የኪዳነምህረት ቤተክርስቲያን ሲሆን ፡ ቤተክ...
08/22/2026

መካኖች ልጅ ያገኙበት የኪዳነምህረት ቤተክርስቲያን‼️

እንኳን አደረሳችሁ‼️

ይህ ቤተክርስቲያን በሰሜን ጎንደር ዞን ደባርቅ ወረዳ ኪኖ ቀበሌ የሚገኘዉ የኪዳነምህረት ቤተክርስቲያን ሲሆን ፡ ቤተክርስቲያኗ ስዕለት ሰሚ እንደሆነች እና ብዙ ገቢረ ተአምራት እንደተፈፀመባት አባቶች ምስክርነታቸውን ሰጥተዋል። ከገቢረ ተዓምራቶች መካከል አንዱ መካኖች በኪዳነምህረት ምልጃ ልጅ ማግኘት ችለዋል።

ቤተክርስቲያኑ ለረዥም አመታት ግንባታ ላይ ቢሆንም በአሁኑ ሰአት በገንዘብ ችግር ቤተክርስቲያኑ ሙሉ በሙሉ ከመሰራት ቆሟል። ስለሆነም ቤተክርስቲያኑን ለማሰራት አባቶች በእግዚአብሔር ስም ጥሪ አቅርበዋልና የበረከቱ ተሳታፊ እንሁን።

ድጋፍ ለማድረግ

👇

ንግድ ባንክ- 1000201850022

አቢሲኒያ- 255527077

አባይ- 2361119451656012

👉 ለብዙዎች እንዲዳረስ እባካችሁ ሼር አድርጉት‼️

Address

Silver Spring, MD

Opening Hours

Monday 9am - 5pm
Tuesday 9am - 5pm
Wednesday 9am - 5pm
Thursday 9am - 5pm
Friday 9am - 5pm
Saturday 9am - 5pm
Sunday 9am - 5pm

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when EthioTimes posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to EthioTimes:

Shortcuts

Share