Wollo Addis

Wollo Addis Our Website www.wolloaddis.com

የሄኒን ኢንተርቬው ሰማሁት። ሄኖክ በየዋህነት ተነሳስቶ፤ በኢትዮጵያ ታሪክ ተሰምቶ በማይታወቅ ሁኔታ "ህዝብ በገንዘቡ የሚሳተፍበት አንድ ፊልም" ለመስራት አልሞ የገንዘብ እርዳታ ጠየቀ። የጊዜ...
18/05/2026

የሄኒን ኢንተርቬው ሰማሁት። ሄኖክ በየዋህነት ተነሳስቶ፤ በኢትዮጵያ ታሪክ ተሰምቶ በማይታወቅ ሁኔታ "ህዝብ በገንዘቡ የሚሳተፍበት አንድ ፊልም" ለመስራት አልሞ የገንዘብ እርዳታ ጠየቀ።

የጊዜው የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ሁኔታ የትናንቱን መቶ ሺህ ብር ዛሬ የመቶ ብር ያህል እንኳ ዋጋ እያሳጣ ቃል የማያስጠብቅ ለዕቅድ የማይመች ሆኖ ፈረጃ የተባለውን ፊልም ለማውጣት ከህዝብ የሰበሰበው ሶስት ሚሊየን ብር የሶስት መቶ ሺህ ብር አሽቆልቁሎበት ክፉኛ ተሰቃየ።

ሄኖክ በቃለ መጠይቁ ላይ በሰፊው እንደ ገለጸው በእጅጉ የጎዳው የገንዘብ እጥረቱ ብቻ ሳይሆን የኛ ሰው "የሀበሻ" ኮሜንት (ዘለፋና ስድብ) ነበር። --- ገንዘብ ከለገሰው ይልቅ ዳር ቆሞ የተመለከተው ነበር በስድብ ሲያጥረገርገው የሰነበተው። ልጁ ግን ለአላማው ቁርጠኛ፤ ለቃሉም ታማኝ ነበርና ቃሉን በተግባር ተርጉሞ ፊልሙን ለእይታ አበቃ።

የኛ ሰው (ሀበሻ) እጅግ ከባድ (አስቸጋሪ) ከሚባሉ የአለም ህዝቦች ዋነኛው ይመስለኛል። ሰው ሲያገኝም ከስር ከስር መገዝገዝ፣ ቀን ሲዘምበትም ምሳር (መጥረቢያ) ይዞ ለመጣል መሯሯጥ። ....ይህ የሆነው ደግሞ በዚህ ዘመን የተፈጠረው (ቀለም ገብቶኛል፣ ሰለጠንኩ) ያለው ትውልድ በተነሳበት መሆኑ ደግሞ በእጅጉ አስገራሚ ነው።.....

ብቻ ሄኖክ ወንድሙ ለብዙዎቻችን በብዙ መልኩ ምሳሌ ሊሆን የሚችል አርቲስት ነው። ወንድማችን የሞራል ስብራት ሳይደርስበት፣ የማንም ስድብና ማጥላላት ተስፋ ሳያስቆርጠው ህልሙን ለስኬት ማብቃቱ በእጅጉ የሚደነቅ ምናልባትም በሲኒማው ኢንዱስትሪ ስሙን በደማቅ ቀለም ለመጻፍ የቻለ በመሆኑ ለአምስት አመታት የለፋበትን ፈረጃ ፊልሙን ለማየት እንጓጓለን!

በYetneberk Tadele

''ከሰው እስከ መኪና በጎጃምኛ የተጨፈረበት ሳምንት''''የማን ነህ እያሉት ኮራ አለ ጅንኑ ከየት ነህም ሲሉት ዝም አለ ጅንኑያስታዉቅ የለም ወይ ጎጃሜ መሆኑ''መቼም ሰሞኑን ከሰዎች ተሻግሮ ...
17/05/2026

''ከሰው እስከ መኪና በጎጃምኛ የተጨፈረበት ሳምንት''

''የማን ነህ እያሉት ኮራ አለ ጅንኑ
ከየት ነህም ሲሉት ዝም አለ ጅንኑ
ያስታዉቅ የለም ወይ ጎጃሜ መሆኑ''

መቼም ሰሞኑን ከሰዎች ተሻግሮ መኪና እንቅጥቅጥ እስክስታ የወረደበት ሳምንት ነበር ።

እዉነት ለመናገር እንደዚህ ሳምንት የጎጃምኛ ምት ያላቸው ሙዚቃዎች በሁሉም በማህበራዊ ሚዲያው መነጋገሪያ የሆኑበት ጊዜ አላስታውስም ። እንዲያውም የጎጃም ሳምንት ቢባል ማጋነን አይሆንም ።

ለዚህም ምክንያት የሆኑት ሐስዩምቃል" ዘነጡ ጎጃሞች "እና የቢሆን ዘዉዴ " ጅንኑ "ሙዚቃዎች ሲሆኑ የሰው ልጆች ከተፈጥሮ ጋር ያላቸውን ቁርኝት፤ እንዲሁም እርስ በርስ ያላቸውን ግንኙነት በሚገልፁበት የኪነት መድረክ ላይ ጎጃም ያለዉን ሁለንተናዊ ሀብት በሚገባው እንድናይ አድርገዋል ማለት ይቻላል ።

በዚህ እንደ ማህበረሰብ ተነግሮ የማያልቅ የተፈጥሮ የመልከአምድር የአስተዳደር የአኗኗር የሰርግ የዉበት የስራ ባህል እያሉን አንዷን ጀግንነት ብቻ በማንሳት በለው በለው የሚል ጦረኝነት ብቻ መነሳቱ ለሌላው ህዝብ አንድም ታጋሹ አራሹ ቀዳሱ ፍትህ አዋቂዉ ህዝብ ጦር የሚሰብቅ መጀመሪያ በሰላም ለመፍታት ሞክሮ አማራጭ ሲያጣ ብቻ ቢሆንም ተዋጊ ጦር ሰባቂ እንዲመስል ሙዚቃዎች ያደረጉትን ተፅዕኖ በመገዳደር የጥይት ኳኳታ የሌለባቸው ቱባዉን የጎጃም የሰርግ ስርዓት የስራ ባህል አምራችነት ፍትህ አዋቂነት አስተዋይነት ኩራት ምሁርነት በግጥም በዜማና በክሊፖቹ ቪዲዮዎች አሳይተዋል ።

ከዮቶር እስከ ተዋናይ ከማኛ አምራችነት እስከ ልምላሜዉ ባህሉን እሴቱን አኗኗሩን ከ እነማይ ኤልያስ ዳሞት ደጀን ጉዛምን ማርቆስ ዘጌ እነሴ ዘልቀው በዜማ በግጥም በምስልም እንድናይ አድርገዋል ።

ኪነት ከከፍተኛ ቁጥጥር ወደ ስርአት አልባ የገበያ ውድድር ከጫፍ ወደ ጫፍ በዘለለችበት ዘመንና ብዙ የሚነገርለትን ማህበረሰብ ስሜት በመኮርኮር አንጋች በማስመሰል ለሸቀጥ በሚዉልበት መድረክ የአማራ ህዝብ ጀግንነቱ በጦረኝነት ብቻ አለመሆኑን ስላሳያችሁ እናመሰግናለን ።

በነገራችን ላይ በሀገራችን የባህል ሙዚቃዎች ታሪክ በበርካቶች እይታ በማግኘት ቀዳሚዉ የጎጃምኛ ሙዚቃ ቀጥሎ ትግርኛ ናቸዉ ። ብዙ የተዘፈነላት ደግሞ ጎንደር ።

የማን ነህ እያሉት ኮራ አለ ጅንኑ
ከየት ነህም ሲሉት ዝም አለ ጅንኑ
ያስታዉቅ የለም ወይ ጎጃሜ መሆኑ

Via:- በታዴየማመይልጅ

የውበትና የግርማ ሞገስ መገለጫ የሆም አበባ !" እንደ ሆማ ቅጠል ዘራቸዉ ለምለም ግዬንን ተችረዉ ከአለም ምድራቸዉ ለምለም ነዉ ጎጃም "በጎጃም ሰርግ ላይ “የሆም አበባዬ” እየተባለ የሚዜመው...
17/05/2026

የውበትና የግርማ ሞገስ መገለጫ የሆም አበባ !

" እንደ ሆማ ቅጠል ዘራቸዉ ለምለም
ግዬንን ተችረዉ ከአለም
ምድራቸዉ ለምለም ነዉ ጎጃም "

በጎጃም ሰርግ ላይ “የሆም አበባዬ” እየተባለ የሚዜመው ዜማ የማኅበረሰቡን ሥነ-ውበት፣ የተፈጥሮ ትስስርና ማኅበራዊ ፍልስፍና የያዘ ትልቅ የባህል መገለጫ (Cultural Expression) ነው።

የሆም አበባ ቅጠሉ ሰፋፊ ለምለም ዛፍ ነው። ​የሆም አበባ ተፈጥሯዊ ዛፍ ቢሆንም በፎክሎር ጥናት እንደቁሳዊ ባህል (Material Culture) ምንነቱና እና ትዕምርታዊ (Symbolic) ትንታኔው ይፈከራል፦

​፩. የሆም አበባ ምንድነው?
​በእፅዋት ሳይንስና በጎጃም አካባቢ የአነጋገር ዘይቤ “ሆም” ወይም “ኮም” የሚባለው፣ በኢትዮጵያ ደጋማና ወይና-ደጋማ አካባቢዎች (በተለይም በጎጃም የምድር ገጽታ ላይ) በብዛት የሚበቅል፣ ቁጥቋጦአማ በጣም ያላጠረ በጣምም የማይረዝም የዛፍ ዝርያ ነው። (ዮሐንስ አበራ 2013)

የሆም ዛፍ አበባ ሲያብብ እጅግ ያማረ፣ ደስ የሚል መዓዛ ያለውና ፈካ ያለ ነጭ ወይም ቢጫማ መልክ የሚይዝ ነው።
​በማኅበረሰብ ዘንድ ይህ አበባ የንጽሕና፣ የውበት፣ የጥሩ መዓዛና የልምላሜ፤ ማሳያ ተደርጎ ይወሰዳል። በሠርግ ዘፈን ውስጥ የሆም አበባዬ ተብሎ የሚነገረው ለሙሽሪት (አልፎ አልፎም ለሙሽራው) ሲሆን፣ ሰውን ከአካባቢው ተፈጥሮ ጋር በማዛመድ የሚሰጥ የክብር ስም ነው።

​፪. ትዕምርታዊ ትንታኔ፦ በጎጃም የሆም አበባ ትዕምርታዊ ትርጉም አለው።
​ሀ. የንጽሕና ትዕምርት
​የሆም አበባ በተፈጥሮው ንጹሕና ሳቢ ነው። በሠርግ ሥነ-ሥርዓት ላይ ሙሽሪትን የሆም አበባዬ ማለት፣ ሙሽሪት በቤተሰቦቿ ዘንድ በጥንቃቄ ተጠብቃ የኖረች፣ ንጽሕናዋን ድንግልናዋን የጠበቀችና ለትዳር የበቃች መሆኗን ማብሰሪያ ነው። ልክ አበባው በጫካው ውስጥ ተለይቶ ከችግኝ እስከ አበባ እንደሚበቃ ሁሉ፣ እሷም በቤተሰቧ መሐል አድጋ ለትዳር ማዕረግ መብቃቷን ያሳያል። (አበባው ገረመው 2011)

​ለ. የተስፋና የልምላሜ፦ ​አበባ የፍሬ መጀመሪያ ነው። ሆም አብቦ ወደ ፍሬ ይሸጋገራል። ስለዚህ በሠርግ ላይ ይህንን አበባ መጥራት ሙሽሮቹ አዲስ ሕይወት ሲጀምሩ እንደ አበባው አብበው፣ እንደ ፍሬው ተክተው፣ ልጅ ወልደው እንዲስፋፉና እንዲባረኩ የሚቀርብ የቀደመ ባህላዊ ምርቃትና ምኞት መግለጫ ነው።

​ሐ. የውበትና የግርማ ሞገስ፦ ​የጎጃም የሠርግ ግጥሞች የሰውን ውበት ከተፈጥሮ ጋር የማዋሃድ ከፍተኛ ጥበብ አላቸው። ሙሽሪትን የሆም አበባ ማለታቸው፣ ውበቷ ሰው ሠራሽ ያልሆነ፣ የተፈጥሮና የአካባቢውን ለምለም ገጽታ የተላበሰ መሆኑን ለመግለጽ ነው።

​መ. የማኅበረሰባዊ ትስስርና የይዞታ መግለጫ፦ ​የሆም ዛፍ በየጓሮውና በየዱሩ የሚበቅል፣ ሀገር በቀል እፅዋት ነው። ሙሽሪትን በዚህ አበባ መመሰል የእኛ አካባቢ ፍሬ፣ የእኛ አገር ቡቃያ፤ የማለት የባለቤትነትና የኩራት ስሜትን ይፈጥራል። ከአካባቢው ማኅበራዊ ሥነ-ልቦና ጋር ጥብቅ ቁርኝት እንዳላት ያሳያል። (አበባው ገረመው 2011)

​፫. የዜማና ግጥም እይታ፦ የጎጃም ሕዝብ ሥነ-ቃል (Oral Literature) ከተፈጥሮ ቁሳቁስ (Material Nature) ጋር ምን ያህል የተቆራኘ መሆኑን ያሳያል። ማኅበረሰቡ ደስታውን፣ ምኞቱንና የውበት መለኪያውን የገለጸው ከሩቅ አገር በመጣ ፈሊጥ ሳይሆን፣ በእለት ተእለት ሕይወቱ በሚያየውና በሚያሸተው የሆም አበባ ነው። (ዮሐንስ አበራ 2013)

​ስለዚህ የሆም አበባዬ የሚለው ስያሜ ተራ የሰርግ ማጀቢያ ሳይሆን፣ የሴትነት ክብር፣ የትውልድ ቀጣይነት እና የአካባቢያዊ ማንነት መገለጫ ተደርጎ የሚወሰድ ጥልቅ ትዕምርት ነው።

የማጣቀሻ
►አበባው ገረመው (2011)፦ በምሥራቅ ጎጃም ዞን የሚገኙ የሠርግ ዘፈኖች ይዘትና ውበት ትንታኔ። አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ።
► ዮሐንስ አበራ (2013)፦ እፅዋት በሥነ-ቃል፦ የአበባና ዛፎች ትዕምርታዊ ትርጉም በኢትዮጵያ ሰርግ። የፎክሎርና ባህል ጥናት መጽሔት።

የሀብከ ብርሃኔ ጥላሁን

''በዘጠኝ ሰከንድ 17ሰው መግደል እችላለሁ'' የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት አባል ሰውየው እንደሚለው መንግስት ወደ ሩስያ የላከው ወታደራዊ ስልጠና እንዲያገኝ ነው፣ ይሁንና ማህበራዊ ሚድያ ላ...
17/05/2026

''በዘጠኝ ሰከንድ 17ሰው መግደል እችላለሁ'' የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት አባል

ሰውየው እንደሚለው መንግስት ወደ ሩስያ የላከው ወታደራዊ ስልጠና እንዲያገኝ ነው፣ ይሁንና ማህበራዊ ሚድያ ላይ ግን ''በዘጠኝ ሰከንድ 17 ሰው መግደል እችላለሁ እያለ እንደ ጀብድ እያወራ ነው።

ለቁጥር የሚታክት ህዝብ በየቀኑ የጥይት ሰለባ በሚሆንበት ሀገር እንዲህ አይነት የጅምላ ግድያ መልዕክት ከመከላከያ ሰራዊት አባል መተላለፉ ታስቦበት ወይስ ሌላ? የሀገር ዳር ድንበር ያስጠብቃል የተባለ ተቋምን የሰው ልጅን በጅምላ ከመግደል ጋር አያይዞ ማቅረብ መልሶ ራስን መግረፍ ነው።

ሀገሬን ልጠብቅ እና ዘብ ልሆን ነው ማለት እያለ ያውም ከሌላ ሀገር ጋር ሊዋጋ ሳይሆን የአንድ ሀገር ህዝብ በእርስ በርስ ጦርነት በሚጫረስባት ሀገር ላይ ሌላ ወንድሙን ለመግደል ይሄ ሁላ... ያሳዝናል።

ህዝቡ ችግሩን የሚቀርፍለት እንጂ የሚገድለው መቼ አጣ?

Via:- Elias Meseret

''ከአውሮፓ፣ ከአሜሪካ እየመጡ በኢትዮጵያ እድገት እና ለውጥ እየተደመሙ ነው'' አዲስ አበባ ብቻ ኢትዮጵያ ናትን?ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ በተለያዩ ጊዜያት በሚያደርጓቸው ንግግሮች፤ ዓ...
17/05/2026

''ከአውሮፓ፣ ከአሜሪካ እየመጡ በኢትዮጵያ እድገት እና ለውጥ እየተደመሙ ነው'' አዲስ አበባ ብቻ ኢትዮጵያ ናትን?

ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ በተለያዩ ጊዜያት በሚያደርጓቸው ንግግሮች፤ ዓለም በኢትዮጵያ እድገት እና ለውጥ ቢደመምም በርካታ ኢትዮጵያውያን ግን የተሰራውን ስራ በቅጡ ለመገንዘብ እና ለማድነቅ እንደሚያዳግታቸው ሲናገሩ ተደምጠዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ትላንት ቅዳሜ ግንቦት 8፤ 2018 በተካሄደ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ ላይ ባደረጉት ንግግርም ይህንኑ አቋማቸውን ደግመውታል።

ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ንግግሩን ያደረጉት በአዲስ አበባ ከተማ የተገነባው የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ ምርቃት መርሃ ግብር ላይ እንዳነሱት ከውጭ ሀገራት የሚመጡ ሰዎችን ያስደሰተ ያሉትን የኢትዮጵያን የኢኮኖሚ ዕድገት አንስተዋል።

ኢትዮጵያ 10.2 ፐርሰንት የምታድግ ብቸኛ አገር ናት ያሉ ሲሆን በድፍን አፍሪካ 10.2 ፐርሰንት እድገት የሚያድግ አንድም ሃገር የለም ብለዋል።

አዲስ አበባ ብቻ ኢትዮጵያ ናትን?

ሀሳብዎን ያካፍሉን?

''ኢትዮጵያ ውስጥ የስራ ሳይሆን የሰራተኛ ችግር ነው ያለው ስራ በየቦታው አለ።  የውጭ ሀገር ዜጎችን እየተጠቀምን ነው፤ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ''በዛሬው ዕለት በገላን ጉራ ኢንዱስት...
16/05/2026

''ኢትዮጵያ ውስጥ የስራ ሳይሆን የሰራተኛ ችግር ነው ያለው ስራ በየቦታው አለ። የውጭ ሀገር ዜጎችን እየተጠቀምን ነው፤ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ''

በዛሬው ዕለት በገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ ምረቃ ስነ-ስርዓት ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ባስተላለፉት መልዕክት ኢትዮጵያ ውስጥ ሰራተኛ ማግኘት ከባድ ነገር ሆኗል። ወጣቱ ስራ እያለ መስራት አልቻለም ሲሉ ወቅሰዋል። በየቦታው በምንሰራው ስራ ላይ እንቅፋት እየሆነ የመጣው የጉልበት ሰራተኛ ችግር ነው በማለት አብራርተዋል።

ኢትዮጲያ ውስጥ የስራ ሳይሆን የሰራተኛ ችግር ነው ያለው፤ሌላው ቀርቶ የቤት ሰራተኛ እንኳን ማግኘት ችግር ነው ያሉ ሲሆን ይህን ችግር ለመግረፍ የውጭ ዜጎችን ለመጠቀም ተገደናል በማለት'' ለምሳሌ ያክል የቻይና፣ ፊሊፒንስ፣ ኬኒያና ናይጀሪያ ዜጎችን በስፋት እያሳተፍን ነው ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመልዕክታቸው

በጠቅላይ ሚኒስትሩ መልዕክት እርሰዎ ምን ይላሉ ሃሳብዎን ያካፍሉን?

''አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ፡ በሙስሊም ተማሪዎች የኒቃብ ጥያቄና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ ውይይት ተካሄደ''አዲስ አበባ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ የሚማሩ ሙስሊም ተማሪዎች ባነሱት የኒቃብ አጠ...
16/05/2026

''አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ፡ በሙስሊም ተማሪዎች የኒቃብ ጥያቄና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ ውይይት ተካሄደ''

አዲስ አበባ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ የሚማሩ ሙስሊም ተማሪዎች ባነሱት የኒቃብ አጠቃቀም መብት ጥያቄ ዙሪያ፣ ትናንት ምሽት ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ሰፊ ውይይት መደረጉ ተሰማ።

ተማሪዎቹ ያለምንም የኒቃብ ክልከላ ትምህርታቸውንና ሌሎችንም የካምፓስ አገልግሎቶች ማግኘት በሚችሉበት ሁኔታ ላይ ትኩረት ያደረገው ይህ ውይይት፤ ውጥረቶችን በማርገብ ረገድ ተስፋ ሰጪ ስምምነት ላይ ደርሷል።

በከፍተኛና መደበኛ የትምህርት ተቋማት ውስጥ በተደጋጋሚ የሚስተዋለው የሂጃብና የኒቃብ ክልከላ በተማሪዎች ስነ-ልቦና እና የመማር ማስተማር ሂደት ላይ ከፍተኛ ጫና ሲፈጥር መቆየቱ ይታወቃል። በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲም ይህ ጉዳይ ለረጅም ጊዜ እልባት ሳያገኝ በመቆየቱ፣ ተማሪዎች በትምህርታቸው ላይ ትኩረት ለማድረግ መቸገራቸውን ሲገልጹ ቆይተዋል።

ይህንኑ ተከትሎ፣ ተማሪዎቹ መብታቸው እንዲከበርና ዘላቂ ምላሽ እንዲሰጣቸው በመጠየቅ ዓርብ ግንቦት 7/2018 ዓ.ል. ከቀኑ 7፡00 ሰዓት ጀምሮ በዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ጽሕፈት ቤት በር ላይ በሰላማዊ መንገድ በመሰብሰብ እስከ ምሽቱ 4፡30 ድረስ ድምጻቸውን አሰምተዋል።

የተማሪዎቹን ጥያቄ ተመልክቶ መፍትሔ ለመፈለግ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የፕሬዝዳንት ፅህፈት ቤት ሃላፊ እና የሂጃብ ጉዳይ ኮሚቴ ሰብሳቢ ኡስታዝ አቡበከር አህመድ የተመራ ልዑክ በቦታው ተገኝቷል። ልዑኩ ከተማሪዎቹ ተወካዮች እና ከዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ጋር ያደረገውን ጥልቅ ውይይት ተከትሎ የሚከተሉት ውሳኔዎች ተላልፈዋል፦

ተማሪዎቹ ለቀረበው የመብት ጥያቄ ዘላቂና የመጨረሻ ውሳኔ እስኪያገኙ ድረስ፣ ኒቃባቸውን ለብሰው የመማርም ሆነ ሌሎች የዩኒቨርሲቲውን አገልግሎቶች ያለምንም እገዳ የማግኘት መብታቸው ተረጋግጧል።

በዚህም መሰረት ተማሪዎቹ በጊዜያዊነት ወደ ትምህርት ገበታቸውና ወደ ማደሪያ ክፍሎቻቸው (ዶርማቸው) እንዲመለሱ ስምምነት ተፈጥሯል።

የኮሚቴው ሰብሳቢ ኡስታዝ አቡበከር አህመድ እንደገለጹት፤ የተጀመረው የውይይት መድረክ ተጠናክሮ የሚቀጥል ሲሆን፣ የተማሪዎቹ የመብት ጥያቄ ሙሉ በሙሉ ዘላቂ ምላሽ እንዲያገኝ በቁርጠኝነት ይሰራል ብለዋል።

በዚህ ወሳኝ የሰላም ውይይት ላይ በርካታ ከፍተኛ አመራሮች የተገኙ ሲሆን፣ ከእነዚህም መካከል፦

• ኡስታዝ ሺሐቡዲን ሸህ ኑራ (የአዲስ አበባ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት የአስተዳደርና ተቋማት ልህቀት ምክትል ፕሬዝዳንት)

• ኡስታዝ አዩብ ደርባቸው (የስራ አስፈፃሚ አባል)

• ሃጂ ሪያድ ጀማል (ዋና ስራ አስኪያጅ) ይገኙበታል።

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት (መጅሊስ) ይህንን የኒቃብና ሂጃብ ክልከላ ችግር በዘላቂነት ለመፍታት ከዚህ ቀደምም ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር ተደጋጋሚ ውይይቶችን ሲያደርግ መቆየቱ ይታወሳል።

Via:- የአዲስ አበባ እስልምናን ጉዳዮች ከፍተኛ ም/ቤት

''የደብረ ማርቆስ አውሮፕላን ማረፊያ የመጀመሪያ የሙከራ በረራውን በስኬት አስተናገደ''‎ግንቦት8/2018ዓ.ም የደብረ ማርቆስ ከተማና የአካባቢው ማህበረሰብ ለብዙ አመታት በጉጉት ሲጠብቀው የ...
16/05/2026

''የደብረ ማርቆስ አውሮፕላን ማረፊያ የመጀመሪያ የሙከራ በረራውን በስኬት አስተናገደ''

‎ግንቦት8/2018ዓ.ም የደብረ ማርቆስ ከተማና የአካባቢው ማህበረሰብ ለብዙ አመታት በጉጉት ሲጠብቀው የነበረው የደብረ ማርቆስ አውሮፕላን ማረፊያ የመጀመሪያውን የሙከራ በረራ በዛሬው ዕለት በስኬት አስተናግዷል።

‎ይህ ታሪካዊ ክስተት ለአካባቢው የኢኮኖሚ፣ የንግድና የቱሪዝም እንቅስቃሴ አዲስ ምዕራፍ የከፈተ ታላቅ ስኬት መሆኑ ተገልጿል።


‎​የአውሮፕላን ማረፊያው የደብረ ማርቆስና አካባቢውን ህዝብ የልማት ጥያቄ የመለሰና ደብረ ማርቆስን ከሌሎች የሃገሪቱ ክፍሎች ጋር በቅርብ የሚያስተሳስር የልማት ምሰሶ ነው ሲሉ የአስተዳደሩ የስራ ሃላፊዎች ገልጸዋል።


‎የመጀመሪያ በረራ በተሳካ ሁኔታ መጠናቀቁን ተከትሎ በቀጣይ መደበኛ በረራዎች የሚቀጥሉ ሲሆን ይህም የከተማዋን ሁለንተናዊ የዲጂታልና የማህበራዊ ትስስር ይበልጥ እንደሚያሳድገው ይጠበቃል።

Via:- ደብረ ማርቆስ ኮሙኒኬሽን

''በትግራይ ክልል አዲስ ኃይል ስልጣን እንዲረከብ ፌደራል መንግስት እገዛ ያድርግ'' ጄ/ል ሳሞራ የኑስየትግራይ ክልልን ስልጣን የሚረከብ አዲስ ኃይል እንዲመጣ ፌደራል መንግስት ኃላፊነት ወስ...
16/05/2026

''በትግራይ ክልል አዲስ ኃይል ስልጣን እንዲረከብ ፌደራል መንግስት እገዛ ያድርግ'' ጄ/ል ሳሞራ የኑስ

የትግራይ ክልልን ስልጣን የሚረከብ አዲስ ኃይል እንዲመጣ ፌደራል መንግስት ኃላፊነት ወስዶ ግፊት ያድርግ ሲሉ ጄነራል ሳሞራ የኑስ ጥሪ አቀረቡ። ሰሞኑን የተደረገው ''የፈርሰ ምክር ቤትን ተጠቅሞ ውዝፍ አመራር ወደ ስልጣን የመመለስተግባር'' ህዝቡን ለከፍተኛ ስጋትና ጭንቀት የዳረገ ክስተት ብለውታል።

የቀድሞው የኢፌዲሪ ጠቅላይ ኤታማጆር ሹም ጄነራል ሳሞራ የኑስ፣ ወቅታዊውን የትግራይ ፖለቲካዊ ሁኔታ አስመልክተው ዛሬ ከወጋሕታ ጋዜጣ ጋር በትግርኛ ቋንቋ ባካሄዱት ቃለምልልስ እንደገለጹት፣ የህወሓት አመራሮች ሰሞኑን የወሰኑት ህገወጥ ውሳኔ ህዝባዊ ድጋፍ ያለው እንዲመስል ብዙ የፕሮፖጋንዳ ስራ ቢሰራበትም እውነታው ግን ከመቶ በማይበልጡ ሰዎች ምክክር ብቻ ውስጥ ለውስጥ ተወስኖ ተግባራዊ የተደረገ የጥቂቶች ፍላጎት መሆኑን አብራርተዋል።

ድርጊቱን "በጣም መጥፎ" ሲሉ የገለጹት ጄነራል ሳሞራ በሀገር ውስጥም ሆነ በውጭ የሚገኘው የትግራይ ተወላጅ በዚህ ድርጊት እጅግ መቆጣቱን ገልጸው የዚህ ዋና አላማ ደግሞ "ስልጣንን ለማስቀጠልና ከተጠያቂነት ለማምለጥ ታሳቢ ያደረገ ተግባር" ሲሉ ገልጸውታል።

በጄ/ል ሳሞራ እምነት ይህ የ"እንጠየቃለን" ስጋት የፖለቲከኞቹ ብቻ ሳይሆን የክልሉ ወታደራዊ አዛዦች ስጋትም ጭምር እንደሆነ በማብራራት ሁለቱም ተቀናጅተው ይህን ያስፈጸሙበት ምክንያት "ተጠያቂ እንሆናለን" ከሚል ስጋት የመነጨ እንደሆነ ያብራራሉ።

ጄነራሉ በዚሁ ቃለምልልሳቸው የሰሞንኛው እንቅስቃሴ ዋና አላማ "ስልጣንን ለማስቀጠልና ከተጠያቂነት ለማምለጥ" መሆኑን ቢገልጹም እንደገና መልሰው ደግሞ የዚሁ እንቅስቃሴ ዋና ዓላማ "የፌዴራል መንግስት የሚያካሂደውን ሀገራዊ ምርጫ ለማስተጓጎል ያለመ" ሊሆን እንደሚችል ግምታቸውን ይገልጻሉ።

የፌዴራል መንግስት ጉዳዩን በረጋ መንፈስ እና በብስለት ሊፈታው እንደሚገባ የሚመክሩት ጄነራል ሳሞራ፣ የትግራይ ህዝብ ከዚህ በላይ እነዚህን አመራሮች መታገስ እንደሌለበት በአጽንኦት ገልጸው ፌደራል መንግስት ኃላፊነት ወስዶ አዲስ ኃይል መጥቶ ስልጣን እንዲረከብ ግፊት እንዲያደርግ አሳስበዋል።

ጄነራሉ "ወደፊት መጥቶ ስልጣን ይረከብ" የሚሉት አዲስ ኃይል የትኛው ኃይል እንደሆነ ግን በዚሁ ቃለምልልሳቸው በዝርዝር አልገለጹም።

አውራምባ
#በዝርዝር #ሸር

16/05/2026

ትውልዱ ስራ አጥቶ፣ በ9ወራት 98ቢሊዮን ብር የሀገር ሀብት ይዘረፋል'' ፓለቲካ አበበ አካሉ ይናገራሉ Full video on YouTube https://youtu.be/sv3LJAG0oC4?si=aC8TuftbSsCClpFZ

''አዲስ አበባ ላይ ጎዳና የሚያስወጣ እና ምግብ የሚያስለምን ነገር የለም''ክብርት ከንቲባችን አዳነች አበቤ " አዲስ አበባ ላይ ጎዳና የሚያስወጣ ነገር ምግብ የሚያስለምን ነገር ምን እንደሆ...
15/05/2026

''አዲስ አበባ ላይ ጎዳና የሚያስወጣ እና ምግብ የሚያስለምን ነገር የለም''

ክብርት ከንቲባችን አዳነች አበቤ " አዲስ አበባ ላይ ጎዳና የሚያስወጣ ነገር ምግብ የሚያስለምን ነገር ምን እንደሆነ ምክንያቱን አላውቅም።

በአሁኑ ሰአት አዲስ አበባ ላይ ምግብ የሚያስለምን ምንም ምክንያት የለም። በየምገባ ማእከሎቻችን ትኩስ የተመጣጠነ ጣፋጭ ምግብ ተዘጋጅቶ ይጠብቃችሗል ጎራ ብላችሁ በነፃ መብላት ብቻ ነው ከናንተ የሚጠበቀው "ብላለች።

ምን ትጠብቃላችሁ በዚህ በተወደደ ኖሮ ጎራ እያላችሁ ብሉ እንጅ

Address


Telephone

+251929332211

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Wollo Addis posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Wollo Addis:

  • Want your business to be the top-listed Media Company?

Share