Zegabi Zegabi is Ethiopian news and views online journal published by Mereja Media. It is based in Maryland, USA.

06/24/2026

አፋብን ለአውሮፓ ህብረት የህግና ፍትህ ማዕከል ደብዳቤ ላከ።

እለታዊ ዜና | የሸዋ ግንባሮች ትንቅንቅ | የምኒልክ እዝ መኮንኖች ምረቃ | በወለጋ የድሮን ጥቃት ተፈፀመ June 24, 2026
06/24/2026

እለታዊ ዜና | የሸዋ ግንባሮች ትንቅንቅ | የምኒልክ እዝ መኮንኖች ምረቃ | በወለጋ የድሮን ጥቃት ተፈፀመ June 24, 2026

Enjoy the videos and music you love, upload original content, and share it all with friends, family, and the world on YouTube.

06/23/2026

የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው እዝ ጠቅላላ ጉባኤ አካሄደ።

https://youtu.be/C8zZN4vr9y0

ሰበር | የአማራሳይንቱ ድል | በሸዋ ደራ የንፁሃን እልቂት | ትብብር ለኢትዮጵያ ፓርቲ ወንበሩን ውድቅ አደረገ June 23, 2026
06/23/2026

ሰበር | የአማራሳይንቱ ድል | በሸዋ ደራ የንፁሃን እልቂት | ትብብር ለኢትዮጵያ ፓርቲ ወንበሩን ውድቅ አደረገ June 23, 2026

Enjoy the videos and music you love, upload original content, and share it all with friends, family, and the world on YouTube.

ሰበር | የዳውንቱ አሳዛኝ ክስተት | የህወሓት ጥቃት በአፋር ክልል | ሁለት ሬጅመንት ያለቀበት የወለጋው ውጊያ  June 22, 2026
06/22/2026

ሰበር | የዳውንቱ አሳዛኝ ክስተት | የህወሓት ጥቃት በአፋር ክልል | ሁለት ሬጅመንት ያለቀበት የወለጋው ውጊያ June 22, 2026

Enjoy the videos and music you love, upload original content, and share it all with friends, family, and the world on YouTube.

06/18/2026

በአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ቁጥጥር ስር በሚገኙ አካባቢዎች የ6ኛ ክፍል እና የ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተናዎች ያለምንም የጸጥታ ችግር እየተሰጡ መሆኑ ታውቋል።

በትግል ቀጠናዎች ውስጥ መማርና ማስተማርን ማስቀጠል የህልውናው ተጋድሎ አንዱ አካል መሆኑን የገለጹት የዕዙ አካላት፣ የተማሪዎችን እና የመምህራንን ደህንነት አስተማማኝ ለማድረግ ጥበቃ እየተደረገ መሆኑን አስታውቀዋል። ይህ ወታደራዊ መዋቅር በአንድ በኩል የሚሰነዘሩበትን ጥቃቶች እየመከተ፣ በሌላ በኩል ደግሞ ትውልዱ በትምህርት እንዳይሰናከል የራሱን ሚና እየተወጣ እንደሚገኝ ከአካባቢው የወጡ መረጃዎች ያመላክታሉ።

የአካባቢው ነዋሪዎችና የትምህርት ባለሙያዎች እንደሚያስረዱት፣ በአሁኑ ወቅት በአማራ ክልል ውስጥ ባለው ወቅታዊ ሁኔታ ምክንያት በርካታ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ እሴቶች ተጎድተዋል። የአገዛዙ ባለስልጣናት ማህበረሰቡን በስነ-ልቦና እና በኢኮኖሚ ለማዳከም የተለያዩ እቅዶችን እያወጡ በሚንቀሳቀሱበት በዚህ ፈታኝ ወቅት፣ የትምህርት ተቋማት ክፍት ሆነው እንዲቀጥሉ መደረጉ ትልቅ ትኩረት ስቧል።

የፋኖ ኃይሎች በበኩላቸው የአካባቢውን ሰላም በማረጋገጥ የፈተና ሂደቱ ያለምንም ስጋት እንዲጠናቀቅ የጀርባ አጥንት መሆናቸውን ይናገራሉ።በተለያዩ ዞኖች የአገዛዙ ኃይሎች የፈተናውን ሂደት ለማደናቀፍና የትምህርት ተቋማትን አገልግሎት ለማቋረጥ ወታደራዊ ሙከራዎችን ቢያደርጉም፣ በዕዙ የጸጥታ መዋቅር ጥረት ሳይሳካላቸው መቅረቱ ተገልጿል።

ከ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ፈተናዎች በተጨማሪ፣ ከአንዳንድ አካባቢዎች በተገኙ መረጃዎች መሰረት ከ9ኛ እስከ 11ኛ ክፍል ያሉ ተማሪዎች የሁለተኛ መንፈቅ ዓመት ማጠቃለያ ፈተናቸውን ያለምንም የደህንነት ስጋት መውሰድ ችለዋል። ይህ ስኬት ሊመዘገብ የቻለው ዕዙ ባደረገው ሁለንተናዊ የደህንነት ጥበቃ እና የሎጂስቲክስ ድጋፍ እንደሆነ የአካባቢው አስተማሪዎች አረጋግጠዋል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ የአገዛዙ ኃይሎች በተለያዩ ማህበረሰቦች ውስጥ የሚገኙ የትምህርት ተቋማትን በከባድ መሳሪያዎችና በድሮን በመምታት ጉዳት ማድረሳቸውን የሰብአዊ መብት ተሟጋቾች በተደጋጋሚ ሲያጋልጡ ቆይተዋል። ይህንን ሴራ ቀድሞ በመረዳት ትምህርት ቤቶች እንዳይዘጉ ማድረግ መቻሉን የገለጹት የዕዙ አመራሮች፣ መምህራን ያለምንም ፍርሃት ሙያዊ ግዴታቸውን እንዲወጡ ሌት ተቀን እየሰሩ መሆኑን አስታውቀዋል። ይህ ሂደት የፋኖ ኃይሎች ለወታደራዊ ግዳጅ ብቻ ሳይሆን ለማህበረሰቡ ዘላቂ ደህንነትና ለነገው ትውልድ ግንባታ ትኩረት የሚሰጡ መሆናቸውን የሚያሳይ ተግባራዊ ማስረጃ ተደርጎ ተወስዷል።

ሰኔ 11/2018 ዓ.ም
ዘጋቢ ሚዲያ

06/18/2026

የብልፅግና አገዛዝ በዓለምአቀፍ ሪፖርት ተጋለጠ።

ዓለም አቀፉ የትምህርት ተቋማትን ከጥቃት የመከላከል ጥምረት (GCPEA) ባወጣው አዲስ ይፋዊ ሪፖርት መሠረት፣ ባለፉት ሁለት ዓመታት ውስጥ በዓለም አቀፍ ደረጃ በትምህርት ቤቶች፣ በተማሪዎች እና በመምህራን ላይ የሚፈጸሙ ጥቃቶች አስደንጋጭ ደረጃ ላይ ደርሰዋል። በዚህም መሠረት ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ጥቃት ከተመዘገቡባቸው የዓለም ግንባር ቀደም ሀገራት መካከል ኢትዮጵያ አንዷ ሆና ተመዝግባለች።

በትናንትናው ዕለት ይፋ በሆነው «ትምህርት በሰይፍ ስር 2026» በተሰኘው በዚህ ዓለም አቀፍ ሪፖርት ላይ፣ በሀገሪቱ ያለው የጸጥታ መበላሸት በትምህርት ማህበረሰቡ ላይ ያሳደረው ቀውስ በዝርዝር ተቀምጧል።ይህ ተቋም በዓለም ዙሪያ ባደረገው የሁለት ዓመት ጥናት፣ በ2024 እና በ2025 ዓመታት መካከል ብቻ ቢያንስ 8 ሺህ 566 በትምህርት ተቋማት ላይ ያነጣጠሩ ጥቃቶችን መዝግቧል።

ይህ ቁጥር ካለፈው የሪፖርት ጊዜ (ከ2022 እና 2023) ጋር ሲነጻጸር ከ40 በመቶ በላይ ከፍተኛ ጭማሪ ያሳየ መሆኑ በጥናቱ ተረጋግጧል። በዓለም አቀፍ ደረጃ ይህ መቅሰፍት በከፍተኛ ሁኔታ ከታየባቸው ስድስት ሀገራት መካከል ኢትዮጵያ ከኮሎምቢያ፣ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ፣ ሄይቲ፣ ፍልስጤም እና ዩክሬን ጋር እኩል ስሟ ተጠቃሽ ሆኗል።

ሰኔ 11/2018
ዘጋቢ ሚዲያ

የአርበኛ ብሩክ ስለሺ መልዕክት ስለ ደራ።በየትኛውም ቦታ በየትኛውም ሁኔታ ህዝባችን ላይ የሚደርሰውን በደል ዝም ብለን አናይም። የአማራን ሁለንተናዊ የህልውና አደጋ ቀልብሰን በልኩ ታፍሮና ተ...
06/18/2026

የአርበኛ ብሩክ ስለሺ መልዕክት ስለ ደራ።

በየትኛውም ቦታ በየትኛውም ሁኔታ ህዝባችን ላይ የሚደርሰውን በደል ዝም ብለን አናይም። የአማራን ሁለንተናዊ የህልውና አደጋ ቀልብሰን በልኩ ታፍሮና ተከብሮ እንዲኖር የማድረግን ታሪካዊ ምዕራፍ በድል እናጠናቅቀዋለን።

በደራ በህዝባችን ላይ እየደረሰ ያለውን ግፍና በደል እያደረሰ ያለው ወሮበላ ቡድን በሚገባው ቋንቋ እናናግረዋለን። የብልፅግናው ዘር ዓጥፊ ስርዓት በስውርም በግልፅም ባዋቀረው አጥፊ ቡድን ህዝባችንን ለማጥፋት ሌት ተቀን እንደሚሰራ ከቅጥፈት ምርጫ ማግስት በአሩሲ የጀመረውን ጭፍ*ጨፋና ግድ*ያ አጠናክሮ ጫካ ባስቀመጠው ሸኔ እንዲሁም በአገልጋዩ ሰራዊት ህዝቡ ላይ እርምጃ እየወሰደ ይገኛል።

ስለዚህ በተለይ የደራና አካባቢው ሚኒሻ ከዚህ በፊት በተደጋጋሚ አድርገነው በነበረው ጥሪ መሰረት ከወንድምህ ፋኖ ጎን እንድትሰለፍ የቀረበልህን ታሪካዊ ጥሪ ተቀብለህ ለነፃነትህ እንድትታገል እያልኩ ሰሞኑን አገዛዙ እያደረገ እንዳለው በሸኔና በቅጥረኛ ሰራዊት መሃል እያስገባ እያስጨረሰህ መሆኑን አይተሃል ተረድተሃል።ህዝባችንን የነካውን ሃይል በሚገባው ቋንቋ ከዚህ በፊት እንደምናደርገው እናናግረዋለን።
ክብር ለተሰውት
ድል ለአማራ ህዝብ


!!

ሰበር | የደራ አማራዎች የድረሱልኝ ጥሪ | በጎንደር ትምህርትቤት በድሮን ተደበደበ | በወሎ እና በጎጃም የደፈጣ ጥቃት June 17, 2026
06/17/2026

ሰበር | የደራ አማራዎች የድረሱልኝ ጥሪ | በጎንደር ትምህርትቤት በድሮን ተደበደበ | በወሎ እና በጎጃም የደፈጣ ጥቃት June 17, 2026

Enjoy the videos and music you love, upload original content, and share it all with friends, family, and the world on YouTube.

Address

Washington D.C., DC

Telephone

+12026565117

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Zegabi posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Zegabi:

Share