Zeአራዳ

Zeአራዳ Melake:
Ethiopia's news & entertainment hub. Follow for updates! Bringing you the pulse of Ethiopia!

From breaking news to the hottest trends in entertainment, join our community and celebrate our rich culture.

የተወለደው በምድረ አንጾኪያ ሶርያ በ3ኛው መቶ ክ/ዘመን ነው፡፡ በቤተ ክርስቲያን የሰማዕታት አለቅነት ከተሰጣቸው ሰማዕታት አንዱ ነው፡፡ አባቱ ዮሐንስ በትውልድ ግብጻዊ የሆነ ክርስቲያን ነው...
27/07/2025

የተወለደው በምድረ አንጾኪያ ሶርያ በ3ኛው መቶ ክ/ዘመን ነው፡፡

በቤተ ክርስቲያን የሰማዕታት አለቅነት ከተሰጣቸው ሰማዕታት አንዱ ነው፡፡ አባቱ ዮሐንስ በትውልድ ግብጻዊ የሆነ ክርስቲያን ነው፡፡ እናቱ ግን አስቸጋሪና ጣዖት አምላኪ ሶርያዊት ነበረች፡፡

ባልና ሚስት አብረው ሲኖሩ ሚስት ባሏ ክርስቲያን መሆኑን አታውቅም ነበር፡፡ ቴዎድሮስ የእግዚአብሔር ስጦታ ማለት ነው፣ በተወለደ ጊዜ ግን ጠብ ተነሳ፡፡ እሱ ክርስትና ለማስነሳት፣ ሚስት ደግሞ ወደ ጣዖት ቤት ለመውሰድ ተጋጩ፡፡ ሚስት ወገኖቿ ባለስልጣኖች ናቸውና ልጁን ቀምታ ባሏን ዮሐንስን ወደ ግብፅ አሳደደችው፡፡ ዮሐንስ በስደት ባለበት ሃገር ስለ ልጁ ፈጽሞ ይጸልይ ሲያለቅስ እግዚአብሔር ልመናውን ሰማ፡፡ ማር ቴዎድሮስ ወጣት በሆነ ጊዜ ማንም ሳይጠራው ወደ ቤተ ክርስቲያን ሔዶ ተማረ፣ ተጠመቀ፡፡ በየዕለቱም ለጾምና ጸሎት፣ ለምጽዋት ጋር ያበዛ ድንግልናውንም ለመጠበቅ ይተጋ ነበር፡፡

ገና በ20 ዓመቱ ኃያልና ብርቱ፣ በጸባዩም የሚወደድ ቅን፣ መልከ መልካምም ሆነ፡፡ ከተወዳጅነቱ የተነሳም ነገሥታቱም የአንጾኪያ የጦር ሠራዊት አለቃ አድርገው ሾሙት፡፡ አሁንም ድረስ "የሠራዊት አለቃ" በሚለው ስያሜ የሚጠራው ማር ቅዱስ ቴዎድሮስ በተሳተፈባቸው ጦርነቶች ሁሉ ተሸንፎ አያውቅም፡፡ ይልቁኑ ጠላትን በመማረክ ነበር የሚታወቀው፡፡ በአንድ ወቅት ከፋርስ ሰዎች ጋር በተደረገ ጦርነት ብቻውን አሸንፏቸዋል፡፡ በዚህ ውጊያ የእግዚአብሔር መልአክ ከሰማይ ወርዶ ሰይፍ ሰጠው፡፡ ፋርሶችን "በከንቱ ከምትጠፉ ወደ ሃገራችሁ ተመለሱ" ሲላቸው ተሳለቁበት፡፡ ከፈረሱ ወርዶ ወደ ምስራቅ ዙሮ ጸልዮ በመስቀል ካማተበ በኋላ በመካከላቸው እየተመላለሰ በመልአኩ ሰይፍ ፈጽሞ አጠፋቸው፡፡

ማር ቴዎድሮስ አንድ ቀን ወደ አንድ ከተማ ሲገባ 24 ክንድ የሚረዝም ዘንዶ ሲመለክና የአንዲት ክርስቲያን ልጆችንም ለመስዋዕትነት ሲያቀርቧቸው ተመለከተ፡፡ በፈረሱ ላይም እንዳለ በስመ ሥላሴ አማትቦ ዘንዶውን በጦር ገደለው፡፡ ከጊዜ በኋላ ስለ አባቱ ያለውን እውነታ ሲሰማ አፈላልጎ አገኘው፡፡ ሕይወቱ እስኪያልፍም አብሮት ቆይቶ ወደ አንጾኪያ ሲመለስ ክርስቶስ ተክዶ፣ ጣዖት ቁሞ፣ አብያተ ክርስቲያናት ተቃጥለው፣ የክርስቲያኖች ደም ፈሶ፣ ከተማዋ በግፍ ተሞልታ ተመለከተ፡፡ ማር ቅዱስ ቴዎድሮስም በዚያች ሰዓት የክብር ልብሱን አውልቆ ባጭር ታጥቆ በንጉሡ ዲዮቅልጢያኖስ ፊት ቆሞ “እኔስ የክብር ባለቤት ክርስቶስን በፍጹም ልቤ አመልከዋለሁ፣ ለእርሱም ብቻ እሠዋለሁ::" አለ፡፡ ንጉሡም በቁጣ መሬት ላይ ጥለው እንዲደበድቡት አዘዘ፡፡ ወታደሮቹ ደሙ እስኪንጠፈጠፍ ገረፉት፡፡

ብዙዎች የሚመኙት ዓለማዊ ክብር ቢኖረውም ስለ ክርስቶስ ፍቅር ስጋን የሚያስመርር የተለያየ ስቃይ ሲያደርሱበት በደስታ ተቀበለው፡፡ በእሳት ሲያቃጥሉትም በጸሎቱ እሳቱን ውሃ አደረገው፡፡ ከበዛ ስቃዩም በእግዚአብሔር ኃይል ጸና፣ ታገሠም፡፡ በመጨረሻም ጌታችን በግርማ ወርዶ "ወዳጄ ቴዎድሮስ ስምህን የጠራ፣ መታሠቢያህን ያደረገ፣ ገድልህን ዜናህን የጻፈ፣ ያጻፈ፣ ያነበበ፣ ገዝቶ በቤቱ ውስጥ ያኖረውን ሁሉ እምርልሃለሁ፣ በስምህም ረድኤት ይደረጋል" ብሎት ዐረገ፡፡ ወታደሮቹ አንገቱን ሲሰይፉትም የክብር አክሊል ተቀብሏል፡፡ ተጋድሎውን አይተው ያመኑ እጅግ ብዙ ሺህ ሰዎችም አብረውት ተሰይፈዋል፡፡ ዓለምንና ክብራቸውን ስለክርስቶስ ፍቅር የናቁ ገዳማውያንም የጸሎታቸው በረከት ለብዙዎች ይተርፋል፣ የነፍስ ምህረት የስጋ ድህነት ያሰጣልና ገዳማቸውን እናግዝ በዓታቸውንም እናጽና፡፡


ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም

ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391

ወይም

አቢሲኒያ ባንክ
141029444

የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444

🌟 ማቭሪክ  ፕሮፌሽናል የመስታወት እና  አሉሚኒየም ሥራ  🌟በልዩ ጥራት  የሚከተሉትን አገልግሎቶች እንሰጣለን ✅ የአሉሚኒየም ተንሸራታች በር ና መስኮት✅ የቢሮ ፓርቲሽን ስራ✅ የደህንነት መ...
26/07/2025

🌟 ማቭሪክ ፕሮፌሽናል የመስታወት እና አሉሚኒየም ሥራ 🌟

በልዩ ጥራት የሚከተሉትን አገልግሎቶች እንሰጣለን

✅ የአሉሚኒየም ተንሸራታች በር ና መስኮት
✅ የቢሮ ፓርቲሽን ስራ
✅ የደህንነት መስታወት (Tempered Glass)
✅ የፈለጋችሁትን አይነት ዘመናዊ ሻወር ቦክስ
✅ ማንኛውም የመስታወት ሃንድሬል እና ሥራ
✅ ዘመናዊ የኮሪደር ስታንዳርድ አጥር ስራዎች

🔴 ማንኛውንም መስታወት በሚፈልጉት ሳይዝ Tempered አድርገን እናቅርባለን !

📞 ለምርጥ አገልግሎት ይደውሉ: +251 907 724 626

🏠 ጥራት | ዘመናዊ ዲዛይን | አስተማማኝ ስራ

እናመሰግናለን! 🙏

አጼ ሀይለ ስላሴ መሬት ወድቀዉ ለፈጣሪያቸዉ ሲፀልዩ🙏ሰላም ለሀገራችን💚💛❤መልካም ቀን‼️
26/07/2025

አጼ ሀይለ ስላሴ መሬት ወድቀዉ ለፈጣሪያቸዉ ሲፀልዩ🙏
ሰላም ለሀገራችን💚💛❤
መልካም ቀን‼️

26/07/2025

እንኳን ለመልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ በዓል አደረሳችሁ፤ አደረሰን!!!

መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል የልባችሁን መልካም መሻት ይሙላላችሁ!!!

ሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል ድንቅ ተአምር ያደረገበት ዕለት ነው ሐምሌ 19፡፡

ቅድስት ኢየሉጣ የሮም ግዛት በሆነው አንጌቤን በሚባል ሀገር በክርስትና ሃይማኖት በበጎ ምግባር፣ በፈሪሃ እግዚአብሔር ጸንታ ትኖር የነበረች ደግ ሴት ነበርች፡፡ ልጇ ቅዱስ ቂርቆስንም በስርዓት ነበር ያሳደገችው፡፡

በሐዋርያት ሥራ 14:21 “ወደ እግዚአብሔር መንግስት በብዙ መከራ እንገባ ዘንድ ያስፈልገናል” ተብሎ እደተጻፈ፣ ሰማዕታት ከአላውያን ነገስታት፣ ከአላውያን መኳንንት ዘንድ ስለ ሚያገኛቸው መከራ ሳይፈሩ ስለ ክርስቶስ አምላክነት መስክረው የክብር አክሊል ተቀዳጅተዋል፡፡ ከእነዚህ መካከል ገና በሶስት ዓመቱ ሰማዕትነትን የተቀበለው ቅዱስ ቂርቆስና እናቱ ቅድስት ኢየሉጣ ይገኙበታል፡፡ ቅድስት ኢየሉጣ በዘመኑ የነበረውን አረማዊ አስተዳዳሪ እለእስክንድሮስን በመፍራት ከልጇ ጋር ወደ ጠርሴስ ብትሰደድም መኰንኑ እነርሱ የሚገኙበት ሀገር ገብቶ ክርስቲያኖችን እያሳደደ መግደል ጀመረ፡፡

የንጉሡ ወታደሮችም እግዚአብሔርን እንዲክዱ፣ ለጣዖት እንዲሰግዱ ቅድስት ኢየሉጣንና ቅዱስ ቂርቆስን አስፈራሯቸው፡፡ ቅዱሳኑ ግን በክሕደት ለመወሰድ ፈቃደኛ አልሆኑም፡፡ በዚህም ምክንያት ጽኑ መከራ አደረሱባቸው፡፡ በጋሉ ብረቶች በመቸንከርና መላ ሰውነታቸውን በመብሳት፣ በዓይንና በአፍንጫቸው ውስጥ ጨውና ሰናፍጭ በመጨመር አሰቃዩዋቸው፡፡ በዚህ ሁሉ መከራቸው ውስጥ ግን አምላካችን እግዚአብሔር ስቃያቸው እንዳይሰማቸው ያጸናቸው ነበር፡፡ ንጉሱ ጸጉራቸውን ከነቆዳቸው በመላጨት በእሳት አቃጠላቸው፡፡ ሕጻኑ ቅዱስ ቂርቆስም ገና በሶስት ዓመቱ የሚደርስበትን ይህን መከራ በእግዚአብሔር ቸርነት ተቋቁሞ ከእናቱ ጋር በተጋድሎው ቀጠለ፡፡ በፍጹም እምነትና የሃይማኖት ፍቅር “እኔ ክርስቲያን ነኝ” እያለ ደጋግሞ ያናገር ነበር፡፡

ንጉሱም ህፃን ሳለ ይህን ያህል መጽናቱ እያስገረመው ሊያስፈራራውና ለጣኦታቱ እንዲሰግድ ሊያሳምነው ይሞክር ነበር፡፡ ሰውነታቸውን ከላይ እስከ ታች በችንካር ሲቸነክሯቸው ሊቀ መላዕክት ቅዱስ ገብርኤል አዳናቸው፣ በመጋዝ ሰንጥቀው በብረት ምጣድ ሲቆሏቸው እግዚአብሔር ከሞት አስነሳቸውና ዳግም በገዢዎች ፊት ቆመው ስለ ክብሩ መሰከሩ፡፡ አሁንም ቀኑን ሙሉ በልዩ ልዩ የሥቃይ መሣሪያዎች ቢያስጨንቃቸውም የእግዚአብሔር ኃይልና የቅዱስ ገብርኤል ተራዳኢነት አልተለያቸውም ነበርና ምንም ዓይነት ጉዳት አልደረሰባቸውም፡፡ እንደ ገናም በመጋዝ ሰንጥቀው በብረት ምጣድ በቆሏቸው ጊዜ ጌታችን ከሞት አነሣቸውና በመኰንኑ ፊት ድንቅ ተአምራትን አደረጉ፡፡ በዚህ የተበሳጨው ንጉስም በፍጹም ተአምራት መኮንኑ ያደረገውን ጫማ ወደ በሬነት የቀየረውንና “እኔ ክርስቲያን ነኝ” እያለ የሚናገረውን ቅዱስ ሕጻን ምላሱን አስቆረጠው፡፡ እግዚአብሔር ግን በቸርነቱ አድኖለታል፡፡

በመጨረሻም በፈላ ውሃ የተሞላ ትልቅ ጋን ውስጥ ሊጨምራቸው ሲዘጋጁ እናቱ ቅስት ኢየሉጣ ፈራች፡፡ ይሁንና ሕጻኑ ቅዱስ ቂርቆስ “እናቴ ሆይ አትፍሪ ሶስቱን ሕጻናት ያደነ አምላክ ያድነናል” እያለ ያጽናናት ነበር፡፡ በዚህ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ደርሶ እቶኑን ወደ ቀዝቃዛ ውሃ ቀይሮታል፡፡ ከዚህ በኋላም ብዙ ዓለማዊ ክብር እንደሚሰጧቸው ቃል ቢገቡላቸውም፣ ከክብሮች ሁሉ የሚበልጠውን የመንግስተ ሰማያት ክብር በመምረጥ በብዙ ተጋድሎና በጽኑ መከራ ውስጥ ሃይማኖታቸውን ጠብቀው ቆይተው ጥር 15 ቀን በመንፈቀ ሌሊት አንገታቸውን ተቈርጠው በሰማዕትነት አርፈዋል፡፡ ዓለምን ንቀዋት የእግዚአብሔርን መንግስት አስቀድመዋል፡፡ ዛሬም በየገዳማቱ ዓለምን ንቀው የሚኖሩ መነኮሳትና ገዳማውያን በጸሎታቸው ኃይል ያደርጋሉ፡፡ ገዳማቸውን እናግዝ በዓታቸውን እናጽና፡፡

ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም

ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391

ወይም

አቢሲኒያ ባንክ
141029444

የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444

እንኳን ለመልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ በዓል አደረሳችሁ፤ አደረሰን!!!መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል የልባችሁን መልካም መሻት ይሙላላችሁ!!!ቅዱስ ገብርኤል የስሙ ትርጓሜ “አምላክ ወሰብእ” ሰውና...
26/07/2025

እንኳን ለመልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ በዓል አደረሳችሁ፤ አደረሰን!!!

መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል የልባችሁን መልካም መሻት ይሙላላችሁ!!!

ቅዱስ ገብርኤል የስሙ ትርጓሜ “አምላክ ወሰብእ” ሰውና አምላክ ማለት ሲሆን ከዋነኞቹ የመላዕክት አለቆች አንዱ ነው፡፡ ነቢዩ ዳንኤል የመላእክት አለቃ የቅዱስ ገብርኤልን አስፈሪ ግርማ በተመለከተ ጊዜ “ዐይኖቼንም አነሣሁ እነሆም በፍታ የለበሰውን፣ ጥሩም የአፌዝን ወርቅ በወገቡ ላይ የታጠቀውን ሰው አየሁ፡፡ አካሉም እንደ ቢረሌ ይመስል ነበር፤ ፊቱም እንደ መብረቅ አምሳያ ነበረ፤ ዐይኖቹም እንደሚንበለበል ፋና፣ ክንዶቹና እግሮቹም እንደ ጋለ ናስ፣ የቃሉም ድምፅ እንደ ብዙ ሕዝብ ድምፅ ነበረ፡፡ ይህንም ታላቅ ራእይ አየሁ፤ ኀይልም አልቀረልኝም፤ ክብሬም ወደ ውርደት ተለወጠብኝ ኀይልም አጣሁ፡፡ የቃሉን ድምፅ በሰማሁ ጊዜ ደንግጬ በምደር ላይ በግምባሬ ተደፋሁ” አለ፡፡ በዳንኤል 10÷5-9 የተገለጸው የዚህ መልአክ ግርማ የአምላክን ግርማ ይመስላል፡፡

ሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስንና እናቱ ቅድስት ኢየሉጣንም ከእሳት ያወጣ እርሱ ነው፡፡ አምላካቸው ክርስቶስን አንክድም በማለታቸው የፈላ ጋን ውስጥ የተወረወሩት ቅዱስ ቂርቆስና እናቱን ቅድስት ኢየሉጣን ሐምሌ 19 ቀን የመላእክት አለቃ ቅዱስ ገብርኤል መጥቶ አዳናቸው። ቅድስት ኢየሉጣ ልጇ እንዳይገደል ለራሷም ከሚፍለቀለቀው ውሃ ድምፅ የተነሣ ለጊዜው ፍርሀት ሥጋዊ ቢያገኛትም ልጇ ወደ ጌታችን ሲጸልይላት ፍርሃቱ ርቆላታል፡፡ መልአከ ብርሃን ቅዱስ ገብርኤልም ከሰማይ ወርዶ የሚንተከተከውን ውሃ አቀዝቅዞ አውጥቷቸዋል፡፡ ቅዱስ ገብርኤልም ከዐበይት የመላእክት ነገዶች መካከል አንዱ በሆነው አርባብ፣ አጋእዝት ወይም ጌቶች በሚባለው ዐቢይ ነገድ ላይ የተሾመ ሲሆን ከበታቹም የሚመራቸው ዐሥር ነገደ መላእክት አሉ፡፡

ነቢዩ ኢሳይያስ በምዕራፍ 14÷16 በሰማያት የሳጥናኤል ትዕቢትና ውድቀት ምን እንደሚመስል ሲጽፍልን “አንተ በንጋት የሚወጣ አጥቢያ ኮከብ ሆይ እንዴት ከሰማይ ወደቅህ! ወደ አሕዛብ መልእክትን የላክ አንተ ሆይ እንዴት እስከ ምድር ድረስ ተቀጠቀጥህ! አንተም በልብህ ወደ ሰማይ ዐርጋለሁ ዙፋኔንም ከእግዚአብሔር ከዋክብት በላይ ከፍ ከፍ አደረጋለሁ፤ በልዑልም እመሰላለሁ አልህ፡፡ ዛሬ ግን ወደ ሲኦል ትወድቃለህ፤ ወደ ምደር ጥልቅም ትወርዳለህ” ይለናል፡፡ ቅዱስ ገብርኤል በቅድስና ሕይወት ለተጋውና በገዢዎች ዘንድ የእግዚአብሔር ቅዱስ መንፈስ ያደረበት ሰው ተብሎ ለተመሰገነው ለነቢዩ ዳንኤል ማስተዋልንና ጥበብን የሰጠ፣ እግዚአብሔር አምላክ የሰው ልጆችን ከሰይጣንና ከሞት ባርነት ነጻ ሊያወጣቸው ሰው እንደሚሆንና ሰማይንና ምድርን አሳልፎ በቅዱሳን ላይ ነግሦ እንደሚኖር በምሳሌ ገልጾ ያስተማረው መልአክ ነው፡፡

ቅዱስ ጳውሎስም በቈላስያስ 1÷16 በቅዱሳን መላእክት ዘንድ ስላሉት ነገዶች ሲገልጽ “… በሰማይ ያለውን በምድር ያለውን የሚታየውንምና የማይታየውን መናብርትም ቢሆኑ አጋእዝትም ቢሆኑ መኳንንትም ቢሆኑ ቀደምትም ቢሆኑ ሁሉም በእጁ ሆነ፤ ሁሉም በእርሱ ለእርሱ ተፈጠረ” በማለት ነገደ መላዕክትን ይዘረዝራቸዋል፡፡ ቅዱሳን መላእክት በቅዱስ ሚካኤል ፊት አውራሪነት የሰው ልጆች ጠላት ዲያብሎስን ተዋግተው ድል ከመንሳታቸው አስቀድሞ መላዕክት ማን ፈጠረን ብለው ግራ ሲጋቡ ቅዱስ ገብርኤል ፈጣሪ ነኝ ያለውን ሳጥናኤልን በመቃወም “አይዞአችሁ ፈጣሪያችን ፈጥሮ አይጥለንምና አስክናገኘው፣ እስክናውቀው ድረስ በያለንበት ጸንተን እንቁም፡፡” በማለት አረጋግቷቸዋል፡፡ ዛሬም ይህን አማላጅነቱንና ፈጣን ተራዳኢነቱን ያመኑ ገዳማውያ አባቶች በጸሎታቸው ይጠሩታል እርሱም ይራዳቸዋል፡፡ እኛም ገዳማቸውን ስንደግፍ በዓታቸውን ስናጸና የበረከታቸው ተሳታፊ እንሆናለን፡፡

ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም

ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391

ወይም

አቢሲኒያ ባንክ
141029444

የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444

እንኳን ለፈጥኖ ደራሹ ለራማው ልዑል ለቅዱስ ገብርኤል አመታዊ በአል በሰላም አደረሳችሁ
25/07/2025

እንኳን ለፈጥኖ ደራሹ ለራማው ልዑል ለቅዱስ ገብርኤል አመታዊ በአል በሰላም አደረሳችሁ

በ4ኛው መቶ ክ/ዘመን የነበሩ ቅዱሳን ባልና ሚስት ናቸው፡፡ ከልጅነት ጀምረው ቃለ እግዚአብሔርን በመማርና በስርዓተ ቤተክርስቲያን አድገዋል፡፡ በፈቃደ እግዚአብሔርም በሥርዓተ ተክሊል ጋብቻቸው...
25/07/2025

በ4ኛው መቶ ክ/ዘመን የነበሩ ቅዱሳን ባልና ሚስት ናቸው፡፡

ከልጅነት ጀምረው ቃለ እግዚአብሔርን በመማርና በስርዓተ ቤተክርስቲያን አድገዋል፡፡ በፈቃደ እግዚአብሔርም በሥርዓተ ተክሊል ጋብቻቸውን ፈጸሙ፡፡ ነገር ግን እንድራኒቆስና አትናስያ የሙሽርነታቸው የደስታ ጊዜ 40 ቀን ከተፈጸመ በኋላ "ፈጣሪያችን በምን እናስደስተው" በሚል ቁጭ ብለው ተወያዩ፡፡

እናም ሁልጊዜም እንግዳ ለመቀበል፣ ነዳያን ለማሰብ፣ በጸሎት፣ በጾምና በስግደት ሊተጉ፣ አብሮ ለመተኛት በጣም ውስን ጊዜ ለመስጠት ተስማሙ፡፡ ከዘመናት የቅድስና ጉዞ በሁዋላ በፈቃደ እግዚአብሔር 2 ልጆችን አከታትለው ወለዱ:: ወንዱን ዮሐንስ ሴቷን ማርያም አሏቸው፡፡ እነርሱን ከወለዱ በኋላ ለ12 ዓመታት በጾምና በጸሎት ተወስነው አልጋ ለይተው ኖሩ፡፡ ከ12 ዓመታት በኋላ 2ቱም ልጆቻቸው በአንድ ቀን ታመው ሞቱ፡፡ ይህ የመጨረሻው አሰቃቂ ፈተና ቢሆንም እንድራኒቆስና አትናስያ ልጆቻቸውን ቀበሩ፡፡

እንድራኒቆስ ከቀብር በሁዋላ ወደ ቤተ ክርስቲያን ገብቶ ምርር ብሎ አለቀሰ:: "አምላከ ኢዮብ! አንተ ሰጠኸኝ አንተም ነሳኸኝ፣ ስምህ ለዘለዓለም ይባረክ" ብሎም አመስግኖ ሔደ፡፡ አትናስያ ግን ከሐዘን ብዛት ልቡናዋ ሊሠወር ደረሰ፡፡ የልጆቿ መቃብር ላይ ተደፍታ ስታለቅስ ቅዱስ መልአክ ልቡናዋን ወደ ሰማይ አሳረገው፡፡ ልጆቿ ዮሐንስና ማርያም በገነት ውስጥ ከቅዱሳን ጋር ሐሴትን ሲያደርጉም ተመለከተች፡፡ ወዲያው ወደ ቤት ተመልሳ ለባሏ እንድራኒቆስ ያየችውን ነገረችውና ደስ አላቸው፡፡ እዛው ላይ "ለዚህ ውለታው ከነፍሳችን ውጪ የምንሰጠው የለም" ብለው ሊመንኑ ተስማሙ፡፡ እጅግ ሃብታሞች ነበሩና ነዳያንን ሰብስበው ሃብት ንብረታቸውን ቤት ርስታቸውን አካፍለው ወደ ገዳመ አስቄጥስ ሔደው እርሷ ከሴቶች ገዳም እርሱ ደግሞ ከወንዶቹ ገቡ፡፡

ለ12 ዓመታት በፍጹም ተጋድሎ ለፈጣሪያቸው ተገዙ፡፡ በእነዚህ ዘመናት ተያይተው ወይም አንዱ ስለ ሌላው ሰምቶ አያውቅም፡፡ በጸሎት ግን ያለማቁዋረጥ ይተሣሠቡ ነበር፡፡ ከ12 ዓመታት በሁዋላ የፍቅር አምላክ በሁለቱም ልቡና በተመሳሳይ ሰዓት ተመሳሳይ ሐሳብን አመጣ፡፡ እርሱ ከአበ ምኔቱ ታላቁ አባ ዳንኤል እርሷም ከእመ ምኔቷ አስፈቅደው ወደ ኢየሩሳሌም ከቅዱሳት መካናት ለመባረክ ጉዞ ጀመሩ፡፡ በየፊናቸው ጥቂት እንደተጉዋዙ እርስ በርስ ተያዩ፡፡ እርሷ ለየችው እርሱ ግን ጭራሽ ሊለያት አልቻለም፡፡ ይህም ጥበበ እግዚአብሔር ነው፡፡ 2ቱም እየተጫወቱ እየጸለዩ በሰላም ተባርከው ወደ ግብጽ ተመለሱ፡፡ በእነዚህ ጊዜያት ቅድስት አትናስያን የሚለያት አልነበረም፡፡ አካሏ በገድል ከመለወጡ ባሻገር የለበሰችው እንደ ወንድ መነኮሳት ነበር፡፡

ወደ ገዳመ አስቄጥስ ሲደርሱ ጸጋው ተሰጥቶታልና አባ ዳንኤል ባልና ሚስት መሆናቸውን አወቀ፡፡ "ለምን አብራችሁ አትኖሩም?" አላቸው፡፡ እርሷ እያወቀችው፣ እርሱ ሳያውቃት ለ12 ዓመታት አብረው በቅድስና ኖሩ፡፡ ከእነዚህ ዘመናት በሁዋላ ግን ሐምሌ 28 ቀን ቅድስት አትናስያ ታመመች፡፡ አባ ዳንኤል ሥጋውን ደሙን አቀብሏትም ዐረፈች፡፡ ሊገንዟት ሲቀርቡ ቅዱስ እንድራኒቆስ መልኩዋን ልብ ሲለው ሚስቱ ናት፡፡ በአንድ ጊዜ ሚስቱንና የሚወደውን ባልንጀራ በማጣቱ አለቀሰ፡፡

እርሷን ቀብረው ወደ በዓቱ ተመልሶ "ጌታ ሆይ! ውሰደኝ?" አለ፡፡ እርሱም ተከትሏት ዐረፈ፡፡ አባ ዳንኤል እርሱንም ቀብሮ ጥዑም ዜና ገድላቸውን ጻፈ፡፡ ገዳማውያን ተድላ ደስታቸውን ትተው ማንነታቸውን ረስተው በተጋድሎ እየተጉ ፈጣሪያቸውን ያገለግላሉ፡፡ ገዳማቸውን ስንደግፍ በዓታቸውን ስናጸና በረከታቸው ያድርብናል፡፡

ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም

ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391

ወይም

አቢሲኒያ ባንክ
141029444

የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444

ወላጆቹ ስምዖንና ማርያም ይባላሉ፡፡የመጀመሪያው ሊቀ ዲያቆናት፣ የሐዲስ ኪዳን ቀዳሚው ሰማዕት፣ በመጀመሪያው መቶ ክ/ዘመን አስገራሚ ማንነት ከነበራቸው እሥራኤላውያን አንዱ ነበር፡፡ ገና ከልጅ...
24/07/2025

ወላጆቹ ስምዖንና ማርያም ይባላሉ፡፡

የመጀመሪያው ሊቀ ዲያቆናት፣ የሐዲስ ኪዳን ቀዳሚው ሰማዕት፣ በመጀመሪያው መቶ ክ/ዘመን አስገራሚ ማንነት ከነበራቸው እሥራኤላውያን አንዱ ነበር፡፡

ገና ከልጅነቱ ቁም ነገር ወዳድ የነበረው ቅዱስ እስጢፋኖስ፤ ቅዱስ ዻውሎስን፣ ናትናኤልንና ኒቆዲሞስን ጨምሮ በርካታ ቅዱሳንን ካስተማረው ከታላቁ መምሕረ ኦሪት ገማልያል ዘንድ፣ ኦሪቱን ነቢያቱን ጠንቅቆ ተምሯል፡፡ የመጥምቁ ቅዱስ ዮሐንስን የንስሃ ጥምቀት ከእግዚአብሔር ሆኖ ቢያገኘው ደቀ መዝሙሩ ሆነ፡፡ ለ6 ወራት ተግቶ ካገለገለው በኋላም ጌታችን ሲጠመቅ የተደረገውን ታላቅ ተአምር አይቶ ቅዱስ ዮሐንስን አስፈቅዶ ከጌታ ዘንድ ሔዶ፣ እጅ ነስቶ ተማረ፣ ጌታም ደቀ መዝሙሩ፣ ከ72ቱ አርድእትም አንዱ አድርጐት ለአገልግሎት ላከው፡፡

ኃይለ አጋንንትን የሚያስጨን ድውያንን የሚፈውስ የመንፈስ ቅዱስ ማደሪያ ነበር፡፡ ጌታችን ከሙታን ከተነሳ በኋላ ወደ ሰማይ ሲያርግ ደቀ መዛሙርቱን በአንብሮተ እድ በባረከበት ጊዜ እርሱም ቅስናንና፣ ዽዽስናን ተሹሟል፡፡ በበዓለ ሃምሳ መንፈስ ቅዱስ ሲወርድላቸውም ከ72ቱ አርድእት የእርሱን ያህል ልሳን የበዛለት ምሥጢርም የተገለጠለት አልነበረም፡፡ በፍጹም እውቀት ያለፍርሃት ወንጌልን ይሰብክ ገባ፡፡ በቤተ ክርስቲያን ላይ ማዕድ ሥርዓት ምክንያት አለመግባባት ሲፈጠርና ችግሩን እንዲፈቱ በመንፈስ ቅዱስ መሪነት 7 ዲያቆናት ሲመረጡ እርሱ ሊቀዲያቆናትና፣ የ8ሺው ማሕበር መሪ ሆኗል፡፡ ቅዱስ እስጢፋኖስ ከጌታ ዕርገት በኋላ ለአንድ ዓመት ያህል 8ሺውን ማኅበር እየመራ ወንጌልን እየሰበከ ክርስትናን እጅግ አስፋፋ፡፡ አይሁድ ክርስትናን ለማጥፋት መፍትሔው ቅዱስ እስጢፋኖስን መግደል ነው ብለው በማመናቸው በድንጋይ ሊወግሩት ከከተማ አወጡት፡፡

ሲወግሩትም ፊቱ እንደ እግዚአብሔር መልአክ እያበራ እንደ ጌታችን በድንጋይ ለሚወግሩት ሰዎች ምሕረትን ይለምን ነበር፡፡ ደቀ መዛሙርቱም ታላቅ ለቅሶ እያለቀሱ ቀበሩት፡፡ ቅዱስ እስጢፋኖስ ካረፈ ከ300 ዓመታት በኋላ በኢየሩሳሌም ለሚኖር ሉክያኖስ ለሚባል አንድ ደግ ሰው በተደጋጋሚ በራዕይ እየተገለጠ "ሥጋየን አውጣ" ይለው ነበርና ሔዶ ለዻዻሱ ነገራቸው:: ዻዻሱም ደስ ብሏቸው ካህናትና ምዕመናንን ሰብስበው መምሕሩ ወደ ነበረው ወደ ገማልያል ርስት ሔደው ቦታውንም በቆፈሩ ጊዜ ታላቅ መነዋወጥ ሆነ፡፡ መላእክት በዝማሬ ሲያጥኑ በጐ መዓዛ ሸተተ፡፡ ሕዝቡና ዻዻሱም በቅዱስ እስጢፋኖስ ፊት ሰግደው፣ በታላቅ ዝማሬና በሐሴት ዐጽሙን ከዚያ አውጥተው በጽርሐ ጽዮን በተቀደሰችው ቤት አኖሩት፡፡ ቅዱስ እስጢፋኖስን እጅግ የሚቀደው እለ እስክንድሮስ የተባለ ደግ ሰው ቤተ ክርስቲያን አንጾለት ወደዚያ አገቡት፡፡

ከ5 ዓመታት በኋላም እለ እስክንድሮስ ሲያርፍ ስለ ፍቅሩ ሲሉ በሳጥን አድርገው በቅዱሱ ጐን አሳረፉት፡፡ ሚስቱ ወደ ሃገሯ ቁስጥንጥንያ ስትመለስ የባሏ ሥጋ መስሏት የቅዱስ እስጢፋኖስን ቅዱስ ሥጋ በመርከብ ጭና ወሰደችው፡፡ መንገድ ላይ ከሳጥኑ ውስጥ ዝማሬ ሰምታ ብታየው ያመጣችው የቅዱሱን ሥጋ ነው፡፡ እጅግ ደስ አላት አምላክ ለዚህ አድሏታልና፡፡ እርሷም ወስዳ ለታላቁ ንጉሥ ቅዱስ ቆስጠንጢኖስ አስረከበች፡፡ በከተማውም ታላቅ ሐሴት ተደረገ፡፡ ሥጋውን ሊያኖሩት በበቅሎ ጭነው ሲወስዱትም በቅሎዋ በሰው ልሳን ተናግራ ማረፊያውን አሳወቀች፡፡ በዚያም ላይ ትልቅ ቤተ ክርስቲያን ታንጾለታል፡፡ የዘመናችን ሰማዕታት ስለክርስቶስ ፍቅር ዓለምን የተዉአት ገዳማውያን ናቸው፡፡ ገዳማቸውን እየደገፍን በዓታቸውን እያጸናን የበረከታቸው ተሳታፊ እንሁን፡፡

ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም

ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391

ወይም

አቢሲኒያ ባንክ
141029444

የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444

ኢትዮ ቴሌኮም የ2017 ዓም በጀት አመቱን ማጠናቀቁን ተከትሎ የ1 ጂቢ ነጻ የኢንተርኔት አገልግሎት ለደንበኞቹ ይፋ አድርጓል። ነጻ አገልግሎቱ ከዛሬ ምሽት ለሊት ሰባት ሰአት ጀምሮ መጠቀም የ...
24/07/2025

ኢትዮ ቴሌኮም የ2017 ዓም በጀት አመቱን ማጠናቀቁን ተከትሎ የ1 ጂቢ ነጻ የኢንተርኔት አገልግሎት ለደንበኞቹ ይፋ አድርጓል።

ነጻ አገልግሎቱ ከዛሬ ምሽት ለሊት ሰባት ሰአት ጀምሮ መጠቀም የሚቻል ሲሆን የስጦታ ጥቅሉ የድምጽ፣ የመልእክት እና የኢንተርኔት አገልግሎቶችን ያካትታል።

በዚህም መሰረት ከዛሬ ሐምሌ 17 ለሊት ሰባት ሰአት ጀምሮ እስከ ሐምሌ 20 ከቀኑ 12 ሰአት ድረስ በየቀኑ 5 ደቂቃ የድምጽ፣ 341 Mb የኢንተርኔት እና 8 የSMS አገልግሎት በ ነጻ አገልግሎት መጠቀም ይቻላል።

ላልተገደበ ኢንተርኔት ተጠቃሚዎች የነጻ ስጦታ አገልግሎቱ 10 ደቂቃ አለም አቀፍ ጥሪን ያካትታል።

ለቴሌ ብር ሱፐር አፕ ተጠቃሚ ደንበኞች ደግሞ ተጨማሪ የ 1 ጂቢ ነጻ የኢንተርኔት አገልግሎት ማቅረቡን ተቋሙ አሳውቋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ

@

New Man Utd front 3
24/07/2025

New Man Utd front 3

Address


Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Zeአራዳ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

  • Address
  • Alerts
  • Claim ownership or report listing
  • Want your business to be the top-listed Media Company?

Share