Zeአራዳ

Zeአራዳ Melake:
Ethiopia's news & entertainment hub. Follow for updates! Bringing you the pulse of Ethiopia!

From breaking news to the hottest trends in entertainment, join our community and celebrate our rich culture.

ሰበር መረጃ የኦሮሞ አባገዳዎች ቲክቶከር አዶናይ በሽምግልና እንዲፈታ በዛሬው እለት ወደ አዲስ አበባ ጉዞ እንደጀመሩ ተሰምቷል ! የኦሮሞ አባገዳዎች ቲክቶከር አዶናይ በሽምግልና እንዲፈታ ከተ...
12/14/2025

ሰበር መረጃ

የኦሮሞ አባገዳዎች ቲክቶከር አዶናይ በሽምግልና እንዲፈታ

በዛሬው እለት ወደ አዲስ አበባ ጉዞ እንደጀመሩ ተሰምቷል ! የኦሮሞ አባገዳዎች ቲክቶከር አዶናይ በሽምግልና እንዲፈታ ከተለያዩ የእምነት ተቋም መሪዎች ጋር

ወደ አዲስ አበባ እንዳመሩ ለማወቅ ተችሏል ! ሀገራችን ካሏት ባህሎች አንዱ ሽምግልና ሲሆን የገዳ ስርአት ደግሞ

ጥፋትን በቅጣት ሳይሆን በእርቅና በማስተማር ችግሮችን በመፍታት የሚታወቅ ስርአት ነው ::

ጥብቅ መረጃ! ስስ ፌስታል መጠቀም ተከለከለ! 🚫🛍️የኢትዮጵያ አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን፣ ከጥር 23 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ስስ የፕላስቲክ ከረጢቶችን (ፌስታል) መጠቀም በጥብቅ የተከለከለ ...
12/14/2025

ጥብቅ መረጃ! ስስ ፌስታል መጠቀም ተከለከለ! 🚫🛍️

የኢትዮጵያ አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን፣ ከጥር 23 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ስስ የፕላስቲክ ከረጢቶችን (ፌስታል) መጠቀም በጥብቅ የተከለከለ መሆኑን አስታውቋል።

ይህንን ህግ ተላልፎ ስስ ፌስታል ይዞ የተገኘ ማንኛውም ሰው ከ5,000 እስከ 10,000 ብር የገንዘብ ቅጣት እንደሚጠብቀው ተገልጿል።

የፕላስቲክ ከረጢቶችን ማመረት፣ ወደ ሀገር ውስጥ ማስገባት እና መጠቀምን የሚከለክለው እና በእስራትና በገንዘብ የሚያስቀጣው አዋጅ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መጽደቁ ይታወሳል።

ቅጣቱ ከባድ ስለሆነ ጥንቃቄ ያድርጉ! ለአካባቢ ደህንነት ሲባል አማራጭ መያዣዎችን ይጠቀሙ።

አባታቸው ስምዖን እናታቸው አቅሌስያ ይባላሉ፡፡ ወላጆቻቸው ልጅ አጥተው ሠላሳ ዘመን ሲያዝኑ ኖረዋል፡፡ አንድ ቀን አቅሌሲያ ቤተ እግዚአብሔር ገብታ ከሥዕለ ሥላሴ ሥር ወድቃ ስትማጸን “ሥልጣኑ...
12/14/2025

አባታቸው ስምዖን እናታቸው አቅሌስያ ይባላሉ፡፡

ወላጆቻቸው ልጅ አጥተው ሠላሳ ዘመን ሲያዝኑ ኖረዋል፡፡ አንድ ቀን አቅሌሲያ ቤተ እግዚአብሔር ገብታ ከሥዕለ ሥላሴ ሥር ወድቃ ስትማጸን “ሥልጣኑ ከሰማይ ከፍታ ከፍ የሚል፣ ንጽሕናው ከሚካኤል ከገብርኤል የሚተካከል፣ ክህነቱ እንደ መልከ ጼዴቅ እንደ መጥምቁ ዮሐንስ እንደ ነቢዩ ኤልያስ የሆነ ልጅ እንቺ ተቀበይ” የሚል ድምጽ ሰማች፡፡

አቅሌስያም በመጋቢት 29 ቀን ፀንሳ በታኅሣሥ 29 ቀን ደም ግባቱ እጅግ የሚያምር ወንድ ልጅ ግብጽ ወስጥ ንሂሳ በምትባል ቦታ ወለደች፡፡ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል በሰው አምሳል መጥቶ “የዚህ ልጅሽ ስሙ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ይሁን” አላት፡፡ ወዲያውም ሕፃኑ ከእናቱ ጭን ወርዶ ለአብ ለወልድ ለመንፈስ ቅዱስ ሦስት ጊዜ ሰገደ፡፡ “ከጨለማ ወደ ብርሃን ለአወጣኸኝ ለአብ ለወልድ ለመንፈስ ቅዱስ ምስጋና ይሁን” አለ፡፡

አባታችንም ከዚህ በኋላ እናታቸው አላቀፈቻችውም፤ ጡትም አልጠቡም፡፡ ሦስት ዓመት ሲሞላቸውም በእግዚአብሔር አምላክ ትዕዛዝ ብርሃናዊው መልአክ የራማው ልዑል ቅዱስ ገብርኤል ከሰማይ ወርዶ ሕፃኑን ከእናቱ ክንድ ወስዶ በክንፎቹ አቅፎና ስሞ እስከ ሰባቱ ሰማይ አውጥቶ በሥሉስ ቅዱስ ፊት አቅርቦት አስባረከው፡፡ እግዚአብሔርም መልአኩን “ወደ እናቴ ወደ ማርያም ውሰደውና ትባርከው” አለውና ወስዶት እመቤታችንም ባረከችው፡፡ ከአዳም ጀምሮ ያሉ ቅዱሳንም ሁሉ ባረኩት፡፡ አምላካችን እግዚአብሔርም አጸናው አበረታው፡፡ ከዚህም በኋላ መልአኩ አባ ዘመደ ብርሃን ወዳለበት ገዳም አወረደውና ሕፃኑን ከበር ላይ አስቀምጦ ምግቡ የእግዚአብሔር ቃል እንደሆነ ነገረው፡፡ አባ ዘመደ ብርሃንም ሕፃኑን አስገብቶ የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት ሁሉ እያስተማረ አሳደገው፡፡ ትምህርቱን በጨረሰ ጊዜ ዲቁና ተቀብሎ እንደ ቅዱስ እስጢፋኖስ ጸጋንና ሞገስን የተመላ ሥራው የተቃና ሆነ፡፡
አባ ዘመድ ብርሃንም እንደ ቅዱስ እንጦንስ አስኬማን ሰጠው፡፡

ከዚህም በኋላ ቅስናን ተቀበሉና በጾም በጸሎት ተጠምደው በታላቅ ተጋድሎ መኖር ጀመሩ፡፡ እንደ ሐዋርያትም የተአምራትና የፈውስ ሀብት ተሰጣቸውና ድውያንን የሚፈውሱ፣ ሙታንን የሚያነሡ፣ አጋንንትን የሚያወጡ ሆኑ፡፡ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ዳግመኛ ተገልጦላቸው ወደ ሰማይ አሳረጋቸው፡፡ እግዚአብሔርም ከባረካቸው በኋላም ከሰው ተለይተው ከአናብስትና ከአናብርት ጋር እንዲኖሩ፣ እንስሳቱም የእግራቸውን ትቢያ እየላሱ እንደሚኖሩ ነገራቸው፡፡ ሰውነታቸውም ሁሉ በጠጉር ተሸፈነ፡፡ በፍጹም ተጋድሎም ከኖሩ በኋላ በቀንና በሌሊት የክርስቶስን መከራ እያሰቡ ስለ ኃጥአንም ጥፋት እንባቸውን እያፈሰሱ ይጸልዩ ነበር፡፡ በጸሎታቸውም ብዙ እልፍ ነፍሳትን አስምረዋል፡፡ ሦስት መቶ ዓመት ከኖሩ በኋላም ከ60 አንበሶችና ከ60 ነብሮች ጋር ወደ ኢትዮጵያ መጡ፡፡

ብርሃናዊው መልአክ ቅዱስ ገብርኤልም በነፋስ ሠረገላ ጭኖ ምድረ ከብድ አደረሳቸው፡፡ ደብር ቅዱስ የሚባለው ዝቋላንም አሳያቸው፡፡ ሰው የገዛ ፊቱን በመሥታወት እንደሚያይ አባታችንም የኢትዮጵያን ሰዎች ኃጢአታቸውን በግልጽ በተመለከቱ ጊዜ ተወርውረው ወደ ባሕሩ በመግባት የኢትዮጵያን ሕዝብ ማርልኝ ብለው ለአንድ መቶ ዓመት ተዘቅዝቀው ስጋቸው እስኪያልቅ ጸልየዋል፡፡ ጌታችንም መጥቶ ኢትዮጵያን ምሬልሀለሁ ውጣ አላቸው፡፡ ሲወጡም ሰውነታቸውን ዳሶ አደሳቸው፡፡ ታላቅ ቃል ኪዳንም ሰጣቸው፡፡ አባታችን በሀገራችን 262 ዓመታት በጸሎትና በትምህር እየቀዱሱዋት፣ አጋንንትን እያሳደዱ ኖረው በተወለዱ በ562 ዓመታቸው በዕለተ እሁድ አርፈዋል፡፡

በቅዱሳኑ ምልጃ ያመኑ ገዳማውያን ሁሉን ትተው ተከትለውታል፣ ገዳማቸውን እንደግፍ በዓታቸውን እናጽና፡ ከበረከታቸው እንሳተፍ።

ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም

ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391

ወይም

አቢሲኒያ ባንክ
141029444

ለበለጠ መረጃ:- 09 38 64 44 44/0918077957

12/14/2025

3ቱንም ግቦች ውልቭሶች ባስቆጠሩበት ጨዋታ አርሰናል 3 ነጥቦች ይዞ ወቷል😢🤣

ሰበር ዜና!!የቀድሞ ኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ኢንጅነር ኃይለማርያም ደሳለኝ ቀጣዩ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ፀሐፍ ለመሆን አፍሪካን ወኪሎ እጩ መሆናቸውን የዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃ...
12/13/2025

ሰበር ዜና!!

የቀድሞ ኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ኢንጅነር ኃይለማርያም ደሳለኝ ቀጣዩ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ፀሐፍ ለመሆን አፍሪካን ወኪሎ እጩ መሆናቸውን የዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን እየዘገቡ ይገኛሉ!!

#መልካም ዕድል!!

አዲስ ዜና! ተወዳጁ አርቲስት ጋሽ ሰለሞን በቅርቡ በተካሄደው የመኪና ሽልማት እንዳሸነፉ የሚታወቅ ሲሆን ብሩክ ሪል እስቴትም መኪናውን ለማስረከብ ዝግጅቱን ማጠናቀቁን አስታውቋል።አርቲስቱም  ...
12/13/2025

አዲስ ዜና!
ተወዳጁ አርቲስት ጋሽ ሰለሞን በቅርቡ በተካሄደው የመኪና ሽልማት እንዳሸነፉ የሚታወቅ ሲሆን

ብሩክ ሪል እስቴትም መኪናውን ለማስረከብ ዝግጅቱን ማጠናቀቁን አስታውቋል።

አርቲስቱም ሽልማቱ እውን እንዲሆን ላደረጉት ለሁሉም ውድ ኢትዮጵያውያን እና ኤርትራውያን ታላቅ ምስጋና አቅርቧል።

"ይህን ሁሉ እንዲሳካ ላደረጋችሁ ውድ ኢትዮጵያውያን እና ኤርትራውያን ፈጣሪ ይስጥልኝ!" ብለዋል።

ነገር ግን ጋሽ ሰለሞን ከሽልማት አሰጣጡ ሂደት ጋር በተያያዘ አንድ ልብ የሚነካ ውሳኔ አስተላልፈዋል።

"እኔ ግን የዚህ ነገር ትልቅ ጀማሪና ጠንሳሽ ውድ ልጄ አዶናይ በተገኘበት ብቻ የመኪና ሽልማቱን ለመቀበል ወስኛለሁ።"

በመጨረሻም አርቲስቱ "እግዚአብሔር ልጆቿንና ህዝቦቿን ይባርክ!" በማለት መልካም ምኞቷቸውን ገልፀዋል።

🙏🙏🙏
ጉርሻ Page

‎ለባህርዳር ከተማ ሌላ ውበት ይሰጣታል የተባለለት አስፓልት በመጠናቀቅ ላይ ነው‎‎በሬማ ጀኔራል ቢዝነስና ኮንስትራክሽን አማካኝነት ከአልማ ዋተርፍሮንት ሆቴል እየተነባ የሚገኘው በጣም ዘመናዊ...
12/13/2025

‎ለባህርዳር ከተማ ሌላ ውበት ይሰጣታል የተባለለት አስፓልት በመጠናቀቅ ላይ ነው

‎በሬማ ጀኔራል ቢዝነስና ኮንስትራክሽን አማካኝነት ከአልማ ዋተርፍሮንት ሆቴል እየተነባ የሚገኘው በጣም ዘመናዊና ልዩ መንገድ በቅድመ ክፍያ ብቻ አስፓልት የማንጠፍ ስራ እየተከናወነ መሆኑን የሬማ ኮንስትራክሽን ፕሮጀክት ማናጀር አቤኔዘር ማስረሻ ተናገሩ።

‎ይህ መንገድ በመሠራቱ የአካባቢው ነዋሪ እጅግ ደስተኛ በመሆኑ የባህርዳር ከተማ አመራሮችንና ሬማ ኮንስትራክሽንን እያመሠገነ እንደሚገኝ አቶ አቤኔዘር ገልጸዋል።

‎የአስፓልት ስራው የ3 ወር እቅድ ቢሆንም በመሀል የነበረው የክረምት ሁኔታ ቲኒሽ ቀናቶችን ቢገፋውም በአድቫንስ ብቻ በአጭር ጊዜ መንገዱን ሰርቶ ማጠናቀቅ ተችሏል።

‎በትላንትናው ዕለትም አቶ ጎሹ እንዳላማው የባሕርዳር ከተማ ከንቲባ፣ አቶ ሞላ ሁሴን የባሕርዳር ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ሀላፊ፣ አቶ አስሜ ብርሌ የባሕርዳር ከተማ ምክትል ከንቲባ በቦታው ተገኝተው ጎብኝተዋል።

‎የኮንክሪት አስፓልት መንገዱ 8 መቶ ሜትር ርዝመት እና 40 ሜትር የጎን ስፋት ያለው ሲሆን ይህ አስፓልት በፍጥነትና በቅድመ ክፍያ ብቻ እየተሰራ መሆኑን የሬማ ኮንስትራክሽን ባለቤትና መሥራች አቶ ፍቅሬ አስፋው ተናግረዋል።

‎መንገዱ ለነዋሪዎች ዘመናዊ እና የተሳለጠ የትራንስፖርት አገልግሎት ከመስጠት በተጨማሪ ከተማዋን ከጣና ሀይቅ ጋር የሚያስተሳስር መሆኑ ተገልጧል።

‎የመንገዱ ግንባታ የመኪና፣ የእግረኛ፣ የብስክሌት፣ የግሪነሪ ልማቶችን ያካተተ ሲሆን የመብራት፣ የቴሌ፣ የውሀ መስመሮች በዘላቂነት በመሰረተ ልማት ስራው ተቀናጅተው የተሰሩ መሆኑ የተናገሩት የባህርዳር ከተማ ከንቲባ አቶ ጎሹ እንዳላማው ናቸው።

የብሕንሳው ኤዺስቆዾስ ሲያርፉ በምትካቸው የሚሾሙትን ሲያፈላልጉ መንፈስ ቅዱስ አባ ሕርያቆስን መረጠው፡፡ ቅዱሳን ሐዋርያት የተማረና ግብረ ገብ የሆነ ይሾም፤ ሁለቱን አስተባብሮ የያዘ ባይገኝ ...
12/13/2025

የብሕንሳው ኤዺስቆዾስ ሲያርፉ በምትካቸው የሚሾሙትን ሲያፈላልጉ መንፈስ ቅዱስ አባ ሕርያቆስን መረጠው፡፡

ቅዱሳን ሐዋርያት የተማረና ግብረ ገብ የሆነ ይሾም፤ ሁለቱን አስተባብሮ የያዘ ባይገኝ የተማረ ከሆነ ይሾም በትምህርቱ መናፍቃንን ተከራክሮ ይመልሳልና፡፡ ደግሞም ግብረ ገብም ከሆነም ይሾም፤ ምክንያቱም በጸሎቱ ይጠብቃል በትሩፋቱ ያጸድቃልና ብለዋል፡፡ በዚህም መሠረት አባ ሕርያቆስ የተማረው ለጸሎት ለቅዳሴ ያህል ትንሽ ቢሆንም ግብረ ገብ ነውና ትምህርቱን ውሎ አድሮ ያደርገዋል ብለው በብሕንሳ ገዳም በ10 ሺህ መነኮሳትና በ10 ሺህ መነኮሳይያት ላይ ተሹሞ የገዳሙ አስተዳዳሪ ሆነ፡፡ ሕርያቆስ ማለት የተመረጠ ማለት ነው፡፡ አንድም ምሥጢረ ሥላሴን ከሁሉ ይልቅ አራቆ ይናገራልና ሕርያቆስ ማለት ረቂቅ ማለት ነው፡፡ አብ ፀሐይ ወልድ ፀሐይ መንፈስ ቅዱስ ፀሐይ ብሎ አመስግኗልና ፀሐይ ማለት ነው፤ የምእመናንን ልቡና በትምህርቱ ብሩህ አድርጓልና ብርሃንም ማለት ነው፡፡

ንብ የማትቀምሰው አበባ እንደሌለ ሁሉ ሕርያቆስም ያልቀሰመው ሰማያዊ ዕውቀት የለምና እርሱንም የማይጠቅሰው ሊቅ የለምና ንብ ማለትም ነው፡፡ አባ ሕርያቆስ ከልጅነቱ ጀምሮ እመቤታችንን እጅግ ከመውደዱ የተነሣ ስሟን ሲጠራ በመስጦ ልቡናው ይሰወርበት፣ እርሷም ትጠብቀው ነበር፡፡ ዘወትር ፍቅሯን ያስብም ነበር፡፡ የአባ ሕርያቆስ የሌት ተቀን ሞኞቱ እንደ ቅዱስ ኤፍሬም የእመቤታችን ምስጋና እንደ ባሕር አሸዋ እንደ ሰማይ ኮከብ በዝቶልኝ እንደልብስ ለብሼም እንደ ምግብ ተመግቤው የሚል ነበር፡፡ አባ ሕርያቆስ የተሾመባት ብሕንሳ የወንድና የሴት የአንድነት ገዳም ነበረች፡፡ እርሱ የነበረበት ዘመን የሊቃውንት ዘመን ስለነበር ሁሉም ለትምህርት ሲተጉ አባ ሕርያቆስ ለጸሎትና ለደግነት ይተጋ ነበር፡፡ ብዙም ትምህርት ስላልነበረውም ይንቁት፣ በምን ምክንያት እንሻረው እያሉም ይመክሩ ነበር፡፡

እርሱ ግን እንደጠሉኝ ልጥላቸው ሳይል በፍቅር በትሕትና ይመክራቸው ነበር፡፡ ከዕለታት በአንድ ቀን ቀድሰህ አቁርበን እንበለውና ሲያቅተው እንሻረው? ብለው መከሩ፡፡ እርሱም ሥርዓተ ቅዳሴውን ፈጽሞ ወደፍሬ ቅዳሴው ሲደርስ ከቅዳሴ ሐዋርያት በስተቀር የሚያውቀው የለምና የትኛውን ከባድ ቅዳሴ ቀድስ እንበለው? እያሉ ሲመካከሩ፣ የለመኗትን የማትነሳ የነገሯትን የማትረሳ እመቤታችን ወርዳ ረቂቅ የሆነ ቅዳሴዋን ገለጸችለት፡፡ “ጎስዐ ልብየ ቃለ ሠናየ፣ ልቡናዬ በጎ ነገርን አወጣ” በማለት ጀምሮ “ዛሬም አብን ወልድንና መንፈስ ቅዱስን እናመስግን” እስከሚለው ድረስ ሰተት አድርጎ ቀደሰ፡፡ የሚንቁት “ይህ የነገሩትን ቀለም እንኳን አከናውኖ መናገር የማይችል ዛሬስ እንግዳ ድርሰት እደርሳለው ብሎ የቆጥ የባጡን ይቀባጥራል” ብለው አፌዙበት፡፡ የሚወዱትና የሚያከብሩት ግን “ከመንፈስ ቅዱስ ነው እንጂ እንዲህ ያለ ምሥጢር ከስጋ ለባሽ ይገኛልን!” ብለው አደነቁለት፡፡

ወዲያው የሚወዱት የሚያከብሩት “ጽፈን ደጉሰን እንያዘው!? አሉ፡፡ የሚንቁት የሚጠሉት ግን “ማን ተናገረው ብለን እንይዘዋለን?” አሉ፡፡ በሀገራቸው ልማድ መሠረት ጽፈው ደጉሰው ሊይዙት ተስማሙ፡፡ ጽፈው ደጉሰው ከእሳት፣ ከውሃ ላይ በየተራ ጣሉት ምንም ሳይሆን ወጣ፡፡ በደውይ ላይ ጣሉት ድውይ ፈወሰ፤ ይልቁንም ሙት አስነሥቷል፡፡ ከዚህም በኋላ ደገኛ ድርሰት ነው ብለው ጽፈው ደጉሰው በጥራዝም 14ኛ ቅዳሴ አድርገው ይዘውታል፡፡ ይህም ቅዳሴ ማርያም ስለ እመቤታችን እጅግ በጠለቀ ሁኔታ የሚያመሰጥር በመሆኑ በሰሙነ ፍልሰታ ይቀደሳል ይተረጎማል፡፡

ገዳማውያንም በረከት ያለበት ቅዳሴዋን ሳይደግሙ አይውሉም፡፡ ገዳማቸውን ስንደግፍ በዓታቸውን ስናጸና የበረከታቸው ተካፋዮች እእንሆናለን፡፡

ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም

ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391

ወይም

አቢሲኒያ ባንክ
141029444

ለበለጠ መረጃ:- 09 38 64 44 44/0918077957

ዛሬ ቲክቶከሮች ጌም ሲጀምሩ በብሔራዊ መዝሙር ነበር  😂
12/13/2025

ዛሬ ቲክቶከሮች ጌም ሲጀምሩ በብሔራዊ መዝሙር ነበር 😂

ናንሲ የታገቢኛለሽ ጥያቀውን ተቀብላለች 🎉🎊
12/12/2025

ናንሲ የታገቢኛለሽ ጥያቀውን ተቀብላለች 🎉🎊

እንኳን ለበዓታ ለማርያም አደረሳችሁ፤ አደረሰንወደ ቤተ መቅደስ ገባች🙏🙏🙏❤️❤️❤️በመካንነት የነበሩት ወላጆቿ ኢያቄምና ሐና በንጽህና በቅድስና ቢኖሩም በወቅቱ የነበሩት ካሕናተ ኦሪት ልጅ ስ...
12/12/2025

እንኳን ለበዓታ ለማርያም አደረሳችሁ፤ አደረሰን

ወደ ቤተ መቅደስ ገባች🙏🙏🙏❤️❤️❤️

በመካንነት የነበሩት ወላጆቿ ኢያቄምና ሐና በንጽህና በቅድስና ቢኖሩም በወቅቱ የነበሩት ካሕናተ ኦሪት ልጅ ስላልወለዱ መስዋዕታቸውን እንኳን ሊቀበሏቸው ፈቃደኛ አልነበሩም፡፡

ወላጆቿ ወደ እግዚአብሔር ጸልየው፣ ልጅ ከሰጣቸው ለቤተ እግዚአብሔር ሊሰጡ ስዕለት ገብተው ቅድስት ድንግል ማርያምን ወለዱ፡፡ እመቤታችን ገና በቅድስት ሐና ማሕጸን ከነበረችበት ወቅት ጀምሮ ተአምራት ታደርግ ነበር፡፡ ቤርሳቤህ የተባለች ሴት የሀናን መጽነስ ስትሰማ በደስታ ልትጎበኛት መጣች፡፡ አንድ አይኗን አጥታ የነበረችው ይህች ሴት ቅድስት ሐናን እንኳን ደስ አለሽ ብላ ሆዷን ከዳሰሰቻት በኋላ በዚያው እጇ ዓይኗን ብትነካው ዐይኗ በርቶላታል፡፡

ይህን ምሳሌ አደርገው ድውያን እየመጡ ሆዷን ዳሰው ይፈወሱ ነበር፡፡ በቅድስት ድንግል ማርያም መወለድ ወላጆቿ ቅዱስ ኢያቄምና ቅድስት ሀና ፍሬ አጊኝተዋል፡፡ ዓለም ደግሞ የመድኃኒቱን እናት አጊኝቷል፡፡

እናታችን ቅድስት ሐና እመቤታችን ጸንሳ ሳለች ሳሚናስ የሚባል የአጓቷ ልጅ ይሞታል፡፡ ቅድስት ሐናም እጅግ ትወደው የአልጋውን ሸንኮር እየዞረች ስታለቅስ ከሞተበት ተነስቶ “የሰማይና የምድር ፈጣሪ አያት ሆይ ላንቺ ክብር ይገባሻል!!!” ብሎ መስክሮ አርፏል፡፡ አይሁድም “ቀድሞ የእነዚህ ዘር የነበሩ ዳዊትና ሰሎሞን አርባ፣ አርባ ዘመን ገዙን አሁን ከዚህች የሚወለድ ምን ሊያደርገን ነው?” ብለው በድንጋይ ሊወግሯት ተነሱ፡፡ የራማው ልዑል ቅዱሰ ገብርኤል እየመራ ወደ ሊባኖስ ተራራ ወሰዳቸው፡፡ በእዚያም ቅድስት ድንግል ማርያም ተወለደች፡፡ ሰማያት ብርሃን ሰጡ፣ ቅዱሳን መላእክት አዲስ ምስጋና ተቀኙላቸው፣ የሊባኖስ ተራራም በብርሃን ደመቀ፡፡ በጨለማውስጥ የነበረው ዓለም ብርሃን የሚያይባት፣ የእውነተኛው ጸሐይ እናቱ ተወለደች፡፡ አባቷ ንጉስ ሰሎሞን “ሙሽራዬ ሆይ ከሊባኖስ ከእኔ ጋር ነዪ” እንዳለ በሊባኖስ ተራራ ተወለደች፡፡

ኢያቄምና ሐና የተሳሉትን ስእለታቸው አስታውሰው በሦት ዓመቷ ወስደው ለቤተ እግዚአብሔር ሲሰጧትም ካህኑ ዘካርያስ ስለምግቧ ስለተጨነቀ፤ ሕዝቡን ሰብስቦ ሳለ መልአኩ ፋኑኤል ኅብስት ሰማያዊ ጽዋዕ ይዞ ከሰማይ ወረደ፤ ዘካርያስ ለእርሱ የመጣ ሀብት መስሎት ሊቀበል ሲቀርብ ወደ ላይ ራቀበት፡፡ ከእርሱ በታች ካለው ስምዖን ጀምሮ በዚያ የተሰበሰቡት ሰዎችም በየተራ ቢሞክሩ በተመሳሳይ መልኩ ወደ ላይ ራቀባቸው፡፡ ምን አልባት ለእንግዶች የመጣ ሀብት እንደሆነ ብለው ሐናና ኢያቄም እንዲቀርቡ አደረጓቸው፤ ነገር ግን ለእነርሱም ራቀባቸው፤ ዘካርያስም ሐናን “እግዚአብሔር የሚያደርገውን የሚያውቅ የለምና ልጅቷን ትተሸ ወደዚህ ነይ” አላት፤ በዚያም ጊዜ ቅድስት ማርያም እናቷን ስትከተል መልአኩ ፋኑኤል ፈጥኖ ወርዶ አንድ ክንፉን አንጥፎ አንድ ክንፉን ጋርዶ መግቧት፤ በክብር ዐረገ፡፡

ሊቀ ካህናቱና ሕዝቡም “የምግቧ ነገር ከተያዘልን በቤት እግዚአብሔር ትኑር” ብለው ታህሣስ 3 ቀን ወደ ቤተ መቅደስ አስገቧት፡፡ ለ12 ዓመታትም ሰማያዊ ኅብስትና መጠጥ እየተመገበች በቤተ መቅደስ ኖረች፡፡ በ15 ዓመቷም ለአቅመ ሔዋን በመድረሷ ከቤተ መቅደስ ትውጣልን በማለት አይሁድ በጠላትነት ተነሡባት፡፡ ካህኑ ዘካርያስም በጸለየ ጊዜ እግዚአብሔር አረጋዊው ዮሴፍ እንዲጠብቃት ምልክትን ሰጣቸው፡፡ ርግብም መጥታ በራሱ ላይ ዐረፈች፤ ስለሆነም ዮሴፍ እንዲጠብቃት ተወሰነ፡፡ ቤተ መቅደስም እየተመላለሰች ታገለግል ነበር፡፡

በመልአኩ ብስራትም የዓለሙ መድኅን ጌታን ጸንሳለች፡፡ ይህችን ብርሃን፣ የብርሃን እናት ገዳማውያን አባቶችና እናቶች ዘወትር በጸሎታቸው ያስቧታል፡፡ ገዳማቸውን እናግዝ፣ በዓታቸውን እናጽና፡፡

ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም

ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391

ወይም

አቢሲኒያ ባንክ
141029444

ለበለጠ መረጃ:- 09 38 64 44 44/0918077957

 #ገብተዋል  Policeበቁጥጥር ስር ዋሉ....
12/11/2025

#ገብተዋል
Police
በቁጥጥር ስር ዋሉ....

Address

14914 Saddle Creek Drive Burtonsville
Washington D.C., DC
MD20866

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Zeአራዳ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share