Zeአራዳ

Zeአራዳ Melake:
Ethiopia's news & entertainment hub. Follow for updates! Bringing you the pulse of Ethiopia!

From breaking news to the hottest trends in entertainment, join our community and celebrate our rich culture.

09/24/2025

አብርሐም ግዛዉ ኢንተርቴመንት "መስቀልና ባህላዊ አከባበር" የተሰኘ የመዝናኛ ኘሮግራም ቅዳሜ መስከረም 17 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 10:00-12:00 ሠዓት አርትስ ቴሌቪዥን ይዞላቹ ይቀርባል።

አሳዛኝ ዜና፡ አትሌት ሸዋረግ አለነ አማረ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየችበ2025 የስዊድን ስቶክሆልም ማራቶን አሸናፊ የነበረችው አትሌት ሸዋረግ አለነ አማረ፣ በአዲስ አበባ ልምምድ ላይ እያለች ...
09/24/2025

አሳዛኝ ዜና፡

አትሌት ሸዋረግ አለነ አማረ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየች

በ2025 የስዊድን ስቶክሆልም ማራቶን አሸናፊ የነበረችው አትሌት ሸዋረግ አለነ አማረ፣ በአዲስ አበባ ልምምድ ላይ እያለች ከዚህ ዓለም በሞት መለየቷ ተዘግቧል።

አትሌቷ ልምምድ ላይ ሳለች የድካም ስሜት ተሰምቷት ወደ ሆስፒታል ከተወሰደች በኋላ ህይወቷ ማለፉን የደረሰን መረጃ ያመለክታል።

ኑሮዋን በሜክሲኮ ያደረገችው አትሌት ሸዋረግ አለነ፣ ለልምምድ ወደ አዲስ አበባ መጥታ ነበር። አትሌቷ የቀድሞው አትሌት አለነ አማረ ልጅ ስትሆን፣ አባቷ ለ25 ዓመታት ያህል በአሜሪካ፣ ኒው ዮርክ ሲኖሩ እንደነበርም ታውቋል።

አትሌት ሸዋረግ ከስቶክሆልም ማራቶን በተጨማሪ በርካታ ታላላቅ ውድድሮችን አሸንፋለች። ከነዚህም መካከል፦

* ሜክሲኮ ሲቲ ማራቶን - 2012 እና 2014
* ሳንቲያጎ ደ ቺሌ ማራቶን - 2013 እና 2014
* ማራቶን ኢንተርናሽናል ላላ - 2014
ነፍስ ይማር!

©️Ethio Runner

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን• መንፈሣዊ ተልዕኮ ተቀብላችሁ ለአገልግሎት የምትፋጠኑ ብጹዐን ሊቃነ ጳጳሳት ፣ ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን ፣ ካህናት እና ዲያቆናት• ከፍተ...
09/24/2025

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን
• መንፈሣዊ ተልዕኮ ተቀብላችሁ ለአገልግሎት የምትፋጠኑ ብጹዐን ሊቃነ ጳጳሳት ፣ ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን ፣ ካህናት እና ዲያቆናት
• ከፍተኛ የመንግስት እና የግል ሚዲያ ተቋማት
• የማህበራዊ ሚዲያ ባለሙያዎች እና ጥሪ የተደረገላችሁ ተጋባዥ እንግዶች ጥሪያችንን አክብራችሁ ስለተገኛችሁ በልዑል እግዚአብሔር ስም ልባዊ ምስጋናችንን ለማቅረብ እንወዳለን።

ወደ ዕለቱ ጋዜጣዊ መግለጫ ከመግባታችን በፊት ሐዋርያው ቅዱስ ዮሐንስ በራዕዩ "እነሆ ዅሉን አዲስ አደርጋለሁ … አዲስ ሰማይንና አዲስ ምድርንም አየሁ፤ ፊተኛው ሰማይና ፊተኛቱ ምድር አልፈዋልና። ባሕርም ወደ ፊት የለም››(ራእ. 21፥1-5) በማለት እንደተናገረው በማያልቀው ቸርነቱ መግቦቱ እና ጠብቆቱ የዘመናት ባለቤት ልዑል እግዚአብሔር ወቅትን እያፈራረቀ አዲስ ዓመትን ይሰጠናል። ዛሬም ቁጣውን በምህረት በደላችንን በትዕግስት አሳልፎልን ለ2018 ዓ.ም የዘመን መለወጫ ደርሰናል። እዚህ የተገኛችሁ እንግዶቻችን ፣ ይህን መርሃ ግብር በቀጥታ ስርጭት የምትከታተሉ ፣በተለያየ ሁኔታ ውስጥ እና በተለያየ የዓለም ክፍል የምትገኙ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን እንኳን ከዘመነ ማቲዎስ ወደ ዘመነ ማርቆስ በሰላም አሸጋገረን።
በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ “ገዳማዊ ህይወት” ራስን ለእግዚአብሔር በማስገዛት ትህትናን ገንዘብ አድርጎ እያንዳንዷን ሰዓት ፣ አንደበትን ፣ ጉልበትን እና ሃሳብን ለእግዚአብሔር በመስጠት የዓለም ዝና ሃብት ንብረት አላፊ የሆነውን ንግሥናን ውበትን በመናቅ ቤተሰብ እና ዘመድን ተለይቶ በመውጣት በገዳም ውስጥ በስርዓተ አበው ተወስኖ መስቀሉን ተሸክሞ መኖር መሆኑን ትነግረናለች።
ለዚህም ፋናዎች በብሉይ ኪዳን ከነበሩ ታላላቅ ነብያት ውስጥ የነብዩ ኤልያስን ፣ የነብዩ ኤልሳዕ እና የነብዩ ሄኖክን ህይወት መመልከት ይቻላል። ኤልሳዕ አባት እና እናት ያለው በአስራ ሁለት ጥማድ በሬ የሚያርስ የነበረ ፣ በዓለማዊው ህይወት ሲኖር ምንም ያልጎደለበት ነበር። ነገር ግን የእግዚአብሔር ነብይ ኤልያስ ተከተለኝ ብሎ ጥሪ ሲያቀርብለት ምንም ሳያቅማማ በሬዎቹን አርዶ ለህዝቡ አብልቶ አባት እና እናቱን ተሰናብቶ ወደ ቀርሜሎስ ተራራ ወደ ምድረ በዳ ወደ በርሃ ነብዩን ኤልያስን ተከትሎ ወጣ። ነብዩ ሔኖክም ቤተሰብ መስርቶ የሚኖር የነበረ ነገር ግን የበለጠ እግዚአብሔርን ለማገልገል ስለፈለገ አኗኗሩን እና አካሄዱን ከእግዚአብሔር ጋር በማድረጉ እግዚአብሔር ሰውሮታል።

በሐዲስ ኪዳንም ገዳማዊ ሕይወትን በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ተባርኮ እና ስርዓት ተዘርግቶ ተሰጥቶናል። የአዳምን በደል ይሽር ዘንድ በስጋ ከድንግል የተወለደው መድኃኔዓለም ይህ ህይወት የቅድስና መሆኑን እንድረዳው ከሁሉ አስቀድሞ የባረከው መሆኑን ልብ ልንለው የሚገባ ነው።
በነብያት እና በሐዋርያት ያላበቃው የገዳም ህይወት በእግረ ልቦና የሚከተሏቸው ብዙ ቅዱሳን ንዑዳን ብሩካን ጻድቃን አባቶቻችን እና እናቶቻችን በፍጹም ተጋድሎ ለጽድቅ በቅተው ገዳማዊ ህይወትን ገድሉን እና ትሩፋቱን ኖረው አሳይተውናል። ቅዱስ ጳውሎስ በዕብራውያን መልዕክቱ ላይ የነብያት እና የሐዋርያትን ተጋድሎ እንዲህ ሲል ያስረዳናል። ''በድንጋይ ተወግረው ሞቱ ተፈተኑ በመጋዝ ተሰነጠቁ በሰይፍ ተገድለው ሞቱ ሁሉን እያጡ መከራን እየተቀበሉ እየተጨነቁ የበግና የፍየል ሌጦ ለብሰው ዞሩ፤ ዓለም አልተገባቸውምና በምድረ በዳ በተራራ በዋሻ እና በምድር ጉድጓድ ተቅበዘበዙ ይላል።

ስለ ስሜ ቤቱን ፣ ወንድም እህቶቹን ወይም አባት እናቱን ፣ ሃብት ንብረቱን የተወ ሁሉ መቶ እጥፍ ይቀበላል የተባለው ዓለምን ንቀው ለተከተሉት ገዳማውያን ጭምር የተነገረ ቃል መሆኑን ቤተክርስቲያናችን ታስተምራለች። ዛሬም በተለያዩ ገዳማት ውስጥ ግርማ ለሊቱን ድምጸ አራዊቱን ታግሰው ስለ ዓለም ሰላምን ፣ ድኅነት ሌት ተቀን የሚማጸኑ በሱባኤ እና በአርምሞ ያሉ መነኮሳይት እና መነኮሳት ይገኛሉ። ከነዚህም መካከል በሙት አንሳ ማር ቅዱስ ሚካኤል አንድነት ገዳም የሚገኙ መነኮሳትን መጥቀስ ይቻላል።

ከዚህም ቀደም እንደሚታወሰው የካቲት 14 ቀን 2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ ዋቢ ሸበሌ ሆቴል በተሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ በገዳሙ የነበሩ ችግሮች የተሰሩ ስራዎችንና በቀጣይ የሚሰሩ ዕቅዶችን በተመለከተ ዝርዝር ጉዳዮች ተነስተዋል። ገዳማውያኑ የሚቀምሱት እህል የሚለብሱት ልብስ እንዲሁም በሱባዔ የሚወሰኑበት በዓት እንደሌላቸው በተፈጥሮአዊ እና ሰው ሰራሽ አደጋዎች እየተፈተኑ መሆናቸው ይታወሳል።

ያሉባቸውን ዘርፈ ብዙ ተግዳሮቶች ከግምት በማስገባት ከህዝበ ክርስቲያኑ እና ከተቋማት በተገኙ ድጋፎች የእህል እና የአልባሳት ድጋፍ የተደረገ ሲሆን የእናቶች በዓት ግንባታ ተጠናቆ እናቶችን ማስገባት ተችሏል። ገዳሙ በኢኮኖሚ ነጻነት እንዲኖረው ራሱን እንዲችል ለማድረግ በጠቅላይ ቤተክህነት እና በሐገረ ስብከቱ እውቅና በገዳሙ ስም የባንክ አካውንቶች ተከፍተው ይፋ ተደርጓል።

ገዳሙም የተለያዩ ፕሮጀክቶችን በወረዳ ቤተክህነት ፣ በሐገረ ስከብት እና በጠቅላይ ቤተክህነት ጸድቆ በሊቃነ ጳጳሳት ቡራኬና የቅርብ ክትትል እየተደረገበት ከምዕመናን በሚገኘው ድጋፍ ስራዎች እየተሰሩ ይገኛል።

እነዚህን የልማት ሥራዎችን ለማከናወን የሚያስችል ገቢ የማሰባሰብ ሂደት ዕቅዶችን በመንደፍ እና በመቅረጽ ተግባራዊ ለማድረግ እየተንቀሳቀስን እንገኛለን። ለአብነትም ገዳሙ ያለበትን አሁናዊ እና ተጨባጭ ሁኔታ የሚገልፁ እና የሚያሳዩ የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ዶግማ፣ ቀኖና እንዲሁም ትውፊት በጠበቀ መልኩ፦
• በቴሌቪዥን እና ራዲዮን ማስታወቂያዎችን በማስተላለፍ ህብረተሰቡ መረጃው ኖሮት ድጋፍ እንዲያደርግ ጥሪ ተደረጓል።
• በማህበራዊ ሚዲያ በመጠቀም ለታቀዱት የልማት ስራዎች የሚያስፈልገውን ገቢ ለማሰባሰብ ጥረት ተደርጓል። በዚህም እስከ አሁን 29,750,620 /ሃያ ዘጠኝ ሚሊዮን ሰባት መቶ ሃምሳ ሺህ ስድስት መቶ ሃያ/ ብር። የገንዘብ ድጋፍ እና 6,208,810 /ስድስት ሚሊዮን ሁለት መቶ ስምንት ሺህ ስምንት መቶ አስር/ ብር የሚገመት የአይነት ድጋፍ ማሰባሰብ ተችሏል።

በሙት አንሳ ማር ቅዱስ ሚካኤል አንድነት ገዳም የተጀመረው ፕሮጀክት 18 (አስራ ስምንት) ወራትን ያስቆጠረ ሲሆን በነዚህ ጊዜያት በመጀመሪያው ምዕራፍ የፕሮጀክቱን ከ45% በላይ ማሳካት ተችሏል። ከእነዚህም መካከል፦
• የእናቶች በዓት እና የእንግዳ ማረፊያ በጥሩ ሁኔታ ተገንብቷል።
• ለገዳማውያኑ ለእንቅስቃሴ የማይመች እና አዳጋች የነበረው መንገድ 179 ሜትር ተራራ ተቦርቡሮ በአርማታ ደረጃ ተሰርቶለት አገልግሎት መስጠት ጀምሯል።
• የቤተ እግዚአብሔር ግንባታ ተከናውኖ ሙሉ ቁሳቁስ ተሟልቶ እየተገለገሉበት ይገኛል።
• በተደጋጋሚ የሚገጥመውን የምግብ አቅርቦት ችግር እና የአቅም ውስንነት በተወሰነ መልኩ ተፈቷል። በዘላቂነት ለመቅረፍ ጥረት እየተደረገ ይገኛል።
• ምንኩስና እና ሥራ የአንድ ሣንቲም ሁለት ገጽታዎች በመሆናቸው ገዳማውያኑ የእደ ጥበብ ውጤቶችን የሚያመርቱበትን ማምረቻ ሼድ ግንባታ ተከናውኗል ለስራው የሚያስፈልጉ መሳሪያዎች እና የጥሬ ዕቃ ግብአቶች ተሟልተዋል። ስለ ስራው ክህሎት እና ዕውቀት እንዲኖራቸው መነኮሳት ሙያዊ ስልጠና በብቁ ባለሙያዎች እንዲወስዱ ተደርጓል።
• የሻማ እና የጧፍ መስሪያ ማሽኖች ግዢ ተፈጽሞ ወደ ምርት ተገብቷል።
• አካባቢው በረሃማ እና በተደጋጋሚ በድርቅ የሚጠቃ በመሆኑ የአካባቢ ጥበቃ ሥራዎች እየተከናወኑ ይገኛል።
• ወደ ገዳሙ የሚያደርስ 8 (ስምንት) ኪሜ ደረጃ አንድ የጠጠር መንገድ ተሰርቶ ለአካባቢው ህብረተሰብ ጨምሮ አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛል።
• አስቸጋሪ የነበረው የጋቢዮን መልከአ-ምድር እጅጉኑ ባመረ መልኩ ተገንብቶ ተጠናቋል።
• በሐሙሲት ከተማ የገዳሙን እራስን የመቻል እንቅስቃሴ ለማጠናከር የንዋያተ ቅዱሳን መሸጫ እንዲሁም የችርቻሮ እና የጅምላ መሸጫ ሱቅ ተከፍቷል።
• በገዳሙ የአረጓዴ ልማትን ለማስፋፋት አመርቂ የሆኑ ስራዎች ተሰርተዋል።
• ለእናቶች መነኮሳይት ብቻ አገልግሎት የሚሰጥ ደረጃውን የጠበቀ ሻወር እና መጸዳጃ ቤት ተገንብቷል ።
• ለግንባታ አገልግሎት የሚውል የሲሚንቶ ማቡኪያ ማሽን የብረታ ብረትና የእንጨት መስሪያ ማሽነሪ ግዢ ተፈጽሟል።
• ከመንግሥት ተቋማት እና ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ውይይቶችን በማድረግ የገዳሙ ይዞታ ህጋዊ የማድረግ ሥራ ተከናውኗል።
• ለአብነት ት/ቤት ፣ ከቅድመ አንደኛ ደረጃ እስከ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ፣ መካከለኛ ደረጃ ጤና ጣቢያ እና ሌሎች አስፈላጊ የልማት ስራዎች የሚሰሩበት ህንጻ ግንባታ የሚገነባበት 30,000(ሰላሳ ሺህ) ካሬ ሜትር ቦታ በሀሙሲት ከተማ ላይ ከመንግስት በሊዝ ተረክቧል።
• ገዳሙን ከማስተዋወቅ እና ግንዛቤ ከመፍጠር አኳያ በቤተክርስቲያን አገልግሎት ላይ የሚገኙ ብጽዓን ሊቃነ ጳጳሳት፣ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን፣ መምህራነ ወንጌል እና ዘማሪያን ቦታው ድረስ ተገኝተው ገዳሙ ያለበትን ሁኔታ እና እየተሰሩ ያሉ ስራዎችን እንዲመለከቱ ተደርጓል።
• የቅዱስ ሚካኤልን በረከቱን ፣ ምልጃውን እና ተዓምሩን የሚገልጽ እና ገዳሙን ከማስተዋወቅ አኳያ በዲ/ን አቤል መክበብ "ማር ሚካኤል" የሚል ዝማሬ ተሰርቶ እና ቀረጻው በገዳሙ ላይ ተከናውኖ በማኅቶት ሚዲያ አማካኝነት ለህዝብ እንዲደርስ ተደርጓል አሁንም በእይታ ላይ ይገኛል።
• ቤተክርስቲያን አሐቲ እንደመሆኗ ትኩረታቸውን ሐይማኖታዊ ይዘት አድርገው ከሚሰሩ ሚዲያዎች ጋር በመተባበር ገዳሙን ለምዕመናን ተደራሽ እናደርጋለን ባልነው መሰረት በተለያዩ ሚዲያዎች ዘጋቢ ፊልሞችን እና ሰፊ ማብራሪያዎች ለምዕመኑ ተደራሽ ተደርጓል።
• ከገዳሙ ወደ ጸበል ቦታ እና ከጸበልተኞች ማደሪያ ወደ ጸበል ቦታ የሚወስደው አስቸጋሪ የተራራ መንገድ የነበረ ሲሆን ተራራው እየተቆረጠ ደረጃ ተሰርቶለት ለአቅመ ደካሞች እና በህመም ላይ ሆነው ፈውስን ለሚጠብቁ ጭምር ለእንቅስቃሴ ምቹ ተደርጎ ግንባታው ተጠናቋል።
በገዳሙ የሚታየው የልማት እንቅስቃሴ አበረታች የሚባል ቢሆንም ገዳማውያኑ ካሉበት ችግር አንፃር በተሻለ ፍጥነት ሥራዎች እንዳይከናወኑ ተግዳሮቶች ማጋጠማቸው አልቀረም። ከነዚሀም መካከል ፦
• በግንባታ ዕቃዎች ላይ ከጊዜ ወደ ጊዜ የሚስተዋል የዋጋ ልዩነት።
• ሰው ሰራሽና ተፈጥሮአዊ ችግሮች ዛሬም ድረስ የራሳቸውን አሉታዊ ተጽዕኖ መፍጠራቸው።
• በገዳሙ ውስጥ ስራ የሚሰራባቸው ቀናት ውስን መሆን ማለትም ገዳማውያኑ የሚያከብሯቸው በዓላት ሲቀነሱ በወር ውስጥ የሚሰራባቸው ቀናት ከ4-14 የሚሆኑት ቀናት ብቻ መሆኑ በዋናነት መጥቀስ ይቻላል።
እነዚህን ተግዳሮቶች ተቋቁሞ እያለፈ እስከአሁን የተከናወኑ ሥራዎች በተለይም የእናቶችን ችግር በመቅረፍ ደረጃ ጥሩና ገንቢ ናቸው።
ይህ የልማት ስራ ቀጣይነቱን ወደ አባቶች መነኮሳት በማድረግ ሥራዎች ተጀምረዋል። በትኩረት እየተሰሩ ከሚገኙ ስራዎች መካከል፦
• የአባቶች በዓት ግንባታ ሥራ
• የአባቶች ቤተ እግዚአብሔር ግንባታ ሥራ
• የእንጨት እና የብረታብረት ውጤቶች ማምረቻ ሼድ ግንባታ ሥራ
• የእህል መጋዘን ግንባታ ሥራ
• የጸበልተኞች ማረፊያ ቤት ግንባታ ሥራ
• የቅዱስ ሚካኤል ህንጻ ቤተክርስቲያን ግንባታ ሥራ
• የውሃ እና የመብራት አገልግሎት እንዲያገኙ የማድረግ ሥራ
• የአብነት ትምህርት ቤት ፣ የአስኳላ ትምህርት ቤት ፣ መካከለኛ ደረጃ ክሊኒክ ፣ የንጽህና መጠበቂያ ማቴሪያሎች ማምረቻ ፣ የምግብ ማቀነባበሪያ እና የከብት እርባታ በቀጣይ ከሚሰሩት ስራዎች መካከል ተጠቃሾች ናቸው።
በገዳሙ የሚከናወኑ የልማት ስራዎችን ከፍጻሜ አድርሶ ገዳማዊያኑም ካሉባቸው ተደራራቢ ችግሮች እንዲወጡ ለማድረግ በቀጣይ ለሚሰሩት የልማት ሥራዎች ማከናወኛ 210,000,000 /ሁለት መቶ አስር ሚሊዮን/ ብር የሚያስፈልግ ሲሆን ሁለት ዓመት ከስድስት ወር እስከ ሶስት ዓመት ያህል ይህንን የልማት ስራ ለማጠናቀቅ የግንባታ ወቅት የሚያስፈልግ በመሆኑ ለዚህም የሚሆን ድጋፍ ለማሰባሰብ የተለያዩ መርሀ-ግብሮች የሚከናወኑ ይሆናል።
ለአብነትም፦
 ጥቅምት 16 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 5፡00 ጀምሮ በሚሊኒየም አዳራሽ “ገዳማዊ ልማት ለቤተክርስትያን ትሩፋት’’ በሚል መሪ ቃል ብጹዓን ሊቃነ ጳጳሳት እና ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን በተገኙበት የገቢ ማሰባሰቢያ ጉባኤ ይኖረናል፤ ይሄ ጉባኤ ሰፊና ከ10,000 ሰዎች በላይ ይታደሙበታል ተብሎ የሚጠበቅ ጉባኤ ሲሆን በኛ በኩልም ዝግጅታችንን አጠናቀናል።
 በተመሳሳይ መልኩ በጎንደር እና በባህር ዳር ከተማዎች ላይ ጉባኤዎች የሚካሄዱ ይሆናል።
 የተለያዩ ባዛሮችን በማዘጋጀት በገዳሙ ላይ የሚመረቱ ምርቶችን ለምዕመኑ ተደራሽ እንዲሆን ይደረጋል ።
 የተለያዩ ሽልማቶችን የያዙ የሎተሪ እጣዎች ተዘጋጅተው ለምዕመኑ የሚቀርቡ ይሆናል።
 በተለያዩ ሚዲያ ገጾች አሁን እየሰራናቸው ያሉ ገዳሙን የማስተዋወቅና ገቢም የማሰባሰብ ስራ ይቀጥላል።
በፍትሐ ነገሥት ፍትሕ መንፈሳዊ አንቀጽ 16 ቊ125-127 እንደተገለጠው ምጽዋት ምሕረት ነው።እግዚአብሔር ከሰጪዎች ጋር የሚሰጥ ከተቀባዮች ጋር ሁኖ የሚቀበል በመስጠትና በመቀበል በሰዎች መካከል መተሳሰብና መረዳዳት እንዲኖር ባለጸግነትን ለባለጸጋዎቸ የሚሰጠው ከእነርሱ የሚያንሱትን እንዲያስተናግዱበት ነው ይላል። “ስጡ ይሰጣችኋል” ተብሏልና በምጽዋት የተጠቀሙ ብዙዎች ናቸው።
በቅዱስ ወንጌል እንደምናነበው ምናሴ ጠላቶቹ ከመከሩበት መቅሠፍት የዳነው ምጽዋትን በመመጽወቱ ነበር፤የጌታን ትእዛዝ፣ፈቃድና ትምህርት መሠረት አድርገው ያስተማሩ ቅዱሳን ሐዋርያትም “ካለው የሚሰጥ ብፁዕ ነው” በሚል ኃይለ ቃል የምጽዋትን ነገር ትኩረት ሰጥተውት እናገኛለን።
ከዚህም በተጨማሪ በመፅሐፍ ቅዱስ ላይ (የሐዋ.ሥራ 20 ፥ 35) (ማቴ. 10 ፥ 8)
(2ኛ ቆሮ. 9፥7-12) እና (መፅሀፈ ዕዝ 9፥5) ላይ በሰፊው ስለምጽዋት እና ከመስጠት ስለሚገኘው በረከት ተፅፎ እናገኛለን።
ጠቢቡ ሰሎሞንም ‹ለድሃ ቸርነትን የሚያደርግ ለእግዚአብሄር ያበድራል፣በጎነቱንም መልሶ ይከፍለዋል› ይላል ፤ ዛሬም በዚህ በእኛ ዘመን ፣ ለዓለሙ ሰላም፣ ለሰው ልጆች ሁሉ ድህነት ዘወትር የሚማጸኑት እነዚህ ገዳማዊያን በተለያዩ ችግሮች እየተፈተኑ ነውና ፣ ያሉባቸው ችግሮች ተፈተውላቸው፣ ዓለሙን ትተው የሄዱበትን የምንኩስና ህይወት ፈጣሪን መማጸን ላይ ብቻ ትኩረት እንዲያደርጉ፣ ሁሉም ምዕመን ባለው በጸጋ በዕውቀቱ፣ በጉልበቱ እና በገንዘቡ ድጋፍ እንዲያደርግ በልዑል እግዚአብሄር ስም ጥሪ እናቀርባለን።

ወስብሐት ለእግዚአብሔር!
መስከረም ፲፬ ቀን ፳፲፻፲፰ ዓ.ም

ከሰብዐቱ ሊቃነ መላእክት አንዱ ሩፋኤል እኔ ነኝቊጥሩ ከሰባቱ ሊቃነ መላእክት ሲሆን፤ “ሩፋ” ማለት ሐኪም፤ ኤል ማለት እግዚአብሔር ማለት ሲኾን ሩፋኤል ማለት “እግዚአብሔር ሐኪሜ ነው” ማለት...
09/23/2025

ከሰብዐቱ ሊቃነ መላእክት አንዱ ሩፋኤል እኔ ነኝ

ቊጥሩ ከሰባቱ ሊቃነ መላእክት ሲሆን፤ “ሩፋ” ማለት ሐኪም፤ ኤል ማለት እግዚአብሔር ማለት ሲኾን ሩፋኤል ማለት “እግዚአብሔር ሐኪሜ ነው” ማለት ነው፡፡

ቅዱስ ኤጲፋንዮስም በመጽሐፈ አክሲማሮስ “በራማ ሰማይ የሚገኘውን ሁለተኛውን ዐሥሩን ነገድ መናብርት ሲላቸው አለቃቸው ቅዱስ ሩፋኤል ነው፤ እነዚህም ረቂቅ የሆነ የመብረቅ ጋሻ የእሳት ጦር ይዘው ከነፋስ ይልቅ የፈጠኑ ሲሆኑ በራማ በሁለተኛው ክፍል ላይ አስፍሯቸዋል፡፡

ቅዱስ ሩፋኤል ነገደ መናብርት የሚባሉትን ራማ በሚባለው ሰማይ የሚኖሩትን ነገደ መላእክት የሚመራቸው ናቸው፡፡ አባ ጊዮርጊስም በሰዓታቱ “ጽርሐ አርያም አዳራሹ፤ የትጉሃን መኖሪያ ቦታው የሚኾን እግዚአብሔር ቅዱስ፣ ቅዱስ፣ ቅዱስ ተብሎ በአንድነት በሦስትነት ይመሰገናል፤ ካህናተ ሰማይ በዙሪያው ይቆማሉ፤ በዙፋኑ ፊት እየሰገዱ አክሊሎቻቸውን ያወርዳሉ፤ እሳትነቱ በሚበርቅ፣ በሚል ጊዜ እንዳይመታቸው ይንቀጠቀጣሉ” ይላል፡፡

ቅዱስ ሩፋኤል ከሚመራው ከዚህ ነገድ 24ቱ ካህናተ ሰማይ ወጥተዋል፡፡” ይለናል፡፡ በመጽሐፈ ሄኖክ 6÷3 ላይም “በሰው ቁስል ላይ የተሾመ ከከበሩ መላእክት አንዱ ቅዱስ ሩፋኤል ነው” ተብሏል፡፡ ሊቁ ቅዱስ ባስልዮስም “በፊቱ የሚቆሙ የመላእክት ሰራዊትም ሁሉ ጩኸው ያመሰግኑታል፤ የመላእክት አለቆችም ለማይታይ ለባለዚህ ስም ዘንበል ብለው ይሰግዳሉ፤ ዙፋኑን የሚሸከሙ አርባዕቱ እንስሳ ጩኸው ያመሰግኑታል፤ ዕጣንን የተመሉ የወርቅ ማዕጠንት በእጆቻቸው ያለ ሃያ አራቱ ካህናተ ሰማይ ይኸውም የቅዱሳን ጸሎት ነው እስከ ዘላለሙ ሕያው በሆነው ፊት የሚቀበለው መሥዋዕት አድርገው ወደ ላይ ያሳርጋሉ” በማለት አስተምሯል፡፡ በ720 ዓ.ዓ ዐሥሩ ነገደ እስራኤል ሲማረኩ ጦቢት የተባለ ጻድቅ ሰው ዐብሮ ተማርኳል፡፡ ቅዱስ ሩፋኤል ይህን ጦቢትን የተራዳ መልአክም ነው፡፡

በመጽሐፈ ጦቢት 2÷14 እንደተጻፈው ሰውን በመርዳት በደግነቱ የታወቀው ጦቢት ከመንገድ ወድቆ የተገኘ በድን ቀብሮ፤ በዚያው ሌሊት ከቅጥሩ አጠገብ ፊቱን ተገልጦ ተኝቶ ሳለ አዕዋፍ ትኩስ ኩስ ዐይኑ ላይ ጥለውበት እንደ ብልዝ ያለ ወጥቶበት ዐይኑ ጠፋ፤ ሚስቱም ባለማስተዋል “በጐነትህ ምጽዋትህ ያዳነህ ወዴት ነው?” በማለት ስትናገረው ዐዝኖ ሞትን ተመኘ፡፡ ቅዱስ ሩፋኤልም አይኑን ሲፈውሰው፣ በላይዋ ላይ ያደረ ጋኔን ባሎቿን ይገድልባት ቤተሰቦቿ ያንቋሽሿት የነበረችውን የራጉኤል ልጅ ሳራን ያደረባትን ርኩስ መንፈስ አስወጥቶ የጦቢት ልጅ ጦብያ እንዲያገባት አድርጓል፡፡ ቅዱስ ሩፋኤልም ከዚህ በኋላ ወደ ጦቢት በመኼድ ረዥም ዘመን የታወረ ዐይኑን አብርቶለት ከሰብዐቱ ሊቃነ መላእክት አንዱ ሩፋኤል እኔ ነኝ ብሏቸው ተሰውሯል፡፡

ጦቢት 12÷15፡፡ የመላዕክት ተራዳኢነት በቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ትልቅ ስፍራ አለው፡፡ ፈታሔ ማኀፀን ወሰፋድል። መወለድ መንፈሳዊ። ወሐኪም ሰማያዊ ይባላል። የወላድ ማኀፀን እንዲፈታ በእግዚአብሔር ስለተሾመ አዋላጅ ብትኖርም ባትኖርም ቅዱስ ሩፋኤል በዚያ አይታጣም፡፡ በተለይ በባላገር ያሉ ሴቶች በምጥ ጊዜ ሁሉ መልክአ ሩፋኤል በአንገታቸው ያነግታሉ፣ ይጸልያሉ፣ የተጸለየበትንም ጸበል ይጠጣሉ፤ በፍጥነትም ይወልዳሉ። በየወሩ በ13 ቀን መታሰቢያ በዓሉ የሚከበር ሲሆን ጳጉሜ 3 ደግሞ ዓመታዊ በዓሉ ነው፡፡ የቅዱስ ሩፋኤል በረከትና ረድኤቱ አይለየን፤ ምልጃው ይጠብቀን፡፡ ገዳማውያንም ይህን ተራዳኢነቱን በመታመን ዘወትር በጸሎታቸው ይጠሩታል፡፡ ገዳማቸውን በመደገፍና በዓታቸውን በማጽናት የበረከታቸው ተሳታፊ እንሁን፡፡

ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም

ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391

ወይም

አቢሲኒያ ባንክ
141029444

የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444

ያማል የአመቱ ምርጥ ወጣት ተጫዋች ተባለ ! በ ውድድር አመቱ ከ 21 አመት በታች ድንቅ ብቃታቸውን ላሳዩ ታዳጊ ተጫዋቾች የሚሰጠው " Kopa Trophy " አሸናፊ ይፋ ተደርጓል ። የባርሴሎ...
09/23/2025

ያማል የአመቱ ምርጥ ወጣት ተጫዋች ተባለ !

በ ውድድር አመቱ ከ 21 አመት በታች ድንቅ ብቃታቸውን ላሳዩ ታዳጊ ተጫዋቾች የሚሰጠው " Kopa Trophy " አሸናፊ ይፋ ተደርጓል ።

የባርሴሎናው የፊት መስመር ተጫዋች ላሚን ያማል የአመቱ ምርጥ ወጣት ተጫዋች በመባል መመረጡ ይፋ ሆኗል።

ስፔናዊው የፊት መስመር ተጫዋች ላሚን ያማል ለተከታታይ ሁለተኛ አመት የአመቱ ምርጥ ወጣት ተጫዋች ሽልማት አሸንፏል።

ከአምስቱ የ " Kopa Trophy " ሽልማቶች መካከል አራቱን የባርሴሎና ተጨዋች ማሸነፍ ችለዋል።

Source: TikVah

ቡርኪናፋሶ፣ ማሊ እና ኒጀር ከዓለም አቀፉ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት ለቀው መውጣታቸውን አስታወቁበቅርቡ ከምዕራብ አፍሪካ ቀጣናዊ ቡድን ኢኮዋስን በይፋ ለቀው በመውጣት "የሳህል ግዛቶች ሕብረት"...
09/23/2025

ቡርኪናፋሶ፣ ማሊ እና ኒጀር ከዓለም አቀፉ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት ለቀው መውጣታቸውን አስታወቁ

በቅርቡ ከምዕራብ አፍሪካ ቀጣናዊ ቡድን ኢኮዋስን በይፋ ለቀው በመውጣት "የሳህል ግዛቶች ሕብረት" የተሰኘ የየራሳቸው ቡድን የመሠረቱት ቡርኪናፋሶ፣ ማሊ እና ኒጀር የዓለም አቀፉ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት (ICC)ን “የቅኝ ግዛት ጭቆና መሣሪያ” ሲሉ በመጥራት ከፍርድ ቤቱ በይፋ መውጣታቸውን ትናንት ሰኞ በጋራ ባወጡት መግለጫ አስታውቀዋል፡፡

ቡርኪና ፋሶ፣ ማሊ እና ኒጀር እ.ኤ.አ. በ2020 እና 2023 መካከል በተደረጉ መፈንቅለ መንግሥቶች በወታደራዊ መሪዎች ቁጥጥር ሥር መዋላቸው የሚታወቅ ሲሆን፤ ራሳቸውን ከምዕራባዊያን ለማግለል በማሰብ በቅርቡ የሳህል መንግሥታት ሕብረት (ኤ.ኢ.ኤስ) በተባለ ኮንፌዴሬሽን መስርተዋል፡፡

በወታደራዊ አገዛዝ ሥር የሚገኙት ሦስቱ ሀገራት ከምዕራቡ ዓለም እየተነጠሉ እንደ ሩሲያ ካሉ ሀገራት ጋር እየተቀራረቡ መምጣታቸውም ይታወቃል።

የሀገራቱ ወታደራዊ መሪዎች በትናንትናው ዕለት በጋራ በሰጡት መግለጫ ደግሞ፤ መቀመጫውን በኔዘርላንድስ ሄግ ያደረገው የዓለም አቀፉ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት "በኢምፔሪያሊዝም እጅ ውስጥ ያለ የኒዮ-ቅኝ አገዛዝ ጭቆና መሳሪያ ነው" ሲሉ ከሰውታል፡፡

"ፍርድ ቤቱ የተረጋገጡ የጦር ወንጀሎችን በሰው ልጆች ላይ የሚፈጸሙ ወንጀሎችን፣ የዘር ማጥፋት ወንጀሎችን እና የጥቃት ወንጀሎችን ለመቆጣጠር እና ለፍርድ ለማቅረብ እንደማይችል አረጋግጠናል" ብለዋል በመግለጫቸው።

ሦስቱ ሀገራት "ሰላምና ፍትሕን የሚያጠናክሩ አገር በቀል ዘዴዎችን" መፍጠር እንደሚፈልጉም መናገራቸውን ኤኤፍፒ ዘግቧል።

ይህም የሀገራቱ ከፍርድ ቤቱ የመውጣት ጥያቄ በይፋ ተግባራዊ የሚሆነው፤ ጉዳዩ በይፋ ለተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ከቀረበ ከአንድ ዓመት በኋላ ነው።

ቡርኪና ፋሶ፣ ማሊ እና ኒጀር በተለይ እንደ ሩሲያ ካሉ ሀገራት ጋር ያላቸውን ግንኙነት በማጠናከር ላይ የሚገኙ ሲሆን፤ የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን እ.ኤ.አ ከመጋቢት ወር 2023 ጀምሮ በዩክሬን ጦርነት ምክንያት በፍርድ ቤቱ የእስር ማዘዣ እንደወጣባቸው ይታወቃል፡፡

እ.ኤ.አ. በ2002 የተመሠረተው የዓለም አቀፉ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት፤ ሀገራት እንደ ጦር ወንጀሎች ያሉ ከባድ ወንጀል ፈፃሚዎችን ራሳቸው በቁጥጥር ሥር ለማዋል ፍላጎት እና አቅም በሚያጡበት ወቅት ለፍርድ የማቅረብ ተልዕኮን የያዘ ቢሆንም፤ በዓለም አቀፍ የዳኝነት ስርዓቱ ላይ በተደጋጋሚ ጥያቄዎች ይነሱበታል፡፡

ከዚህ ቀደም ሃንጋሪ ከ23 ዓመታት አባልነት በኋላ ከዓለም አቀፉ ወንጀለኞች ፍርድ ቤት አባልነት መውጣቷን ማስታወቋ ይታወሳል፡፡

#አሐዱ

🚨የደምበሌ ለቅሶ ምክንያቱ ምን ነበር?ኦስማን ዴምቤሌ ስሜታዊ ንግግሩን ሲያደርግ ሲያለቅስ የነበረው ሰው ሙስጠፋ ዲያታ ይባላል።ሁለቱ ከልጅነታቸው ጀምሮ የሚተዋወቁ ሲሆን በወጣት ቡድኖች ውስጥ...
09/23/2025

🚨የደምበሌ ለቅሶ ምክንያቱ ምን ነበር?

ኦስማን ዴምቤሌ ስሜታዊ ንግግሩን ሲያደርግ ሲያለቅስ የነበረው ሰው ሙስጠፋ ዲያታ ይባላል።

ሁለቱ ከልጅነታቸው ጀምሮ የሚተዋወቁ ሲሆን በወጣት ቡድኖች ውስጥ የቡድን አጋሮች ነበሩ። ኦስማን ፕሮፌሽናል ተጫዋች ሆነ። ሙስጠፋ ግን ህልሙን ሳያሳካ በጉዳት ምክንያት ከእግርኳስ ተገለለ።

🇫🇷 ኦስማን ደምበሌ🎙" ይህ ለአንተም ነው ምርጥ ጓደኛዬ። እኔ እና ሙስጠፋ ዲያታ የልጅነት ጓደኛሞች ነን። በሚገርም ሁኔታ ሙስጠፋ ከአራት አመት ጀምሮ የማውቀው ጓደኛዬ ነው። አንድ ጊዜ ሙስጠፋ አንድ ነገር ነገረኝ። አንድ ቀን በዓለም ላይ ምርጥ ተጫዋች ትሆናለህ። ሁሉንም ነገር አንድ ላይ አድርገናል። ቡዙ ነገር አጋጥሞናል። እሱ ሁልጊዜ ይደግፈኛል። እናም እስከ መጨረሻው ድረስ እሱ እና እኔ አብረን እንሆናለን።"

ሙስጠፋ እና ኡስማን የባሎንዶርን አሸናፊ መሆኑን ካወቁ በኋላ አብረው ማልቀስ ጀመሩ! 🥹

በዚህ ዓለም ከበጎ ነገር እንድታጡ አላደርጋችሁምቅዱስ ሚካኤል የልባችንን መልካም መሻት ይሙላልን🙏አምላካችን እግዚአብሔር ሳጥናኤልን አለቃ አድርጎ ቢሾመውም የተሰጠውን ክብር ትቶ አምላክነትን ...
09/22/2025

በዚህ ዓለም ከበጎ ነገር እንድታጡ አላደርጋችሁም

ቅዱስ ሚካኤል የልባችንን መልካም መሻት ይሙላልን🙏

አምላካችን እግዚአብሔር ሳጥናኤልን አለቃ አድርጎ ቢሾመውም የተሰጠውን ክብር ትቶ አምላክነትን በመሻቱና በትዕቢቱ ሥልጣኑ ተገፎ ወደ ምድር ሲጣል ኅዳር 12 ቀን ቅዱስ ሚካኤልን በቦታው ተሾሟል፡፡ በኢያሱ 5÷13-14 እንደተጻፈው ቅዱስ ሚካኤል ለኢያሱ ወልደ ነዌ የተመዘዘ ሰይፍ በእጁ ይዞ በፊቱ ቆሞ በሰው አምሳል ተገልጦ ታየው፣ ኢያሱም “አንተ ከእኛ ወገን ነህ ወይስ ከጠላቶቻችን?” አለው፡፡ እርሱም “እኔ የእግዚአብሔር ሠራዊት አለቃ ነኝ፤ አሁንም ወደ አንተ መጥቻለሁ” አለው፡፡ ኢያሱም ወደ ምድር በግንባሩ ተደፍቶ ሰገደ” ይህም የመልአኩን ክብር ያሳየናል፡፡ እስራኤላውያን በግብፅ ባርነት ለ215 ዓመታት በስቃይ ሲኖሩ ዕንባቸው መንበረ ጸባዖት ደርሶ በሊቀ ነቢያት ሙሴ መሪነት ባሕረ ኤርትራን ተሻግረውና ዐርባ ዘመናት ተጉዘው ምድረ ርስት ሲገቡ ቀኑን በደመና ሌሊቱን በብርሃን እየመራ ያደረሳቸው ቅዱስ ሚካኤል ነው፡፡

ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል በነገደ መላእክት ላይ ብቻ የተሾመ አይደለም፤ በእግዚአብሔር ሕዝብ ሁሉ ላይ እንጂ፡፡ ለእኛ ለሰዎች የምሕረት አማላጅ ሲሆን ለቅዱሳን፣ ለፃድቃንና ለሰማዕታት ደግሞ ረዳታቸው ነው፤ በሕይወታቸውና በተጋድሏቸውም እስከ መጨረሻው ያጸናቸዋል፡፡ በቤተ ክርስቲያናችን በመጽሐፈ ስንክሳርና በድርሳነ ሚካኤል እንደተጻፈው መልአኩ ቅዱስ ሚካኤል ዱራታዎስንና ሚስቱ ቴዎብስታን ከዲያብሎስ ፈተና ታድጓቸዋል፡፡ ዱራታዎስና ቴዎብስታ ሁልጊዜ ያለማቋረጥ የዚህን የከበረ መልአክ የቅዱስ ሚካኤልን የበዓሉን መታሰቢያ ያደርጉ ነበር፡፡ ነገር ግን በሀገር ውስጥ ችግር በሆነ ጊዜ ገንዘባቸው አለቀ፡፡ ለቅዱስ ሚካኤልም ለበዓሉ መታሰቢያ የሚያደርጉትን እስኪያጡ ድረስ ቸገራቸው፡፡ ዱራታዎስም የእርሱንና የሚስቱን ልብስ ሸጦ ለመልአኩ በዓል መታሰቢያ ያደርገው ዘንድ ይዞ ወጥቶ ሄደ፡፡

የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤልም በታላቅ መኮንን አምሳል ለዱራታዎስ ተገለጠለትና ወደ ባለ ጸጎች ሄዶ በእርሱ ዋስትና በአንድ ዲናር አንድ በግ፣ ወደ ባለ ስንዴ ሄዶ በእርሱ ዋስትና ስንዴን እንዲወስድ፣ ዳግመኛም ወደ ዓሣ አጥማጅ ሄዶ አንድ ዓሣ እንዲወስድ፣ ነገር ግን ወደ ቤቱ ሳይርስ የዓሣውን ሆድ እንዳይቀድ አዘዘው፡፡ ዱራታዎስም እንደታዘዘው አደረገ፡፡ ወደ ቤቱም በተመለሰ ጊዜ ቤቱ ሁሉ በበረከት ተመልቶ አገኘው፡፡ እርሱም እጅግ ተደስቶ የዚህን የክቡር መልአክ የመታሰቢያውን በዓል አደረገ፡፡ ጦም አዳሪዎችንና ድኆችንም ጠርቶ አጠገባቸው፡፡ ለዱራታዎስና ለሚስቱ ቴዎብስታ ቅዱስ ሚካኤል ለሁለተኛ ጊዜ ተገለጠላቸው፡፡ ዱራታዎስንም የዓሣውን ሆድ እንዲሰነጥቅ አዘዘው፡፡ በሰነጠቀውም ጊዜ ሦስት መቶ የወርቅ ዲናር በዓሣው ሆድ ውስጥ ተገኘ፡፡

ቅዱስ ሚካኤልም ዱራታዎስንና ሚስቱን ቴዎብስታን “ከዚህ ዲናር ወስዳችሁ ለባለ በጉ፣ ለባለ ዓሣውና ለባለ ስንዴው ዕዳችሁን ክፈሉ፡፡ የቀረውም ለፍላጎታችሁ ይሁናችሁ እግዚአብሔር አስቧችኋልና በጎ ሥራችሁን፣ መሥዋዕታችሁንና ምጽዋታችሁን አስቦ በዚህ ዓለም አሳመረላችሁ፣ በኋለኛውም መንግሥተ ሰማያትን አዘጋጅቶላችኋል” አላቸው፡፡ እነርሱም ይህን ነገር ሲሰሙ ደነገጡ፤ የከበረ ገናናው መልአክም “ከመከራችሁ ሁሉ ያዳንኳችሁ የመላእክት አለቃ እኔ ሚካኤል ነኝ፤ መሥዋዕታችሁንና ምጽዋታችሁን ወደ እግዚአብሔር ፊት ያሳረግሁ እኔ ነኝ፡፡ አሁንም በዚህ ዓለም ከበጎ ነገር እንድታጡ አላደርጋችሁም” አላቸው፡፡ ይህንንም ከነገራቸው በኋላ ወደ ሰማያት ወጣ፤ እነርሱም በፍርሃትና በክብር ሰገዱለት፡፡ ገዳማውያን ይህን ተራዳኢነቱን አምነው ዘወትር ይማጸኑታል፣ ይሰማቸውማል፡፡ ገዳማቸውን ስንደግፍ በዓታቸውን ስናጸና የጸሎታቸውና የበረከታቸው ተሳታፊ እንሆናለን፡፡

ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም

ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391

ወይም

አቢሲኒያ ባንክ
141029444

የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444

ቅዱስ ሚካኤል የልባችንን መልካም መሻት ይሙላልን🙏በዚህ ዓለም ከበጎ ነገር እንድታጡ አላደርጋችሁምአምላካችን እግዚአብሔር ሳጥናኤልን አለቃ አድርጎ ቢሾመውም የተሰጠውን ክብር ትቶ አምላክነትን ...
09/22/2025

ቅዱስ ሚካኤል የልባችንን መልካም መሻት ይሙላልን🙏

በዚህ ዓለም ከበጎ ነገር እንድታጡ አላደርጋችሁም

አምላካችን እግዚአብሔር ሳጥናኤልን አለቃ አድርጎ ቢሾመውም የተሰጠውን ክብር ትቶ አምላክነትን በመሻቱና በትዕቢቱ ሥልጣኑ ተገፎ ወደ ምድር ሲጣል ኅዳር 12 ቀን ቅዱስ ሚካኤልን በቦታው ተሾሟል፡፡ በኢያሱ 5÷13-14 እንደተጻፈው ቅዱስ ሚካኤል ለኢያሱ ወልደ ነዌ የተመዘዘ ሰይፍ በእጁ ይዞ በፊቱ ቆሞ በሰው አምሳል ተገልጦ ታየው፣ ኢያሱም “አንተ ከእኛ ወገን ነህ ወይስ ከጠላቶቻችን?” አለው፡፡ እርሱም “እኔ የእግዚአብሔር ሠራዊት አለቃ ነኝ፤ አሁንም ወደ አንተ መጥቻለሁ” አለው፡፡ ኢያሱም ወደ ምድር በግንባሩ ተደፍቶ ሰገደ” ይህም የመልአኩን ክብር ያሳየናል፡፡ እስራኤላውያን በግብፅ ባርነት ለ215 ዓመታት በስቃይ ሲኖሩ ዕንባቸው መንበረ ጸባዖት ደርሶ በሊቀ ነቢያት ሙሴ መሪነት ባሕረ ኤርትራን ተሻግረውና ዐርባ ዘመናት ተጉዘው ምድረ ርስት ሲገቡ ቀኑን በደመና ሌሊቱን በብርሃን እየመራ ያደረሳቸው ቅዱስ ሚካኤል ነው፡፡

ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል በነገደ መላእክት ላይ ብቻ የተሾመ አይደለም፤ በእግዚአብሔር ሕዝብ ሁሉ ላይ እንጂ፡፡ ለእኛ ለሰዎች የምሕረት አማላጅ ሲሆን ለቅዱሳን፣ ለፃድቃንና ለሰማዕታት ደግሞ ረዳታቸው ነው፤ በሕይወታቸውና በተጋድሏቸውም እስከ መጨረሻው ያጸናቸዋል፡፡ በቤተ ክርስቲያናችን በመጽሐፈ ስንክሳርና በድርሳነ ሚካኤል እንደተጻፈው መልአኩ ቅዱስ ሚካኤል ዱራታዎስንና ሚስቱ ቴዎብስታን ከዲያብሎስ ፈተና ታድጓቸዋል፡፡ ዱራታዎስና ቴዎብስታ ሁልጊዜ ያለማቋረጥ የዚህን የከበረ መልአክ የቅዱስ ሚካኤልን የበዓሉን መታሰቢያ ያደርጉ ነበር፡፡ ነገር ግን በሀገር ውስጥ ችግር በሆነ ጊዜ ገንዘባቸው አለቀ፡፡ ለቅዱስ ሚካኤልም ለበዓሉ መታሰቢያ የሚያደርጉትን እስኪያጡ ድረስ ቸገራቸው፡፡ ዱራታዎስም የእርሱንና የሚስቱን ልብስ ሸጦ ለመልአኩ በዓል መታሰቢያ ያደርገው ዘንድ ይዞ ወጥቶ ሄደ፡፡

የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤልም በታላቅ መኮንን አምሳል ለዱራታዎስ ተገለጠለትና ወደ ባለ ጸጎች ሄዶ በእርሱ ዋስትና በአንድ ዲናር አንድ በግ፣ ወደ ባለ ስንዴ ሄዶ በእርሱ ዋስትና ስንዴን እንዲወስድ፣ ዳግመኛም ወደ ዓሣ አጥማጅ ሄዶ አንድ ዓሣ እንዲወስድ፣ ነገር ግን ወደ ቤቱ ሳይርስ የዓሣውን ሆድ እንዳይቀድ አዘዘው፡፡ ዱራታዎስም እንደታዘዘው አደረገ፡፡ ወደ ቤቱም በተመለሰ ጊዜ ቤቱ ሁሉ በበረከት ተመልቶ አገኘው፡፡ እርሱም እጅግ ተደስቶ የዚህን የክቡር መልአክ የመታሰቢያውን በዓል አደረገ፡፡ ጦም አዳሪዎችንና ድኆችንም ጠርቶ አጠገባቸው፡፡ ለዱራታዎስና ለሚስቱ ቴዎብስታ ቅዱስ ሚካኤል ለሁለተኛ ጊዜ ተገለጠላቸው፡፡ ዱራታዎስንም የዓሣውን ሆድ እንዲሰነጥቅ አዘዘው፡፡ በሰነጠቀውም ጊዜ ሦስት መቶ የወርቅ ዲናር በዓሣው ሆድ ውስጥ ተገኘ፡፡

ቅዱስ ሚካኤልም ዱራታዎስንና ሚስቱን ቴዎብስታን “ከዚህ ዲናር ወስዳችሁ ለባለ በጉ፣ ለባለ ዓሣውና ለባለ ስንዴው ዕዳችሁን ክፈሉ፡፡ የቀረውም ለፍላጎታችሁ ይሁናችሁ እግዚአብሔር አስቧችኋልና በጎ ሥራችሁን፣ መሥዋዕታችሁንና ምጽዋታችሁን አስቦ በዚህ ዓለም አሳመረላችሁ፣ በኋለኛውም መንግሥተ ሰማያትን አዘጋጅቶላችኋል” አላቸው፡፡ እነርሱም ይህን ነገር ሲሰሙ ደነገጡ፤ የከበረ ገናናው መልአክም “ከመከራችሁ ሁሉ ያዳንኳችሁ የመላእክት አለቃ እኔ ሚካኤል ነኝ፤ መሥዋዕታችሁንና ምጽዋታችሁን ወደ እግዚአብሔር ፊት ያሳረግሁ እኔ ነኝ፡፡ አሁንም በዚህ ዓለም ከበጎ ነገር እንድታጡ አላደርጋችሁም” አላቸው፡፡ ይህንንም ከነገራቸው በኋላ ወደ ሰማያት ወጣ፤ እነርሱም በፍርሃትና በክብር ሰገዱለት፡፡ ገዳማውያን ይህን ተራዳኢነቱን አምነው ዘወትር ይማጸኑታል፣ ይሰማቸውማል፡፡ ገዳማቸውን ስንደግፍ በዓታቸውን ስናጸና የጸሎታቸውና የበረከታቸው ተሳታፊ እንሆናለን፡፡

ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም

ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391

ወይም

አቢሲኒያ ባንክ
141029444

የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444

መብራት ተቋርጧል‼️መብራት በደብረብርሃን፣በአዲስአበባ በከፊል፣ በወልዲያ፣ በቆቦ፣በሸዋሮቢት፣በሰቆጣ፣በአዳማ፣በሁመራ፣በወላይታ፣በቢሾፍቱ፣በአላማጣ፣በጅጅጋ፣በባሌሮቤእና በሌሎች የሀገሪቱ ክፍል ከ...
09/21/2025

መብራት ተቋርጧል‼️

መብራት በደብረብርሃን፣በአዲስአበባ በከፊል፣ በወልዲያ፣ በቆቦ፣በሸዋሮቢት፣በሰቆጣ፣በአዳማ፣በሁመራ፣በወላይታ፣በቢሾፍቱ፣በአላማጣ፣በጅጅጋ፣በባሌሮቤእና በሌሎች የሀገሪቱ ክፍል ከ ምሽቱ 1:20 ሰዓት ጀምሮ መብራት ተቋርጧል።

ድሮ  ሽምግልና ሲላክ እንደዚህ ወዝ ነበረው ! ሽማግሌ የሚሆኑት የሚከበሩ ፣ የሚወደዱ ፣ ሄደውም የሚያኮሩ ሰዎች ነበሩ። በሙሽራው ቤተሰቦች እንደ ዳይኖሰር ተፈልገው'ና ተመርጠው ነበር የሚላ...
09/21/2025

ድሮ ሽምግልና ሲላክ እንደዚህ ወዝ ነበረው ! ሽማግሌ የሚሆኑት የሚከበሩ ፣ የሚወደዱ ፣ ሄደውም የሚያኮሩ ሰዎች ነበሩ። በሙሽራው ቤተሰቦች እንደ ዳይኖሰር ተፈልገው'ና ተመርጠው ነበር የሚላኩት።

ከመኪናዎቹ ፣ ከልብሳቸው ፣ ከውስኪው ፣ ከስጋው ምናምን በላይ ሰዎቹ ነበር የሚከብዱት። የሚከበሩት። ሰዎቹ ነበር የልጁን ምንነት የሚመሰክሩት። የእነዚህ ሽማግሌዎች ውጣ ውረዳቸው ፣ ዕድሜያቸው ፣ እርጅናቸው ፣ ስክነታቸው ፣ ምድር ላይ ያሳለፉት የትዳር ህይወታቸው ለአዲሶቹ ሙሽራዎች ዋስ'ና ጠበቃ ፣ ልጃቸውን ለሚሰጡት ለሴቷ ቤተሰቦችም እፎይታ ነበር !

አሁን አሁን ከጊቢው አልፈው ሰፈሩን ሳይቀር እየቀወጡት'ና እየነጠሩ ገብተው 'ልጆትን ለልጃችን...' ብለው የሚጠይቁት ገና ጨፍረው ያልጨረሱ ፣ ገና ሱሪያቸውን ከፍ አድርገው ያልታጠቁ የሙሽራው ታናናሽ ጀለሶቹ ሆነዋል ...

ሽማግሌ ተልኮ አባቷ 'ልጁ ምን አለው ?' ብለው ሲጠይቁ ፣ 'እንዴ ልጆትስ ምን አላት ?' ብሎ የሚያፈጥ ትውልድ አፍርተናል...

......የሁሉ ስፖርት ቡሬ ካፕ ፌስቲቫልበ16 የጤና ቡድኖች መካከል ሲደረግ የነበረው ውድድር ሪቼ ፈረንሳይን በመለያ ምት 4-2 በማሸነፍ ሻምፒዮን ሆነዋል።ሪቼ የዋንጫ ፣ የሜዳሊያ እና የ1...
09/21/2025

......የሁሉ ስፖርት ቡሬ ካፕ ፌስቲቫል
በ16 የጤና ቡድኖች መካከል ሲደረግ የነበረው ውድድር ሪቼ ፈረንሳይን በመለያ ምት 4-2 በማሸነፍ ሻምፒዮን ሆነዋል።
ሪቼ የዋንጫ ፣ የሜዳሊያ እና የ100,000 ሺ ብር ሽልማት ተሸልሟል ።

የውድድሩ ኮከብ ጎል አስቆጣሪ በረከት ከቤላ የውድድሩ ኮከብ በረኛ ኤሊያስ ከሪቼ ኮከብ ተጫዋች ፍቃዱ ከፈረንሳይ የዋንጫ ተሸላሚ ሆነዋል።

ሁሉ ስፖርት ሁሌም እንዲአይነት መሰል ውድድሮችን በማዘጋጀት ከስፖርቱ ጎን ይቆማል።

Address

14914 Saddle Creek Drive Burtonsville
Washington D.C., DC
MD20866

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Zeአራዳ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share