የዳሞት ፑላሳ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት-Damot Pulasa Prosperity Party Office

  • Home
  • የዳሞት ፑላሳ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት-Damot Pulasa Prosperity Party Office

የዳሞት ፑላሳ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት-Damot Pulasa Prosperity Party Office ይህ የዳሞት ፑላሳ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ትክክለኛ ፔጅ ነው።

ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር አረንጓዴ አከባቢን ለመፍጠር ህብረተሰቡ ችግኝ መትከልና ማሳደግ ይገባል፦ አቶ ግዛቴ ግጄሐምሌ 16/2017 የወላይታ ዞን ደን አከባቢ ጥበቃና ልማት መምሪያ ከ...
23/07/2025

ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር አረንጓዴ አከባቢን ለመፍጠር ህብረተሰቡ ችግኝ መትከልና ማሳደግ ይገባል፦ አቶ ግዛቴ ግጄ

ሐምሌ 16/2017 የወላይታ ዞን ደን አከባቢ ጥበቃና ልማት መምሪያ ከወርልድ ቪዥን ኢትዮጵያ ጋር በመሆን የተራቆቱ አካባቢዎችን መልሶ ለማልማት በድጉና ፋንጎ ወረዳ የአረንጓዴ አሻራ መርሃግብር አካሂዷል።

በመርሃግብሩ የተገኙት የክልሉ ደን አከባቢ ጥበቃና ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ግዛቴ ግጄ ሀገራችን ኢትዮጵያ የአየር ለውጥ ተፅዕኖን ለማቋቋም የሚያስችል አረንጓዴ አሻራን ቀርጻ እየተገበረች ትገኛለች ብለዋል።

በክልሉ አንድ ተራራን በአንድ አከባቢን ለማልማት ታቅዶ እየተሰራ ይገኛል ያሉት ኃላፊው፥ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር አረንጓዴ አከባቢን ዕውን ለማድረግ የአረንጓዴ አሻራ ሚናው የጎላ እንደሆነም ጠቅሰዋል።

ተራሮች የስጋት ቀጠና ሳይሆኑ የሀብት ምንጭ እንዲሆኑ መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ጋር በመቀናጀት እየተሰራ መሆኑንም ገልፀዋል።

በተለይም የካርቨን ፕሮጀክት በመቅረጽ ሀብት ለመፍጠር ከወርልድ ቪይዥን ጋር እየተሰራ እንደሚገኝ የገለጹት ኃላፊው፥ በአረንጓዴ አሻራ በአለም አቀፍ አቅፍ ደረጃ ምሳሌ የሚሆኑ ስራዎች በክልሉ መኖሩንም ተናግረዋል።

የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ረዳት ፕሮፌሰር ሳሙኤል ተሰማ ህብረተሰቡ የአከባቢ ሥነ ምህዳር የሚቀየር ችግኝ በመትከል አካባቢውን መጠበቅና መንከባከብ እንዳለበት አሳስበዋል።

እንደዞን ለአየር ለውጥ የማይበገር አረንጓዴ አካባቢን ለመጠበቅ አንድ ተራራን የማልማት እና አረንጓዴ አሻራ መርሃግብር ተጠናክሮ መቀጠሉንም ገልፀዋል።

ሁሉም ህብረተሰብ አካባቢውን ለመጠበቅ በየአካባቢው ችግኝ መትከል እንዳለበት ያሳሰቡት ዋና አስተዳዳሪው፥ ችግኝ መትከል ብቻ ሳይሆን የተተከለውን መጠበቅምና ማሳደግ እንደሚገባም አሳስበዋል።

በድጉና ፋንጎ ወረዳ የተጎዳውን 'ዩሪያ' ተራራን መልሶ ለማልማት ከወርልድ ቪዥይን ጋር በመሆን እየተሰራ እንደሚገኝም ገልፀዋል።

የወላይታ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ ዶ/ር አማረ አቦታ ችግኝ መትከል ከምንም ነገር በላይ እንደሆነና ጠቀሜታውም እጅግ የጎላ መሆኑን ገልጸዋል።

አካባቢያችን ለመጠበቅ ችግኝ መትከል አስፈላጊ መሆኑን የገለጹት ኃላፊው፥ ህብረተሰብ ችግኝ የመትከል መርሃግብር አጠናክሮ እንዲያስቀጥልም ጥሪ አቅርበዋል።

የክልሉና የወላይታ ዞን ከፍተኛ አመራሮች በድጉና ፋንጎ ወረዳ ፋንጎ ቦሎሶ ቀበሌ 'ዩሪያ' ተራራን ለማልማት "በመትከል ማንሰራራት" በሚል መሪ ቃል አረንጓዴ አሻራቸውን አኑረዋል።

የህዝቡን ጥያቄዎች ለመፍታት በበጀት ዓመቱ የተገኙ ስኬቶችን ማስፈንጠሪያ አድርገን ልንጠቀም ይገባል፦ ረዳት ፕሮፌሰር ሳሙኤል ተሰማሐምሌ 15/2016 የወላይታ ዞን አስተዳደር ምክር ቤት የ20...
22/07/2025

የህዝቡን ጥያቄዎች ለመፍታት በበጀት ዓመቱ የተገኙ ስኬቶችን ማስፈንጠሪያ አድርገን ልንጠቀም ይገባል፦ ረዳት ፕሮፌሰር ሳሙኤል ተሰማ

ሐምሌ 15/2016 የወላይታ ዞን አስተዳደር ምክር ቤት የ2017 የስራ አፈጻጸም በመገምገምና በ2018 ዕቅድ ዝግጅት ዙሪያ በመወያየት ቀጣይ አቅጣጫን አስቀምጧል።

በመድረኩ የተገኙት የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ረዳት ፕሮፌሰር ሳሙኤል ተሰማ በሁሉም ዘርፍ የተከናወኑ ተግባራት አፈጻጸም ከህዝባችን ተጠቃሚነት አንጻር መገምገም ወሳኝ እንደሆነ ገልፀዋል።

በ2017 በሁሉም ዘርፍ የተመዘገቡ ስኬቶችን ይበልጥ አጠናክረን ማስቀጠል ይጠብቅብናል ያሉት ዋና አስተዳዳሪው፥ ለዚህም አመራሩ የተገኙ ስኬቶችን ማጎልበት እንደሚገባም አሳስበዋል።

የተገኘው ውጤት የህዝባችንን ሁለንተናዊ ብልፅግና ለማረጋገጥ በሚያደርገው ጥረት አቅም የሚሆናቸው መሆናቸውንም ጠቅሰዋል።

የህዝባችን የልማት ፍላጎት እጅግ ከፍተኛ መሆኑን የተናገሩት ዋና አስተዳዳሪው፥ ይህም በጀት የሚጠይቅ በመሆኑ ደረጃ በደረጃ ህዝቡን በማሳተፍ እንፈታለንም ብለዋል።

በየአካባቢው ያለውን ፀጋዎችንና ትልቁን የህዝብ አቅም በመጠቀም በተባበረ ክንድ ተጋግዘንና ተደጋግፈን መሰራት ይጠብቅብናልም ነው ያሉት።

በሁሉም አከባቢዎች የሌማት ትሩፋት በየመንደሩ እንዲኖር ማድረግ አለብን ያሉት ዋና አስተዳዳሪው፥ በግብርናው ዘርፍ ምርታማነትን ለማሳደግ ከመቼውም ጊዜ በላይ ትኩረት መሰጠት እንዳለበትም አሳስበዋል።

የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ እና በጤና ተቋማት የአገልግሎት አሰጣጥን ለማሻሻል ልዩ ትኩረት መስጠት እንደሚጠይቅ አመላክተዋል።

ኑሮ ውድነትን ለማረጋጋት የሰንበት ገበያ ቋሚነት ባለው መልኩ ለማስቀጠል የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት መቀናጀት እንዳለባቸውም አሳስበዋል።

የኢንቨስትመንት መሬት አቅርቦት፣ ለወጣቱ የስራ ዕድል መፍጠር፣ የገቢ አቅምን ማሳደግ እና ሌሎች መሠረታዊ የህዝብ ጥያቄዎች የቀጣይ ትኩረት አቅጣጫዎች አድርገን መንቀሳቀስ አለብን ሲሉም አመላክተዋል።

የህዝቡን ጥያቄን መመለስ የሚያስችል ዕቅድ አዘጋጅተን ቀጣይ መረባረብ እንደሚያስፈልግም አቅጣጫ አስቀምጠዋል።

የወላይታ ዞን ም/አስተዳዳሪና የከተማና መሠረተ ልማት መምሪያ ኃላፊ አቶ ተስፋሁን ታዴዎስ ከተሞች ለነዋሪዎቹ ምቹ፣ ወቅቱንና ዘመኑን የሚመጥኑ እንዲሆኑ የተጀመሩ የኮሪደር ልማት ስራዎችን ማጠናከር ያስፈልጋል ብለዋል።

ከተሞች በፕላን መምራት እንዳለባቸው ያሳሰቡት ም/አስተዳዳሪው፥ ከተሞችን የብልፅግና ተምሳሌት ለማድረግ የማዘመን ስራ መሰራት እንዳለበትም አሳስበዋል።

የገጠር ኢንቨስትመንት ተያይዞ የሚስተዋሉ ችግሮችን መፍታት ይጠይቃል ያሉት፤ ዋና አስተዳዳሪው የኢንቨስትመንት መሬት ወስዶ ያለሙና ያላለሙ የመለየት ስራ መሰራት እንዳለበትም ጠቅሰዋል።

ለወጣቱ የተለያዩ ስራ አማራጮችን በመጠቀም ስምሪት መስጠትና ነባሮችን የመሸጋገር ስራ መሰራት እንደሚገባም አጽንኦት ሰጥተዋል።

የንጹህ መጠጥ ውሃ ተደራሽነት እና የማዕድን ዘርፍ ልማት በአግባቡ መጠቀም ይገባል ያሉት ም/አስተዳዳሪው፥ የወላይታ ቡናን ለዓለም ገበያ ለማቅረብ እየተሰሩ ያሉ ስራዎች መጠናከር እንዳለባቸውም አሳስበዋል።

የዘንድሮ የወላይታ ዘመን መለወጫ ጊፋታ በዓል ሁሉም ህብረተሰብ በነቂስ ወጥተው እንዲያከብሩ ከወዲሁ አስፈላጊውን ዝግጅት መሰራት እንዳለበትም አንስተዋል።

የወላይታ ዞን ፕላን ልማት መምሪያ ኃላፊ አቶ ወንድሙ ወርስሶ አስፈፃሚ ሴክተር መሥሪያቤቶች የተጣለውን ግብ ለማሳለጥ እና ለተግባር ውጤታማነት እርስበርስ ተናብቦ መሰራት እንዳለባቸው አሳስበዋል።

''በጎነት ለኢትዮጵያ  ከፍታ''በሚል መሪ ቃል የተጀመረው የ2017 ዓ.ም ክረምት ወራት የወጣቶች በጎ ፈቃድ አገልግሎት በዳሞት ፑላሳ ወረዳ በሁሉም ቀበሌ መዋቅሮች ተጠናክሮ እንደቀጠለ ይገኛ...
22/07/2025

''በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ''በሚል መሪ ቃል የተጀመረው የ2017 ዓ.ም ክረምት ወራት የወጣቶች በጎ ፈቃድ አገልግሎት በዳሞት ፑላሳ ወረዳ በሁሉም ቀበሌ መዋቅሮች ተጠናክሮ እንደቀጠለ ይገኛል
*********
ዳሞት ፑላሳ፤ሐምሌ 15/2017 ''በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ''በሚል መሪ ቃል የተጀመረው የ2017 ዓ.ም ክረምት ወራት የወጣቶች በጎ ፈቃድ አገልግሎት በዳሞት ፑላሳ ወረዳ በሁሉም ቀበሌ መዋቅሮች ተጠናክሮ እንደቀጠለ ይገኛል።

በዛሬው ዕለት የወረዳው ወጣቶች አደረጃጀት ከጋሜ ካቤቾ ቀበሌ ወጣቶች ጋር በመሆን ለአቅመ ደካማ አቶ ተፈሪ ሀትሶ የቤት ግንባታ አስጀምረዋል።

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በሀገሪቱ በሁሉም አካባቢዎች ከፍተኛ ትኩረት ተሰጥተው እየተከናወነ ያለው የበጎ ሥራ በርካቶችን ከችግራቸው እንዲላቀቁ አድርጓል።

በወረዳው የ2017 ዓ.ም በበጎ ተግባራት ማለትም የአረጋውያን የቤት ግንባታና ጥገና፣የደም ልገሳ፣ የአረንጓዴ አሻራ ማኖር፣የፅዳትና የውበት ተግባራት፣የክረምት የማጠናከሪያ ትምህርቶች ወዘተ ተጠናክሮ በመተግበር ላይ ይገኛል።

የወላይታ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ወጣቶች ክንፍ ጽ/ቤት የክረምት ወራት የወጣቶች በጎ ፈቃድ አገልግሎት አስጀምሯልሐምሌ 15/2017 ዓ/ም የ2017/18 የወጣቶች የክረምት በጎ ፈቃድ አ...
22/07/2025

የወላይታ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ወጣቶች ክንፍ ጽ/ቤት የክረምት ወራት የወጣቶች በጎ ፈቃድ አገልግሎት አስጀምሯል

ሐምሌ 15/2017 ዓ/ም የ2017/18 የወጣቶች የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት የተለያዩ በጎ ተግባራትን አከናውኗል።

የወላይታ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ወጣቶች ክንፍ ጽ/ቤት ኃላፊ ወጣት ታደለ ሜጋ "በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ" በሚል መሪ ቃል የተጀመረው የክረምት ወራት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ተግባርን ተጠናክሮ መቀጠሉን አስታውቋል።

በወላይታ ዞን በክረምት ወጣቶች በጎ አገልግሎት ከ98 ሺ በላይ የወጣቶች ክንፉ አባላት እየተሳተፉ እንደሚገኙ ተናግረዋል ።

ለአቅም ደካሞችን በመደገፍ በበጎ አገልግሎት ላይ በስፋት እንዲሳተፉ በማድረግ የማህበረሰቡን የማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮችን በመፍታትና የበጎ ፈቃደኝነት ባህል ለማጎልበት ዓላማ ያደረገ እንደሆነ ገልጸዋል።

የበጎ ፈቃድ አገልግሎት የዜጎችን አብሮነት፣ መተሳሰብ፣ ሁለንተናዊ ትብብርና መተጋገዝ ለማጠናከር ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያበረክታል ብለዋል።

በርካታ ወጣቶች በክረምት ወራት ጊዚያቸውን በበጎ ዓላማ በማዋልና አቅም ደካሞችን የመደገፍ ሥራ እያከናወኑ እንደሚገኙ ገልጿል።

አቶ ምህረቱ ዳና የወላይታ ዞን የወጣቶች ምክር ቤት ፕረዚዳንት እንደጠቆሙት በጎ ፈቃድ አገልግሎት በሀገራችን ተጀምሮ የቆየ ቢሆንም ከለውጥ ወዲህ በኃላ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ እንደሚገኝም አስታውቀዋል።

አቶ ያኪኒ ማርቆስ የገሱባ ከተማ የመንግስት ዋና ተጠሪ እንደገለፁት ወጣቶች በጎነት ከፈጣሪ በረከትን የሚያስገኝ ተግባር በመሆኑ ሁሉም ማህበረሰብ በዚህ መልካም መሳተፍ እንደሚገባ አሳስበዋል ።

በንቅናቄው መድረክ የአቅመ ደካሞች ቤት ግንባታ፣ የችግኝ ተከላና ለአቅመ ደካማ ቤተሰብ ተማሪዎች ደብተር ለግሰዋል።

በወላይታ ዞን ህብረተሰቡ የዲጂታል መታወቂያ (ፋይዳ) ባለቤት እንዲሆኑ በንቅናቄ መልኩ በሁሉም ወረዳና ከተማ አስተዳደር ምዝገባው ተጠናክሮ ቀጥሏል።ፋይዳ መታወቂያ እንደ ስሙ ፋይዳው ብዙ ነው...
22/07/2025

በወላይታ ዞን ህብረተሰቡ የዲጂታል መታወቂያ (ፋይዳ) ባለቤት እንዲሆኑ በንቅናቄ መልኩ በሁሉም ወረዳና ከተማ አስተዳደር ምዝገባው ተጠናክሮ ቀጥሏል።

ፋይዳ መታወቂያ እንደ ስሙ ፋይዳው ብዙ ነው:: ፋይዳ መታወቂያ በማውጣት ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን እናድርግ!!

የዳሞት ፑላሳ ወረዳ ሴቶችና ህፃናት ጉዳዮች ጽ/ቤት ከወረዳው ሴቶች አደረጃጀት ጋር በመሆን በህሌና ቆርኬ ቀበሌ የመኖሪያ ቤት ያልነበራት ለአቅመ ደካማ ወ/ሮ ስራቴ ጋሞ የቤት ግንባታ አስጀመ...
22/07/2025

የዳሞት ፑላሳ ወረዳ ሴቶችና ህፃናት ጉዳዮች ጽ/ቤት ከወረዳው ሴቶች አደረጃጀት ጋር በመሆን በህሌና ቆርኬ ቀበሌ የመኖሪያ ቤት ያልነበራት ለአቅመ ደካማ ወ/ሮ ስራቴ ጋሞ የቤት ግንባታ አስጀመሩ
*********
ዳሞት ፑላሳ፤ሐምሌ 15/2017 በወላይታ ዞን የዳሞት ፑላሳ ወረዳ ሴቶችና ህፃናት ጉዳዮች ጽ/ቤት ከወረዳው ሴቶች አደረጃጀት ጋር በመሆን በህሌና ቆርኬ ቀበሌ የመኖሪያ ቤት ያልነበራት ለአቅመ ደካማ ወ/ሮ ስራቴ ጋሞ የቤት ግንባታ ሂደት አስጀምረዋል።

በቦታው ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የዳሞት ፑላሳ ወረዳ ሴቶችና ህፃናት ጉዳዮች ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ አየለች ቆልቻ እንዳሉት በጎነት ከንፁህ ህልውና የሚመነጭ ሰብዓዊነትን መሰረት ያደረገ ፓርቲያችን አንግቦ ከተነሳው ሰው ተኮር ሥራዎቻችን ውስጥ ቀዳሚ አጀንዳ ነው ብለዋል።

ወ/ሮ ስራቴ ጋሞ በወረዳው ህልና ቆርኬ ቀበሌ ነዋሪ ሲትሆን የመኖሪያ ቤት ባለመኖሩዋ ምክንያት በሰው ቤት እየተሰቃየች መቆየቷን ገልጿል።

መጽሐፍ ቅዱስ ሁሌም ከእጇ እንደማይጠፋ እና አንድ ቀን ፈጣሪ ቤት ይሰጠናል ብላ በቀበሌው እየዞረች ለሰው ሁሉ በተስፋ ስትናገር የቆየች መሆኑንም ኃላፊው አክለዋል።

የዳሞት ፑላሳ ወረዳ መንገድና ትራንስፖርት ልማት ጽ/ቤት ም/ኃላፊ እና የቀበሌው ደጋፊ አመራር አቶ ፀጋው ሳሙኤል በበኩላቸው በጎ ለመሥራት ሀብታም መሆን ብቻ አይጠበቅበትም በማለት በየደረጃው ያለው ህብረተሰብ ካለው አካፍለው የመስጠት ባህል ማሳደግ እንዳለበትም ጠቁመዋል።

የወረዳው ሴቶች አደረጃጀት በጎነትና አብሮነት ለኢትዮጵያ ከፍታ በሚል መሪ ቃል በዛሬው ዕለት የ2017 ዓ.ም የክረምት ወራት በጎ ሥራ ያስጀመሩ ሲሆን የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ መርሐግብርም ተከናውኗል።

የዳሞት ፑላሳ ወረዳ ፖሊስ ጽ/ቤት አመራሮችና አባላት ሳምንታዊ ኑ ቡና ጠጡ ፕሮግራም  በሌራ ቀበሌ ኮሚንቲ ፖሊሲንግ ማዕከል አካሄዱ ****ዳሞት ፑላሳ፤ሐምሌ 14/2017 በወላይታ ዞን ዳሞት...
21/07/2025

የዳሞት ፑላሳ ወረዳ ፖሊስ ጽ/ቤት አመራሮችና አባላት ሳምንታዊ ኑ ቡና ጠጡ ፕሮግራም በሌራ ቀበሌ ኮሚንቲ ፖሊሲንግ ማዕከል አካሄዱ
****
ዳሞት ፑላሳ፤ሐምሌ 14/2017 በወላይታ ዞን ዳሞት ፑላሳ ወረዳ ፖሊስ ጽ/ቤት አመራሮችና አባላት ሳምንታዊ ኑ ቡና ጠጡ ፕሮግራም የወረዳ ደጋፊ አመራሮችና ሌሎች የሚመለከታቸው አካላት በተገኙበት በሌራ ቀበሌ ኮሚንቲ ፖሊሲንግ ማዕከል አካሄደዋል።

''ወንጀልን በጋራ እንከላከል''በሚል መሪ ቃል በተዘጋጀው ሰነድ ዙሪያ ከተሳታፊዎች ጋር ሰፋ ያለ ምክክር ተደርጎበታል።

በዘላቂነት ወንጀልን ለመከላከል ሁሉም የባለድርሻ አካላት ሚና የጎላ መሆን እንዳለበት የተገለፀ ሲሆን ከህብረተሰቡ ጋር ቀጣይነት ያለው ምክክር በየጊዜው እንደሚካሄድም ተመላክቷል።

በዛሬው ዕለት በሌራ ቀበሌ ኮሚንቲ ፖሊሲንግ ማዕከል የተካሄደው መደበኛ ሳምንታዊ የውይይት መድረክ በቀጣይ ሳምንት ደግሞ በጉድቾ ቀበሌ የሚካሄድ መሆኑን ከወረዳው ፖሊስ ጽ/ቤት ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።

የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ረዳት ፕሮፌሰር ሳሙኤል ተሰማ ዛሬ በአሪ ዞን ደቡብ አሪ ወረዳ ከመር ቀበሌ በተፈጠረዉ የመሬት ናዳ ምክንያት የደረሰውን አደጋ አስመልክቶ የሐዘን መግለጫ መልዕክ...
21/07/2025

የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ረዳት ፕሮፌሰር ሳሙኤል ተሰማ ዛሬ በአሪ ዞን ደቡብ አሪ ወረዳ ከመር ቀበሌ በተፈጠረዉ የመሬት ናዳ ምክንያት የደረሰውን አደጋ አስመልክቶ የሐዘን መግለጫ መልዕክት አስተላልፈዋል።

ዛሬ በአሪ ዞን ደቡብ አሪ ወረዳ ከመር ቀበሌ በተፈጠረዉ የመሬት ናዳ ምክንያት አምስት የአንድ ቤተሰብ አባላት በሙሉ ህይወታቸዉ አልፏል።

በተፈጠረዉ ተፈጥሮ አደጋ ምክንያት በሰው ህይወት ላይ በደረሰው ሞት የወላይታ ዞን አስተዳደር የተሰማዉን ሀዘን ይገልጻል።

ለመላዉ ቤተሰቦች እና ለዞኑ ህዝብ መጽናናትን እንመኛለን ።

ህይወታቸው ያለፈ ወገኖቻችን ነፍሳቸዉን ፈጣሪ በአፀደ ገነት ያኑራቸዉ።

በዚህም አጋጣሚ በዞናችን የአደጋ ስጋት እና ተጋላጭ በሆኑ በካዎ ኮይሻ፣ ኪንዶ ኮይሻ፣ ኪንዶ ዲዳዬ እና ሌሎችም አካባቢ ያላችሁ ወቅቱ የዝናብ ወቅት በመሆኑ ከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲደረግ እያሳሰብን የመንግሥት አመራር አካላትም በከፍተኛ ዝግጅት ጥንቃቄ እንዲደረግ ለማስገንዘብ እወዳለሁ።

የህዝቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የታቀዱ ተግባራትን ለማሳለጥ ሁሉንም አካላት ባሳተፈ መልኩ ልዩ እርብርብ እና ክትትል ማድረግ ያስፈልጋል፦ አቶ ዳዊት ኦይካ*******ዳሞት ፑላሳ፤ሐምሌ 14/2...
21/07/2025

የህዝቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የታቀዱ ተግባራትን ለማሳለጥ ሁሉንም አካላት ባሳተፈ መልኩ ልዩ እርብርብ እና ክትትል ማድረግ ያስፈልጋል፦ አቶ ዳዊት ኦይካ
*******
ዳሞት ፑላሳ፤ሐምሌ 14/2017 በወላይታ ዞን ዳሞት ፑላሳ ወረዳ የሁለተኛ ዙር የ90 ቀናት ዕቅድ አፈጻጸም ያለበት ደረጃ ግምገማና ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎች ላይ ያተኮረ የባለድርሻ አካላት ውይይት ተካሄደዋል።

የመድረኩን ማጠቃለያ ሀሳብ ያስቀመጡት የዳሞት ፑላሳ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዳዊት ኦይካ እንዳሉት የህዝቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የታቀዱ ተግባራትን ለማሳለጥ ሁሉንም አካላት ባሳተፈ መልኩ ልዩ እርብርብ እና ክትትል ሊደረግ እንደሚገባ አሳስበዋል።

አመራሩ እያንዳንዱ ተግባራትን በተቀመጠው አቅጣጫ መሰረት በመተግበር የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ ከምንጊዜውም በላይ ቅንጅታዊ አሰራር ማጠናከር ወሳኝ መሆኑንም አመላክቷል።

በመጀመሪያው ዙር 90 ቀናት የተመዘገቡ ስኬቶችን አጠናክረን በማስቀጠል እንደ ጉድለት የተለዩ አፈጻጸሞችን በፍጥነት ማረም እንደሚገባም አስገንዝበዋል።

የዳሞት ፑላሳ ወረዳ የመንግሥት ዋና ተጠሪ አቶ ፍሬዘር ዘለቀ በበኩላቸው በተግባር አፈጻጸም ያጋጠሙ ችግሮችን ለይቶ ለመፍታት እና ከችግሮች ለመውጣት አመራሩ ፈጠራንና ፍጥነትን መጨመር እንዳለበትም አሳስበዋል።

አመራሩ በ2ኛ ዙር የታቀዱ የ90 ቀናት የፓርቲና የመንግስት ተግባራትን ለማሳለጥ አባላትንና ህዝቡን ማስተባበርና ማሳተፍ ይገባል ያሉት የመንግሥት ዋና ተጠሪው የህዝቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ መረባረብ እንዳለበትም ጠቅሰዋል።

የገቢ አሰባሰብ፣ የመኸር እርሻ ሥራ፣ ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለመሸጋገር የተጀመሩ ስራዎች፣ የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት፣ የማህበረሰብ አቀፍ መድኃኒት ቤት ግንባታ፣ ወባን የመከላከልና የመቆጣጠር እና ሌሎች ወቅታዊ ንቅናቄ ተግባራት በልዩ ትኩረት መመራት እንዳለባቸውም አጽንኦት ሰጥተዋል።

የዳሞት ፑላሳ ወረዳ የመንግሥት ረዳት ተጠሪ እና የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ አቶ አድማሱ ሄስቦ ለተሳታፊዎች የውይይት መነሻ ሰነድ አቅርቧል።

የዳሞት ፑላሳ ወረዳ ሴቶችና ህፃናት ጉዳዮች ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ አየለች ቆልቻ የሴቶች ልማት ህብረት ለማጠናከር የሚያስችል የንቅናቄ መድረክና የ2017 ዓ.ም በሴቶች አደረጃጀት የሚከናወኑ የበጎ ተግባራት ሰነድ በስፋት ለተሳታፊዎች አቅርቧል።

የተሻለ አፈጻጸም ላስመዘገቡ የቀበሌ መዋቅሮች እውቅና ተሰጥቶባቸዋል።

የዳሞት ፑላሳ ወረዳ አሰተባባሪ አካላትና አጠቃላይ መካከለኛ አመራሮች፣የቀበሌ አስተዳዳሪዎችና የግብርና ልማት ጽ/ቤት ኃላፊዎች ጨምሮ ሌሎችም ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።

ዴሞክራሲያዊ የተረጋጋ የፖለቲካ እንቅስቃሴ ለሰላም እና ለልማት ግንባታ እጅግ ወሳኝ መሆኑን ተገለፀ ሐምሌ 14/2017 የወላይታ ዞን ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት የ2018 የሥራ ዕቅድ ...
21/07/2025

ዴሞክራሲያዊ የተረጋጋ የፖለቲካ እንቅስቃሴ ለሰላም እና ለልማት ግንባታ እጅግ ወሳኝ መሆኑን ተገለፀ

ሐምሌ 14/2017 የወላይታ ዞን ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት የ2018 የሥራ ዕቅድ እና የሪፎርም ስራዎች አፈጻጸም በመገምገም ቀጣይ አቅጣጫ አስቀምጧል።

የወላይታ ዞን ብልፅግና ፓርቲ የፖለቲካና ህዝብ ግንኙነት ዘርፍ ኃላፊና የምክርቤቱ ም/ሰብሳቢ አቶ መስፍን ቶማስ ብልፅግና ፓርቲ እያደረገ ያለው አከታችነትና አሳታፊነትን አጠናክሮ እንደሚያስቀጥል ገልፀዋል።

የህዝቡን ሁለንተናዊ ብልፅግናን ለማረጋገጥ በጋራ ተቀናጅተን መሰራት ወሳኝ ነው ያሉት አቶ መስፍን፥ ለዚህም ምክርቤቱ የሚጠበቅበትን ድርሻ መውጣት እንዳለበትም አሳስበዋል።

በየደረጃው የሚገኙ የጋራ ምክርቤቶችን ሪፎርም ማድረግ ችግሮችንና ጉድለቶችን ለማረም እጅግ የሚያግዝ መሆኑን አንስተዋል።

በየአካባቢው የሚስተዋሉ የመልካም አስተዳደር ችግሮች ለመፍታት በጋራ ተጋግዘን መሰራት አለብን ያሉት አቶ መስፍን፥ መንግስት የህዝቡን ጥያቄዎችን ደረጃ በደረጃ እየፈታ እንደሚገኝም ጠቅሰዋል።

የወላይታ ዞን ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሰብሳቢ አቶ መስፍን መንግስቱ ቀጣይ የጋራ ምክርቤቱን የሚያጠናክሩ ስራዎችን አጠናክረን መሰራት ይጠብቅብናል ብለዋል።

የጋራ ምክርቤቱ የ2018 ዕቅድ በተያዘለት የጊዜ ገደብ የተሻለ አፈጻጸም ለማስመዝገብ በቅንጅትና በትብብር መሰራት እንደሚገባም አሳስበዋል።

በዞኑ የዴሞክራሲ ስርዓት እና ሠላም ግንባታ በማስፈን ፖለቲካ ፓርቲዎች የሚያጋጥማቸውን ችግር ተቀራርቦ በመሰራት ማቃለልና መፍታት ያስፈልጋል ብለዋል።

የወላይታ ዞን ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ፀሐፍ አቶ ተፈሪ ማሞ በበኩላቸው ፖለቲካ ፓርቲዎች በዞኑ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ህይወት ውስጥ ያላቸውን ሚና ከፍተኛ በመሆኑ የድርሻችንን መውጣት አለብን ብለዋል።

በግብርናው ዘርፍ የታቀዱ ተግባራትን በተቀናጀና በተደራጀ ሁኔታ በመፈፀም የህዝቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ መትጋት ይጠብቅብናል፦ ዶ/ር ዘማች ሶርሳሐምሌ 14/2017 የወላይታ ዞን ግብርና መምሪ...
21/07/2025

በግብርናው ዘርፍ የታቀዱ ተግባራትን በተቀናጀና በተደራጀ ሁኔታ በመፈፀም የህዝቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ መትጋት ይጠብቅብናል፦ ዶ/ር ዘማች ሶርሳ

ሐምሌ 14/2017 የወላይታ ዞን ግብርና መምሪያ ኃላፊ ዶ/ር ዘማች ሶርሳ ከመምሪያው አጠቃላይ ሠራተኞች ጋር የትውውቅ መድረክ በማካሄድ የቀጣይ ሥራዎች ዙሪያ አቅጣጫ አስቀምጠዋል።

በትውውቅ መድረኩ የወላይታ ዞን ግብርና መምሪያ ኃላፊ ዶ/ር ዘማች ሶርሳ እንደተገለፁት፥ በተቋሙ የሚለካ እና የሚተገበር ዕቅድ ማዘጋጀት ያስፈልጋል ብለዋል።

በግብርናው ዘርፍ የታቀዱ ተግባራትን ለማሳካት እጅ ለእጅ ተያይዘን አንድነታችን በማጠናከር በመፍጠንና መፍጠር መሰራት ይጠብቅብናል ብለዋል።

ለጋራ በስኬት በጋራ መሰራትና መረባረብ አለብን ነው ያሉት።

ጊዜ የማይሰጡ ተግባራት በተለይም የመኸር እርሻ ተግባር፣ የእንስሳት ሀብት ልማት፣ የአረንጓዴ አሻራ ልማት፣ ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ከሌሎችም ጋር የሚያያዙ የተጣሉ ግቦች እና የተቋሙን የለውጥ ሥራዎች በእጃችን ያሉ ሀብቶችን በማቀናጀት መሰራትና መፈፀም ያስፈልጋል ብለዋል።

የመምሪያው ም/ኃላፊና የተፈጥሮ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ደመቀ ኩኬ በበኩላቸው መንግስት ሀገራዊ ኢንሼቲቭ ካስቀመጠቸው መካከል በርካቶች በግብርናው ዘርፍ የሚፈጸሙ መሆናቸውን ገልጸዋል።

በተለይም የሌማት ትሩፋት፣ ከተረጂነት ወደ ምርታማነት እና በመትከል ማንሰራራት እና ሌሎችም በተደራጀ ሁኔታ በመፈጸም ተግባራዊ ማድረግ ይጠይቃልም ብለዋል።

የህዝቡን ሁለንተናዊ ብልፅግናን ለማረጋገጥ በጋራ እየሰራንና እየገመገመ በሁሉም ዘርፍ የታቀዱ ግቦችን ለማሳካት መትጋት ይጠብቅብናል ነው ያሉት።

በ2017 በጀት ዓመት በሥራው ላይ የታዩ ችግሮች በማረም በ2018 በጀት ዓመት በአስተሳሰብ እና በተግባር አንድ በማጠናከር የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ ቁርጠኝነት እንደሚጠይቅም ተመላክቷል።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት የጽ/ቤቱን የ 2017 ዓ.ም የዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ እና የ2018  ዕቅድ ዝግጅት መድረክ መካሄድ ጀምሯልሐምሌ 14/2017 ዓ.ምየደቡብ ኢ...
21/07/2025

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት የጽ/ቤቱን የ 2017 ዓ.ም የዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ እና የ2018 ዕቅድ ዝግጅት መድረክ መካሄድ ጀምሯል

ሐምሌ 14/2017 ዓ.ም

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት የ 2017 ዓ.ም የጽ/ቤቱን የዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ እና የ2018 ዕቅድ ዝግጅት መድረክ በወላይታ ስዶ ከተማ መካሄድ ጀምሯል።

መድረኩ በበጀት ዓመቱ የፓርቲ አቅሞችን በማስተባበር የመጡ ስኬቶችና የተገኙ ለውጦችን መነሻ በማድረግ የሚካሄድ የአፈፃፀም ግምገማ እና የውይይት መድረክ እንደሆነ ተገልጿል።

ካለፈው ዓመት መልካም አፈጻጸም ልምዶችን ማስፋት እንዲቻል እንዲሁም በጉድለት የተገመገሙ ጉዳዮችን ለማረም በሚያስችል መንገድ የጋራ መግባባት ለመፍጠር ታስቦ የሚካሄድ መድረክ እንደሆነም ታዉቋል።

በመድረኩ የክልሉ ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ገ/መስቀል ጫላን ጨምሮ የክልሉ ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ከፍተኛ አመራሮች በመሳተፍ ላይ ናቸዉ።

Address


Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የዳሞት ፑላሳ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት-Damot Pulasa Prosperity Party Office posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

  • Address
  • Alerts
  • Claim ownership or report listing
  • Want your business to be the top-listed Media Company?

Share