12/12/2025
እዚህ ቦታ ተፈጥሮ አፍ አውጥቶ ይናገራል። ለዓይን ማረፊያ፣ ለነፍስ እረፍትና ለአእምሮ ሰላምን የሚሰጥ የፈጥሮ ስጦታ የተፈጥሮ ቦታ ነው።
ይህ ውበት በተለያዩ መልኮች ይገለጣል።
እኔ ምደሰተው እኔ ምረካው ከሰማይ ጠቀስ ተራሮች ግርማ ሞገስ እስከ ለምለም ሜዳዎች ስፋት አይደለም ።
የኔዋ የልጅነት እድሜ መጋዣዬ። በዚች ቦታ እርፍ ስል ነው።
ባህር ማዶ አያስመኝ ። ከአድማስ የረዘመ የባህር ዳርቻ እስከ ጥልቅና ንጹህ ወንዞች ፍሰት ድረስ አያስጎመጅ ።
ይህ ከጀርባዬ ያለው ተፈጥሮ በውብ ብሩሽ ሰአሊ የሳለው የሚመስል ተፈጥሯዊ ገፅታ ነው። ግን ተፈጥሯዊ ነው።
በፀሐይ መውጫ ወይም መጥለቂያ ጊዜ ተራሮችና ደመናዎች የሚላበሱት ቀለማት፣ የዛፎችና የቁጥቋጦዎች አረንጓዴነት፣ እንዲሁም የዱር አራዊትና የአእዋፍ የዕለት ተዕለት እንቅስቃሴ የሚያሳየው ህያውነት እጅግ ማራኪ ምድር ነው።
ንጹህ አየር፣ በቅጠሎች መካከል የሚነፍሰው ልስልስ ያለ ነፋስና የአእዋፍ ዝማሬ ለአእምሮ መረጋጋትና ለመንፈስ እርካታ ያጎናጽፋል ።
የከተማ ጩኸትና ግርግር ርቀን እውነተኛ ሰላምን የምናገኝበት ነው። በተፈጥሮ ውስጥ መመላለስ፣ አንዱ ጫፍ ላይ ሆኖ አድማስን መቃኘት ወይም በወንዝ ዳርቻ ተቀምጦ ማሰላሰል የሰውን ልጅ ከተፈጥሮው ዓለም ጋር የሚያገናኝና የስነ ልቦና ጤንነትን የሚያጎለብት ነው።
እዚህ ቦታ የፍጭም ፉርጥ ላይ ሆነህ አይንህ ያማትራል። ዋዠራ ዳባ ኗገጀ ጅማ ወለኔ ወሸርቤ ወልቂጤ ያስቃኛል