Yonas Tade

Yonas Tade ይህ ቻናል መንፈሳዊ መልእክቶች እና ዝማሬዎች ይተላለፉበታል:

12/11/2025

የምንተማመንባት ፀሐይ ስትጠልቅ ያልጠበቅናቸው ጨረቃና ከዋክብት ይወጣሉ:: ምክንያቱም የማይተውህ እግዚአብሔር ቸር ነውና::

12/11/2025

ሰላም ለሁላችሁ- ሁለቱን አንድ ያደረገ ኤፌ 2:14 ክርስቶስ መስቀል ላይ ሆኖ ያስታረቀን ከራሳችን ጋ ጭምር ነው። ሰው ራሱ ሲሸሸው የተቃወሰ ኑሮ ይኖረዋል። ለሰው የሚሰጠውም ዋጋ ካልተቀበለው ከማንነቱ ያነሰ ስለሚሆን በተለምዶ አስቸጋሪ ሰው! የምንለው አይነት ይሆናል። መንፈሳዊነት የመጀመሪያ ስራው ክርስቶስ ከሞተለት ማንነታች ጋ ራሳችንን ማስታረቅ ነው። ዋጋ ያለንና በዓላማ የተፈጠርን ውብ መሆናችንን ማሳየት ነው። ህይወት በክርስቶስ ሲመዘን ፍጹም ጤና ነውና።
እባካችሁ ለሌሎች አካፍሉት
ቀሲስ አሸናፊ ገ/ማርያም

12/11/2025

እግዚአብሔር ከልባችን ይልቅ ታላቅ ነውና ሁሉንም ያውቃል። 1ዮሐ3:20

12/11/2025

እግዚአብሔር የድሆችን ምኞት ሰማ፥ ጆሮውም የልባቸውን አሳብ አደመጠች
መዝ 10:17

12/10/2025
ሰላም ለሁላችሁ:- ሎጥ መርጦ በኖረባት ሃገር ክፉ ልምምድ ነፍሱ ስትሳቀቅ ኖሯል። ነገር ግን የሃገሩ ሜዳ አደግነት በእርሱ እና በቤተሰቡ ላይ ተጽዕኖን ጥሎ ነበር። እንግዶቹን ከህዝቡ ጥቃት ...
12/09/2025

ሰላም ለሁላችሁ:- ሎጥ መርጦ በኖረባት ሃገር ክፉ ልምምድ ነፍሱ ስትሳቀቅ ኖሯል። ነገር ግን የሃገሩ ሜዳ አደግነት በእርሱ እና በቤተሰቡ ላይ ተጽዕኖን ጥሎ ነበር። እንግዶቹን ከህዝቡ ጥቃት ለማትረፍ ያቀረበው ዘግናኝ አማራጭ ነበር። ወንድ ያላወቁ ልጆቼን ልስጣችሁ አላቸው። አባት ለቤተሰቡ ሲል መሞት ነበረበት። ያኔ ከአብርሃም ጋ ወላጆቹን ጥሎ እግዚአብሔርን አምኖ የወጣው ሎጥ ዛሬ ግን አቅም አልበረውምና ልጆቹን አሳልፎ ሰጪ ሆነ! የመረጣት ከተማ መንፈሳዊ ጉልበቱን በልታበት ነበር። ቢሆንም ለተነገረለት ቃል በእምነት የታዘዘ፣ እንግዶችን የተቀበለ ስለነበረ ከጥፋት አመለጠ። ድንግል ያላቸው ሴት ልጆቹም ሥጋቸው እንጂ በመንፈሳቸው በሰዶማውያን መንፈስ ተወርሶ ነበር። በዞአር አባታቸውን አስክረው አብረውት ተኝተው ሞአብና አሞንን ወለዱ። ሁለቱ ነገዶች የእስራኤል ጠላቶች ነበሩ። ይህ ቤተሰብ ለኑሮ የመረጠው ሃገር ምን ያህል ተጽዕኖ እንዳሳደረበት ተመልከቱ! እኛም ወንጌልንና እግዚአብሔርን መፍራትን ሃገር አድርገን እንኑር። ቤታችንም ቅዱሳን መላእክት የሚያድሩበት ለእንግዶች ክፍት ይሁን። ያኔ በበራችን ዙሪያ የሚቆሙ ርኩሳት መናፍስት አይናቸው ታውሮ በራችንን ማግኘት አይችሉም። በሩ ዝግት ያለ ህይወት አልባ ቤት፣ ስስታም ኑሮ፣ የእግዚአብሔርን መላእክት የናቀ ኑሮ ግን በሥጋ ድንግል በመንፈስ ግን ርኩሰትን የተሸከመ ፍሬ ይፈራበታል። ለበሩም ጠባቂ አያገኝም።
እባካችሁ ለሌሎች አካፍሉት
ቀሲስ አሸናፊ ገ/ማርያም

ሰላም ለሁላችሁ፦ ቅዱስ እስጢፋኖስ የሞት ፍርድ ተፈርዶበት በህዝብ ድንጋይ እየተደበደበ ሳለ ለጸሎት ተንበረከከ። ይህ ሁኔታ እንኳን ለመንበርከክ በስርዓት ለመሞትም ፋታ አይሰጠም ነበር። ግን ...
12/09/2025

ሰላም ለሁላችሁ፦ ቅዱስ እስጢፋኖስ የሞት ፍርድ ተፈርዶበት በህዝብ ድንጋይ እየተደበደበ ሳለ ለጸሎት ተንበረከከ። ይህ ሁኔታ እንኳን ለመንበርከክ በስርዓት ለመሞትም ፋታ አይሰጠም ነበር። ግን ጌታው ፊት ምን ያህን በአክብሮት መጸለይ እንዳለበት እየሞተም አልረሳም። በአስቸጋሪ ሁኔታም ውስጥ እምላኩን በአክብሮት አከበረ። እኛ እየኖርን ምን ያህል ለክብሩ የሚገባ ስግደት እንሰጣለን? ስንቶቻችን ለጸሎት ከመቀመጫችን እንነሳለን? በሰላም የምኖነረው እኛ ለጌታ ሰዓት አጥሮን ምክንያት መደርደራችንን እስጢፋኖስ ቢሰማ ምን ይል ይሆን? እርሱ አምኖ ሲሞት አምኖ መኖር ምን ያህል እንደሚያስፈልገን ተረዳችሁ? እግዚአብሔርን ከወደድነው መቸም ቢሆን ለርሱ ጊዜ አለን። ለአምልኮ ጊዜ ያጣነው ሰዓት ስላጣን ሳይሆን ለርሱ ፍቅር ስላጣን ነው። ይህን ማንም እንዳይረሳ። ተሰብስበን ወደማይቀረው ዓለም መጠራታችን አይቀርም። ወደ ዘላለሙ ስፍራ መድረሳችን አይቀርም። ስለዚህ ቀን ሳለ ጌታችንን ማክበር ወደ ፍለጋው መመልከት እንጀምር። ማንም የማይሰራበት ሌሊት ይመጣልና።
እባካችሁ ለሌሎች ያካፍሉት
ቀሲስ አሸናፊ ገ/ማርያም

12/09/2025

ሰይጣን ክርስትያኖችን የሚዋጋበት ታላቁ ውጊያው ተስፋ ማስቆረጥ ነው::
ወዳጄ በምንም ሁኔታ በእግዚአብሔር ተስፋ አትቁረጥ ቢዘገይም ማንም የማይቀድመው አባት አለህና በዚህ ደስ ይበልህ!!!!!!

12/09/2025

ምነው ተኝተሃል? እንዳንጠፋ እግዚአብሔር ያስበን እንደ ሆነ ተነሥተህ አምላክህን ጥራ:: ዮናስ 1:6

12/09/2025

ታካች ሰው በብርድ ምክንያት አያርስም፤ ስለዚህ በመከር ይለምናል፥ ምንም አያገኝም።
ምሳ 20:4

12/08/2025

ያለ ሰዓቱ አይነጋም::

12/07/2025

እግዚአብሔርን የሚፈሩ ሰዎች ሀብት ንብረትን ለማውረስ ሳይሆን ሃይማኖትን እና እምነትን ለማውረስ ይጨነቃሉ::

Address

Atlanta, GA

Telephone

+14047865011

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Yonas Tade posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Yonas Tade:

Share