Nine-eared Press

  • Home
  • Nine-eared Press

Nine-eared Press Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Nine-eared Press, Media/News Company, .

 #አስደሳች ዜና፦ ለአሶሳ ከተማ እና ለአከባቢው ለምትገኙ ነዋሪዎች በሙሉ  #ጥቅምት 8 /02/18 ዓ /ም በአሶሳ ከተማ ቤኒሳይኬን ሆቴል  ታላቅ  በአይነቱ ለየት ያለ በተከበሩ አመንቴ ጌሽ...
12/10/2025

#አስደሳች ዜና፦

ለአሶሳ ከተማ እና ለአከባቢው ለምትገኙ ነዋሪዎች በሙሉ #ጥቅምት 8 /02/18 ዓ /ም በአሶሳ ከተማ ቤኒሳይኬን ሆቴል ታላቅ በአይነቱ ለየት ያለ በተከበሩ አመንቴ ጌሽ የተፃፈው ‎በሺናሻ ህዝብ ታሪክ ፣ ባህል እና ማንነት ዙሪያ የሚያጠነጥነው "ቦር ዘ _ኢትዮ #ቅጽ 1 ታሪክ እና ትውፊት ጥናት መነሻዎች" የተሰኘው እና በአቶ አመንቴ ገሺ የተፃፈው በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው መፅሃፍ ጥቅምት በቀን #8/02/18 ዓ/ም አሶሳ ቤንሳይከን ሆቴል 3::00 ይመረቃል።

‎ይህ በአይነት እና ይዘቱ ለያት ያለ መፅሃፍ ከመሆኑ በተጨማሪ እጅግ አነጋጋሪ ይዘቶችን አካቷል። ከዚህ በኃላም "ቦር _ ዘኢትዮጵያ #ቅጽ 2 እና #ቅጽ 3 በሂደት ላይ መሆናቸውን ከመጽሃፉ መግቢያ ላይ ተመላክቷል።

ይህን ድንቅ መፅሐፍ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች ና በተጋባዥ እንግዶች ለማስመረቅ ዝግዥት ላይ እንገኛለን ሁላቸውም እንድትታደሙ ና እንድታስመርቁ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን

ኑ ይህን በአይነቱ በይዘቱ ለየት ያለውን ቦር _ ዘኢትዮጵያ የተሰኘውን ቅጽ 1 መፅሐፍ እናስመርቅ።

‎እንኳን ደስ ያለህ ወንድማችን

እንደ አንቺ የታገስነው የለም። የኛ ክልል ሳንጋራዳ አመራር አስካል አልቦሮ የምርጫ ሴራና አሻጥር በፀሀይ ሞርካ ላይ የሰራሽን ሰራ በዝርዝር እንመለሳለን።
13/04/2025

እንደ አንቺ የታገስነው የለም።

የኛ ክልል ሳንጋራዳ አመራር አስካል አልቦሮ የምርጫ ሴራና አሻጥር በፀሀይ ሞርካ ላይ የሰራሽን ሰራ በዝርዝር እንመለሳለን።

ከሁለት አመት በፊት በአብዮት አልቦሮ የግል ቂም አበራ አልቦሮ  ለወራት ታስሮ ነፃ ሁኑ መውጣቱ ሁሉም የሚያውቀው እውነታ ነው። አበራ አልቦሮ ዳግም  በአብዮት አልቦሮ ታላቅ እህት አስካል አ...
12/04/2025

ከሁለት አመት በፊት በአብዮት አልቦሮ የግል ቂም አበራ አልቦሮ ለወራት ታስሮ ነፃ ሁኑ መውጣቱ ሁሉም የሚያውቀው እውነታ ነው።

አበራ አልቦሮ ዳግም በአብዮት አልቦሮ ታላቅ እህት አስካል አልቦሮ ትዛዛ መታሰራቸውን እየሰማን ነው ሰልጣንን ለግል ቂም መወጫ ማድረግ አግባብነት የለውም አቶ አበራ አልቦሮ ለእውነት፣ ለፍትህና ለእኩልነት ስታገል ቆይቷል።

አሁን አበራን በማሰር ቦዴፓን እናዳክማለን ብሎ ማሰብ ከንቱ ቅጀት ነው። የውሸት ውንጀላ ውድቀታችሁን ያፋጥናል።

አቶ አበራ አልቦሮ በአስቸኳይ ሊፈታ ይገባል። ስልጣን የግል ቂም መወጫ መሆን የለበትም አስካል አልቦሮ ከድርጊትሽ ማትቆጠቢ ከሆነ የሚከተልሽን ታውቂያለሽ።

 #አንድ መምህር ሕዳሴ ግድብ ይፍረስ እያለ ነው‼️""""""🤜🤜🤜👉👉""""""""የአንድ የአሶሳ ዩኒቨርስቲ መምህር ያውም የEconomics ሙሁር ተንታኝም ጭምር ነው። አቶ መሐመድ እብራሂም ...
08/04/2025

#አንድ መምህር ሕዳሴ ግድብ ይፍረስ እያለ ነው‼️
""""""🤜🤜🤜👉👉""""""""
የአንድ የአሶሳ ዩኒቨርስቲ መምህር ያውም የEconomics ሙሁር ተንታኝም ጭምር ነው። አቶ መሐመድ እብራሂም ይባላል። የአሶሳ ዩኒቨርስቲ መምህር ሲሆን በሆሞሻ ወረዳ እስከ ሸርቆሌ ድረስ ያለው መንገድ ወቅቱን ያልጠበቀ ዝናብ ለብልሽት ማደረጉ ይታወቃል።

ይህ መምህር ሙሁር ከመሆኑ አንፃር መፍተሔ የሚበጅ ሀሳብ ከመፃፍ ይልቅ በአፍሪካ ቀንድ ጂኦፖለቲክስ ለኢትዮጵያ ሕዝብ የሕልውና ጉዳይ የሆነው ታላቁ ሕዳሴ ግድብ ነቅላችሁ ውሰዱ መንግስት አናቅም ይለናል።

የፌድራል መንግስት እንደዚህ አይነት ሙሁራን ከሱዳን ተልዕኮ ይወሰድ ምንነቱ እንዲጣራ እና የአንድ ሀገር ፕሮጀክት ማንቋሸሽ ከተጠያቂነት አያድንም።

06/04/2025

ስትታመም ታማ ስትሞት ተቀበረች አንተ ስትነሳ የኔናት የት ቀረች የሚለውን የሴት ልጅ ታሪክ አስታወሳችሁኝ።

የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የብልፅግና አመራሮችም ሆነ አጋፋሪዎቹ የጉሙዝ እና ሽናሻ ህዝብ የመረጣችሁ ህዝቡን ወክላችሁ የህልውና ጥያቄ ትመልሳላችሁ ብሎ እንጂ እንደ ኩማሪ ጥቅም ባያችሁ ቁጥር ጭናችሁን ከፍታችሁ እንድትሰጡ አይደለም።

በቅርቡ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልላዊ መንግስት የተሻሻለዉ የየእርከኑን ምክር ቤት ተወካዮች ብዛት ለመወሰን ያወጣው ረቂቅ አዋጅ የክልሎች ህገመንግስታት መነሻቸው ከሆነው የፌደራሉ ህገመንግስት የሚቃረኑ፣ አግላይና ከፋፋይ መኑን መለየት የማትችሉ ህዝብ ወክላችሁ ምክርቤት እንደ ፑፔት ጋርድ የተሰየማችሁ ራሳችሁን ዘወር ብላችሁ ልታዩ ይገባል።

የሀገሪቱ ሕገ መንግስት አንቀጽ 25 “ሁሉም ሰዎች በሕግ ፊት እኩል ናቸው፣ በመካከላቸውም ማንኛውም ዓይነት ልዩነት ሳይደረግ በሕግ እኩል ጥበቃ ይደረግላቸዋል፡፡

በዚህ ረገድ በዘር፣ በብሔር ብሔረሰብ፣ በቀለም፣ በጾታ፣ በቋንቋ፣ በሃይማኖት፣ በፖለቲካ፣ በማኅበራዊ አመጣጥ፣ በሀብት፣ በትውልድ ወይም በሌላ አቋም ምክንያት ልዩነት ሳይደረግ ሰዎች ሁሉ እኩልና ተጨባጭ የሕግ ዋስትና የማግኘት መብት እንዳላቸው” ቢደነግግም ይህ ግን በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ተግባራዊ እየተደረገ አይደለም።

ይህ በእንዲህ እንዳለ በፖለቲካ ሴራ ትንተና ሃልዮት አንዱ የሌላው ጠላት እየተደረገ ለሚያልፍ ቀን የማያልፍ ድርጊት ይፈጸማል አንዱ አሳዳጅ ሌላው ተሳዳጅ

አንዱ አሳሪ ሌላው ታሳሪ፣አንዱ በግፍ ሟች ሌላው ገዳይ ሆኖ የሚቀጥልበት ስርዓት በህግ እይታ ምንም ዓይነት ተቀባይነት የሌለው እና ሕግን አስከብራለው ከሚል ፖሊስና ፍትህ ተቋም የማይጠበቅ ድርጊት እየተደረገ በህዝብ የተመረጠው የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል አመራሮች የተሰጣቸውን ሀላፊነት ካላግባብ በመጠቀም ለተለያዩ የጥፋት ዘመቻ ላይ በመሰማራት የሽናሻ ብሄር ላይ ያነጣጠረ የእስር ዘመቻ ላይ ይገኛሉ።

ስለሆነም የክልሉ መንግስት ከንደነዚህ አይነት የጥፋት ዘመቻ ሊታቀብ እንደሚገባ ሊወገዝ ይገባል።።።።


1ኛ, ዮሐኒስ ተሰማ ገርቢ፣
2ኛ, ዳምጠው ገሺ ተፈራ፣
3ኛ,ሽባባው ሃይሌ
4ኛ, ሙሉቀን አስፋው በጋዎና
5ኛ, ጌታቸው ገለታ
6ኛ, ሰለሞን ጀርናል ሙለታ

  ??????????????????????????የቡለን ወረዳ ፍትህ መምሪያ ሀላፊ አቶ ባይሞት ገታሁን ትዛዝ ዜጎች በደረቅ ጣቢያ እየተሰቃዩ ነው። የቡለን ወረዳ ፖሊስ ጣቢያ ወደ ማረሚያ ቤት ተ...
04/04/2025


??????????????????????????
የቡለን ወረዳ ፍትህ መምሪያ ሀላፊ አቶ ባይሞት ገታሁን ትዛዝ ዜጎች በደረቅ ጣቢያ እየተሰቃዩ ነው።

የቡለን ወረዳ ፖሊስ ጣቢያ ወደ ማረሚያ ቤት ተቀይሮ ነው ወይስ አልገባንም???? ሰሞነኛ ያለምንም ጥፋታቸው ያለምንም ወንጀላቸው ታስሮ የነበሩት ወንድሞቻችን ያለምንም ጥያቄ ከደረቅ ጣቢያ ሶስት ሳምንት እና ከዝያ በላይ መቆየታቸው የመተከል ዞን ፍትህ መምሪያ እንድያውቅልን እንላለን አንድ ዜጋ ቢታሰርም ከደረቀ ጣቢያ እንደት ከ 48 ሰዓት በላይ ይታሰራል ከደረቅ ጣቢያ ይቆያል።

ግልባጭ ለመተከል ፍትህ መምሪያ እንላለን
የፓሊስና ፍትህ ተቁዋም የዜጎችን መብት ለማስከበር እና አጥፊዎችን ለመለየት የሚረዳው ዜጎችን ከማሰሩ በፊት ከጥርጣሬ በላይ በወንጀል መሳተፋቸውን የሚያስረዳ መረጃና ማስረጃ እንዲኖረው የሚያስገድደውን መሠረታዊ መርህ ወደጎን በመተው በወንጀል ድርጊት ተሳታፊነት ጠርጥሬያቸዋለው በሚል የፖለቲካ ጭምብል በመልበስ ያለምንም ምክንያት በእስር እንዲቆዩ በማድረግ ሰብዓዊ መብታቸው እዳይከበር የቤኒሻንጉል ክልል ከፍተኛ አመራሮች በፖሊስና ፍትህ ተቋም ላይ ጫና በመፍጠርየፖለቲካ ቅማሩን እየተወኑ ይገኛሉ::

በእውኑ የሚያሳስበን የሚያበሳጨን ዓመት ቆጥረን የምናስታውሰው ሺህ ዓመታትን ያሳለፈውን የእነ ቀያፋ እና ጲላጦስ ተግባር የእነ ይሁዳ ክዳትና መጨረሻ ታሪክና የክርስቶስን መከራ ብቻ ነው ወይስ እሱ ራሱ እንዳለው ለወንድሙ ያደረገ ለኔ አደረገ ነውና በእሱ አምሳል የተፈጠሩ ወገኖቻችን መከራና ስቃይ እንዴት አያስቆጨንም ? የታሉ የፓለቲካ ፓርቲዎች ጩኸት? ከጥቂቶች በስተቀር የብዙዎቹ ድምጽ አይሰማም። በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ከሽፍታ፣ ከገዳዮቻችንና አብረዋቸው ለሚያብሩት ግን ስማቸውን ስንጠራና ስንዘክር እንውላለን።

ከዚህ ዓይነቱ አንዱ አሳሪ ሌላው ታሳሪ ከሚሆንበት አዙሪት ካልወጣን አደገኛ ነውና ዛሬም በግፍ እስር ላይ ያሉ እውቁ የነጻነት ታጋይ
ከመንገድ እየታፈኑ የታሰሩ የግፍ እስረኞች በሙሉ የሚፈጸምባቸው ስቃይ ቆሞ ከእስር እንዲፈቱ ድምጻችንን እናሰማለን።

04/04/2025

የቡለን ፖሊስ ጣቢያ የዜጎች ስውር ማሰቃያ ጣቢያ ሁኗል።

ያለምን ጥፋታቸው በደረቅ ጣቢያ የታሰሩት ዜጎች ቃላቸው ሳይጠየቅ ለፍርድ ቤትም ጉዳያቸው ሳይቀርብ ዜጎች ያለምንም ጥፋታቸው በስውር ጣቢያ ላይ እየተሰቃዩ ይገኛሉ።

ወንድማችን አቶ ዳምጠው ገሺ ያለምንም ወንጀል ታስሮ ዘጠኝ ቀን ከቆየ ቦሀላ ቃሉ ተመርምሮ ከየትኛውም ወንጀል ነፃ ከሆነና በዋስ መብት ከእስርቤት መዉጣቱ  ይታወቃል። ከየትኛዉም ወንጀል ነፃ ...
02/04/2025

ወንድማችን አቶ ዳምጠው ገሺ ያለምንም ወንጀል ታስሮ ዘጠኝ ቀን ከቆየ ቦሀላ ቃሉ ተመርምሮ ከየትኛውም ወንጀል ነፃ ከሆነና በዋስ መብት ከእስርቤት መዉጣቱ ይታወቃል።

ከየትኛዉም ወንጀል ነፃ የሆነዉን ወንድማችን አቶ ዳምጠዉን ከእስርቤት ካስወጡት ቦሀላ ለፖሊሶች ህጋዊ እና ህጋዊ ያልሆነ ትዛዝ በመስጠታቸው መልሳቹሁ እስር ቤት አስገቡ ብለው የቡለን ወረዳ የብልግና አመራሮች ካላይ ተደዉሎልናል ለምን ፈታቹሁ ተብሎናል ሲሉ ፖሊሶችን አስፈራርተዋል።

ፖሊሶች ደሞ እኛ ከየትኛውም ፖሎቲካ ነፃ ነን እና ታስሮ ከውንጀል ነፃ የሆነውን እና በነፃ ከእስርቤት የወጣዉን ግለሰብ መልሰን አናስርም ሲሉ ቃላቸውን ሲገልፁ ፖሊሶችንን በማንገራገር መልሰው እስርቤት እንዲገባ ተደርጓል።

ይህ እንዳለ ሁኖ ወንድማችን አቶ ሰለሞን ጀርናል ያለምንም ጥፋት በቡለን ወረዳ ፖሊስ ጣቢያ ተስሮ የሚገኘዉን አቶ ዳምጠው ገሺን ለማየት ሲሄድ አንተም ትገባለህ እንደት እሱን ማየት ትመጣለህ በማለታቸው አቶ ሰለሞን ጀርናልን ጭምር አሳስሯል አሳሪው የቡለን ወረዳ የብልግና አመራር እንጂ የፖሊስ መዋቅር እንዳልሆነ ተረጋግጧል።

የታሰሩት ግለሰቦች ምንም አይነት ወንጀል አለመስራታቸው የቡለን ፖሊስ መዋቀር አምኗል።

የታሰሩት ወንድሞቻችን ያለምንም ጥፋት ግዜ ቀጠሮ ሊጠየቅብን ነው እያሉ ማዉራታቸው ታውቋል ፍትህ ያለምንም ለታሰሩት ወንድሞቻችን እንላለን።

01/04/2025

"ሐይቅ ዳር ተሰብስበው እንቁራሪቶቹ አብዝተው ስለጮሁ ሀይቁ የእንቁራሪቶች ነው ማለት አይደለም።
ለክብራቸው ሲሉ ዝም ያሉ ብዙ አሳዎች ሀይቁ ውስጥ አሉ"

ወንድማችን ያለምንም ወንጀል ታስሮ ዘጠኝ ቀን ከቆየ ቦሀላ ትናንትና ቃሉ ተመርምሮ በነፃ ከእስርቤት ከወጣ ቦሀላ ዛሬ ደሞ ካላይ ተደዉሎልናል ለምን ፈታቹሁ ተብሎናል ብለው መልሰው ማሳሰር ህጋ...
01/04/2025

ወንድማችን ያለምንም ወንጀል ታስሮ ዘጠኝ ቀን ከቆየ ቦሀላ ትናንትና ቃሉ ተመርምሮ በነፃ ከእስርቤት ከወጣ ቦሀላ ዛሬ ደሞ ካላይ ተደዉሎልናል ለምን ፈታቹሁ ተብሎናል ብለው መልሰው ማሳሰር ህጋዊ አይመስለኝም እዉነት እና ፍትህ ተዛብቷል።

ወንድማችን ዳምጠው ገሺ  ከእስር ተፈቷል ከህግ አግባብ ውጪ ታስረው የሚገኙ የሰላማዊ ፖለቲካ አቀንቃኝ ወንድሞቻችንም በቅርቡ እንደሚፈቱ ተስፋ እንደርጋለን ሳያጣሩ ቢያስሩም አጣርቶ መፍታት የ...
31/03/2025

ወንድማችን ዳምጠው ገሺ ከእስር ተፈቷል

ከህግ አግባብ ውጪ ታስረው የሚገኙ የሰላማዊ ፖለቲካ አቀንቃኝ ወንድሞቻችንም በቅርቡ እንደሚፈቱ ተስፋ እንደርጋለን

ሳያጣሩ ቢያስሩም አጣርቶ መፍታት የግድ ይላል።

የዚህ ፎቶ ትርጉምና ምንነት የገባዉ ሰዉ ካለ የሚያስረዳኝ!!!ወይንስ እነዚህ ሰዎች ጉልት ገበያ መሸጥ ጀምረዉ ነዉ!!!
31/03/2025

የዚህ ፎቶ ትርጉምና ምንነት የገባዉ ሰዉ ካለ የሚያስረዳኝ!!!

ወይንስ እነዚህ ሰዎች ጉልት ገበያ መሸጥ ጀምረዉ ነዉ!!!

Address


Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Nine-eared Press posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

  • Want your business to be the top-listed Media Company?

Share