የባሶና ወራና ወረዳ ባህልና ቱሪዝም ጽ/ቤት basso culture and tourism office

  • Home
  • የባሶና ወራና ወረዳ ባህልና ቱሪዝም ጽ/ቤት basso culture and tourism office

የባሶና ወራና ወረዳ ባህልና ቱሪዝም ጽ/ቤት basso culture and tourism office ይህ ገጽ የባሶናወራና ወረዳ ታሪካዊ፣ባህላዊና ሃይማኖታዊ ክ?

14/10/2022

የቦረን ዋሻ ደብረ - እንቁ ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን ታሪክ
በባሶና ወራና ወረዳ በርከት ያሉ የቱሪስት መስህቦች ይገኛሉ፡፡ እነዚህም የተፈጥሮ ስፍራዎች እና ታሪካዊ የሃይማኖት ተቋሞች ናቸው፡፡ ከተፈጥሮ የቱሪስት መዳረሻዎች መካከል የምኒሊክ መስኮት ፣ የሙሽ አርኪኦሎጂ ስፍራ ፣ ራስ ጎበና ዋሻ ፤ ደጃች መንገሻ ዋሻ --- እና እንደ ቶራ መስክ ያሉ የጦር ሜዳዎች ይጠቀሳሉ፡፡ ከታሪካዊ የሃይማኖት ተቋማት ደግሞ እድሜያቸው በመቶ የሚቆጠሩ ከ50 በላይ ሲሆኑ ከመቶ አመት በታች የሚሆናቸው እጅግ ብዙ ናቸው፡፡ ከእድሜያቸው ባሻገር አሰራራቸውና ሃይማኖታዊ ይዘታቸው እንዲሁም በያዙት ጥንታዊ ቅርስ አንፃር የጎብኝን አይን ብቻ ሳይሆን ውስጣዊ አዕምሮንም ጭምር በደስታ የሚያስደንቁ ናቸው፡፡ ከነዚህም መካከል ዘጎ ቅድስት ማርያም ፣ ሚጣቅ አማኑኤል ፣ መጥቆሪያ ተክለሃይማኖት ፣ ወርቄ ሚካኤል ፣ ጌጣት ስላሴ ፣ ገነት ዋሻ ማርያም ፣ መለጥ መድሃኒአለም የመሳሰሉት ሲገኙ በ2004 ዓ.ም ተጠንቶ በቅርስነት ከተያዙ እና ለጎብኝዎች መዳረሻ ከሆኑት መካከል የወረዳውን ገፀ በረከት ፍንትው አድርጋ የምታሳየውን የቦረና ዋሻ ደብረ እንቁ ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን ታሪክን ልናስጎበኛችሁ ወደድን፡፡
ባለ አንድ ድንጋይ ፍልፍል የተፈጥሮ ዋሻ ዉስጥ ያለችዉ የቦረና ዋሻ ደብረ እንቁ ቅድስት ማሪያም በባሶና ወረና ወረዳ በዘንደጉር ቀበሌ ልዩ ስሙ ቦረና ዋሻ በተባለ ጎጥ ዉስጥ ከወረዳዉ ዋና ከተማ ደብረብረሀን 26 ኪሜ ርቀት ላይ ትገኛለች፡፡ ገዳማትን በማቃጠል ጉዳት በደረሰበት በአፄ ልብነ ድንግል ዘመነ መንግስት እንደሆነ ይገመታል፡፡ የዘመኑ አባቶች ፅላቷን ለመሸሸግ በዚህ ደን በተሸፈነ ዋሻ ዉስጥ ከመላዕኩ ሩፋኤል ጋር በሳጥን አድርገዉ እንደአስቀመጧት አዋቂ አባቶች ይናገራሉ፡፡ ይህ ታቦተ ህጉን በዉስጡ ይዞ የሚገኘዉ ዋሻ በአፄ ኃይለ ስላሴ ዘመነ መግስት ብልሽት ደርሶበት ከየካቲት 10 ቀን 1947 ዓ.ም እስከ ግንቦት 21 ቀን 1949 አ.ም ድረስ ዕድሳት የተደረገለት መሆኑን መረጃዎች ይጠቁማሉ፡ አባቶች እንደሚሉት በአካባቢዉ በጎችና ቦሮች ሲያግድ አንዷ በግ በዋሻዉ ዉስጥ ገበታ ስለወለደች እና ስለጠፋች እረኛዉ ለፍለጋ በገባበት አጋጣሚ ግልገሏ አልነሳ ብላዉ ቅጠል ሲያፈላግ ወላዷ በግ መጎናፀፊያ ከሳር ጋር በአፏ አንጠልጥላ አየ፡፡ አትኩሮ ሲመለከት ደግሞ በግንብ ዉስጥ በወርቅ የተለበጠ ሳጥን በማየቱ ለሰዉ ተናግሮ የማሪያም እና ሩፋኤል ፅላት እንዲገኝ ያደረገ ሲሆን ቦታዉም ቦሮች እረኛ ከሚለዉ ተወስዶ ቦረን ዋሻ ተብሎ ተሰይሟል፡፡ በሌላ በኩል ይች ቤተክርስቲያን ከ 900 ዓመታት በፊት እንደተመሰረተች አባቶች ሲናገሩ በአጥር ግቢዉ ዉስጥ የሚገኙት ዕድሜ ጠገብና ወፋፍር የሃገር በቀል ዛፎች ቤተክርስቲያኗ እድሜ ጠገብ ለመሆኗ ምስክርነታቸዉን ይሰጣሉ፡፡

26/09/2022

እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ በሰላም በጤና አደረሳችሁ፡፡ በዓሉ የሰላም የጤና የአብሮነት እንዲሆንላችሁ እየተመኘን በዓሉን ስናከበር ሃይማኖታዊ ይዘተን እና ባህላዊ ትውፊቱን የጠበቀ እንዲሆን እንመኛለን ፡፡ የባሶና ወራና ወረዳ ባህልና ቱሪዝም ጽ/ቤት

22/09/2022

በባሶና ወራና ወረዳ ባህልና ቱሪዝም ጽ/ቤት የዓለም ቱሪዝም ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ43ኛ ጊዜ፣ በሀገር ደረጃ ለ35ኛ ጊዜ፣ በክልል ደረጃ ለ30ኛ ጊዜ እንዲሁም በዞናችና በወረዳችን ደግሞ ለ12ኛ ጊዜ Rethinking Tourism"አዲስ እሳቤ ለቱሪዝም"በሚል መሪ ቃል በባሶ ደንጎራ ቀበሌ ምኒልክ መስኮት በተለያዩ ሁነቶች መስከረም 16/2015 ይከበራል፡፡
የባሶና ወራና ወረዳ ባህልና ቱሪዝም ጽ/ቤት
ደ/ብርሃን

23/08/2022

በሰሜን ሸዋ ዞን የባሶና ወራና ወረዳ ባህልና ቱሪዝም ጽ/ቤት በአቋቋማቸው የአማትር ክበባት አማካይነት ከጉዶበረት ታዳጊ ከተማና ጉዶበረት ዙሪያ ቀበሌ ጋር በጋራ በመሆን ባህሎቻችንን በጋራ እንገንባ የሚል ፕሮግራም በትናንትናወ እለት ማለትም በ16/12/2014 የወረዳ አመራሮች ፤ የቀበሌው ማህበረሰብና ተጋባዥ እንግዶች በተገኙበት በደማቅ ሁኔታ በፓናል ውይይት ተከብሯል፡፡ በፕሮግራሙ ላይ የወረዳው ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ ግሩም ወንድሙ ፣ የብልጽጋና ጽ/ቤት ሃለፊው አቶ ዘሪሁን ሀ/ጊይርጊስ እንድሁም የባህልና ቱሪዝም ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ ዘውዱ ታደሰ ንግግር ያደሩጉ ሲሆን በፓናል ውይይቱ ባህላችንን እና ቅርሶቻችንን እንዴት እንጠብቅ በሚል ዙሪያ እና ከማህበረሰቡ ከተነሱ ተጨማሪ ሀሳቦች ላይ ውይይት ተደርጓል፡፡ የጉዶበረት ታዳጊ ከተማ በባህል ቱሪዝም ጽ/ቤት የተቋቋመው አንድነት ክበብ 8ኛ አመት የምስረታ በዓሉን አስመልክቶ የስነ ጽኁፍ ምሽት አካሂዶ ታዳሚውን በማዝናናት እና ሁሉም ሰዉ ቅርሶቻችንን እና አባቶቻችን ያቆዩልንን ባህል በማሳደግ እና በመጠበቅ ሃላፊነታችንን መወጣት እንደሚገባ ታዳሚዎቹ ባደረጉት ዉይይት ላየ መግባባትና በቀጣይም ከዚህ በበለጠ ዝግጅት ማድረግ እንደሚገባ የጋራ መግባባት የተፈጠረበት ፕሮግራም በማድረግ ዝግጅቱን በጥሩ ሁኔታ መፈጸም ተችሎል፡፡
በህላችንን እና እሴቶቻችንን በጋራ እናልማ

17/05/2022

የደብረ- ገነት ቅድስት ማርያምና የክርስቶስ ሰምራ አንድነት ገዳምን እናስተዋውቅዎ
ስለ ጅብ አስራ ማርያም ያዉቁ ኖሯል?
የደብረ ገነት ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን በሰ/ሸዋ ዞን በባሶና ወራና ወረዳ በባሶ ደንጎራ ቀበሌ በአንዲት ፅድ ጎጥ ትገኛለች፡፡
ቤተክርስቲያኗ ከሃገሪቷ ዋና ከተማ አ/አ ወደ መቀሌ በሚወስደው አስፋልት መንገድ በ270 ኪ/ሜ ፣ ከደ/ብርሃን 40 ኪ/ሜ ርቀት በመኪና ከተጓዙ በኋላ በእግር የ380 ሜትር ርቀት ገባ ብሎ ትገኛለች፡፡
የደብረ ገነት ቅድስት ማሪያም ጥንት በአፄ ይኩኖ-አምላክ ዘመነ መንግስት በቅዱሳን አባቶች አማካኝነት መንዝ ከሚባል አካባቢ መጥታ አሁን የክርስቶስ ሰምራ ገዳም በሚገኝበት ቦታ ላይ እንደተተከለች ቄስ ሙሉጌታ ከአያት ቅድመ አያቶቻቸው ያገኙትን አፈታሪክ አጋርተውናል፡፡
የማሪያም ቤተ-ክርስቲያን መጀመሪያ የተሰራችው በሳር ክዳን/ሰንበሌጥ/ ስለነበረ ፈርሶ ዝናብ ማፍሰስ ሲጀምር በ1977ዓ.ም ግንቦት 21 ቀን በፊት ከነበረችበት ቦታ ላይ ተነስታ አሁን ያለችበት ቦታ ላይ /100 ሜትር ከፍ ብሎ/ ተሰርታ እንደገባች አቶ አወቀ ይናገራሉ፡፡
የደብረ ገነት ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን ብዙ ስያሜዎችን ያዘለች ጥንታዊት ቤተ-ክርስቲያን ናት፡፡
የአካባቢው ማህበረሰብ እመቤታችንን የምታደርገውን ተዓምራት እያዩ የተለያዩ ስያሜዎችን ሲያጎናፅፏት እሷም ተዓምራቷን ስታደርግ እንደቆየች ቄስ ሙሉጌታ ይናገራሉ፡፡
ጅብ አስራ ማርያም ለምን ተባለች ብለን ጠየቅናቸው
እነሱም ይናገራሉ፤ቀሳውስቱ ለአገልግሎት የሚውል ከበሮ በቆዳ ጠፍረው ቤተክርስቲያን አስቀምጠው ይሄዳሉ፤ እናም አያጅቦ ቆዳውን ለመብላት ከበሮውን ይዞ ወደ አንድ ወንዝ ይሄዳል፤ በነጋታው ቀሳውስቱ ወደ ቤ/ክ መጥተው ከበሮው ሲፈለግ ይጠፋል፡፡ነገር ግን ጅቡ ከበሮውን ሳይበላው ጅቡም ከበሮውም በእመቤታችን ታስረው ወንዝ ዳር ተገኙ፡፡ በዚህ ምክንያት ጅብ አስራ ማርያም ተባለች አሉ፤እውነትም ጅብ አስራ ማርያም፡፡
ግንድ አጠመሚት ማርያም ለምን ተባለች ጥያቆው ቀጥሏል፡፡
መጀመሪያ የማርያም ቤ/ክ ያለችበት ቦታ ላይ አንድ ለመቁረጥ አስቸጋሪ የሆነ ትልቅ ዛፍ ነበር፡፡ ያ ዛፍ ከቀን ቀን የቤተክርስቲያኗ ጣሪያ ላይ ለማረፍ እያዘመመ እያዘመመ ይሄዳል፤ ታዲያ በዚህ የተነሳ የአካባቢው ነዋሪዎች ይጨነቃሉ፤ ይህ ዛፍ የእመቤታችንን ቤት ሊያፈርስብን ነው እያሉ ያስባሉ፤ እናም አንድ ቀን ቆርጠው ለመጣል ይስማሙና የአካባቢው ነዋሪዎች፣ ወጣቱ ፣ሴቱ፣ አዛውንቱ ሳይቀር ቀላድ ያለው ቀላድ፣ አናፂ … ይዘው እንዲመጡ ተስማምተው ወደ ቤታቸው ይሄዳሉ፡፡ ጧት ሲመጡ ያ ትልቅ ዛፍ ከቤተክርስቲያኑ አናት ተነስቶ ግንዱ ተጣሞ ያገኙታል፡፡ በዚህ የተነሳ የአካባቢው እናቶች ግንድ አጠመሚት ማርያም አሏት፡፡ አሁንም ድረስ ግንድ አጠመሚት ማርያም ታውቃለች ይሏታል፡፡
ወደ መጨረሻው ስያሜዋ ስንመጣ በ1994 ዓ.ም ሰኔ 21 ቀን ነው፤ ካህናቱ የሌሊት ማህሌት በቆሙበት ሰዓት የማርያምም ስዕል ዓድህኖ ማሸብሸብ ጀመረ፡፡ ይህንን ተዓምር ለሰ/ሸዋ ዞን ኃገረ ስብከት ሊቀ-ጳጳስ ለአቡነ ኤፍሬም ሪፖርት ተደረገላቸው፡፡ተዓምሯም ተነገራቸውና ከዚያ አቡነ ኤፍሬም እመቤታችን ከፈቀደች ብዙ ተዓምር ትሰራለች፤ ብለው ከዚህ ጀምሮ ደብረ ገነት ማርያም ትባል ብለው ስያሜ ሰጥተዋታል፡፡
በቤተ ክርስቲያኗ ዙሪያ
 የማርያም
 የአቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስ
 የመጥምቁ ዮሃንስ ፀበል ፈልቀው ፈውስ እየሰጡ ይገኛሉ፡፡
በፀበሉ የተፈወሱ ሰዎች ምስክርነትና የፀበሉ ፈዋሽነት
ከካናዳ አገር የመጣ ዜግነቱ ኢትዮጵያዊ የሆነ በድንገት ልሳኑ ይዘጋል/ መናገር አይችልም ነበር ፡፡ ወደ ደብሯ መጥቶ ለ3 ቀን ፀበል ሲፀበል ቆይቶ በ3ኛው ቀን ሌሊት በህልሙ መራር ነገር ከሆዴ ሲወጣ አየሁት ፤ በዚያውም ጩከት ነገር /ድምፅ/ ሰማሁ አለ፡፡ በዚያው መናገርቻለ ፡፡
መናገር የማይችሉ መናገር ችለዋል ፤ መሄድ የማይችሉ መሄድ ችለዋል፡፡
የነቀርሳ ፣ እከክ በሽታ ያለባቸው ሰዎች ተፈውሰዋል፡፡
አንድ ህፃን 8 አመት ሙሉ እንጀራ አይበላም ነበር ፤ አንድ ቀን ከደብሯ አባቶች የተረፈ ምሳ ወስደው ሲያቀምሱት መብላት እንደጀመረ ቤተሰቦቹ ምስክርነት ሰጥተዋል፡፡
ተክለ ማርያም ይባላል ፤ የቤተክርስቲያኗን አጥር ያሰራ አባት ነው፡፡ እናም በድንገት ይታመምና ወደ ሆስፒታል ሲሄድ ኢትዮጵያን ጨምሮ ሌሎች ሃያላን የአለም ሃገራትን ያስጨነቀው ኮቪድ 19/ኮሮና/ ወረርሽን እንደተያዘ ይነገረዋል፡፡ እሱም ለእመቤታችን ፀሎት ያዙልኝ ብሎ ለደብሩ አባቶች ይናገራል ፤ የደብሩ አባቶችም ለ3 ቀን ማህሌት ፣ ቆመው ፀሎት ያደርጉለትና ከኮቪድ ወረርሽኝ ተፈውሷል፡፡
የደብረ ገነት ቅድስት ማርያም ብዙ ተዓምራትን ያደገረች ቢሆንም እኛ ግን ጥቂቱን ፃፍንላችሁ፡፡ እናንተ ደግሞ ወደ ተቀደሰ ቦታዋ መጥታችሁ የበረከት ተካፋይ ትሆኑ ዘንድ እናሳስባለን፡፡

10/05/2022

Address


Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የባሶና ወራና ወረዳ ባህልና ቱሪዝም ጽ/ቤት basso culture and tourism office posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

  • Address
  • Alerts
  • Claim ownership or report listing
  • Want your business to be the top-listed Media Company?

Share