Hanos Media ሐኖስ ሚዲያ

Hanos Media  ሐኖስ ሚዲያ -Current Affairs
-Music and Entertainment
-Geopolitical Analysis
-Economic and Development will entertaining here. TV Ethiopia (NTV Ethiopia).

10/07/2025

አርሰናል ቀነ ገደብ ተሰጠው

ስፖርቲንግ ሊዝበን አርሰናል የቪክቶር ዮኬርሽን ዝውውር እንዲያጠናቅቅ ቀነ ገደብ ሰጠ

አርሰናል የስፖርቲንግ ሊዝበን አጥቂውን ቪክቶር ዮኬሬሽን ለማስፈረም ድጋሚ አዲስ መነቃቃትን የጀመረ ሲሆን የፖርቹጋሉ ክለብ በሚቀጥሉት 48 ሰዓታት ውስጥ ከባድ ድርድር ለመቀጠል መዘጋጀቱን ዘ ሚረር ጆን ክሮስ ዘግቧል።

ለ27 አመቱ ስዊድናዊ ኢንተርናሽናል የዝውውር ክፍያ ላይ በተፈጠረ አለመግባባት በስፖርቲንግ የመሸጥ ፍላጎት መቀዛቀዝ የታየ ሲሆን ከአውሮፓ ድንቅ አጥቂዎች አንዱን ለማስፈረም ድርድር ለማካሄድ በድጋሚ ውይይት እንደሚያደርጉ ይጠበቃል።

አርሴናል ከ 2025/26 የውድድር ዘመን በፊት የ9 ቁጥር ተጫዋች ለመጨመር በዚህ ክረምት ዮኬሬሽ የአንድሬ በርታ እና የ አርቴታ ምኞት ዝርዝር አናት ላይ ይገኛል።

በ2023 ከኮቨንተሪ ሲቲ ስፖርቲንግን ከተቀላቀለ በኋላ አጥቂው በ102 ጨዋታዎች 97 ጎሎችን አስቆጥሯል፤ ባለፈው የውድድር አመት 54 ጎሎችን በ52 ጨዋታዎች ያስቆጠረ ሲሆን በቻምፒየንስ ሊግ ማንቸስተር ሲቲ ላይ ሃትሪክ መስራቱ ይታወቃል።
Via [ Mirror Football ]

ትልቅ ዜና
06/07/2025

ትልቅ ዜና

#...

26/06/2025

አርሰናል የቫሌንሲያዉን ተከላካይ ክርስቲያን ሙስኩኤራን ለማስፈረም ንግግር ጀመረ

ከአጥቂ በተጨማሪ ተከላካይ የማስፈረም ፍላጎት ያላቸው መድፈኞቹ የ20 አመቱን ስፔናዊ ተከላካይ ማስፈረም ይፈልጋሉ፡፡

ሙስኩኤራ በቫሌንሲያ 90 ጨዋታዎችን ያደረገ ሲሆን ባለፈዉ የዉድድር አመት ክለቡ በላሊጋዉ ካደረጋቸዉ 38 ጨዋታዎች በ37ቱ በቋሚነት ተሰልፏል፡፡

አርሰናል የቼልሲዉን ግብ ጠባቂ ኬፓ አሪዝባላጋ ፣ የብሬንትፎርዱን አማካይ ክርስቲያን ኖርድጋርድን ዝውውር ሊያጠናቅቅ ተቃርቧል።

26/06/2025

የመድፈኞቹ ፈርጥ፣ የእንግሊዝ ብሄራዊ ቡድን ተስፋና የሊጉ ኩራት የሆነው አስደናቂው ቡካዮ ሳካ 23ኛ አመቱ ላይ ቢገኝም ያለው ክህሎት፣አበርክቶና ተጽእኖ ከእድሜው በላይ መሆኑን እያሳየን ይገኛል።
ቡካዮ አዮይንካ ቴሚዳዮ ሳካ የተወለደው ኑሯቸውን በለንደኗ ኢሊንግ ካደረጉ ናይጄራዊያን ወላጆቹ በሴፕቴምበር 5 2001 ሲሆን ለቤተሰቦቹ 3ኛ ልጅ ነው።
በዮሩባ ቋንቋ ቡካዮ ማለት ተጨማሪ ደስታ ማለት ሲሆን መላው የአርሰናልና የእንግሊዝ ብሄራዊ ቡድን ደጋፊዎች በ23 አመቱ ኮከብ ጥበበኛ እግሮች ተጨማሪ ደስታን እየሰጣቸው መሆኑን ይመሰክራሉ።
ቡካዮ ሳካ በ2010 8 አመት ሲሞላው በመድፈኞቹ የታዳጊዎች አካዳሚ ታቅፎ የእግርኳስ ህይወቱን ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ በሁሉም የእድሜ አርከኖች ያለውን እምቅ ችሎታ እያሳየ የ3 ጊዜ የፕሪሚየር ሊግ ሻምፕዮኖቹ ተስፋ ለመሆን ጊዜ አልፈጀበትም።
👉ከታች ባለው ማስፈንጠሪያ ሙሉውን ይከታተሉ።
https://youtu.be/zxWJ2D1VEoI

Send a message to learn more

በዛሬ ውሎ የተሰሙ አጫጭር ስፖርታዊ መረጃዎች++++++++የመድፈኞቹ አማካይ ጋናዊው ቶማስ ፓርቴ ከክለቡ በነጸ ዝውውር ሊለያይ መሆኑ ተሰምቷል፡፡ ተጫዋቹ ቀጣይ ሳምንት በሰሜን ለንደኑ ክለብ ...
26/06/2025

በዛሬ ውሎ የተሰሙ አጫጭር ስፖርታዊ መረጃዎች
++++++++
የመድፈኞቹ አማካይ ጋናዊው ቶማስ ፓርቴ ከክለቡ በነጸ ዝውውር ሊለያይ መሆኑ ተሰምቷል፡፡ ተጫዋቹ ቀጣይ ሳምንት በሰሜን ለንደኑ ክለብ ያለው ኮንትራት ይጠናቀቃል፡፡ አርሰናል የቶማስ ፓርቴን የደመዎዝ ጨማሪ ጥያቄ ባለመቀበሉ የውል ማራዘሚያ ስምምነት ላይ ሁለቱ ወገኖች መድረስ አለመቻላቸው ነው የተነገረው፡፡ የስፔኑ ባርሴሎና የ32 ዓመቱ አማካይ ስፍራ ተጫዋች ቀዳሚ ፈላጊ መሆኑ ተነግሯል፡፡በተመሳሳይ የሰሜን ለንደኑ ክለብ በቶማስ ፓርቴ ምትክ ዴንማርካዊውን የብሬንትፎርድ አማካይ ክርስቲያን ኖርጋርድን በ11 ሚሊየን ዩሮ ለማስፈረም ከስምምነት መድረሱ ተሰምቷል፡፡ እንዲሁም መድፈኞቹ ስፔናዊውን ግብ ጠባቂ ኬፓ አሪዛባላጋን በ5 ሚሊየን ፓውንድ ከቼልሲ ለማስፈረም ከስምምነት ደርሰዋል፡፡

👉 የሳዑዲው አልናስር አሰልጣኝ ስቴፋኖ ፒዮሊ ከክለቡ ጋር መለያየታቸው ተነግሯል፡፡ የቀድሞው ኤሲሚላን፣ ፊዮረንቲና፣ ኢንተር ሚላን፣ ላዚዮ እና ቦሎኛ አሰልጣኝ ፒዮሊ አልናስርን በአሰልጣኘነት የተረከቡት በተጠናቀቀው የውድድር ዓመት ሉዊስ ካስትሮን በመተካት ነበር፡፡በተመሳሳይ ፖርቹጋላዊው ኮከብ ክርስቲያኖ ሮናልዶ በአልናስር ለመቆየት መስማማቱ ተነግሯል፡፡ የ40 ዓመቱ ተጫዋች ኮንትራቱ በዚህ ክረምት መጠናቀቁን ተከትሎ ክለቡን ይለቃል ሲባል ቢቆይም በአልናስር ለመቆየት ወስኗል፡፡

👉ሉካ ሞድሪች የጣልያኑን ክለብ ኤሲ ሚላን ለመቀላቀል በቃል ደረጃ ከስምምነት መድረሱ ተሰምቷል፡፡ በመጪው መስከረም ወር 40 ዓመቱን የሚደፍነው ሞድሪች ከፊፋ የክለቦች ዓለም ዋንጫ በኋላ የሕክምና ምርመራውን በማድረግ በይፋ የኤሲ ሚላን ተጫዋች ይሆናል ተብሎ ይጠበቃል፡፡
👉የካታላኑ ክለብ ባርሴሎና የ2025/26 የውድድር ዓመት የመክፈቻ ጨዋታን በሜዳው ካምፕ ኑ ለማድረግ ላ ሊጋን መጠየቁ ተጠቅሷል፡፡ ባርሴሎና ሜዳው ካምፕ ኑ በእድሳት ላይ የሚገኝ ሲሆን÷ ግንባታው ሙሉ ለሙሉ ሲጠናቀቅ 105 ሺህ ተመልካች በመያዝ በስፔን ከፍተኛ ተመልካች የሚይዝ ግዙፍ ስታዲየም ያደርገዋል፡፡
ክለቡ የቅድመ ውድድር ዓመት ጨዋታውን በመጪው ሐምሌ በካምፕ ኑ በ25 ሺህ ደጋፊዎች ፊት ለማድረግ ማቀዱም ተጠቁሟል፡፡
👉ኤደርሰን ሞራዬስ በማንችስተር ሲቲ እንደሚቆይ አስታወቀ።የውሃ ሰማያዊዎቹ ግብ ጠባቂ በያዘነው የክረምት መስኮት ክለቡን ይለቃሉ ከተባሉ ተጫዋቾች አንዱ እንደነበር አይዘነጋም።በክለቦች አለም ዋንጫ እየተጫወተ የሚገኘው ኤደርሰን፣ በሲቲ ስለሚኖረው ቆይታ ተጠይቆ “ተጨማሪ ዓመታትን በክለቡ እቆያለሁ" ሲል አስተያየቱን ሰጥቷል።
የኔን ቆይታ በተመለከት እየተዘገበ የሚገኘው ሁሉ ሃሰት ነው” ያለው ብራዚላዊ ተጨማሪ ትልልቅ ስኬቶችን ከቡድኑ ጋር ማሳካት እንደሚፈልግ ተናግሯል።ተጫዋቹ ይህንን ይበል እንጂ ከሳዑዲ አረቢያ ክለቦች ጋር ስሙ በስፋት ሲያያዝ መቆየቱ እና ወኪሎቹም ዝውውሩን በተመለከተ ሲደራደሩ እንደነበር አይዘነጋም።ማንችስተር ሲቲም የፖርቶውን ግብ ጠባቂ ዲዬጎ ኮስታን ለማስፈረም በሂደት ላይ እንደነበር ይታወሳል።አሰልጣኝ ፔፕ ጋርዲዮላ የተጫዋቹ አድናቂ መሆናቸው እና ሲቲም ግብ ጠባቂውን ወደ ኢቲሃድ መውሰዱ አይቀርም እየተባለ ይገኛል።

🚨𝐁𝐑𝐄𝐀𝐊𝐈𝐍𝐆:የመሀል ሜዳ ሞተሩ ጋናዊው Thomas Partey በሚያሳዝን ሁኔታ አርሰናልን ይለቃል አርሰናል ፓርቴን በክለቡ ለማቆየት ደሞዙን አልጨምርም በማለቱ ፓርቴ እና አርሰናል ተለይል...
25/06/2025

🚨𝐁𝐑𝐄𝐀𝐊𝐈𝐍𝐆:

የመሀል ሜዳ ሞተሩ ጋናዊው Thomas Partey በሚያሳዝን ሁኔታ አርሰናልን ይለቃል

አርሰናል ፓርቴን በክለቡ ለማቆየት ደሞዙን አልጨምርም በማለቱ ፓርቴ እና አርሰናል ተለይልተዋል።

#እና

25/06/2025

እየሩሳሌም-ጋዛ ዉስጥ 7 የእስራኤል ወታደሮች ተገደሉ
ደቡባዊ ጋዛ ሠርጥ ኻን ዩኑስ ዉስጥ የሸመቁ ታጣቂዎች በከፈቱት ጥቃት 7 የእስራኤል ወታደሮች ገደሉ፤ ሌላ አንድ ወታደር ክፉኛ አቆሰሉ።ሮይትረርስ ዜና አገልግሎት እንደዘገበዉ ወታደሮቹ የተገደሉት ይጓዙበት የነበረዉን ብረት ለበስ ተሽከርካሪን ታጣቂዎቹ በፈንጂ አንጉደዉት ነዉ።የእስራኤል ጦር ቃል አቀባይ ብርጌድየር ጄኔራል ኤፊ ዴፍሪን እንዳሉት የፍልስጤም ታጣቂዎች እዚያዉ ኻን ዩንስ ዉስጥ በከፈቱት ሌላ ጥቃት አንድ የእስራኤል ጦር በጠና ቆስሏል።እስራኤል፣ዩናይትድ ስቴትስ፣ የአዉሮጳ ሕብረትና ተባባሪዎቻቸዉ ባሸባሪነት የፈረጁት ሐማስ ጥቃቱን ማድረሱን አስታዉቋል።ሐማስና ኢስላሚክ ጀሐ,ድ መስከረም 2016 ደቡባዊ እስራኤል ላይ በከፈቱት ጥቃት 1200 ሰዎች መግደላቸዉን የእስራኤል ባለሥልጣናት አስታዉቀዋል።ታጣቂዎቹ ጥቃቱን በከፈቱበት ወቅት ካገቷቸዉ 251 ሰዎች መካከል 50ዉ እስካሁን አልተለቀቁም።የእስራኤል ጠቅላይ ሚንስትር ቢኒያሚን ኔታንያሁ ሐማስን ማጥፋት፣ታጋቾቹን ማስለቀቅና ጋዛ ዳግም ለእስራኤል እዳታሰጋ የማድረግ ግብ እንዳለዉ በተናገሩት የእስራኤል የብቀላ ጥቃት የጋዛ ሰርጥ ወድማለች።የእስራኤል ጦር ከ56 ሺሕ በላይ ፍልስጤማዉያንን ገድሏል።ከሟቾቹ 5 ሺሕ 7 መቶዉ የተገደሉት እስራኤል ከሐማስ ጋር ያደረገችዉን የተኩስ አቁም ሥምምነት ጥሳ ባለፈዉ መጋቢት አጋማሽ ዳግም ጋዛን መደብደብ ከጀመረች ወዲሕ ነዉ። የፍልስጤም ባለሥልጣናት እንደሚሉት አብዛኞቹ ሟቾች ሴቶች፣ ሕፃናትና አቅመ ደካሞች ናቸዉ።ከመስከረም 2016 ወዲሕ የእስራኤል ጦር የተገደሉበት ወታደሮች ቁጥር ከ860 በልጧል።

Here we go!😘😘😘
23/06/2025

Here we go!😘😘😘

https://youtu.be/McCHjMfsr60?si=TVRe08Nk-b9ee-Ky
21/09/2023

https://youtu.be/McCHjMfsr60?si=TVRe08Nk-b9ee-Ky

music merabete traditional wedding song,የቆጥኣስር የሰርግ ጭፈራ መራቤቴ ፡ባል የሚስትን ቤተሰበ ካገለገለና ልጃቸዉን ካገባ በኋላ የሚካሄድ ሰርግ ክፍል ENTERTA...

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Hanos Media ሐኖስ ሚዲያ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share