Ethio Media Center

  • Home
  • Ethio Media Center

Ethio Media Center Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Ethio Media Center, Media/News Company, .

ጌታቸዉ ረዳ ስለ ቴዲ አፍሮ አንድ ወቅት በአዲስ ነገር ጋዜጣ ይህንን ብሏል..."ቴዲ አፍሮ ያለዉን ተወዳጅነትና ያካበተዉን ስምና ዝና በሚመለከት ብዙ የሚያጠያይቅ ነገር ይኖራል ብየ አልገምት...
09/04/2025

ጌታቸዉ ረዳ ስለ ቴዲ አፍሮ አንድ ወቅት በአዲስ ነገር ጋዜጣ ይህንን ብሏል...

"ቴዲ አፍሮ ያለዉን ተወዳጅነትና ያካበተዉን ስምና ዝና በሚመለከት ብዙ የሚያጠያይቅ ነገር ይኖራል ብየ አልገምትም። በእርግጥም በአጭር ጊዜ ዉስጥ ባደረገዉ የግሉ ጥረት አሁን ያለበት ደረጃ ላይ የደረሰ ነዉ። ለሌሎች በመሰል ሙያ ላይ የመሳተፍ ዝንባሌ ላላቸዉ ወጣቶች ሊያስተላልፈዉ የሚችለዉ በርካታ ቁም ነገር እንዳለም አይካድም። በዚህ ረገድ የብዙ ሰዎች አርአያ ለመሆን ስለመቻሉም በእርግጠኝነት መናገር ይቻላል..."

ምንጭ- ኢትዮ ፎረም

በኢትዮ ሳት ላይ ተቋርጦ የነበረው ኢቢኤስ ቴሌቪዥን ዳግም ወደ አየር ተመልሶ ስርጭት ጀምሯል።
26/03/2025

በኢትዮ ሳት ላይ ተቋርጦ የነበረው ኢቢኤስ ቴሌቪዥን ዳግም ወደ አየር ተመልሶ ስርጭት ጀምሯል።

ሶስቱም የኢቢኤስ ቻናሎች ስርጭት አቆሙ‼️ሰሞኑን ከወጣት ብርቱካን የእሁድን በኢቢኤስ ፕሮግራም ጋር ተያይዞ ውዝግብ ውስጥ የገባው ኢቢኤስ ቴሌቪዥን በዛሬው ዕለት ሶስቱም ቻናሎቹ በኢትዮ ሳት ...
26/03/2025

ሶስቱም የኢቢኤስ ቻናሎች ስርጭት አቆሙ‼️

ሰሞኑን ከወጣት ብርቱካን የእሁድን በኢቢኤስ ፕሮግራም ጋር ተያይዞ ውዝግብ ውስጥ የገባው ኢቢኤስ ቴሌቪዥን በዛሬው ዕለት ሶስቱም ቻናሎቹ በኢትዮ ሳት ላይ ስርጭት ቆሟል።

ለግሸን ደብረ ከርቤ ገዳም ማሰሪያ በ EOTC የቀጥታ ስርጭት የገቢ ማሰባሰቢያ እየተካሔደ ሲሆን በአጠቃላይ ለመሰብሰብ ከታቀደዉ  300 ሚሊዮን ብር ዉስጥ 26 ሚሊዮን ብር ተሰብስቧል። ድጋፍ...
22/03/2025

ለግሸን ደብረ ከርቤ ገዳም ማሰሪያ በ EOTC የቀጥታ ስርጭት የገቢ ማሰባሰቢያ እየተካሔደ ሲሆን በአጠቃላይ ለመሰብሰብ ከታቀደዉ 300 ሚሊዮን ብር ዉስጥ 26 ሚሊዮን ብር ተሰብስቧል። ድጋፍ ለማድረግና ከበረከቱ ለመሳተፍ የምትፈልጉ👇

ንግድ ባንክ- 1000542382957
አቢሲኒያ ባንክ- 1353212121
Zelle- 2409456213
https://www.youtube.com/live/W4TT5XSAplU?si=ldgKfbTyk5oPFyHX

"ኒቃብ ከመማር፣ ከፍተኛ ውጤት ከማምጣትና ከመሸለም አያግድም" ▣ ከአርባምንጭ ዩንቨርሲቲ በሜዲስን ዲፓርትመንት የወርቅ ሜዳለያ ተሸላሚዋ ዛኪራ ተባረክ ተማሪ ዛኪራ ተባረክ ከአርባምንጭ ዩኒቨ...
22/02/2025

"ኒቃብ ከመማር፣ ከፍተኛ ውጤት ከማምጣትና ከመሸለም አያግድም"

▣ ከአርባምንጭ ዩንቨርሲቲ በሜዲስን ዲፓርትመንት የወርቅ ሜዳለያ ተሸላሚዋ ዛኪራ ተባረክ

ተማሪ ዛኪራ ተባረክ ከአርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ በሜዲስን ትምህርት ክፍል 3.87 አምጥታ በከፍተኛ ውጤት በዛሬው እለት ተመርቃለች።

ዛኪራ ተባረክ በዛሬው ዕለት በተካሄደው የአርባምንጭ ዩንቨርስቲ የምርቃ መርኃግብር ላይ በሶስት ዘርፍ ተሸላሚ ሆና ነው የተመረቀችው። ከሁሉም የህክምና ተማሪዎች አንደኛ በመውጣት፣ ከሁሉም ሴቶች አንደኛ በመውጣት፣ ከሁሉም ተማሪዎች አንደኛ ወጥታ የወርቅ ሜዳለያ ተሸላሚ መሆኗን እንዲሁም በጀመአ እንቅስቃሴ ላይ በስፋት እንደምትሳተፍ የሙስሊም ተማሪዎች ህብረት ለሀሩን ሚድያ ያደረሱን መረጃ ያመላክታል።

Via-ሀሩን ሚድያ

በኢስት አፍሪካ አርትስ ኤንድ ካልቸራል አሶሴሽን ኮሜዲያን እሸቱ መለሰ በሲያትል ዕውቅና ተሰጠው    | የዘንድሮ የኢስት አፍሪካ አርትስ ኤንድ ካልቸራል አሶሴሽን አዋርድን (East Afric...
19/02/2025

በኢስት አፍሪካ አርትስ ኤንድ ካልቸራል አሶሴሽን ኮሜዲያን እሸቱ መለሰ በሲያትል ዕውቅና ተሰጠው

| የዘንድሮ የኢስት አፍሪካ አርትስ ኤንድ ካልቸራል አሶሴሽን አዋርድን (East African Arts and Cultural Association) በKing Solo Promotion አስተባባሪነት በተዘጋጀው የሲያትሉ የኮሜዲ ምሽት ላይ በመገኘት
ተወዳጁን ኮሜዲያን እሸቱ መለሰ ተሸላሚ አድርጏል ።

ኮሜዲያን እሸቱ መለሰ በስታንዳፕ ኮሜዲ ሥራው በበርካቶች ዘንድ የሚታወቅ ሲሆን በሚሠራቸው በጎ ተግባራትም ኮሜዲያኑ በሕዝብ ዘንድ በሠፊው ይታወቃል።

አቶ መሸሻ ታደሰ አቶ አዲሱ በላይነህ የእስማርት ለሪኒግ ሴንተር መሥራች እና ሊቀመንበር እና ወይዘሪት ፂዮን ወ/ኪሮስ የአሜሪካን ፋሚሊ ኢንሹራስ ኤጀንት በክብር እንግድነት ዝግጅቱላይ ተገኝተዋል ።

ከዚህ በፊት የኢስት አፍሪካ አርትስ ኤንድ ካልቸራል አሶሴሽን ድምፃዊ ቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ) እንዲሁም ድምፃዊ ጎሳዬ ተስፋዬ እና ሌሎችም የኪነጥበብ ሰዎች መሸለሙ እና ዕውቅና መስጠቱ ይታወሳል።

 ፡20 400, 000, 000 ብር ደረሰ 💚💛❤🙏ያስጀመረን ያስጨርሰናል‼️በመላው ዓለም የሚገኙ ልበ ቀና "ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን በቂ ነው" ያሉ ሰዎች ድጋፋቸውን ቀጥለው አጠቃላይ የተሰበ...
18/02/2025

፡20

400, 000, 000 ብር ደረሰ 💚💛❤🙏

ያስጀመረን ያስጨርሰናል‼️

በመላው ዓለም የሚገኙ ልበ ቀና "ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን በቂ ነው" ያሉ ሰዎች ድጋፋቸውን ቀጥለው አጠቃላይ የተሰበሰበው ብር 400 , 000, 000 (አራት መቶ ሚሊዮን) ብር መድረስ ችሏል።

ቀናችንን በበጎ ስራ እንጀምር‼️**************************መነኮሳት ዛሬም ጥሪ አቅርበዋል። በሰሜን ጎንደር ሀገረ ስብከት  በደባርቅ ወረዳ  ቤተክህነት ስር በአደጋት ቀበሌ ውስ...
03/02/2025

ቀናችንን በበጎ ስራ እንጀምር‼️
**************************
መነኮሳት ዛሬም ጥሪ አቅርበዋል። በሰሜን ጎንደር ሀገረ ስብከት በደባርቅ ወረዳ ቤተክህነት ስር በአደጋት ቀበሌ ውስጥ የሚገኘው የምዕራፈ ቅዱሳን አፅሐራራ ቅዱስ ጊዮርጊስ አንድነት ገዳም በቅድስት አመተ ክርስቶስ በ14ኛዉ ክፍለ ዘመን የተመሠረተ ታላቅ እና ታምራዊ ገዳም ሲሆን በጊዜ ብዛት የድሮው ቤተክርስቲያን ፈርሷል። ጣራዉን ለማደስም አስቸኳይ ነዉና በዉስጥም በውጭም ያላችሁ ወገኖቻችን በሰማዕቱ በቅዱስ ጊዮርጊስ ስም የአቅማችሁን በማገዝ ከበረከቱ እንድትሳተፉ እንለምናችዋለን በማለት መነኮሳቱ ተማፅኗቸዉን አሰምተዋል‼️
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ - 1000331624334
☎️ 0934654964 ወይም 0918532706
ለብዙዎች እንዲዳረስ እባካችሁ ሼር አድርጉት‼️
መልካም ቀን🙏

>        " ድምፃዊ አለማየሁ ሂርጶ "ድምፃዊ አለማየሁ ሂርጶ ከFm አዲስ 97.1 መሰንበቻየሬዲዮ ፕሮግራም ላይ ከአዘጋጅና አቅራቢው ጋዜጠኛሰለሞን ጫላ ጋር ያደረገውን ጣፋጭ ቆይታ በወፍ...
02/02/2025

>
" ድምፃዊ አለማየሁ ሂርጶ "

ድምፃዊ አለማየሁ ሂርጶ ከFm አዲስ 97.1 መሰንበቻ
የሬዲዮ ፕሮግራም ላይ ከአዘጋጅና አቅራቢው ጋዜጠኛ
ሰለሞን ጫላ ጋር ያደረገውን ጣፋጭ ቆይታ በወፍ በረር
ላስቃኛችሁ ፦

✦ የተሰኘውን አዲሱ ስራዬን አብዱ ኪያር ነው
የሰጠኝ። ዜማና ግጥሙን ብቻ አይደለም የሰጠኝ።
ለስቱዲዮ ከፍሎ ፣ ለሙዚቀኞች ከፍሎ የሚደረገውን
በሙሉ አድርጎ ይኼ የኔ ስጦታ ነው። በድምፅህ ግባና
የራስህ አድርገው ብሎ ነው የሰጠኝ።

✦ የሚለውን ግጥም እዮቤል ብርሃኑ
አመጣና አሳየኝ። በጣም ብቃት ያለው ደራሲ ነው።
አሌክስ ይኼንን ስራ ከፃፍኩት 13 ዓመቴ ነው።
ለማንም ሰው ሰጥቼው አላውቅም አለኝ። ይኼ
ምናልባት አንተን ጠብቆ ሊሆን ይችላል አለኝ።
ዜማ ሰራንለትና ልናወጣው ቻልን።

✦ እናቶች 200 እና 300 ብር ተቀብለው ያንን ሁሉ ቤተሰብ
የሚያሳድጉበት ጥበብ ይገርመኛል።

✦ ሰው የሚሰጠው አስተያየት በጣም ነው የገረመኝ።
ሰው ይኼንን ያህል ይወደኛል እንድል ነው ያደረገኝ።
አንዳንዶቹ የሚፅፉት ፅሁፎች ትልልቅ ደራሲዎች ነው
የሚመስሉት። በዚህ አጋጣሚ በጣም ላመሰግናቸው
እፈልጋለሁ።

✦ በምንም ሁኔታ ውስጥ ብታልፍ መኖር ደስ ይላል።
በበሽታ ውስጥ ልታልፍ ትችላለህ። በመከራ ውስጥ
ልታልፍ ትችላለህ። አልጋ ውስጥም ሆነህ መኖር ደስ
ይላል። ኖርዌይ እያለሁ አትተርፍም ተብዬ ነበር።
እኔ ጋር የነበሩ 13 ሰዎች ሞተዋል።
አልሞትም የሚል ተስፋ ውስጥ ስገባና ፈጣሪዬም
ስለረዳኝ እኔ ላይ የተሞከረው መድሃኒት ሰራ እና ልተርፍ
ቻልኩኝ።

✦ #ኢቫንጋዲ አልበምን መስፍን ታምሬ ነው ፕሮዲውስ
ያደረገው። እኔና ጎስሽን ከሕዝብ ጋር በደንብ ያስተዋወቀን
ስራ ነው። ወልዶናል ማለት ይቻላል።

✦ #ባይተዋር የአለማየሁ ደመቀ ግጥምና ዜማ ነው።
አለማየሁ ለእናቱ ማስታወሻ የሰራው ስራ ነው።
እኔም በ 3 ወር ውስጥ ነው እናትና እህቴ ያረፉት።
እና ያ ስሜት እኔም ጋር ተጋባና ዘፈኑን ከልብ እና ከስሜት
ጥሩ አድርገን ሰራነው።

✦ የዛን ጊዜ ታዳጊዎችና ወጣቶች የነበሩ አሁን አድገው
ያስታውሱኛል። ያን ዘመን ይነግረኛል። እኔንም ወደኋላ
ይመልሱኛል። በጣም ነው ደስ የሚለኝ ኢቫንጋዲ።

✦ #ዴዝዴሞና ሀሳቡን ለመሰለ ጌታሁን ነገርኩትና እሱም
ጥሩ አድርጎ ጻፈው። በሕዝብ ዘንድም በጣም ተወደደ።

✦ አለምገና ኪነት የሚባል ነበር። እዛ ስጫወት የዛን ጊዜ
በሃሎ ሃሎ እየጮሁኩኝ ነበር የምጫወተው። ከዛ ከፍተኛ
5 ኪነት ገባሁ። እዛ ከታዋቂ ዘፋኞች ጋር ነበር የምሰራው
ክለብ ላይ የነባህታ የነተሾመ ምትኩን እጫወት ነበር።
አሮሰ ሆቴል ሰው በብዛት ይመጣ ነበር። ሰብስበን
መረጥንና በካሴት አወጣኋቸው።

✦ እኔ ዘፋኞቹን መምሰል አልችልም። እኔ ዘፈኑ እንዲያምር
ነው የምፈልገው። ተጨንቄ በራሴ ስታይል ነው አሳምሬ
የምጫወታቸው። ዘፋኞቹም መጥተው ሲሰሙም በጣም
ነው ደስ የሚላቸው።

✦ እኔ አሁን ኤፍሬም ታምሩን በጣም ስለምወደው ኤፍሬምን
መሆን አልችልም። የኤፍሬምን ሞክሬ አላውቅም።
የሱን ስሰማው ነው ደስ የሚለኝ።

✦ ኖርዌይ እያለሁ ከቤት አልወጣም ነበር። የዛን ጊዜ ጥሩ
አልነበርኩም። ብዙ አርቲስቶች ሊያገኙኝ ብዙ ጊዜ
ይመጣሉ። ስልክ ሁሉ ይደውላሉ። እኔ ግን አላገኛቸውም
ጥሩ ሁኔታ ላይ አልነበርኩም። እተርፋለሁ የሚል ሁኔታ
ውስጥም አልነበርኩም።
ብቻዬን ብዬ ዘፍኜ ብቻዬን ቤት ውስጥ ቀረሁኝ።
ባይተዋር ብዬ ዘፍኜ ባይተዋር ሆንኩኝ።
ለራሴ ነው እንዴ የዘፈንኩት እል ነበር።
ሆድዬ ብዬ ስንት አሳር መከራ አይተሃል ይበቃሃል
ብዬ መጥቻለሁ።

✦የድምጼ አለመቀየር ምክንያቱ ፦ አንደኛ አርፊያለሁ።
ከሱስ ጋር በተያያዘ ሁሉንም ነገር አቁሚያለሁ። ከውሃ
በስተቀር ምንም አልጠቀምም። ስፖርት እሰራለሁ።
ያ የረዳኝ ይመስለኛል።

✦ አዲስ አልበሜን ጨርሻለሁ። ወደ 14 ዘፈኖች ደርሻለሁ።
በ 3 ወር ውስጥ ነው የጨረስኩት።
አዲሱ አልበሜ ላይ በግጥምና ዜማ የተሳተፉት ፦
አለማየሁ ደመቀ ፣ ብስራት ሱራፌል ፣ አቡዲ ፣
አብዱ ኪያርና ሌሎችም ተሳትፈዋል።

✦ የምኖርበትን ቤት የሰጠኝ ዑመር መሐመድ ይባላል።
ኪቦርድም ጨምሮ ነው የሰጠኝ። በጣም ደግ ሰው ነው።
ጠዋት ከእንቅልፌ ተነስቼ አዲሱ ጓደኛዬ ኪቦርዱ ጋር
ነው የምውለው። አሁን ብቻዬን አይደለሁም።

✦ በመጨረሻ ማስተላለፍ የምፈልገው አልበሜን በቅርብ
ቀን ስለምለቀው You Tube ቻናሌን ሰብስክራይብ
እያደረጋችሁ አበረታቱኝ። እናንተን የሚመጥን ቆንጆ
ስራዎችን ይዤ እመጣለሁ።

በማለት ድምፃዊ አለማየሁ ሂርጶ ጣፋጭ ቆይታውን
አጠናቋል።

አሌክስ የ9ዐዎቹ ድምቀት አዲሱ አልበምህን ለመስማት
ጓጉቻለሁ።

ዘሪሁን ተዝናኑ

 #ይህ ድንግልና ለእርሷ ብቻ የተሰጠ ነው  “እግዚአብሔር አንድ ልጁን እስኪሰጥ ድረስ ዓለሙን እንዲሁ ወድዶአልና። ፍቅርም እንደዚህ ነው፤ እግዚአብሔር እርሱ ራሱ እንደ ወደደን ስለ ኃጢአታች...
24/01/2025

#ይህ ድንግልና ለእርሷ ብቻ የተሰጠ ነው

“እግዚአብሔር አንድ ልጁን እስኪሰጥ ድረስ ዓለሙን እንዲሁ ወድዶአልና። ፍቅርም እንደዚህ ነው፤ እግዚአብሔር እርሱ ራሱ እንደ ወደደን ስለ ኃጢአታችንም ማስተስረያ ይሆን ዘንድ ልጁን እንደ ላከ እንጂ እኛ እግዚአብሔርን እንደ ወደድነው አይደለም፤” ይላል። ዮሐ፡3፥17፣ 1ኛ፡ዮሐ፡4፥10። ይህን መውደድ ይህን ፍቅር የገለጸው ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም በድንግልና በመወለድ ነው። የእመቤታችን ድንግልና በሦስት ወገን በሥጋዋ፥ በነፍሷና በልቡናዋ ነው። ይህ ድንግልና፡- የዘለዓለም ድንግልና ነው። ነቢየ እግዚአብሔር ቅዱስ ኢሳይያስ “ስለዚህ ጌታ ራሱ ምልክት ይሰጣችኋል፤ እነሆ ድንግል ትፀንሳለች፣ ወንድ ልጅም ትወልዳለች፣ ስሙንም አማኑኤል ብላ ትጠራዋለች፤” ብሎአል። ኢሳ፡7፥14።

ነቢዩ ቅዱስ ሕዝቅኤልም “ወደ ምሥራቅ ወደሚመለከተው በስተውጭ ወዳለው ወደ መቅደሱ በር አመጣኝ፤ ተዘግቶም ነበር። እግዚአብሔርም ይህ በር ተዘግቶ ይኖራል እንጂ አይከፈትም፣ ሰውም አይገባበትም፤ የእስራኤል አምላክ እግዚአብሔር ገብቶበታልና ተዘግቶ ይኖራል፤” ብሎአል። ሕዝ፡44፥1። የተዘጋ የመቅደስ በር የተባለች እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ናት። “ይህ በር ተዘግቶ ይኖራል እንጂ አይከፈትም፤” የሚለው ኃይለ ቃል በድንግልና ጸንታ እስከ ዘለዓለሙ እንደምትኖር ይነግረናል። “ሰው አይገባበትም የእስራኤል አምላክ እግዚአብሔር ገብቶበታልና ተዘግቶ ይኖራል” ሲልም እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በድንግልና ፀንሳ፥ በድንግልና የወለደችው ኢየሱስ ክርስቶስ የባህርይ አምላክ በመሆኑ፥ ከርሷ በተዋህዶ ሰው የሆነ የባህርይ አምላክ እንጂ ዕሩቅ ብእሲ አይወለድምና በድንግልና እንደጸናች ትኖራለች።

እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ከመጽነሷ በፊት፣ በጸነሰችም ጊዜ፣ ከጸነሰችም በኋላ ድንግልናዋ የጸና ነው፤ ከመውለዷ በፊት፣ በወለደችም ጊዜ፣ ከወለደችም በኋላ ኅትምት በድንግልና ናት። የውዳሴ ማርያም አንድምታ ሊቀ መላዕክት ቅዱስ ገብርኤል አንቺ ከሴቶች ሁሉ ተለይተሽ የተባረክሽ ነሽ ያላትን አብራርቶ ይነግረናል፡፡ እመቤታችን መልአኩ ሲያበስራት “ወንድ ሳላውቅ ይህ ነገር እንደምን ይሆንልኛል?” የሚል ጥያቄ አንስታ ነበር፡፡ ይህን ያለችው ክብር ይግባትና የወንድ ሀሳብ በአእምሮዋ ፈጽሞ ተመላልሶ ስለማያውቅ ነው፡፡ ሌሎች ሴቶች ስለወንድ ከመናገርና በሕጋዊ ሩካቤ ከመገናኘት ቢታቀቡ ከማሰብ ግን አይነጹም፡፡ እምቤታችን ግን ከመናገር ከማድረግ ከማሰብ ንጽህት ናት፡፡

በሥላሴ አኗኗር ወልድ ለአብ ተቀዳሚና ተከታይ የሌለው አንድ ልጅ እንደሆነ ሁሉ ለእናቱ ለቅድስት ድንግል ማርያምም ተቀዳሚና ተከታይ የሌለው አንድ ልጇ ነው። በጳጳስ ወንበር ቄስ፣ በንጉሥ ዙፋን ራስ ደፍሮ እንደማይቀመጥ ሁሉ በአምላክ ዙፋን በቅድስት ድንግል ማርያም ማኅፀን ማን ያድራል? ለዚህም ነው እግዚአብሔር ለነቢዩ ለሕዝቅኤል አስቀድሞ የነገረው። ጠቢቡ ሰሎሞንም “እኅቴ ሙሽራ የተቈለፈ ገነት፣ የተዘጋ ምንጭ፣ የታተመ ፈሳሽ ናት፤” ብሎአል። መኃ 4፥12። እንደተቆለፈች አምላክ ብቻ አድሮባት የወጣባት ገነት፣ እንደተዘጋች የዘለዓለምን ሕይወት ክርስቶስን ያመነጨች፣ እንደታተመች የሕይወትን ውኃ ክርስቶስን በአራቱም ማዕዝን አፍስሳ የተጠሙ ነፍሳትን ያረካች፣ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ብቻ ናት።

ድጋፍ ለማድረግ:- ምዕራፈ ቅዱሳን ቅዱስ ጊዎርጊስ አንድነት ገዳም

ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000331624334

የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0934654964 ወይም 0918532706

አስቸኳይ  የድጋፍ  ጥሪ ‼️***********************እንኳን ለጥምቀት በዓል አደረሳችሁ። ገዳማዊያን በአሉን በበረከት እንድታሳልፉት ጥሪ አቅርበዋል። በሰሜን ጎንደር ሀገረ ስብከት...
18/01/2025

አስቸኳይ የድጋፍ ጥሪ ‼️
***********************
እንኳን ለጥምቀት በዓል አደረሳችሁ። ገዳማዊያን በአሉን በበረከት እንድታሳልፉት ጥሪ አቅርበዋል። በሰሜን ጎንደር ሀገረ ስብከት በደባርቅ ወረዳ ቤተክህነት ስር በአደጋት ቀበሌ ውስጥ የሚገኘው የምዕራፈ ቅዱሳን አፅሐራራ ቅዱስ ጊዮርጊስ አንድነት ገዳም በእናታችን ቅድስት አመተ ክርስቶስ በ14ኛዉ ክፍለ ዘመን የተመሠረተ ታላቅ እና ታምራዊ ገዳም ሲሆን በጊዜ ብዛት የድሮው ቤተክርስቲያን ፈርሶብናል። ጣራዉን ለማደስ አስቸኳይ ነዉና በውጭም ያላችሁ ወገኖቻችን በሰማዕቱ በቅዱስ ጊዮርጊስ ስም የአቅማችሁን በማገዝ ከበረከቱ እንድትሳተፉ እንለምናችዋለን‼️
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ - 1000331624334
☎️ 0934654964 ወይም 0918532706
ለብዙዎች እንዲዳረስ እባካችሁ ሼር አድርጉት‼️

አስቸኳይ  የድጋፍ  ጥሪ ‼️*********************** በሰሜን ጎንደር ሀገረ ስብከት  በደባርቅ ወረዳ  ቤተክህነት ስር በአደጋት ቀበሌ ውስጥ የሚገኘው  የምዕራፈ ቅዱሳን አፅሐራራ...
08/01/2025

አስቸኳይ የድጋፍ ጥሪ ‼️
***********************
በሰሜን ጎንደር ሀገረ ስብከት በደባርቅ ወረዳ ቤተክህነት ስር በአደጋት ቀበሌ ውስጥ የሚገኘው የምዕራፈ ቅዱሳን አፅሐራራ ቅዱስ ጊዮርጊስ አንድነት ገዳም በእናታችን ቅድስት አመተ ክርስቶስ በ14ኛዉ ክፍለ ዘመን የተመሠረተ ታላቅ እና ታምራዊ ገዳም ሲሆን በጊዜ ብዛት የድሮው ቤተክርስቲያን ፈርሶብናል። ጣራዉን ለማደስ አስቸኳይ ነዉና ከውጭም ከዉስጥም ያላችሁ ወገኖቻችን በሰማዕቱ በቅዱስ ጊዮርጊስ ስም የአቅማችሁን በማገዝ ከበረከቱ እንድትሳተፉ እንለምናችዋለን‼️
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ - 1000331624334
☎️ 0934654964 ወይም 0918532706
ለብዙዎች እንዲዳረስ እባካችሁ ሼር አድርጉት‼️

Address


Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethio Media Center posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

  • Want your business to be the top-listed Media Company?

Share