Amhara Today

Amhara Today Peace for Amhara people

ይህ ህዝብ መናቅ ነዉ።ብርቱካን  ተመስገንን ተጠቅማችሁ የሰራችሁትና በአደባባይ የተዋረዳችሁበትን አሳፋሪ ድርጊት ማን ይረሳል።ዛሬ ነፍጥ አንግባ ጫካ በመግባት እንድትታኮስ በሆይሆይታ እና በሞ...
16/10/2025

ይህ ህዝብ መናቅ ነዉ።

ብርቱካን ተመስገንን ተጠቅማችሁ የሰራችሁትና በአደባባይ የተዋረዳችሁበትን አሳፋሪ ድርጊት ማን ይረሳል።

ዛሬ ነፍጥ አንግባ ጫካ በመግባት እንድትታኮስ በሆይሆይታ እና በሞቅታ አስገብታችሁ ያስገደላችሗትን ወጣት ነፍስ እናንተን ትወቅሳለች።

አዳዲስ ትርክት እየፈጠራችሁ ፕሮፓጋንዳ ማስተጋባት በእዉነት ህዝቡን መናቅ ነዉ።

መነሻ እና መዳረሻ የሌለዉ አላማቢስ ግጭት በመፍጠር ህዝቡን በማጎሳቆልና ወጣቱን በማስጨረስ እመኑኝ ጊዜዉ ሲደርስ ትጠየቃላችሁ።

ሲዋጉ ታጋይ ሲደመሰሱ ንጹሀን!ሰላም የሚጎረብጠዉ የህዝቡ ስቃይና መከራ ምቹ መደላድል የፈጠረለት ጽንፈኛ ቡድን ከሰሞኑ አንዳንድ የአማራ ከልል  አከባቢዎች ትንኮሳ መፈጸሙን ከተለያዩ የማህበራ...
16/10/2025

ሲዋጉ ታጋይ ሲደመሰሱ ንጹሀን!

ሰላም የሚጎረብጠዉ የህዝቡ ስቃይና መከራ ምቹ መደላድል የፈጠረለት ጽንፈኛ ቡድን ከሰሞኑ አንዳንድ የአማራ ከልል አከባቢዎች ትንኮሳ መፈጸሙን ከተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ ትስስርና ገጾች ማየት ችያለሁ።

እነዚህ በአማራ ህዝብ መካከል የበቀሉ አረሞች የማይወጡትን ትግል ጀምረዉ ወጣቶችን ለማስጨረስ የሚያደርጉትን ግብግብ ሳይ ይከነክነኛል።

ይሄ ብቻ አይደለም ትንኮሳ በፈጸሙበት አካባቢ ሁሉ እንደ እሳት ራት እየነደዱ እየቀሩ ነዉ። ወጣቶችን ለዳግም እልቂት ለማዘጋጀት ግን አሟሟታቸዉን ያሽሞነሙኑታል፤ ያበጃጁታል።

ይሄ ለአማራዉ ወጣት በግልጽ ግባ እና ለኛ ጥቅምና ስልጣን እሳት ዉስጥ ተማገድ የሚል ግልጽ ጥሪ ነዉ። በርግጥም ባዶ ጩኸት መሆኑ አይደለም አዲስ ሊቀላቀላቸዉ ነባሮችም "የመንግስት ያለህ" እያሉ የተደረገላቸዉን የሰላም ጥሪ ተቀብለዉ እየጎረፉ ነዉ።

የአማራ ወጣት ሆይ ከሗላ ሁነዉ በስሜት እየነዱ ያስጨፈጭፉሃል ስትሞት የታጋይ የዳቦ ስም ያወጡልሃል ንቃ።

15/10/2025

ሕወሓት ራሱ ባደራጀዉ ሰራዊት ተቃዉሞ ገጥሞት እየታመሰ ነዉ።

ዛሬም በትግራይ ክልል ተቃውሞው ቀጥሏል።
ከመቐለ ወደ መኾኒ አላማጣ የሚወስደው መንገድ ተዘግቷል።

በተንቀሳቃሽ ምስሉ የሚየፈታዩት አርሚ 33 እና 43 አባላት ናቸው።

ወያኔ ለሌላው ኢትዮጵያዊ የቀበረችው ፈንጅ እየፈነዳ እራሷን መብላት ጀምሯል።

ተደምስሷል!በደቡብ ጎኖደር ዞን ፋርጣ ወረዳ ጋሳይ ከተማ በተወሰደ ኦፕሬሽን የፅንፈኛዉ ሻለቃ መሪ እዮብ ሙጨዬ ተደምስሷል።አንድ ሻለቃ ሲደመሰስ ምን ያህሉ አጃቢና ጀሌ እንደተደመሰሰ መገመት ...
11/10/2025

ተደምስሷል!

በደቡብ ጎኖደር ዞን ፋርጣ ወረዳ ጋሳይ ከተማ በተወሰደ ኦፕሬሽን የፅንፈኛዉ ሻለቃ መሪ እዮብ ሙጨዬ ተደምስሷል።

አንድ ሻለቃ ሲደመሰስ ምን ያህሉ አጃቢና ጀሌ እንደተደመሰሰ መገመት ቀላል ነዉ።

የተፈናቀሉ ወገኖች ወደ ቀያቸው ተመልሰው እንዲኖሩ ለመቀበል ዝግጁ ነንከወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን የተፈናቀሉ ወገኖች ወደ ቀያቸው ተመልሰው ኑሯቸውን እንዲቀጥሉ ለማድረግ ዝግጁ መሆናቸው...
09/10/2025

የተፈናቀሉ ወገኖች ወደ ቀያቸው ተመልሰው እንዲኖሩ ለመቀበል ዝግጁ ነን

ከወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን የተፈናቀሉ ወገኖች ወደ ቀያቸው ተመልሰው ኑሯቸውን እንዲቀጥሉ ለማድረግ ዝግጁ መሆናቸውን የወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን ከፍተኛ አመራሮች ገለጹ።

የወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አሸተ ደምለው እና የወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን ምክትል ዋና አስተዳዳሪና የሰላምና ፀጥታ መምሪያ ኃላፊ ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ በሰጡት ማብራሪያ፤ በሰሜኑ ጦርነት ወቅት ከዞኑ የተፈናቀሉ ወገኖች ወደ አካባቢያቸው እንዲመለሱና ሰላማዊ ኑሯቸውን እንዲቀጥሉ እየተደረገ ነው ብለዋል።

የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አሸተ ከዞኑ የተፈናቀሉና ያልተመለሱ ወገኖች ወደ ቀያቸው ተመልሰው ሰላማዊ ኑሯቸውን እንዲቀጥሉ እንደሚቀበሏቸው ገልጸዋል።

በአሁኑ ወቅት በወልቃይት ጠገዴ የሚኖሩ በርካታ የትግራይ ተወላጆች ሰላማዊ ህይወታቸውን እየመሩ እንደሚገኙ ጠቅሰው፤ የአማራና የትግራይ ህዝብ ለዘመናት አብረው የኖሩ መሆናቸውን ተናግረዋል።

የሰሜኑ ጦርነት በተከሰተበት ወቅት ብዙዎች በኖሩበት አካባቢ እየኖሩ መሆኑን አስታውሰው፤ በወቅቱ ተደናግጠው ከሄዱት መካከል ደግሞ ወደ ዞኑ ተመልሰው ሰላማዊ ህይወት መምራት የጀመሩ መኖራቸውን ተናግረዋል።

ምክትል ዋና አስተዳዳሪው ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ በበኩላቸው እንደገለጹት ከዞኑ የተፈናቀሉ ወገኖች ወደ አካባቢያቸው መመለስ አለባቸው።

በአካባቢው ሰላም ለመፍጠር አንድን ማህበረሰብ አፈናቅለህ አንዱን ማኖር የሚቻል አይመስለኝም ብለዋል።

ምክትል ዋና አስተዳዳሪው፤ የተፈናቃዮች ጉዳይ በሰላማዊ መንገድ እልባት እንዲያገኝ በሁሉም በኩል ቁርጠኝነት እንደሚያስፈልግም አብራርተዋል።

መንግስት ተፈናቃዮች ወደ ቀያቸው እንዲመለሱ ለማድረግ በተከታታይ የተለያዩ ተግባራትን ሲያከናውንና ጥረቶች ሲያደርግ መቆየቱ ይታወቃል።

09/10/2025

የአማራ ህዝብ ማንነቴን አትንኩ፤ የአባቶቼን አጽመ ርስት አትንጠቁኝ አለ እንጅ ብቻየን ልብላ አላለም። የሰዉም ሃብት በግፍ ልዉሰድ አላለም ሃቁ ይሄዉ ነዉ።

ኑ አብረን በትናንት የነበረ ማንነታችን አብረን እንኑር እያለ ነዉ።

👉

08/10/2025

ወዲህም ሗላቀር ወዲያም ባህላዊ ጀነራሎቾ!

በስምህ ሲጠራህ አቤት ማለትህ ተፈጥሯዊ ነዉ። ከሰሞኑ የጽንፈኛዉ የማህበራዊ ሚዲያ ክንፍ ያሰማራቸዉ ባንዳዎችና ያዘዙን ባዳዎች ባደባባይ ስማቸዉ ከእነ ግብራቸው ተነገረ ብለዉ "ታመምን" እያሉ...
07/10/2025

በስምህ ሲጠራህ አቤት ማለትህ ተፈጥሯዊ ነዉ።

ከሰሞኑ የጽንፈኛዉ የማህበራዊ ሚዲያ ክንፍ ያሰማራቸዉ ባንዳዎችና ያዘዙን ባዳዎች ባደባባይ ስማቸዉ ከእነ ግብራቸው ተነገረ ብለዉ "ታመምን" እያሉ ነዉ።

መሪ እንደመሪ ሌባን ሌባ፣ ባንዳን ባንዳ፣ ባዳን ባዳ ማለት ካልቻለ ምኑን መሪ ሆነዉ።

የኢፌዴሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህም ያደረጉት ለህዝባቸዉ የሚመጥነዉን እንጅ ለአጥፊዎች የሚጠቅመዉን አይደለም።

ወዳጀ ሰዉየዉ ንግግራቸዉም ሆነ ግብራቸዉ ለባንዳና ለባዳ አይመችም።

ለዚህ ነዉ ስታዩት የሚያዞራችሁ፣ ስተሰሙት የሚያማችሁ!

07/10/2025

ቃል በተግባር!

ለዉቢቷ ባህርዳር!

ገጥሞ የምን ለቅሶ!የአማራን ህዝብ ሊዘርፍ፣ ሊሰርቅ፣ ሊያግትና ልጆቹን ከትምህርት ገበታ በመስተጓጐል ስልጣን ላይ ሊወጣ ጫካ የገባ ጽንፈኛ ቡድን ግብሬን በአደባባይ ለህዝብ አጋለጡብኝ በሚል ...
07/10/2025

ገጥሞ የምን ለቅሶ!

የአማራን ህዝብ ሊዘርፍ፣ ሊሰርቅ፣ ሊያግትና ልጆቹን ከትምህርት ገበታ በመስተጓጐል ስልጣን ላይ ሊወጣ ጫካ የገባ ጽንፈኛ ቡድን ግብሬን በአደባባይ ለህዝብ አጋለጡብኝ በሚል በየሚዲያው ሲያለቅስ እያየን ነዉ።

ለነገሩ አፍንጫ ሲመታ አይን ያለቅሳል እንዲሉ ዘዉ ብለዉ ፎቶ ለመነሳት በገቡበት አካባቢ ሁሉ መዉጣት ህልም ሁኖባቸዉ እንደጉም ተነዉ እየቀሩ ስለሆነ የዛ ስሜት እንደሚሆን አልጠራጠርም።

የጽንፈኛዉ የሚዲያ ክንፍ የሆኑት ሙሉጌታ አንበርብርና አሳየ ደርቤ የተባሉ ቅጥረኞች የኢፌዴሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ለህዝብ ግብራችን አጋለጠ በሚል "ታመን አደርን" ሲሉ አይቸ ሞኝ ባያፍር የሞኝ ዘመድ ያፍር እንዲሉ አፍሬያለሁ።

ሰዉየዉ እንደሆኑ ቆፍጣና ታታሪ መሪ ናቸዉ፤ ብረትን እንደጋለ መቀጥቀጥ ይችሉበታል።

አንተ የተለያየ የዳቦ ስም እየሰጠህ የሚመራዉን ህዝብ ለጉስቁልና እየዳረክ የመላእክት ስም ያዉጣልህ ወይ!?

እኛም እንላለን!
👉ሌባማ ሌባ ነዉ!
ባንዳም ባንዳ ነዉ!
ባዳም ባዳ ነዉ!
ጽንፈኛም ያዉ ጽንፈኛ ነዉ! 👈

06/10/2025

ያሳፍራል!

የአማራ ህዝብ ለፅንፈኛ ወጥመድ አይመችም!የሻብያን ተልእኮ አዝሎ የሚንገዳገዳው የአንድ ጀምበር እድሜ የቀረዉ  ጽንፈኛ ቡድን ንፁሃንን በመረሸን በሕዝብ መካከል መለያየት ሊሚፈጥር ቢሞክርም በ...
04/10/2025

የአማራ ህዝብ ለፅንፈኛ ወጥመድ አይመችም!

የሻብያን ተልእኮ አዝሎ የሚንገዳገዳው የአንድ ጀምበር እድሜ የቀረዉ ጽንፈኛ ቡድን ንፁሃንን በመረሸን በሕዝብ መካከል መለያየት ሊሚፈጥር ቢሞክርም በህዝቡ የነበረ ፍቅር ከሽፎበታል።

የተጋመደን ህዝብ የተዋረዶ ጽንፈኛ አይነጣጥለውም። በተግባር አንድነት ህይወታችን ነውና ይህን ጽንፈኛ ቡድን በጋራ እንታገለዋለን።

Address


Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Amhara Today posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

  • Want your business to be the top-listed Media Company?

Share