Amhara Today

Amhara Today Peace for Amhara people

የሽንፈት መጨረሻ_ ህዝብን በማገት የሚገኝ ድል! ​የህዝብን ደህንነት ለመጠበቅ ሲባል እየተባለ የሚነገረው የተለመደው የሽንገላ ፖለቲካ አሁን ለአማራ ህዝብ አይሰራም። እነ   ህዝብ ከቦታ ቦታ...
28/05/2026

የሽንፈት መጨረሻ_ ህዝብን በማገት የሚገኝ ድል!

​የህዝብን ደህንነት ለመጠበቅ ሲባል እየተባለ የሚነገረው የተለመደው የሽንገላ ፖለቲካ አሁን ለአማራ ህዝብ አይሰራም።

እነ ህዝብ ከቦታ ቦታ እንዳይንቀሳቀስ፣ ነጋዴው እንዳይነግድ፣ አርሶ አደሩ የህልውናው መሰረት የሆነውን ዘርና ማዳበሪያ እንዳያገኝ መንገድ ዘግተናል ማለታቸዉን ከመግጫቸዉ አነበብኩ። ይህ የማይካካ የቁልቁት ጉዞ ህዝብን የመጠበቅ ሳይሆን ህዝብን የማጥፋት፣ የማስራብና የማሰቃየት የለየለት የጭካኔ ስትራቴጂ ነው።

​ማህበራዊ ሚዲያ ላይ ብቻ በመጮህና የሀሰት ፕሮፓጋንዳ በመርጨት የፖለቲካ ትርፍ ማግኘት አይቻልም። እውነታው ያለው መሬት ላይ ነው! የክልሉ ህዝብ በነቂስ ወጥቶ ለብልጽግና ፓርቲ ያለውን ደጋፍ በሰልፍ በግልጽ እያሳየ ባለበት በዚህ ወቅት፣ በጫካም ሆነ በሃሳብ ፖለቲካ የተሸነፈ ቡድን መሆኑን ህዝቡ አዉቆት ያደረ ሀቅ ነዉ።

​ዛሬ ነገሩ ሁሉ ከቁጥጥራችሁና ከአቅማችሁ ውጪ ሆኗል። ህዝብ የእናንተን የጥፋት መንገድ ውድቅ አድርጎ ከቁጥጥራችሁ ወጥቷል። አለማቀፉ ማህበረሰብም ቢሆን የት እንዳላችሁና ምን እንደምትሰሩ እንኳን አያውቅም። የእለት ጉርስ የሚያደርሳችሁ ዲያስፖራም አቅማችሁን አዉቆታል።

​ በማህበራዊ ሚዲያ ጫጫታ መንግስት መሆን አይቻልም! ህዝብን በማስራብ የሚመጣ ለውጥም የለም!

መረጃ! ከሰሞኑ በማዕከላዊ ጎንደር ዞን በነባሩ ጭልጋ ወረዳ በኳክ ገንበልዋ ቀበሌ በአካባቢው ይንቀሳቀሱ በነበሩ ታጣቂዎች ላይ በጸጥታ ሀይሉ ክትትልና ኦፕሬሽን ተደርጎ ነበር። በዚህ ኦፕሬሽን...
19/05/2026

መረጃ!

ከሰሞኑ በማዕከላዊ ጎንደር ዞን በነባሩ ጭልጋ ወረዳ በኳክ ገንበልዋ ቀበሌ በአካባቢው ይንቀሳቀሱ በነበሩ ታጣቂዎች ላይ በጸጥታ ሀይሉ ክትትልና ኦፕሬሽን ተደርጎ ነበር።

በዚህ ኦፕሬሽንም አንድ አባላቸዉ እጅ እንዲሰጥ በማድረግ ታጣቂዎች ይጠቀሙቀት የነበሩ በርካታ የስልክ ቀፎዎችና ሲም ካርዶች እንዲሁም የብር ኖቶች ተይዘዋል።

እኔ ምለዉ እጅ ወደላይ ከማለት እና በክብር የተደረገን የሰላም ጥሪ መቀበል ልዩነቱ አይገባቸዉም እንዴ?

ቅዱስ ቃሉን ለርኩስ ዓላማ 🤝 የጽንፈኞች የማታለያ ስልት! ​ጽንፈኛ ቡድኖች የመጽሐፍ ቅዱስን ጥቅሶች ለራሳቸው እኩይ ዓላማና ለጥፋት ድርጊታቸው ማስፈጸሚያ የሚጠቀሙባቸው በርካታ ስነ-ልቦናዊ፣...
15/05/2026

ቅዱስ ቃሉን ለርኩስ ዓላማ 🤝 የጽንፈኞች የማታለያ ስልት!

​ጽንፈኛ ቡድኖች የመጽሐፍ ቅዱስን ጥቅሶች ለራሳቸው እኩይ ዓላማና ለጥፋት ድርጊታቸው ማስፈጸሚያ የሚጠቀሙባቸው በርካታ ስነ-ልቦናዊ፣ ፖለቲካዊና ስልታዊ ምክንያቶች አሉ። ይህ ድርጊት በአብዛኛው የሃይማኖት ጽሑፎችን ለራስ ፍላጎት የማጣመም (Religious Manipulation) ስልት ሲሆን፤ ጽንፈኞች በስፋት የሚገለገሉበት አደገኛ መሣሪያ ነው።

​ ጽንፈኞች የራሳቸውን ሰብአዊ፣ ፖለቲካዊ ወይም ጥላቻን ያዘሉ አጀንዳዎች ተቀባይነት ለማስገኘት ሲሉ የራሳቸውን ቃል ሳይሆን የእግዚአብሔርን ቃል እየተናገሩ እንደሆነ አድርገው ያቀርባሉ። ይህ ሲሆን ተከታዮቻቸው የሚፈጽሙትን ጥፋት እንደ ወንጀል ሳይሆን እንደ ቅዱስ ግዴታ እንዲቆጥሩት ያደርጋቸዋል።

ጥቅሶችን ከዐውዳቸው ነጥሎ ማውጣት (Proof-texting) ዋነኛው ስልታቸው ነው። መጽሀፍ ቅዱስ ውስጥ ያሉ የተወሰኑ የታሪክ ጦርነቶችንና ፍርዶችን በመጥቀስ፣ ዛሬ ባለው ዘመን በሰዎች ላይ ጥቃት ወይም ጥላቻ ለማድረስ እንደ ፍቃድና መመሪያ አድርገው ያቀርቡታል።

ሃይማኖት ከሰዎች ጥልቅ ስሜትና ማንነት ጋር የተቆራኘ በመሆኑ፣ ጽንፈኞች የሰዎችን ንጹህ የሃይማኖት ፍቅርና ቅንነት ለክፉ ዓላማቸው መሣሪያ ያደርጉታል። እምነታችሁ አደጋ ላይ ነው ወይም ይህንን ካላደረጋችሁ ኃጢአት ይሆንባችኋል በማለት ፍርሃትና ቁጣን ይዘራሉ። ይህም ሰዎችን በቀላሉ ለመሪነታቸው ተገዢ ለማድረግና ለኃይለኛ ተግባር ለማሰለፍ ይረዳቸዋል።

ጽንፈኛ ቡድኖች መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ያሉትን የበረከትና የጽድቅ ክፍሎች ለራሳቸው ብቻ በመስጠት፤ የፍርድና የርግማን ክፍሎችን ደግሞ እነሱ ለሚጠሏቸው ወይም ለሚቃወሟቸው ወገኖች ያደላሉ። በዚህ መንገድ እኛ የእግዚአብሔር ሕዝቦች ነን፤ ተቃዋሚዎቻችን ደግሞ የክፉ ወገኖች ናቸው የሚል የተሳሳተ ትረካ በመፍጠር በሰዎች መካከል ግጭትና መለያየትን ይፈጥራሉ።

የሰው ልጅ በተፈጥሮው ክፉ ነገር ሲያደርግ ሕሊናው ይወቅሰዋል። ጽንፈኞች ግን የራሳቸውን ሕሊና ለመሸወድና ተከታዮቻቸውም ያለ ምንም የሕሊና ወቀሳ ጭካኔ የተሞላበት እርምጃ እንዲወስዱ ለማድረግ የመጽሐፍ ቅዱስን ጥቅሶች እንደ ማደንዘዣ ወይም ማጽደቂያ ይጠቀሙባቸዋል።

​ባጠቃላይ ጽንፈኞች ጥቅሶችን የሚጠቀሙት የእግዚአብሔርን እውነት ለመፈለግ ወይም መጽሐፍ ቅዱስ የሚያስተምረውን የፍቅር፣ የሰላምና የወንድማማችነት መልእክት ለመከተል አይደለም። ይልቁኑ ቀድመው የወሰኑትን ክፉ አጀንዳ ተቀባይነት ለማስገኘትና በሰዎች ዘንድ ቅቡልነት ለመግዛት ጥቅሶችን እንደ መሸፈኛ መሣሪያ (Pretext) ነው የሚጠቀሙባቸው።

በመሆኑም፣ እንዲህ ባሉ ጽንፈኛ ትርጓሜዎች እንዳንታለል የሃይማኖት ጽሑፎችን አጠቃላይ ይዘት፣ መንፈስና ታሪካዊ ዐውድ በጥንቃቄ ማስተዋልና ማስተማር ይገባል።

የእነዘመነ ካሴ እና በድኑ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅስም ማንን ለማታለል እንደሆነ ግልጽ ነዉ!

Selamawit Yohans

09/05/2026

የትግራይ ወጣት ይናገራል!

"የለመደች ጦጣ ሁልጊዜ-----" አለ ያገሬ ሰው!!!!ሴረኞች ትናንት ለጥፋት የሄዱበትን የክህደት መንገድ ተከትለው ዛሬም ኢትዮጵያን ለማድማት እየተጠራሩ ይታያሉ።ነገሩ እንዲህ ነው:-በ1980...
07/05/2026

"የለመደች ጦጣ ሁልጊዜ-----" አለ ያገሬ ሰው!!!!

ሴረኞች ትናንት ለጥፋት የሄዱበትን የክህደት መንገድ ተከትለው ዛሬም ኢትዮጵያን ለማድማት እየተጠራሩ ይታያሉ።

ነገሩ እንዲህ ነው:-
በ1980ዎቹ መጀመሪያ ላይ ሻብያ አንድ የጥፋት ታክቲክ በደርግ መንግስት ላይ ፈፅሞ ነበር።

የኢትዮጵያን ወድ ሃብት ምፅዋ ወደብን ለማጥቃትና ለመያዝ ሲዘጋጅ በታሪክ ለመጀሪያ ጊዜ በሜካናይዝድ የታገዘ ማጥቃት በምዕራብ ኢትዮጵያ በአሶሳ ቡኩል ነበር የፈፀመው።

በዚያ አቅጣጫ በወቅቱ "ሻብያ ፣ ወያኔ እና የሱዳኑ አልበሺር" ነበር የተሰለፉት።

ከዚህኛው ወገን ደግሞ ደርግና ከደቡብ ሱዳን SPLM ነበሩ።

ደርጉ በድርቅና ብቻ በዚህኛው መጡብኝ ብሎ ትኩረቱን ወደ ቤንሻንጉል አቅጣጫ ሲያዞርና ኃይሉን ሲያንቀሳቅስ እነድመት ሻዕቢያ በፍጥነት ሃይላቸውን ወደሰሜን በመመለስ መልሰው ምፅዋን አጠቁ።

የዚህ ሰሞኗ የነአልቡርሃን የክስ ዳርዳርታና በኩርሙክ አቅጣጫ ሀይል መጨመር ፣ የግብፆች ማቀሳሰር ፣ የደብረፂዮን አንጃ ከአልቡርሃንና ሻዕቢያ እግር ስር ሱክሱክ ማለት አሁንም የኛን ትኩረት ለማዛባት የተሸረበች ሴራ መሆኗ ግልፅ ናት።

እናማ ወገን "እኛም ነቅተናል ጉድጓድ ምሰናል" ያለችው ማን ነበረች እባካችሁ!!!!!?

በትግራይ ህዝብ ላይ የተደቀነው የዳግም መከራ ደመና ​በጦርነት ማዕበል ውስጥ አልፎ ገና ትንፋሽ ያልዘራው የትግራይ ህዝብ፣ ዛሬም በገዛ ልጆቹ እብሪትና የሥልጣን ጥማት ምክንያት ሌላ የግጭት ...
05/05/2026

በትግራይ ህዝብ ላይ የተደቀነው የዳግም መከራ ደመና

​በጦርነት ማዕበል ውስጥ አልፎ ገና ትንፋሽ ያልዘራው የትግራይ ህዝብ፣ ዛሬም በገዛ ልጆቹ እብሪትና የሥልጣን ጥማት ምክንያት ሌላ የግጭት አውድማ አፋፍ ላይ ቆሟል።

ያየግጭት አንቴና የሆነዉ ደብረጺዮን እና ቡድኑ ዳግም በትግራይ ህዝብ አናት ላይ ተተክሏል። ይህ ቡድን ከትናንት ጥፋቱ ያልተማረ፣ በትግራይ ወጣቶች ደም የሥልጣን መንበሩን ለማደላደል የሚተጋ እና የእናቶችን እምባ እንደ ውሃ የሚቆጥር ጨካኝ ስብስብ መሆኑን ዳግም እያሳየ ይገኛል።

​ይህ ነፍሰ-በላ ስብስብ ለሥልጣኑ ማቆያና ለፈጸማቸው መጠነ-ሰፊ የሙስና እና የስርቆት ወንጀሎች መሸሸጊያ ይሆነው ዘንድ የትግራይን ወጣቶች እንደ ማገዶ ለመጠቀም በመዘጋጀት ላይ ነው። ለዚህ ቡድን ጦርነት ማለት የችግር መፍቻ ሳይሆን፣ የጥፋት አጀንዳውን ማስፈጸሚያና ህዝቡን በአስፈሪ ሁኔታ ውስጥ አስገብቶ የመግዣ ስልቱ ነው።

​በሺዎች የሚቆጠሩ ወጣቶችን ደም በከንቱ ያፈሰሰው ይህ ቡድን፣ አሁንም ተጨማሪ ደም ለመገበር አሰፍስፏል። ልጆቻቸውን በሞት ያጡ፣ ያለ ጧሪና ቀባሪ የቀሩ እናቶችን ቁስል ከመጠገን ይልቅ፣ በቁስላቸው ላይ እንጨት እየሰደደ ይገኛል።

የትግራይ ህዝብ እንደ ከዚህ ቀደሙ ለዚህ አሸባሪና የእፉኝት ስብስብ እጁን ይሰጣል ተብሎ ባይታመንም፤ አሁን ያለው ሁኔታ ግን ከፍተኛ ጥንቃቄን ይጠይቃል።

ያለ ሥልጣን መኖር የማይችለው፣ በህዝብ ሰላም ላይ ቁማር የሚጫወተው ይህ ቡድን ሊያደርስ የሚችለው መከራና ስቃይ በቀላሉ የሚታይ አይደለም።

​ስለሆነም፣ የትግራይ ህዝብና በተለይም ወጣቱ ከዚህ አጥፊ ስብስብ እኩይ ሴራ ራሱን ሊጠብቅ ይገባል። ለዚህ ስብስብ የስልጣን ጥማት ለማርካት ሲባል የትግራይ ህዝብ የደም ዋጋ እንዲከፍል ሊፈቀድለት አይገባም።

ፅንፈኛው ቡድን በ18 ንጹሃን ዜጎች ላይ ዘግናኝ የጅምላ ጭፍጨፋ ፈፀመ፤ ​የአማራን ሕዝብ ስቃይ ለማራዘም መሬት ላይ የሌለን ሀቅ በማናፈስ የሀሰት ፕሮፖጋንዳ ሲነዛ የቆየው ፅንፈኛ ቡድን በን...
04/05/2026

ፅንፈኛው ቡድን በ18 ንጹሃን ዜጎች ላይ ዘግናኝ የጅምላ ጭፍጨፋ ፈፀመ፤

​የአማራን ሕዝብ ስቃይ ለማራዘም መሬት ላይ የሌለን ሀቅ በማናፈስ የሀሰት ፕሮፖጋንዳ ሲነዛ የቆየው ፅንፈኛ ቡድን በንጹሃን ዜጎች ላይ የሚፈፅመውን ግፍ ቀጥሎበታል።

​በ25/08/2018 ዓ.ም ከባህር ዳር ወደ ጃዊ ይጓዙ የነበሩ 18 ንጹሃን ዜጎችን የጫነች የሕዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪ (ሃይሩፍ) "ጅግራ ውሃ" በተባለ ስፍራ በፅንፈኛው ኃይል ተዋጊዎች ተጠልፋለች።

ራሱን ፋኖ ብሎ የሚጠራው ይህ ቡድን በውስጧ የነበሩትን 18 መንገደኞች በሙሉ በአሰቃቂ ሁኔታ ረሽኗቸዋል።

​ቡድኑ ይህንን ዘግናኝ ግድያ ፈፅሞ እያለ በተለመደ የማታለል ስልቱ የሰራዉን ግፍ ለመሸፈንና ለወንጀሉ ሌላ ተጠያቁ ለመፈለግ ጥረት እያደረገ ይገኛል።

ሆኖም የአማራ ህዝብ አርቆ አስተዋይነት የቡድኑን ማንነት በማጋለጥ ድርጊቱን ማውገዝ እንዲጀምር አድርጎታል። ይህ ትውልደ-በላ ድርጊት በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚያስጠይቅ የሽብር ተግባር በመሆኑ፣ መላው ሕዝብ ይህን እኩይ ድርጊት እና ጽንፈኛዉን ሊያወግዘው ይገባል።

​ለሟች ቤተሰቦች መጽናናትን ለሟቾችም እረፍተ ነፍስን እንመኛለን።

የአገውን ሕዝብ ለህወሃት ተልእኮ እያደማ የሚገኘው ቡድን-አዴንአዴን የሰላም አመራጩን ወደ ጎን በመተው በፃግብጂ ወረዳ ላይ ተደጋጋሚ ትንኮሳ እየፈፀመ ይገኛል።በፃግብጂ ወረዳ አራት ቀበሌዎች ...
01/05/2026

የአገውን ሕዝብ ለህወሃት ተልእኮ እያደማ የሚገኘው ቡድን-አዴን

አዴን የሰላም አመራጩን ወደ ጎን በመተው በፃግብጂ ወረዳ ላይ ተደጋጋሚ ትንኮሳ እየፈፀመ ይገኛል።
በፃግብጂ ወረዳ አራት ቀበሌዎች ላይ የሚንቀሳቀሰው እራሱን አዴን ብሎ የሚጠራው ሀይል በሰላማዊ መንገድ የፖለቲካ ፍላጎትን እንዲጠይቅና ቀጠናው ጦርነት እና ግጭት እንዳይኖር ተስማምቶ ለ4 አመታት ያክል ትጥቅ አወርዶ ተሃድሶ ይወስዳል እየተባለ ሲጠበቅ የነበረ መሆኑ ይታወቃል።

ይሁን እንጂ ላኪው ህውሃት ተኩስ ሲል የሚተኩስ አቁም ሲል የሚያቆም በመሆኑ ምክንያት በተደጋጋሚ ጦርነት ሲጎስም ይታያል ። ከሰሞኑም የህወሃት እብደት ተጋቦቱ ደርሶት እየተወራጨ ይገኛል።

ይባስ ብሎ ደግሞ በ22/08/2018 ዓ.ም ደግሞ ከምሽቱ 5 ሰዓት ላይ የተለያዩ ትጥቆችን ይዞ 02 ቀበሌ ሽምኻይሉ በሚባል መንደር ላይ በመግባት ሲቪል ግለሰብ አግኝቶ ደብድቦ የቀደመ ግብሩን ባለመርሳት 44ሺ ብር፣ ዱቄት እና በርበሬ ሳይቀር ዘርፎ ሰላም አስከባሪ ሀይል ወደ አካባቢው ሲመጣበት ተመልሶ ፈርጥጧል።

ይህ የባንዳነትና ፀረ ሰላምነት እንቅስቃሴ በራስ ወገን ላይ የሚፈፀም ነውረኝነት ነው። ቡድኑ ከህወሃት ተልዕኮ እየተቀበለ እና ከሌሎችም የጥፋት ኃይሎች ጋር እየተጣመረ ሲንቀሳቀስ ተደጋጋሚ ቢመከርም ከነውሩ አልተመለሰም።

አሁንም ፀብ አጫሪነት አቁማችሁ በሰላማዊ መንገድ እንድትንቀሳቀሱ ስንመክር ከህወሃት ተልእኮ በመውሰድ በጥፋት መሰለፉ ግን ውጤቱ የከፋ እንደሚሆን እንድታጤኑት በመንገርም ጭምር ነው።

ምርጫ ለምን የጽንፈኞች ህልውና ጠንቅ ሆነ? ጽንፈኝነት በባሕርዩ እኔ ብቻ ትክክል ነኝ በሚል ግትር አስተሳሰብ ላይ የተመሠረተ ነው። ምርጫ ደግሞ የተለያዩ አማራጮች የሚቀርቡበትና የሕዝብ ውሳ...
27/04/2026

ምርጫ ለምን የጽንፈኞች ህልውና ጠንቅ ሆነ?

ጽንፈኝነት በባሕርዩ እኔ ብቻ ትክክል ነኝ በሚል ግትር አስተሳሰብ ላይ የተመሠረተ ነው። ምርጫ ደግሞ የተለያዩ አማራጮች የሚቀርቡበትና የሕዝብ ውሳኔ የሚከበርበት ሂደት በመሆኑ ጽንፈኞች የራሳቸውን የበላይነት ሊያሳጣኝ ይችላል በሚል ስጋት ጥላቻ ያሳድራሉ።

​ጽንፈኞች አብዛኛውን ጊዜ ከውይይትና ከድርድር ይልቅ ኃይልን ወይም ጫናን እንደ መፍትሔ ይመርጣሉ። በመሆኑም በሰላማዊ መንገድ በሚካሄድ የምርጫ ሂደት ከማመን ይልቅ ሂደቱን የማጠልሸትና የሕዝብን ተስፋ የማስቆረጥ ሥራ ይሠራሉ።

​ምርጫ የብዙኃነት መገለጫ ነው። ጽንፈኞች ግን ከእነሱ አስተሳሰብ ውጭ ያሉ ወገኖችን እንደ ጠላት ስለሚፈርጁ እነዚህ ወገኖች በምርጫ ተሳትፈው ድምፅ ሊያገኙ የሚችሉበትን ዕድል ለመዝጋት ይጥራሉ።

​ለጽንፈኞች ምርጫ ሰላምን የሚያሰፍን ከሆነ ለእንቅስቃሴያቸው ምቹ አይሆንም። የእነሱ ህልውና የሚመሠረተው በብጥብጥና በሁከት ውስጥ በመሆኑ ምርጫን እንደ ትርጉም የለሽ ወይም አድሏዊ አድርጎ በመሳል ሕዝቡ በምርጫው ላይ አመጽ እንዲቀሰቅስ ይቀሰቅሳሉ። አመጹ ካልተሳካላቸዉ በምርጫዉ ላይ የሚሳተፍ ህዝብ ላይ ይዝታሉ።

​ባጠቃላይ የጽንፈኞች የምርጫ ጥላቻ የሚመነጨው ለሕዝብ ድምፅ ካላቸው ንቀትና የራሳቸውን ፍላጎት በኃይል ለመጫን ካላቸው ጉልበተኛ ፍላጎት ነው።

ህወሃቶች የጥፋትና መነጠላቸውን ሒሳብ ለመሸፈን የቱንም ጩኸት በማንም በኩል ብታስተጋባ ሰሚ የለምየሕወሃት ቡድን በትግራይ ሕዝብ ስም እያስመሰለ ሲበዘብዝ ኖሮ አሁን ከሁሉ ሲተፋ ሕዝብን አነሳ...
25/04/2026

ህወሃቶች የጥፋትና መነጠላቸውን ሒሳብ ለመሸፈን የቱንም ጩኸት በማንም በኩል ብታስተጋባ ሰሚ የለም

የሕወሃት ቡድን በትግራይ ሕዝብ ስም እያስመሰለ ሲበዘብዝ ኖሮ አሁን ከሁሉ ሲተፋ ሕዝብን አነሳሳበታለሁ ወዳለው የፈጠራ ወሬ ተመልሷል።

የወልቃይት ጠገዴ ማህበረሰብ የዘር ማጥፋትና የማንነት ገፈፋን ጨምሮ ተደራራቢ ግፍ የተሰራበት ሲሆን ዛሬም ማንነቱን አስከብሮ ከትግራይ ተወላጅ ንፁሃን ዜጎች ጋርም ተባብሮ እየኖረ ይገኛል። ይህ ሁኔታ ከሁሉ የነጠላት ህወሃት የትግራይን ሕዝብ ለጦርነት ለማነሳሳት በሂውማን ራይትስ በኩል ሰርገው በገቡ አባሎቿ የሀሰት መረጃ አውጥታ እየጮኸች ነው። ጩኸቱ ግን መሬት ላይ ያለውን እውነት አይቀይረውም።

መሬት ላይ ያለ የግፍ መዝገባችሁን በፈጠራ ጩኸት አትሽሩትም። በስሙ ስትበድሉና ስትዘርፉ ኖራችሁ የትግራይን ሕዝብ ድግም ወደ ጦርነት እሳተ ማስገባትም የምትችሉ አይመስለንም። የሚገባም ካለ የህወሃት ደጋፊና የወንጀል ማህበር አባል ብቻ ይሆናል።

Address


Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Amhara Today posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

  • Want your business to be the top-listed Media Company?

Share