Fetan Zena - ፈጣን ዜና

Fetan Zena - ፈጣን ዜና Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Fetan Zena - ፈጣን ዜና, Dallas, TX.
(1)

09/01/2025

ጥያቄ?

አለሌ ምን ማለት ነው?

08/27/2025

"ጊዚያዊ አስተዳደሩ የማያውቀው ተፈናቃዮች ለመመለስ ያለመ ድብቅ አካሄድ ተቀባይነት የለውም" - ፕሬዜዳንት ታደሰ ወረደ (ሌ/ጀነራል)

ከመኪና አደጋ የተረፈው የተዋናይ ሄኖክ ድንቁ መልክት ድንግል ማርያም ከልጇ ጋር ከአስከፊዉ የመኪና አደጋ አትርፈዉኝ ድጋሚ የመኖር እድል ሰለሰጡኝ አመሰግናለሁ ብሏል ፍጣሪ እንኳን እተረፈህ ...
07/20/2025

ከመኪና አደጋ የተረፈው የተዋናይ ሄኖክ ድንቁ መልክት

ድንግል ማርያም ከልጇ ጋር ከአስከፊዉ የመኪና አደጋ አትርፈዉኝ ድጋሚ የመኖር እድል ሰለሰጡኝ አመሰግናለሁ ብሏል

ፍጣሪ እንኳን እተረፈህ በሉት

ሰበርየጋሞ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት የአለልኝ ባለቤት እና የባሌቤቱ እህት ባልን በተጨዋቹ ሞት ጥፋተኛ ናቸው ብሎ ወስኗል::ፍርድ ውሳኔውን ለመስማት ለከሰዓት ቀጠሮ ታይዟል::አለልኝ አዘነ ራሱ...
07/18/2025

ሰበር

የጋሞ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት የአለልኝ ባለቤት እና የባሌቤቱ እህት ባልን በተጨዋቹ ሞት ጥፋተኛ ናቸው ብሎ ወስኗል::

ፍርድ ውሳኔውን ለመስማት ለከሰዓት ቀጠሮ ታይዟል::

አለልኝ አዘነ ራሱን አጥፍቶ አልሞተም!

ሸገር ስፖርት

የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶ/ር ካሳሁን ጎፌ በሙሉ ጤንነት ላይ ናቸው! ሰኔ 15 ቀን 2017 ዓ.ም ምሽት ላይ ወደ ቤታቸው ሲመለሱ በካርል አደባባይ አካባቢ ድንገተኛ የመኪ...
06/30/2025

የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶ/ር ካሳሁን ጎፌ በሙሉ ጤንነት ላይ ናቸው!

ሰኔ 15 ቀን 2017 ዓ.ም ምሽት ላይ ወደ ቤታቸው ሲመለሱ በካርል አደባባይ አካባቢ ድንገተኛ የመኪና አደጋ ቢደርስባቸውም፣ ሚኒስትሩ ወዲያውኑ ወደ ሆስፒታል ተወስደው ተገቢውን ህክምና አግኝተዋል፡፡ አሁን በሙሉ ጤንነት ላይ ይገኛሉ። ከተወሰነ የእረፍት ጊዜ በኋላ ወደ መደበኛ ስራቸው ይመለሳሉ፡፡

በማህበራዊ ሚዲያ የተሰራጩ መሰረተ ቢስ መረጃዎችን እንዳትመኑ፣ እውነተኛውን መረጃ ለማወቅ የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱን መግለጫ ይከታተሉ፡፡

🛑 ለጥንቃቄ      በኢትዮጵያ አየር መንገድ ውስጥ በአንዱ ካፌ አንድ ዝንጅብል ሻይ 629 ብር ይሸጣል ቢባል አትከራከሩ ።ካፌው አማረ ብላችሁ  ሻይ ቡና ልበል ብላችሁ ገብታችሁ ጉድ እንዳት...
06/21/2025

🛑 ለጥንቃቄ
በኢትዮጵያ አየር መንገድ ውስጥ በአንዱ ካፌ አንድ ዝንጅብል ሻይ 629 ብር ይሸጣል ቢባል አትከራከሩ ።
ካፌው አማረ ብላችሁ ሻይ ቡና ልበል ብላችሁ ገብታችሁ ጉድ እንዳትሆኑ።

ሰናይ ቅዳሜ ሰንበት

ከነቢዩ ሲራክ
ሰኔ 14 ቀን 2017 ዓም

መልካም የአባቶች ቀን ❤️
06/15/2025

መልካም የአባቶች ቀን ❤️

የቀድሞው ጠ/ሚ ኃይለማርያም ደሳለኝ በወላይታ ግዙፍ ሎጅ ሊገነቡ ነውየቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ በወላይታ ዞን፣ በበሌ አዋሳ ከተማ ግዙፍ የቱሪስት ሎጅ ለመገንባት በይ...
06/10/2025

የቀድሞው ጠ/ሚ ኃይለማርያም ደሳለኝ በወላይታ ግዙፍ ሎጅ ሊገነቡ ነው

የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ በወላይታ ዞን፣ በበሌ አዋሳ ከተማ ግዙፍ የቱሪስት ሎጅ ለመገንባት በይፋ ማስጀመራቸው ተዘግቧል። ይህ ፕሮጀክት በ"ኃይለማርያምና ሮማን ፋውንዴሽን" አማካኝነት የሚካሄድ ሲሆን፣ ሲጠናቀቅ በአፍሪካ ደረጃ ግዙፍ ከሚባሉት የቱሪዝም መዳረሻዎች አንዱ እንደሚሆን ተገልጿል።

አቶ ኃይለማርያም በቦታው የመስክ ምልከታ ባደረጉበት ወቅት፣ ሎጁ ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ እና በቅርብ ጊዜ ውስጥ ግንባታው ተጠናቆ ለህዝብ ክፍት እንደሚሆን አስታውቀዋል። ይህ ሎጅ በቴክኖሎጂ እገዛ ዘመን ተሻጋሪ እንዲሆን ልዩ ትኩረት የሚሰጠው ሲሆን፣ ሲጠናቀቅም ለአካባቢው ወጣቶች በርካታ የሥራ ዕድሎችን እንደሚፈጥር ታውቋል።

ከ16 ሚሊዮን ብር በላይ የሚያወጡ የኮንትሮባንድ ዕቃዎች በቁጥጥር ስር ዋሉበምስራቅ ሀረርጌ ዞን ኮምቦልቻ ወረዳ እና በባሌ ዞን ደሎ መና ወረዳ ከ16 ሚሊዮን ብር በላይ የሚያወጡ በርካታ የኮ...
05/29/2025

ከ16 ሚሊዮን ብር በላይ የሚያወጡ የኮንትሮባንድ ዕቃዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ

በምስራቅ ሀረርጌ ዞን ኮምቦልቻ ወረዳ እና በባሌ ዞን ደሎ መና ወረዳ ከ16 ሚሊዮን ብር በላይ የሚያወጡ በርካታ የኮንትሮባንድ ቁሳቁሶች በቁጥጥር ስር ዋሉ። ከተያዙት ዕቃዎች መካከል የቦንዳ አልባሳት እና የተሽከርካሪ ጎማዎች ይገኙበታል።

በምስራቅ ሀረርጌ የተያዙ ኮንትሮባንዶች

በምስራቅ ሀረርጌ ዞን ኮምቦልቻ ወረዳ፣ በተለይም በዋራና መልከ ራፉ ቀበሌዎች በተደረገ ፍተሻ፣ ከ6 ሚሊዮን ብር በላይ የሚያወጡ የኮንትሮባንድ ቁሳቁሶች ተይዘዋል። የዞኑ ፖሊስ ኮሙኒኬሽን ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ካስዬ አበበ እንዳስታወቁት፣ በራፉ ቀበሌ ብቻ ከ4 ሚሊዮን ብር በላይ የሚያወጡ ዕቃዎች ተይዘዋል። ከእነዚህም መካከል ግንቦት 12 ቀን 2017 ዓ.ም የተያዘው ኮድ 3 81635 ኦሮ አይሱዙ የጭነት ተሽከርካሪ ከጃርሶ ወረዳ ሲጋራዎችን እና የተለያዩ የተሽከርካሪ ጎማዎችን ጭኖ ሲጓዝ የነበረው ይጠቀሳል።

በተጨማሪም በኮምቦልቻ ወረዳ ዋሬ ቀበሌ ከ2.5 ሚሊዮን ብር በላይ የሚያወጣ የኮንትሮባንድ ዕቃ በቁጥጥር ስር ውሏል። እነዚህ የተያዙ ቁሳቁሶች ለሀረር ጉምሩክ ጽሕፈት ቤት ገቢ የተደረጉ ሲሆን፣ ተጠርጣሪ ግለሰቦችም ምርመራቸው ተጠናቆ ለሚመለከተው አካል እንደሚላኩ ምክትል ኢንስፔክተር ካስዬ ገልፀዋል።

በባሌ ዞን የተያዙ የቦንዳ አልባሳት

በሌላ በኩል፣ በባሌ ዞን ደሎ መና ወረዳ ግንቦት 15 ቀን 2017 ዓ.ም ምሽት 4 ሰዓት ላይ በተደረገ ድንገተኛ ፍተሻ፣ መነሻውን ከበርበሬ ወረዳ ያደረገ ካሶኒ የጭነት ተሽከርካሪ ተይዟል። ተሽከርካሪው የዋጋ ግምቱ 16 ሚሊዮን 126 ሺህ 600 ብር የሚያወጡ 188 የተለያዩ የቦንዳ አልባሳት ይዞ ሲንቀሳቀስ እንደነበር ከሀረር ጉምሩክ ባለስልጣን የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

በመባ ወርቅነህ

05/26/2025

ይህ ወጣት ዲያቆን ለሃይማኖቱ እያደረገ ያለው ነገር ሊበረታታና ትልቅ ድጋፍ ሊሰጠው የሚገባ ነው።

ዲያቆን ፈለገ አትናቴዎስ ብዙ ከመስመር የሳቱ ወጣቶችን በትህትና እና በመልካም አስተምህሮ ወደ ቀልባቸው እንዲመለሱ እያደረገ ያለ ታታሪ አገልጋይ ነው።

በርታ ዲያቆን! እረጅም እድሜ ከጤና ጋር እንመኝልሃለን።

Via: ጉርሻ

በአዲስ አበባ የመንግሥት ሠራተኞችን የቤት ባለቤት ለማድረግ ስምምነት ተፈረመበአዲስ አበባ ከተማ የሚገኙ የመንግሥት ሠራተኞችን የቤት ባለቤት ለማድረግ የሚያስችል የውል ስምምነት ተፈረመ። ስም...
05/24/2025

በአዲስ አበባ የመንግሥት ሠራተኞችን የቤት ባለቤት ለማድረግ ስምምነት ተፈረመ

በአዲስ አበባ ከተማ የሚገኙ የመንግሥት ሠራተኞችን የቤት ባለቤት ለማድረግ የሚያስችል የውል ስምምነት ተፈረመ። ስምምነቱን የፈረሙት የአዲስ አበባ ከተማ ቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ እና የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ናቸው።

ይህ ስምምነት መምህራንን ጨምሮ በከተማዋ የሚገኙ የመንግሥት ሠራተኞችን የቤት ተጠቃሚ የሚያደርግ መሆኑ ተገልጿል። ስምምነቱ በአነስተኛ የወለድ መጠን በ25/75 የብድር መርሃ ግብር የሚከናወን ይሆናል።

ቀደም ሲል ተደራጅተው በመጠባበቅ ላይ ለነበሩ ቤት ፈላጊ መምህራን በዚህ መርሃ ግብር ቅድሚያ እንደሚሰጣቸው ተብራርቷል። የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በከተማ አስተዳደሩ ለሚገኙ ቤት ፈላጊ ሠራተኞች በዝቅተኛ የወለድ መጠንና በ20 ዓመት የሚከፈል ብድር ማመቻቸቱን አስታውቋል።

በከተማዋ የሚገኙ ከ40 ሺህ በላይ የመንግሥት ሠራተኞችን ተደራሽ ለማድረግ መታቀዱን ፋና ዘግቧል።

Address

Dallas, TX

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Fetan Zena - ፈጣን ዜና posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share