Mekane-Selam Media - MSM

  • Home
  • Mekane-Selam Media - MSM

Mekane-Selam Media - MSM Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Mekane-Selam Media - MSM, Media/News Company, .

የመካነ ሰላም ከተማ አመሰራረት=====================መካነ ሰላም   መካነ + ሰላም ከሚሉ ከ6 ፊደላት  የተሰየመች ከተማ ስትሆን ትርጉሙም  እጅግ  የሰላም ቦታ  /ሰላሟ የበዛ /...
17/08/2025

የመካነ ሰላም ከተማ አመሰራረት
=====================
መካነ ሰላም መካነ + ሰላም ከሚሉ ከ6 ፊደላት የተሰየመች ከተማ ስትሆን ትርጉሙም እጅግ የሰላም ቦታ /ሰላሟ የበዛ / እንደማለት ነው ፡፡
መካነ ሰላም ከተማ የምትገኘው ከደሴ በስተምእራብ አቅጣጫ 182 ኪሎሜትር እርቀት ላይ ነው፡፡መካነሰላም ከተማ አሃድ ብላ የተቆረቆረችው በደጃች ጎበና አመዴ ገዥበነበሩበት ዘመን 1941 ዓ.ም ሐምሌ 5 ቀን መካነ ሰላም ከተማ በያኔየው አጠራር አንድ(ጭቃ) መሬት (ቀበሌ) ሆና ተቆረቆረች ፡፡ የያኔየም አሮጌው ሰፈር ላይ የተቆረቆረቸው መካነ ሰላም እምብዛም እዛ ቦታ ላይ ሳትቆይ የበርካታ ሙህራንን ያፈራው የቦረና ከፍተኛ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ፊት ለፊት አለው ሰፈር ቦታ ላይ ድን ኳን ጥለው እንድመሰረት ካደረጉ በኋላም የጭቃ ሹም ደግሞ ከበደ ሙሃመድን አድርገው ሹመውም ነበር፡፡

በኋላ ላይ ደግሞ አሁንፒያሳ የሚባለው ቦታ ቴሌ ፊትለፊትላይ የመካነሰላም ከተማ የውሃ ታንከር አለበት ቦታ አካባቢ እጣፈንታዋ ተወስኖ ቤቶች እንድስሩ በማድርግ የከተማዋ ዋና ቦታ ሆኖ ተመሰረተ:: ከዘህ በኋላ ከተማይቱ እንድህ እንድህ እያለች እየሰፋች መጣች ከተማዋ ፒያሳና አራዳ ሰፈሮች ላይ በማንሰራራት አራዳና ፒያሳ ዋና የሸቀጣሸቀጥ ሶቆች ሞቅ ደመቅ በማድረግ መከፈት ጀመሩ ፡፡ ከተማዋ በፈጣን እድገት እየሰፍች ሲትሄድም ጥሩ ጥሩ ቢሮዎች አሁን አስተዳደር ግቢ የሚባለው ላይ በወቅቱ በነበረው የአውራጃ አስተዳዳሪ በአቶ እሸቱ ሰይድ ሃሳብ አፍላቂነት አማካኝነት ህብረተሰቡን በማስተባበር ቢሮዎች እንድገነቡ ሆነዋል፡፡ ለምሳሌ በወቅ ቱ አጠራር ገንዘብ ሚኒስቴር በጣም የተሻለ ቢሮ ሲሆን ሌሎችንም እንደ ፍርድቤት ፍትህ ፓሊስ እና ትምህርት ሚኒስቴር ቢሮዎችን አስገንብተው ለአገልግሎት አብቅተዋል፡፡

በኋላም ከተማዋ እየሰፍች ስትሄድ በ1981ዓ.ም መንግስት የቦታ ምሪት በመፍቀዱ ቲታኤ ሰፈር ቀላዱ /መድረሳ/ በኋላም ቄራ በሚባሉ ሰፈሮች በስፍት የመስሪያ ቦታ መሬት በመሰጠቱ የመንግስት ሰራተኞች ቤት ተሰርተዋል፡፡ ከተማዋ እንድትሰፋም በወቅቱ እድል ፍጥሮም ነበረ ፡፡ ከ2004 በኋላ ደግሞ መንግስት ለመንግስት ሰራተኞች የቦታ ምሪት እንድሰጥ በማድረጉ ግብርና ሰፈር አየር ጤና በመካነሰላም ጤና ጣቢያ በታች በላንቂሳና ደንቢ ለገአማራ አሻጋሪ አሮጌው ሶዩ ከተማይቱ የመስፍት እድል አግኝታለች አሁን ደግም ጨፌ ደንበሌ ናበጎማጣ አድስ ምራት እየተሰጠ ነዉ።

መካነሰለም አሁን ላይ በልጆቿ ጥረት በመልሶ ግንባታ በፈጣን እድገት ላይም ትገኛለች፡፡
ይች ከተማ እንድህ እንድህ እያለች እያደገች በመጣቷ የተነሳ ህብረተሰቡም የነቃ ህዝብ በመሆኑ በ2001 ዓም ራሷን ችላ የከተማ አስተዳደር እንድትሆን መስፈርቱን በማሟላቷ የከተማ አስተዳደርነት ቦታ ክልሉ ሰጥቷታል ፡፡በዚች ከተማ የሚኖረውም ህዝብ አሁን ላይ ከ85ሽ ህዝብ በላይ ህዝብ በከተማዋ ውስጥ ይኖራል፡፡ ከተማዋም በ5 ቀበሌዎች የተዋቀረች ስትሆን በከተማዋውስጥም 1 ዩኒቭርስቲ 1ቴክኒክና ሙያ ኮሌጂ 1የግል ጤና ኮሌጅ ማሰልጠኛ 1 የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል 1ጤና ኬላ 1ጤና ጣቢያ በግል ደግሞ 2 መካከለኛ ክሊኒክ 1 አስራሰባት(17 )ባንክ የመንግስትና የግል ሌላዉ የጂነአድም ባልተቤት ነች፡፡
ከተማዋን ለማሳደግም በውስጧ አቅፍ በያዘቻቸው ወጣት ባለሃብት ልጆቿ ያላሰለሰ ጥረት ከተማይቱ የመልሶ ግንባታ ለአይን ማረፊያ ህንጻዎች ተገንብተዋል፡፡ ሌላው የወደፊት የከተማዋን እጣፈንታ የሚወስን የገበያ ማእከል የከተማዋ ባለሃብቶች እየሰሩበትና እየገነቡ ነው፡፡ ሌላው የመቅደላ አምባ ዮኒቭርስቲበመከፈቱ ለከተማዋ እድገትበ ፈጥሮአል ፡፡ የግል የጤና ሳይንስ ኮሌጃም ተከፍቶየአርሶ አደሩ ልጆቹን ወደ ደሴ እና ሌሎች ቦታዎ ች ልኮ ልጆቹን በኤክስቴሽን እንዲማሩ ልኮ ያስተምር ስለነበር አሁን ላይ ደግሞ መካነሰላም ከተማ በመከፈቱ ሁሉ በደጀ ብሎማስተማር ችሎአል፡፡
ተተኳሪ ጉዳዮች
==========
የመካነሰላም ከተማ ያልተሻገረቻቸው ተግዳሮቶችንም ስናነሳ
በፌደራል መንገዶች ባለስልጣን ያሰራው ከኮምቦልቻ መካነሰላም ግንደ ወይን መንገድ ፕሮጀክት መሰራቱ ጥሩ ሆኖ እያለ የተሰራው የመሃል አገረ መስመሩን ለማገናኘትና ንግዱንም ይሁን ከወደብ የሚመጡ እቃዎችንም ለማጓጓዝ ናለማሳለጥ ታሳቢ ያደረገ ቢሆንም የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ያሰራው መገድ በ1999 ዓ.ም ጨረታ በማውጣት ለቻይና መንገድ ስራ ፕሮጀክት በመስጠት በ5አመት ውስጥ እንድጠናቀቅ ወል ቢቆረጥለትም ተጨማሪ 3 አመት በመጨመር ልክ በ8 አመቱ ተጠናቆ በ2007 ዓ.ም 2ኛ ሩብ አመት ላይ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስቴር ደመቀ መኮንንና በወቅቱም ትራንስፓርት ሚኒስቴር በነበሩት ወረቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር )ተመርቆ በይፍ ተክፍቶአል፡፡ ይህ በፌደራል መንግስት በጀት ከኮምቦልቻ መካነ ሰላም ግንደ ወይን የተሰራው አስፓልት መንገድ ወረዳዋንም ይሁን ከተማዋን የ76 ኪ.ሜ ተጠቃሚ አድርጎ በመሀል ከተማው አቋርጦ ከማለፉም ባሻገር በአባይ ወንዝ ምክንያት ተራርቀውና ተነፋፍቀው ይኖሩ የነበሩ የምስራቅ ጎጃም ዞንና የደቡብ ወሎ ዞን ህብረተሰቦች በቀላሉ በማገናኘት በሁለቱም ዞኖች መካከል ያለውን የህብረተሰብ ትስስር ከማጠናከሩም ባሻገር ኑሮን በማሻሻል ትልቁን ሚና ይጫወታል፡፡
ለመሃል አገር እንደ ዋና መገናኛ ኮሪደር ተደረጎ እያገለገለ እና ለመንግስትም በጅንታው ጦረነት እንደዋና እስትራቴጅ ሆኖም አገልግሎል፡፡
መንገድ ግን እምብዛም አገልግሎት ሳይሰጥ ለብልሽት ተዳርጎአል ባለሃብቶችም በዚህ መስመራ ለመሄድ አዳጋች መሆኑን ለመንግስት አቤቱታ ቢያሰሙም የመንገዱ እድሳቱም ሰሚ ያጣ ይመስላል፡፡ትራንስፖርቴሽን ሲስተሙም መንገዱ ወዳው እንደተሰራ ደሴ 3.00 ሰዓት የሚገባ ሲሆን አሁን ላይ ደግሞ 7.00 ሰዓት ለዶልፊንና ለሃይ ሩፍ የሚወስድ ሲሆን ለሌሎች የጭነት መኪኖች ደግሞ ያው የዱሮው አካሄድ ውስጥ ገብተዋል፡፡ እናዚህ መኪኖችም እንደበፊቱ ተፍ ተፍ ብለው እመስመሩ ላይ ሲሰሩ አይታዩም፡፡ ለምንቢባልም መንገዱ ከጊዜ ወደጊዜ የብልሽት መጠኑ እየጨመረ ስለመጣነው ፡፡
ሌላው የከተማይቱ ትልቅ ተግዳሮት ባለፉት ተከታይ አመታት የውሃ ችግር ህብረተሰቡን እያማረረ ሲሆን ከዚህ ችግር የተነሳ ህብረተሰቡ የሰነበተ ውሃ እስከመጠጣት ተገዶአል ፡፡ አሁን ላይተስፍ የተታለበት የሆጨጨ ግድብ ዘላቂ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት በመንግስት በጎአሳቢነት በባለሙያዎች ና በጎ አሳቢ ሰዎች ባደረጉት እርብርብ ፕሮጀክቱ ዘላቂና አስተማማኝ ውሃ መሆኑ ቢታወቅም ወደስራ ለመግባት በተከታታይ አመታት የጥናቱ ውጤትና የመሬት ካሳ ክፍያ ሁኔታዎች ተደርገዋል። እምብዛም በ2011 ጀምሮ ወደ ስራ ያልተገባ ሲሆን አሁን ላይ ከክልሉ ባለፈ የውሀ ሀብት ሚኒስቴር በበላይነነት ይዞት 2018 ከህዳር ወር በኋላ እንደሚተገበር ታዉቋል።

የህብረተሰቡ የውሃችግር አሳሳቢ እየሆነ በመማጣቱ ለዚህ ፕሮጀክት መሳካት መንግስት ህብረተሰቡ ሙህራን ተወላጆችእና እኔም ለዚህ ፕሮጀክት ያገባኛል የሚል ሁሉ የከተማዋን የውሃ የማገኘት እጣፈንታ ከችግር እንድወጣ ሁሉም በአንድ ለይ በመረባረብ የከተማይቱ የውሃችግር እንድቀረፍ ፋታ የማይሰጠው ጉዳይ ነው ።

ሌላው መካነ ሰላም ከተማ ከየካቲት 23;1965በኋላ ከተማዋ የአውሮፕላን ማረፊያ የነበራት ቢሆንም እስከ 1997ግንቦት8 ድረስ በረራ ሲደረግ ቆይቶ በውል ባልጣወቀ ምክኒያትም ተዘግቶአል፡፡ ከተማዋ ደግሞ የቱሪስት መሰብ ያለትና የቦረና ሳይንት ወረሂመኖ ብሄራዊ ፓርክ /የቦሳወብፓ/ ጽ/ቤት መገኛ በመሆኗ የመቅደላ አምባ ዩኒቭረስቲ በዚቹከተማ ያለ ሲሆን አውሮፕላን ማረፊያው ቢከፈት ለከተማይቱ ከፍተኛ መነቃቃትን ይፈጥራል ተብሎ ይታሰባል፡፡

ሌላው ከተማዋ ለኢንድስትሪ ቦታ አመች ብትሆንም የመብራት ችግር ያለባት ወረዳነች የራሷ የሆነ ሰብ እስቴሽን ሰለሌላት መንግስት ይህንችግር በውል በማጤን አሜጃ ዶሮ ሰደቃላይ ከተማይቱ የረሷ የሆነ የመብራት ሰብ እስቴሽን ይገነባልተብሎ ከፌደራል ቃል ቢገባም እስካሁንድረስ ወደትግበራ ባለመገባቱ የከተማዋ ልክ እንደሰሟ መካነ ሰላም ከሰላም ወጭ ምንም ኩሽ የማይለባት ከተማ መሆን እንዳለባት በማመንና የሚያጋጥሙ ችግሮችንም ህዝብ ከመንግስት ጎን በመቆምና መንግስት ጋር በመነጋገር መፍታት አሌ የማይባል ሃቅ ነው።

ወግዲ በለምለሙ ሳር አጠገብ ከሚገኙ የግራር ዛፎች መካከል አንዷ ስር ሆኜ ከደረባ የእረኝነት ዘመን ትዝታዎች ውስጥ ጥቂቱን እየጨለፍከኩ በመፃፍ ላይ ነኝ ። (ጋሻው መኮነን ከወግዲ ወረዳ)በነ...
30/07/2025

ወግዲ
በለምለሙ ሳር አጠገብ ከሚገኙ የግራር ዛፎች መካከል አንዷ ስር ሆኜ ከደረባ የእረኝነት ዘመን ትዝታዎች ውስጥ ጥቂቱን እየጨለፍከኩ በመፃፍ ላይ ነኝ ።
(ጋሻው መኮነን ከወግዲ ወረዳ)
በነገራችን ላይ ቀደም ሲል በሀገራችን ዘመናዊ መገናኛ ብዙኀን ባልነበረበት ወቅት " እረኛ ምን አለ ? " እየተባለ እረኞች በግጥም መልክ የሚያቀርቧቸው ትችቶች ይመከርባቸው እንደነበር መረጃዎች ይጠቁማሉ ።

ይሄን አስታውሸ በቀጥታ ወደ ደረባ የእረኝነት ዘመን ትዝታዎች ዘንድ አብረን እንድንጓዝ እየጋበዝኩ .....

በጽሁፌ ውስጥ እረኞች ያኔ ይናገሯቸው የነበሩትን አካባቢያዊ የአማርኛ ቃላቶች ከነትዝታቸው እንዳለ የተጠቀምኩባቸው መሆኑን ለመግለጽ እፈልጋለሁ ።

አሁን ወደ ተነሳሁበት ሀሳብ ላምራ ።

እረኞች ለደረባ የሚመርጧቸው ቦታዎች ቆላማ አካባቢወችንና የክረምት ወቅተን በመከተል ሲሆን ፣ ቆላማ አካባቢዎች የክረምቱ ወር ገብቶ ሰማዩ ገና ማስገምገም ሲጀምር በተለየ ሁኔታ ያምራሉ ።

ሳሩ ይለመልማል ። እንጨቱ ያቆጠቁጣል ። ወንዞች ሁሉ በውስጣቸው ሌትተቀን የሚንፎለፎል የምንጭ ውሃን ሲያፈልቁ ውለው ያድራሉ ።

በዚህ በሚያምር ምድር ላይ እረኞች ደረባቸውን ሰርተው ከብቶቻቸውን ያሰማሩበታል ። ከብቶቻቸውን አሰማርተው ከመጠበቅ ባሻገርም የተለያዩ ተግባራትን በፍቅር ያከናውኑበታል ።

ዳቦት ያበጃሉ ፣ የማገዶ እንጨት ይለቅማሉ ፣ ወንጭፍና ጅራፍ ይፈትላሉ ። የፈተሉትን ጅራፍም በየድቡ ላይ እየዘለቁ በማንጓት ወለለቱን ከአንዱ ጋራ ወደ ሌላው ጋራ እንዳስተጋባ ያደረጋሉ ።

ደረባ የገባ እረኛ ወተቱን በአኮሌ በቁሙ እየደበሰቀ ጨሌ እንዳየ እንቦሳ በየተረተሩ ላይ ከወዲያ ወድህ ይፈነጥዝበታል ። በጠጣው ቅቤና ወተት ሰውነቱ እንደ ቅቤ ቅል ስለ ሚያንፀባርቅ የልጃገረዶችን ልብ በፍቅር ለማቅለጥ ጊዜ አይፈጅበትም ።

የወተት ነገር ከተነሳ በተለይም የመጋላ ጊደር ወተትን ጠብ እርግፍ እያለ ይወደዋል ። ወተት ለጤና ለጉልበትና ለጀግንነት ሁሉ ይጠቅማል ብሎም ያምናል ። በብረት ምጣድ ቂጣውን ጋግሮ በቅቤ ይለክካል ። ልቡ ፣ ወኔው ፣ ድፍረቱ ሁሉ ቲም ይላል። ማንንም አይሰማም።

የመጋላ ጊደር ወተት የጠጣ ሰው

የጠይም ልጅ ከንፈር የወለመጠ ሰው

ኧረ እንደት አድርጎ ገላጋይ መለሰው

የጠይም ልጅ ከንፈር ወልምጠህ -
ወልምጠህ

ወደት ትሸሻለህ ወገብክን ለምጠህ ።

በሚለው ቃላዊ ግጥም እንዳይሸነቆጥም ጥንቃቄ ያደርጋል ።

ደረባ የገባ እረኛ ሌላም ጉዳይ አለው ። ጉ ፈ ሬ ማጎፈር !!
ጉፈሬውን ቅቤ እየተቀባ ከእንጨት በተሰራ ሚዶ ይነቅሰዋል ፣ ያበጥረዋል ። ጥርሱን ጉራማይሌ ይወቀራዋል ። አይኖቹንም ይኳላቸዋል ።

አይኑን በቀጫጭን የተኳኳለው
ጥርሱን ጉራማይሌ የተዋቀረው
ይምጣ ያገሬ ልጅ እኔ እምወደው
.....

ይባልለታል ።

የማሽላ እሸት ይበላል ። የጥንቅሽ አገዳ ይከሸክሻል ። ውልብኝን ይቅማል ። እንጉዳይም ይገምጣል ። እንኮይ ፣ አጋምና ቀጋም በአከባቢው የሚገኙ የራሱ ሲሳዮች ናቸው ።

ጅራፍ ግርፊያና የወንዝ ውሃ ዋናም ሳይዘነጉ ይከወናሉ ። የውሃ ዋናን ጉዳይ ሲያስታውሱት ግርም ይላል ።

ክረምት ሲገባ ከትንሽ እስከ ትልቅ ያሉ ወንዞች ሞልተው ይፈሳሉ ። የአንዳንዱ ወንዝ ውሃ ሙላት ደግሞ ለየት ብሎ ይታያል ። ሲበዛ ቁጡ ነው!!

በወንዙ ዳርና ዳር ያገኘውን ሁላ እየጠራረገና ከወዲያ ወድህ እያላጋ ባህሩ ላይ ጉትና አዙሪት ይሰራበታል ። ለም አፈሩንም እየበጠበጠ ፣ አለቱን እያጋጨና እያፋጨ በመልካው ላይ ያለ ከልካይ ይገማሸራል ።

ለእረኞች ይሄ ልዩ ትርኢት ነው ። ዳር እስከ ዳር ሞልቶ የሚፏልለውን ወንዝ በዋና ለማቋረጥም የሚደፍር ከመካከላቸው አይጠፋም ። ወንዙ ትንሽ መጉደል ከጀመረማ ብዙወች ይ ወ ና ጨ ፉ በ ታ ል ። ከነዚህ መካከል አንዱ እኔ ነበርኩ ። ወ ይ ጊ ዜ .... የሩቅ ዘመን ትዝታ ከፊት ለፊቴ ድቅን አለ ።

ከሩቅ ዘመን ትዝታ ወደዚህኛው ሁኔታ ልመልሳችሁ ነው ። አሁን ወደ ምትመለከቱት ፎቶ ። !!

የምትመለከቱት ፎቶ ደብረከርቤ አፋፍን በከፊል የሚያሳይ ነው ። ደብረ ከርቤ አፋፍ ቆላው ውስጥ የተሰሩ የእረኞችን ደረባ አሻግሮ ለማየትና ቁልቁል ለመመልከት ምቹ ናት ።

የ028 ቀበሌን ቆላማ ከፍልን ፣ የሌንጮን ገመገም ፣ ለሚን እስከላይ ድረስ ታሳያለች ። እስከ መካነሰላም ጥግ ያሉትን አካባቢዎችም ይቃኙ ባ ታ ል ።

እዚያ ሆኜ ጽሁፌን ሳጠናቅቅ ወግዲ 01 ከተማ የጠራችኝ መሰለኝ ። የምጽፈውን አቁሜ ፊቴን ወደ እሷው አዞርኩ ። ጉዞየም ወደዛው ሆነ ።

የወግዲ ከተማ አፋፍ ላይ የተመሰረተች በመሆኗ በየአቅጣጫው ብቅ እያሉ ገጠር ላይ ያሳለፍናቸውን የክረምት ትዝታዎች ለማስታወስ ተመራጭ ነች ።

አካባቢያችንን በመውደድ ያሳለፍነውን ህይወት እንደገና በትዝታ እያጣጣምን በደስታ መኖርን እንልመድ እላለሁ ።

የዛሬውን በዚሁ አበቃሁ ። ጋሻው መኮንን ከ ወ ግ ዲ ።

ደቡብ ወሎ አማራ ሳይንት 017 ጉልሜዳ ቀበሌ የሚገኘው ዓመቱን ሙሉ ልምላሜ የማይለየው የአትክልቱ ቦታ 🍃 ዋካ ሚካኤል እና ወፍ አምጭ ማርያም አካባቢ
19/07/2025

ደቡብ ወሎ አማራ ሳይንት 017 ጉልሜዳ ቀበሌ የሚገኘው ዓመቱን ሙሉ ልምላሜ የማይለየው የአትክልቱ ቦታ 🍃
ዋካ ሚካኤል እና ወፍ አምጭ ማርያም አካባቢ

18/07/2025

🙏
የተፈጥሮ ሙሽራዋ ምዕራብ ወሎ ( #መካነሰላም)
ድንቅ ተፈጥሮ ነገር ግን እንደ አገልግል ተለጉሞ የተቀመጠ እንቁ❤

ውቢቱ መካነሰላም የድሮው ደብረሲና አውራጃ መቀመጫ ስትሆን የተመሰረተችውም በ1945 ዓ.ም ነበር:: በአውራጃው ውስጥ የቦ/ሳ/ወ ብሄራዊ ፓርክ ብቻ ሳይሆን የወለቃ አባይ በቶ ብሄራዊ ፓርክም ይገኛል:: ይህ ፓርክ 3 ወረዳወችን ማለትም መካነሰላም ከተማ ዙሪያ ገጠር ወረዳ እና ወግዲ ወረዳ እንዲሁም ከላላ ወረዳን የሚያካልል ነው:: ፅ/ቤቱ ወግዲ ወረዳ ውስጥ ይገኛል:: ምዕራብ ወሎ ውስጥ ካሉት 11 ወረዳወች 6ቱ የቦ.ሳ.ወ ፓርክ ባለቤቶች ሲሆኑ 3ቱ ደግሞ
የወለቃ አባይ በቶ ብሄራዊ ፓርክ ጌታወች ናቸው::

ጥንታዊው ደገር መስጂዲ፣ ደባት መስጂዲ፣ ደብሪቱ መስጂዲ፣ ተድባበ ማርያም፣ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ፣ ምስካቤ ቅዱሳን፣ ሰፋጢራ ኪዳነምህረት፣ ዋካ ሚካኤል እና ሌሎች ሀይማኖታዊ ስፍራዎች እንዲሁም የአፄ ቴዎድሮስ አፅም ያረፈበት መቅደላ አምባ እና የበላይ ዘለቀ ምሽግ የሚገኘው እዚሁ ምዕራብ ወሎ ውስጥ ሲሆን የጃንሆይ ቤተመንግስትም አለ!

በፊት የመሀል ሳይንት፣ ከላላ፣ ደብረሲና፣ አማራ ሳይንት፣ ወግዲ እንዲሁም ከፊል ለጋምቦ ወረዳ ማዕከል ነበረች አሁን ከተማይቱ 5 ቀበሌወችን አቅፋለች:: ዙሪያዋን ደግሞ በገጠር ወረዳው ውስጥ 36 ቀበሌዎች አሉ::

መካነሰላም አሁን ላይ ባለ ኮኮብ ሆቴሎች እና ሌሎች አገልግሎት ሰጭ ተቋማት አሏት:-

ለአብነት ያክል:-

1ኛ ህዳሴ ሆቴል
2ኛ ቦረና ሳይንት ሆቴል
3ኛ አሰፋ ገበየ ሆቴል
4ኛ ሰኒላንድ ሆቴል
5ኛ ባህር ሆቴል
6ኛ ባየ ሆቴል
7ኛ ደብረሲና ሆቴል
8ኛ ዘላለም ሆቴል
9ኛ ላኮመንዛ ሆቴል
10ኛ አልየ ሆቴል
11ኛ ቤተሰብ ሆቴል
12 ፍቅረማርያም ሆቴል ወዘተ ሲሆኑ ፋይናንስን በሚመለከት ደግሞ ህዝብ የሚገለገልበት ብዙ የፋይናንስ ተቋም የሚገኝባት ከተማ ናት ከነዚህም ውስጥ:-

1ኛ CBE መካነሰላም ቅርንጫፍ
2ኛ CBE አባይ በር ቅርንጫፍ
3ኛ አቢሲኒያ ባንክ መካነ ሰላም ቅርንጫፍ
4ኛ አቢሲኒያ ባንክ አራዳ ቅርንጫፍ
5ኛ አዋሽ ባንክ መካነሰላም ቅርንጫፍ
6ኛ ዳሽን ባንክ መካነሰላም ቅእንጫፍ
7ኛ አማራ ባንክ መካነ ሰላም ቅርንጫፍ
8ኛ ልማት ባንክ መካነሰላም ቅርንጫፍ
9ኛ ዘምዘም ባንክ መካነሰላም ቅርንጫፍ
10ኛ ፀደይ ባንክ መካነሰላም ቅርንጫፍ
11ኛ ህብረት ባንክ መካነሰላም ቅርንጫፍ
12ኛ ፀደይ ባንክ ቦረና ቅርንጫፍ
13ኛ ሂጅራ ባንክ መካነሰላም ቅርንጪ
14ኛ አባይ ባንክ መካነሰላም ቅርንጫፍ
15ኛ ቡና ባንክ መካከለኛ ቅርንጫፍ
16ኛ CBE ደባት ቅርንጫፍ ሲሆኑ በትምህርት ተቋም ደረጃም ከተማይቱ ውስጥ ያለውን የመቅደላ አምባ ዩኒቨርስቲ ካምፓስን ጨምሮ የግል ኮሌጆችም አሉ::

ጤና ተቋም:- የመካነሰላም ጄኔራል ሆስፒታል እንዲሁም ጤና ጣቢያ እና የግል ክሊኒኮች አሏት::

መካነሰላምን ይጎብኙ:)

አ    በ    ደ    ች ....! (ተፃፈ በጋሻው መኮነን)መካነሰላም ላይ ያሳለፍነውን ወርቃማ ህይወት ከጓደኛዬ ጋ እያነሳን ወደ ኋላ በሩቅ ዘመን ትዝታ ተጉዘናል። ከትዝታ ስመመን ውስጥ ስ...
16/07/2025

አ በ ደ ች ....! (ተፃፈ በጋሻው መኮነን)

መካነሰላም ላይ ያሳለፍነውን ወርቃማ ህይወት ከጓደኛዬ ጋ እያነሳን ወደ ኋላ በሩቅ ዘመን ትዝታ ተጉዘናል። ከትዝታ ስመመን ውስጥ ስነቃ መንገዴን ወደ ባስ እስቴሽን አደረኩ። መሃል ፒያሳን አቋርጨ ትንሽ እንደተጓዝኩ ባሷን አገኘኋት። ገባሁ።

ጉዞ ወደ ምርታማዋ ምድር ወግዲ...!!

በቅርስና በታሪካዊ ቦታወቿ አንቱታን ወዳተረፈችው የቆንጆዎች አገር በጊዜ ለመድረስ መክነፍ ጀመርኩ። ወግዲ ሌላ ብዙ ትዝታ ይዛ እንደምትጠብቀኝ ቅንጣት ታክል አልጠራጠርም።

እንደተመኘሁት ጉዞዬ ሰምሮልኝ ወግዲ ስደርስ በክረምቱ የሚጥለው ዝናብ አቧራውን ስላስወገደው ደስስስስስ አለኝ።

ብርቱካን ግን የኔን ያክል ደስተኛ አልነበረችም።

ብርቱካን አሰፋ የመካነሰላም ልጅ ስትሆን ወደ ወግዲ ስትመጣ ለመጀመሪያ ጊዜ መሆኑ ነው። የያዘ ይዟት እንጂ መንገዱን እንደ ሲኦል ነው የምትፈራው። ገና የቆላውን መግቢያ ' ሀ ' ስንል ማሸድ ጀመረች።

ከዚያ በላይ ግን የወግዲ ልጅ ትኩስ ፍቅር እረቷታልና እንደምንም የመንገዱን ተጽዕኖ ተቋቁማ ወግዲ ከተማ ገብታለች። የፍቅርን ሃያልነት ከእሷ መረዳት ይቻላል። ፍቅር ........ፍቅር ........ፍቅር አጃባሆዬ።

በሌላ በኩል ደግሞ አንጀቷን እርር ያደረጋት ነገር አለ። ሀሜት...ሀሜት...ሀሜት ...!!

ከሀሜት ለመገላገል በፍቅር የከነፈችለትን የወግዲ ልጂ ይዛው እልም ብትል ደስታዋ ወደር የለውም። ለማንኛውም ስሜቷን እንድህ ነበር የገለጸችው።

የምገዛው የለኝ የሚሸመት ነገር፣
አንተኑ ፍለጋ መጣሁ ስንቀለቀል።

መጣሁ ስንቀለቀል ከመካነሰላም፣
እኔ ባንተ ጉዳይ የማልሆነው የለም።

የማልሆነው የለም ሰማሁ ክፉ - ክፉ፣
አበደች እያሉ - እያሙኝ አለፉ።

ልታማ ግዴለም ፍቅር ነው ስበቡ፣
ሰው አይችለው የለም ካፈቀረ ልቡ።

ካፈቀረ ልቡ አንዴ ከወደደ፣
አይቆረቁረውም ቢባልም አበደ።

የኔ አመለ ምቹ ጥርሰ ጉራማይሌ፣
ባለ ግርማ ሞገስ ሸጋዋ ጎምላሌ።

ወድጄህ - ወደኸኝ፣
አምኜህ - አምነኸኝ፣
ገናናው ፍቅራችን እንደተጀመረ፣
ስሜ መነሳቱ መታማት ከልቀረ፣
ይዠህ እልም ብል ይሻለኝ ነበረ።

ይሄው ነው.............❤️❤️

ያልተዘመረለት!!!ከሸህ ሁሴን ጅብሪል ቀየ አፋፍ፤ ከጉጉፍቱ ምድር ጀምሮ፤ እስከ ዋለልኝ መኮንን ሃገር ቦረና ድረስ የተዘረጋው፤ በጎኑ ወረኢሉንና ወረሂመኖን አቅፎ የተኛው፤ የምእራብ ወሎ ምድ...
09/07/2025

ያልተዘመረለት!!!

ከሸህ ሁሴን ጅብሪል ቀየ አፋፍ፤ ከጉጉፍቱ ምድር ጀምሮ፤ እስከ ዋለልኝ መኮንን ሃገር ቦረና ድረስ የተዘረጋው፤ በጎኑ ወረኢሉንና ወረሂመኖን አቅፎ የተኛው፤ የምእራብ ወሎ ምድር፤ ለዘመናት ውሎ ያደረ የትምህርትና የልማት ጥያቄ ነበረው።

ይህንኑ ጥያቄ መንግስት እልባት ለመስጠት በማሰብ፤ የመቅደላ ዩኒቨርስቲን ሲተክልና ሲገነባ፤ ዩኒቨርስቲውን ከጠፍና ከባዶ መሬት ጀምሮ ዛሬ ወደ ደረሰበት ግዙፍ ተቋምነት ለማድረስ ከጣሩትና ከጋሩት ጥቂት አይናማ አመራሮች መሃከል አንዱ ዶር ታምሬ ዘውዴ ነበር።

ስራ ወዳድ፤ ሰርቶ አይጠግቤ፤ ሃላፊነትን መሸከምና በብቃት መወጣት የሚችል፤ በተግዳሮትና በመከራ መሃል የሚታይና የሚዳሰስ ስራ በማሳየት ለእሱም ሆነ ለአጋሮቹ ኩራት የሆነ ልሂቅና መሪ የነበረው ይህ ታላቅ ሰው ከዚህ ዓለም ድካም ማረፉን በሰማሁ ጊዜ የማያልፍ ታሪክ ጥሎ ማለፉ ትዝ ቢለኝ፤ ነፍስ ይማር ለማለት መጣሁ።

መቅደላ ተረተሩ ሲነሳ፤ የመይሳው ካሳ ስም አብሮ እንደሚነሳ ሁሉ፤ ምዕራብ ወሎ ላይ የተተከለው የመቅደላ ዩኒቨርስቲ ሲነሳ ደግሞ፤ የዶክተር ታምሬ ዘውዴ ስምና ግብር አብሮ ይነሳል።

ጥቂት ጀግኖች አሉ የእጆቻቸው ስራ ሙሉ ምድሪቱን የሚሸፍንላቸው። ዶር ታምሬ ዘውዴ እኔደዚህ አይነት ሰው ሆኖ አለፈ። ዶክተር ሆይ፤ ለወሎ ህዝብ የማይረሳ ውለታ ውለሃልና ስምህና ግብርህ ከመቅደላ ኮረብታ ላይ ደምቆ እንደሚኖር ስንነግርህ በኩራት ነው!!!

ነፍስ ይማር!!!

@ጠበቃ መንግስቱ ዘገየ

ሼጌ የዱላው ለት የሸሽህ እንደሆንሼጌ የጠቡ ለት የሸሸህ እንደሆንእንኳን ከንፈር ወዳች ጎረቤትም አንሆን።አጀብ ነው ወሎ አቦወሎ ሚዲያ
08/07/2025

ሼጌ የዱላው ለት የሸሽህ እንደሆን
ሼጌ የጠቡ ለት የሸሸህ እንደሆን
እንኳን ከንፈር ወዳች ጎረቤትም አንሆን።

አጀብ ነው ወሎ አቦ
ወሎ ሚዲያ

ቦረና ናት አሉኝ አማራ ሳይንትቶሎ ድረሽ በሏት ልመጀንባትአይኗ የተኳለ ከንፈሯ ቀዘባወሎ ያበቀላት የጥቅምት አበባእነነዬ መጀን ወሎ ዘሩ ይርባ!!በምክንያት የተደገመ ግጥም እንኳን ግጥም ድግም...
07/06/2025

ቦረና ናት አሉኝ አማራ ሳይንት
ቶሎ ድረሽ በሏት ልመጀንባት
አይኗ የተኳለ ከንፈሯ ቀዘባ
ወሎ ያበቀላት የጥቅምት አበባ
እነነዬ መጀን ወሎ ዘሩ ይርባ!!

በምክንያት የተደገመ ግጥም እንኳን ግጥም ድግምት ይደገማል😋

!!

_____💚💛❤_____

ውቡ ታሪክ እና አይረሴው የጊምባ እረኛ ሊቅነት!የፊቱን የሚፈርድ የጥንቱ መለኛ፣እንደት ነህ በሉልኝ ያን የጊምባ እረኛ።የሚለውን ስንኝ በመጀመሪያው ክፍል አስታውሰናችሁ ነበር:: ያው በጊምባ ...
01/06/2025

ውቡ ታሪክ እና አይረሴው የጊምባ እረኛ ሊቅነት!

የፊቱን የሚፈርድ የጥንቱ መለኛ፣
እንደት ነህ በሉልኝ ያን የጊምባ እረኛ።

የሚለውን ስንኝ በመጀመሪያው ክፍል አስታውሰናችሁ ነበር::
ያው በጊምባ እረኛ ዙሪያ ሰሞኑን ሁለት ተከታታይ ፅሁፎች ማጋራታችን ይታወሳል:: ዛሬም በጊምባ እረኛ ዙሪያ ግልጽ ያልሆኑ ነገሮች ግልጽ የተደረጉበትን ፅሁፍ ልናጋራችሁ መጥተናል::

የጊምባ እረኛ ምን አለ? በማለት ነገሥታት ጭምር የእረኞችን ትንቢት ለመስማት አስበው ይጠይቁ ያስጠጡቁ እንደነበር ታሪክ አዋቂወች ይናገራሉ::

ጊምባ በደቡብ ወሎ ዞን ለጋምቦ ወረዳ ውስጥ የሚገኝ አካባቢ መሆኑን መናገራችንን እንዳትዘነጉ:: ስለዚህ የታሪካችን መቼት ወሎ እና ቅድመ ደርግ ዘመን ነው::

ስለ ጊምባ እረኛ:- እልወ በሚል ዜማ ትንቢት ይናገራል:: የጊምባ ረኞች "እልወን" የሚያዜሙት በጉረሯቸው የላይኛው ክፍል አካባቢ በጣታቸው ነካ እያረጉ "ምታዊ ዜማ" የሚያወጡበት ተወዳጅ ዜማ አፍላቂ ሀገርኛ ጥበብ ነው ።

ትንቢት በጊምባ እረኛ ተነግሮ ሳይፈፀም አይቀርም ይባላል:: አብዛኛው የኢትዮጵያ ህዝብ ዘመን በተለወጠ ቁጥር የጊምባ እረኞች ምን አሉ? እያለ ይጠይቃል ይባላል:: ትንቢታቸው እውነተኛ ነው።

አድስ አመት ሲገባ ከመስከረም እስከ ጥር ባሉት ወራት ነው ትንቢት የሚናገሩት ይባላል::

የጊምባ እረኛ ትንቢት የሚናገረው በወልይነት አግባብ ነው ወይስ የተለየ መለኮታዊ ፀጋ ተችሮት በሚለው ዙሪያ ታላላቅ የጊምባ ሰወች ሲጠየቁ ይህ ትንቢት ተናጋሪነት ከፈጣሪ የተሰጠ መለኮታዊ ፀጋ ነው ይላሉ!!

በጊዜው የነበሩ ታላላቅ ሰወች ለልጅ ልጅ ስለ እረኞች ታሪክ ያወረሱት እሳቤ:- በእነዚህ ምንም በማያውቁ "ህፃናት" በኩል የሚመጣ ተዓምራዊ ትንበያ እውነተኛና ለብዙ ዘመናት የተናገሯቸውን ትንቢት እውነት እና የተናገሩት ተፈፃሚ የሚሆነው:-

- ህፃናቱ ምንም የማያውቁና በዘር እና በሀይማኖት የማይከፋፈሉ፣

- የፍቅራቸው ጥናት ጧት ነግቶ ጊምባ ሜዳ እስከሚገናኙ የሚቸኩሉ፣

- እርስ በርስ የሚከበባበሩ እና በጊምባ ሜዳ አንድም ትልቅ ሰው በማይውልበት ቦታ እንደ ዘመኑ ልጅ አንድ ከአንዱ ጋር የማይጣሉ፣

- ልክ እንደ አዋቂ ተከባብረውና ተፋቅረው ማታ ወደ ቤታቸው ሲሄዱ በናፍቆት የሚለያዩ፣

- ያላቸውን በጋራ ስለሚካፈሉ እና ንፁህ ስለሆኑ ነው::

ጧት ከቤታቸው ሲወጡ በኸረጭት (ቁርቁምባ ) ይዘውት የሚሄዱትን የገብስ ቆሎ ከሁሉም አካባቢ የመጡት እረኞች ከቀርመሜ፣ ጉሎ፣ ቡክዳ፣ ጭሮ እና ከሌሎችም አካባቢዎች የሚመጡ እረኞች በአንድ ላይ ተሰባስበው ሁሉም የያዘውን ቆሎ አውጥቶ ካሉት እረኞቾ በአንዱ ልብስ ላይ በማድረግ በጋራ ይበላሉ፡፡

እረኞቹ በዚህ ሰዓት እንኳን ሊጣሉ ቀርቶ አንተ ብላ አንተ ብላ እየተባባሉ በፍቅር ሁሉም አብረው ይበላሉ::

የወለዱ በጎችን ወተት በማለብ እንገር፣ ወተት፣ እርጎ እና አሬራ ያከማቻሉ በጋራ ይጠቀማሉ::

ወተት ከማለብ እስከ ማንገር፣ ማርጋትና መግፋት በጋራ ሰርተው በጋራ በፍቅር ይጠጡ ነበር፡፡ እናም የእነዚህን ልጆች ፍቅር እና ምንም በውስጣቸው ክፋት የሌላቸው ህፃናት መሆናቸውን ያየው ፈጣሪ መለኮታዊ መልዕክት በእነሱ በኩል እንደሚልክ ነው ሲነገር የኖረው::

ፍቅር ባለበት ሁሉ ፈጣሪ አለ ይባላል::

ፍቅር ይስጠን💚

Mekaneselam Tube

እንደሚመስለኝ የኦሮሞ ብልጽግና ሰዎች አላማቸው ወሎን በራዴፓ፣ በአገው ፓርቲ እና በወዴፓ አማካኝነት ከሦስት በመከፋፈል ደቡብ ወሎና ኦሮሞ ብሄረሠብ ዞንን ወደ ኦሮሚያ መጠቅለል እንዲሁም የራ...
29/05/2025

እንደሚመስለኝ የኦሮሞ ብልጽግና ሰዎች አላማቸው ወሎን በራዴፓ፣ በአገው ፓርቲ እና በወዴፓ አማካኝነት ከሦስት በመከፋፈል ደቡብ ወሎና ኦሮሞ ብሄረሠብ ዞንን ወደ ኦሮሚያ መጠቅለል እንዲሁም የራያ እና የአገው ክልሎችን መፍጠር ነው። ለዚህም ሲባል የኦሮሞ ብልጽግና ሰዎች ራዴፓ፣ የአገው ፓርቲዎችንና ወዴፓን በከፍተኛ ደረጃ በመደገፍ አይዟችሁ እያሏቸው ይገኛሉ።

የሆነ ሆኖ ወዴፓ ወሎን ወደ ኦሮሚያ ለመጠቅለል እና አካባቢያችንን ወደማያባራ ጦርነት ለማስገባት በኦህዴድ ወይም በኦሮሞ ብልጽግና ሰዎች ስፖንሰርነት የሚንቀሳቀስ እንደሆነ ማሳያው Brook Abegaz ያጋራን የሚከተለው መረጃ ነው።

በOMN እንደተገለጸው የወሎ ክልልነት ጥያቄን አስተባባሪ ሆነው ጥያቄውን ለፌደሬሽን ምክር ቤት ያቀረቡት Obboo ደጀኔ ገ/ማርያም ማን ናቸው?

ግለሰቡን የሚያውቃቸው ወዳጄ ይሄን ልኮልኛል?

Obboo ደጀኔ ኦሮሚያ ክልል ተወልደዉ ያደጉ የሸዋ ኦሮሞ ሲሆኑ በ1980ዎቹ አጋማሽ ገና በወጣትነት እድሚያቸው በህወሓት አማካኝነት በክፍለ-ሕዝብነት ወደ ከሚሴ በመምጣት የኦሮሞ ብሔረሰብ ዞንን ከማደራጀት ባሻገር በዞኑ በተለያዩ የኃላፊነት ቦታዎች እስከ 1990ዎቹ አጋማሽ ድረስ ሲያገለግሉ የነበሩ ታታሪና ትሁት ወጣት ነበሩ።

የቀድሞ ባለቤታቸውም በተመሳሳይ ከኦሮሚያ ክልል ወለጋ የመጡ ወ/ሮ አለሚቱ አጋ የሚባሉ ኦሮሞ ሲሆኑ እሳቸውም በተመሳሳይ በክፍለ-ህዝብነት ተመድበው በኋላም በከሚሴ ከተማ እና በቀድሞው እሶዬ-ጉላ ወረዳ በተለዪዩ የኃላፊነት ዘርፎች ሲያገለግሉ ቆይተዋል። በወቅቱ የደጀኔ ባለቤት ወ/ሮ ዓለሚቱ አጋ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርታቸውን ለክፍለ-ሕዝቦች ተብሎ በተዘጋጀው ጢጣ አዳሪ ት/ቤት ከከሚሴ ደሴ-ጢጣ በመመላለስ ይማሩ ነበር ፤ በወቅቱ አንድ ልጅ አፍርተው በኋለ ላይ ተለያይተዋል።

ደጀኔ በአሁኑ ወቅት በምን ኃላፊነት ወይም በምን የስራ ዘርፍ እንደተሰማሩ በውል ባይታወቅም በ1990 ዎቹ አጋማሽ ከኦሮሞ ብሔ/ብ አስተዳደር ዞን አመራርነታቸው ተዛውረው በኦሮሚያ ክልል በተለያዩ የኃላፊነት ቦታዎች አገልግለዋል በ1990ዎቹ መጨረሻ አካባቢ ኦህዴድን ወክለው በጠቅላይ ሚንስትር ጽ/ቤት ሕዝብ አደረጃጀት ዘርፍ ውስጥ የአንድ ስራ ክፍል ኃላፊ ሆነውም አገልግለዋል። ባለቤታቸውም በ1990ዎቹ መጨረሻ ላይ ከከሚሴ ወደ ኦሮሚያ ክልል በስራ ምክንያት ተዛውረው ሄደዋል።

አሁን ደግሞ ከበርካታ ዓመታት በኋላ Oboo ደጀኔ የወሎ ወኪል ሆነው ብቅ ማለታቸው የማን ተልዕኮ ተቀብለው ይሆን የሚል ጥያቄ ያስጭራል? ይሁንስ ከተባለ የወሎን ሕዝብ ፍላጎትና ጥያቄ ማወቅና ማቅረብ ያለበት ማን ነበር? ምናልባት የደጀኔ ስም በተለምዶ ኦሮሞነትን የሚያሳብቅ ስያሜ ስላልሆነ የወሎ ክልልነት ጥያቄ የኦሮሞ ዘውግ ባላቸው ሰዎች የተቀነቀነ አይደለም ለማሰባል ተፈልጎ ይሆን?

ለማንኛውም የኦሮሞ ተወላጁን Oboo ደጀኔን ከ1980ዎቹ አጋማሽ እስከ 1990 ዎቹ አጋማሽ በከሚሴ እና በአጠቃላይ በኦሮሞ ብሔረሰብ ዞን የማያውቃቸው ሕዝብም ሆነ ነባር የብአዴን አመራር የለም ቢባለ ማጋነን አይሆንም።
ዋግ ኸምራ

19/05/2025

🤣

27/04/2025

የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ሩሲያ እና ዩክሬን ስምምነት ላይ ለመድረስ መቃረባቸውን ተናገሩ❗️

የትራምፕ የመካከለኛው ምስራቅ ልዩ መልዕክተኛ ስቲቭ ዊትኮፍ ከፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ጋር ለሶስት ሰዓታት ያህል ከተወያዩ በኋላ ነው ትራምፕ መግለጫውን የሰጡት፡፡

ተስፋ የተሞላበት ውይይት መደረጉን፤ ሩሲያ እና ዩክሬን ተገናኝተው ስምምነቱን በቶሎ መጨረስ እንዳለባቸው የተናገሩት ትራምፕ፤ በዋና ዋና ጉዳዮች ላይ ከስምነት ተደርሷል፤ ደም መፍሰስም መቆም አለበት ብለዋል፡፡

በሌላ በኩል የዩክሬኑ ፕሬዝዳንት ቮሎድሚር ዘለንስኪ ዘላቂ የተኩስ አቁም ስምምነት እንዲደረግ፤ ሞስኮ ላይ ከፍተኛ ጫና መደረግ አለበት እያሉ ነው፡፡

ዋሽንግተን ባቀረበችው የተኩስ አቁም ስምምነት መሰረት ኬይቭ የተወሰኑ ግዛቶቿን በሩሲያ ቁጥጥር እንዲሆኑ ትፈቅዳለች።

ሩሲያ በፈረንጆቹ 2014 የክሬሚያን ግዛት በይዞታዋ ስር እንድታስቀጥል እንደሚፈልጉ ትራምፕ ገልጸዋል።

የዩክሬኑ ፕሬዝዳንት ቮሎድሚር ዘለንስኪ ግን ይህንን ሀሳብ እንደማይቀበሉት እየተናገሩ ነው፡፡ ሩሲያ በፈረንጆቹ 2022 ልዩ ዘመቻ በሚል ወደ ዩክሬን ከገባች ጀምሮ 20 በመቶ የዩክሬንን ግዛት መቆጣጠሯ ይታወሳል ፡፡
ቢቢሲ፤ ዘ ጋርዲያን እና ኤዥያ ዋን ዘግበውታል ፡፡

Address


Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Mekane-Selam Media - MSM posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

  • Want your business to be the top-listed Media Company?

Share