Mekane-Selam Media - MSM

  • Home
  • Mekane-Selam Media - MSM

Mekane-Selam Media - MSM Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Mekane-Selam Media - MSM, Media/News Company, .

ቦረና ናት አሉኝ አማራ ሳይንትቶሎ ድረሽ በሏት ልመጀንባትአይኗ የተኳለ ከንፈሯ ቀዘባወሎ ያበቀላት የጥቅምት አበባእነነዬ መጀን ወሎ ዘሩ ይርባ!!በምክንያት የተደገመ ግጥም እንኳን ግጥም ድግም...
07/06/2025

ቦረና ናት አሉኝ አማራ ሳይንት
ቶሎ ድረሽ በሏት ልመጀንባት
አይኗ የተኳለ ከንፈሯ ቀዘባ
ወሎ ያበቀላት የጥቅምት አበባ
እነነዬ መጀን ወሎ ዘሩ ይርባ!!

በምክንያት የተደገመ ግጥም እንኳን ግጥም ድግምት ይደገማል😋

!!

_____💚💛❤_____

ውቡ ታሪክ እና አይረሴው የጊምባ እረኛ ሊቅነት!የፊቱን የሚፈርድ የጥንቱ መለኛ፣እንደት ነህ በሉልኝ ያን የጊምባ እረኛ።የሚለውን ስንኝ በመጀመሪያው ክፍል አስታውሰናችሁ ነበር:: ያው በጊምባ ...
01/06/2025

ውቡ ታሪክ እና አይረሴው የጊምባ እረኛ ሊቅነት!

የፊቱን የሚፈርድ የጥንቱ መለኛ፣
እንደት ነህ በሉልኝ ያን የጊምባ እረኛ።

የሚለውን ስንኝ በመጀመሪያው ክፍል አስታውሰናችሁ ነበር::
ያው በጊምባ እረኛ ዙሪያ ሰሞኑን ሁለት ተከታታይ ፅሁፎች ማጋራታችን ይታወሳል:: ዛሬም በጊምባ እረኛ ዙሪያ ግልጽ ያልሆኑ ነገሮች ግልጽ የተደረጉበትን ፅሁፍ ልናጋራችሁ መጥተናል::

የጊምባ እረኛ ምን አለ? በማለት ነገሥታት ጭምር የእረኞችን ትንቢት ለመስማት አስበው ይጠይቁ ያስጠጡቁ እንደነበር ታሪክ አዋቂወች ይናገራሉ::

ጊምባ በደቡብ ወሎ ዞን ለጋምቦ ወረዳ ውስጥ የሚገኝ አካባቢ መሆኑን መናገራችንን እንዳትዘነጉ:: ስለዚህ የታሪካችን መቼት ወሎ እና ቅድመ ደርግ ዘመን ነው::

ስለ ጊምባ እረኛ:- እልወ በሚል ዜማ ትንቢት ይናገራል:: የጊምባ ረኞች "እልወን" የሚያዜሙት በጉረሯቸው የላይኛው ክፍል አካባቢ በጣታቸው ነካ እያረጉ "ምታዊ ዜማ" የሚያወጡበት ተወዳጅ ዜማ አፍላቂ ሀገርኛ ጥበብ ነው ።

ትንቢት በጊምባ እረኛ ተነግሮ ሳይፈፀም አይቀርም ይባላል:: አብዛኛው የኢትዮጵያ ህዝብ ዘመን በተለወጠ ቁጥር የጊምባ እረኞች ምን አሉ? እያለ ይጠይቃል ይባላል:: ትንቢታቸው እውነተኛ ነው።

አድስ አመት ሲገባ ከመስከረም እስከ ጥር ባሉት ወራት ነው ትንቢት የሚናገሩት ይባላል::

የጊምባ እረኛ ትንቢት የሚናገረው በወልይነት አግባብ ነው ወይስ የተለየ መለኮታዊ ፀጋ ተችሮት በሚለው ዙሪያ ታላላቅ የጊምባ ሰወች ሲጠየቁ ይህ ትንቢት ተናጋሪነት ከፈጣሪ የተሰጠ መለኮታዊ ፀጋ ነው ይላሉ!!

በጊዜው የነበሩ ታላላቅ ሰወች ለልጅ ልጅ ስለ እረኞች ታሪክ ያወረሱት እሳቤ:- በእነዚህ ምንም በማያውቁ "ህፃናት" በኩል የሚመጣ ተዓምራዊ ትንበያ እውነተኛና ለብዙ ዘመናት የተናገሯቸውን ትንቢት እውነት እና የተናገሩት ተፈፃሚ የሚሆነው:-

- ህፃናቱ ምንም የማያውቁና በዘር እና በሀይማኖት የማይከፋፈሉ፣

- የፍቅራቸው ጥናት ጧት ነግቶ ጊምባ ሜዳ እስከሚገናኙ የሚቸኩሉ፣

- እርስ በርስ የሚከበባበሩ እና በጊምባ ሜዳ አንድም ትልቅ ሰው በማይውልበት ቦታ እንደ ዘመኑ ልጅ አንድ ከአንዱ ጋር የማይጣሉ፣

- ልክ እንደ አዋቂ ተከባብረውና ተፋቅረው ማታ ወደ ቤታቸው ሲሄዱ በናፍቆት የሚለያዩ፣

- ያላቸውን በጋራ ስለሚካፈሉ እና ንፁህ ስለሆኑ ነው::

ጧት ከቤታቸው ሲወጡ በኸረጭት (ቁርቁምባ ) ይዘውት የሚሄዱትን የገብስ ቆሎ ከሁሉም አካባቢ የመጡት እረኞች ከቀርመሜ፣ ጉሎ፣ ቡክዳ፣ ጭሮ እና ከሌሎችም አካባቢዎች የሚመጡ እረኞች በአንድ ላይ ተሰባስበው ሁሉም የያዘውን ቆሎ አውጥቶ ካሉት እረኞቾ በአንዱ ልብስ ላይ በማድረግ በጋራ ይበላሉ፡፡

እረኞቹ በዚህ ሰዓት እንኳን ሊጣሉ ቀርቶ አንተ ብላ አንተ ብላ እየተባባሉ በፍቅር ሁሉም አብረው ይበላሉ::

የወለዱ በጎችን ወተት በማለብ እንገር፣ ወተት፣ እርጎ እና አሬራ ያከማቻሉ በጋራ ይጠቀማሉ::

ወተት ከማለብ እስከ ማንገር፣ ማርጋትና መግፋት በጋራ ሰርተው በጋራ በፍቅር ይጠጡ ነበር፡፡ እናም የእነዚህን ልጆች ፍቅር እና ምንም በውስጣቸው ክፋት የሌላቸው ህፃናት መሆናቸውን ያየው ፈጣሪ መለኮታዊ መልዕክት በእነሱ በኩል እንደሚልክ ነው ሲነገር የኖረው::

ፍቅር ባለበት ሁሉ ፈጣሪ አለ ይባላል::

ፍቅር ይስጠን💚

Mekaneselam Tube

እንደሚመስለኝ የኦሮሞ ብልጽግና ሰዎች አላማቸው ወሎን በራዴፓ፣ በአገው ፓርቲ እና በወዴፓ አማካኝነት ከሦስት በመከፋፈል ደቡብ ወሎና ኦሮሞ ብሄረሠብ ዞንን ወደ ኦሮሚያ መጠቅለል እንዲሁም የራ...
29/05/2025

እንደሚመስለኝ የኦሮሞ ብልጽግና ሰዎች አላማቸው ወሎን በራዴፓ፣ በአገው ፓርቲ እና በወዴፓ አማካኝነት ከሦስት በመከፋፈል ደቡብ ወሎና ኦሮሞ ብሄረሠብ ዞንን ወደ ኦሮሚያ መጠቅለል እንዲሁም የራያ እና የአገው ክልሎችን መፍጠር ነው። ለዚህም ሲባል የኦሮሞ ብልጽግና ሰዎች ራዴፓ፣ የአገው ፓርቲዎችንና ወዴፓን በከፍተኛ ደረጃ በመደገፍ አይዟችሁ እያሏቸው ይገኛሉ።

የሆነ ሆኖ ወዴፓ ወሎን ወደ ኦሮሚያ ለመጠቅለል እና አካባቢያችንን ወደማያባራ ጦርነት ለማስገባት በኦህዴድ ወይም በኦሮሞ ብልጽግና ሰዎች ስፖንሰርነት የሚንቀሳቀስ እንደሆነ ማሳያው Brook Abegaz ያጋራን የሚከተለው መረጃ ነው።

በOMN እንደተገለጸው የወሎ ክልልነት ጥያቄን አስተባባሪ ሆነው ጥያቄውን ለፌደሬሽን ምክር ቤት ያቀረቡት Obboo ደጀኔ ገ/ማርያም ማን ናቸው?

ግለሰቡን የሚያውቃቸው ወዳጄ ይሄን ልኮልኛል?

Obboo ደጀኔ ኦሮሚያ ክልል ተወልደዉ ያደጉ የሸዋ ኦሮሞ ሲሆኑ በ1980ዎቹ አጋማሽ ገና በወጣትነት እድሚያቸው በህወሓት አማካኝነት በክፍለ-ሕዝብነት ወደ ከሚሴ በመምጣት የኦሮሞ ብሔረሰብ ዞንን ከማደራጀት ባሻገር በዞኑ በተለያዩ የኃላፊነት ቦታዎች እስከ 1990ዎቹ አጋማሽ ድረስ ሲያገለግሉ የነበሩ ታታሪና ትሁት ወጣት ነበሩ።

የቀድሞ ባለቤታቸውም በተመሳሳይ ከኦሮሚያ ክልል ወለጋ የመጡ ወ/ሮ አለሚቱ አጋ የሚባሉ ኦሮሞ ሲሆኑ እሳቸውም በተመሳሳይ በክፍለ-ህዝብነት ተመድበው በኋላም በከሚሴ ከተማ እና በቀድሞው እሶዬ-ጉላ ወረዳ በተለዪዩ የኃላፊነት ዘርፎች ሲያገለግሉ ቆይተዋል። በወቅቱ የደጀኔ ባለቤት ወ/ሮ ዓለሚቱ አጋ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርታቸውን ለክፍለ-ሕዝቦች ተብሎ በተዘጋጀው ጢጣ አዳሪ ት/ቤት ከከሚሴ ደሴ-ጢጣ በመመላለስ ይማሩ ነበር ፤ በወቅቱ አንድ ልጅ አፍርተው በኋለ ላይ ተለያይተዋል።

ደጀኔ በአሁኑ ወቅት በምን ኃላፊነት ወይም በምን የስራ ዘርፍ እንደተሰማሩ በውል ባይታወቅም በ1990 ዎቹ አጋማሽ ከኦሮሞ ብሔ/ብ አስተዳደር ዞን አመራርነታቸው ተዛውረው በኦሮሚያ ክልል በተለያዩ የኃላፊነት ቦታዎች አገልግለዋል በ1990ዎቹ መጨረሻ አካባቢ ኦህዴድን ወክለው በጠቅላይ ሚንስትር ጽ/ቤት ሕዝብ አደረጃጀት ዘርፍ ውስጥ የአንድ ስራ ክፍል ኃላፊ ሆነውም አገልግለዋል። ባለቤታቸውም በ1990ዎቹ መጨረሻ ላይ ከከሚሴ ወደ ኦሮሚያ ክልል በስራ ምክንያት ተዛውረው ሄደዋል።

አሁን ደግሞ ከበርካታ ዓመታት በኋላ Oboo ደጀኔ የወሎ ወኪል ሆነው ብቅ ማለታቸው የማን ተልዕኮ ተቀብለው ይሆን የሚል ጥያቄ ያስጭራል? ይሁንስ ከተባለ የወሎን ሕዝብ ፍላጎትና ጥያቄ ማወቅና ማቅረብ ያለበት ማን ነበር? ምናልባት የደጀኔ ስም በተለምዶ ኦሮሞነትን የሚያሳብቅ ስያሜ ስላልሆነ የወሎ ክልልነት ጥያቄ የኦሮሞ ዘውግ ባላቸው ሰዎች የተቀነቀነ አይደለም ለማሰባል ተፈልጎ ይሆን?

ለማንኛውም የኦሮሞ ተወላጁን Oboo ደጀኔን ከ1980ዎቹ አጋማሽ እስከ 1990 ዎቹ አጋማሽ በከሚሴ እና በአጠቃላይ በኦሮሞ ብሔረሰብ ዞን የማያውቃቸው ሕዝብም ሆነ ነባር የብአዴን አመራር የለም ቢባለ ማጋነን አይሆንም።
ዋግ ኸምራ

19/05/2025

🤣

27/04/2025

የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ሩሲያ እና ዩክሬን ስምምነት ላይ ለመድረስ መቃረባቸውን ተናገሩ❗️

የትራምፕ የመካከለኛው ምስራቅ ልዩ መልዕክተኛ ስቲቭ ዊትኮፍ ከፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ጋር ለሶስት ሰዓታት ያህል ከተወያዩ በኋላ ነው ትራምፕ መግለጫውን የሰጡት፡፡

ተስፋ የተሞላበት ውይይት መደረጉን፤ ሩሲያ እና ዩክሬን ተገናኝተው ስምምነቱን በቶሎ መጨረስ እንዳለባቸው የተናገሩት ትራምፕ፤ በዋና ዋና ጉዳዮች ላይ ከስምነት ተደርሷል፤ ደም መፍሰስም መቆም አለበት ብለዋል፡፡

በሌላ በኩል የዩክሬኑ ፕሬዝዳንት ቮሎድሚር ዘለንስኪ ዘላቂ የተኩስ አቁም ስምምነት እንዲደረግ፤ ሞስኮ ላይ ከፍተኛ ጫና መደረግ አለበት እያሉ ነው፡፡

ዋሽንግተን ባቀረበችው የተኩስ አቁም ስምምነት መሰረት ኬይቭ የተወሰኑ ግዛቶቿን በሩሲያ ቁጥጥር እንዲሆኑ ትፈቅዳለች።

ሩሲያ በፈረንጆቹ 2014 የክሬሚያን ግዛት በይዞታዋ ስር እንድታስቀጥል እንደሚፈልጉ ትራምፕ ገልጸዋል።

የዩክሬኑ ፕሬዝዳንት ቮሎድሚር ዘለንስኪ ግን ይህንን ሀሳብ እንደማይቀበሉት እየተናገሩ ነው፡፡ ሩሲያ በፈረንጆቹ 2022 ልዩ ዘመቻ በሚል ወደ ዩክሬን ከገባች ጀምሮ 20 በመቶ የዩክሬንን ግዛት መቆጣጠሯ ይታወሳል ፡፡
ቢቢሲ፤ ዘ ጋርዲያን እና ኤዥያ ዋን ዘግበውታል ፡፡

27/04/2025
አብን ዛሬ ጠቅላላ ጉባኤ አድርጓል===================የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ (አብን) ዛሬ መጋቢት 28, 2017 ዓ.ም. ባደረገው ፫ኛው ጠቅላላ ጉባኤ 5 የቁጥጥር ኮሚሽን እና 45...
06/04/2025

አብን ዛሬ ጠቅላላ ጉባኤ አድርጓል
===================
የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ (አብን) ዛሬ መጋቢት 28, 2017 ዓ.ም. ባደረገው ፫ኛው ጠቅላላ ጉባኤ 5 የቁጥጥር ኮሚሽን እና 45 የምክር ቤት አባላትን መርጧል።

ምክር ቤቱም ዶክተር በለጠ ሞላን የድርጅቱ ሊቀመንበር አቶ መልካሙ ፀጋዬን ምክትል አድርጎ ሰይሟል።

Negarit - ነጋሪት

18/03/2025

ከአማራ ፋኖ ወሎ ዕዝ የተሰጠ የሃዘን መግለጫ!

ደምህ ይመለሳል፣ አላማህም በቆራጥ ጓዶችህ ይሳካል

ቦረና ሳይንት ወረሂመኖ ብሄራዊ ፓርክ“ምንይዋብ” የዉብና ድንቅ መስህብ ባለቤት👉መገኛየቦረና ሳይንት ወረሂመኖ ብሔራዊ ፓርክ በደቡብ ወሎ ዞን በስድስት ወረዳዎች ማለትም በቦረና፤ በመሃል ሳይን...
28/02/2025

ቦረና ሳይንት ወረሂመኖ ብሄራዊ ፓርክ
“ምንይዋብ” የዉብና ድንቅ መስህብ ባለቤት

👉መገኛ

የቦረና ሳይንት ወረሂመኖ ብሔራዊ ፓርክ በደቡብ ወሎ ዞን በስድስት ወረዳዎች ማለትም በቦረና፤ በመሃል ሳይንት፤ በሳይንት፤ በሌጋምቦ፤ በመቅደላና በተንታ ወረዳዎች እና በእነዚህ ወረዳዎች በሚገኙ 34 ቀበሌዎች ይገኛል፡፡

የቦረና ሳይንት ወረሂመኖ ብ/ሄራዊ ፓርክ ከአዲስ አበባ በደጀን ብቸና፤ ደብረወርቅ ጉምደዎይን መርጦለማሪም መካነሰላም 461ኪሎሜትር፤ ከባህር ዳር፤ ሞጣ ፤ጉምደወይን መርጦ ለማሪያም አባይ፤ መካነ ሰላም 298 ኪ.ሜ፣ ከደሴ 198 ኪ.ሜ ጽ/ቤቱ ከሚገኝበት ከቦረና ወረዳ ዋና ከተማ መካነ ሰላም ስሜን ምእራብ 18 ኪ.ሜ ርቀት ላይ ይገኛል፡፡ ከፍታዉ ከባህር ወለል በላይ 1900-4280 ሜትርና ከሞንታኔ እስከ ዉርጭ ቀመስና ዉርጭ፤ ስርዓተምህዳር ያቀፈ ነዉ፡፡

👉የጥበቃና ክለላ ታሪክ

የቦረና ሳይንት ወረኂመኖ ብሄራዊ ፓርክ የምእራብ ወሎ ተራሮችና የተፈጥሮ ደኖች አካል ሲሆን መነሻዉ ምን ይዋብ ተብሎ ይጠራ የነበረዉና በአጼ ዘርዓ ያእቆብ (1434-1468) ጥብቅ የንጉስ ደን፤ በ1950ቹ የመንግስት ደን በኋላም በ1980ቹ ዋና የመንገስት ጥብቅ ደን ተብሎ ሲጠበቅ የነበረዉ ደንቆሮ ጫካ ነዉ፡፡ በ1997 እና 1998 ዓ.ም የመጀመሪያና ዝርዝር ጥናት ተካሂዶና ከአካባቢዉ ህብረተሰብና ባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት ክለላ ከተካሄደ በኋላ በአማራ ክልል ምክር ቤት በ2001 ዓ.ም 4575 ሄ/ር በቦረና፤ በሳይንትና መሃል ሳይንት ወረዳዎች በ13 ቀበሌዎች ተካሎ በአማራ ክልል ምክር ቤት ዝክረ ህግ 69/2000 ህጋዊ እዉቅና አገኘ፡፡ በመቀጠል የአዋሳኝ ወረዳዎች፣ ቀበሌዎች ባለ ድርሻ አካላትና ህብረተሰቡ የብሄራዊ ፓርኩን ጠቀሜታ ግንዛቤ በማደጉ በ2004 ዓ.ም የጥናትና የማስፋት ክለላ በ4 ወረዳዎች ሳይንት፤ መቅደላ፤ ተንታና ሌጋምቦ ወረዳዎችና 21 ቀበሌዎች በማስፋፋት ወደ 15,262 ሄ/ር አድጎ ዝክረ ህግ 155/2009 ዳግም ህጋዊ ሰዉነት አግኝቷል፡፡

👉 የተፈጥሮ ገጽታ፤ የስርዓተምሀዳርና ብዝሃ ሕይወት

የተፈጥሮ ገጽታ የቦረና ሳይንት ወረሂመኖ ብ/ሄራዊ ፓርክ በመሬት አቀማማጥ ገጽታዉ ወጣገባና ማራኪ ሲሆን በትልልቅ እድሜ ጠገብ አገር በቀል ዛፋች የተሸፈኑ የቡቄ፤ ግሸዋ፤ የአለባቸዉ ዋሻ፤ ቦቃ ዋሻ፤ የነጭ ሃሮ፤ የደንቆሮ ወንዝ አናት፤ የቀርከሃና የጥር ወንዝ ዳገታማና ገደላማ ቦታዎች፡፡ በጅብራ/መገራ/፤ በአምጃና በጓሳ የለበሱ ሜዳማና ተራራማ አብዛኛዉን የደቡብ ወሎ ከፍተኛና መመልከቻና መስህብ የሆኑ የቦረናን ልም መስክ፤ ካቡጎራ፤ሞሰቢት፤ ይላስ ጎራ፤ ቀርከሃ ራስና ሸፍታ ጎራ፤ የመሃል ሳይንትን ቆይ ዋሻን‹ ቆጠትና ቅድመ ማሪያምን የሳይንትን ካራ አባቦጊ፤ የጥር ወንዝን፤ ታቦርንና ሃረር ሜዳ፤ የሌጋምቦን ጎላቴን‹ ቆርጣሚትና አካባቢዉን፤ በኢትዮጵያ ከፍተኛ ቦታዎች አምባ ፈሪጥ የሚባለዉን የተንታንና የታሪካዊቷን የመቅደላ አምባዎችን የያዘ በተራራማ፤ በዋሻወች፤ ሜዳማና ሸለቋማ የዉሃ ማማ፤ የተፈጥሮና ታሪካዊ ገጽታዎችን የተላበሰ ነዉ፡፡

👉የስርዓ ተምሀዳር የቦረና ሳይንት ወረሂመኖ ብሄራዊ ፓርክ የእጽዋት ክምችት

ስርዓተምህዳሮች / Ecosystems/ የወንዝ ዳር ደኖች /Riverine Mixed Montane Riverine Forest/ ዶቅማ፤ ሸላ፤ ችብሃ፤ ከግልገል ደንቆሮ ከቡቄ ደን አስከ ግሸዋ ደን ፤ በዝቅተኛዉ የቀርከሃ ሸለቆና የጥር ወንዙን ተከትሎ የተሸፈኑ፡፡ የዳታማ በዉርጭ ቀመስ በጥቅጥቅ ደኖች /Dense Sub Afro Alpine Forest / በአስታ፤ የሃበሻ ጽድ፤ ዝግባ፤ ወይራ፤ ዉልክፋ፤ ኮሶ ወዘተ የተሸፈኑ፡፡ ሜዳማና ተራራማ ከፍተኛ ዉርጭ / Afro Alpine Forest / በጅብራ/መገራ/፤ በአምጃ፤ በአሸንዳ፤ በጓሳ ሳር፤ጨረፌና ከፊል በአስታ የተሸፈነ፡፡

ብዝሃ ሕይዎት የቦረና ሳይንት ወረሂመኖ ብሄራዊ ፓርክ የብዝሃ ሕይዎት ሃብቶች እጽዋት፡- 496 ዝርያዎች 12 ብርቅዬ /Endemic/ 8 አመላካች /indicator plant species/፡፡ አጥቢ የዱር እንስሳት፡- የቦረና ሳይንት ወረሂመኖ ብሄራዊ ፓርክ አጥቢ እንስሳት 23 ዝርያዎች ነብር፤ ተራ ቀበሮ፤ አነር፤ ድኩላ ጉሬዛ፤ ሰሳ፤ ሚዳቋ፤ አዉጭ፤ አፍን ወዘተ፡፡ ብርቅዬ 3 ትልልቅ (ጭላዳ፤ የኢትዮጵያ ቀይ ቀበሮና የሚኒሊክ ድኩላ) 2 ትንንሽ (የስታርክ ጥንቸልና አርቪክነተስ አይጥ/፡፡ አእዋፋት፡- 77 ዝርያዎች ብርቅየ 4 / የሶረኔ ቆቅ ፤ የአብሲኒያ ድመት መሳይ፤ የአብሲኒያ ግንደቆርቁር፤ ራስ ጥቁር ጩጨ/ ናቸዉ፡፡

ታሪካዊና ባህላዊ የቦረና ሳይንት ብሄራዊ ፓርክ ሃይማኖታዊ ባህላዊና ታሪካዊ ቅርሶች፤ መጽሃፍትና መገልገያዎች፤ አልባሳት፤ የነጻነት ትግልና የባህላዊ ዳኝነት አደባባይ፤ ዋሻዎችና የስብሰባ ቦታዎች፤ የእንስሳት ቅራት /ደረባ/፤ በጋራ ንብ ማርባት /ዘዳ/ እና ባህላዊ ጨዋታና ወጎች፤ምግቦችና መጠጦች ይታወቃሉ፡፡ ከእነዚህ ጥቂቶቹ ቅድመ ማሪያም፤ መስካቤ ቅዱሳን፤ ዳባት መስጊድ፤ ተድበበማራያም፤ መቅደላ አምባ ወዘተ ናቸዉ)፤

👉የቦረና ሳይንት ወረሂመኖ ብሄራዊ ፓርክ ጠቀሜታዉ

የቦረና ሳይንት ወረሂመኖ ብሄራዊ ፓርክ ጥበቃና ልማት አላማ የፓርኩን የተፈጥሮ፤ ታሪካዊና ባህላዊ ሃብቶች ለመጠበቅ፤ ለማልማትና ለመጠቀም ሲሆን በዚህም በተፈጥሮ ደኑ ላይ የሚደረሱትን አሉታዊ ጫናዎች ለመቀነስና የባለድርሻ አካላትን፤ የአካባቢ አስዳደሮችንና የአካባቢዉን ህብረተሰብ ተጠቃሚነትና ሀላፊነት በመወጣትና የፓርኩን ስነምህዳራዊ፤ አገራዊና አለማቀፋዊ አማራጭ ጥቅም፤ ለማረጋገጥ፤ ሃብቱን በተፈጥሮ ገጽታዉ ለማቆየት፤ ለማስተዋወቅና ለትዉልድ ማስተላላፍ ነዉ፡፡

ባላፉት 12 አመታት የብሄራዊ ፓርኩን የብዝሃ ህይዎት ሃብቶችና መኖሪያ አካባቢያቸዉን ለመጠበቅ የቢሮ ግንባታና የመስክና የቢሮ መገልገያዎችን በማሟላት ይህን የሚያግዝ የጂአይዜድ የብዝሃ ህይዎትና የደን ፕሮግርም የፓርኩን ስርዓተ አያያዝ ሰነድ ዝግጅት፤ አመታዊ በጀት በመመደብ ለሰራተኞች የአቅም ግንባታ ስልጠና በመስጠት፤ ግባቶችን በማሟላት፤ የልማት ስራወችን በመደገፍና የጥበቃና የቁጥጥር ስራዉ ሳይንሳዊ በሆነና በኤሌክትሮኒክስ ሪሞት /SMART/ ክትትልና ቁጥጥር በማካሄድ ዉጤታማ መሆንና በአማራጭ የገቢ ምንጭ በአትክልት፤ ፍረፍሬ ምርቶች፤ የደን ችግኝ ልማት በተለይም በአካባቢዉ የማይታወቀዉ የአፕል ምርት እየተስፋፋ ይገኛል፡፡

የብሄራዊ ፓርኩ ስነምህዳረዊ ጥቅም የዝናብ ስርጭት በማስተካከልና የአካባቢዉ አርሶ አደሮች በዓመት ሁለት ጊዜ እንዲያመርቱ ምርታማነት እንዲጨምር፤ከብሄራዊ ፓርኩ በተገኘዉና በዳበረዉ ገጸና ከርሰ ምድር ዉሃ ለመካነሰላም ከተማ መጠጥ ዉሃና ለመስኖ አገልግሎት የሚዉል ግድብ በመሰራት ላይ ነዉ፡፡ ከደኑ ዉጤት የጓሳ ሳር ከሌላ ቦታ ይመጣ የነበረዉ ቀጥታ ከፓርኩ መጠቀም ችለዋል፤ ለንብ እርባታና ለቤት እንስሳት መኖ ዘለቄታዊ በሆነ መንገድ ህብረተሰቡ ተጠቃሚ መሆን፡፡

በተጨማሪም ፓርኩ የሚሰጠዉን ስነምህዳራዊ አገልግሎት መሰረት በማድረግ በአዋሳኝ ስድሰት ወረዳዎች የተራቆቱ መሬቶችን በደን በመሸፈን ህብረተሰቡ እንዲጠቀም ከኬኤፍደብሊዉ የጀርመን የፈይናነስ ተቋም ደኑ ከለማ የማይመለስ ብድር እንዲያገኙ ለደን ልማት የገንዘብ፤ የሰዉ ሃይልና የተሸከርካሪ ድጋፍ ለሁሉም ወረዳዎች መገኘቱ፡፡ በእነዚህ አካባቢያዊ ጠቀሜታዎች የህበረተሰቡ የባለቤትነት ስሜት ተፈጥሯል፡፡ እነዚህ ጠቀሚታዎች እየተገኙ ቢሆንም አሁንም የብሄራዊ ፓርኩ የመሰረተልማት ግንባታ፤ማስተዋወቅና የቱሪዝም አገልግሎት ልማት በተጠናከረ ሁኔታና በሚፈለገዉ ደረጃ ባለመሆኑ ብሄራዊ ፓርኩ ሊሰጥ የሚችለዉን ጥቅም እያስገኘ አይደለም፡፡ የሚመለከታቸዉ ሁሉ እነዚህ ችግሮች እንዲፈቱ የሚችሉትን ጥረት እንዲያደርጉ እናሳስባለን፡፡

የቦረና ሳይንት ወረሂመኖን ብሄራዊ ፓርክ ማራኪ የተፈጥሮና ባህላዊ መስህቦች በመጎብኘት እራስዎንና ቤተሰበዎን ያዝናኑ የተፈጥሮን ሚስጥር ያድንቁ!!

ኑ አብረን እንፈር፤ሻለቃ ደምሴ ይመርን ቃሊም አንዲት ትምህርት ቤት ውስጥ ዘግተውበት እንደሰነበተ ፍንጭ ደርሶኛል:: ከቃሊም ወደ ዞብል እንደወሰዱት እየተነገረ ነው:: ለማወዛገብ የተጠቀሙት ...
18/07/2024

ኑ አብረን እንፈር፤

ሻለቃ ደምሴ ይመርን ቃሊም አንዲት ትምህርት ቤት ውስጥ ዘግተውበት እንደሰነበተ ፍንጭ ደርሶኛል:: ከቃሊም ወደ ዞብል እንደወሰዱት እየተነገረ ነው::

ለማወዛገብ የተጠቀሙት ስልት ሊሆን ስለሚችል ቃሊም አካባቢ ያላችሁ ወጣቶች ልዩ ክትትል አድርጋችሁ ሰብሰብ ብላችሁ በመሄድ የልጅ ሽማግሌ ሆናችሁ ወንድማችሁን ከእገታ ብታስለቅቁት ለህዝባችን ትልቅ ውለታ ነው::

ወደ ቃሊም የወሰዱት የፊጥኝ አስረው እየገፈተሩ ነው::

በነገራችን ላይ እሁድ ለሰኞ ሌሊት ወልዲያ ከተማ ውስጥ በተሰራው ኦፕሬሽን ለቆሰሉ የሻለቃ ደምሴ ሁለት ፋኖዎች የተገዛ ሙዝ፣ ጁስ፣ እርጎ እና ቴምር ጭምር ጉፍፍ አድርገው በልተው የተረፋቸውን ደፍተውት የሚይዙትንም ይዘው ነው የሄዱት:: ለሴት ፋኖዎች የተገዛ የንፅህና መጠበቂያ ቁሳቁስ እንኳ አልቀራቸውም::

አበበ ፈንታው፣ አባተ ካሳ እና ተሾመ ፈንታ በልዩ ሁኔታ የእገታው ሴራ ጠንሳሾች ናቸው:: ይህ መንጋ ማለት ኮሎኔል ሞገስ ዘገዬን በነገር አዋክቦ ከኮሎኔል ፈንታው ሙሀባ ነጥሎ ወደ ራያ የወሰደ እልም ያለ መንደርተኛ ነው:: ለኮሎኔል ሞገስ እየደወሉ "አንተ እኮ እዛ ብቻህን ነህ..ኮሎኔል ፈንታው ያጠፋሀል!! በነብስህ ብትወጣ ይሻልሀል" እያሉ በመንደር እሳቤ እንድኮበልል ያደረጉ አስተሳሰበ ቅንጭር ናቸው:: ኮሎኔል ሞገስ በጣም የዋህ ስለሆነ እኔ አሁን ደውዬ "ጋሼ- እከሌ እኮ ሊገድልህ ጠብመንጃ እየወለወለ ነው" ብለው ያ አህያ ልክ ነህ ይወለውላል ቆይማ ትጥቁን ልቀማው ነው የሚለው:: የዚህን ያልክ የዋህ ነው:: ሴራ አይችልም!!

ኮሎኔል ሞገስን አስከድተው የወሰዱበትን ሂደት ስንፈትሽው መንጋዎቹ ከመንደራቸው ውጭ ያለውን ሰው አያምኑም ከማጥፋትም አይቦዝኑም ማለት ነው:: እንዲህ አይነቶችን ደግሞ በግልፅ ካልታገልናቸው ሳይለንት ኪለር ሆነው ጀግና እያጠፉ ብቻቸውን እንደ አህያ ጡት ይንጎባለላሉ::

መፍትሄው ሴረኛን እና የደም ነጋዴን ማጋለጥ ነው:: ገና ብዙ የማሰጣው ሚስጥር አለ:: አሁን ወደ ውስጥ በደንብ አልዘለኩም ምናልባት ከለቀቁት ብዬ ሀይላይት ብቻ ነው እየፃፍኩ ያለሁት:: ውስጥ ስገባ ብዙ የሚዘነኮር ጉድ አለ::

ወሎ አማራ ሳይንት ተድባበ ማርያም ዳግማዊት ኢየሩሳሌም
09/06/2024

ወሎ አማራ ሳይንት ተድባበ ማርያም
ዳግማዊት ኢየሩሳሌም

በሰሜን ወሎ ዞን የአላማጣ ከተማ ነዋሪዎች ሕወሓት በራያ ሕዝብ ላይ እየፈጸመ ያለውን ግፍ ሰኔ 2 ቀን 2016 ዓ.ም በሕዝባዊ ሰልፍ ተቃውመዋል፡፡ ሰልፈኞቹ የፌዴራል መንግሥት ለራያ ሕዝብ ጥ...
09/06/2024

በሰሜን ወሎ ዞን የአላማጣ ከተማ ነዋሪዎች ሕወሓት በራያ ሕዝብ ላይ እየፈጸመ ያለውን ግፍ ሰኔ 2 ቀን 2016 ዓ.ም በሕዝባዊ ሰልፍ ተቃውመዋል፡፡

ሰልፈኞቹ የፌዴራል መንግሥት ለራያ ሕዝብ ጥያቄ አፋጣኝ ምላሽ ሊሰጠን ይገባል፤ መንግሥት ህወሓትን ከአካባቢያችን ያስወጣልን፤ ህወሓት ትጥቅ ፈትቶ በሰላም እንኑር፤ ከአሸባሪነቱ ያልተለየው ህወሓትን የፖለቲካ ፓርቲ ኾኖ መመዝገብን እንቃወማለን፤ የራያ የማንነት ጥያቄ በሀገር አፍራሾች አይድበሰበስም የሚሉ መልዕክቶችንም አስተላልፈዋል፡፡

ህወሓት በሰዎች ላይ ግድያ እና በተቋማት ላይ ውድመት እየፈጸመብን ነው ብለዋል ነዋሪዎቹ። አሁንም በትህነግ መገደላቸው መቀጠሉን እና ጉዳት መድረሱን የተቃወሙት ሰልፈኞች፣ የራያ እናት ዳግም በልጇ ሞት ማልቀስ የለባትም፤ ለማንነታችን መመለስም በሰላማዊ መንገድ እንታገላለን ብለዋል፡፡

ከሰልፉ ተሳታፊዎች መካከል አስተያየታቸውን ለአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን የሰጡ የራያ ነዋሪ ባለፉት ጊዜያት የህወሓት የጥፋት ተግባር መቀጠሉን ጠቅሰው ባለፉት ሁለት ቀናትም የሰዎች ግድያ መፈጸሙን ጠቅሰዋል።

ማኅበረሰቡም ግፉ ስለበዛበት እንደመረረው እና ከገዳዩ ቡድን ጋር አንኖርም በሚል መብቱ እና ሰላሙ እንዲከበር መጠየቁን ተናግረዋል፡፡ በገጠሩ የእርሻ ሰብሉን እያወደመ ያለው የታጠቀው የህወሓት ቡድንን መንግሥት ከራያ እንዲያስወጣልን ነው እየጠየቅን ያለነው ብለዋል፡፡

አስተያየት ሰጪው "ለተወሰኑ ጊዜያት በሰላም ኖረን ነበር አሁን ግን ህወሓት ተመልሶ በመምጣት ሰላማችንን እያደፈረሰው፣ እየገደለን እና እየዘረፈን ነው" ብለዋል፡፡ በየገጠሩ ሰውን በዱላ እና በጥይት በመደብደብ በራያዎች ላይ ግፍ እየፈጸሙ ነው ብለዋል፡፡

የህወሓት ታጣቂ ኀይል ዙሪያውን እንደከበባቸው፣ ትምህርት ቤቶችን የወታደር ካምፕ እንዳደረጓቸው እና የፌዴራል መንግሥት ሕግ በማስከበር የህወሓትን ታጣቂ ኀይል ከራያ ምድር እንዲያስወጣላቸው ነው የጠየቁት፡፡ የአማራ ክልል መንግሥትም የራያ ወሎ አማራነት ጥያቄያቸውን ለፌዴራል መንግሥት እንዲያቀርብላቸው ጠይቀዋል፡፡

ሌላኛው የሰላማዊ ሰልፉ ተሳታፊ እና የወሎ ራያ ማንነት እና ወሰን አስመላሽ ኮሚቴ አመራር ሕዝቡ ባለፉት 30 ዓመታት በህወሓት ከፍተኛ በደል ሲደርስበት እና ይህንንም ሲታገል እንደቆየ ገልጸዋል፡፡ ህወሓት አሁንም በድጋሚ የፕሪቶሪያውን ስምምነት በመጣስ አካባቢውን በመውረር የራያ ነዋሪዎችን በመግደል፣ በመዝረፍ፣ አፍኖ በመውሰድ እንዲሁም ንብረት እና ሰብል በማውደም ላይ መኾኑን ተናግረዋል፡፡

በኮረም፣ በራያ ባላ፣ በገርጀሌ፣ በኮረም ወፍላ እና ዛታ ሰዎችን በመግደል፣ አፍኖ በመውሰድ እና በመቀማት ጉዳት እያደረሰ ነው ብለዋል አስተያየት ሰጪው። የሰልፉ ጥያቄ የፕሪቶሪያው ስምምነት ይከበር፤ ግድያ ይቁምልን፤ በሰላም ወጥተን የመግባት ደኅንነታችን ይከበርልን፤ ትምህርት ቤቶች ከጦር ካምፕነት ነጻ ይሁኑ የሚል ጥያቄ ነው ይዘን የተሰለፍነውም ብለዋል፡፡

ህወሓት ከእኩይ ተግባሩ ባለመላቀቅ እየወረረ እና ግድያ እየፈጸመ ሕጋዊ የፖለቲካ ፓርቲነትን መፍቀድ የራያ ሕዝብ እንዲሰቃይ መፍቀድ መኾኑን እያሳሰብን ነውም ብለዋል፡፡ የተወካዮች ምክር ቤት ያወጣውን ሕግ ዳግም እንዲያጤነውም እናሳስባለን ብለዋል፡፡

ነዋሪዎቹ መንግሥት የፕሪቶሪያው ስምምነት እንዲከበር ማድረግ አለበትም ብለዋል። ህወሓት የራያን ሕዝብ እየወረረ ያለው አማራ ክልል ላይ ያለውን የሰላም መደፍረስ እንደ ጥሩ አጋጣሚ ተጠቅሞ ነው፡፡ የአማራ ሕዝብ የውስጥ ችግሮቹን በውይይት ፈትቶ፣ አንድነቱን ጠብቆ እና ተናብቦ ከጎናችን እንዲኾን እንጠይቃለን ብለዋል፡፡

ሰልፈኞ ከያዟቸው እና ካሰሟቸው መልዕክቶች መካከል፦

👉ራያ ወሎ አማራ ነው!

👉ፍትሕ በህወሓት ለተገደሉ ወገኖቻችን!

👉ታጥቀው ትምህርት ቤት ላይ የመሸጉ የህወሓት ኀይሎች በአፋጣኝ ይውጡልን!

👉ከመንግሥት ኀይል ጋር ተቃውሞ የለንም፤

👉ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር! የሚሉት ይገኙበታል፡፡

Address


Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Mekane-Selam Media - MSM posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

  • Address
  • Alerts
  • Claim ownership or report listing
  • Want your business to be the top-listed Media Company?

Share