Mekane-Selam Media - MSM

  • Home
  • Mekane-Selam Media - MSM

Mekane-Selam Media - MSM Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Mekane-Selam Media - MSM, Media/News Company, .

ለምን ይሆን ሰው ሰውን የሚገድለው 🤔
23/10/2025

ለምን ይሆን ሰው ሰውን የሚገድለው 🤔

 #ገነቴሀገርሽ ገነቴ ፣ የተወለድሽበትከነሸህ ሙሳ አገር ፣ ሁሉ ከሞላበት --- ገነቴከደ/ወሎ ዞን ዋና ከተማ ከደሴ 130 ኪሎ ሜትር ፣ ከወረዳው መቀመጫ አቀስታ በ30 ኪሎ ሜትር፣ ከቦረና ...
18/10/2025

#ገነቴ

ሀገርሽ ገነቴ ፣ የተወለድሽበት
ከነሸህ ሙሳ አገር ፣ ሁሉ ከሞላበት --- ገነቴ

ከደ/ወሎ ዞን ዋና ከተማ ከደሴ 130 ኪሎ ሜትር ፣ ከወረዳው መቀመጫ አቀስታ በ30 ኪሎ ሜትር፣ ከቦረና መቀመጫ መካነ ሰላም እና ከወግድ በ50 ኪሎ ሜትር እና ከሳይንትና መሀል ሳይንት ወረዳዎች በ60 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ትገኛለች።
ገነቴ በለጋምቦ ወረዳ ውስጥ ከሚገኙ ከተሞች ውስጥ አንዷ ስትሆን ስትራቴጅክ ከተማም ናት። ከተማዋ በማደግ ላይ ያለች ወይና ደጋ ለኑሮ ተስማሚ እና ምቹ የአየር ንብረት ባለቤት ናት። ከጎተራ ተርፎ እህል በጉርጓድ የሚከዘንበት ለመጣ ለሄደው አህሪቡ በሞቴ ብሉልኝ ጠጡልኝ ብሎ ያለውን የሚሰጥ ምርቱ የተትረፈረፈ ሁሉን አብቃይ ለም ምድር ገነቴ ሁሉን መስጠት ይችላል።

ቦረና ቦረና ቦረና ገነቴ
እያብረከረከች ገባች በጉልበቴ

እየተባለ የሚዜምላት ተወዳጇና በፍቅር ልብ ቅልጥ፣ጉልበትን ዛልና ብርክርክ የምታደርገው ገነቴ ከእምቧጮ በር እስከ ሰላም በር ፣ ከወለቃ እስከ አራጣ ፣ ከጅንጎ እስከ ጎሀ መንቃቆ ፣ ከእርሜቲ እስከ ሂጤጤራ ፣ ከቢዮ እስከ ላፍቶ በሎ ጋራና ወንዛ ወንዙ ሜዳና አቀበቱ ሁብና ሙሀባ ተጎንጭቶ ፣ የደግነትና የጀግንነት ወይባ ታጥኖ የሚታደግበት የፍቅር ሰፈር ነው።

አገርሽ ገነቴ ፣ ያበቀለሽ ወሎ
የቆንጆዎች ቆንጆ ፣ የፀይም መለሎ

የጨነቀለታም የገነቴ የእርሜቲ ጎረምሳ ሽመሉን ካነሳና አንደየ ካገሳ ቋ ሲል የሚሰማው ዱላው እንጅ ግንባሩ አይደለም ፣ ቁሞም ተንበርክኮም ተኝቶም የሚመክት የወንድነት ውሀ ልክ የጀግንነት ጥግ የሚታይበት ቆንጆዎችና መልከ መልካሞች የሚወለዱበት ፣ የየዋሆችና የደጋጎች ምድር ገነቴ ሁሉ ነገሯ ይመስጣሉ።

የለፍጀሌው (የተበችሳው) የልጃገረዶች ስርቅርቅታ መሳጭ ዜማና የጎረምሶች ግፍቻና ቀውጢ ሆታ ምንግዜም ቢሆን ከውስጥ አይጠፋም!!!

የፍቅር የሰላም ከተማ------- ገነቴ

Mohammed Husien

የማይነጋ ሕልም ሳልምየማያድግ ችግኝ ሳርምየማይድን በሽታ ሳክምየሰው ሕይወት ስከረክም እኔ ለእኔ ኖሬ አላውቅም
09/10/2025

የማይነጋ ሕልም ሳልም
የማያድግ ችግኝ ሳርም
የማይድን በሽታ ሳክም
የሰው ሕይወት ስከረክም
እኔ ለእኔ ኖሬ አላውቅም

ሰበር ዜና💪ጀግናው የአማራ ክልል አድማ ብተና ፖሊስ ወረኢሉ ላይ ጽንፈኛውን አይቀጡ ቅጣት ቀጥቶታል።💪💪💪💪
08/10/2025

ሰበር ዜና💪

ጀግናው የአማራ ክልል አድማ ብተና ፖሊስ ወረኢሉ ላይ ጽንፈኛውን አይቀጡ ቅጣት ቀጥቶታል።💪💪💪💪

መስከረም23 ቀን2018ዓ.ም በመካነሠላም ከተማ በኑር መስጅድ በግፍ በመስግድ (ሚህራብ) ውስጥ ለተገደሉት ቤተሰቦች ለማገዝ የቦረና መካነ ሠላም ኮሚቴ ተወያይቶ የሚከተለውን አካውንት በሸኽ መ...
07/10/2025

መስከረም23 ቀን2018ዓ.ም በመካነሠላም ከተማ በኑር መስጅድ በግፍ በመስግድ (ሚህራብ) ውስጥ ለተገደሉት ቤተሰቦች ለማገዝ የቦረና መካነ ሠላም ኮሚቴ ተወያይቶ የሚከተለውን አካውንት በሸኽ መከተ ሙሔ፣ በዶ/ር ሚስባህ ሳኒ እና ሰይድ ጌታቸው ስም ከፍቶ የኢትዮጵያ ህዝብ የተጎጂዎቹን ቤተሰብ እንዲያግዝ ጥሪ አቅርቧል።

የኢትዬጱያ ንግድ ባንክ፦

1000721919351
Mekete Muhe & Misbah Sani and Seid Getachew

ሙስሊም ክርስቲያን ሳትሉ ድጋፋችሁን በማሳየት አንድነታችሁን በተግባር አሳዩ!

ለኸይር ሥራ እንረባረብ!

በደቡብ ወሎ ዞን መቅደላ ወረዳ ከጸጥታ መዋቅሩ ጋር ዉይይት ተካሂዷል።ማሻ= መስከረም 24/2018 ዓ.ም(መቅደላ ኮሙኒኬሽን)የወረዳዉ አስተዳዳሪ አቶ እንዳልካቸዉ አረጋ እንደገለጹት "የመቅደላ...
04/10/2025

በደቡብ ወሎ ዞን መቅደላ ወረዳ ከጸጥታ መዋቅሩ ጋር ዉይይት ተካሂዷል።

ማሻ= መስከረም 24/2018 ዓ.ም(መቅደላ ኮሙኒኬሽን)
የወረዳዉ አስተዳዳሪ አቶ እንዳልካቸዉ አረጋ እንደገለጹት "የመቅደላ የጸጥታ መዋቅር በየወቅቱ ህብረተሰቡን ለማጎሳቆልና ለመዝረፍ የሚመጣን ዘራፊ ሀይል አይቀጡ ቅጣት በመቅጣት ማህበረሰቡን የታደገ የቁርጥ ቀን ልጅ ነዉ።

የወረዳዉ ጥምር ጦር ሀይል ሰሞኑን ከዉስጥ ባንዳ ጋር በመነጋገር ወደ ማሻ ከተማ በመግባት ለመዝረፍ አቅዶ የመጣን የህዝብ ጠላት አዋርዶ መልሷል።
ያለምግብ ዉርጭ ላይ አድሮና ዉሎ የወረዳዉን ህዝብ ሀብትና ንብረት በመጠበቅ ክብር ህይወቱን አሳልፎ እስከመስጠት ጀብድ የፈጸመዉ የጸጥታ መዋቅር ክብርና ምስጋና ይገባዋል ብለዋል ።

በቀጣይም ይበልጥ በመናበብ የጠላትን ሴል በመበጣጠስ ህዝቡን የሰላሙ ባለቤት በማድረግ ዘላቂ ሰላም ማረጋገጥ ያስፈልጋል ብለዋል።
በዉይይቱ የወረዳዉ ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ተስፋየ ወዶኝ ፣የአደረጃጀት ዘርፍ ሀላፊ አቶ ይመር አመደ፣ የጸጥታ ካቢኔ አባላት ተገኝተዋል።

04/10/2025
ፋኖ ......😭😭መካነሰላም ኑር መስጅድ ገብቶ የመስጅዱ ምእመናን ላይ ከፍተኛ ጭፍጨፋ ፈፅሟል።የመስጅዱ ኢማሞችን ኻዲሞችንና ሌሎችንም ሰጋጆችን መግደላቸው እየተነገረ ነው።ኢናሊላሂ ወኢና ኢለ...
04/10/2025

ፋኖ ......😭😭

መካነሰላም ኑር መስጅድ ገብቶ የመስጅዱ ምእመናን ላይ ከፍተኛ ጭፍጨፋ ፈፅሟል።

የመስጅዱ ኢማሞችን ኻዲሞችንና ሌሎችንም ሰጋጆችን መግደላቸው እየተነገረ ነው።

ኢናሊላሂ ወኢና ኢለይሂ ራጂኡን!

ከአሁኑ በገቡባቸው ከተሞች ያውም ወሎ ምድር ላይ የሀይማኖት ጦርነት አወጁ። ይህንን ግፍ ሙስሊሙም ክርስቲያኑም አብሮ በጋራ እንዲቃወምና የነዚህ አሸባሪዎችን የሀይማኖት ጦርነትን ወሎ ላይ የማስነሳት ሴራ ሊያከሽፍ ይገባል።

እነዚህ ግለሰቦች ላይ ዘላቂ እርምጃ ካልተወሰደ ህዝባችን እጅግ አደጋ ላይ ነው።

ፋኖን የምትረዱና የምትደግፉ ሙስሊሞች በሙሉ እንኳን ደስ አላችሁ 😥
04/10/2025

ፋኖን የምትረዱና የምትደግፉ ሙስሊሞች በሙሉ እንኳን ደስ አላችሁ 😥

መረጃው ለሁሉም ይድረስ 🙏 ሼርይሄ ከታች እምትመለከቱት ግለሰብ የደቡብ ወሎ አካባቢ ልጅ ሲሆን ትክክለኛ ስሙ ሰጠ ሀይለ ማሪያም ይባላል።ፌስቡክ ላይ Esamael Dawed Endris እሚል  ...
04/10/2025

መረጃው ለሁሉም ይድረስ 🙏 ሼር

ይሄ ከታች እምትመለከቱት ግለሰብ የደቡብ ወሎ አካባቢ ልጅ ሲሆን ትክክለኛ ስሙ ሰጠ ሀይለ ማሪያም ይባላል።ፌስቡክ ላይ Esamael Dawed Endris እሚል በሙስሊም ስም ፌክ አካውንት በመክፈት ሙስሊም በመምሰል የተንሸዋረሩ እና የተሳሳቱ መረጃዎችን እያሰራጨ ይገኛል።በተለይ መካነሰላም ላይ የተፈጠረውን ነገር በጣም አሳፋሪ እና አስነዋሪ በሆነ መንገድ እየፖሰተ ያለው ግለሰብ ይሄ ነው።

ሙስሊም ለሚመስላችሁ ሰዎች እንዳትሸወዱ

ለጥንቃቄ ሸር ይደረግ 🙏

የመካነሰላም ጭፍጨፋ መረጃ 😥"ሙስሊሞች መስጅድ ውስጥ ሚሊሻ ደብቀዋል"አሁን በኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር ከቀኑ 6:20ሰዓት አካባቢ ነበር መካነሰላም ከተማውስጥ ነዋሪ ወደሆኑ ወዳጆቸ በድጋሚ ስ...
04/10/2025

የመካነሰላም ጭፍጨፋ መረጃ 😥

"ሙስሊሞች መስጅድ ውስጥ ሚሊሻ ደብቀዋል"

አሁን በኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር ከቀኑ 6:20ሰዓት አካባቢ ነበር መካነሰላም ከተማውስጥ ነዋሪ ወደሆኑ ወዳጆቸ በድጋሚ ስልክ የደወልኩት።
ትናንት ደውዬ "ከተማ ውስጥ ተኩስ ስላለ መረጃ የለንምና ጠብቀን "ብለውኝ ነበር።
ዛሬ ግን ቅስማቸው በተሰበረ የኃዘን ድባብ ውስጥ ሆነው የሰጡኝ መረጃ በዕውነትም ቅስም ይሰብራል።

መካነሰላም መስጅድ ውስጥ የመሰጅዱን ኢማም ጨምሮ ከ5 በላይ ሙስሊሞች መጨፍጨፋቸው ዕውነት ነው። ጭፍጨፋውን ያካሄደው በአባይ ሸለቆ ውስጥ የተደበቀው የዘመነ ካሴ ገዳይ ቡድን ነው።ሌሊት ሰርጎ በመግባት በከተማው ውስጥ በርካታ ንፁሐንን እንደገደለ የሚናገሩት ወገኖቸ በተለይ መስጅድ ውስጥ በሙስሊም ወገኖቻችን ላይ የተፈፀመው ፋሽስታዊ ጭፍጨፋ ዘግናኝ ነው ይላሉ።

ይህ ገዳይ ቡድን ከተማውን ለቆ ከመሸሹ በፊት ጠዋት ወደመጅዱ ገብቶ ጭፍጨፋ የፈፀመው "ሙስሊሞች የከተማውን ሚሊሻ አዛዥ በመስጅድ ውስጥ ደብቀዋል"በሚል ሰበብ እንደሆነ አረጋግጠውልኛል።

ካሁን በፊትም በተለይ በወያኔ ወረራ ዘመን የጎጃሙ ነፍሰገዳይ ቡድን ወደከተማው ገብቶ ለመግደልና ለመዝረፍ ሙከራ ባደረገበት ወቅት ሙስሊሞች በመስጅዳቸው ውስጥ ተሰባስበው ተቃውመውት እንደነበር የሚያስታውሱት ነዋሪዎች "አሁን የቆዬ ፀረ-እስልምና ቂማቸውን ተበቀሉ"ይላሉ።

ሀቁ ይህ ሆኖ እያለ የዚሁ ነፍሰገዳይ ቡድን ደጋፊዎችና የሻዕቢያና የወያኔ የሳይበር ሠራዊቶች ተባብረው ፋሽታዊ ጭፍጨፋውን የፈፀመው የክልሉ መንግስት ለማስመሰል በቲክቶክና በሌሎችም ማህበራዊ ሚዲያዎች እየተረባረቡ ነው።እንደ ዋሱ መሐመድ ያሉ "ገለልተኛ"መሳይ ሰዎችም ሀቁን ለማድበስበስ እየሞከሩ ነው።

የአማራው የሻዕቢያ ጉዳይ አስፈፃሚ ነፍሰገዳይ ካሁን በፊትም በጎንደር እንፍራንዝ÷ቀጎጃም ሞጣና በመሳሰሉት ቦታዎች ሙስሊሞችን እየመረጠ ሲገድልና ሲዘርፍ እንደነበረ ሁሉ አሁን መስቀል መሳይ እንጨት አንጠልጥሎ የፈፀመው ያንኑ አረመኔያዊ ድርጊቱን ነው።ይህ መስል መሰል እንጨት አንጠልጣይ የሞአ ተዋህዶ ነፍሰገዳይ ቡድንና የሻዕቢያ አገልጋይ ቃል አቀባዮቹ ለፍርድ ካልቀረቡ ኢትዮጵያ ውስጥ እስከመቼውም ፍትህ ተበይኖ ሰላም አይሰፍንም።የጭካኔ ጭፍጨፋው እጅግ አስቆጭ ነው🙄

via Al abebe

«በጣም ጠቃሚ ስለሆነ ልብ ብለው ያንብቡት»፡♠ በአንድ ዩኒቨርሲቲ የሳይኮሎጂ ዲፓርትመንት መምህሯ ተማሪወቿን አንድ Assignment መስጠት ፈለገች..!! ተማሪወቿን ድንች ይዘዉ እንዲመጡ አ...
03/10/2025

«በጣም ጠቃሚ ስለሆነ ልብ ብለው ያንብቡት»

♠ በአንድ ዩኒቨርሲቲ የሳይኮሎጂ ዲፓርትመንት መምህሯ ተማሪወቿን አንድ Assignment መስጠት ፈለገች..!! ተማሪወቿን ድንች ይዘዉ እንዲመጡ አዘዘች ፡፡ ድንቾቹ ላይም የሚጠሏቸዉን ሰወች ስም እንዲፅፉ አዘዘቻቸዉ ፡፡

♠ የሚያመጡት የድንች ብዛትም በሚጠሏቸዉ ሰወች ብዛት ልክ እንዲሆን አለች ፡፡ በሁለተኛዉ ቀን አንዳንዶቹ 3 ሌሎች 5 ቀሪዎቹ ደግሞ 8 ድንቾቹን የሚጠሏቸዉን ሰወች ስም ፅፈዉ አመጡ ፡፡ መምሯ ደግሞ ከዛሬ ጀምሮ ለአንድ ሳምንት እኒህን ድንቾች በሻንጣችሁ ይዛችሁ ትዞራላችሁ ፡፡ ሽንት ቤት ስትሄዱ እንኳ መተዉ አትችሉም! ብላ አዘዘች ፡፡

♠ ቀኑ እየጨመረ ሲሄድ ድንቹ በመበላሸቱ ሽታዉ ይረብሻቸዉ ስለጀመረ ተማሪዎቹ ቅሬታ ማቅረብ ጀመሩ ፡፡ በተለይም 8 የያዙት ከሽታው በተጨማሪ ክብደቱ እንደበዛባቸው መናገር ጀመሩ ፡፡

♠ ከሳምንት በኋላ የአሳይመንቱ ገደብ ስላበቃ ተማሪወች ድንቹን አዉጥተዉ እንዲጥሉ ተፈቀደላቸዉ

♠ ከዛም መምህሯ እህ እንዴት ነበር ? ብላ ጠየቀቻቸዉ ፡፡ ሁሉም ማጉረምረም ጀመሩ ፡፡ "አረረረ ከክብደቱ ሽታዉ ፡፡ አረ በጣም ነዉ የሚያስጠላዉ" አሉ

♠ መምህሯ አያችሁ በልባችሁ የምትሸከሙት ጥላቻም እንዲሁ ነዉ ፡፡ ጥላቻ ልብን ይመርዛል ፡፡ በምትሄዱበት ሁሉም እየተከተለ ይረብሻችኋል ፡፡ ለአንድ ሳምንት የተበላሸ ድንችን ሽታ መቋቋም አልቻላችሁም ፡፡ አስቡት ደሞ በጥላቻ የተመረዘን ልብ እድሜ ልካችሁን ይዛችሁ ስትኖሩ !! አለቻቸዉ ፡፡

♠ ጥላቻን ከዉስጣችሁ አዉጡትና ከእዳ የፀዳችሁ ሁኑ!! እዉነተኛ ፍቅር እንከን አልባን ሰዉ ማፍቀር ሳይሆን ንፁህ ያልሆነን ሰዉ በንፁህነት መዉደድ ነዉና !!!

✿ ከተመቻችሁ Like/Comment

✿ «ሼር በማድረግ ለወዳጆ ያካፍሉ»

Address


Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Mekane-Selam Media - MSM posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

  • Want your business to be the top-listed Media Company?

Share