Sheko Wereda Communication Affairs

  • Home
  • Sheko Wereda Communication Affairs

Sheko Wereda Communication Affairs Sheko Wereda Communication Affairs

በፈዋሽነታቸው የሚታወቁ የሸኮ የባህል መድኃኒቶች በአገር አቀፍ ደረጃ እውቅና እንዲያገኙ በትኩረት እየተሰራ ነው============================ሐምሌ 10/2017ዓ/ም በፈዋሽነታቸ...
17/07/2025

በፈዋሽነታቸው የሚታወቁ የሸኮ የባህል መድኃኒቶች በአገር አቀፍ ደረጃ እውቅና እንዲያገኙ በትኩረት እየተሰራ ነው
============================
ሐምሌ 10/2017ዓ/ም በፈዋሽነታቸው የሚታወቁ የሸኮ የባህል መድኃኒቶች በአገር አቀፍ ደረጃ እውቅና እንዲያገኙ በትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝ የሸኮ ወረዳ ባህል ቱሪዝምና ስፖርት ጽህፈት ቤት ገለጸ።

ለተግባራዊነቱ ለባህል ህክም አዋቂዎች ስልጠና በሸኮ ወረዳ እየተሰጠ ነው።

የወረዳው ባህል ቱሪዝምና ስፖርት ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ተክሌ ቡይትን ፈዋሽ የሸኮ የባህል መድኃኒቶችን በመሰነድ ለትውልድ እንዲተላለፉ እንዲሁም በአገር አቀፍ ደረጃ እውቅና እንዲያገኙ በመስራት ላይ ይገኛል ብለዋል።

የሸኮ ማህበረሰብ የበርካታ የባህል እውቀት ባለቤት መሆኑን የመሰከሩት ኃላፊው ዘመናዊ ህክምና ባልነበረበት ወቅት የተለያዩ በሽታዎችን በመፈወስ ለማህበረሰቡ አገልግሎት ሲሰጡ መቆየታቸውን ገልጸዋል ።

የባህል ህክምና ከእጽዋቶች የሚቀመም መሆኑን ጠቅሰው በአካባቢ ጥበቃ ስራዎች እጽዋቶችን ማቆየት እንደሚገባ አንስተዋል ።

የባህል እውቀቶች ተጠብቀው እንዲቆዩ ፣ለትውልድ እንዲተላለፉ ፣እውቅና እንዲያገኙና የባህል እውቀት ባለቤቶችም ከዘርፉ ተጠቃሚ ለማድረግ ስልጠናው መዘጋጀቱን ገልጸዋል ።

የወረዳው አስተዳደር ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ተገኝ ይርዳ በበኩላቸው የሸኮ ማህበረሰብ ከጥንት ጀምሮ በባህል እውቀቱ ጤናውን ሲጠብቅ እንደነበረ አመልክተዋል ።

በሸኮ የባህል ህክምና በርካታ በሽታዎችን የሚፈዉሱ የአገር በቀል እውቀት ባለቤቶች መኖራቸው ገልጸው የወረዳው ባህል ቱሪዝምና ስፖርት ጽህፈት ቤት በባህል እውቀት ጥበቃ ዘርፍ እያከናወነ ላለው ተግባር አመስግነዋል ።

የስልጠናው ተሳታፊዎች መካከል የባህል ህክምና አዋቂ ወይዘሮ ጣይቱ ተረፈ፣አቶ ሃብታሙ ፈጠነ እና አቶ ተመስገን ቴንባብ በርካታ በሽታዎችን በባህል ህክምና ማዳን እንደሚቻል ተናግረዋል ።

የባህል ህክምና ሲሰጥ በእውቀትና በጥንቃቄ መሆኑን እንዳለበትም አክለዋል ።

ለባህል መድህኒት መሰረቱ እጽዋቶች በመሆናቸው የተለያዩ በሽታዎችን የሚፈውሱ እጽዋቶች በአንድ አካባቢ ተተክለው ጥበቃና ክብካቤ ማድረግ እንደሚገባ አሳስበዋል ።

የሸኮ የባህል ህክምና አዋቂዎች በስልጠናው መድረክ በርካታ ሰዎችን አክመው ማዳናቸውን ገልጸዋል ።

የባህል እውቀት እውቅና አግኝቶና ተሰንዶ ለትውልድ እንዲተላለፍ ለማድረግ በተሰጠው ስልጠና ግንዛቤ መጨበጣቸውን ተናግረዋል ።

ፖሊስ እግርኳስ ቡድን በአመራር እግርኳስ ቡድን ተሸነፈ!!!ስፖርት ለወዳጅነት በሚል መርህ የሸኮ ወረዳና ከተማ አስተዳደር አመራር ቡድን  እና የፖሊስ ቡድን እግርኳስ ግጥሚያ በአመራር ቡድን ...
16/07/2025

ፖሊስ እግርኳስ ቡድን በአመራር እግርኳስ ቡድን ተሸነፈ!!!
ስፖርት ለወዳጅነት በሚል መርህ የሸኮ ወረዳና ከተማ አስተዳደር አመራር ቡድን እና የፖሊስ ቡድን እግርኳስ ግጥሚያ በአመራር ቡድን አሸናፊነት ተጠናቀቀ።

የአመራር ቡድኑ ከፖሊስ ጋር ባካሄደው የወዳጅነት እግርኳስ ፊልሚያ 2 ለ1 ማሸነፍ ችሏል።

በተካሄደው ጨወታ አዝናኝ ትዕይንቶች ተከናውኗል ።

የወረዳው እና ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ሁለት ጊዜ የወረዳውና ከተማ አስተዳደሩን መምህራን እግርኳስ ቡድን ገጥሞ ሁለቱንም ጨዋታ አንድ አቻ ማጠናቀቅ ቢችልም ዛሬ በአመራር ቡድኑ ተረቷል።

በእንስሳት እርባታ ዘርፍ አርሶአደሩን ተጠቃሚ ለማድረግ እየተሰራ ነው===========================ፎሉር ፕሮጀክት በወረዳው  ለአየርንብረት ለውጥ ተስማሚ የእንስሳት እርባታ አርሶ...
16/07/2025

በእንስሳት እርባታ ዘርፍ አርሶአደሩን ተጠቃሚ ለማድረግ እየተሰራ ነው
===========================
ፎሉር ፕሮጀክት በወረዳው ለአየርንብረት ለውጥ ተስማሚ የእንስሳት እርባታ አርሶአደሩን ተጠቃሚ ለማድረግ በትኩረት እየሰራ ይገኛል ።

ከዘርፉ በወረዳው ያሉአርሶአደሮችን ተጠቃሚ ለማድረግ ለ120 ሞዴል አርሶአደሮች ከዘርፍ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ስልጠና በመስጠት ላይ ነው።

በወረዳው ፎሉር ፕሮጀክት አስተባባሪ አቶ ስዩም ሞላ ፕሮጀክቱ የአካባቢ ጥበቃን መርህ ያደረግ የግብርና ስራዎች በተጨማሪ በእንስሳት እርባታ አርሶአደሩን ተጠቃሚ ለማድረግ በትኩረት እየሰራ ይገኛል ብለዋል።

ኢትዮጵያ በአለም በእንስሳት ብዛት 10ኛ እንዲሁም ከአፍሪካ 1ኛ ደረጃ ላይ እንደምትገኝ የገለጹት አቶ ስዩም
የእንስሳት ብዛት በአገሪቱ ከፍተኛ ቢሆንም ከምርታማነት አንጻር ዝቅተኛ መሆኑን ጠቅሰዋል።

ምርታማነትን በማጎልበት አርሶአደሩን ተጠቃሚ ለማድረግ እንደአገር የምግብ ዋስትናው የተረጋገጠ በኢኮኖሚ የበለጸገ አርሶአደር ለመፍጠር እየተከናወኑ ያሉ ስራዎች ስኬታማ ለማድረግ እየተደረገ ያለውን ጥረት ፎሉር በመደገፍ ላይ እንደሚገኝ ነው የገለጹት።

ለገቢራዊነቱ ለሞዴል አርሶአደሮች ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር እንስሳት እርባታን የተመለከተ ስልጠና በወረዳው የእንስሳት ዘርፍ ባለሙያ በሳምራዊት አሰፋ ተሰጥቷል ።

በስልጠናው የሞዴል አርሶአደሮች የእንስሳት እርባታ ስራዎች ምክክር በማድረግ የእውቀትና ክህሎት ሽግግር ተደርጎበታል ።

ፎሉር ፕሮጀክት የገንዘብ ድጋፍ በማድረግ በወረዳው 100 ሴት አርሶአደሮች በማደራጀት የሸኮ ወረዳ ፎለር ፕሮጀክት የሴቶች ህብረት ስራ ዩኒየን እንዲመሰረት አድርጓል ።

የምግብ ዋስትና ስራዎቹ 7ሺህ ዶሮችን ለሴት አርሶአደሮቻችን ደጋፍ ማድረጉ ይታወሳል ።

አመራሮች  ከ ፖሊስ ጋር  ይጫወታሉ ስፖርት ለወዳጅነት በሚል መርህ የሸኮ ወረዳና ከተማ አስተዳደር አመራሮች እና  ፖሊስ እግርኳስ ግጥሚያ ያካሂዳሉ ።የወረዳው እና ከተማ አስተዳደር  ፖሊስ ...
15/07/2025

አመራሮች ከ ፖሊስ ጋር ይጫወታሉ
ስፖርት ለወዳጅነት በሚል መርህ የሸኮ ወረዳና ከተማ አስተዳደር አመራሮች እና ፖሊስ እግርኳስ ግጥሚያ ያካሂዳሉ ።

የወረዳው እና ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ሁለት ጊዜ የወረዳውና ከተማ አስተዳደሩን መምህራን እግርኳስ ቡድን የገጠመ ሲሆን ጨወታውን አንድ አቻ አጠናቋል።

ነገ ሐምሌ 9/2017ዓ/ም አመራሮች ከፖሊስ የሚያደርጉትን የእግርኳስ ግጥሚያ ከቀኑ 5 ጀምሮ ሸኮ ሁለገብ ስቴዲየም ተገኝተው እንዲመለከቱ ተጋብዘዋል ።

የክረምት ወራት እግርኳስ ሻምፒዮና በወረዳው በመካሄድ ላይ ነው============================ሐምሌ 8/2017ዓ/ም የክረምት ወራት እግርኳስ ሻምፒዮና በወረዳው በመካሄድ ላይ ነው...
15/07/2025

የክረምት ወራት እግርኳስ ሻምፒዮና በወረዳው በመካሄድ ላይ ነው
============================
ሐምሌ 8/2017ዓ/ም የክረምት ወራት እግርኳስ ሻምፒዮና በወረዳው በመካሄድ ላይ ነው።

የሸኮ ወረዳ ባህል ቱሪዝም እና ስፖርት ጽህፈት ቤት በወረዳው የክረምት ወራት እግርኳስ ሻምፒዮና እያካሄደ መሆኑን ገልጿል ።

የጽህፈት ቤቱ ኃላፊ አቶ ተክሌ ቡይትን እንደገለጹት በውድድሩ በወረዳው ያሉት ቀበሌዎች እግርኳስ ቡድኖች በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ ።

የክረምት ወራት ወጣቱ የእረፍት ጊዜው መሆኑን የጠቆሙት አቶ ተክሌ ስፖርቱ ከሚሰጠው የጤና ጥቅሞች ባሻገር አልባሌ ቦታ እንዳይውል ፣አንድነት፣ወንድምማማችነት እንዲሁም የጎለበተ ማህበራዊ መስተጋብር ይፈጥራል ሲሉ ገልጸዋል ።

በአራት ምድብ ተከፍለው ውድድሩ በሸኮ ሁለገብ ሜዳ እየተካሄደ የሚገኘውን ጨዋታ ህብረተሰቡ በመታደም ወጣቶችን ሊያበረታታ ይገባል ብለዋል።

በወረዳው ከ120 በላይ ሞዴል አርሶአደሮች የተሳተፉበት ስልጠና በሸኮ ወረዳ ፎለር ፕሮጀክት እየተሰጠ ነው============================በወረዳው ከ120 በላይ ሞዴል አርሶአደሮች...
15/07/2025

በወረዳው ከ120 በላይ ሞዴል አርሶአደሮች የተሳተፉበት ስልጠና በሸኮ ወረዳ ፎለር ፕሮጀክት እየተሰጠ ነው
============================
በወረዳው ከ120 በላይ ሞዴል አርሶአደሮች የተሳተፉበት ስልጠና በፎለር ፕሮጀክት እየተሰጠ ይገኛል ።

የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋም ሞዴል እና ለኑሮ ተስማሚ አረንጋዴ አካባቢ ፣ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የምግብ ዋስትናው የተረጋገጠ ማህበረሰብ መፍጠር የስልጠናው ዓላማ መሆኑ ተጠቁሟል ።

ፎለር ፕሮጀክት በወረዳው ከ120 በላይ ለሚሆኑ ሞዴል አርሶአደሮች በሰጠው ስልጠና የተፈጥሮ ሃብትና ክብካቤ እንዲሁም ጥምር እርሻን አስመልክቶ ለአርሶአደሮቹ ግንዛቤ ተፈጥሮላቸዋል ።

የወረዳው የተፈጥሮ ሃብት ኤክስፐርት አቶ ፍቃዱ ታደሰ እንደገለጹት የአካባቢ ጥበቃና ክብካቤን አስመልክቶ በሰጡት ስልጠና የተፈጥሮ ሃብቶችን ክብካቤ በማድረግ የተፈጥሮ ሚዛንን መጠበቅ ይገባል።

በአንድም ሆነ በሌላ መንገድ መሬት ይጎዳል የተጎዳ መሬትም ክብካቤ በማድረግ ወደቀድሞው ገጽታ መመለስ እንደሚቻል አብራርተዋል።

የወረዳው ፎለር ፕሮጀክት የቡና ልማት አስተባባሪ አቶ ምስራቅ ከበደ አካባቢ ጥበቃን መርህ ያደረገ ጥምር እርሻን አስመልክተው ስልጠና ሰጥተዋል።

ሸኮ ወረዳ ቡና አምራች በመሆኑ አርሶአደሩ የተፈጥሮ ሃብቶችን ጠብቆ ቡናን በብዛትና በጥራት አምርቶ እንዲጠቀም በፎለር ፕሮጀክት
ድጋፍ እየተደረገላቸው እንደሚገኝ አመልክተዋል ።

የሸኮ ወረዳ ፎለር ፕሮጀክት አስተባባሪ አቶ ስዩም ሞላ "የተራቆቱ አካባቢዎች እንዲያገግሙና ወደ ቀድሞ አረንጓዴ ገጽታቸው እንዲመለስ እንዲሁም የቡና ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የአርሶአደሩን ኑሮ ለማሻሻል በወረዳው አምስት ቀበሌዎችን ተደራሽ በማድረግ እየተሰራ ይገኛል"ብለዋል።

ከአርሶ አደሩ ተጠቃሚነት ባሻገር እየተከናወኑ ባሉት የአካባቢ ጥበቃ ስራዎች ብዛህይወትን ከመጥፋት መታደጉን አክለዋል ።

የሸኮ ወረዳ ያሉት ጥብቅ የተፈጥሮ ደኖች ተጠብቀው ለትውልድ እንዲተላለፍ ብሎም ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ስነምህዳር ለመፍጠር እየተከናወኑ ያሉትን ተግባራትን ስኬታማ ለማድረግ ፕሮጀክቱ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያደረገ ይገኛል ።

ክረምቱን ተከትሎ የትራንስፖርት አገልግሎት እንዳይስተጓጎል ከተማ አስተዳደሩ የመንገድ ጥገና ስራዎችን በትኩረት እየሰራ ነው፦አቶ ከድር ይማም============================ሐምሌ ...
15/07/2025

ክረምቱን ተከትሎ የትራንስፖርት አገልግሎት እንዳይስተጓጎል ከተማ አስተዳደሩ የመንገድ ጥገና ስራዎችን በትኩረት እየሰራ ነው፦አቶ ከድር ይማም
============================
ሐምሌ 8/ 2017 ዓ.ም
ክረምቱን ተከትሎ የትራንስፖርት አገልግሎት እንዳይስተጓጎል የሸኮ ከተማ አስተዳደር የመንገድ ጥገና ስራዎችን በትኩረት እየሰራ እንደሚገኝ ተመላከተ።

የሸኮ ከተማ አስተዳደር በከተማው በርካታ የመሰረተ ልማት ስራዎችን በትኩረት በማከናወን ላይ እንደሚገኝ የገለጹት የከተማ አስተዳደሩ ኢንተርፕራይዝ ትራንስፖርት ከተማ ግብርና ልማት ህብረት ስራ ክላስተር አስተባባሪ አቶ ከድር ይማም ለነዋሪዎች ምቹ ከተማ ለመፍጠር የኮሪደር፣የውስጥ ለውስጥ መንገድ ከፈታ እና ሌሎች ልማት የተሰራ ይገኛል ።

ኮሪደርና የውስጥ ለውስጥ መንገድ ልማት ስራዎች ባሻገር ዋና መንገድ በክረምት ዝናብ ምክንያት ተበላሽቶ የትራንስፖርት አገልግሎቱ እንዳይስተጓጎል በከተማ አስተዳዳሩ ጥገና እየተደረገለት ይገኛል ብለዋል።

የሸኮ ከተማ አስተዳደር መዋቅር የለውጡ መንግስት ትሩፋት ሲሆን የህብረተሰቡን የልማት ፣መልካም አስተዳደር እና ዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ተሳታፊ እና ተጠቃሚ ለማድረግ እየተከናወኑ ያሉት ተግባራትም ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ነው አቶ ከድር የገለጹት ።

ፕሮጀክቱ የግብርና ዘርፉን በመደገፍ ለማህበረሰቡ ኑሮ መሻሻል እየሰራ እንደሚገኝ የወረዳው ግብርና አካባቢ ጥበቃና ህብረት ስራ ጽህፈት ቤት አስታወቀ ==========================...
15/07/2025

ፕሮጀክቱ የግብርና ዘርፉን በመደገፍ ለማህበረሰቡ ኑሮ መሻሻል እየሰራ እንደሚገኝ የወረዳው ግብርና አካባቢ ጥበቃና ህብረት ስራ ጽህፈት ቤት አስታወቀ
===========================
ሐምሌ 8/2017ዓ/ም ፎለር ፕሮጀክት የግብርና ዘርፉን በመደገፍ ለማህበረሰቡ ኑሮ መሻሻል እየሰራ እንደሚገኝ
የወረዳው ግብርና አካባቢ ጥበቃና ህብረት ስራ ጽህፈት ቤት አስታወቀ ።

ለሞዴል አርሶአደሮች የእውቀትና ክህሎት ማጎልበቻ ስልጠና በሸኮ ወረዳ በፎለር ፕሮጀክት እየሰጠ ነው።

የወረዳው ግብርና አካባቢ ጥበቃና ህብረት ስራ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ታታሪው ዘርክንስ ፕሮጀክቱ የግብርና ዘርፉን በመደገፍ ለማህበረሰቡ ኑሮ መሻሻል እየሰራ ይገኛል ብለዋል።

የግብርና ሁሉም ዘርፎችን ያቀፉ ምርትና ምርታማነትን የሚያሻሽሉ በአጠቃላይ ግብርናን የሚያዘመኑ ተግባራትን እያከናወኑ እንደሚገኝ ገልጸዋል ።

ፕሮጀክቱ በወረዳው የአካባቢ ጥበቃን መሰረት ያደረገ ዘርፈ ብዙ የግብርና ስራዎችን በመደገፍ ከግለሰብ እስከ አገር የሚጠቅሙ ፋይዳ ያላቸውን ተግባራት ማከናወኑን ጠቅሰዋል ።

ከአካባቢ ጥበቃ ስራዎች ባሻገር የቡና ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የአርሶአደሩን ኑሮ ለማሻሻል ከ6ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ በማድረግ 6 የቡና መጎንደያ ማሽን፣12 የቡና ጉርጓድ መቆፈሪያ ማሽን፣ከ500 በላይ መጋበዝ ፣ከ7ሺህ በላይ ዶሮችን እና ሌሎች ግብዓቶችን ለማህበረሰቡ ድጋፍ ማድረጉን አመልክተዋል ።

ፎለር ፕሮጀክት ለማህበረሰቡ ህይወት መሻሻል እያከናወነ ባለው ተግባራት ተስፋ ሰጪ ውጤቶች እየተመዘገቡ እንደሚገኝ በመጠቆም ሞዴል አርሶአደሮች ስልጠናውን በአግባቡ እንዲከታተሉ አስገንዝበዋል ።

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልላዊ መንግስት ፎለር ፕሮጀክት አስተባባሪ በእውቀቱ ኃይሌ (ዶ/ር) እንደገለጹት ፕሮጀክቱ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ስነ ምህዳር ለመፍጠር እየሰራ ይገኛል።

ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ስነ ምህዳር
ለመፍጠር ወይም የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋም አካበቢ ለመፍጠር የአካባቢ ጥበቃና ክብካቤ ስራዎች በትኩረት በመከናወን ላይ እንደሚገኝ ገልጸዋል ።

የምግብ ዋስትናው የተረጋገጠ በኢኮኖሚ የበለጸገ ማህበረሰብ ለመፍጠር ከስነ ህይወታዊ የአፈር እና ውኃ ጥበቃ ስራዎች በተጨማሪ አርሶአደሩን የሌማት ትሩፋት ተጠቃሚ ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን በመግለጽ ሞዴል ሰልጣኝ አርሶአደሮች ከስልጠናዎች ያገኙትን እውቀትና ክህሎት ለሌሎች አርሶአደሮች ተደራሽ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው ገልጸዋል ።

ፎለር ፕሮጀክት በአገር አቀፍ ደረጃ 22 ፣በክልል 6 በዞን ደረጃ 3 ወረዳዎችን የሸኮ ወረዳን ጨምሮ ተደራሽ በማድረግ የአርሶ አደሩን ኑሮ ለማሻሻል በርካታ ተግባራትን በማከናወን ላይ ይገኛል ።

በፍለር ፕሮጀክት ሞዴል የአርሶአደሮች ስልጠና መድረክ የክልሉ ፎለር ፕሮጀክት አስተባባሪ በእውነቱ ኃይሌ(ዶ/ር)፣በክልሉ የፕሮጀክቱ ፋይናንስ አስተባባሪ አቶ ታረቀኝ አስፋው፣የወረዳው ግብርና አካባቢ ጥበቃና ህብረት ስራ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ታታሪው ዘርክንስን ጨምሮ ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል ።

የክረምቱን ዝናብ ተከትሎ ሊከሰቱ ከሚችሉ አደጋዎች ህብረተሰቡ ቅድመ ጥንቃቄ ማድረግ እንዳለበት ተገለጸ============================የክረምቱን ዝናብ ተከትሎ ሊከሰቱ ከሚችሉ አደ...
14/07/2025

የክረምቱን ዝናብ ተከትሎ ሊከሰቱ ከሚችሉ አደጋዎች ህብረተሰቡ ቅድመ ጥንቃቄ ማድረግ እንዳለበት ተገለጸ
============================
የክረምቱን ዝናብ ተከትሎ ሊከሰቱ ከሚችሉ አደጋዎች ህብረተሰቡ ቅድመ ጥንቃቄ ማድረግ እንዳለበት ተገለጸ ።

ወረዳው እንደገለጸው የክረምት ወራት ዝናብን ተከትሎ በክልሉ፣በዞኑና አጎራባች አካባቢዎች የመሬት መንሸራተት፣ የጎርፍ አደጋ እንዲሁም የመሬት ናዳ ተከስቷል።

የሸኮ ወረዳ ምክትል አስተዳዳሪ እንዲሁም ሰላም ጸጥታና ሚሊሻ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ በዱሉ ቴርካ እንደገለጹት የክረምቱን ተከታታይነት ያለው ዝናብ መጣልን ተከትሎ የተፈጥሮ አደጋ ስጋት ያለባቸው አካባቢ የሚኖሩ የህብረተሰብ ክፍሎች ጥንቃቄ ማድረግ እንዳለባቸው ተናግረዋል ።

በአይበራ ሳንቃ እና በወረዳው ሌሎች አካባቢዎች መሰል የመሬት መንሸራተት አደጋ አምና የተከሰተ መሆኑን በዋቢነት ያስረዱት ምክትል አስተዳዳሪው የአደጋ ምልክቶች ሲስተዋሉ ህብረተሰቡ ከአካባቢው በአፋጣኝ መራቅ እና ለሚመለከተው አካል ፈጥኖ መረጃ ማድረስ እንደሚገባ ጠቁመዋል ።

የወረዳው ግብርና አካባቢ ጥበቃና ህብረት ስራ ጽህፈት ቤት አደጋ ስጋት ቅነሳና ቅድመ ጥንቃቄ ስራ ሂደት አስተባባሪ አቶ ባይነሳኝ አሰፋ የቅድመ ጥንቃቄ መልዕክቶች በጽህፈት ቤታቸው በኩል ለህብረተሰቡ ተላልፏል ።

መሰል የተፈጥሮ አደጋዎች አምና በወረዳው እና በሸኮ ከተማ አስተዳደር መከሰቱን ያመለከቱት የአደጋ ስጋት ባለሙያው አደጋዎችን ቀድሞ ለመከላከል እንዲሁም ቢከሰት እንኳ በህብረተሰቡ ላይ የከፋ ጉዳት እንዳያደርስ በወረዳውና ከተማ አስተዳደሩ በቅንጅት እየተሰራ ይገኛል ።

ዜና እረፍት የሸኮ ወረዳን ማህበረሰብ ለረጅም ዓመታት በመምህርት ሞያ ያገለገሉት አንጋፋዋ መምህርት ጊፍቶ ናስር ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ።የሸኮ ወረዳ ትምህርት ጽህፈት ቤት በመምህርት ጊፍቶ ...
14/07/2025

ዜና እረፍት
የሸኮ ወረዳን ማህበረሰብ ለረጅም ዓመታት በመምህርት ሞያ ያገለገሉት አንጋፋዋ መምህርት ጊፍቶ ናስር ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ።

የሸኮ ወረዳ ትምህርት ጽህፈት ቤት በመምህርት ጊፍቶ ናስር ህልፈተ ህይወት የተሰማውን ጥልቅ ሃዘን ገልጿል።

ጽህፈት ቤቱ በመግለጫው ጊፍቶ ናስር በመምህርነት ሞያ የሸኮን ማህበረሰብ ለረጅም ዓመታት ማገልገላቸውን አስታውቋል ።

በህልፈተ ህይወታቸው የተሰማውን ጥልቅ ሃዘን የገለጸው ጽህፈት ቤቱ ለወዳጅ ዘመድ መጽናናትን ተመኝቷል።

የህብረተሰቡን የልማት ፍላጎቶች ለማሟላት  ግብርን  የህልውና ጉዳይ አድርጎ መስራት እንደሚገባ ተመላከተ ===========================ሐምሌ 2/2017ዓ/ም የሸኮ ወረዳ ገቢዎች ...
09/07/2025

የህብረተሰቡን የልማት ፍላጎቶች ለማሟላት ግብርን የህልውና ጉዳይ አድርጎ መስራት እንደሚገባ ተመላከተ
===========================
ሐምሌ 2/2017ዓ/ም የሸኮ ወረዳ ገቢዎች ጽህፈት ቤት እና የወረዳው ኢንዱስትሪ እና ንግድ ጽህፈት ቤት የ2017/18 የግብር መክፈያና የንግድ ፍቃድ እድሳት ንቅናቄ መድረክ አካሂደዋል ።

በተካሄደው የግብር እንዲሁም ንግድ ፍቃድ እድሳት ንቅናቄ መድረክ የወረዳው የ2017 ዓ/ም አፈጻጸም እና የ2018ዓ/ም እቅድ ላይ ውይይት ተደርጎበታል ።

የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ አሪ ጉርሙ እንደገለጹት የህብረተሰቡን የልማት ፍላጎቶች ለማሟላት ጤናማ የንግድ ስርዓትን በመፍጠር ግብርን የህልውና ጉዳይ አድርጎ መስራት ይገባል ብለዋል።

የህብረተሰቡ የልማት ፍላጎት እየጨመረ መምጣቱን የገለጹት ዋና አስተዳዳሪው ፍላጎቶቹን ለማሟላት ወረዳው ከሚያመነጨው የገቢ አማራጮች ሁሉ ገቢ ለመሰብሰብ ባለድርሻ አካላት ተቀናጅተው መስራት እንዳለባቸው አሳስበዋል ።

የወረዳው ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊና የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ገዛኸኝ ኡፕም እንደገለጹት መንግስት የኢትዮጵያን እድገት እና ብልጽግና የሚያረጋግጡ በርካታ የልማት ስራዎች በመከናወን ላይ ይገኛል ።

በወረዳው የተጀመሩ የልማት፣የዴሞክራሲ እና የመልካም አስተዳደር ስራዎችን ገቢራዊ በማድረግ የህዝቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ገቢ ላይ ትኩረት ሰጥቶ መስራት እንደሚገባ አመልክተዋል ።

የወረዳው ገቢዎች ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሲሳይ መርፌ በተገባደደው በጀት ዓመት ከ128 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን ገልጸው የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ይበልጥ ለማረጋገጥ የገቢ አፈጻጸሙን ማሻሻል ይገባል ብለዋል።

ባለድርሻ አካላት ሚናቸው ከፍተኛ መሆኑን ተረድተው ኃላፊነታቸውን ትኩረት በመስጠት መወጣት መቻል እንዳለባቸው ጠቅሰዋል ።

በ2017 ዓ/ም በገቢ አሰባሰብ እና ንግድ ፍቃድ እድሳት የተከናወኑ ተግባራት አፈጻጸም በጥንካሬና በድክምት ተለይተው ምክክር ተደርጎበታል ።

በተደረገው ውይይት የማዘጋጃ ቤት አፈጻጸም ፣የገጠር መሬት ግብር፣የማዕድን ገቢ አፈጻጸም ዝቅተኛ መሆኑ ነው የተገለጸው።

ትምህርት፣ጤና፣ግብርና ፣ውኃ ማዕድንና ኢነርጅ ጽህፈት ቤቶች በኩል መሰብሰብ ያለበትን ሃብት በአግባቡ መሰብሰብ እንደሚገባ ውይይት ተደርጎበታል ።

በመጨረሻም በተገባደደው በጀት ዓመት የተስተዋሉ ጉድለቶችን የሚያርሙ መልካም አፈጻጸሞችን የሚያስቀጥሉ አቅጣጫዎች ተቀምጠው መግባባት ላይ ተደርሶ መድረኩ ተጠናቋል።

በሸኮ ወረዳ የ2017/18 የግብር መክፈያና የንግድ ፍቃድ እድሳት ንቅናቄ  መድረክ በመካሄድ ላይ ነው==========================ሐምሌ 2/2017ዓ/ምበሸኮ ወረዳ የ2017/18 ...
09/07/2025

በሸኮ ወረዳ የ2017/18 የግብር መክፈያና የንግድ ፍቃድ እድሳት ንቅናቄ መድረክ በመካሄድ ላይ ነው
==========================
ሐምሌ 2/2017ዓ/ም
በሸኮ ወረዳ የ2017/18 የግብር መክፈያና የንግድ ፍቃድ እድሳት ንቅናቄ መድረክ እየተካሄደ ይገኛል ።

በበጀት ዓመቱ በወረዳው ከ251 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ለመሰብሰብ መታቀዱ ተጠቁሟል ።

የሸኮ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አሪ ጉርሙ እንደገለጹት ወረዳው ከሚያመነጨው ኢኮኖሚ ግብርን በተገቢው በመሰብሰብ የህዝቡን የልማትና መልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ለመመለስ በትኩረት እየተሰራ ይገኛል ።

መንግስት ከሚሰበስበው ገቢ የበለጸገ አገር ለመፍጠር እንደአገር በርካታ ብልጽግናን የሚያረጋግጡ የልማት ስራዎችን ማከናወን ተችሏል ።

ማህበረሰቡን የልማት ትሩፋቶች ተጠቃሚ ለማድረግ በወረዳው በርካታ የልማት ስራዎች በመከናወን ላይ መሆናቸውን የጠቆሙት ዋና አስተዳዳሪው ከገቢ አማራጮች ሁሉ ገቢ ለመሰብሰብ ባለድርሻ አካላት ተቀናጅተው መስራት እንደሚጠበቅባቸው አሳስበዋል ።

በወረዳው ከገቢ አማራጮች ሁሉ ገቢ ከመሰብሰብ አንጻር ያሉትን ጉድለቶች በማረም ከገጠር መሬት ግብር ፣ ከእርሻ መሬት እንዲሁም ከሌሎችም ምንጮች የሚሰበሰበው ገቢ ማስደግ እንደሚገባ አስገንዝበዋል ።

የወረዳው ገቢዎች ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሲሳይ መርፌ እንደገለፁት በ2018 በጀት ዓመት 251 ቢሚሊዮን 455 ሺህ 309 ብር ገቢ ለመሰብሰብ ታቅዶ እየተሰራ እንዲገኝ ገልጸዋል ።

ከመንግሥት ትሬጀሪ እየወረደ ያለው በጀት እየቀነሰ መምጣቱን ጠቅሰው የህብረተሰቡን የልማት ፍላጎት ለማሟላት ባለድርሻ አካላት የበኩላቸውን ድርሻ በቁርጠኝነት ሊወጡ ይገባል ብለዋል።

የበጀት ዓመቱ የደረጃ "ሐ" ግብር መክፈያ ጊዜ ከሐምሌ አንድ እስከ ሐምሌ ሰላሳ 2017ዓ/ም መሆኑን ጠቁመው ፤የንግዱ ማህበረሰብ በወቅቱ ግብሩን በመክፈል ከመጨናነቅ እና መቀጮ ራሳቸውን ሊከላከሉ እንደሚገባ ተናግረዋል ።

የወረዳው ኢንዱስትሪ ንግድ ልማት ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሃብታሙ ጌታነው እንደገለጹት
በ2018 በጀት ዓመት ለ135 አዲስ ነጋዴዎች ንግድ ፍቃድ ለመስጠት ታቅዷል።በተጨማሪም ለ395 ነባር ነጋዴዎች የንግድ ፈቃድ እድሳት አገልግሎት እንደሚሰጥ ተናግረዋል ።

የግብር አከፋፈል እና የንግድ ፍቃድ እድሳት ስርዓትን ፈጣንና ቀልጣፋ ለማድረግ ዲጂታል የክፍያ እና ፍቃድ እድሳት ተግባራዊ እንደሚደረግ ነው የተገለጸው።

በገቢ እና ንግድ ንቅናቄ መድረክ የወረዳው አስተባባሪ ኮሚቴዎች፣አመራሮች፣የቀበሌ አስተዳዳሪዎች፣ስራ አስኪያጆች ፣የገቢ እና ንግድ ጽህፈት ቤት ማኔጅመንት አባላትን ጨምሮ ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል ።

Address


Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Sheko Wereda Communication Affairs posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

  • Address
  • Alerts
  • Claim ownership or report listing
  • Want your business to be the top-listed Media Company?

Share