Black Kingdom

  • Home
  • Black Kingdom

Black Kingdom Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Black Kingdom, Digital creator, .

 !!  እንደሚባል     ላይ በተጨባጭ ስለተረዳን ካሁን በኃላ የአቡራሞ ወረዳ በቀላሉ  ፣ ብልፅግናን መስሎ ነገር ግን   በማከናወን ላይ የሚገኙ ነው ።👉እስቲ ፈጣሪ ያሳያችሁ ፣ አቶ  ፣_...
13/06/2025

!!

እንደሚባል ላይ በተጨባጭ ስለተረዳን ካሁን በኃላ የአቡራሞ ወረዳ በቀላሉ ፣ ብልፅግናን መስሎ ነገር ግን በማከናወን ላይ የሚገኙ ነው ።
👉እስቲ ፈጣሪ ያሳያችሁ ፣ አቶ ፣_ከ300_ሄክታር በላይ መሬት ቀሪ የሌላቸው መስሎት ይደብቅና ህዝብን እያጉላላ ለካ በየጊዜው ከሌቦችና አጭበርባሪዎች ጋር በስልክና በአካል እየተነጋገረ ፣ ሙሉ የህዝብን መሬት ያለ ምንም ማስረጃ ለግለሰቡ ለማስረከብ ከፍተኛ ጥረት ማድረግ ላይ አንደሆኑ ሁሉ ።
👉ለምሳሌ ያህል #በሀሙስ ቀን የአንድ ወረዳ ሰው ተታለው ፣ የህዝብን መሬት የወረረ ግለሰብም የአቡራሞ ቀበሌ ልጅ ስለሆነ ብቻ የህዝብ መሬት ነው በማለት ከዞን ተደውሎለት የሁሉም ጆሮ እየሰማ በተናገራቸው ቃላቶች ብቻ ጨዋታው የት እንደሆነ ተገንዝበናል ።
ይህም #በማስረጃነት ሊያዝልን ይገባል እንላለን ።
👉ሲጀመር የጋምቤላ ተወላጅ ቢሆን ኖሮ ከቤተሰቡ የወረሰውን መሬት ይባላል ነበር ፣ ግን ሰው መሬቱን በምን አግባብ ነው ያገኘው እንኳ ተብሎ የማጣራት ስራ መስራት ሲቻል በተቃራኒ ግን ሽፋን መስጠት ነው የታየ ልብ በሉ።
👉ደግሞ የቀበሌ ብሎ የሱ ተላላኪ የሆነው ከቀበሌ አመራሮች ሁሉ ተልኳል ።
በዚህ አንድ ነገር ልንታዘብ ይገባል ።
ግን ይባላል የለም !! ባይገርማችሁ (እንደ_መታጀቢያ_ክላሲካል) እንሰማለን ስሉ ተደምጠዋልና ህሊና ያለው ይታዘበን።
ስለሆነም ካለ እኛ ፣_አንጠላም፣ ግን በዚህ የህዝብ መሬት ጋር ተያይዞ ያለውን ጨዋታ ሁሉ ለገለልተኛ የፍትህ ተሰጥቶ፣ ይፋ የሆነ የማጣራት ስራ ካልተሰራ ቀኑን ጠብቆ ይጋለጣል፣ የህዝብ እንባ ደርቆ አይደርቅም።

09/06/2025

#ስልጣንን ለማራዘም ብለን የሚስኪኑን ህዝብ ሀብት አንሸጥ !!

06/06/2025

06/06/2025

!❤

29/04/2025
01/04/2025

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ በባለፉት ሰባት አመታት ውስጥ ምን አሉ!!

“ወንዝ ዳር ቆሞ የምትጠጣውን ውኃ ከሰማይ እስኪዘንብ እንደምትጠብቅ ወፍ፣ እግር እና እጃችንን አሣሥረን በመቀመጥ መና ከሰማይ የምንጠብቅ ሳይሆን፤ እየለፋን እየተጋን በትጋታችን ልክ ውጤታማ የምንሆንበት ነገር እንዲፈጠር ወጣቶቻችን በከፍተኛ እልህ እንድትተጉ ከአደራ ጭምር ላሳስብ እወዳለሁ።”

"አንድ ግለሰብ ሐሳቡ ቢመረዝ ራሱን ብቻ ሳይሆን አከባቢውንም ያጠፋል። አካባቢን ከማጥፋት ራሱን ለመታደግ አእምሮ እና ውስጥን ማጽዳት እንዴት ይቻላል? ሰው የተመረዘ ምግብ እያወቀ አይበላም። የተመረዘ ምግብ እንደሚገድለው ያውቃል። ሳያውቅ እንኳን የበላ እንደሆነ የተመረዘውን ነገር ከውስጡ ከደሙ ለማውጣት ይሞክራል። መዳኃኒት ይወስዳል። ነገር ግን ወደ አእምሮ የሚወሰድ የተመረዘ ሐሳብ ምን ያክል ድርጊቶቻችን እንደሚወስን ግንዛቤው አናሳ ነው። የሁሉ ድርጊት መሠረቱ ሐሳብ ነው።"

“አዲስ አበባን እውነተኛ አዲስ አበባ እናደርጋታለን! እንደ ስሟ እውነተኛ አዲስ አበባ ትሆናለች፤ ካልን በኋላ የአፍሪካ መዲና መሆኗን ለማረጋገጥ ሰፋፊ ሥራዎች እየተሠሩ ነው። ዛፍ መትከል፣ ማጽዳት፣ ፓርኮች ማስፋት ይህን ሥራ በሚቀጥሉት ሦስት ዓመታት ወደሚቀጥለው ‘ሌየር’ ካሳደግነው፣ ሙሉ በሙሉ አንድነት ፓርክ ግቢውን ከያዘ፤ ይሄንን ሥራውን ጨርሶ ለሕዝብ ክፍት ከሆነ፣ ቦሌ መንገድ ላይ የጀመርነው ሥራ ካሣለጥን እና እስክ እንጦጦ ከወጣን፤ ካለ ምንም ጥርጥር በየትኛውም የአፍሪካ ሀገር በዚህ ደረጃ የቱሪስት መስሕብ መሆን የሚችል፤ ታሪክ ያለው፣ ዛፍ ያለው፣ እጅግ የሚያምር የአየር ንብረት ያለው እና መልካ ምድሩ የተለየ ውበት ያለው ቦታ ያለ አይመስለኝም። ካለም ለኔ አንደኛው ቦታ ይሄ ነው።"

“ስንሠራ የሚረዱ፣ የሚርዱ፣ የሚያርዱ አሉ። ስንሠራ የሚረዱ ባያግዙም ይገባቸዋል። የሚረዱን ደግሞ በጊዜ፣ በገንዘብና በዕውቀት የሚያግዙን ናቸው። የሚርዱት ብልጽግናችን የሚያስጨንቃቸው ናቸው። የሚያርዱት ግን “እውነትና ንጋት እያደር ይጠራል” የሚለውን የኢትዮጵያ አባባል “ውሸትና ምሽት እያደር ይነግሣል” ብለው ለመተካት የሚጥሩ ብቻ ናቸው። እኛ ግን የሚረዱንን አስከትለን፣ ለሚረዱን ታምነንና ሳንሰርቅ በንጹሕ ልብ እያገለገልን፣ የሚርዱትን አጽናንተን፣ የሚያርዱትን ደግሞ አስታግሠን፣ ሥራችንን እንቀጥላለን። ኢትዮጵያ እንደ ቅኔ ነች፤ እኛ እንደ ገጣሚ ነን። አሁን የምንጽፈው ታሪክ ዛሬ ሳይሆን በልጆቻችን ሲተረክ ይኖራል። እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ዛሬ ቢነቃና ዐሻራ ላይ ቢያተኩር፤ አዲስ ሥራ ቢሠራ፤ ቢተባበር፣ ቢቀናጅ ኢትዮጵያ እውነትም የአፍሪካ ፈርጥ መሆን ትችላለች።”

"በተቻለ መጠን የዚህ አመራር ዋነኛ ዓላማ መሆን ያለበት የተሸፈኑ ነገሮችን ገለጥ ገለጥ አድርጌ ይቺን ሀገር እንደ ስሟ ትልቅ አድርጌ ኢትዮጵያውያን እንዳይለምኑ፣ እንዳይሰደዱ ማድረግ እችላለሁ። መሬት አለን፣ ውኃ አለን፤ ሰብሰብ አድርገን ብንሠራ ቢያንስ “ስንዴ ብርቅ አይሆንብንም” ብሎ የቆረጠ፤ የወሰነ፤ ሊመራ የተዘጋጀ ኃይል እንዲሆን ነው የሚፈለገው። ይሄን ማሳካት ከቻላችሁ አዲሱ ትውልድ ደግሞ ላቅ ያለ ራእይ ስለሚሰንቅ በዚያው ጉዞ ውስጥ ይገባ እና ይበልጥ ያማረ ከምናስበውም በብዙ የላቀ ነገር ሊፈጠር ይችላል። ጫናዎች፣ መከራዎች፣ ግፊቶች ብታምኑም ባታምኑም፣ የኢትዮጵያ ብልጽግና የተዘጋውን መስኮት የሚከፍቱ እንጂ የሚያዳፍኑ ሊሆኑ አይችሉም፡፡"

"ኢትዮጵያ ትበለጽጋለች፤ የአፍሪካ የኃይል ምንጭ ትሆናለች፤ በአፍሪካ

01/04/2025

በለውጡ እየተወሰዱ የሚገኙ የትምህርት ተደራሽነትና ጥራት ማሻሻያ እርምጃዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የክልሉ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ተመስገን ዲሳሳ (ዶ/ር) ተናገሩ
**************
(ባምባሲ፣ መጋቢት 23/2017 ዓ.ም) ሀገራዊ ለውጡን ተከትሎ የትምህርት ተደራሽነትና ጥራትን ለማሻሻል እየተወሰዱ በሚገኙ እርምጃዎች የተገኙ ስኬትችን አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባ የክልሉ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ተመስገን ዲሳሳ (ዶ/ር) ተናገሩ።

የክልሉ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ተመስገን ዲሳሳ (ዶ/ር) ባለፉት የለውጥ ዓመታት በትምህርት ዘርፉ የተከናወኑ ሥራዎችን እና የተገኙ ስኬቶችን አስመልክተው ከሚዲያ ጋር ቆይታ አድርገዋል።

የቢሮው ኃላፊ ተመስገን ዲሳሳ (ዶ/ር) ሀገራዊ ለውጡን ተከትሎ በፖለቲካ፣ በኢኮኖሚ፣ በመልካም አስተዳድር ዘርፎች በርካታ ስኬቶችን ተመዝግበዋል ብለዋል።

ለውጡን ተከትሎ በትምህርት ዘርፉ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለማረም በርካታ እርምጃዎች ተወስደዋል ያሉት ኃላፊው፣ የትምህርት ፍኖተ ካርታ፣ የትምህርት ፖለሲ፣ የትምህርት አዋጅን ጨምሮ ለትምህርት ጥራት ከፍተኛ ፋይዳ ያላቸው ማሻሻያዎች በትግበራ ላይ መሆናቸውን ተናግረዋል።

በክልሉ የትምህርት ተደራሽነትን ለማሻሻል በተሰሩ ሥራዎች የአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን ከ579 ወደ 620፣ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን ደግሞ ከ74 ወደ 94 ማሳደግ ተችሏል ብለዋል።

ቀደም ሲል ያልነበሩ የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች በሁሉም ትምህርት ቤቶች ማስጀመር መቻሉን ገልጸው፣ ይህም የትምህርት ጥራትን ለማሻሻል ከፍተኛ ፋይዳ እንዳለው አስረድተዋል።

በክልሉ የትምህርት ተደራሽነትና ጥራትን ለማሻሻል እየተወሰዱ በሚገኙ እርምጃዎች የተገኙ ስኬትችን አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባም ተመስገን ዲሳሳ (ዶ/ር) ተናግረዋል።

የለውጡ አንዱ ትኩረት የሆነው የተማሪዎች ምገባ መርሃ-ግብር በ45 ትምህርት ቤቶች መጀመሩን አንስተዋል።

በሀገር አቀፍ ደረጃ እየተካሄደ በሚገኘው የ"ትምህርት ለትውልድ" ንቅናቄ በቀዳማዊት እመቤት ጽ/ቤት እና በኦሮሚያ ክልል መንግስት ድጋፍ ሶስት ትምህርት ቤቶች ተገንብተው አገልግሎት እየሰጡ እንደሚገኙ ገልጸዋል።

በክልሉ አሁን የተፈጠረውን ሰላም ተከትሎ በጸጥታ ችግሩ የተጎዱ በርካታ ትምህርት ቤቶች በመልሶ ግንባታ ሥራ ጀምረዋል ያሉት ኃላፊው፣ ህብረተሰቡ ከ196 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት ድጋፍ አድርጓል ብለዋል።

የአፍ መፍቻ ትምህርትን በማጠናከር፣ በለውጡ የተገኙ የትምህርት ዘርፍ ስኬቶችን ለማጠናከር የጋራ ጥረት እንደሚደረግም ተናግረዋል።

#የክልሉ መንግስት ኮሙኒኬሽን

ጀግናው መሪያችን ክብር ላንተ ይሁን !!
20/03/2025

ጀግናው መሪያችን ክብር ላንተ ይሁን !!

Address


Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Black Kingdom posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

  • Address
  • Alerts
  • Claim ownership or report listing
  • Want your business to be the top-listed Media Company?

Share