Kembata World Wide Media Network

Kembata World Wide Media Network KWWMN registered inSouth Africa non-profit-organization.withheadquartersin Johannesburg,South Africa
(3)

Kembata worldwide Media Network registered in South Africa based as an independent and non-organization with headquarters in Johannesburg, South Africa. The organization is made up mainly of ambassadors, doctors, other professions that help in achieving to serve the Ethiopian community in South Africa It is an institution that provides genuine information and access to those in need.

የሰብዓዊነት ድል በሕፃፅ!የቲክቶክ ባለሙያዎች ከስክሪን ባሻገር ለወገናቸው አለኝታነታቸውን በተግባር እያሳዩ ነው! 🇪🇹💪[ሕፃፅ] — በኢትዮጵያ የማህበራዊ ሚዲያ ታሪክ አዲስ ምዕራፍ እየተፃፈ ...
24/12/2025

የሰብዓዊነት ድል በሕፃፅ!

የቲክቶክ ባለሙያዎች ከስክሪን ባሻገር ለወገናቸው አለኝታነታቸውን በተግባር እያሳዩ ነው! 🇪🇹💪

[ሕፃፅ] — በኢትዮጵያ የማህበራዊ ሚዲያ ታሪክ አዲስ ምዕራፍ እየተፃፈ ይገኛል። ታዋቂ የቲክቶክ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች (TikTokers) ለወገኖቻቸው ያላቸውን ፍቅር በቃላት ብቻ ሳይሆን፣ እልህ አስጨራሽ በሆነው የመስክ ስራ እና የቁሳቁስ ድጋፍ በተግባር እያሳዩ ነው።

በሕፃፅ መጠለያ የሚገኙ ወገኖቻችንን ለመታደግ የተጀመረው የገንዘብ ማሰባሰብ ዘመቻ ውጤት ከማምጣቱም ባለፈ፣ እነዚህ ወጣቶች እራሳቸው ቦታው ድረስ በመገኘት፦

* ከፍተኛ መጠን ያለው የምግብና የመድኃኒት ቁሳቁስ በጫንቃቸው በመሸከም፤

* ከወገኖቻቸው ጎን በመቆም መከራቸውን በመጋራት፤
* የእርዳታ እጆችን በማስተባበር ታላቅ አለኝታነታቸውን እያስመሰከሩ ነው።

ቲክቶክሮቹ የህዝብን ድምጽ በማስተጋባት በአጭር ጊዜ ውስጥ በሚሊዮኖች የሚቆጠር ገንዘብ ከማሰባሰባቸውም በላይ፣ አሁን ላይ በመስክ ተገኝተው እያደረጉት ያለው ርብርብ በብዙዎች ዘንድ አድናቆትን እያተረፈ ይገኛል።

"ኢትዮጵያዊነት ሲቸገሩ መድረስ ብቻ ሳይሆን፣ ችግሩን አብሮ መሸከምም ጭምር ነው!"

ይህ መልካም ተግባር እንዲቀጥል እና ለወገኖቻችን የሚደርሰው ድጋፍ እንዳይቆም ሁላችንም የበኩላችንን እናድርግ። የዚህ ደግ ተግባር ተሳታፊ የሆናችሁ ሁሉ ታሪክ ይዘክራችኋል!

ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ከ10 ወራት በኋላ የኮባልት ማዕድን ወደ ውጪ መላክ ጀመረችታሕሣሥ 14፣ 2018 ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ከ10 ወራት በኋላ የኮባልት ማዕድንን ዳግም ወደ ውጪ ሀ...
23/12/2025

ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ከ10 ወራት በኋላ የኮባልት ማዕድን ወደ ውጪ መላክ ጀመረች

ታሕሣሥ 14፣ 2018 ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ከ10 ወራት በኋላ የኮባልት ማዕድንን ዳግም ወደ ውጪ ሀገራት መላክ ጀመረች፡፡

ሀገሪቱ በዓለም አቀፍ ደረጃ የኮባልት አቅርቦት መጨመሩን ተከትሎ የማዕድኑ ዋጋ በመቀነሱ ወደ ውጪ መላክ አቋርጣ ቆይታለች፡፡

ማዕድኑ የስማርት ስልኮችና የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን ባትሪ ለማምረት እንደሚውል የተገለጸ ሲሆን፥ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ደግሞ በዓለም ቀዳሚዋ የኮባልት አምራች ሀገር ናት፡፡

የሀገሪቱ የገንዘብ ሚኒስትር ዱዱ ፍዋምባ እንዳሉት፥ ሀገሪቱ ለአስር ወራት ያህል አቋርጣው የነበረውን የኮባልት ማዕድን ኤክስፖርት ባለፈው አርብ ዳግም ጀምራለች፡፡

ሀገሪቱ በዓለም ከ70 በመቶ በላይ የኮባልት ማዕድንን እንደምታቀርብ የገለጹት ሚኒስትሩ፥ ነገር ግን ዋጋውን መወሰን አለመቻሏ ተቀባይነት የለውም ነው ያሉት፡፡

ምርቱን ለዓለምአቀፍ ገበያ ማቅረብ ያቆመችውም በዚሁ ምክንያት መሆኑን ሚኒስትሩን ጠቅሶ ኤኤፍፒ ዘግቧል፡፡

ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ በፈረንጆቹ 2024 ከዓለም የኮባልት ማዕድን ምርት 76 በመቶ ያህሉን ማቅረቧን የአሜሪካ ጂኦሎጂካል ሰርቬይ መረጃ ያመለክታል፡፡

የደቡብ ኮሪያ የመጀመሪያዋ የንግድ ሮኬት በብራዚል መከስከሷን ሮይተርስ ምንጮችን ጠቅሶ ዘግቧልየኢኖስፔስ ንብረት የሆነው ‘ሃንቢት-ናኖ’ የተሰኘው መንኮራኩር ፣ በብራዚል ከሚገኘው አልካንታራ ...
23/12/2025

የደቡብ ኮሪያ የመጀመሪያዋ የንግድ ሮኬት በብራዚል መከስከሷን ሮይተርስ ምንጮችን ጠቅሶ ዘግቧል

የኢኖስፔስ ንብረት የሆነው ‘ሃንቢት-ናኖ’ የተሰኘው መንኮራኩር ፣ በብራዚል ከሚገኘው አልካንታራ የጠፈር ጣቢያ በተተኮሰ በትንሽ ደቂቃዎች ውስጥ ተከስክሷል።

ለክስተቱ መንስኤ የሆነው ቴክኒካዊ ብልሽት (technical anomaly) መሆኑ ተገልጿል።

ልዩ የነፍስ አድን እና የክትትል ቡድኖች ሮኬቱ ወደ ወደቀበት ቦታ ተሰማርተዋል ያለው ፊደል ፖስት ነው።

"በ24 ሰዓት ውስጥ 11 ሚሊዮን ብር" አምኖ ለመቀበል የሚከብድ ከ24 ሰዓት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ 11,000,000 Birr 11ሚሊዮን ብር ተሰብስቧል።በአዶናይ ግሩፕ የተጀመረው ለሕፃፅ ለተቸገ...
23/12/2025

"በ24 ሰዓት ውስጥ 11 ሚሊዮን ብር" አምኖ ለመቀበል የሚከብድ ከ24 ሰዓት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ 11,000,000 Birr 11ሚሊዮን ብር ተሰብስቧል።

በአዶናይ ግሩፕ የተጀመረው ለሕፃፅ ለተቸገሩ ወገኖች የሚደርስ እርዳታ በተገቢው መንገድ እየሄደ ነው። የህዝብ ማዕበል የታየበት የገቢ ማሰባሰቢያ ሆኗል። እያንዳንዷ የተሰጠች 100 ብር ተጠራቅማ 11ሚሊዮን ደርሷል ከተባበርን የማይሆን ነገር የለም

ክብር ይገባዋል የኢትዮጵያ ህዝብ

ብራቮ አዶናይ 🙏🏾🙏🏾🙏🏾🙏🏾

ሴኔጋል ቦትስዋናን አሸነፈችታሕሣሥ 14፣ 2018 በአፍሪካ ዋንጫ የምድብ አራት የመጀመሪያ ዙር ጨዋታ ሴኔጋል ቦትስዋናን 3 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፋለች፡፡የሴኔጋልን የማሸነፊያ  ግቦች ኒኮላ...
23/12/2025

ሴኔጋል ቦትስዋናን አሸነፈች

ታሕሣሥ 14፣ 2018 በአፍሪካ ዋንጫ የምድብ አራት የመጀመሪያ ዙር ጨዋታ ሴኔጋል ቦትስዋናን 3 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፋለች፡፡

የሴኔጋልን የማሸነፊያ ግቦች ኒኮላስ ጃክሰን(2) እና ንዳዬ አስቆጥረዋል።

በዚሁ ምድብ አስቀድሞ በተደረገ ጨዋታ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ቤኒንን 1 ለ 0 በሆነ ውጤት ማሸነፏ ይታወቃል፡፡

በምድብ-3 ናይጄሪያ ከታንዛኒያ ምሽት 2 ሰዓት ከ 30 እንዲሁም ቱኒዚያ ከዩጋንዳ ምሽት 5 ሰዓት ላይ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡

ሁላችሁም ስለወንድሜ ማስተር አብነት አበክራችሁ ጠይቃችሁኛል እኔም በዛሬው እለት በአካል አግኝቼው ብዙ ነገሮችን ተጨዋውተናል ወንድሜ በአሁኑ ሰአት ጥሩ የህክምና ክትትል እየተደረገለት ይገኛል...
23/12/2025

ሁላችሁም ስለወንድሜ ማስተር አብነት አበክራችሁ ጠይቃችሁኛል እኔም በዛሬው እለት በአካል አግኝቼው ብዙ ነገሮችን ተጨዋውተናል ወንድሜ በአሁኑ ሰአት ጥሩ የህክምና ክትትል እየተደረገለት ይገኛል። ሁላችንም ከህመሙ ተፈውሶ ወደሚወደው ወደቀደመው ስራ ይመለስ ዘንድ በፀሎታችን እናስበው እያልኩ በቀጣይም አዲስ ነገር ሲኖር የማሳውቃችሁ ይሆናል።

ይሄን መልእክት ሁላችሁም ሼር እያረጋችሁ ስለወንድሜ ማስተር አብነት ደህንነት ለተጨነቁት በሙሉ አድርሱልኝ🙏

ዶክተር አብይ ታደሰ

ኢትዮጵያና አሜሪካ የ1 ነጥብ 466 ቢሊየን ዶላር የትብብር ስምምነት ፈረሙታሕሣሥ 14፣ 2018 ኢትዮጵያ እና አሜሪካ የ1 ነጥብ 466 ቢሊየን ዶላር ትብብር የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርመዋል...
23/12/2025

ኢትዮጵያና አሜሪካ የ1 ነጥብ 466 ቢሊየን ዶላር የትብብር ስምምነት ፈረሙ

ታሕሣሥ 14፣ 2018 ኢትዮጵያ እና አሜሪካ የ1 ነጥብ 466 ቢሊየን ዶላር ትብብር የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርመዋል።

የአሜሪካ መንግሥት በኢትዮጵያ ለጤናው ዘርፍ ልማት ትብብር የሚውል የ 1 ነጥብ 01 ቢሊዮን ዶላር ድጋፍ ይፋ አድርጓል።

ትብብሩ ለአምስት ዓመት ለጤና ዘርፍ ዘላቂ ልማት እና የጋራ ኢንቨስትመንት ማጠናከሪያ ትብብር የሚውል ነው።

የመግባቢያ ስምምነቱን የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሺዴ፣ የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ እና በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኧርቪን ማሲንጋ ፈርመዋል።

ድጋፉ በኢትዮጵያና አሜሪካ ትብብር ታሪካዊ የተባለለት ሲሆን የአዲሱ የትብብር ምዕራፍ የጠበቀ ግንኙነት ማሳያ እንደሆነም ተነስቷል።

120 ዓመታትን የተሻገረው የኢትዮጵያ እና አሜሪካ ወዳጅነት በተለያዩ የትብብር መስኮች ሲገለጥ መቆየቱ ይታወሳል።

(ኤፍ ኤም ሲ)

ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከ27 ቢሊየን ብር በላይ የብድር ስምምነት ተፈራረሙታሕሣሥ 14፣ 2018 ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከ27 ቢሊየን...
23/12/2025

ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከ27 ቢሊየን ብር በላይ የብድር ስምምነት ተፈራረሙ

ታሕሣሥ 14፣ 2018 ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከ27 ቢሊየን ብር በላይ የብድር ስምምነት ተፈራርመዋል፡፡

በፊርማ ሥነ ሥርዓቱ ላይ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው እንዳሉት፤ አየር መንገዱ በዓለም አቀፍ ደረጃ ትልቅ ቦታ ያለው እንዲሆን በማድረግ ረገድ የድርጅቱ ሰራተኞች ሚና ከፍተኛ ነው፡፡

አየር መንገዱ ከዚህ በፊት ለሰራተኞቹ 1 ሺህ 200 ቤቶችን ገንብቶ ማስረከቡን አስታውሰው፤ አሁን ላይ 5 ሺህ ቤቶችን በመገንባት ላይ ይገኛል ብለዋል።

ይህ የቤት ግንባታ እንዲሳካ ለማድረግ በዛሬው ዕለት ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የ27 ነጥብ 8 ቢሊየን ብር የብድር ስምምነት መፈረሙን ነው የገለጹት።

የብድር ስምምነቱ ለረዥም ዓመታት የዘለቀውን የሁለቱን ተቋማት ትብብር ወደ ላቀ ደረጃ የሚያደርሰው እንደሆነም ጠቁመዋል።

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዚዳንት ተወካይና የኮርፖሬት አገልግሎቶች ኤክስኪዩቲቭ ምክትል ፕሬዚዳንት ኤፍሬም መኩሪያ በበኩላቸው፤ ባንኩ የብድር አገልግሎትን በበቂ ደረጃ ተደራሽ ለማድረግ እየሰራ እንደሚገኝ አብራርተዋል።

በተለይም ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርሙ የብድር አገልግሎት ለመስጠት ምቹ ምህዳር ፈጥሯል ነው ያሉት፡፡

በዛሬው ዕለት ከአየር መንገዱ ጋር የተፈረመው ስምምነት ዘርፈ ብዙ ጥቅም እንደሚያስገኝ ጠቁመው፤ ተቋማቱ በሀገራዊ ስትራቴጂካዊ ጉዳዮች ላይ በትብብር መስራታቸውን እንደሚቀጥሉም አረጋግጠዋል፡፡
ኤፍ ኤም ሲ)
KWWMN የልማት ቲቢ

የኬንያ ፕሬዚዳንት ለሥራ ጉብኝት ኢትዮጵያ መጡታሕሣሥ 14፣ 2018 የኬንያ ፕሬዚዳንት ዊልያም ሩቶ  ለአንድ ቀን የሥራ ጉብኝት ወደ ኢትዮጵያ መጥተዋል።የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት መረጃ ...
23/12/2025

የኬንያ ፕሬዚዳንት ለሥራ ጉብኝት ኢትዮጵያ መጡ

ታሕሣሥ 14፣ 2018 የኬንያ ፕሬዚዳንት ዊልያም ሩቶ ለአንድ ቀን የሥራ ጉብኝት ወደ ኢትዮጵያ መጥተዋል።

የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት መረጃ እንዳመለከተው፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለአንድ ቀን የሥራ ጉብኝት ወደ ኢትዮጵያ የመጡትን የኬንያ ፕሬዚዳንት ዊልያም ሩቶን ተቀብለዋል።

ስለ ማስተር አብነት ከበደ ጸሎቱ ይቀጥል አንጋፋዉ ፕሮፌሰር ብሩክ ላምቢሶ የማስተር አብነትን የጤና መታወክ ሁኔታ ለማወቅ ለበርካታ ቀናት ክትትል ሲያደርጉ ቆይተዋል። ዛሬ አመሻሹ ላይ ደግሞ ...
22/12/2025

ስለ ማስተር አብነት ከበደ ጸሎቱ ይቀጥል
አንጋፋዉ ፕሮፌሰር ብሩክ ላምቢሶ የማስተር አብነትን የጤና መታወክ ሁኔታ ለማወቅ ለበርካታ ቀናት ክትትል ሲያደርጉ ቆይተዋል። ዛሬ አመሻሹ ላይ ደግሞ አዲስ አበባ ሲልክ ሮድ ሆስፒታል ስለ ቀጣይ ህክምና ምክረ-ሀሳብ እንዲያቀርቡ ተገብዘዋል።

በመሆኑም ፕሮፌሰሩ ከሆስፒታሉ ከፍተኛ ሰብ-ስፔሻሊስት ሐኪሞች ጋር መክረዋል። ፕሮፌሰሩን ስለጉብኝታቸዉ፣ ማስተር አብነትን ስላበረታቱትና ስለ እቅጣጫ አመልካች ሀሳባቸዉ እናመሠግናለን። ቀጣዩን ሂደት እየተከታተልን እናሳዉቃችኋለን። ፕሮፌሰሩ እግዚአብሔር ሁሌም መፍትሄ አለዉ ጸሎቱ ይቀጥል ብለዋል።

አዲስ አበባ ሲልክ ሮድ ሆስፒታል የህዝቡን አደራ በመቀበል ላደረጉልን ከፍተኛ ድጋፍ፣ ክትትልና ህክምና ከልብ እናመሠግናለን።
Silk Road General Hospital
Biruk Lambisso Wamisho

ከቤተሰብ

ምርጫ ቦርድ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ዙሪያ ከፖለቲካ ፓርቲ ተወካዮች ጋር ተወያየ ታሕሣሥ 13፣ 2018 (የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ዙሪያ ከፖለቲካ ፓርቲ ተወካዮች ጋ...
22/12/2025

ምርጫ ቦርድ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ዙሪያ ከፖለቲካ ፓርቲ ተወካዮች ጋር ተወያየ

ታሕሣሥ 13፣ 2018 (የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ዙሪያ ከፖለቲካ ፓርቲ ተወካዮች ጋር ተወያይቷል፡፡

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የ7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ረቂቅ የጊዜ ሠሌዳ ጥቅምት 10 ቀን 2018 ዓ.ም ይፋ ማድረጉ ይታወሳል፡፡

በዚህ ወቅትም “የዕጩዎች የድጋፍ ፊርማ ማቅረብ ይቅር/ይታገድ” እና “ከገዢው ፓርቲ ጋር መወያየት እንፈልጋለን” የሚሉ ጥያቄዎች ከፖለቲካ ፓርቲዎች ተነስተው እንደነበር ተጠቅሷል፡፡

ቦርዱም ከፓርቲዎች የተነሱ ጥያቄዎች መልስ ሊያገኙ በሚችሉበት አግባብ ላይ ሲሠራ መቆየቱ ነው የተገለጸው፡፡

በዚህ መሰረትም የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት ሕዳር 25 ቀን 2018 ዓ.ም ባካሄደው 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 3ኛ መደበኛ ስብሰባው “የዕጩዎች የድጋፍ ፊርማ ማቅረብ” የሚለውን ሃሳብ ማገዱ ተመላክቷል፡፡

በዛሬው ዕለትም ምርጫ ቦርድ 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ አስመልክቶ ገዢውን ፓርቲ ጨምሮ ከፖለቲካ ፓርቲ ተወካዮች ጋር መክሯል።

የቦርዱ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ በዚህ ወቅት ÷ መድረኩ የተዘጋጀው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ነፃ፣ ፍትሐዊና ገለልተኛ እንዲሆን ከማን ምን ይጠበቃል፣ አስቻይ የፖለቲካ ምኅዳር መፍጠርን እንዲሁም የውይይቱ ቀጣይነት በምን መልኩ መሆን አለበት የሚለውን የሁሉም ፖለቲካ ፓርቲዎች ተወካዮች ባሉበት መወያየት አስፈላጊ በመሆኑ ነው ብለዋል፡፡

ተሣታፊ ፖለቲካ ፓርቲዎቹ የዕጩ ድጋፍ ፊርማ ማቅረብ መታገድን እና የመድረኩ መዘጋጀትን አስመልክቶ ለቦርዱ ያላቸውን አድናቆት ገልጸዋል፡፡

ምርጫውን አስመልክቶ መሟላት አሉባቸው ያሏቸውን ሁነቶች አስቻይ ሁኔታና የውይይቱ ቀጣይነትን ጨምሮ በርካታ ጉዳዮች ላይ ተሣታፊ ፖለቲካ ፓርቲዎቹ ያሏቸውን አስተያየቶችና ጥያቄዎች አጋርተዋል።

ሰብሳቢዋ በማጠቃለያ ንግግራቸው የፀጥታ አስቻይ ሁኔታን በተመለከተና ሌሎች ምርጫውን የተመለከቱ ጉዳዮች ዙሪያ የሚኖሩ የምክክርና የውይይት መድረኮች ቀጣይነት እንዳላቸው ተናግረዋል።

የአስፈጻሚዎችን ገለልተኝነት አስመልክቶ ለተነሣው ጥያቄ ቦርዱ ዝርዝራቸውን ለፖለቲካ ፓርቲዎቹ መላኩን አመልክተዋል፡፡

በገለልተኝነቱ/ቷ ላይ ጥያቄ ያላቸው አስፈጻሚ ካገኙ ዝርዝሩን እንዲልኩ ቦርዱ በመጠበቅ ላይ መሆኑ ን አንስተው÷ በተመሳሳይ መልኩ ለፓርቲዎች በጀት ለማከፋፈልም ፓርቲዎቹ ሠነድ እንዲያቀርቡ እየተጠበቀ ነው ብለዋል፡፡

“በትግራይ ምርጫ ይካሄዳል ወይ” ለሚለው ጥያቄም ቦርዱ በሌሎች ክልሎች እንደሚያደርገው በትግራይ ክልልም ምርጫ ለማድረግ ዝግጅት እያከናወነ እንደሚገኝ አስረድተዋል፡፡

ባሳለፍነው ሣምንትም ከትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ጋር በትግራይ ምርጫ ስለሚካሄድበት ሁኔታ እንደተወያዩና ቦርዱ ምክክሩን ተከትሎ ጥሩ ውጤት እንደሚጠብቅ አብራርተዋል፡፡

ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ደህንነታቸው የተጠበቀ የዲጂታል ስርዓቶች የሚበራከቱበት ነው - ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ ሉዓላዊ እና ደህንነታቸው ...
22/12/2025

ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ደህንነታቸው የተጠበቀ የዲጂታል ስርዓቶች የሚበራከቱበት ነው - ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ

ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ ሉዓላዊ እና ደህንነታቸው የተጠበቀ የዲጂታል ስርዓቶች የሚበራከቱበት ነው አሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የብሔራዊ የዲጂታል ትራስፎርሜሽን ምክር ቤት ሊቀ መንበር ተመስገን ጥሩነህ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂን ይፋ አድርገዋል።

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ማጠናቀቂያ እና በዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ ይፋዊ ማስጀመሪያ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት፤ ስትራቴጂው ዜጎችን ማዕከል ያደረገ መንግሥታዊ ስርዓት የበለጠ የሚሰፋበት መሆኑን ተናግረዋል።

ስትራተጂው አካታች የዲጂታል አገልግሎቶች የሚቀርቡበት፣ ሉዓላዊ እና ደህንነታቸው የተጠበቀ የዲጂታል ስርዓቶች የሚበራከቱበት ነው ብለዋል።

ከዚህም ባለፈ የውስጥ ፈጠራ የሚበረታታበት እንደሆነ ገልጸው፤ መንግሥት የዲጂታል ኢትዮጵያ መርሃ ግብርን መዘርጋቱን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያን የዲጂታል ጉዞ ወደ አዲስ ምዕራፍ ያሸጋገረው የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ የአገልግሎት አሰጣጥን፣ የህዝብ ትስስርን፣ የንግድ ስርዓትን፣ የመንግስት ተደራሽነትን፣ የፀጥታ እና ደህንነት አጠባበቅን ጨምሮ የተለያዩ አሰራሮችን ቀይሯል ነው ያሉት።

ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ በቅርቡ በሚኒስትሮች ምክር ቤት መፅደቁን አስታውሰው፤ ስትራቴጂው በጋራ ጥረት፣ ትጋት እና ትብብር የተጀመሩ የዲጂታል ውጥኖች በፍጥነት የሚስፋፉበት መሆኑን ገልጸዋል።

እንዲሁም ተናባቢ የዲጂታል ስነ-ምህዳር የሚገነባበት፣ ዘላቂ የዲጂታል እምርታ የሚመጣበትና ሀገራዊ ትራንስፎርሜሽን የሚረጋገጥበት ማዕቀፍ ነው ብለዋል።

ታሕሣሥ 13፣ 2018
KWWMN የልማት ቲቢ

Address

144 Pangani Heihght
Botswana
00100

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Kembata World Wide Media Network posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Kembata World Wide Media Network:

Share

Category

Kembata World Wide Media Network -KWWMN

KWWMN የልማት ቲቪ ኢትዮጵያ ሰፊ የከምባታ አለም አቀፍ መገናኛ አውታር Update ወርልድ ዋይድ ቴሌቪዥን ይዘን እንቀርባለን ዘር ቀለም ሳይለዩ አገራቸውን በታማኝነት እናገለግላለን። ከታች በሚገኘው አድሬስ መልስ የፈለጉትን መልዕክት ማስቀመጥ ይችላሉ እናመሰግናለን የእርስዎ ምክር እና አስተየት ነው እዚህ ያደረሠን Thanks for messaging us. I value your comments, recommendations, suggestions and questions. try to respond as soon as possible. please understand that for me. thank u! ከከምባታ የልማት ቲቪ የዝግጅት ክፍል. WWW.KWWMN.OCM

[email protected] & [email protected]