Kembata World Wide Media Network

Kembata World Wide Media Network KWWMN registered inSouth Africa non-profit-organization.withheadquartersin Johannesburg,South Africa
(2)

Kembata worldwide Media Network registered in South Africa based as an independent and non-organization with headquarters in Johannesburg, South Africa. The organization is made up mainly of ambassadors, doctors, other professions that help in achieving to serve the Ethiopian community in South Africa It is an institution that provides genuine information and access to those in need.

ኤችአይቪን የሚከላከል መድኃኒት በአነስተኛ ዋጋ ሊቀርብ ነውአዲስ ኤችአይቪን የሚከላከል መድኃኒት በአነስተኛ ዋጋ ተደራሽ ሊደረግ ነው።በሁለት ዓመታት ጊዜ ውስጥ ከ100 በላይ አነስተኛ ገቢ ባ...
25/09/2025

ኤችአይቪን የሚከላከል መድኃኒት በአነስተኛ ዋጋ ሊቀርብ ነው

አዲስ ኤችአይቪን የሚከላከል መድኃኒት በአነስተኛ ዋጋ ተደራሽ ሊደረግ ነው።

በሁለት ዓመታት ጊዜ ውስጥ ከ100 በላይ አነስተኛ ገቢ ባላቸው አገራት መድኃኒቱ እንደሚቀርብ ተገልጿል።

በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ሰዎች መድኃኒቱን እንዲያገኙ ዕድል የሚሰጥ ይሆናል። ዓለም የኤችአይቪ/ኤድስ ወረርሽኝን ለመግታት አንድ እርምጃ ወደፊት እንድትጓዝም ይረዳል ተብሏል።

ሌናካፓቪር (Lenacapavir) የተባለው መድኃኒት በመርፌ የሚሰጥ ነው። በዚህ ዓመት ማገባደጃ መድኃኒቱን ማቅረብ ይጀመራል።

መድኃኒቱ በነፍስ ወከፍ ለአንድ ዓመት የሚያስከፍለው 28,000 ዶላር ሲሆን፣ አዲስ በተደረገ ስምምነት መሠረት ግን ዋጋው ወደ 40 ዶላር የሚወርድ ይሆናል።

እአአ በ2027 የመድኃኒቱ ዋጋ ቀንሶ በ120 አነስተኛና መካከለኛ ገቢ ያላቸው አገራት ይሰራጫል።ሳይንቲስቶች እንዳሉት ቫይረሱ ራሱን እንዳያባዛ መድኃኒቱ ይከላከላል።

በታዳጊ አገራት የሚኖሩና ኤችአይቪ ያለባቸው ሰዎች መድኃኒቱን በርካሽ እንዲያገኙ የሚያስችለው ስምምነት እንዲፈረም የቀድሞው የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ቢል ክሊንተን ከመድኃኒት አምራች ተቋሞች ጋር ድርድር አድርገዋል።

ክሊንተን ኸልዝ አክሰስ ኢኒሼቲቭ፣ ከጌትስ ፋውንዴሽን እንዲሁም ከደቡብ አፍሪካው የምርምር ተቋም አርኤችአይ ጋር ስምምነት ተፈራርመዋል።

መድኃኒቱ በተደረገበት ሙከራ አስደናቂ ውጤት ማሳየቱ ተገልጿል። ከሁለት ወራት በፊትም የዓለም ጤና ድርጅት ፀረ ኤችአይቪ ክፍል ይሁንታ ሰጥቶታል።

መርፌው በዓመት ሁለት ጊዜ ይወሰዳል። ለስድስት ወራት ኤችአይቪን ለመከላከል ይረዳል። ባለሙያዎች እንዳሉት አዲስ ኢንፌክሽንን ለመከላከል መድኃኒቱ ጠቀሜታው የጎላ ነው።

በተለይም ከፍተኛ ተጋላጭነት ያላቸው ወጣቶችና ሴቶች፣ የተመሳሳይ ፆታ አፍቃሪዎች እና በወሲብ ንግድ የሚተዳደሩ ሰዎችን ከበሽታው ለመከላከል ያግዛል።

አሁን ኤችአይቪን ለመከላከል ጥቅም ላይ እየዋለ ያለውን መድኃኒት (PrEP ወይም pre-exposure prophylaxis) እንደሚተካ ተገልጿል።

ይህ እንክብል በነፍስ ወከፍ በዓመት 40 ዶላር ያስከፍላል። እንክብሉ በየቀኑ ስለሚወሰድ ለሕሙማን ምቹ አይደለም። የበለጠ እንዲገለሉም ያደርጋል።

በየቀኑ የሚወሰድ መሆኑ በቀላሉ እንዳይገኝም ምክንያት ሆኗል። ጌትስ ፋውንዴሽን እንዳለው ከዚህ መድኃኒት ተጠቃሚ መሆን ከሚችሉ ሰዎች 18% ብቻ ናቸው እያገኙት ያለው።
አዲሱ መድኃኒት በአሜሪካና አውሮፓ መድኃኒት ተቆጣጣሪ ተቋማት ፈቃድ አግኝቷል።

አምና ሰኔ ላይ ጊሌድ የተባለ የአሜሪካ መድኃኒት አምራች መድኃኒቱ ላይ በሠራው ምርምር 100% ውጤታማ ሆኖ ተገኝቷል።

ከ18 ወራት በኋላ መድኃኒቱ ተደራሽ እንደሚሆን ይጠበቃል።አንድ ጥናት እንደሚጠቁመው አዲሱ መድኃኒት 4 በመቶ ተደራሽ ቢሆን 20 በመቶ አዲስ በሕመሙ የሚያዙ ሰዎችን ቁጥር ይቀንሳል።

ሰዎች በቫይረሱ እንዳይያዙ ከማገዙ ባሻገር ቫይረሱ ያለባቸውን ሰዎች ለማከምም ይውላል።

የፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር ለኤችአይቪ/ኤድስ የሚደረግ ዓለም አቀፍ እርዳታ ላይ ቅነሳ ማድረጉ ቀውስ በፈጠረበት ወቅት ነው የአዲሱ መድኃኒት አቅርቦት ይፋ የተደረገው።

የመንግሥታቱ ድርጅት ፀረ ኤድስ መረጃ 40 ሚሊዮን ሰዎች ቫይረሱ እንዳለባቸው ያሳያል።

እአአ ከ2000 ጀምሮ የቫይረሱን ስርጭት ለመቀነስ ዓለም አቀፍ ንቅናቄዎች ተደርገዋል። ሆኖም ባለፈው ዓመት ብቻ 1.3 ሚሊዮን ሰዎች በቫይረሱ ተይዘዋል።

ከ600,000 በላይ ሰዎች ከኤድስ ጋር በተያያዘ ሞተዋል። ደቡብ አፍሪካ ከፍተኛ የሕሙማን ቁጥር ያላት አገር ናት። አደሱ መድኃኒት ከሚቀርብባቸው አገራት መካከል ትገኛለች።

የአገሪቱ የጤና ሚኒስቴር "አነስተኛና መካከለኛ ገቢ ላላቸው አገራት ነፍስ አድን መድኃኒትን የማቅረብ እንቅስቃሴን እንደግፋለን" ብሏል ሲል ቢቢሲ ዘግቧል።

በአሜሪካ ጎት ታለንት መድረክ ኢትዮጵያን ያስጠራው ቲቲ ቦይስ የሰርከስ ቡድን አቀባበል ተደረገለትበአሜሪካ በተካሄደው የአሜሪካን ጎት ታለንት ውድድር ላይ በሰርከስ ዘርፍ ኢትዮጵያን በመወከል ...
25/09/2025

በአሜሪካ ጎት ታለንት መድረክ ኢትዮጵያን ያስጠራው ቲቲ ቦይስ የሰርከስ ቡድን አቀባበል ተደረገለት

በአሜሪካ በተካሄደው የአሜሪካን ጎት ታለንት ውድድር ላይ በሰርከስ ዘርፍ ኢትዮጵያን በመወከል የተሳተፉት እና እስከመጨረሻው ዙር ድረስ በመጓዝ የአገራቸውን ስም ከፍ አድርገው ያስጠሩት ቲቲ ቦይስ የሰርከስ ቡድን አባላት በባህል እና ስፖርት ሚኒስቴር አቀባበል ተደርጎላቸዋል፡፡

በአቀባበል ስነ ስርዓቱ ላይ የተገኙት የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ዴኤታ ረዳት ፕሮፌሰር ነብዩ ባዬ፤ በአሜሪካን ጎት ታለንት ላይ የተካፈሉት የቲቲ ቦይስ ሰርከስ ቡድን አባላት ለብዙ ወጣት የሰርከስ አርቲስቶች አርአያ መሆናቸውን ተናግረዋል።

የሰርከስ ቡድኑ የአሜሪካ ጉዞ በታሪክ የሚመዘገብ እንደሆነ ያነሱት ሚኒስትር ዴኤታው፤ ይህ ውጤት ለሌሎች የኪነጥበብ ስራዎች መነቃቃትን የሚፈጥር እንደሆነም ገልጸዋል፡፡

የሰርከስ ቡድኑ አባላት በበኩላቸው፤ በተደረገላቸው አቀባበል መደሰታቸውን ገልጸው፤ በጉዟቸው ሁሉ ድጋፍ ያደረጉላቸውን አካላት አመስግነዋል፡፡

በቀጣይ ከዚህ የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ እንደሚተጉም ተናግረዋል።

5 ልጆችን በአንድ ጊዜ የወለደችው እናት - ከነቀምቴ ከተማ በኦሮሚያ ክልል የነቀምቴ ከተማ ነዋሪ የሆነችው ወ/ሮ አስቴር ተረፈ የተባለች እናት በወለጋ ዩኒቨርሲቲ ጠቅላላ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታ...
25/09/2025

5 ልጆችን በአንድ ጊዜ የወለደችው እናት - ከነቀምቴ ከተማ

በኦሮሚያ ክልል የነቀምቴ ከተማ ነዋሪ የሆነችው ወ/ሮ አስቴር ተረፈ የተባለች እናት በወለጋ ዩኒቨርሲቲ ጠቅላላ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል 5 ልጆችን በአንድ ጊዜ ወልዳለች።

ወ/ሮ አስቴር 3 ወንድ እና 2 ሴት እንደወለደች እና የሕፃናቱ የጤና ሁኔታ በጥሩ ደረጃ ላይ እንደሚገኝ ሆስፒታሉ አስታውቋል።

ከአምስት ዓመት በፊት አንድ ልጅ የወለደችው ይህች እናት ከዚያ በኋላ ልጅ ሳትወልድ የቆየች ቢሆንም አሁን ላይ 5 ልጆችን በአንድ ጊዜ መገላገል መቻሏ ተገልጿል።

በቢታኒያ ሲሳይ

በ2025 በርካታ ህዝብ የሚኖርባቸው የአፍሪካ ከተሞች በአፍሪካ የከተማ እድገት እና መስፋፋት እየጨመረ መምጣቱን ተከትሎ በኢኮኖሚ ፍላጎት የተነሳ መኖሪያቸውን በከተማ የሚያደርጉ ሰዎች ቁጥር ...
25/09/2025

በ2025 በርካታ ህዝብ የሚኖርባቸው የአፍሪካ ከተሞች

በአፍሪካ የከተማ እድገት እና መስፋፋት እየጨመረ መምጣቱን ተከትሎ በኢኮኖሚ ፍላጎት የተነሳ መኖሪያቸውን በከተማ የሚያደርጉ ሰዎች ቁጥር በከፍተኛ ደረጃ እየጨመረ ይገኛል።

በተለይም በዋና ከተማዎች የሚገኝ መጠኑ ከፍ ያለ የምጣኔ ሀብት እንቅስቃሴ ሰዎች ወደ ከተሞች እንዲሳቡ ማድረግ ስለመቻሉ የወርልድ ፖፑሌሽን መረጃ ይጠቁማል።

በዚህ የተነሳም ከሁለት ሚሊየን በላይ ነዋሪ ያላቸው የአፍሪካ ከተሞች ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ ይገኛል።

ባለፉት አስርት አመታት እየታየ ያለው እድገት በፈረንጆቹ 1975 ከነበረው ቁጥር ጋር ሲነፃፀር ከፍተኛ ለውጥ የታየበት ነው።

ቀደም ሲል በአፍሪካ 6 ሚሊዮን ነዋሪ በመያዝ ተጠቃሽ የሆኑ ከተሞች ቁጥር በጣት የሚቆጠሩ የነበረ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት ግን 23 ሚሊዮን ነዋሪ በመያዝ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተፎካካሪ የሆኑ ከተሞች በአህጉሯ መፈጠር ችለዋል።

ግዙፍ ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ ያላቸው ከተሞች፤ በስራ እድል ፈጠራ ፣ በመሰረተ ልማት ፣ በመኖሪያ ቤት እና በሌሎችም ዘርፎች ያላቸው አቅም ከአጎራባች ትናንሽ ከተሞች እና ከገጠር አካባቢዎች ዜጎችን በመሳብ የነዋሪያቸው ቁጥር አድጓል።

ካይሮ፣ ኪንሻሳ እና ሌጎስ 17 ሚሊየን እና ከዛ በላይ ነዋሪዎችን በመያዝ ከአፍሪካ በቀዳሚነት ከሚጠሩት ከተሞች መካከል የሚጠቀሱ ናቸው።

የአፍሪካ ከተሞች እድገት እና የነዋሪዎች ቁጥር መጨመር ለሥነ-ህዝባዊ አሰፋፈር እና ለኢኮኖሚ እድገት ሚናው የላቀ መሆኑ ይነገራል።

በዚሁ ልክ ይህ የህዝብ ቁጥር በትክክለኛው የከተማ ፖሊሲ ካልተመራ በመሰረተልማት፣ በትራንስፖርት፣ በመኖሪያ ቤት እና በኃይል አቅርቦት ላይ ተጽዕኖ እንደሚኖረው መረጃው ጠቁሟል።

ይህን የህዝብ ቁጥር ወደ ኢኮኖሚያዊ አቅም ለመቀየር፤ ከተሞች በስራ እድል ፈጠራ እና በመሰረተ ልማት ላይ የሚከተሉት አካሄድ ወሳኝ መሆኑም ተነስቷል።

በ2025 በርካታ ነዋሪዎችን በመያዝ ከ23 ሚሊዮን በላይ ህዝብ የሚኖርባት የግብጽ መዲና ካይሮ ቀዳሚ ስትሆን፤ የዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎዋ ኪንሻሳ 17 ሚሊየን ነዋሪን በመያዝ ትከተላለች።

ሌጎስ ፣ ሉዋንዳ እና ዳሬሰላም ከሶስት እስከ አምስት ያለውን ደረጃ ሲይዙ፤ አዲስ አበባ ከ5 ሚሊዮን 956 ሺህ በላይ ህዝብ መኖሪያ በመሆን 9ኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች።

ኒኮላስ ሳርኮዚ በምርጫ ዘመቻቸዉ ወቅት ከሊቢያ መንግስት የገንዘብ ድጋፍ ተቀብለዋል በሚል ክስ የአምስት አመታት እስር ተፈረደባቸዉየቀድሞው የፈረንሳይ ፕሬዝዳንት ኒኮላስ ሳርኮዚ፤ ከሟቹ የሊቢ...
25/09/2025

ኒኮላስ ሳርኮዚ በምርጫ ዘመቻቸዉ ወቅት ከሊቢያ መንግስት የገንዘብ ድጋፍ ተቀብለዋል በሚል ክስ የአምስት አመታት እስር ተፈረደባቸዉ

የቀድሞው የፈረንሳይ ፕሬዝዳንት ኒኮላስ ሳርኮዚ፤ ከሟቹ የሊቢያ መሪ ኮሎኔል ሙአመር ጋዳፊ በሚሊየን የሚቆጠር ዩሮ የገንዘብ ድጋፍ ጋር በተያያዘ በወንጀል ተከሰው የአምስት ዓመት እስራት ተፈርዶባቸዋል።

ከ2007 እስከ 2012 ፈረንሳይን በፕሬዝዳንትነት የመሩት የ70 አመቱ አዛውንት፤ ውሳኔውን ለህግ የበላይነት እጅግ የከበደ ነዉ ሲሉ ገልፀውታል።

በ2007 የምርጫ ዘመቻቸውን ለመደገፍ ከጋዳፊ የተገኘውን ገንዘብ ተጠቅመዋል ተብሎ ክስ የቀረበባቸዉ ሳርኮዚ፤ ጉዳዩ የፖለቲካ ተነሳሽነት ነው ሲሉ ክሱን ውድቅ አድርገዉታል፡፡

በገንዘብ ድጋፉ ምላሽም ፕሬዝዳንቱ፤ በምዕራባውያን ሀገራት እንደ ወንጀለኛ የሚታዩበትን መጥፎ ስም ለመዋጋት ጋዳፊን ለመርዳት ቃል ገብተዋል ሲል አቃቤ ህግ ክስ አቅርቧል።

ሳርኮዚ ለምርጫ ዘመቻው የገንዘብ ድጋፍ ለማግኘት የቅርብ ረዳቶቻቸው ከሊቢያ ባለስልጣናት ጋር እንዲገናኙ ፈቅደዋል ተብሏል፡፡

ነገር ግን ፍርድ ቤቱ ሳርኮዚ የህገወጥ የምርጫ ቅስቀሳ የገንዘብ ድጋፍ ተጠቃሚ እንደነበሩ ለማረጋገጥ በቂ ማስረጃ የለም ሲል ቢወስንም የአምስት ዓመት እስራት ፈርዶባቸዋል።

የቀድሞዉ ፕሬዝዳንት ውሳኔውን ይግባኝ ቢሉም ፤ ፍርዱ በእስር ቤት እንዲቆዩ የሚያዝ ነዉ፡፡

በ2012 በድጋሚ ምርጫ ከተሸነፉ በኋላ ሳርኮዚ ለበርካታ የወንጀል ምርመራዎች ኢላማ ሆነዋል።

በ2012 የምርጫ ዘመቻቸዉ ወቅት ከመጠን በላይ ገንዘብ ወጪ በማድረግ እና ይህንንም ለመሸፈን የህዝብ ግንኙነት ድርጅት በመቅጠራቸው ጥፋተኛ ናቸዉ ተብሎ በ2024 የተወሰነባቸዉ ፕሬዝዳንቱ፤ ይግባኝ ጠይቀዉ የአንድ ዓመት እስራቱ ወደ ስድስት ወራት ተቀንሶላቸዉ እንደነበር ይታወሳል፡፡

በሌላ ክስ ደግሞ በ2014 አንድን ዳኛ ለመደለል ሞክረዋል በሚል ጥፋተኛ ተብለው ቅጣት የተጣለባቸዉ የመጀመሪያው የቀድሞ የፈረንሳይ ፕሬዝዳንት በመሆን እስራት ተፈርዶባቸዉ ነበር እንደ ቢቢሲ ዘገባ፡፡

Via Ethio fm

"እንኳን ደስ አላችሁ" - አንቶኒዮ ጉተሬዝ "ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ ከተባበሩት መንግስታት ዋና ጸሐፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ  ጋር ተወያይተዋል።በውይይታቸውም ሁለቱ ወገኖች በቀጣናው ብሎም በ...
25/09/2025

"እንኳን ደስ አላችሁ" - አንቶኒዮ ጉተሬዝ

"ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ ከተባበሩት መንግስታት ዋና ጸሐፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ ጋር ተወያይተዋል።

በውይይታቸውም ሁለቱ ወገኖች በቀጣናው ብሎም በዓለም አቀፍ የጋራ ጉዳዮች ላይ መክረዋል።

አንቶኒዮ ጉተሬዝ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ተጠናቅቆ በመመረቁ ኢትዮጵያውያን እንኳን ደስ አላችሁ ብለዋል።

በተጨማሪም በቅርቡ ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ጉባዔን በስኬት ማስተናገዷን አስታውሰው፥ ለዚህም የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።

በተመሳሳይ ፕሬዚዳንት ታዬ ከ80ኛው የተባበሩት መንግሥታት ጠቅላላ ጉባዔ ጎን ለጎን አፍሪካን በኤሌክትሪክ ለማዳረስ ዓላማ ያደረገው“ተልዕኮ 300" ኢነርጂ ኢኒሼቲቭ ላይ ተሳትፈዋል።

ኢትዮጵያ ተልዕኮውን መቀላቀሏ እያካሄደችው ያለውን የኢነርጂ ማሻሻያ የሚያጠናክር ዕውቅና በመሆኑ ትልቅ ምዕራፍ ነው፡፡

ኢትዮጵያ ባለፈው ጥር ወር በታንዛኒያ በተዘጋጀው “ተልዕኮ 300” ኢነርጂ ኢኒሼቲቭ ስብሰባ ላይ ቡድኑ ውስጥ እንድትካተት ማመልከቷ ይታወሳል፡፡

አሁን ላይም ለአባልነት የሚያበቃትን ስትራቴጂና የትግበራ የጊዜ ሰሌዳዎችን በማዘጋጀት ቁርጠኝነቷን በድጋሚ ለማረጋገጥ የገባችውን ቃል በተግባር አረጋግጣ ኢኒሼቲቩን ተቀላቅላለች፡፡

መስቀልን በጉራጌ የሚያከብሩ የሀገር ልጆች ከአዲስ አበባ ሲወጡ ያለው ድባብ በሰላም ወጥታችሁ በሰላም አክብራችሁ በሰላም ተመለሱ።
25/09/2025

መስቀልን በጉራጌ የሚያከብሩ የሀገር ልጆች ከአዲስ አበባ ሲወጡ ያለው ድባብ
በሰላም ወጥታችሁ በሰላም አክብራችሁ በሰላም ተመለሱ።

መስቀል በጉራጌ! በመሀመድ ሽሁር ጂጆ የመስቀል በዓል አጀማመር መሰረት የሆነው የኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል መገኘት ጋር የተያይዘ ሲሆን ከ4ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ጀምሮ እንደሚከበር የታሪክ ድር...
25/09/2025

መስቀል በጉራጌ!

በመሀመድ ሽሁር ጂጆ

የመስቀል በዓል አጀማመር መሰረት የሆነው የኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል መገኘት ጋር የተያይዘ ሲሆን ከ4ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ጀምሮ እንደሚከበር የታሪክ ድርሳናት ያስረዳሉ፡፡

ይህ ታላቅ በዓል በሁሉም የኢትዮጵያ ብሔር፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች ባህል፣ አኗኗርና ወግ በተላበሰ መልኩ የሚከበር ቢሆንም የበዓሉ አከባበር ደረጃና የሚሰጠው ትኩረት ከቦታ ቦታ ይለያያል፡፡

በጉራጌ ብሔረሰብ ዘንድ በድምቀት ከሚከበሩ በዓላት መካከል ትልቁና ዋነኛው የመስቀል በዓል እንደሆነ ከጉራጌ ባህል እና እሴቶቹ ከተሰኘው መጽሃፍ የተገኘው መረጃ ያመላክታል፡፡

የመስቀል በዓል በጉራጌ ብሔረሰብ ያለው ማህበራዊ ፋይዳ

የመስቀል በዓል ዓመቱን ሙሉ ተለያይተው የኖሩ ቤተሰቦችና ዘመዳሞች የሚገናኙበት፣ የሚጠያየቁበት፣ ማህበራዊ ችግሮቻቸው የሚፈቱበት፣ ወጣቶች የሚተጫጩበት፣ በጋብቻ የተሳሰሩ ቤተሠቦች የሚጠያየቁበት፣ በጥል የተለያዩ ባልና ሚስቶች እንዲሁም የተጣሉ ሠዎች የሚታረቁበት፣ እዳ የሚሠረዝበትና በዳይና ተበዳይ ይቅር የሚባባሉበት በዓል ነው፡፡

ወጣቶችና አዛውንት ደመራ ለማብራት በወጡበት በእድር ደንቦች በአካባቢ ልማት፣ በግብርናና ንግድ ስራዎች ላይ የሚመክሩበት፣ ወጣቶች በአባቶች የሚመረቁት፣ ጎልማሶች ከአባቶች ኃላፊነት የሚረከቡት፣ የወላድ ማህፀን የሚባረከው፣ ሟርተኞች የሚረገሙት በዚሁ በዓል ነው፡፡

ወላጆች ለበዓሉ የተዘጋጀን ሰንጋ ከፊታቸው አቁመው ሻኛውን በመዳሰስ ትውልዱን ይመርቃሉ /ይባርካሉ/፤ ለአገር ሰላምና ብልፅግና ፈጣሪያቸውን በፀሎት ይለምናሉ፡፡ በጎረቤት እና በአካባቢ ያለን ችግረኛ የሚያስቡበት፣ ለወለደች አራስ የሸሉዳ ስጋ፣ ለተገረዙ ልጆች ጭቅና ስጋ የሚሰጡበት በዓል ነው፡፡

ከመስከረም 16 ጀምሮ እስከ ጥቅምት 5 ድረስ ባህላዊ የአዳብና ጨዋታ በተለያዩ የገበያ ስፍራዎችና የጋራ መሠብሠቢያ ቦታዎች በሚኖረው የዘፈንና ጭፈራ ትዕይንቶች በመሳተፍ ወጣት ወንዶችና ሴቶች ሎሚ፣ ብርቱካን እና የሸንኮራ አገዳ በመለዋወጥ ጓደኛ የሚመርጡበትና ለመጻኢ ህይወታቸው መሰረት የሚጥሉበትና የሚወስኑበት በዓል ነው፡፡

በዓሉ በአዲሱ ዓመት የሚሠሩ ስራዎች ተለይተው እንዴት መሠራት እንዳለባቸው የሚመከርበትና የሚታቀድበት በመሆኑ ማህበራዊ ፋይዳው እጅግ የላቀ ነው፡፡

የመስቀል በዓል ዝግጅት

መስቀል በጉራጌ ብሔረሠብ ዘንድ ትልቅ በዓል እንደመሆኑ መጠን ዝግጅቱም እንዲሁ ከበድ ያለ ነው፡፡ የመስቀል በዓል ዝግጅት የሚጀምረው መስቀል በተከበረበት ዓመት ለሚቀጥለው በዓል አከባበር ማሠብ ይጀመራል፡፡

በዚህ መነሻነትም ከትውልድ ቀዬአቸው ርቀው የሚኖሩ የብሔረሰቡ ተወላጆች ከትንሽ እስከ ትልቅ ገቢ ያላቸውንም ጨምሮ ለመስቀል በዓል ማሰብ የሚጀምሩትና ገንዘብ የሚያጠራቅሙት በየዓመቱ ከጥቅምት ወር ጀምሮ ነው፡፡ በአገር ቤት የሚኖሩ ሴቶች የመስቀልን በዓል ለማክበር ቅቤ ማጠራቀም የሚጀምሩበት ወዲያው መስቀል እንደወጣ ነው፡፡

የመስቀል በዓል በተለይም ሶስትና አራት ወራት ገደማ ሲቀሩት አንስቶ ዝግጅቱ እየተጧጧፈ ይሄዳል፡፡

በመሆኑም በዚህ ወቅት የሥራ ክፍፍሉ በዕድሜና በፆታ እንደየ አቅሙና ችሎታው ይሠጣል፡፡ የልጆችና የወጣቶች ወንዶች የስራ ድርሻ ለመስቀል በዓል ዝግጅት የሚሆን ፍልጥ እንጨት ማዘጋጀት ሲሆን አባወራዎች ደግሞ ለዕርድ የሚቀርቡ ሰንጋዎች ማድለብና ማዘጋጀት፣ በመስቀል በዓል ወቅት ከብቶች የሚበሉትን ሳር የማዘጋጀት፣ ክልክል የሳር ቦታዎች መከለል እንዲሁም የተለያዩ ደረጃ ያላቸው ቢለዋዎች ያዘጋጃሉ፡፡

በሌላ በኩል የወጣት ሴቶች የሰራ ድርሻ ቤት የማሳመር ማለትም የተለያዩ ቀለም ባላቸው አፈሮች ቤት መቀባት ሲሆን እማወራዎች በቅድሚያ እንሰት ፍቀው የማዘጋጀት ፣ ጅባ የመሥራት ወይም የመግዛት፣ ለክትፎ ግብዓት የሆኑት እንደ ቂቤ፣ ሚጥሚጣ የማዘጋጀት ሀላፊነት ይወጣሉ፡፡

ከነሐሴ 12 /ከቡሄ/ ጀምሮ ዝግጅቱ እንደገና በአዲስ መልክ ተጠናክሮ ይከናወናል፡፡ ምክንያቱም መስቀል ደርሷልና ነው፡፡

ለአብነትም የመስቀል ደመራ ይደመራል፤ ወጣት ወንዶች የመስቀል እንጨት ጫካ ሄደው መፍለጥና ማዘጋጀት የሚጀምሩት ከቡሄ ጀምሮ እንደሆነና ሌሎች ማንኛውም ነገሮች ሁሉ በትጋትና በንቃት ይከናወናሉ፡፡

መስቀል በጉራጌ አስቀድሞ ሰፊ ቅድመ ዝግጅት ከተደረገበት በኋላ በዓሉ ከመስከረም 12 እስከ ጥቅምት 5 ድረስ ለበዓሉ ተብሎ የተዘጋጁ ባህላዊ ምግቦችና መጠጦች እየተጠቀሙ በታላቅ ደስታና ጭፈራ እንዲሁም ልዩ ልዩ ክንዋኔዎችን በማካሄድ የሚከበር ሲሆን የቀናቱ ስያሜና የሚከናወኑ ተግባራት ከዚህ በታች እንደሚከተለው ቀርቧል፡፡

መስከረም 13 ወሬት የኸና

በመስቀል በዓል ለምግብ ማቅረቢያነት የሚውሉ ቁሳቁሶች ከየግድግዳው የሚወርዱበት ቀን ነው፡፡ የቤት መገልገያ ቁሳቁሶች በጥንቃቄ ፀድተው እስከ ጥቅምት 5 ድረስ በምግብ ማቅረቢያነት ያገለግላሉ፡፡

በተጨማሪም ሁሉም ቤቱን አፅድቶ አዳዲስ ጅባዎች አነጣጥፎ መስቀልን ለማክበር ዝግጅት የሚጠናቀቅበት ዕለት ነው፡፡

መስከረም 14 ደንጌሳት /የዴጚያ/የዴንጋ እሳት(ይፍት)

ለሁሉም የቤተሰብ አባል በተዘጋጀለት የሸክላ ጣባት የጎመን ክትፎ የሚበላበት ዕለት ሲሆን የዚህ ቀን ሙሉ ወጪ ሴቶች ይሸፍናሉ፡፡

በዚህ ዕለት ማታ በየደጃፉ በልጆች የተደመሩ ደመራዎች ይቃጠላሉ፤ በብሔረሰቡ አጠራር የዴጚያ/የዴንጋ ኧሳት (የባዮች ኧሳት ቀነ) ይባላል፡፡ ስለሆነም ደመራው ሲቃጠል ጎረ ጎረ ፣ ጎረ ጎረ... እያሉ ፈጣሪን ለዚህ እለት ላደረስከን ብለው ሲያመሰግኑ ሴቶች ደግሞ በእልልታ ያደምቁታል፡፡

መስከረም 15 ወኸመያ /ጨርቆስ/ የእርድ ማይ/

በጉራጌ ብሔረሰብ ዘንድ ዋናው የመስቀል በዓል የሚከበርበት በእዚህ ዕለት ነው፡፡ በዕለቱም የአባወራዎች ተግባር ጎልቶ የሚታይበት ሆኖ እያንዳንዱ የቤተሰብ አባል ሁለትና ከዚያ በላይ በመሆን የደለበ ሰንጋ የሚያርድበት ነው፡፡ በዚህ ዕለት ስጋውን ወንድየው እንዳስገባ ጥሬ ስጋ በቅቤ በመንከር (ጨፉየ) ቀጥሎም ተወዳጁ የጉራጌ ክትፎ ይበላል፡፡

መስከረም 16 ያባንዳ እሳት/ የጉርዝ እሳት

ዋናው መስቀልና ትልቁ /የአባቶች/ ደመራ የሚበራበት ዕለት ሲሆን በአብዛኛው ሀይማኖታዊ ይዘት ጎልቶ ይወጣል፡፡ ወጣት ወንዶችና ሴቶች ቤተክርስቲያን ሄደው ባህላዊ ጭፈራ የሚጨፍሩበትና ሀይማኖታዊ ሥርዓት የተከተለ ደመራ የሚቃጠልበት ቀን ነው፡፡

ወጣቶቹ ከጭፈራ ቦታቸው ወደ ቤት ከተመለሱ በኃላ ወደ ማታ አካባቢ ዋናው ዳመራ በየአካባቢው ይቃጠላል፡፡ በዳመራው ስርም ባህላዊ ጭፈራ ይደምቃል፣ ይጠጣል፡፡ ከዚህ ሁነት በኋላ ሁሉም ወደ ቤቱ ገብቶ በተዘጋጀለት ጣባ ክትፎ ይመገባል፡፡

መስከረም 17 ንቅ ባር/ የከሰል ማይ

ከለሊቱ 12:00 ሰዓት ጀምሮ በአንድ አጥቢያ የሚተዳደሩ ዕድርተኞች ደመራ ወደ ተቃጠለበት ቦታ በመሰብሰብ ቃለ መሀላ በማስገባት አዲስ የአካባቢ ዳኛ የሚሾምበትና ያለፈው ርክክብ የሚያደርግበት፣ አዲስ የአባልነት ጥያቄ የሚቀርብበትና ምዘገባ የሚካሔድበት ዕለት ነው፡፡

መስከረም 18 የፊቃቆ ማይ

ሴት ልጃገረዶች የተለያዩ የሥፌት ጌጣ ጌጦች /ዕቃዎች/ ለማዘጋጀት የሚረዳ ሰንደዶ ለቀማ የሚጀመርበት ዕለት ሲሆን በየመንደሩ ልጃገረዶች ባህላዊ ዜማ እያዜሙ ስንደዶ ለቀማ ያደርጋሉ፡፡

ከመስከረም 17 እስከ መስከረም 23

ዕለቱ አማትና አማች የመጠየቂያ ጊዜ ነው፡፡ ሴት ልጆች ለእናቶቻቸው የፀጉር ቅቤ ለአባቶቻቸው ባርኔጣና ጭራ ሲይዙ ባሎቻቸው ደግሞ ሙክት በመያዝ ይሄዳሉ፡፡ ራሳቸው የአብራካቸው ክፋይ የሆኑትም ልጆቻቸው በወላጆቻቸው የሚመረቁ ሲሆን በጠቅላላ አማቾቻቸው ዘንድ ትልቅ ክብርና ሞገስ ያጎናፅፏቸዋል፡፡

ባህላዊ የመስቀለ በዓል ጨዋታ

አዳብና ከመስቀል በዓል ጋር ተያይዞ ከመስከረም 16 እስከ ጥቅምት 5 ባሉት ቀናት ውስጥ በተለያዩ የገበያ ቦታዎችና አቢያተ-ክርስቲያናት የሚከወን የወጣቶች ባህላዊ ጭፈራ ስነ- ስርዓት ነው፡፡

በዚህ ሰነ- ስርዓት ላይ በተለያዩ ምክንያቶች ከየትውልድ ቀዬያቸው ርቀው የቆዩ ዘመድ አዝማዶች፣ አብሮ አደጎች ተገናኝተው ናፍቆታቸውን ይወጣሉ፤ የሰውም ሆነ የጥበብ ናፍቆት፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ክብ እየሰሩ የሚዘፍኑ ወጣት ወንዶችና ሴቶች ዜማና ዳንኪራ በሚደምቀው በዚሁ የአዳብና ጭፈራ ወቅት የትዳር ጓደኛ የመምረጥ ስራ ይከናወናል፡፡

ወንዱ ልጅ ለጭፈራ ከወጡት ኮረዳዎች መሀከል ቀልቡ ካረፈባት ልጅ የሎሚ ስጦታ በመስጠት /ወርውሮ/ በመምታት ለትዳር የምትሆነውን ልጅ በባህሉ መሠረት ያጫል፡፡ በአዳብና ከሚከወናወት የተለያዩ ባህለዊ ጨዋታዎች መካከል በወንዶች ብቻ የሚከወን የዝላይ ትዕይንትም አለ፡፡

ሌላው የሙየቶች ክዋኔ ጥበብ አንዱ ነው፡፡ ሙየቶች ለአዳብና ጭፈራ ከሚወጣው የክዋኔው ታዳሚ ለየት ያለ ቋንቋ፣ ዜማና ዳንኪራ ያለው ክዋኔ ጥበብ የሚያቀርቡ ማህበረሠብ ሲሆኑ ወደ አናታቸው በአደይ አበባ የተሽቆጠቆጡ ልምጭ ይዘው መሪያቸውን እየተከተሉ ሲያዜሙና ሲጨፍሩ ይስተዋላሉ፡፡

በአጠቃላይ በመስቀል ወቅት የሚከናወኑ ባህላዊ መስተጋብሮችና ትዕይንት በተለይም ለሁለቱም የጉራጌ ዞኖች ቱሪዝም እድገት ትልቅ ሀብት ነው፡፡ በምስራቅ ጉራጌ ዞን በአለም ቅርስነት ከተመዘገበው ጢያ ትክል ድንጋይ ዓለም አቀፍ መካነ ቅርስ ጀምሮ የጊቤ ሸለቆ ብሔራዊ ፖርክ፣ ጥንታዊና ታሪካዊ ገዳማትና መስጅዶች እንዲሁም ውብና ማራኪ የሆኑ መልክአ ምድሮችን የያዙትን ጉራጌና ምስራቅ ጉራጌ ዞኖችን የመጎብኘት እድልን ይፈጥራል፡፡

መልካም በዓል!

ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ በመጠናቀቁ አቶኒዮ ጉቴሬዝ የእንኳን ደስ ያላችሁ መልዕክት አስተላለፉመስከረም 15/2018 ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ በመጠናቀቁ አቶኒዮ ጉቴሬዝ የእንኳን ደስ...
25/09/2025

ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ በመጠናቀቁ አቶኒዮ ጉቴሬዝ የእንኳን ደስ ያላችሁ መልዕክት አስተላለፉ

መስከረም 15/2018 ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ በመጠናቀቁ አቶኒዮ ጉቴሬዝ የእንኳን ደስ ያላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።

ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ ከተባበሩት መንግስታት ዋና ጸሐፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ ጋር ተወያይተዋል።

በውይይታቸውም ሁለቱ ወገኖች በቀጣናው ብሎም በዓለም አቀፍ የጋራ ጉዳዮች ላይ መክረዋል።
አንቶኒዮ ጉተሬዝ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ተጠናቅቆ በመመረቁ ኢትዮጵያውያን እንኳን ደስ አላችሁ ብለዋል።

በተጨማሪም በቅርቡ ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ጉባዔን በስኬት ማስተናገዷን አስታውሰው፥ ለዚህም የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።

“ኢትዮጵያ እና ግብፅ በሶማሊያ ውስጥ እንዲዋጉ አንፈቅድም” - ሐሰን ሼክ ሞሐሙድየሶማሊያው ፕሬዝዳንት ሐሰን ሼክ ሞሐሙድ በአገራቸው በሰላም ማስከበር ላይ የሚሰማሩ የኢትዮጵያ እና የግብፅ ወ...
24/09/2025

“ኢትዮጵያ እና ግብፅ በሶማሊያ ውስጥ እንዲዋጉ አንፈቅድም” - ሐሰን ሼክ ሞሐሙድ

የሶማሊያው ፕሬዝዳንት ሐሰን ሼክ ሞሐሙድ በአገራቸው በሰላም ማስከበር ላይ የሚሰማሩ የኢትዮጵያ እና የግብፅ ወታደሮች ወደ ግጭት ሊገቡ የሚችሉበት ምክንያት እንደሌለ በመግለጽ "የውክልና ጦርነት" አይኖርም አሉ።

ፕሬዝዳንቱ ከቢቢሲ ፎከስ ኦን አፍሪካ ቴሌቪዥን ጋር በነበራቸው ቃለ ምልልስ እንደተናገሩት በሁለቱ አገራት መካከል "በሶማሊያ ምድር" የሚካሄድ ጦርነት እንደማይኖር እና ሶማሊያም ይህንን እንደማትፈቅድ አሳውቀዋል።

ሁለቱ አገራት ወደ ግጭት መግባት የሚፈልጉ ከሆነ በራሳቸው ሊዋጉ ይችላሉ ያሉት ፕሬዝዳንቱ በሶማሊያ የሁለቱ ሀገራት ወታደሮች የሰፈሩበት ቦታ ተቀራራቢ ስላልሆነ ለግጭት የሚያበቃ ዕድል የለም ብለዋል።

በግብፅ እና በኢትዮጵያ ወታደሮች መካከል በመቶዎች የሚቆጠሩ ኪሎ ሜትሮች ርቀት መኖሩን የገለፁት ፕሬዝዳንቱ “ግብፅ ኢትዮጵያን ለመረበሽ የምትፈልግበት ምክንያት አይታየኝም። ኢትዮጵያም በሶማሊያ የሚገኙ የግብፅ ሰላም አስከባሪ ኃይልን ለመረበሽ የምትፈልግበት ምክንያት አይታየኝም” ብለዋል።

የኢትዮጵያ እና የግብፅ ወታደሮች ሶማሊያን የጦርነት አውድማ የሚያደርግ “የውክልና ጦርነት” ማድረግ እንደማይቻል ሶማሊያም ይህ በግዛቷ እንዲከናወን እንደማትፈቅድ አሳውቀዋል።

ፕሬዝዳንት ሐሰን አገራቸው ለአስርታት በተካሄደ ጦርነት መሰላቸቷን እና ተጨማሪ አዲስ ጦርነት እንደማትፈልግም አክለው ተናግረዋል ሲል ቢቢሲ ዘግቧል።

መሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት ፈጣንና ቀልጣፋ አገልገሎት ለመስጠትና ብልሹ አሰራርን ለመከላከል ፋይዳው የላቀ ነው - ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) መስከረም 14/2018:- የመ...
24/09/2025

መሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት ፈጣንና ቀልጣፋ አገልገሎት ለመስጠትና ብልሹ አሰራርን ለመከላከል ፋይዳው የላቀ ነው - ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

መስከረም 14/2018:- የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት ለህዝብ ፈጣንና ቀልጣፋ አገልገሎት ለመስጠትና ብልሹ አሰራርን ለመከላከል ፋይዳው የላቀ መሆኑን የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) ገለጹ፡፡

የመንግስትን አገልግሎት አሰጣጥ ይበልጥ ቀጣፋ፣ ፍትሃዊና ተጠያቂነት የሰፈነበት የማድረግ ጥረት ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑንም አረጋግጠዋል።

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)፤ በክለሉ የአገልገሎት አሰጣጥን ከማዘመን፣ ፈጣንና ቀልጣፋ ከማድረግ አንፃር እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት በተመለከተ ከኢዜአ ጋር ቆይታ አድርገዋል።

ርዕሰ መስተዳድሩ በማብራሪያቸውም በተለይ የአገልገሎት አሰጣጥ ችግሮችን ለመፍታት የመሶብ አገልገሎትን ጨምሮ በዲጂታል ስርዓት የታገዙ ስራዎች ትኩረት የተደረገባቸው መሆኑን ገልጸዋል።

የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎትን ስራ ለማስጀመር ቀደም ብሎ የሰው ሃይልና የማእከል ዝግጅት ተደርጎ በመጠናቀቁ ተግባራዊ የማድረግ ምእራፍ ላይ እንገኛለን ብለዋል።

መሶብ ለህዝብ ፈጣንና ቀልጣፋ አገልገሎት ለመስጠትና ብልሹ አሰራርን ለመከላከል ፋይዳው የላቀ መሆኑንም ርዕሰ መስተዳድሩ አስረድተዋል።

የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት ከሆሳዕና ከተማ ባለፈ በአደረጃጀቱ መሰረት በክላስተር ከተሞችም ተግባራዊ ለማድረግ የሚያስችል እንቅስቃሴ እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል።

  Heritage day to my fellow African brothers and sisters ,l wish you all peace and love  share one another Ubuntu. God b...
24/09/2025

Heritage day to my fellow African brothers and sisters ,l wish you all peace and love share one another Ubuntu. God bless Africa and the whole world
G 🌼✊G2GM&IAYDOfounder CEOImage of Africa youth Development Organization
KWWMN የልማት ቲቢ

Address

144 Pangani Heihght
Botswana
00100

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Kembata World Wide Media Network posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Kembata World Wide Media Network:

Share

Category

Kembata World Wide Media Network -KWWMN

KWWMN የልማት ቲቪ ኢትዮጵያ ሰፊ የከምባታ አለም አቀፍ መገናኛ አውታር Update ወርልድ ዋይድ ቴሌቪዥን ይዘን እንቀርባለን ዘር ቀለም ሳይለዩ አገራቸውን በታማኝነት እናገለግላለን። ከታች በሚገኘው አድሬስ መልስ የፈለጉትን መልዕክት ማስቀመጥ ይችላሉ እናመሰግናለን የእርስዎ ምክር እና አስተየት ነው እዚህ ያደረሠን Thanks for messaging us. I value your comments, recommendations, suggestions and questions. try to respond as soon as possible. please understand that for me. thank u! ከከምባታ የልማት ቲቪ የዝግጅት ክፍል. WWW.KWWMN.OCM

[email protected] & [email protected]