Kembata World Wide Media Network

Kembata World Wide Media Network KWWMN registered inSouth Africa non-profit-organization.withheadquartersin Johannesburg,South Africa
(3)

Kembata worldwide Media Network registered in South Africa based as an independent and non-organization with headquarters in Johannesburg, South Africa. The organization is made up mainly of ambassadors, doctors, other professions that help in achieving to serve the Ethiopian community in South Africa It is an institution that provides genuine information and access to those in need.

የፋይናንስ እምርታ በኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) “የፋይናንስ እመርታ በኢትዮጵያ” በሚል በተሰናዳው እና ስድስት የሀገራችንን የፋይናንስ እና የገቢ ሥርዓት በመምራት ላይ...
15/01/2026

የፋይናንስ እምርታ በኢትዮጵያ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) “የፋይናንስ እመርታ በኢትዮጵያ” በሚል በተሰናዳው እና ስድስት የሀገራችንን የፋይናንስ እና የገቢ ሥርዓት በመምራት ላይ ያሉ ዐበይት ተቋማት አፈፃፀም በሚገመግሙበት እና ለሚቀጥሉት አምስት አመታት የሚኖራቸውን ስትራቴጂያዊ የቅድሚያ ምልከታ በሚያደርጉበት ኮንፈረንስ ላይ ተገኝተዋል።

ኢትዮጵያ ባለፉት አምስት አመታት በፋይናንስ አካታችነት ተጨባጭ እድገት ያስገኙ እና ሰፊ መዳረሻ ያላቸው የማክሮኢኮኖሚ ሪፎርሞች አካሂዳለች።

ከገበያ መር የውጭ ምንዛሬ ሥርዓት እስከ ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርም አፈፃፀሞች እና የዲጂታል የክፍያ ሥርዓት ድረስ የእነዚህ አምስት አመታት ክንዋኔ በፋይናንስ ዘርፉ ተወዳዳሪነትን በሚያሳድጉ በመንግሥት ቆራጥ እና ስኬታማ ተግባራት የሚገለጥ ነው።

15/01/2026
አዋሽ ባንክ! እስከ ጥር 9፣2018 ዓ.ም ይሳተፉ!የገና እና የጥምቀት ስጦታ ከአዋሽ ባንክ! ይወዳደሩ፤ ከአዋሽ ባንክ የ100 ሺህ ብር ሽልማት ያሸንፉ! አዋሽ ባንክን ከአንድ ደቂቃ ባነሰ አ...
15/01/2026

አዋሽ ባንክ! እስከ ጥር 9፣2018 ዓ.ም ይሳተፉ!

የገና እና የጥምቀት ስጦታ ከአዋሽ ባንክ! ይወዳደሩ፤ ከአዋሽ ባንክ የ100 ሺህ ብር ሽልማት ያሸንፉ!

አዋሽ ባንክን ከአንድ ደቂቃ ባነሰ አጭር ተንቀሳቃሽ ምስል፣ ስዕል፣ ኢንፎ ግራፊክስ ወይም በፎቶ መግለፅ ያሸልማል።

ውድደሩ ከአዋሽ ባንክ አገልግሎቶች፣ መተግበሪያዎች ወይም መለያ ምልክት ሎጎ መካከል አንዱን በመምረጥ በተለየ ሁኔታ በቪድዮ፣ በስዕል፣ በኢንፎ ግራፊክስ ወይም በፎቶ መግለፅ ነው።

በዚሁ መሠረት የውድድር ጊዜው በአጠቃላይ ከታሕሳስ 25 እስከ ጥር 9፣ 2018 ዓም ብቻ የሚቆይ ነው። ተወዳዳሪዎች ያዘጋጁትን ተንቀሳቃሽ ምስል፣ ስዕል ፣ የኢንፎ ግራፊክስ ውጤት ወይም ፎቶ ለዚሁ ውድድር በተዘጋጀው የቴሌግራም ቻናል https://t.me/awashchallenge ውስጥ በመግባት ቻናሉ ስር የሚገኘውን የመልዕክት ሳጥን በመጫን Awash Challenge Message ላይ ወይም ከላይ የቴሌግራም ቻናሉን ስም በመንካት Discuss የሚለውን በመጫን የመወዳደሪያ ይዘታችሁን መላክ የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።

IShowSpeed ግብፅ ገብቶ የቀጥታ ስርጭቱን ጀምሯል! ትላንት የጉርሻ ፔጅ "አይሾው ስፒድ ግብፅ ገብቷል፣ ከቡድኑ ጋርም ተነጋግረናል" ብሎ ሲዘግብ አንዳንዶቻችሁ ጥርጣሬ አድሮባችሁ እንደነ...
15/01/2026

IShowSpeed ግብፅ ገብቶ የቀጥታ ስርጭቱን ጀምሯል!

ትላንት የጉርሻ ፔጅ "አይሾው ስፒድ ግብፅ ገብቷል፣ ከቡድኑ ጋርም ተነጋግረናል" ብሎ ሲዘግብ አንዳንዶቻችሁ ጥርጣሬ አድሮባችሁ እንደነበር እናስታውሳለን።

ነገር ግን ቃላችንን በተግባር በማረጋገጥ፣ ስፒድ አሁን በግብፅ ፒራሚዶች ስር ሆኖ አለምን እያስደመመ ይገኛል!

በልምድ ና በአንጋፋነቱ የ9ኛ ዓመት በፊስቡክ ቆይታ ጉርሻ ፔጅ በስህተት የተዘገቡት ሁለት ዜናዎች ብቻ ናቸው።
እኛ እርግጠኛ ያልሆንንበትን ነገር በፍጹም አንፖስትም!

ስለዚህ ጉርሻ ካለ፣ አለ ነው!" የሚለውን መርህ አምናችሁ እንድትቀበሉ በድጋሚ እናረጋግጣለን። እውነታው ለራሳችሁ ምስክር ነው::

ባለፈው የኢትዮጵያ ቆይታው በነበረው የሰብስክራይብ ብዛት እና በLive Streaming ተመልካች ቁጥር (view) ኢትዮጵያ እስካሁን የአንደኝነትን ደረጃ ይዛ ትገኛለች።

የኢትዮጵያዊያን ፍቅር እና ድጋፍ አሁንም በአለም መድረክ ላይ ታሪክ እየሰራ ነው።

አይርሱ ጉርሻ ፔጅ የታማኝ መረጃ ምንጭዎ ነው::
መልካም ቀን ይሁንልዎ::

ሞሮኮ ናይጄሪያን በማሸነፍ ለፍጻሜ አለፈችበ35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ የግማሽ ፍፃሜ ጨዋታ አዘጋጇ ሀገር ሞሮኮ ናይጄሪያን በማሸነፍ ለፍጻሜ አልፋለች።የሁለቱ ብሔራዊ ቡድኖች ጨዋታ በመደበኛው 90...
15/01/2026

ሞሮኮ ናይጄሪያን በማሸነፍ ለፍጻሜ አለፈች

በ35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ የግማሽ ፍፃሜ ጨዋታ አዘጋጇ ሀገር ሞሮኮ ናይጄሪያን በማሸነፍ ለፍጻሜ አልፋለች።

የሁለቱ ብሔራዊ ቡድኖች ጨዋታ በመደበኛው 90 ደቂቃ እንዲሁም በተጨማሪ 30 ደቂቃ ያለግብ አቻ የተጠናቀቀ ሲሆን፥ ሞሮኮ በመለያ ምት አሸንፋለች።

በዚህም መሠረት ሞሮኮ እና ቀደም ሲል ግብጽን በማሸነፍ ለፍጻሜ የደረሰችው ሴኔጋል የፍጻሜ ተፋላሚ መሆናቸውን አረጋግጠዋል።

የአፍሪካ ዋንጫ የፍጻሜ ጨዋታ በመጪው እሑድ ይደረጋል።

የሟች አሜን አሸናፊ ገዳይ ወንድም የወላይታ ድቻ ምክትል አሰልጣኝ ግዛቸው ጌታቸው መሆኑ ተሰምቷል። አሰልጣኝ ግዛቸው ረብጣ ገንዘቦችን በማፍሰስ የፍትህ ሥርዓት እንዲጓደል ካደረጉ ሰዎች የገዳ...
15/01/2026

የሟች አሜን አሸናፊ ገዳይ ወንድም የወላይታ ድቻ ምክትል አሰልጣኝ ግዛቸው ጌታቸው መሆኑ ተሰምቷል።

አሰልጣኝ ግዛቸው ረብጣ ገንዘቦችን በማፍሰስ የፍትህ ሥርዓት እንዲጓደል ካደረጉ ሰዎች የገዳይ ዋነኛ ተባሪ እንደሆነ ታውቋል። የወላይታ ዞን ፖሊስን፣ የሟች አሜን አሟሟት በተመለከተ የተደራጀውን የምርመራ ቡድንን፣ አቃቤ ሕግን እና የወላይታ ሶዶ ከተማ ፖሊሶችን ሁሉንም በገንዘብ ደልሎ በመያዝ ገዳይ ወንድሞቹን ነፃ ማውጣት ችሏል።

ዛሬ ላይ የገንዘብ ጡንቻ ስላለህ ብቻ ፍትህን ማጓደል ትችል ይሆናል። ነገር ግን መቼም እውነት ተቀብራ አትቀርም።

ይሄን መረጃ ለፌደራል ፖሊስ እና ለሰብአዊ መብት ተሟጋቾች እንዲደርስ ሼር አድርጉት። የእናንተ አንድ ሼር ለፍትህ ትልቅ አስተዋፅኦ አለው! 👇📢

ፍትህ ለአሜን😭

የአይሾው ስፒድ የኢትዮጵያ ቆይታ የሚሊየኖች ዐይን ወደ አዲስ አበባ እንዲሳብ አድርጓል - ከንቲባ አዳነች አቤቤታዋቂው ዩቲዩበር አይሾው ስፒድ በኢትዮጵያ ያደረገው ጉብኝት በመላዕው ዓለም የሚ...
15/01/2026

የአይሾው ስፒድ የኢትዮጵያ ቆይታ የሚሊየኖች ዐይን ወደ አዲስ አበባ እንዲሳብ አድርጓል - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

ታዋቂው ዩቲዩበር አይሾው ስፒድ በኢትዮጵያ ያደረገው ጉብኝት በመላዕው ዓለም የሚሊዮኖች ዐይን ወደ አዲስ አበባ እንዲሳብ አደርጓል አሉ ከንቲባ አዳነች አቤቤ፡፡

ከንቲባዋ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት÷ ጉብኝቱ ከተማችን ያላትን የቆየና የከበረ የእንግዳ ተቀባይነት ባህልና የከተማችንን ፅዳትና ውበት ለዓለም የገለጠ ስኬታማ መርሐ ግብር ነበር ብለዋል፡፡

የኢትዮጵያን ትክክለኛ ገፅታ ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማስተዋወቅ ትልቅ ዕድል ፈጥሯል ያሉት ከንቲባዋ፥ ወደፊትም ብዙዎችን ወደ ሀገራችን እንደሚስብ እምነታቸውን ገልጸዋል፡፡

ሁነቱ እስካሁንም መነጋገሪያነቱ መቀጠሉን ገልጸው፥ መርሐ ግብሩን ላስተባበሩ ሀገር ወዳድና ተፅዕኖ ፈጣሪ ወጣቶች፣ ለፌደራልና ለአዲስ አበባ መንግስታዊና የግል ተቋማት ምስጋና አቅርበዋል፡፡

በተለይም የቱሪዝም ሚኒስቴር፣ የአዲስ አበባ ከተማ ቱሪዝም ኮሚሽን፣ የአዲስ አበባ ኮሙኒኬሽን ቢሮ፣ ይሳቃል ኢንተርቴይመንትና ሌሎች ባላድርሻ አካላት ላሳዩት ቅንጅት አድናቆታቸውን ገልጸዋል፡፡

👉ለፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎች የፋና ዲጂታል አድራሻዎችን ከአስተያየት መስጫ ሳጥኑ ያግኙ፡-

ወጣት አማኑኤል አሼቦ ከአባታቸው ከአቶ አሼቦ አብሶና ከእናታቸው ወ/ሮ ሙሉ ሌሬቦ በ1992 ዓ/ም ተወልደው በደቡብ አፍሪካ የግል ስራቸውን በመስራት ላይ እያሉ + 30/04/2018 በደረሰባቸ...
14/01/2026

ወጣት አማኑኤል አሼቦ ከአባታቸው ከአቶ አሼቦ አብሶና ከእናታቸው ወ/ሮ ሙሉ ሌሬቦ በ1992 ዓ/ም ተወልደው በደቡብ አፍሪካ የግል ስራቸውን በመስራት ላይ እያሉ + 30/04/2018
በደረሰባቸው ድንገተኛ አደጋ በተወለደ በ26 ዓመታቸው ከዚህ አለም በሞት ተለይተዋል፡፡

የቅዱሳን ሞት በእግዘኣብሔር ፊት የከበረ ነው!! Η 116:15

ለወዳጅ ዘመዶቹ መፅናናትን እንመኛለን ከቤተሰቦቹ

የሀገራዊ ምክክር መረጃዎችን ተደራሽ ለማድረግ የተቋማት ቁርጠኝነት ተቋማት የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የስራ እንቅስቃሴዎችን ጨምሮ የተለያዩ መረጃዎችን ለህብረተሰቡ ተደራሽ ለማድረግ በ...
14/01/2026

የሀገራዊ ምክክር መረጃዎችን ተደራሽ ለማድረግ የተቋማት ቁርጠኝነት

ተቋማት የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የስራ እንቅስቃሴዎችን ጨምሮ የተለያዩ መረጃዎችን ለህብረተሰቡ ተደራሽ ለማድረግ በቁርጠኝነት እንሰራለን አሉ።

ኮሚሽኑ የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ፣ የትምህርት፣ የጤና ዘርፍ ተቋማት እና ማህበራት እንዲሁም ኢትዮ ቴሌኮም ተሳታፊ የሆኑበት የውይይት መድረክ አካሂዷል።

የመድረኩ ዓላማ ኮሚሽኑ የመረጃ ተደራሽነቱን ለማስፋት ያለመ እንደሆነ ተገልጿል።

መድረኩ ከመገናኛ ብዙኃን አማራጮች በተጨማሪ ሕብረተሰቡ በሚገለገልባቸው ቦታዎች፣ የቴክኖሎጂ ውጤቶች እና የትራንስፖርት አማራጮች አማካኝነት ኮሚሽኑ ራሱን በሚያስተዋውቅበትና መረጃዎችን ተደራሽ በሚያደርግባቸው መንገዶች ዙሪያ መክሯል።

የመድረኩ ተሳታፊ ተቋማት ሀገራዊ ምክክሩ ዘላቂ ሰላም የሚረጋገጥበት ብቸኛ መንገድ በመሆኑ በተቋማቸው አገልግሎቶች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎችን በመስራት ሚናቸውን እንደሚወጡ አረጋግጠዋል።

የሀገራዊ ምክክር ሂደቱ በታላቅ ህዝባዊ ተሳትፎ ይሳካ ዘንድ በግንዛቤ ማስጨበጥ ስራ የነቃ ተሳትፎ እንደሚያደርጉ ተናግረዋል።

ኢትዮ ቴሌኮም ከብዝሃ መልዕክት ስርጭት እስከ ሞባይል መተግበሪያ ድረስ ባሉት አማራጮች የኮሚሽኑን መረጃዎች ተደራሽ በማድረግ የሚጠበቅበትን ሀላፊነት እንደሚወጣም ተገልጿል።

የመድረኩ ተሳታፊ ተቋማት ለኮሚሽኑ መረጃዎች ተደራሽነት በየተቋሞቻቸው ሊያከናውኗቸው የሚችሏቸውን ተግባራት ለይተው ለኮሚሽኑ ያስረከቡ ሲሆን፤ ተግባራቱን በመምራት የሚያስፈፅም የጋራ ግብረ-ኃይልም ተቋቁሞ ሥራ ለመጀመር የሚያስችል ስምምነት መደረጉን ኮሚሽኑ ገልጿል።

👉ለፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎች የፋና ዲጂታል አድራሻዎችን ከአስተያየት መስጫ ሳጥኑ ያግኙ፡-

አዲስ አበባ፣ ጥር 6፣ 2018
(ኤፍ ኤም ሲ)
KWWMN የልማት ቲቢ

 በጠደሌ ደረጃ የሚካሄዱት     ።1ኛ/ ከጥር 15-17፣ 2018 ዓ/ም (አርብ፣ቅዳሜ፣ እና እሁድ) ተይዞ የነበረው መንፈሳዊ ኮንፍረንስ፤ እና2ኛ/ (እሁድ) ጥር 24፣ 2018 ዓ/ም ተይዞ ...
14/01/2026



በጠደሌ ደረጃ የሚካሄዱት



1ኛ/ ከጥር 15-17፣ 2018 ዓ/ም (አርብ፣ቅዳሜ፣ እና እሁድ) ተይዞ የነበረው መንፈሳዊ ኮንፍረንስ፤ እና
2ኛ/ (እሁድ) ጥር 24፣ 2018 ዓ/ም ተይዞ የነበረው ሕዝባዊ ኮንፍረንስ፤

ሁለቱም (እንደየቅደም ተከተላቸው) በጠደሌ የአቢያተክርስቲያናት መሪዎች እና የኮካታ መሪዎች በኩል ውይይት ተደርጎባቸው፤ ተለዋጭ ቀናት ተመርጠው ወደፊት የምናሳውቅ ይሆናል።

እስከዚያ ድረስ በዚህ የጥር ወር በየቀበሌዎች የዝግጅት ሥራዎች እየተሠሩ ይቆያሉ። እንዲሁም ሌሎች በቀበሌ ደረጃ የሚከናወኑ ተግባራት ይከናወናሉ።

በዚህ የፌስቡክ ገፅ የተጀመረው ታሪክን የማጋራት ተግባር ይቀጥላል።
ተሜ ቶኪ ጥር 6፣ 2018 አዲስ አበባ ኢትዮጵያ

ታዋቂው ዩቲዩበር አይሾው ስፒድ የኢትዮጵያ ቆይታ…በዩቲዩብ ቻናሉ ከ48 ነጥብ 6 ሚሊየን በላይ ተከታይ ያለው ታዋቂ አሜሪካዊው ዩቲዩበር ዳረን ዋትኪንስ ጁኒየር (አይሾው ስፒድ) በትናንትናው ...
14/01/2026

ታዋቂው ዩቲዩበር አይሾው ስፒድ የኢትዮጵያ ቆይታ…

በዩቲዩብ ቻናሉ ከ48 ነጥብ 6 ሚሊየን በላይ ተከታይ ያለው ታዋቂ አሜሪካዊው ዩቲዩበር ዳረን ዋትኪንስ ጁኒየር (አይሾው ስፒድ) በትናንትናው ዕለት አዲስ አበባን ጎብኝቷል።

የ21 ዓመቱ ዩቲዩበር በአዲስ አበባ የተለያዩ አካባቢዎች በመዘዋወር የጎበኘ ሲሆን÷ በቀጥታ ስርጭት ያስተላለፈውን ጉብኝት ከ260 ሺህ በላይ ሰዎች በቀጥታ ተመልክተዋል እንዲሁም አሁን ላይ ደግሞ የተመልካቾቹ ቁጥር 9 ነጥብ 9 ሚሊየን ተሻግሯል።

ታዋቂ ዩቲዩበሩ በአዲስ አበባ ቆይታው፡-

👉 አዲስ አበባ ሲደርስ የቱሪዝም ሚኒስትሯ ሰላማዊት ካሳ አቀባበል አድርገውለታል
👉 የዓድዋ መታሰቢያ ሙዚየምን በባዶ እግሩ ጎብኝቷል

👉 የተለያዩ ባሕላዊ ውዝዋዜ መሞከር ችሏል
👉 የኢትዮጵያን ቁርጥ ስጋን ጨምሮ የተለያዩ ባሕላዊ ምግቦችን ተመግቧል

👉 በኢትዮጵያ ባህል ስፖርቶች ፌዴሬሽን አዘጋጅነት የገና ባህላዊ ጨዋታን ተጫውቷል
👉 የኢትዮጵያ ባሕላዊ የሙዚቃ መሳሪያ የሆነውን ማሲንቆ ተጫውቷል

👉 ከአምስቱ እህትማማች አትሌቶች (የዲባባ ቤተሰቦች) ጋር ተገናኝቷል
👉 በአዲስ አበባ ከተማ የተሰሩ የኮሪደር ልማቶች እና ፓርኮችን ተዘዋውሮ ተመልክቷል

👉 በሚስ ወርልድ 2025 የቁንጅና ውድድር ከአፍሪካ 1ኛ ከዓለም 2ኛ የወጣችውን ሀሴት ደረጄ ጋር ባደረገው ቆይታ በኢትዮጵያ የተመረተ የሌዘር ጃኬት ስጦታ ተበርክቶለታል

👉 በመዲናዋ የተሰሩ የከተማ ማስዋብ ስራዎችን ለዓለም አስተዋውቋል
👉 የኢትዮጵያን እንግዳ ተቀባይነት በሚሊየን ለሚቆጠሩ ተከታዮቹ አስመልክቷል።

👉ለፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎች የፋና ዲጂታል አድራሻዎችን ከአስተያየት መስጫ ሳጥኑ ያግኙ፡-

ጥር 6፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ)
KWWMN የልማት ቲቢ

🏰 ጎንደር ለጥምቀት አሸብርቃ እንግዶቿን እየተቀበለች ነው!* "እንኳን ተወለድክ መይሳው!"ዛሬ ጥር 6 ቀን 2018 ዓ.ም፤ ጎንደር በሁለት ምክንያት ድርብ ደስታ ላይ ናት። አንደኛው የጥምቀት...
14/01/2026

🏰 ጎንደር ለጥምቀት አሸብርቃ እንግዶቿን እየተቀበለች ነው!

* "እንኳን ተወለድክ መይሳው!"

ዛሬ ጥር 6 ቀን 2018 ዓ.ም፤ ጎንደር በሁለት ምክንያት ድርብ ደስታ ላይ ናት። አንደኛው የጥምቀት እንግዶቿን እየተቀበለች ሲሆን፤ ሁለተኛው ደግሞ የታሪክ ማህደርን የቀየሩት እና ለኢትዮጵያ አንድነት ዋጋ የከፈሉት የዳግማዊ አፄ ቴዎድሮስ 207ኛ ዓመት የልደት ቀን ዛሬ መሆኑ ነው።

​በኢትዮጵያ አየር መንገድ በረራ ቁጥር ET 162 ተሳፍረን አፄ ቴዎድሮስ ኤርፖርት ስንደርስ፤ ጎንደር የጀግንነት እና የመንፈሳዊነት ድባብ ተላብሳ ጠበቀችን።

​የጎንደር ቆይታችን ቅምሻዎች፡-
✈️ አቀባበል፡ በኃይሌ ሪዞርት እና ሆቴል የተደረገልን ኢትዮጵያዊ መስተንግዶ የጉዞ ድካማችንን አስረሳን።

✨ ድባብ፡ ከተማዋ ገና ከወዲሁ የጥምቀትን ድምቀት ለብሳለች። ፋሲል ግንብም በግርማ ሞገስ እንግዶቹን እየተመለከተ ነው።

​በባህልና ስፖርት ሚኒስቴር እንዲሁም በባህል ጥበባት ሚዲያ ፎረም የተዘጋጀው ይህ ጉዞ፤ የታሪክ እና የባህል ድግስን ይዞ ይቀጥላል...

​መልካም የጥምቀት በዓል ለሁላችን!

​✍️ ጌትነት ተመስገን

Address

144 Pangani Heihght
Botswana
00100

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Kembata World Wide Media Network posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Kembata World Wide Media Network:

Share

Category

Kembata World Wide Media Network -KWWMN

KWWMN የልማት ቲቪ ኢትዮጵያ ሰፊ የከምባታ አለም አቀፍ መገናኛ አውታር Update ወርልድ ዋይድ ቴሌቪዥን ይዘን እንቀርባለን ዘር ቀለም ሳይለዩ አገራቸውን በታማኝነት እናገለግላለን። ከታች በሚገኘው አድሬስ መልስ የፈለጉትን መልዕክት ማስቀመጥ ይችላሉ እናመሰግናለን የእርስዎ ምክር እና አስተየት ነው እዚህ ያደረሠን Thanks for messaging us. I value your comments, recommendations, suggestions and questions. try to respond as soon as possible. please understand that for me. thank u! ከከምባታ የልማት ቲቪ የዝግጅት ክፍል. WWW.KWWMN.OCM

[email protected] & [email protected]