Kembata World Wide Media Network

Kembata World Wide Media Network KWWMN registered inSouth Africa non-profit-organization.withheadquartersin Johannesburg,South Africa
(1)

Kembata worldwide Media Network registered in South Africa based as an independent and non-organization with headquarters in Johannesburg, South Africa. The organization is made up mainly of ambassadors, doctors, other professions that help in achieving to serve the Ethiopian community in South Africa It is an institution that provides genuine information and access to those in need.

የቦታ ለዉጥ መደረጉን ለማሳወቅ ይሆናል የወንድማችን አቶ ሚካኤል አበበ የመታሰቢያ ፕሮግራም ቀድሞ ይደረጋል ከተባለው በትዉልድ ለክርስቶስ ቤተክርስቲያን ወደ ኬብሮን ጴንጠቆስጣዊት ቤተክርስቲያ...
12/11/2025

የቦታ ለዉጥ መደረጉን ለማሳወቅ ይሆናል
የወንድማችን አቶ ሚካኤል አበበ የመታሰቢያ ፕሮግራም ቀድሞ ይደረጋል ከተባለው በትዉልድ ለክርስቶስ ቤተክርስቲያን ወደ ኬብሮን ጴንጠቆስጣዊት ቤተክርስቲያን የተደረገ መሆኑን ለማሳወቅ እንወዳለን ።

ከጥዋቱ 4:00 ስዓት በወንድማችን የሺኚት ፕሮግራም ላይ እንድትገኙ እናሳስባለን።

↪️ከሟች ከቤተሰብ 💔💔💔😭😭😭

የደቡብ እና ደቡባዊ አፍሪካ የሚዲያ ጥምረት በዚህ ከባድ ሀዘን የተሰማንን ጥልቅ ሀዘን እየገለጽን ሌሎች የሚዲያ ሽፈን በመስጠት አዳዲስ መረጃዎችን የምናሳውቅ ይሆናል።

ማሳሰቢያ የወንድማችን አቶ ሚካኤል አበበ የመታሰቢያ ፕሮግራም በነገው ዕለት በትዉልድ ለክርስቶስ ቤተክርስቲያን ከጠዋቱ 4:00 ሰዓት ጀምሮ ይካሄዳል ።ስለዚህ በስፍራው በጊዜ በመገኘት የዚህን...
12/11/2025

ማሳሰቢያ

የወንድማችን አቶ ሚካኤል አበበ የመታሰቢያ ፕሮግራም በነገው ዕለት በትዉልድ ለክርስቶስ ቤተክርስቲያን ከጠዋቱ 4:00 ሰዓት ጀምሮ ይካሄዳል ።

ስለዚህ በስፍራው በጊዜ በመገኘት የዚህን ታታሪ እና ሰዉ አክባሪ ወንድማችን ሺኚት ፕሮግራም ላይ እንድትገኙ ይሁን ።

↪️ከሟች ከቤተሰብ

የደቡብ እና ደቡባዊ አፍሪካ የሚዲያ ጥምረት በዚህ ከባድ ሀዘን የተሰማንን ጥልቅ ሀዘን እየገለጽን ሌሎች የሚዲያ ሽፈን በመስጠት አዳዲስ መረጃዎችን የምናሳውቅ ይሆናል።

ዜና ህልፈት 💔😭እጅግ የሚወደድ እና ታታሪ ትጎ ሰራተኛ ወጣት ፍልቅልቅ አቶ ሚካኤል አበባ የሶስት ልጆች አባት እና የአንዲት ሚስት ባል ሲሆን በትላንትናው ዕለት በቅጥረኞች ህይወቱ ልታልፍ ች...
12/11/2025

ዜና ህልፈት 💔😭

እጅግ የሚወደድ እና ታታሪ ትጎ ሰራተኛ ወጣት ፍልቅልቅ አቶ ሚካኤል አበባ የሶስት ልጆች አባት እና የአንዲት ሚስት ባል ሲሆን በትላንትናው ዕለት በቅጥረኞች ህይወቱ ልታልፍ ችላለች።

በጆሀንስበርግ ከተማ ከስራ ሲመለስ ጠብቀው ህይወቱን ነጠቁት በርካታ ጥይቶች እላዩ ላይ በማርከፍከፍ በክፍተኛ ጭካኔ ህይወቱን ነጥቀዋል። ፈጣሪ በደቡብ አፍሪካ የምንኖር ዲያስፖራ ወንድም እህቶችን እና መላው ቤተሰቡን በሀገር ዉስጥ እና ከሀገር ዉጪ ያሉትን ሁሉ ፈጣሪ መፅናናትን ይስጠን። እንደዚህ አይነት ልብ ስባሪ ዜናዎች በተለያዩ ጊዜያት ብንሰማም ከጊዜ ወደ ጊዜ እየከፋ የመጣ እጅግ ጨካኝ ርህራሄ የሌለው በከፍተኛ ፕላን የሚድረግ የተደራጀ ህይወት መንጠቅ ነዉ። የዚህ መንስኤው ምን እንደሆነ ፈጣሪ በአደባባይ እስከሚያገልጥ ከሟች ቤተሰብ ጎን በመቆም እንድታፅናኑ እና እና ፈጣሪ በዚህ ምድር እየፈሰሰ ያለውን ደም እንዲያወጣ እየተማፀናችሁ በልበ ቅንነት ሀዘንተኞችን እንድታፅናኑ
ልናሳስብ እንወዳለን።

የደቡብ እና ደቡባዊ አፍሪካ የሚዲያ ጥምረት በዚህ ከባድ ሀዘንየተሰማንን፣ጥልቅ ሀዘን እየገለጽን ሌሎች መረጃዎችን የሚዲያ ሽፈን በመስጠት አዳዲስ መረጃዎችን የምናሳውቅ ይሆናል ፈጣሪ ነፍስህን በአፀደ ገነት ያኑርልን በሰላም እረፍ ለወዳጅ ጓደኞቹ ለዉድ ባለቤቱ እና ልጆቹ መፅናናትን ይስጥልን 😥😭🙏

20ኛው የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በወሳኝ የታሪክ ምዕራፍ ወቅት የሚከበር ነው  ሕዳር 3፣ 2018 20ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል በርካታ ሀገራዊ አጀን...
12/11/2025

20ኛው የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በወሳኝ የታሪክ ምዕራፍ ወቅት የሚከበር ነው

ሕዳር 3፣ 2018 20ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል በርካታ ሀገራዊ አጀንዳዎች በጋራ በሚከናወኑበት ወሳኝ የታሪክ ምዕራፍ ወቅት የሚከበር ነው አለ የፌዴሬሽን ምክር ቤት።

በም/ቤቱ የመንግሥታት ግንኙነት፣ የዴሞክራሲ አንድነትና የሕገ መንግሥት አስተምህሮ ቋሚ ኮሚቴ ፀሐፊ ባንቺይርጋ መለሰ እንዳሉት ፥ የቀኑ መከበር በሕዝቦች መካከል ሀገራዊ መግባባት እንዲፈጠር ያስችላል፡፡

በተጨማሪም ዴሞክራሲያዊ አንድነት እንዲከበርና ሕብረ ብሔራዊነት እንዲጎለብት እንዲሁም ፌዴራላዊ አስተሳሰብና እሴቶች እንዲጎለብቱ ጉልህ ሚና ይጫወታል ብለዋል፡፡

20ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል በርካታ ሀገራዊ አጀንዳዎች በጋራ በሚከናወኑበት ወሳኝ የታሪክ ምዕራፍ ወቅት የሚከበር መሆኑን አውስተዋል፡፡

በዓሉ ከሕዳር 25 ቀን 2018 ጀምሮ ለአምስት ተከታታይ ቀናት በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የሚከበር ሲሆን ÷ ሕዳር 29 ቀን ደግሞ የማጠቃለያው መርሐ ግብሩ በሆሳዕና ከተማ የሚካሄድ ይሆናል፡፡

በጆርጂያ በወታደራዊ አውሮፕላን መከስከስ አደጋ የ20 ሰዎች ሕይወት አለፈሕዳር 3፣ 2018 በጆርጂያ በተከሰተው የቱርክ ወታደራዊ አውሮፕላን መከስከስ አደጋ 20 ወታደሮች እና የበረራ አባላት...
12/11/2025

በጆርጂያ በወታደራዊ አውሮፕላን መከስከስ አደጋ የ20 ሰዎች ሕይወት አለፈ

ሕዳር 3፣ 2018 በጆርጂያ በተከሰተው የቱርክ ወታደራዊ አውሮፕላን መከስከስ አደጋ 20 ወታደሮች እና የበረራ አባላት ሕይወታቸው ማለፉ ተሰምቷል።

የቱርክ አየር ኃይል ንብረት የሆነውና ሲ-130 የሚል ስያሜ ያለው ወታደራዊ አውሮፕላኑ ከአዘርባጃን ተነስቶ ወደ ቱርክ እየበረረ በነበረበት ወቅት ነው በጆርጂያ ሲግናጊ ማዘጋጃ ቤት አካባቢ የተከሰከሰው።

የተለቀቁ ተንቀሳቃሽ ምስሎች እንደሚያሳዩት የአውሮፕላኑ በረራ ተዛብቶ ወደ መሬት ሲወደቅ ታይቷል፡፡

ትናንት ጠዋት ከቱርኳ ትራብዞን ከተማ ተነስቶ ለወታደራዊ ተልዕኮ ወደ አዘርባጃኗ ጋንጃ ከተማ የተጓዘው አውሮፕላኑ÷ ከጋንጃ ከተማ ወደ ቱርክ እየተመለሰ በነበረበት ወቅት ለ27 ደቂቃ ከራዳር በመሰወር ከደቂቃዎች በኋላ በጆርጂያና አዘርባጃን ድንብር አቅራቢያ መከስከሱም ነው የተገለጸው።

የቱርክ መከላከያ ሚኒስቴር እንዳስታወቀው÷ በአውሮፕላኑ ውስጥ የነበሩ 20 ወታደሮች እና የበረራ አባላት በአደጋው ሕይወታቸው አልፏል፡፡

የቱርኩ ፕሬዚዳንት ረሲብ ጣይብ ኤርዶኻን ከጆርጂያ ባለስልጣናት ጋር በመቀናጀት የአውሮፕላኑን ፍርስራሾች የማስመለስ ስራ እየተከናወነ መሆኑን ገልጸው÷ የአደጋው ምክንያት እየተጣራ ይገኛል ማለታቸውን አር ቲ እና አልጀዚራ ዘግበዋል፡፡

የመንግሥቱ ወርቁ ታሪክ በመፅሀፍ ሊወጣ ነው          ዕዝራ እጅጉ( ተወዳጅ ሚድያ)በኢትዮጵያ  የእግር ኳስ ታሪክ ውስጥ የጎላ አሻራ ከነበራቸው የኳስ ሊቆች ውስጥ አንዱ የሆነው  መንግስ...
12/11/2025

የመንግሥቱ ወርቁ ታሪክ በመፅሀፍ ሊወጣ ነው

ዕዝራ እጅጉ( ተወዳጅ ሚድያ)

በኢትዮጵያ የእግር ኳስ ታሪክ ውስጥ የጎላ አሻራ ከነበራቸው የኳስ ሊቆች ውስጥ አንዱ የሆነው መንግስቱ ወርቁ የእግር ኳስ ታሪኩ በመፅሐፍ ተፅፎ ሊመረቅ ነው።

"መንግስቱ ወርቁ የእግር ኳስ ዕንቁ" የተሰኘውን መፅሐፍ ያዘጋጀው ዶክተር ሰሎሞን በርሄ ሲሆን የምረቃ መርሀ-ግብሩም እሁድ ህዳር
14 2018 ዓ.ም ከምሽቱ 12 ሰዓት ጀምሮ በሀይሌ ግራንድ ሆቴል ይደረጋል።

ይህ የመፅሐፍ ምረቃ መርሀ ግብር ከመካሄዱ ቀደም ብሎ ቅዳሜ ሕዳር 6 2018ዓ.ም ከጠዋቱ በ4 ሰአት በመንግሥቱ ወርቁ ስም የተሰየመው የአቢሲኒያ ባንክ ቅርንጫፍ ቢሮ ይመረቃል ። በማግስቱ እሑድ ሕዳር 7 ደግሞ ከጠዋቱ 3 ሰአት አስከሬኑ ያረፈበት አዲስ ሐውልት በጴጥሮስ ወጳውሎስ ቤተክርስቲያን እንደሚመረቅ ለማወቅ ተችሏል።

መንግሥቱ ወርቁ ይጠቀምባቸው የነበሩ ቁሳቁሶች (ማልያ ፣ ቁምጣ ፣ ገንባሌን ጨምሮ) እና ሽልማቶቹ ለአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ጥናትና ምርምር ተቋም ፣ለሀገሪቱ ባለውለታ የሆኑ ጀግኖች ቅርስ በሚቀመጥበት ሥፍራ በክብር እንደሚቀመጥ ለማወቅ ተችሏል

መንግስቱ ወርቁ ለኳስ ታላቅ ፍቅር ያሳደረ፣ የአገሩንም ስም በመልካም ያስጠራ እንደሆነ መላ የእግር ኳስ አፍቃሪ የሚመሰክረው ሐቅ መሆኑን የመፅሀፉ ደራሲ ይናገራል።

መንግሥቱ ወርቁ ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ተሰልፎ በመጫወት በማንኛውም የአገራችን ተጫዋቾች ያልተደፈሩ ክብረወሰኖች ባለቤት ነው። መንግሥቱ ፣ለሀገሩ በተሰለፈባቸው 98 ጨዋታዎች 61 ግብ በማስቆጠር የብሔራዊ ቡድኑ ባለክብረወሰን ለመሆን የቻለ ነው።

የእግር ኳስ ህይወቱን በወርቃማው ዘመን ያሳየው መንግስቱ አገራችን በአፍሪካ ዋንጫ ያላት ታሪክ ደማቅ እንዲሆን ካደረጉት መካከል በግንባር ቀደምትነት የሚጠቀስ ነው።

የመፅሐፉ ደራሲ ዶክተር ሰሎሞን በርሄ በ1950 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ከተማ ዘውዲቱ ሆስፒታል ውስጥ የተወለደ ሲሆን በትውልድ ከተማው ዳዊት ደግሞ እስከ 12ኛ ክፍል ከተማረ በኋላ ጎንደር ሕክምና ሣይንስ ገብቶ ሕክምና አጥንቷል።የቀለም ትምህርቱን በተመለከተ የሁለት የመጀመሪያ ዲግሪዎች ፣ የአራት የሁለተኛ ዲግሪዎችና የአንድ ፒ.ኤች.ዲ ባለቤትም ነው።

የሥነ-ጽሑፍ ተሳትፎውን በተመለከተ አሥራ ዘጠኝ ሥራዎቹ ለሕትመት ሲበቁ ሦስት ተውኔቶች ጽፎ አንዱ ለመድረክ በቅቷል ።
ባለትዳርና የሁለት ወንዶች ልጆች አባትም ነው ።

ዶክተር ሰሎምን መጽሐፉን ለማዘጋጀት ሐሳብ የነበረው ከስድስት ዓመት በፊት ነው ። በተለያዩ ምክንያቶች ዘግይቶ በልጁ በዳዊት መንግሥቱ ወርቁ አማካይነት "የመንግሥቱ ወርቁ የታሪክ ዳግም ትንሣኤ ኮሚቴ" ሲቋቋም የመጽሐፉን ሥራ እንደገና መጀመሩን ይናገራል።

መጽሐፉን በዓይነቱ የተለየ የሚያደርገው በምርምር ላይ የተመሠረተና የተለያዩ ግብአቶችን የተጠቀመ ከመሆኑም በላይ ከራሱ ከባለታሪኩ አንደበት የተቀዳ በመሆኑም ጭምር ነው ። ከዚህ በተጨማሪም ከመንግሥቱ ጋር አብረው የተጫወቱ ጓደኞቹ ፣ ያሠለጠናቸው ተጫዋቾች ፣ የሥራ ባልደረቦቹ ፣ አድናቂዎቹ ፣ የቅርብ ጓደኞቹ...ስለእርሱ የነበራቸውን ትውስታ ያካፈሉበት መሆኑ ለመጽሐፉ የተለየ ውበትና ድምቀት አጎናጽፎታል ።

ይህን የመፅሐፍ ምረቃ እና መፅሀፉን በመገናኛ ብዙኃን በማስተዋወቅ የማስተባበር ሥራውን እያከናወነ የሚገኘው ተወዳጅ ሚድያ እና ኮምዩኒኬሽን (ዕዝራ እጅጉ) ሲሆን ድርጅቱም የኢትዮጵያ የቀድሞ የእግር ኳስ ታሪክ የድምፅ ዘጋቢ ሥራዎችን በማውጣት የሚታወቅ ነው።

ኢትዮጵያ ኮፕ32ን ለማዘጋጀት ትክክለኛዋ ምርጫ ናት!በብራዚል፣ ቤለም እየተካሄደ ባለው የዓለም የአየር ንብረት ጉባዔ (ኮፕ30) ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2027 የሚካሄደውን ኮፕ32 ለማዘጋጀት በ...
11/11/2025

ኢትዮጵያ ኮፕ32ን ለማዘጋጀት ትክክለኛዋ ምርጫ ናት!

በብራዚል፣ ቤለም እየተካሄደ ባለው የዓለም የአየር ንብረት ጉባዔ (ኮፕ30) ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2027 የሚካሄደውን ኮፕ32 ለማዘጋጀት በይፋ ጥያቄ አቅርባ የተሳታፊ ሀገራቱን ይሁንታ አግኝታለች።

ጉባዔውን ለማዘጋጀት ኢትዮጵያ በእርግጥም ትክክለኛዋ ምርጫ ናት፤ ለምን ቢባል፥
• ቁርጠኝነትን የተላበሰ ጠንካራ አመራር አላት
• የአፍሪካ ዲፕሎማሲ መዲና ናት
• የአየር ንብረት ለውጥን ለመከላከል ተጨባጭ እርምጃ በመውሰድ ላይ ናት
• መዲናዋ አዲስ አበባ ለኮንፈረንስ ቱሪዝም ምቹ ሆና ተዘጋጅታለች
• ጉባዔውን በኢትዮጵያ ማዘጋጀት የአፍሪካን ድምፅ በዓለም ይበልጥ ተደማጭ ያደርገዋል
ወቅታዊ መረጃ ለማግኘት

የላጲሶ ጌ’ዴሌቦ (ፕ/ር) የአስከሬን ሽኝት ሥነ ሥርዓት እየተካሄደ ነውሕዳር 2 ፣ 2018 የላጲሶ ጌ’ዴሌቦ (ፕ/ር) አስከሬን ሽኝት ሥነ ሥርዓት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ 6 ኪሎ ካምፓስ እ...
11/11/2025

የላጲሶ ጌ’ዴሌቦ (ፕ/ር) የአስከሬን ሽኝት ሥነ ሥርዓት እየተካሄደ ነው

ሕዳር 2 ፣ 2018 የላጲሶ ጌ’ዴሌቦ (ፕ/ር) አስከሬን ሽኝት ሥነ ሥርዓት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ 6 ኪሎ ካምፓስ እየተካሄደ ነው፡፡

በሽኝት ሥነ ሥርዓቱ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊ እና የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት አደም ፋራህን ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች፣ የሥራ ባልደረቦችና ወዳጅ ዘመዶች ተገኝተዋል።

የላጲሶ ጌ’ዴሌቦ (ፕ/ር) ሥርዓተ ቀብርም ከቀኑ 7 ሰዓት ላይ በጴጥሮስ ወጳውሎስ መካነ መቃብር ይፈጸማል፡፡

የታሪክ ተመራማሪው ላጲሶ ጌ’ዴሌቦ (ፕ/ር) ባደረባቸው ሕመም ሕክምናቸውን ሲከታተሉ ቆይተው ጥቅምት 30 ቀን 2018 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት መለየታቸው ይታወቃል፡፡

ላጲሶ (ፕ/ር) በኢትዮጵያ እንዲሁም በአፍሪካ የታሪክ ጥናትና ምርምር በማካሄድ የተለያዩ የታሪክ መጻሕፍትን ለአንባቢያን አበርክተዋል፡፡

የኢትዮጵያውያንን የጋራ እሴት፣ ባሕልና ቋንቋ በማውሳት የሕዝቦች ታሪክ ጎልቶ እንዲታወቅ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከታቸውም ተጠቁሟል፡፡

የኢትዮጵያን የእደ-ጥበብ ውጤቶች በዓለም አቀፍ መድረክ ላይ የማስተዋወቅ ሥራ እየተከናወነ ነው። እ.ኤ.አ ከኖቨንበር 9 እስከ 15 ቀን 2025 "Handcrafts Art Authenticity ...
10/11/2025

የኢትዮጵያን የእደ-ጥበብ ውጤቶች በዓለም አቀፍ መድረክ ላይ የማስተዋወቅ ሥራ እየተከናወነ ነው።

እ.ኤ.አ ከኖቨንበር 9 እስከ 15 ቀን 2025 "Handcrafts Art Authenticity and Creative" በሚል መሪ ቃል በአልጄሪያ በሚካሄደው International Handcraft Fair (SIAT-2025) ላይ የኢትዮጵያን የዕደ ጥበብ ውጤቶች የማስተዋወቅ ሥራ እየተከናወነ ነው፡፡

​መርሀ-ግብሩ ላይ ተሳትፎ እያደረጉ የሚገኙት ጤናዳም ማኒፋክቸሪንግ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር እና ጥሩ ዲዛይን በሚል ስያሜያቸው የሚታወቁ ሀገር በቀል ድርጅቶች ልዩ ልዩ የሀገራችንን የዕደ ጥበብ ውጤቶች የሚያንፀባርቁ ሥራዎችን ይዘው በመቅረብ በስፋት የማስተዋወቅ ሥራ እያከናወኑ ነው።

የድርጅቶች ተሳትፎ የኢትዮጵያን ባህላዊ የእደጥበብ ምርቶች ለዓለም አቀፍ ገበያ ለማስተዋወቅና በዘርፉ ካሉ የሌሎች ሀገራት ባለሙያዎች ጋር ልምድ ለመለዋወጥ ወሳኝ አጋጣሚ በመሆኑ በቱሪዝም ሚኒስቴር በኩል አስፈላጊው ትብብር ተደርጎላቸዋል።

የላጲሶ ጌ’ዴሌቦ (ፕ/ር) ቀብር ሥነ ሥርዓት ነገ ይፈጸማልሕዳር 1 2018 የታሪክ ተመራማሪው ላጲሶ ጌ’ዴሌቦ (ፕ/ር) ቀብር ሥነ ሥርዓት በነገው ዕለት ይፈጸማል፡፡የላጲሶ ጌ’ዴሌቦ (ፕ/ር)...
10/11/2025

የላጲሶ ጌ’ዴሌቦ (ፕ/ር) ቀብር ሥነ ሥርዓት ነገ ይፈጸማል

ሕዳር 1 2018 የታሪክ ተመራማሪው ላጲሶ ጌ’ዴሌቦ (ፕ/ር) ቀብር ሥነ ሥርዓት በነገው ዕለት ይፈጸማል፡፡

የላጲሶ ጌ’ዴሌቦ (ፕ/ር) አስከሬን ሽኝት መርሐ ግብር ነገ 5 ሰዓት ላይ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ 6 ኪሎ ካምፓስ እንደሚካሄድ ተመላክቷል፡፡

ሥርዓተ ቀብራቸውም ነገ 7 ሰዓት ላይ በጴጥሮስ ወጳውሎስ መካነ መቃብር እንደሚፈጸም አስተባባሪ ኮሚቴው ለፋና ዲጂታል ገልጿል፡፡

የታሪክ ተመራማሪው ላጲሶ ጌ’ዴሌቦ (ፕ/ር) ባደረባቸው ሕመም ሕክምናቸውን ሲከታተሉ ቆይተው በትናንትናው ዕለት ከዚህ ዓለም በሞት መለየታቸው ይታወቃል፡፡

ላጲሶ (ፕ/ር) በኢትዮጵያ እንዲሁም በአፍሪካ የታሪክ ጥናትና ምርምር በማካሄድ የተለያዩ የታሪክ መጽሐፍትን ለአንባቢያን አበርክተዋል፡፡

የኢትዮጵያውያንን የጋራ እሴት፣ ባሕልና ቋንቋ በማውሳት የሕዝቦች ታሪክ ጎልቶ እንዲታወቅ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከታቸውም ተጠቁሟል፡፡

በተቀናጀ መንገድ ሕገ-ወጥ  የውጭ ምንዛሪ  አሻጥሮችን ሲፈጽሙ የተደረሰባቸው  አንድ መቶ አስራ ሁለት ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ሥር  ዋሉህዳር 1/2018 በተቀናጀ መንገድ ሕገ-ወጥ  የውጭ ምን...
10/11/2025

በተቀናጀ መንገድ ሕገ-ወጥ የውጭ ምንዛሪ አሻጥሮችን ሲፈጽሙ የተደረሰባቸው አንድ መቶ አስራ ሁለት ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ሥር ዋሉ

ህዳር 1/2018 በተቀናጀ መንገድ ሕገ-ወጥ የውጭ ምንዛሪ አሻጥሮችን ሲፈጽሙ የተደረሰባቸው አንድ መቶ አስራ ሁለት ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት አስታወቀ።

አገልግሎቱ ለኢዜአ በላከው መረጃ እንዳስታወቀው፥ መንግሥት ተግባራዊ ያደረገውን የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ በመጻረር በተደራጀ መንገድ በሚፈጽሙ ሕገ-ወጥ የውጭ ምንዛሪ አሻጥሮች ዙሪያ በተቀናጀ መልኩ ምስጢራዊ የመረጃ ስምሪት ሲከናወን ቆይቷል፡፡

የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት፣ የፋይናንስ ደኅንነት አገልግሎት፣ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ፣ የክልል የፀጥታ አካላት እና በህብረተሰቡ ጥቆማ በተደረገ የተቀናጀ ሥምሪት በፋይናንስ አሻጥር የተሰማሩ አንድ መቶ አስራ ሁለት ኢትዮጵያውያንና የተለያዩ የውጭ ሀገር ዜግነት ያላቸው ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን፤ ከሕገ -ወጥ ተግባሩ ጋር ትስስር የነበራቸው አምስት መቶ አስራ ዘጠኝ የባንክ አካውንቶች መታገዳቸውን እንዲሁም የተለያዩ ኤግዚቢቶች መያዛቸውን መግለጫው አመልክቷል፡፡

ሕገ- ወጥ ሃዋላዎች ፣ የገንዘብ ዝውውሮች፣ የውጭ ምንዛሪ ስወራዎች ፣ የግብር ስወራዎች፣ ሕገ- ወጥ ገንዘብን ሕጋዊ የማስመሰልና ሌሎች ተመሳሳይ ወንጀሎች በሀገር ኢኮኖሚ ላይ ከፍተኛ ጉዳት ሲያስከትሉ እንዲሁም አሸባሪዎችንና የታጠቁ ቡድኖችን ለመደገፍ ሲውሉ መቆየታቸውን መግለጫው አመልክቷል፡፡

በተለይም ሕገ- ወጥ በሆኑ ዓለም አቀፍ የገንዘብ አስተላላፊ ድርጅቶች፤ ሕገ- ወጥ የውጭ ምንዛሪ ማስተላለፊያ መተግበሪያዎች፤ የክሪፕቶ ከረንሲ መተግበሪያዎች፤ ሕገ-ወጥ የሃዋላ አዘዋዋሪዎችና ደላላዎች፤ በወጪና ገቢ ንግድ ላይ አሻጥር የፈፀሙ አስመጪዎችና ላኪዎች እንዲሁም ሕጋዊ ንግድ ሳይኖራቸው በሕገ-ወጥ ሃዋላ ላይ በመሰማራት ከፍተኛ ገንዘብ በማንቀሳቀስ በሀገር ኢኮኖሚ ላይ ከፍተኛ ጉዳት ባደረሱ አካላት የማያዳግም ሕጋዊ እርምጃ መወሰዱን መግለጫው ጠቁሟል፡፡

በተለያዩ ዓለማት የሚገኙ ኢትዮጵያውያን የሚልኩት ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ ወደ ሀገር ውስጥ እንዳይገባ የብሔራዊ ባንክን መመሪያ በሚጥስ ሁኔታ በሀገር ኢኮኖሚ ላይ ከፍተኛ ጉዳት ሲያስከትሉ የቆዩ ሕጋዊ ፈቃዳቸው በፈጸሙት ተደጋጋሚ ጥፋት በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የተሰረዘባቸው ዓለም አቀፍ የሃዋላ አስተላላፊዎችና ሕገ-ወጥ የሃዋላ ድርጅቶችም እርምጃው የተወሰደባቸው ናቸው ብሏል።

በተጨማሪም በሀገር ውስጥ ሕገ- ወጥ የውጭ ምንዛሪ ማስተላለፊያ መተግበሪያዎችን በመጠቀም ሀብትን ከሀገር በማሸሽ ላይ ያሉ ድርጅቶች ባለቤቶችም በቁጥጥር ሥር ውለዋል ነው ያለው።

የብሔራዊ ባንክ ሕግን በሚጥስ ሁኔታና ያለምንም ፈቃድ የክሪፕቶ ከረንሲ መተግበሪያን በመጠቀም በሕገ- ወጥ መንገድ የውጭ ምንዛሪን ሲያዘዋውሩ የነበሩ አካለት ላይም እርምጃ መወሰዱንም መግለጫው አመልክቷል፡፡

በሀገሪቱ ብሔራዊ ጥቅም ላይ በማነጣጠር ሲፈጸም የነበረው ኢኮኖሚያዊ አሻጥር ትላልቅ የመንግሥት ፕሮጀክቶችን ለማስተጓጎል፤ ሕዝብ በመንግሥት ላይ ቅሬታ እንዲያድርበት እንዲሁም የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ እንዳያንሰራራ በተቀናጀ መንገድ ሲፈጽሙት የነበረ መሆኑንም አንስቷል፡፡

የሀገርን ደኅንነት ስጋት ላይ በሚጥሉ እና የሀገርን ኢኮኖሚ በሚጎዱ አሻጥሮች ላይ ተሳታፊ የሆኑ አካላትን በመከታተል የማያዳግም እርምጃ ለመውሰድ የተጀመረው የተቀናጀ ጥረት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጿል።

የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት በመግለጫው፥ መላው ሀገር ወዳድ ዜጋ መሰል ወንጀሎችንና ወንጀለኞችን በማጋለጥ እያደረገ ያለውን ተሳትፎ አጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ አቅርቧል፡፡

በተለያዩ አገራት በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ይኖሩ የነበሩ ኢትዮጵያውያንን ወደ አገራቸው የመመለሱ ሥራ ተጠናክሮ  ቀጥሏል-የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ህዳር 1/2018 በተለያዩ አገራት በአስቸጋሪ ሁኔ...
10/11/2025

በተለያዩ አገራት በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ይኖሩ የነበሩ ኢትዮጵያውያንን ወደ አገራቸው የመመለሱ ሥራ ተጠናክሮ ቀጥሏል-የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር

ህዳር 1/2018 በተለያዩ አገራት በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ይኖሩ የነበሩ ኢትዮጵያውያንን ወደ አገራቸው የመመለሱ ሥራ ተጠናክሮ መቀጠሉን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አመልክቷል።

ዜጎች ከህገ ወጥ ጉዞ ራሳቸውን እንዲጠብቁም አሳስቧል።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ በተለያዩ አገራት በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ይኖሩ የነበሩ ኢትዮጵያውያን ወደ አገራቸው የመመለሱ ሥራ ተጠናክሮ መቀጠሉን አመልክቷል።

ከውጭ ግንኙነት ቁልፍ ሥራዎች አንዱ የዜጋ ተኮር ዲፕሎማሲ መሆኑን የገለጸው ሚኒስቴሩ፥ በፖሊሲው አማካኝነት በውጭ አገር የሚኖሩ ዜጎቻችን መብት የማስከበር፣ ለዜጎች ተገቢ የቆንስላ አገልግሎት የመስጠት፣በሄዱበት ሀገር ህጋዊ የመኖሪያ ፍቃድ የሌላቸውና የሀገሩ መንግሥት ዜጎቻችን ሀገራቸውን እንዲለቁ ሲወስን መብታቸው፣ ክብራቸውና ደህንታቸው ተጠብቆ ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ እንደሚገኝ አስታውቋል።

በዚህም መሠረት ባለፉት አራት ዓመታት በተለያዩ የመካከለኛ ምስራቅ፣የአፍሪካ እና እንደ ማይናማር ያሉ የእስያ ሀገራት በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ይኖሩ የነበሩ ከ500 ሺህ በላይ ዜጎቻችንን ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ ማድረግ መቻሉን ጠቁሟል።

ከመስከረም 5 ቀን 2018 ዓ.ም አንስቶ በሳዑዲ አረቢያ በተለያዩ እስር ቤቶችና ማቆያ ማዕከላት የሚገኙ ከ17 ሺህ በላይ ዜጎቻችን መመለስ መቻሉንና በአሁኑ ወቅትም በሳዑዲ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የሚኖሩ ዜጎች የመመለሱ ሥራ መቀጠሉን በመግለጫቸው ላይ ተመላክቷል።

በተመሳሳይ በየመን በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ይኖሩ የነበሩ 36 ዜጎች ወደሀገራቸው እንዲመለሱ የተደረገ ሲሆን ሌሎችንም አስፈላጊውን የሰነድ ማጣራት በማድረግ የጉዞ ሰነድ በማዘጋጀት ወደ ሀገራቸው ለመመለስ ከኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት፣ ከብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት እንዲሁም ከዓለም ዓቀፉ የፍልሰተኞች ድርጅት (አይኦኤም) ጋር በመቀናጀት እየሰራ መሆኑን ገልጿል።

በማይናማር፣ላኦስ እና ካምቦዲያ እንዲሁም በሌሎች ሀገራት በተመሳሳይ አስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የሚኖሩ ዜጎቻችን የመመለስ ጥረት መቀጠሉንም እንዲሁ።

ሆኖም ግን አሁንም ድረስ ዜጎች በተሳሳተ መረጃ በሕገ-ወጥ ደላሎች ተታለው ወደ ተለያዩ ሀገራት በመጓዝ ለእስራት እና ለሞት እየተዳረጉ መሆኑንና መንግሥት ዜጎች ከህገወጥ ጉዞ ራሳቸውን እንዲከላከሉ እና እንዲጠነቀቁ ነው ሚኒስቴሩ ያሳሰበው።

ወደ ውጭ ሃገራት የሚደረጉ ጉዞዎችና የስራ ቅጥሮች በህጋዊና መንግስት ባስቀመጠው አሰራር ብቻ ሊሆን እንደሚገባም አስገንዝቧል።

Address

144 Pangani Heihght
Botswana
00100

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Kembata World Wide Media Network posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Kembata World Wide Media Network:

Share

Category

Kembata World Wide Media Network -KWWMN

KWWMN የልማት ቲቪ ኢትዮጵያ ሰፊ የከምባታ አለም አቀፍ መገናኛ አውታር Update ወርልድ ዋይድ ቴሌቪዥን ይዘን እንቀርባለን ዘር ቀለም ሳይለዩ አገራቸውን በታማኝነት እናገለግላለን። ከታች በሚገኘው አድሬስ መልስ የፈለጉትን መልዕክት ማስቀመጥ ይችላሉ እናመሰግናለን የእርስዎ ምክር እና አስተየት ነው እዚህ ያደረሠን Thanks for messaging us. I value your comments, recommendations, suggestions and questions. try to respond as soon as possible. please understand that for me. thank u! ከከምባታ የልማት ቲቪ የዝግጅት ክፍል. WWW.KWWMN.OCM

[email protected] & [email protected]