01/08/2025
~~~~√√√√√√√√√
#ለሞዓ-ተዋህዶ ንቅናቄ
አደጋን ለመቀልበስ በራስ ተነሳሽነት በሚጀመሩ መቃተቶች የሚፈጠሩ ግልፅ ሆነ ህቡዕ እንቅስቃሴወች ምንም እንኳን ከሙያዊነት እና ከልምድ አኳያ ጉድለት እና ተጋላጭነት ቢኖራቸውም ትልቅ ክብረት የሚሰጠው ነው። ዛሬ አደርጃጀቱ በተቋቋመለት ዓላማ ልክ ይንቀሳቀሳል በሚል የዒላማ ሆነ የተግባር ነፃነት ላለመጋፋት ሲባል "ሞዓ-ተዋህዶ" የሚባልን አደረጃጀት ላይ ትችት ማቅረብ ወደ ጎን በማለት ግለሰባዊ የሆኑ ስህተቶች ላይ የሃሳብ ሙግት ብቻ እንዲሆን ፈልገ ነበር።
አሁን ላይ ግን ጉዳዩ ገፍቶ መጥቶ ከትግሉ ባሻገር የአማራን ህዝብ በትግሉ የሌለበትንም ጨምሮ ከሌላው ሃገርተኛ ህዝብ ጋር አብሮ የመኖር ተስፋው ላይ ጭምር ያነጣጠረ ፤ ጠላት እንኳን በስውር ይናገር የነበረውን እነዚህ በግልፅ አውጥተው ከጠላት ላይ ጠላት እንዲደራረብበት ፣ የመገርሰስ አደጋ የተጋረጠበት የአብይ ስርዓት ሊመዘው ያሰበውን የሃይማኖት ካርድ ወገን በሚመስሉ የግል ኢጎ አቅላቸውን ባሳታቸው ነሁ'ላላወች በኩል እንዲሳለጥ እንዲሁም ስቃይ የወለደውን ትግል ለመከፋፈል ከጠላት ከሚወረወረው እጅጉን የባሰ ሾተል ወርዋሪ ሁኖ በመገኘቱ ከምናውቃቸው ውድመቶች መካከል ጥቂቶቹን ማስቀመጥ አስፈላጊ ሁኖ ተገኝቷል::
፩ኛ:- በ2014 ዓም መጀመሪያ አካባቢ ዶ/ር ወንዶሰን በተባለው ማን እንደላከው የማይታወቅ ሚስጢር የማይጠብቅ ግልብላብ የሆነ በሞዓ-ተዋህዶ ስም የኦሮቶዶክስ አርሚ ( Army of orthodox) በሚል ወታደራዊ ሰነድ በማዘጋጀት ለጠላት በመበተን አብይ አህመድ በፀጥታው ምክር ቤት ስብሰባ ላይ እንዲሁም የብልፅግና ማዕከላዊ ኮሚቴ ስብሰባ ላይ " ዶ/ር ይልቃል ከፋለ የሚመራው ክልል ኦርቶዶክስ አርሚ እያደራጀ ነው" በማለት የአማራን ህዝብ ሌሎች የሃገራችን ህዝቦች እንዲያገሉት እና በጥርጥሬ እንዲመለከቱት ለጠላት ኳስ ያቀበለ፤ ይልቅስ ጠላት በአማራ ህዝብ ላይ ሃይል እንዲያስተባብር ከአረብ ሃይላትም መሳሪያ እንዲጎርፍለት በማድረግ የአማራን ህዝብ በማስጨፍጨፍ ሚናው ከፍተኛ ነበር።
፪ኛ:- ዶ/ር ወንዶሰን ሊያደርግ ያሰበውን ቀድሞ ለጠላት የሚዘራ "የባቄላ ወፍጮ" የሆነ ባተሌ ግለሰብ ባለተገራ የውትፍትፍ አካሄድ በርካታ ንቁ የአማራ ታጋዮችን በጠላት የታርጌት ሰንሰለት ውስጥ እንዲገቡ በማድረግ ግማሾችን ለሞት ሌሎችን ለዕስራት እና እንግልት የዳረገ ውሽልሽል ሁኖ ሳለ በ2016 ዓም ከእስር ቤት በመሆን
"--መሪያችሁ እኔ ነኝ እናንተ ዝም ብላችሁ ተዋጉ እኔ ከእስር ቤት ስወጣ እመራዋለሁ እስከዛ በየመንደራችሁ ተዋጉ በማለት --" የዋህ የአማራ ታጋዮች የተቀናጀ ትግል እንዳያደርጉ በማድረግ በአራቱም ግዛተ አማራ ክፍሎች ከንቱ መስዕዋትነት እንዲኖር፣ የጋራ ድርጅት እንዳይኖር አፍራሽ ሚና ሲወጣ እንደነበረ ብናውቅም ራሱን መከላከል በማይችልበት ሁኔታ ውስጥ ነው በሚል አልፈነው የቆየነው ጉዳይ ነበር።
፫ኛ:- በቅርቡ በተደረገው የአፋብኀ ምርጫ ላይ ከወሎ አንድን የፓለቲካ አመራር የዚህ አጀንዳ አስፈፃሚ እንዲሆን በየቀኑ በመጎትገጎት ድርጅቱ በመመስረት ሂደት ላይ በፈጠረው ሻጥር ለበርካታ አመታት ልዪነት አይቶት የማያውቀውን የወሎን አማራ ህዝብ #የእስልምና እምነት ተከታይ ታጋዮች በመሪወቻቸው ላይ ጥርጣሬ እንዲፈጠር ክፍፍል እንዲፈጠር በማድረግ አርበኛ #ምሬ ወዳጆ የሚመራውን የፋኖ ሃይል ወደ ሁለት እንዲከፈል አድርጎታል።
በተመሳሳይ በሸዋ በአርበኛ ደሳለኝ የሚመራውን በርካታ ተዋጊ የነበረውን ሃይል በዚሁ ምክንያት እየተበተኑ ግማሹ ለጠላት የተቀረው ደግሞ ወደ ሌላ አደረጃጀት እንዲገባ አድርጓል።
በጎንደር በተመሳሳይ አዳጊ የነበሩ ጦር አመራሮችን ባልሆነ ወጥመድ በማስገባት በጥርጣሬ እንዲታዩ በማድረግ በጎንደር አማራ ፋኖ የሚደረገውን የትግል መንፈስ ጥላ እንዲያጠላበት እና የእርስ በርስ መገዳደል እንዲቀየር አድርጓል።
፬ኛ:- እንደ ድርጅት የአማራ ፋኖ በጎጃም የጠነከረ ሁለንተናዊ የሃይል ክምችት ያለው በመሆኑ፤ እንደ ትግል መሪ ግለሰብ አርበኛ #ዘመነ ካሴ አይደለም በአማራ ግዛቶች በመላው ሃገሪቱ የሃቀኝነት እና የመሪነት ተምሳሌት የሆነን መሪ ምነ ትናንት #በፕሮፌሰር አስራት ዘመን አብሯቸው ቢኖር ኖሮ? ብለን የምንመኘውን ግለሰብ የአማራ ፋኖ ትግልን እንዳይመራ በwhatsap ቅንጭብጫቢ ሃሳብ የሚመሩ ጥቂት ጥራዝ ነጠቅ የትግል መሪወችን በመጠምዘዝ ስንት መስዕዋትነት የተከፈለበትን የአንድነት ሂደት ላይ ሻጥር በመስራት በየቀጠናው የሚታገሉ ውድ ወንድሞቻችን የተናጠል ፖለቲካዊ ያልሆነ ያለ ድርጅት የውሻ ሞት እንዲሞቱ ያደረገ ይሄው ግለሰብ እና ጥቂት የሞዓ ተዋህዶ አመራሮች( ዶ/ር ወንዶሰን እና መምህር ፈንታሁን ዋቄ) ናቸው። መምህር ፈንታሁን ዋቄ ያቀደው ሲከሽፍበት በየሚድያው እንደ ጠለተ- በረድ እየተከለፈለፈ መርህ አልባ የሆነ ባህላዊ ፓለቲከኞች(traditional) የሚርመሰመሱበት ስብስብ ውስጥ እኔን አይገልፅም ብሎ ራሱን ሸከፎ ያገለለውን #የአማራ ፋኖ በጎጃም ላይ መለፋደድ ስራየ ብሎ ይዞታል።
፭ኛ:- መምህር #ፈንታሁን ዋቄ የሚባል የዚሁ ንቅናቄ ከፍተኛ አመራር ፖለቲካ ከነገረ -መለኮት ከተፋታ ከ500 አመት በኋላ የአማራ ህዝብ ውስጣዊ ሁኔታ፣ የሃገሪቱ ተጨባጭ ነባራዊ ሁኔታ እንዲሁም የቀጠናው ውስብስብ ፖለቲካ ጋር ፍፁም በተራራቀ ሁኖታ ሰፊ እና ቀጠናዊ የሆነውን የአማራ ህዝብን ትግል ወደ አንድ ጠባብ የሃይማኖት ስልቻ ውስጥ በማስገባት ለአረብ ሃገራት እንደ ስጋት እንዲታይ በማድረግ ለአብይ አህመድ ስርዓት አመቺ ሁኔታ በመፍጠር ከኳታር መንግስት የወታደራዊ ስልጠና ድጋፍ፣ ከኢማራት መንግስት ከጥሬ ገንዘብ ጀምሮ ተተኳሽ እስከ ድሮን፣ ቴክኒካዊ የጦር ሜዳ መሳሪያወች ድጋፍ እንዲሁም ከሳኢዲ መንግስት የገንዘብ እና የፓለቲካ ድጋፍ እንዲደረግለት አድርጓል። በኦሮሚያ እና በሌሎች ክልሎች አማራን በሙስሊምነቱ፣ የወንጌላዊ አማኝ መሆኑ ከጥቃት እንዳላዳነው እየታወቀ ለጠላት ትርክት አመቺ ሁኔታን የሚፈጥር ያልተገራ ንግግር በማድረግ ከፍተኛ ጉዳት አድርሷል።
በሌላ በኩል የአማራ ህዝብ ትግል በምዕራቡ ዓለም ዘንድ እንዳይደመጥ/ስቃዩ እንዳይሰማ ፀረ-ምዕራቡ ዓለም ትርክት በማስተጋባት የአማራን ትግል በጥርጣሬ እንዲመለከቱት እና ወዳጅ አልባ እንዲሆን አውቆትም ይሁን ሳያውቅ የጠላትነት ተግባር እየፈፀመ ያለ ግለሰብ ነው።
፮ኛ:- የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያንን ፀረ አማራ ሃይሎች የአማራ መገለጫ ብቻ ተደርጎ እንዲሳል የተኬደበትን እርቀት የበለጠ በማጠናከር "የአማራ ህዝብ 80% በላይ ኦርቶዶክስ ነው በመሆኑም የፋኖ ትግል የኦርቶዶክስ ትግል ነው መሆን ያለበት " በማለት ነጣይ ፕሮፖጋንዳ በመስራት በፋኖ ትግል ላይ ብቻ ሳይሆን በቤተክርስቲያኒቱ ላይም እንቅስቃሴዓዊ ከፍተኛ ኪሳራ የሚያመጣ ተግባር እየፈፀመ ይገኛል።
፯ኛ:- ዘመድኩን በቀለ የሚባል አንቃር ያልዋጠ ገንዘብ ለከፈለው አፋን የሚከፍት ሞራል-አልባ የሆነ ግለሰብ በማሰማራት የአማራ ፋኖ በጎጃም አመራሮችን ለመበተን "ቃብድ" በልቶ ገብቶ ቢሞክርም፤ የተደራጀ የፖለቲካ ኢሊት፣ በፖለቲካ የነቃ ወታደር፣ ጠላትን በጠረን የሚለይ የትግል ደጋፊ እና የሚድያ ሠራዊት ፣በጠንካራ ድርጅታዊ አሰራር የውስጥ ዝንፈቶችን ሳያውል ሳያሳድር የሚፈታ ድርጅት በበሳል መሪወች የተሸከፈ ሃይል በመሆኑ እንኳን አንድ ከራሱ ጋር የተጣላ ድርጭት ወፍ (በድንጋጤ ብዛት ህይወቷ የሚያልፍ ወፍ ዝርያ) ቀርቶ ከፓስተር እስከ ደብተራ፣ በእስራኤል እና በጀርመን በpsycological warfare የሰለጠኑ ግለሰቦች የሚመሩት ብልፅግና ያሰማራውን የወሬ-ተዋጊ ከ90,000 በላይ የሚድያ ሠራዊት ወደ ተከላካይነት ያወረደ የሳይበር ሠራዊት ያለን ስለሆነ እናጠቃለን እንጅ አልተከላከልነውም።
ሆኖም ግን እኛ የጎጃም አማራ ተወላጅ እና የአማራ ፋኖ በጎጃም አመራሮች በአብዛኛው የኦርቶዶክስ ልጆችም መሆናቸውም ተረስቶ ----እንደ ትናንቱ #ፀረ-ጎጃም አማራ ህዝብ ላይ ኋላ ቀሩ ስርዓት የፈጠረው #ተረታ ተረት ፕሮፖጋንዳ ቫይረስ ተሸካሚ አስቀጣይ ቅሪተ-አካል( remainants) መሆናችሁን በግልፅ የለየን በመሆኑ እስከ መጨረሻው ድረስ ማነኛውም አይነት ትግል የምናደርግ ይሆናል!!
በመጨረሻም የፀረ-ጎጃም አማራ ትርክት አስቀጣይ ግለሰቦችን በየትኛውም ዓለም ይሁኑ በማነኛውም ዓይነት የትግል ስልት ከማ'ጥቃ'ት ወደ ኋላ አንልም!
የሞዓ ተዋህዶ ከፍተኛ አመራሮች ሚናችሁን የለየ በተቋቋማችሁለት አጀንዳ ዙሪያ ጣልቃ እንደማንገባ ሁሉ ፤ በትግሉ ውስጥ እጃቸውን ያስገቡ ጥቂት አመራሮቻችሁን በማስወገድ ለደረሰው ውድመት ይቅርታ በመጠየቅ ከጣልቃ ገብነት ራሳችሁን እንድታርቁልን እንመክራለን።
የፖለቲካን ውስብስብ ነባራዊ ሁኔታወችን ሳይረዱ ፓለቲካ እናስተምራችሁ፣ መሪ እንምረጥላችሁ የሚሉ አላዋቂ ሳሚወችን ንፍ'ጥ እንዲለቀልቁን እድል ሳንፈጥር፤ የአማራ ፋኖ በጎጃም የፖለቲካ ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት ገብተው እንዲማሩ #በሰማያዊ ሳይበር ሠራዊት ኮማንድ በኩል ጥያቄ እንድምናቀርብላቸው ከወዲሁ አሳስባለሁ።
ገና አልጀመርንም!
የሳይበር _ሠራዊት_ ኮማንድ
_cyber_ Army _Command