EthioCyber Group

EthioCyber Group Let's stand Up for Ethiopia!

19/08/2025

መዳረሻችንን ጨረቃን ስንጠቁማችሁ የእናንተ አይን ግን ማየት የሚችለው የጠቆምንበት የጣታችን ጫፍ ነው።

01/08/2025

እኔ "ከበደ" የተባልሁ የፋኖ አመራር አባል በግሌ የኦርቶዶክስ ክርስትና እምነት ተከታይ ነኝ። ስለሆነም እምነቴን የሚገልፅልኝና የሚያዘኝን መስቀል በአደባባይ በኩራት ሳደርግ እታወቃለሁ።

እኔ የፋኖ አመራር ስለሆንሁ ሌሎች መስቀል እንዲያደርጉ ወይንም ሁሉም ፋኖ ከክላሹ እኩል መስቀል ይታጠቅ ማለት ግን አልችልም። ምክንያቱም ይህ የህልውና እንጅ ሀይማኖታዊ ትግል አይደለም።

እኔ "ከበደ" እንደምከተለው እምነት ድንግል ማርያምን እናቴ እላለሁ። ሌሎች ጓዶቼን እናቴ በሉልኝ ማለትም ማስገደድም ግን አልችልም። ወይንም እመብርሃንን ስለምወዳት ክብ ማህተማችን የእሷ ስእለ አድኖ ይሁን ልል አልችልም። ነውር ነው፤ ስህተት፤ ነው። ወንጀልም ነው።

በአማራ ፋኖ በጎጃም ከላይ እስከታች ያለው አመራርና አባል መጠኑ ቢለያይም ኦርቶዶክስ አለ፥ፕሮቴስታንት አለ፥ካቶሊክ አለ፥ሙስሊም አለ፥ምንም ሃይማኖት የሌለውም አለ። ይህ የግለሰቦች እንጅ የትግሉ ጉዳይ አይደለምና ማንም ብድግ ብሎ ድንጋይ ሊያመልክም ይችላል።

ፋኖ የፖለቲካ ግብ ያለው አብዮታዊ ንቅናቄ ነው። እኛ አብዮተኞች እንደ ሰው በየግላችን የምንከተለው ሃይማኖት ሊኖር ይችላል እንጅ የህልውና ትግሉ ብሄራው ወካይ እምነት የለውም። ይህ የህልውና እንጅ የሃይማኖት ትግል አይደለም።

ጤነኛ አእምሮ ያለው የሰው ልጅ በኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ላይ የወረደውንና እየወረደ ያለውን መከራ ይረዳል ብዬ አምናለሁ። ይቆጫል ይንገበገባል ብዬ አምናለሁ። ከዚህ አኳያ ቤተክርስቲያኗን ከጥፋት የመታደግ አላማ የያዘ አንድ ስብስብ ቢፈጠር ሁሉም ሊደግፈው የሚገባ ነው።

በዚህ ረገድ ማንም በግሉ መሰል አላማ ያላቸውን ተቋማት ሊፈጥርና ሊመራ ይችላል። የማይቻለው በሆነ እምነት ስም ተደራጅቶ መጦ ይህን አቢዮት ለመንጠቅ መሞከር ነው። አይቻልም።

ይህ ትግል የየትኛውም ቤተ እምነት የግል ንብረት አይደለም። የህዝብ ትግል ነው። ባለቤቱ ህዝብ ነው። ህዝቡ ውስጥ ደግሞ ሁሉም እምነት አለ። ህዝቡ እምነቱን በነጻነት ማምለክ ይፈልጋል። በግል ሁሉም ለቤተእምነቱ ይቆረቆራል። እውነቱ ይህ ነው።

ፓለቲካዊ የቡድን ፍላጎትን የሀይማኖት ካባ አልብሶ ማምጣት ተቀባይነት የለውም። ይህ ኢሀይማኖታዊም ነው።

እችኑ አንዲት የስእለት ትግል ከአንድ ሽህ አቅጣጫ ሽህ ፍላጎት አዝለው እየመጡ ይወዘውዟታል። መከራችን አበዙት እንጅ አያሸንፉንም። ይህ ትውልድ የትግሉም የድሉም ባለቤት ራሱ ነው።

~~~~√√√√√√√√√ #ለሞዓ-ተዋህዶ ንቅናቄ        አደጋን ለመቀልበስ በራስ ተነሳሽነት በሚጀመሩ መቃተቶች የሚፈጠሩ ግልፅ ሆነ ህቡዕ እንቅስቃሴወች ምንም እንኳን ከሙያዊነት እና ከልምድ...
01/08/2025

~~~~√√√√√√√√√
#ለሞዓ-ተዋህዶ ንቅናቄ
አደጋን ለመቀልበስ በራስ ተነሳሽነት በሚጀመሩ መቃተቶች የሚፈጠሩ ግልፅ ሆነ ህቡዕ እንቅስቃሴወች ምንም እንኳን ከሙያዊነት እና ከልምድ አኳያ ጉድለት እና ተጋላጭነት ቢኖራቸውም ትልቅ ክብረት የሚሰጠው ነው። ዛሬ አደርጃጀቱ በተቋቋመለት ዓላማ ልክ ይንቀሳቀሳል በሚል የዒላማ ሆነ የተግባር ነፃነት ላለመጋፋት ሲባል "ሞዓ-ተዋህዶ" የሚባልን አደረጃጀት ላይ ትችት ማቅረብ ወደ ጎን በማለት ግለሰባዊ የሆኑ ስህተቶች ላይ የሃሳብ ሙግት ብቻ እንዲሆን ፈልገ ነበር።

አሁን ላይ ግን ጉዳዩ ገፍቶ መጥቶ ከትግሉ ባሻገር የአማራን ህዝብ በትግሉ የሌለበትንም ጨምሮ ከሌላው ሃገርተኛ ህዝብ ጋር አብሮ የመኖር ተስፋው ላይ ጭምር ያነጣጠረ ፤ ጠላት እንኳን በስውር ይናገር የነበረውን እነዚህ በግልፅ አውጥተው ከጠላት ላይ ጠላት እንዲደራረብበት ፣ የመገርሰስ አደጋ የተጋረጠበት የአብይ ስርዓት ሊመዘው ያሰበውን የሃይማኖት ካርድ ወገን በሚመስሉ የግል ኢጎ አቅላቸውን ባሳታቸው ነሁ'ላላወች በኩል እንዲሳለጥ እንዲሁም ስቃይ የወለደውን ትግል ለመከፋፈል ከጠላት ከሚወረወረው እጅጉን የባሰ ሾተል ወርዋሪ ሁኖ በመገኘቱ ከምናውቃቸው ውድመቶች መካከል ጥቂቶቹን ማስቀመጥ አስፈላጊ ሁኖ ተገኝቷል::

፩ኛ:- በ2014 ዓም መጀመሪያ አካባቢ ዶ/ር ወንዶሰን በተባለው ማን እንደላከው የማይታወቅ ሚስጢር የማይጠብቅ ግልብላብ የሆነ በሞዓ-ተዋህዶ ስም የኦሮቶዶክስ አርሚ ( Army of orthodox) በሚል ወታደራዊ ሰነድ በማዘጋጀት ለጠላት በመበተን አብይ አህመድ በፀጥታው ምክር ቤት ስብሰባ ላይ እንዲሁም የብልፅግና ማዕከላዊ ኮሚቴ ስብሰባ ላይ " ዶ/ር ይልቃል ከፋለ የሚመራው ክልል ኦርቶዶክስ አርሚ እያደራጀ ነው" በማለት የአማራን ህዝብ ሌሎች የሃገራችን ህዝቦች እንዲያገሉት እና በጥርጥሬ እንዲመለከቱት ለጠላት ኳስ ያቀበለ፤ ይልቅስ ጠላት በአማራ ህዝብ ላይ ሃይል እንዲያስተባብር ከአረብ ሃይላትም መሳሪያ እንዲጎርፍለት በማድረግ የአማራን ህዝብ በማስጨፍጨፍ ሚናው ከፍተኛ ነበር።

፪ኛ:- ዶ/ር ወንዶሰን ሊያደርግ ያሰበውን ቀድሞ ለጠላት የሚዘራ "የባቄላ ወፍጮ" የሆነ ባተሌ ግለሰብ ባለተገራ የውትፍትፍ አካሄድ በርካታ ንቁ የአማራ ታጋዮችን በጠላት የታርጌት ሰንሰለት ውስጥ እንዲገቡ በማድረግ ግማሾችን ለሞት ሌሎችን ለዕስራት እና እንግልት የዳረገ ውሽልሽል ሁኖ ሳለ በ2016 ዓም ከእስር ቤት በመሆን
"--መሪያችሁ እኔ ነኝ እናንተ ዝም ብላችሁ ተዋጉ እኔ ከእስር ቤት ስወጣ እመራዋለሁ እስከዛ በየመንደራችሁ ተዋጉ በማለት --" የዋህ የአማራ ታጋዮች የተቀናጀ ትግል እንዳያደርጉ በማድረግ በአራቱም ግዛተ አማራ ክፍሎች ከንቱ መስዕዋትነት እንዲኖር፣ የጋራ ድርጅት እንዳይኖር አፍራሽ ሚና ሲወጣ እንደነበረ ብናውቅም ራሱን መከላከል በማይችልበት ሁኔታ ውስጥ ነው በሚል አልፈነው የቆየነው ጉዳይ ነበር።

፫ኛ:- በቅርቡ በተደረገው የአፋብኀ ምርጫ ላይ ከወሎ አንድን የፓለቲካ አመራር የዚህ አጀንዳ አስፈፃሚ እንዲሆን በየቀኑ በመጎትገጎት ድርጅቱ በመመስረት ሂደት ላይ በፈጠረው ሻጥር ለበርካታ አመታት ልዪነት አይቶት የማያውቀውን የወሎን አማራ ህዝብ #የእስልምና እምነት ተከታይ ታጋዮች በመሪወቻቸው ላይ ጥርጣሬ እንዲፈጠር ክፍፍል እንዲፈጠር በማድረግ አርበኛ #ምሬ ወዳጆ የሚመራውን የፋኖ ሃይል ወደ ሁለት እንዲከፈል አድርጎታል።
በተመሳሳይ በሸዋ በአርበኛ ደሳለኝ የሚመራውን በርካታ ተዋጊ የነበረውን ሃይል በዚሁ ምክንያት እየተበተኑ ግማሹ ለጠላት የተቀረው ደግሞ ወደ ሌላ አደረጃጀት እንዲገባ አድርጓል።
በጎንደር በተመሳሳይ አዳጊ የነበሩ ጦር አመራሮችን ባልሆነ ወጥመድ በማስገባት በጥርጣሬ እንዲታዩ በማድረግ በጎንደር አማራ ፋኖ የሚደረገውን የትግል መንፈስ ጥላ እንዲያጠላበት እና የእርስ በርስ መገዳደል እንዲቀየር አድርጓል።

፬ኛ:- እንደ ድርጅት የአማራ ፋኖ በጎጃም የጠነከረ ሁለንተናዊ የሃይል ክምችት ያለው በመሆኑ፤ እንደ ትግል መሪ ግለሰብ አርበኛ #ዘመነ ካሴ አይደለም በአማራ ግዛቶች በመላው ሃገሪቱ የሃቀኝነት እና የመሪነት ተምሳሌት የሆነን መሪ ምነ ትናንት #በፕሮፌሰር አስራት ዘመን አብሯቸው ቢኖር ኖሮ? ብለን የምንመኘውን ግለሰብ የአማራ ፋኖ ትግልን እንዳይመራ በwhatsap ቅንጭብጫቢ ሃሳብ የሚመሩ ጥቂት ጥራዝ ነጠቅ የትግል መሪወችን በመጠምዘዝ ስንት መስዕዋትነት የተከፈለበትን የአንድነት ሂደት ላይ ሻጥር በመስራት በየቀጠናው የሚታገሉ ውድ ወንድሞቻችን የተናጠል ፖለቲካዊ ያልሆነ ያለ ድርጅት የውሻ ሞት እንዲሞቱ ያደረገ ይሄው ግለሰብ እና ጥቂት የሞዓ ተዋህዶ አመራሮች( ዶ/ር ወንዶሰን እና መምህር ፈንታሁን ዋቄ) ናቸው። መምህር ፈንታሁን ዋቄ ያቀደው ሲከሽፍበት በየሚድያው እንደ ጠለተ- በረድ እየተከለፈለፈ መርህ አልባ የሆነ ባህላዊ ፓለቲከኞች(traditional) የሚርመሰመሱበት ስብስብ ውስጥ እኔን አይገልፅም ብሎ ራሱን ሸከፎ ያገለለውን #የአማራ ፋኖ በጎጃም ላይ መለፋደድ ስራየ ብሎ ይዞታል።

፭ኛ:- መምህር #ፈንታሁን ዋቄ የሚባል የዚሁ ንቅናቄ ከፍተኛ አመራር ፖለቲካ ከነገረ -መለኮት ከተፋታ ከ500 አመት በኋላ የአማራ ህዝብ ውስጣዊ ሁኔታ፣ የሃገሪቱ ተጨባጭ ነባራዊ ሁኔታ እንዲሁም የቀጠናው ውስብስብ ፖለቲካ ጋር ፍፁም በተራራቀ ሁኖታ ሰፊ እና ቀጠናዊ የሆነውን የአማራ ህዝብን ትግል ወደ አንድ ጠባብ የሃይማኖት ስልቻ ውስጥ በማስገባት ለአረብ ሃገራት እንደ ስጋት እንዲታይ በማድረግ ለአብይ አህመድ ስርዓት አመቺ ሁኔታ በመፍጠር ከኳታር መንግስት የወታደራዊ ስልጠና ድጋፍ፣ ከኢማራት መንግስት ከጥሬ ገንዘብ ጀምሮ ተተኳሽ እስከ ድሮን፣ ቴክኒካዊ የጦር ሜዳ መሳሪያወች ድጋፍ እንዲሁም ከሳኢዲ መንግስት የገንዘብ እና የፓለቲካ ድጋፍ እንዲደረግለት አድርጓል። በኦሮሚያ እና በሌሎች ክልሎች አማራን በሙስሊምነቱ፣ የወንጌላዊ አማኝ መሆኑ ከጥቃት እንዳላዳነው እየታወቀ ለጠላት ትርክት አመቺ ሁኔታን የሚፈጥር ያልተገራ ንግግር በማድረግ ከፍተኛ ጉዳት አድርሷል።

በሌላ በኩል የአማራ ህዝብ ትግል በምዕራቡ ዓለም ዘንድ እንዳይደመጥ/ስቃዩ እንዳይሰማ ፀረ-ምዕራቡ ዓለም ትርክት በማስተጋባት የአማራን ትግል በጥርጣሬ እንዲመለከቱት እና ወዳጅ አልባ እንዲሆን አውቆትም ይሁን ሳያውቅ የጠላትነት ተግባር እየፈፀመ ያለ ግለሰብ ነው።

፮ኛ:- የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያንን ፀረ አማራ ሃይሎች የአማራ መገለጫ ብቻ ተደርጎ እንዲሳል የተኬደበትን እርቀት የበለጠ በማጠናከር "የአማራ ህዝብ 80% በላይ ኦርቶዶክስ ነው በመሆኑም የፋኖ ትግል የኦርቶዶክስ ትግል ነው መሆን ያለበት " በማለት ነጣይ ፕሮፖጋንዳ በመስራት በፋኖ ትግል ላይ ብቻ ሳይሆን በቤተክርስቲያኒቱ ላይም እንቅስቃሴዓዊ ከፍተኛ ኪሳራ የሚያመጣ ተግባር እየፈፀመ ይገኛል።

፯ኛ:- ዘመድኩን በቀለ የሚባል አንቃር ያልዋጠ ገንዘብ ለከፈለው አፋን የሚከፍት ሞራል-አልባ የሆነ ግለሰብ በማሰማራት የአማራ ፋኖ በጎጃም አመራሮችን ለመበተን "ቃብድ" በልቶ ገብቶ ቢሞክርም፤ የተደራጀ የፖለቲካ ኢሊት፣ በፖለቲካ የነቃ ወታደር፣ ጠላትን በጠረን የሚለይ የትግል ደጋፊ እና የሚድያ ሠራዊት ፣በጠንካራ ድርጅታዊ አሰራር የውስጥ ዝንፈቶችን ሳያውል ሳያሳድር የሚፈታ ድርጅት በበሳል መሪወች የተሸከፈ ሃይል በመሆኑ እንኳን አንድ ከራሱ ጋር የተጣላ ድርጭት ወፍ (በድንጋጤ ብዛት ህይወቷ የሚያልፍ ወፍ ዝርያ) ቀርቶ ከፓስተር እስከ ደብተራ፣ በእስራኤል እና በጀርመን በpsycological warfare የሰለጠኑ ግለሰቦች የሚመሩት ብልፅግና ያሰማራውን የወሬ-ተዋጊ ከ90,000 በላይ የሚድያ ሠራዊት ወደ ተከላካይነት ያወረደ የሳይበር ሠራዊት ያለን ስለሆነ እናጠቃለን እንጅ አልተከላከልነውም።

ሆኖም ግን እኛ የጎጃም አማራ ተወላጅ እና የአማራ ፋኖ በጎጃም አመራሮች በአብዛኛው የኦርቶዶክስ ልጆችም መሆናቸውም ተረስቶ ----እንደ ትናንቱ #ፀረ-ጎጃም አማራ ህዝብ ላይ ኋላ ቀሩ ስርዓት የፈጠረው #ተረታ ተረት ፕሮፖጋንዳ ቫይረስ ተሸካሚ አስቀጣይ ቅሪተ-አካል( remainants) መሆናችሁን በግልፅ የለየን በመሆኑ እስከ መጨረሻው ድረስ ማነኛውም አይነት ትግል የምናደርግ ይሆናል!!

በመጨረሻም የፀረ-ጎጃም አማራ ትርክት አስቀጣይ ግለሰቦችን በየትኛውም ዓለም ይሁኑ በማነኛውም ዓይነት የትግል ስልት ከማ'ጥቃ'ት ወደ ኋላ አንልም!
የሞዓ ተዋህዶ ከፍተኛ አመራሮች ሚናችሁን የለየ በተቋቋማችሁለት አጀንዳ ዙሪያ ጣልቃ እንደማንገባ ሁሉ ፤ በትግሉ ውስጥ እጃቸውን ያስገቡ ጥቂት አመራሮቻችሁን በማስወገድ ለደረሰው ውድመት ይቅርታ በመጠየቅ ከጣልቃ ገብነት ራሳችሁን እንድታርቁልን እንመክራለን።

የፖለቲካን ውስብስብ ነባራዊ ሁኔታወችን ሳይረዱ ፓለቲካ እናስተምራችሁ፣ መሪ እንምረጥላችሁ የሚሉ አላዋቂ ሳሚወችን ንፍ'ጥ እንዲለቀልቁን እድል ሳንፈጥር፤ የአማራ ፋኖ በጎጃም የፖለቲካ ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት ገብተው እንዲማሩ #በሰማያዊ ሳይበር ሠራዊት ኮማንድ በኩል ጥያቄ እንድምናቀርብላቸው ከወዲሁ አሳስባለሁ።

ገና አልጀመርንም!

የሳይበር _ሠራዊት_ ኮማንድ
_cyber_ Army _Command

ይኸነው የሸበሉ " ትመጫለሽ ብየ ሳይ ማዶ ሳይ ማዶ ....." አለ አዝማሪ !እንቧይ እንቧይ መስሎ ሚቀላውጥ አይንህ ፣ሰውነትን ክዶ የጉርጥ መሰለብህ ።  ለሙዚቃ አዋሃጁ አዝማሪ የሚሳነው የ...
28/07/2025

ይኸነው የሸበሉ " ትመጫለሽ ብየ ሳይ ማዶ ሳይ ማዶ ....." አለ አዝማሪ !
እንቧይ እንቧይ መስሎ ሚቀላውጥ አይንህ ፣
ሰውነትን ክዶ የጉርጥ መሰለብህ ።
ለሙዚቃ አዋሃጁ አዝማሪ የሚሳነው የለምና ይሄንም ብሏል እሱስ 😂
ልሙጧ ባንዴራ ወደ ብሔረሰቦች ባንዴራ ተለወጠች? አይ ጃል ፋንታሁን ዋቄ ጉቱ ገልዳሳ
ክብርና ምስጋና ለአዲሱ ትውልድ እንጅ ገና የመስቀል ስር፣ የባንዴራ እና የነጠላ ለባሽ ቁማርተኞች ጭንብላቸውን እየገፈፍን ወደ ላኪዎቻቸው በረት እናስገባቸዋለን። ድሮስ ኢትዮጵያዊነትን ለአማራ፣ ኦርቶዶክስ ተዋህዶነትን ለሰሜኖች እንስበክ ስትሉ አይደል ኢትዮጵያ እንዲህ አይነት አረንቋ ውስጥ የወደቀችው። የጃል ፈንታሁን እህት፣ ወንድም፣ አጎትና አያት ቅድመ አያትና ምንዥላት ዛፍን እያመለኩ ቅቤ የሚቀቡ አምላክ የለሽ ፓጋኖችን ሳያስተምር ሰተት አድርገን ያስገባነው ከንቱዎች እኛ ብንሆንም ይሄን ገልቱ ግን ገና ከኤርሚያስ ለገሰ ዋቅጅራ ጋር ቁጭ ብሎ አማራን ሲሳደብ እናየዋለን። አሁን ጃል ፈንታሁን እንደሌላኛው የባንዴራ ስር ቁማርተኛ ታዬ ቦጋለ እየጀማመረው ቢሆንም ፍፃሜውን አሳምርለታለሁ። ይሄ ጉርጥ አይን በእሱ ቤት ከፋፍሎ ሙቶ እሴቶቹን አፋብኃ በደንብ እየጠበቀ ሲሆን አፋጎ እየናደ ነው የሚል የከፋፋይነት ፊሽካ ሊነፋ ሞክሯል። እስኪ አስቡት የላጭን ልጅ ቅማል ሲበላው እኛ እሳት ለብሰን እሳት ጎርሰን የራስ አርበኛ ዘመነ ካሴን መንፈስ የወረስን ትንታጎች እያለን የስልሳ አመት ሽማግሌ እየተጎተተ በላያችን ላይ ጆከር ሊጥልብን ሲነሳ ሲወድቅ አፍንጫውን አስልሰን የምንመልስ ድንቅ አማራዎች መሆናችንን እንዴት እረሳ? ለነገሩ ከብት ምን ያስታውስና። እመኑኝ ይሄን የጃል ዋቄ የክፉ ቀን ሽንት ገና በነጠላው ስር ያለውን ቁማር ስንበላው እንደ አቡነ ሳዊሮስ የወሊሶ ሲኖዶስ ባያቋቁም ከምላሴ ፀጉር።
“እርስ በእርሱ ስጋን በኩበት ይጠብሱ”
"ለበሬው ጠላቱ አራጁ ወይም ቢላዋ ሰሪው ብቻ አይደለም፤ ለበሬ ጠላቱ ሆዱም ጭምር ነው። ሆዱ አኝኮ የተፋው ሰገራው ፤ ከማንነቱ የተፋቀው፤ ደርቆ ከማንነቱ እርቆ ኩበት የሆነው የራሱን የበሬውን ስጋ ይጠብሳል። ኩበቱ ማረር መንደዱ፣ አመድ መሆኑ ላይቀር አራጁን ያስጎመጃል። በሬዎችን ያስፈጃል!" የሚል ፅሁፍ አንብቤ ነበር። አሁንም አመድ መሆናቸው ላይቀር የእኛው ኩበቶች ብዙ ጠባሳዎችን እያደረሱ መሆኑ እጅግ የሚያንገበግበው።
የአማራ የህልውና ትግልን ለምን ሌላ አጀንዳ መስጠት ተፈለገ?
እነዚህ ፀረ-አማራ ሀይሎች የሚጠቀሙት ዘዴ ልዩ ልዩ ቢሆንም ማስፈፀሚያ ስትራቴጂያቸው ግን ያው ነጮች ከ15ኛው እስከ 20ኛው ክፍለ ዘመን አፍሪካ እና እስያ ላይ ለቅኝ ግዛት የተጠቀሙበትን Devide & Rule Strategy ነው። ነጮች የአልገዛም ባይነት ተቃውሞ እንዳይነሳባቸው የዘር፣ የቋንቋ ወይም የጎሳ ልዩነቶችን በማባባስ እርስ በእርስ እንዲዋጉ በማድረግ እነሱ የሚፈልጉትን ይሰሩ ነበር። ፀረ-አማራዎችም ከዚህ ያለፈ ዘዴ የላቸውም። ምናልባት ሆዳቸው አምላካቸው የሆኑ አንዳንድ በልቶ ሟች የሆኑ አህዮችን አግኝተዋል እንጅ ሌላ ተዐምር አልተጠቀሙም።
በተለይ እንግሊዝ ህንድን 100 ዓመት ቅኝ ግዛት የገዛችው Hindus vs. Muslims በሚል ክፍፍል ሲሆን በሩዋንዳ ደግሞ Hutus vs. Tutsi በሚል ነበር። የኦሮሙማው ጉዶች ደግሞ የአማራ የህልውና ትግል የሀይማኖት መልክ እንዲይዝና ጂሃዲስት ተብሎ በእንጭጩ እንዲቀጭ ፈልገው ስላልተሳካላቸው " ፋኖ አራት ኪሎ የሚመጣው ማን ላይ ሊነግስ ነው?" የሚል ጥያቄ አንስተዋል። ይሄን የሚሉት የደቡብ ፋኖ በተመሰረተበትና ሌሎች .... ሌሎች የአፋር ፣ የሶማሌ ተቃዋሚዎችም ጭምር በአገዛዙ ላይ ነፍጥ ባነሱበት ወቅትም ጭምር ነው።
የአማራ ህልውና ትግል ስንል ጠላት አማራ እስከሆንህ ድረስ የትኛውንም ሀይማኖት ብትከተል አይምርህም ነው። አገዛዙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያንን በጠላትነት ፈርጆ እያሳደዳት እንዳለ ይታወቃል። ያ ማለት ግን አማራ እስከሆንህ ድረስ ሙስሊም ፣ ካቶሊክ ወይም ፕሮቴስታንት ብትሆን ይምርሃል ማለት አይደለም። ስለዚህ የህልውና ትግሉ ዳር ደርሶ ጠላት ሲወገድ አማራ የፈለገውን እምነት ይከተላል፤ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያንም ክብሯ ይጠበቃል የሚል እውነታ ነው ያለው። የአማራ ፋኖ የህልውና ትግል በጠላትነት የፈረጀው ህዝብም ሆነ እምነት ግን የለም። እነዚህ ትግሉ የሃይማኖት እንዲመስል የሚጥሩ አካላት የቤተክርስቲያንን ጉዳይ እንዴት ለአማራ ብቻ ማስታጠቅ ፈለጉ? እሺ በእነሱ እሳቤ እናስብላቸው ቢባል የትግራይ ፣ የጉራጌ ፣ የኦሮሞ ፣ የወላይታ ፣ የሲዳማ ክርስቲያኖች እና አብያተክርስቲያናት ጦርነቱን እንዲቀላቀሉ የማያደርጉት ለምንድን ነው? ወይስ ከአማራ ውጭ ክርስቲያን የለም? ታዲያ በየአውደ-ምህረቱ የህልውና ጦርነቱን ተቀላቀሉ ተብሎ እንዲሰበክ የማያደርጉት ለምንድን ነው?
የሙስሊም ፋኖዎችስ ትግሉ አይመለከታቸውም ልትሉን ነው? ዞሮ ዞሮ ግን አጀንዳው የአብይ አህመድ የኦሮሙማ አጀንዳ ነበር እድሜ ለኔ ማንም ሲሽኮረመም ጃል ፈንታሁን ዋዴ ጉቱ ገልዳሳ ብየ አኪሩን ሰበርኩት አጀንዳውም ድባቅ ተመቶባቸዋል። ደስ ይበልህ አማራ ይበልጥም ንቃ !
" ፋኖ አራት ኪሎ የሚመጣው ማን ላይ ሊነግስ ነው ?" ጃል ፋንታሁን ዋቄ ጉቱ ገልዳሳ ነው የጠየቀው ይሄን ጥያቄ :-
በእርግጥ ይሄን መልስ መመለስ ያለበት እኮ በእነ ጃል ፈንታሁን ዋቄ የሞዓ ተዋህዶ ግብረ ሀይል አመቻችነት ጃል ቆቱን አማካሪ አድርጎ የሾመና ትነግሳለህ ተብሎ መረጃው በእነ ጃል ቆቱ በኩል በአባቶች ተነግሮት ሹርባ ተሰርቶ የሚጠብቀው አካል ነበር። የሚገርመው ይሄን የኦሮሙማውን የሃይማኖት ክንፍ ደጋፊ ነኝ ብሎ ብቅ ያለው ከፍተኛ የሆነ የእምነት ስብጥሮች ምናልባት በአንድ ቤተሰብም ውስጥ ሳይቀር 3/4 የተለያየ እምነት ያለበት አካባቢም ጭምር ስለሆነ ያረረበት ያማስል ብዬ ማለፉ አልጠፋኝም ነበር። ነገር ግን እኔን የሚያሳስበኝ ስንቶች የወደቁበት የህልውና ትግል በቅጥረኛ ቁማርተኞች ሲበጠበጥ ቆሜ ማየት ስለማልችል ነው።
እነዚህ አካላት በአደባባይ የአርበኛ ዘመነ ካሴ ደጋፊ መስለው ለመታየት ይሞክሩና ድርጅቱን ግን ሲያበሻቅጡ ታገኟቸዋላችሁ። አርበኛ አስረስ ማረን እየተሳደቡ አርበኛ ዝናቡ ልንገረውን ሲያሞካሹ ታገኟቸዋላችሁ። ይሄን ዘዴ የሚጠቀሙት ከፋፍሎ ለመብላት ብቻ ሳይሆን የመረጃ ጠኔያቸውን ለመሙላት ከተወሰኑ ያልበሰሉ ጨወዎች መረጃ ለመቃረም ስለሚመቻቸው ነው። የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝን ለማዋረድ መረጃ የሚሰበስቡት ከአማራ ፋኖ በሸዋ፤ የአማራ ፋኖ በጎጃምን ለማዋረድ መረጃ ሲለምኑ የሚውሉት ወሎ ከተደበቀው የጎጃም ጠቅላይ ግዛት ዕዝ¡¡ ነው። በሌሎችም ግዛቶች በተመሳሳይ ይሄን ዘዴ ይጠቀማሉ። በዚህ ሁኔታ አገዛዙ ቢሊዮን ብሮችን መድቦ ያላገኘውን መረጃ መሬት ላይ ካሉ ፋኖዎች በነፃ ይወስዳል ማለት ነው።
ለማንኛውም ጃል ፋንታሁን ዋቄ ጉቱ እንደ ጃል ቆቱ ማገዶ ይጨርሳል ብዬ ብሰጋውም ከጃል ግርማ ካሳ ባልተናነሰ ጭንብሉን በብርሃን ፍጥነት አውልቋታል፤ ማርያምን ገና እርቃኑን እሰደዋለሁ። እንዲያውም ጃል ግርማ ካሳ ይሻላል ቢያንስ በነጠላ ምናምን ሰበብ ሳያደርግ በግልፅ ሸዋ ውስጥ በገንዘብ ጭምር የምደግፋቸው ልጆች ነበሩ ካዱኝ ቢሆንም ዛሬም አሉ ሲልም ሰምቸዋለሁ። እንዲያው በአጠቃላይ ከታዬ ቦጋለ ጋር ሆናችሁ በማህበር ተደራጅታችሁ ብትመጡ ምናለበት? ለእኛም መልስ ለመስጠት የተሻለ ይሆን ነበር እኮ።
የአማራን የህልውና ትግል አይንህ እያየ ታልቃታለህ እንጅ አትከፋፍላትም !
Inutile አለ ጣሊያን !

ጠማማ " ክሶች"  ትግላችንን አቆሽሸው አንሰው ሊያሳንሱ የሚዳክሙት ሞኞች ሰሞኑን በመሪዎችና እና በድርጅታችን ላይ መክረው በሚያሰማሯቸው መርዝ ጭነው በሚልኳቸው አፈ ቀላጤዎች አደገኛ ትርክት...
28/07/2025

ጠማማ " ክሶች"

ትግላችንን አቆሽሸው አንሰው ሊያሳንሱ የሚዳክሙት ሞኞች ሰሞኑን በመሪዎችና እና በድርጅታችን ላይ መክረው በሚያሰማሯቸው መርዝ ጭነው በሚልኳቸው አፈ ቀላጤዎች አደገኛ ትርክት በመንዛት የአማራ ፋኖ በጎጃም አመራሮችን "ጎጠኛ " እና "ስልጣን ናፋቂ" የሚሉ የልቅሶ ዜማዎችን ደርሰው ሙሾኛቸውን ሰብስበው የለቀቁት አስር ቁጥር ለባሾች የሔዱበትን የሞኝ መንገድ አይቸ ተደንቂያለሁ።

ከቋራው ቃል ኪዳን በፊት ቁማር መኖሩን ያላወቁ የአፋጎ አመራሮች ጆከሩን ለዴቾች አስረክበው በንፅህና ነበር የአንድነት ምስረታውን ሊያከናውኑ የሔዱት። በነገራችን ላይ ይህ አንድነት እንዲፈጠር አቅማቸውን አሟጠው ሰርተዋል ለፍተዋል ይህ ህዝባችንም ሰራዊታችንም እንዲያውቀው የምፈልገው ሀቅ ነው ከእነሱ በላይ ለፍቻለው ያለም ካለ ወጦ ይናገር፣ድርጅት ቁሞ ትግሉ በአንድ ማዕቀፍ እንዲመራ ከመፈለግ የዘለለ የአፋጎ መሪዎች እኔ ስልጣን ልያዝ አራቱ ቦታ ሰማኒያ ዘጠኙ ድርሻ የኛ ይሁን የሚል ክርክርም ጭብጥም አላነሱም ነበር።

የድርጅት ፈጠራ ሂደቱ የገጠመው ችግር ቀድሞውኑም መምሪያዎችን በኃላፊነት የሚዙት በብቃት እና ባላቸው የመምራት አቅም ተለክቶ በመስፈርት በችሎታቸው መሆን እየተገባው በኮታ እንደልደል የሚለውን ሃሳብ ተቀብለው ወደ ኮታ እና የቁጥር ጨዋታ መገባቱ ስህተት እንደነበረ ይሰማኛል።(ይህ ሁሉንም የሚመለከት ጉድለት ነው) አማራነትን በጎጥ የሸነሸኑት ይሔ የኔ አቅም ነው ያኛው አንተን ይመጥንሀል ይህ አንተ ብትሰራው የተሻለ ነው ከማለት ይልቅ ጎጣችን ወሎ ይሔ ይገባዋል፣ ሰፈራችን ሸዋ ይሔኛው ይሻለናል ፣ እኛም የጎንደር ተወካዮች ይህንን መርጠናል አሉና የአፋጎ ተወካዮችም የሰብሳቢው ቦታ የኔ ይሁን መሪያችንም ይህን ማሟላት ይችላል ብለው ጥያቄ ሲያቀርቡ ቀድመው ቦታ ቦታቸውን የያዙት አስር ቁጥር ለባሾች የጥርስ ቁርጥማት የወገብ ስብራት ፣የአንጀት መታጠፋ ፣ጠጥቶ ማቀርሸት ሆነባቸው ሰበብ ቢያጡ አርበኛ ዘመነ ካሴ መሪ አይሆንም ብለው አረፉት።

ይህ ማለት ጎጃም የተወለደ መሪ አይሆንም ማለቱን አትርሱ ቀድሞ የኮታው ድልድል ጽንስ ሀሳቡም የእነሱ ሁኖ ሳለ አቅም ሳይሆን ጎጥ ቀድሞም እያለ የሚደንቀው ደግሞ የሰብሳቢው ቦታ ለእኛ ይገባል የሚል ክርክር ያነሳ አንድም አለመኖሩ ደግሞ ጭፍን ጥላቻን አጉልቶ ያሳያሳያል ።

እጅግ ስዕብናን በሚገድል ሁኔታ የቀጠለው ውይይት አፋብኃን ኮሚቴ አድርጎ ቢያመጣም መሪ አልባ ጉዞን መሔድ የፈለጉ ተጓዦች እስከ አሁን ከመካከላቸው እኔ አለው ብሎ በሚዲያ እንኳ ብቅ ብሎ ሒደቱን የሚያስረዳ ኃላፊነቱን መሸከም የሚችል አንድም ኃላፊነት የወሰደ አስር ቁጥር ለባሽ አልተገኘም ይልቁንስ ባለቤትነት በሌለው ኡጋንዳ በተቀመጠ ሰው መግለጫ አውጥተው ትግሉን አላገጡበት።

አርበኛ ዘመነ ካሴ ሰብሳቢ የማይሆንበት ምክንያት ምንድነው? ለሚለው ጥያቄ "የተሰጠውን ምላሽ እኔም ላላጮች ዘልየዋለሁ።ከአርበኛ ዘመነ ካሴ የተሻለ መሪ አምጡ ሲባሉ የለንም ይሉና ታዲያስ ከስድስት ወር በኋላ እሱ ይሆናል እስከዚያ ግን እንደ እድር በኮሚቴ እንምራው የሚል የቂል ጨዋታ ደግሞ ይቀጥላሉ ----እሱም ካልተሳካ በየተራ በዙር የመሪነቱን ድርሻ እንወጣም የሚሉ አቋሞች ሲንፀባረቁ ይህንንስ አምኖ የሚቀበል ከኛ ወገን ጠፋ፣ የአፋጎ ጥያቄ አርበኛ ዘመነ ካሴ መሪ ይሁን አሊያም ከሱ የተሻለ አምጡ ሆነ እንጂ አርበኛ አስረስ ማረም ሆነ ሻለቃ ዝናቡ ልንገረው ስልጣን ይገባኛል ድርሻየን እንዳትነኩ አላሉም ነበር ። ነገር ግን ተቃውሞ የበዛባቸው አስር ቁጥር ለባሾች "የጎጃም ጎጠኞች ሁሉንም ስልጣን ስጡን በማለታቸው አፈነገጡ" የሚል ጥላሸት መቀባቱን ተያያዙት።

ነገሩን ነገር ካነሳው እንግዲያስ አሁን እውነቱን እንድፈረው፣ እናንተ አርበኛ ዘመነ ካሴን እናምነዋለን እንከተለዋለን መሪያችን ነው እያላችሁ ስትደልሉን ከምትኖሩ እስኪ ዛሬ አርበኛ ዘመነ ካሴ የአፋብኃ ሰብሳቢ ሁኗል ብላችሁ ኃላፊነቱን ስጡት እና የእናንተን እውነት የእኛንም ውሸት እንይ። እውነት ይህን ትደፍራላችሁ? ከፈለጋችሁ ሸዋም ውሰዱት አሊያም ጎንደር አሊያም ወሎ አሻግሩት እኛን የትም ሁኖ ይምራን፣ ከጀርባችን ከምትዶሉቱ ይህንን ይፋ አድርጉት መሪየ ነው ካላችሁ መሪ አድርጉት አሊያም ከአርበኛ ዘመነ ካሴ እገሌ የተሻለ ነው ብላችሁ መሪ አምጡ እኛም በመሪ እንመራ የእናንተም የእኛም ሰራዊት ተገናኝቶ በጋራ ይታገል።

በግል እየደወላችሁ ለክፍለ ጦሩም ውጭ ላለው ዳያስፖራም ዘመነን እኮ እንዲመራን ተስማምተናል እያላችሁ አሉባልታ ከምትነዙ እስኪ አድርጉት እና ከአፋጎ ውስጥ የእሱን መሪነት የማይቀበለውን ወይም ተጨማሪ ኃላፊነት የሚጠይቀውን አብረን እንታገለው።

እናንተ በያዛችሁት አመጽ እራሳችሁን ሰውራችሁ ይህንን ስጠኝ ብሎ ያልጠየቀዉ አርበኛ አስረስ ማረ፣ ሻለቃ ዝናቡ ልንገረው፣ አርበኛ ማርሸት ፀሐው ሆነ አርበኛ ተሰማ ካሳሁን ሊወቀሱ ሊጠየቁም አይገባም፣ ዋጋ በምንከፍልበት ትግል እናንተን ብቻ ሰፋሪዎች ሰጢታዎችና ነፋጊዎች ያረጋችሁስ ማን ነው?? በእነዚህ እና መሰል ጉዳዬች ሲረቱ የአማራ ፋኖ በጎጃምን ጎጠኛ ለማስመሰል ከአማራ ብሔርተኝነት ለመነጠል የሔዱበትን እርቀት እመለስበታለሁ።

የሚደናገር ህዝብ የሚታለል ሰራዊት አይኖርም ጀግኖች በአደባባይ ደም በሚያፈሱበት ትግል ተደብቆ ጭቃ ማቡካት ፈፅሞ አይቻልም ።
Baye Desta Per

25/07/2025

~~~~~~~~√√√√√
ለመምህር ፈንታሁን ዋቄ
wakie
//
እየውለዎት ትግሉን መደገፍ ይቻላል፤ በትግሉ ውስጥ ግን ገብቶ ብይን ለመስጠት መንቀሳቀስ ግልፅ ጣልቃ ገብነት ነው። የአማራ ብሄርተኝነት እርሰዎ እንደሚሉት ወይም እንደሌሎቹ የአውሬ ብሄርተኝነት አይደለም። የአባቶቻችንን ስነ-ልቦና እናስቀጥላለን እንጅ ከስሪታችን የምናፈገፍገው አይኖርም። ፓለቲካ የጋራ ጉዳይ ነው። የጋራ ካልሆነ ፓለቲካ ሊሆን አይችልም። ይሄ ማለት አይደለም አማራ ህዝብ ውስጥ ያለ ሃይማኖት እና ሌሎች መገለጫወች ቀርቶ የሌላውንም ክብር በሚሰጥ መልኩ የሚኬድበት ነው። ብዙ ጉዳዮች እንደ ትናንት አይደሉም። ዛሬ በአንድ በሚወጣ ቃል ብቻ የቀጣይ ፍላጎት እና እቅድ በቀላሉ በማሽን( AI) የሚታወቅበት ደረጃ ላይ ነው ያለነው። አንድ የተለመደ ሁላችንም የምናውቀው ጉዳይ ላይ ችክ ብሎ የግድ እንዲህ ካልሆነ የሚባል አካሄድ የለምም አይሰራምም!
ይሄ ትግል ሰፊ መስዕዋትነት እየተከፈለበት ያለ ነው። በዚህ ወቅት ጠላት ላይ በመረባረብ ሌሎች ጉዳዮችን በሌላ መልክ መሄድ ይቻል ነበር።
አላስፈላጊ ጣልቃ ገብነትን የተቃወምነው ወደ ፊትም እስከ ጥግ የምንታገለው ትናንት በብዓዴን ውስጥ ጉዳይ እንኳን ህውሃት ገብታ እያዘዘች እያንዳንዳችንን እንደ ህዝብ ከባድ መስዕዋትነት ከፍለናል። በዚያም አላበቃም አብይ አህመድ ብዓዴንን ራሴ እያዘዝኩ ካልመራሁ የአማራ ኢሊት ገብቶ ከስልጣኔ ያስወግደኛል ብሎ ስለፈራ ራሱ መሪወችን እነ ዶ/ር አምባቸውን በጀነራሉ በኩል ጀነራሉን ደግሞ ራሱ በቀጥታ ገድሎ ይሄው ትናንት ከህውሃት ጋር ዛሬ ደግሞ ከእኛ ጋር ይሄን ከባድ መስዕዋትነት እያሰከፈለን ያለው ለዚህ ነው ይሄ ጦርነትም የሃገርን ህልውና የሚፈታተን እንደሆነም ማሰብ ተገቢ ነው። በፓለቲካው ረገድ ትግሉን የጀመሩ መሪወች #ስለትናንት በቂ እውቀት፣ #ስለ ዛሬንሰፊ መረዳት #ስለ ነገም የመተምበይ ብቻ ሳይሆን ነገን የመበየን አቅም ያላቸው መሪወች ስላለን ምንም ጣልቃ ገብቶ እንዲህ አስቡ ተብሎ ምሪት አያሻቸውም።
ለዚህም ነው ውስጣዊ ጣልቃ ገብነትን አምርን የምንፀየፍ እስከ መጨረሻው የምንታገለው!
አሁን በተረዳሁዎት መሠረት ሰፊ የአካሄድ ችግር እንዳለብወት እና ለቀና ነገር እየታገሉ የሚሄዱበት ግን ታጋዮችን የማጠልሸት ፣መጠራጠርን የመዝራት ለጠላት የበለጠ አመቺ ሁኔታን የሚፈጠር እጅግ ያልተሰላ አካሄድ ነው! እርሰዎ የእኛ የህይወት እና የመንፈስ አስተማሪያችን፣ በቤተክርስቲያናችንም ውስጥ በምርምር ከፍተኛ ደረጃ የደረሱ ምሁር ነዎት እኔ በግሌ አከብረወታለሁ። የፓለተካ አካሄደዎ ግን Idealism የበዛበት ይባስም ብሎ ጠላት የሚፈልገውን ምንም የሃሳብ ዝምድና ሳይኖርወት እየፈፀሙለት መስሎ እየተሰማኝ ነው።
ደግሞም እንዲህ ዓይነት ያልተገባ በመረጃ ያልተረጋገጠ speculation እርስወን በማይመጥን መልኩ በተለይ ከሁሉም አቅጣጫ እሳት በሚወርድባቸው በአማራ ፋኖ በጎጃም መሪወች ላይ አጀንዳ የሚያስቀይራቸው አካል/ግለሰብ አለ" ብሎ ጥርጣሬን መፍጠር ተገቢ አይደለም።
በሌሎች በኀልዮት ጉዳዮች ላይ ሃሳብወትን ለመሸጥ የሚያቀርቧቸው ትንተናወችን እኛም የምናዳምጣቸው ናቸው። ጣልቃ ገብነት ሆነ ያለ ሚናችን ግን በውስጥ ጉዳያችን ገብቶ መፈትፈትን ግን ፈፅሞ አንታገስም!
እደግመዋለሁ እስከመጨረሻ እንታገላለን!
ከአክብሮት ጋር!
Bezabih Belachew

19/07/2025
01/05/2025
03/04/2025

Check out MF-ሽፎን’s video.

Dirección

Buenos Aires
Salta
1876

Página web

Notificaciones

Sé el primero en enterarse y déjanos enviarle un correo electrónico cuando EthioCyber Group publique noticias y promociones. Su dirección de correo electrónico no se utilizará para ningún otro fin, y puede darse de baja en cualquier momento.

Compartir