
21/02/2025
ከ15 ዓመት በፊት በኢትዮጵያ የተሰራው እና በተመልካቾች ዘንድ ተወዳጅነትና አድናቆት አትርፎ የነበረዉ ማህደር የተሰኘው ፊልም በቅርቡ በዩቱዩብ ለተመልካቾች ለዕይታ ሊቀርብ መሆኑን የፊልሙ ፕሮዲዮሰር አቶ ዋሲሁን በልሁ (ዋቢ ፊልምስ) ገለፁ ፣
ማህደር ፊልም በቤተሰብ ፣ በጓደኝነት ፣ በፍቅር ፣ አብሮ በመኖርና በመቻቻል ዙሪያ የሚያጠነጥን በኢU ፓ ጊዜ ተወልደው ባደጉ ሁለት ፍቅረኛሞች የህይወት ታሪክ ላይ የሚያጠነጥን ሲሆን፣ የፊልሙ ሰንሰለት ቤተሰቦቻቸው ጋር ወስዶን ይቅር በመባባል፣ ያለፈውን በመተው፣ በመቻቻልና በመከባበር በፍቅር የወደፊቱን ሰላማችንን ማስፈን እንደሚያስፈልገን የሚያሳይ ነው።
በፊልም ላይ በህይወት ያጣናቸውን አርቲስት አልማዝ ኃይሌ፣ ጌታቸው አስመሮም እና ንጉሱ ዘውገን ጨምሮ፣ ታዋቂዎቹ ኪሮስ ኃይለስላሴ፣ አልአዛር ሳሙኤል፣ ሉሌ አሻጋሪ፣ ሔኖክ በርታ፣ ሰለሞን አለሙ፣ ትዕግስት ዳኘው እና ማህሌት ሙሉጌታ ተሳትፈውበታል።
ማህደር ፊልምን ዳይሬክት ያደረገው ነብዩ አምደ ስላሴ ሲሆን የፊልም ፅሁፍ ዝግጅቱ ላይ አዶኒስና አርቲስት ፈለቀ አበበ ተሳትፈዋል። የፊልሙን ሜክ አፕ እና አልባሳት የሰራው ደግሞ ተስፋዬ ወንድምአገኝ ነው።