Fact Check Ethiopia

Fact Check Ethiopia Fact Check

04/26/2026

#ጥቆማ!

የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ለምልመላና ለቅጥር፣ የደኅንነት ማስጠንቀቂያ ለመስጠትና ዜጎች መረጃዎችን እንዲያጋሩ የሚያስችል የኮምዩኒኬሽን ፕላትፎርም ይፋ አድርጓል፡፡

ይህን ተከትሎም በርካታ ጥቆማዎች እየደረሱት ነው፡፡

በብሔራዊ ደኅንነት፣ ጥቅምና በሕዝብ ሥነ-ልቦና ላይ ከፍተኛ ጉዳት የሚያስከትሉ የሽብር ወንጀሎች፣ የኢኮኖሚ አሻጥሮች፣በቁልፍ መሠረተ-ልማቶችና የተለያዩ ሁነቶች ዙሪያ ያነጣጠሩ የጥቃት ሙከራዎች፣ከውጭ ኃይሎች ጋር የሚቀናጁ የጥፋት ሴራዎች እንዲሁም የተዛቡ ኢንፎርሜሽኖችን የተመለከቱ ተዓማኒና ተጨባጭ መረጃዎችን niss.gov.et report information ወይም የመረጃ ሪፖርት በሚለው የጥቆማ መስጫ ሳጥን ያጋሩ፡፡

#ለሀገርዎ ብሔራዊ ደኅንነት መረጋገጥ የዜግነት ድርሻዎን ይወጡ፤ለተጨማሪ መረጃዎች የማኅበራዊ ትስስር ገፆቻችን ይጎብኙ!

ኮምዩኒኬሽን ፕላትፎርም፡- https://niss.gov.et

National Intelligence and Security Service -Ethiopia

ስለ አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን የተወራው ምንድን ነው..?“በጠናም ሀገርም አለቀቅኩም!ደህና ነኝ.!” አምባሳደር ሬድዋን ሁሴንከሰሞኑ በብሄራዊ ደህንነት አገልግሎት ዳይሬክተር ላይ የጤና መታወክ...
04/20/2026

ስለ አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን የተወራው ምንድን ነው..?

“በጠናም ሀገርም አለቀቅኩም!ደህና ነኝ.!” አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን

ከሰሞኑ በብሄራዊ ደህንነት አገልግሎት ዳይሬክተር ላይ የጤና መታወክ እንደደረሰ የሚገልፁ መረጃዎች በማህበራዊ ድረ-ገፆች በሰፊው ተሰራጭተው ነበር፡፡

ከዚህ ባለፈም ዳይሬክተሩ አምባሳደር ሬድዋን ከሰሞኑ ጠጉራቸውን ላጭተው - ግንባራቸው ላይ ሰፊ ጠባሳ/ስንጥቅ የሚታይበት ምስል ተሰራጭቶ ነበር፡፡ ይህ ክስተት በብዙዎች ዘንድ ጥያቄን አስነስቶ ነበር፡፡ ከዚህ ምስላቸው ቀደም ብሎ ለህክምና ወደ ውጭ ሀገር ሄደዋል የሚሉ ጭምጭምታዎችን ያጋሩ ዘገባዎችም ነበሩ፡፡

ነገር ግን Fact Check Ethiopia ባጣራው መረጃ መሰረት አምባሳደር ሬድዋን በመልካም ጤንነት በስራቸው ላይ እንደሚገኙ ለማረጋገጥ ችለናል፡፡

እራሳቸው የብሄራዊ መረጃ እና ደህንነት ዳይሬክተር ጄነራሉ ሬድዋን ሁሴንም ስለ ግል ጤናቸው ይፋዊ መረጃ ሰጥተዋል፡፡

አምባሳደር ሬድዋን ዛሬ ከጥቂት ደቂቃዎች በፊት ለነዚህ ውዝግቦች ምላሽ ሰጥተዋል…

“የግል ሀዘንና ደስታ ፣ ሳቅና ለቅሶ ፣ መታመምና መዳን ሁልጊዜ ለገበያ መቅረብ አለበት ብዬ አላምንም” ያሉት አምሳደር ሬድን “ግን ደሞ አደባባይ የሚያውል ስምሪት ላይ ያለ ሰው ከፊል ህይወቱ ለህዝብ ዕይታና አስተያየት ክፍት መሆኑ የግድ ነው” ብለዋል።

የብሄራዊ መረጃ እና ደህንነት ዳይሬክተር ጄነራሉ - “እናም በዋነኝነት ሰሞኑን ወዳጅና ዘመድ፣ ቢያንስ ኢትዮጵያዊ ስለሆንን አሳሰበን፣ እንደ ሰው ምን ተፈጠረ? በሚል የተጨነቁትን ታሳቢ በማድረግ መርጃ ባጋራ በማለት የሚከተለውን ግልፅ ማድረግ ፈለኩ። በዚያውም የመጥፎ ምኞትና ሀሰትን መሰረት መረጃ በማጥራት አስታክኬ ጎሸም ባደርግ ደግኛ ነው እላለሁ” ብለዋል።

ገፅታቸው ላይ ለውጥ ያመጣው አደጋ እንዴት ተከሰተ..?
ሬድዋን እንዲህ ሲሉ ያብራራሉ…

“ከሁለት ሳምንታት በፊት በሀገራዊ ጉዳይ የሚመክር ስብሰባ አስተናግደን ለምሳ እንዳረፍን ንፋስ ለመከላከል የተጋረደ የእንጫት አካፋይ (Partition Wall) ሚዛን ስቶ ሲወድቅ አናቴ ጋርና ትንሽ ገባ ብሎ አገኘኝ። ስንጥቁ መሰፋት ስለነበረበት ሀኪሞች በከፊል ላጩት። እኔ ደሞ ሙሉውን ቢሆን ይሻላል ብዬ እስከሚደርቅ አነሳሁት። እንደልጅነቴ ተመልጬ ሳየው አልጠላሁትም። ወዳጆችም እንዲያውም ሸጋ ነው አሉኝ። በተመልካች አስተያየት ተበረታትቼ ትንሽ ደሞ በአዲስ መልክ ልሞክረው ብዬ ዘለቅኩበት” ሲሉ ነው ያብራሩት።

የሆነው ይኽው ነው ያሉት ሬድዋን - የታከምኩትም አሚን ሆስፒታል ነው” ሲሉ ወደ ውጭ ሀገር እንዳልወጡ ሞግተዋል።

ማስተባበያቸውን ሲቋጩም “እናማ እንኳን ለህክምና ለስራም ወደ ውጭ ሀገር አልወጣሁም። ምንም ያልተባለውም ምን አዲስ ነገር አለ በሚል ነው። ለማንኛውም ለተጨነቁት ምስጋናና አክብሮቴ ይድረስ” በማለት ነው።

  የታዋቂ ግለሰቦችን እና ተቋማትን ስም እና ምስል (አርማ) በመጠቀም የሚከፈቱ ሀሰተኛ የማህበራዊ ትስስር ገጾች እና አካዉንቶች ለሀሰተኛ እና አሳሳች መረጃዎች ሊያጋልጡን ስለሚችሉ ተገቢዉን...
04/12/2026


የታዋቂ ግለሰቦችን እና ተቋማትን ስም እና ምስል (አርማ) በመጠቀም የሚከፈቱ ሀሰተኛ የማህበራዊ ትስስር ገጾች እና አካዉንቶች ለሀሰተኛ እና አሳሳች መረጃዎች ሊያጋልጡን ስለሚችሉ ተገቢዉን ጥንቃቄ እናድርግ።

የኢትዮጵያ ሕዝባዊ አብዮታዊ ፓርቲ (ኢሕአፓ) ዋና ጸሐፊ የሆኑትን ሚስጥረስላሴ ታምራትን ስም እና ምስል በመጠቀም የተከፈቱ የፌስቡክ ገጾች እና አካውንቶች የተለያዩ መረጃዎችን እያጋሩ መሆናቸዉን ተመልክተናል።

ኢትዮጵያ ቼክ በጉዳዩ ላይ ባደረገዉ ማጣራት በርከት ያሉ ሀሰተኛ የፌስቡክ ገጾች እና አካውንቶች በዋና ጸሐፊዋ ስም መከፈታቸዉን አረጋግጧል።

በሀሰተኛ የፌስቡክ አካውንቶቹ ከተጋሩ መረጃዎች መካከል 7ኛዉን ሀገራዊ ምርጫ ጋር በተገናኘ ግለሰቦች ላይ ያነጣጠሩ የጥላቻ ንግግሮች ይገኙበታል።

ዋና ጸሐፊዋ ከቀናት በፊት በትክክለኛ የፌስቡክ አካውንታቸው ባጋሩት ጽሁፍ “በስሜ ሀሰተኛ የማህበራዊ ትስስር ገጾች እየተከፈቱና እኔን የማይገልጹ ጽሁፎች እንዲሁም ፎቶዎች ተቀናብረው እየተለቀቁባቸው መሆኑን ተመልክቻለሁ” ብለዋል።

በተጨማሪም ትክክለኛ አካውንታቸዉ ከ55 ሺህ በላይ ተከታዮች ያሉት ይህ አካውንት እንደሆነ ለኢትዮጵያ ቼክ አረጋግጠዋል፡፡
https://www.facebook.com/share/17f9UcAsUC/?mibextid=wwXIfr

ከታች በምስሉ የተያያዙት ሀሰተኛ ገጾች መሆናቸው ከተረጋገጡት መካከል የተወሰኑት ናቸው፡፡

2010 E.C/ 2018G.C Fact Check Ethiopiaከታች የተያያዘውን ምስል በማጋራት አሁናዊ መረጃ ለማስመሰል የተሞከረው ሀሰተኛ መረጃን አጣርተናል።  ባደረገው ማጣራት  Mohamed...
04/05/2026

2010 E.C/ 2018G.C

Fact Check Ethiopia

ከታች የተያያዘውን ምስል በማጋራት አሁናዊ መረጃ ለማስመሰል የተሞከረው ሀሰተኛ መረጃን አጣርተናል።

ባደረገው ማጣራት Mohamed Oumer በተሰኘና ከ56 ሺ በላይ ተከታይ ባለው ግለሰብ ከዚህ ስር በቀረበው ሊንክ👇🏽

https://www.facebook.com/share/1SBBr3Un9g/?mibextid=wwXIfr

ከስር የተያያዘውን ስክሪን ሹት በማያያዝ በሶማሊኛ ቋንቋ በሶማሊ ክልል ሊደረግ የታሰበ መድረክ እንዳለና ለመገናኛ ብዙሀን ጥሪ እንደተደረገ ይገልፃል።

ነገር ግን በተደረገው ማጣራት ምስሉ ከ8 አመት በፊት እንደ አውሮፓውያን ዘመን አቆጣጠር አቆጣጠር አፕሪል 2018 የሶማሊ ክልል ኮሚዩኒኬሽን ቢሮ (Somali Regional State, Communication Bureau) የላከው መሆኑን መገንዘብ ተችሏል።

በኢትዮጵያ አቆጣጠር 2010 ወይም በፈረንጆቹ 2018 በኢትዮጵያ ታሪክ የመንግስት ለውጥ የተደረገበት መሆኑ የሚታወቅ ሲሆን ፣ ከ8 አመት በፊት በአውሮፓውያን አቆጣጠር አፕሪል 2018 የተጋራን መልእክት በአሳሳች መንገድ አሁናዊና በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር 2018 በማስመሰል የተሰራጨው መረጃ ፍፁም ሀሰተኛና ሆን ተብሎ የተጋራ መሆኑን ለማረጋገጥ ተችሏል።

ባደረገችው ጥልቅ ማጣራት በ2010E.C/ 2018G.C በሀገሪቱና በክልሉ የነበረውን ለውጥ ተከትሎ በጅግጅጋ የነበረውን ስነስርአት መገናኛ ብዙሀን እንዲዘግቡ የወቅቱ አስተዳደርና ኮሙኒኬሽን ቢሮ ለመገናኛ ብዙሀን ያጋሩትንና በወቅቱ ተጋርቶ የነበረ ምስልን እንደ አሁን (2018E.C/2026G.C) በማስመሰል የተጋራው መረጃ ፍፁም ሀሰተኛ ነው።

 !Fact Check Ethiopiaበማህበራዊ ሚዲያ ላይ የሚሰራጩ ሀሰተኛ መረጃዎች (Fake News) እና የተሳሳቱ መረጃዎች (Misinformation) በአህጉራችን፣ብሎም በሀገራችን በከፍተኛ...
04/05/2026

!
Fact Check Ethiopia
በማህበራዊ ሚዲያ ላይ የሚሰራጩ ሀሰተኛ መረጃዎች (Fake News) እና የተሳሳቱ መረጃዎች (Misinformation) በአህጉራችን፣ብሎም በሀገራችን በከፍተኛ ቁጥር መጨመራቸውን ዓለም አቀፍ ጥናቶች ያመላክታሉ፡፡

እነዚህ መረጃዎች ከፖለቲካ ባሻገር፣ በሀይማኖት፣ ብሄር፣ ማንነትና በሌሎች ስስ በሆኑ ጎኖች ተሸፍነው በመቅረብ የህዝብን ስሜት በማነሳሳት፣ ግጭቶችን በማባባስ እና እውነትን በማዛባት ሀገር እና ህዝብን ወደ ብጥብጥና ሁከት እየከተቱ ይገኛሉ፡፡

እነዚህን መረጃዎች እንዴት መከላከልና ማጣራት እንችላለን? ለሚለው ተከታዮቹን 5 ወሳኝ ነጥቦችን እናጋራችሁ፡፡

1.ከማጋራትዎ በፊት ያስቡ! ማንኛውንም መረጃ ከማጋራትዎ በፊት ትክክለኛነቱን ያረጋግጡ። ስሜትዎን የሚነካ ወይም እጅግ በጣም አስደንጋጭ የሚመስል መረጃ ካዩ፣ እውነትነቱን ሳይመረምሩ አያጋሩ።

2.የመረጃውን ምንጭ ያረጋግጡ:-መረጃው የመጣው ከየት ነው? ታማኝ እና እውቅና ካለው ተቋም ነው ወይስ ከማይታወቅ አካል? የመረጃው ምንጭ ግልጽ ካልሆነ ጥርጣሬ ይኑርዎት።

3.ሌሎች ምንጮችን ይመልከቱ: አንድን መረጃ በአንድ ቦታ ብቻ ካዩት፣ ሌሎች ታማኝ የዜና ምንጮች ወይም ገለልተኛ የመረጃ አጣሪዎች ዘግበውት እንደሆነ ያረጋግጡ።

4.ፎቶዎችን እና ቪዲዮዎችን ያጣሩ: ብዙ ጊዜ ሀሰተኛ መረጃዎች የቆዩ ወይም ከአውድ ውጪ የሆኑ ፎቶዎችን እና ቪዲዮዎችን ይጠቀማሉ። እንደ Google Reverse Image Search ያሉ መሳሪያዎችን በመጠቀም የፎቶውን ወይም የቪዲዮውን አመጣጥ እና መቼ እንደተነሳ ማጣራት ይችላሉ።

5. የቋንቋ አጠቃቀምን ይፈትሹ: ሀሰተኛ መረጃዎች ብዙውን ጊዜ ስሜታዊ፣ አነሳሽ ወይም አስደንጋጭ ቃላትን ይጠቀማሉ። ሰዋሰዋዊ ስህተቶች እና የፊደል ግድፈቶችም በብዛት ይስተዋልባቸዋል፡፡

ያስታውሱ! መረጃዎችን ከማጋራትዎ በፊት በቀላል መንገድ ከላይ የቀረቡትን ነጥቦች በመጠቀም በግልዎ የመረጃውን ታማኝነት ያረጋግጡ፡፡

#ይህን መረጃ ለሌሎች እንዲደርስ ሼር በማድረግ ያጋሩት፡፡
Fact Check Ethiopia

04/05/2026

?
Fact Check Ethiopia

" የሚቆም የትራንስፖርት አገልግሎቱ የለም " - የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴርFact Check Ethiopiaመንግስት የትራንስፖርት አገልግሎት እንዲቆም ያስተላለፈው ምንም ዓይነት ትዕዛዝ...
04/04/2026

" የሚቆም የትራንስፖርት አገልግሎቱ የለም " - የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር
Fact Check Ethiopia
መንግስት የትራንስፖርት አገልግሎት እንዲቆም ያስተላለፈው ምንም ዓይነት ትዕዛዝ እንደሌለ የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር አሳወቀ።

በመካከለኛው ምስራቅ ጦርነት ምክንያት በተፈጠረው የነዳጅ መስተጓጎል " የትራንስፖርት አገልግሎት ይቆማል " በሚል የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤትን ስምና ሎጎ በመጠቀም የሚሰራጨው መረጃ የተሳሳተ እና የውሸት መሆኑን ሚኒስቴሩ ገልጿል።

" መንግስት የትራንስፖርት አገልግሎት እንዲቆም ያስተላለፈው ምንም ዓይነት ትዕዛዝ የለም። አገልግሎቱ እንደተለመደው ይቀጥላል " ብሏል።

ዜጎች ከማይታወቁ ምንጮች የሚወጡ መረጃዎችን እንዳያጋሩ እና የሀሰተኛ ወሬዎችን ስርጭት እንዲከላከሉ ጥሪ ቀርቧል።

በሌላ በኩል ፥ ጠቅላይ ሚኒስትር ፅ/ቤት ዜጎች ከሐሰተኛ ዜናዎች እና የተሳሳቱ መረጃዎች ስርጭት ራሳቸውን እንዲጠብቁ መልእክት አስተላልፏል።

" ‎ከጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ተብሎ የሚደርስዎትን ማንኛውም ‎ይፋዊ መልዕክት ከማጋራትዎ በፊት ሁልጊዜም በጽሕፈት ቤቱ ይፋዊ የማህበራዊ ትስስር ገጾች እና ድህረ-ገጽ በመግባት፣ ትክክለኛነቱን እንዲያረጋግጡ እናሳስባለን " ብሏል።

 !ተስፋ የቆረጡት ኢትዮ ፎረሞች በመጨረሻም እንደ እብድ እያረጋቸው ነው።በአንድ ውሸት ላይ ሌላ ውሸት መደረብ ከውሸት ማምለጫ ስልት የሆናቸው ብቸኛ መንገድ መስሏል።ሲጀምሩ ሾልኮ የወጣ የድም...
04/04/2026

!

ተስፋ የቆረጡት ኢትዮ ፎረሞች በመጨረሻም እንደ እብድ እያረጋቸው ነው።

በአንድ ውሸት ላይ ሌላ ውሸት መደረብ ከውሸት ማምለጫ ስልት የሆናቸው ብቸኛ መንገድ መስሏል።

ሲጀምሩ ሾልኮ የወጣ የድምፅ ቅጅ አገኝን በሚል “ተንገብግበው” ወደ አየር ለማውጣት ሮጡ፡፡

ነገር ግን ይህ “ሾልኮ የወጣ ድምፅ” ምንድን ነው ተብሎ ሲጣራ ነጭ ውሸት ሆኖ ተገኝ፡፡

ድምፁ ርእሰ መስዳድር ሙስጠፋ ሞሀመድ በፈረንጆቹ 2021 በ ClubHouse የቀጥታ ጥያቄ እና መልስ ውይይት ላይ የተናገሩት እና ተቆራርጦ ከተሰራጨው ቅጅ ጋር ፈፅሞ የማይገናኝ ሆኖ ተገኝ፡፡

በዚህ አላበቁም፡፡

እንደገና ሌላ የተስፋ መቁረጥ ሙከራ አረጉ፡፡ አንድ ተራ ታሪክ ፈጥረው የሆነ ጋዜጠኛ በጅግጅጋ ማረሚያ ቤት አነፍንፎ በመግባት ከባድ የአስገድዶ መድፈር ወንጀል መፈፀሙን አጋለጠ ሲሉ “ዘገቡ”፡፡

በዚህ ጉዳይ ላይም የሀሰተኛ መረጃ ማጣራት ስራ አደረግን፡፡

በሚያስቅ መልኩ ይሄም እንደገና ሀሰት ሆኖ ተገኘ፡፡ ጋዜጠኛ የተባለው ሰው የብእር ስም የሚጠቀሙ ሁለት የተቃዋሚ ፖለቲካ አደረጃጀት አባል መሆናቸው ተረጋገጠ፡፡

አንዱ አህመድ ሀሰን ባጄ ነው፡፡ አህመድ መሰረቱን ኬንያ ያደረገ የህወሀት ሴል ጋር የቅርብ ትስስር ያለው በሚገባ የሚታወቅ ግለሰብ ነው፡፡

ሌላኛዋ ሀፍሳ ሞሀመድ ስትሆን ከቀድሞው የክልሉ ርእሰ መስተዳድር አብዲ ኢሌ ጋር አብራ ስትሰራ የነበረች ግለሰብ ናት፡፡

ሀፍሳ በአብዲ ኢሌ የስልጣን ዘመን አንድ አጭበርባሪ NGO መስርቻለሁ በሚል ስትንቀሳቀስ የነበረ በኋላም ከሰባት አመታት በፊት ከሀገር የወጣች እና ተመልሳ ያልመጣች ግለሰብ ናት፡፡

እነዚህን ሰዎች ምንጭ አደረግኩ የሚል፣ ያልተባለ የሚተርክ ፣ድምፅ ቆራርጦ የተናጋሪውን ትክክለኛ አውድ በማጣመም ሙሉ ውሸት ያዘለ መልእክት የሚያሰራጭ ዘገባ ጋዜጠኝነት አይደለም፡፡

ይህ የሙያ ክብርን ያጣና የተገፈፈ የተስፋ ቆራጮች ስብስብ ነው።

Address

Toronto, ON
V5A2Z6

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Fact Check Ethiopia posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share