10/01/2025
የተሰበሩ አጥንቶችን በደቂቃዎች ውስጥ የሚገጥም ግኝት ይፋ ሆነ
***********
የቻይና ተመራማሪዎች ከአጥንት ስብራት ለማገገም ወራት ይፈጅ የነበረውን ሂደት የሚቀይር በ3 ደቂቃዎች ውስጥ የተሰበረ አጥንትን የሚገጥም ግኝት ይፋ አድርገዋል፡፡
'ቦን -02' የሚል ስያሜ የተሰጠው ይህ ግኝት ተጨማሪ ቀዶ ጥገና ሳያስፈልግ የተሰበሩ አጥንቶችን የሚገጥም ነው፡፡
በሃንግዙ ሰር ሩን ሾው ሆስፒታል የአጥንት ሕክምና ባለሙያ የሆኑት ሊን ዢያንፌንግ እንደገለጹት፤ ሕክምናው በመርፌ መልክ የሚሰጥ እና የተሰበሩ አጥንቶችን በደቂቃዎች ውስጥ አንድ ላይ እንዲጣበቁ የሚያደርግ ነው።
'ቦን 02' በሰው አካል ውስጥ ከገባ በኋላ በተፈጥሮ መንገድ እንዲዋሃድ ተደርጎ መሰራቱም ተመላክቷል።
በመሆኑም ከዚህ በፊት ይደረግ እንደነበረው ማጣበቂያውን ለማስወገድ ሁለተኛ ቀዶ ጥገና ባለማስፈለጉም የኢንፌክሽን አደጋን ይቀንሳል ነው የተባለው።
በ'ዠይጂያንግ' ዩኒቨርሲቲ ተመራማሪዎች በተሰራው በዚህ ግኝትም ከ150 በላይ የሚሆኑ ሰዎች ሕክምና በተሳካ ሁኔታ መካሄዱን ኦዲቲ ሴንትራል ዘግቧል።
በሴራን ታደሰ
Abenezer Ayele
Abenezer Ayele official