Gesuba town public service and human resource development office

Gesuba town public service and human resource development office ፈጣን ቀልጣፋና ለሁሉም የማህበረሰብ ክፍል የሚመጥኑ መረጃዎችን እናደርስዎታለን ይከታተሉን።

15/11/2024

ዜና: ብሔራዊ ባንክ ላኪዎች ካመነጩት የውጭ ምንዛሬ 50 በመቶውን በመሸጥ ቀሪውን ላልተወሰነ ጊዜ በአካውንታቸው እንዲያስቀምጡ ፈቀደ

#የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ላኪዎች ያመነጩትን የውጭ ምንዛሬ 50 በመቶ ወዲያውኑ በመሸጥ ቀሪውን 50 በመቶ ላልተወሰነ ጊዜ ኢትዮጵያ ውስጥ ባለ አካውንታቸው ማስቀመጥ የሚችሉበት አሰራር ከዛሬ ህዳር 5 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ተግባራዊ እንደሚደረግ አስታወቀ።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዥ ማሞ ምህረቱ እንዳሉት፣ ላኪዎች ካመነጩት የውጭ ምንዛሬ 50 በመቶውን ለባንኮች ወዲያውኑ በመሸጥ ቀሪውንም በአንድ ወር ውስጥ መሸጥ ይገደዱ ነበር።

በወቅቱ አሰራሩ በጊዜያዊነት ተግባራዊ ሲደረግ የተረጋጋ የውጭ ምንዛሬ ፍሰት እንዲኖር ከመፈለግ እንደነበር አቶ ማሞ አስታውሰዋል።

ከዛሬ ህዳር 5 ቀን ጀምሮ ግን ላኪዎች ያመነጩትን የውጭ ምንዛሬ 50 በመቶ ወዲያውኑ በመሸጥ ቀሪውን 50 በመቶ ላልተወሰነ ጊዜ በአካውንታቸው ማስቀመጥ ይችላሉ ሲሉ መግለጻቸውን ከኢዜአ ያገኘነው መረጃ ያሳያል።

ይህም ማለት ያመነጩትን የውጭ ምንዛሬ በአንድ ወር ውስጥ እንዲሸጡ አይገደዱም ማለት መሆኑን አመላክተዋል።

በተያያዘ ዜና የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የውጭ ምንዛሬ ክምችት ከማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው በፊት ከነበረበት 1 ነጥብ 4 ቢሊየን ዶላር በአሁኑ ወቅት 3 ነጥብ 4 ቢሊዮን ዶላር መድረሱን የባንኩ ገዥ ማሞ ምህረቱ ገለጸዋል።

የግል ባንኮች የውጭ ምንዛሪ ሀብት መጨመሩን ጠቅሰው፤ ከሪፎርሙ በፊት ከነበረባቸው 518 ሚሊዮን ዶላር አሁን ላይ ከእዳ ነፃ መሆናቸውን ተናግረዋል።

19/09/2024

Shout out to my newest followers! Excited to have you onboard! Mikael Seyfu, Paulo's Jorge, Kiya Ye Mariyam Liji, Hanone Baka

የዛሬው የሕዋስ ውይይት በፎቶ
10/05/2024

የዛሬው የሕዋስ ውይይት በፎቶ

የገሱባ ከተማ አስተዳደር ፐብሊክ ሰርቪስና ሰው ሀብት ልማት ጽ/ቤት የመንግሥት መስሪያ ቤቶች የሰው ኃይል የትምህርት ማስረጃዎችን ለማጥራት በተዘጋጀ ዕቅድ ላይ ከተማዊ የኦሬንቴሽን መድረክ ተ...
07/05/2024

የገሱባ ከተማ አስተዳደር ፐብሊክ ሰርቪስና ሰው ሀብት ልማት ጽ/ቤት የመንግሥት መስሪያ ቤቶች የሰው ኃይል የትምህርት ማስረጃዎችን ለማጥራት በተዘጋጀ ዕቅድ ላይ ከተማዊ የኦሬንቴሽን መድረክ ተካሄደ

የገሱባ ከተማ ፦ ሚያዚያ 29/2016 የገሱባ ከተማ አስተዳደር ፐብሊክ ሰርቪስና ሰው ሀብት ልማት ጽ/ቤት የመንግሥት መስሪያ ቤቶች የሰው ኃይል የትምህርት ማስረጃዎችን ለማጥራት በተዘጋጀ ዕቅድ ላይ ከተማዊ የኦሬንቴሽን መድረክ ተካሂዷል።

በዚህ መድረክ ህጋዊ አሠራርንና አካሄድን ተከትለዉ የሁሉም የመንግስት ሠራተኛ የትምህርት ማስረጃ እንደሚጣራ እና የመምህራን በትምህርት ሚንስተር በኩል እንደሚጣራ በመድረኩ ተነስቷል።

የሁሉም ሠራተኛ የትምህርት ማስረጃን የመፈተሽ ተግባር በተቀመጠው የጊዜ ሰለደ መነሻ አድርጎ እንዲጠናቀቅ ሁሉም ባለድርሻ የበኩሉን አስተዋጽኦ እንዲያበረክት ተጠይቋል።

እያንዳንዱ ሴክተር ንዑስ ኮሚቴ ተደራጅተው የተደረገውን የሰራተኛ የትምህርት ማስረጃ በአግባቡ አደራጅቶ ለሚመለከተው አካል እንደሚቀርብ ተጠቁሟል።

የሁሉም የመንግስት ሠራተኛ የትምህርት ማስረጃ በተቀመጠዉ የጊዜ ገደብ ማጣራት እንደሚደረገም በአጽንኦት ተነስቷል።

18/04/2024
የተቋማችን ሕዋስ የብልጽግና ፓርቲ አባላት " የአመራርና የአባላት ድስፕልን መመሪያ" ዙሪያ መደበኛ ውይይት አድርጓል።
12/04/2024

የተቋማችን ሕዋስ የብልጽግና ፓርቲ አባላት " የአመራርና የአባላት ድስፕልን መመሪያ" ዙሪያ መደበኛ ውይይት አድርጓል።

የቀድሞ ጽ/ቤታችን ኃላፊ አቶ መልካሙ አያኖ አዲስ ለተሾሙ ለአቶ ላብሶ ላቆ የሥራ ርክብክብ አድርጓል።
09/04/2024

የቀድሞ ጽ/ቤታችን ኃላፊ አቶ መልካሙ አያኖ አዲስ ለተሾሙ ለአቶ ላብሶ ላቆ የሥራ ርክብክብ አድርጓል።

የገሱባ ከተማ ፐብሊክ ሰርቪስና ሰው ሀብት ልማት ጽ/ቤት    ሕዋስ ለአባላቱ የብልፅግና ፓርቲ  የአመራርና አባላት የዲሲፕሊን መመሪያ ውይይት አድርጓል፡፡ መጋቢት 20 ቀን 2016ዓ.ም የገሱ...
29/03/2024

የገሱባ ከተማ ፐብሊክ ሰርቪስና ሰው ሀብት ልማት ጽ/ቤት ሕዋስ ለአባላቱ የብልፅግና ፓርቲ የአመራርና አባላት የዲሲፕሊን መመሪያ ውይይት አድርጓል፡፡

መጋቢት 20 ቀን 2016ዓ.ም የገሱባ ከተማ ፐብሊክ ሰርቪስና ሰው ሀብት ልማት ጽ/ቤት ሕዋስ ለአባላቱ የብልፅግና ፓርቲ የአመራርና አባላት የዲሲፕሊን መመሪያ ውይይት አድርጓል፡፡ በመድረኩ የጽ/ቤቱ ዋና ኃላፊ አቶ መልካሙ አያኖ፣ የሕዋሱ ሰብሳቢ አቶመርክን መንግስቱ እና አባላት በተገኙበት የውይይት መድረክ ተካሂዷል።

በውይይቱም መንግስትን የመሰረተው ፓርቲ ተግባሮችን በመመርያና ደንብ ማከናወን መጀመሩ መልካም ጅምር መሆኑን የገለፁት አባላት የመመርያው አድማስ በሁሉም ዘርፍ ባሉት አባላት ላይ የሚተግበር መሆኑ ደግሞ የተሻለ ያደርገዋል ብለዋል። በመድረኩ ሀሳብ የሰጡት አባላት የሕዋስ ውይይቱ ወደፊት በበጎ ተግባራት የሚደገፍ መሆን እንዳለበትም አሳስበው የመድረኩ ማጠቃለያ ሆኗል።

24/03/2024

Adresse

Gesuba
Democratic Republic Of The
14

Notifications

Soyez le premier à savoir et laissez-nous vous envoyer un courriel lorsque Gesuba town public service and human resource development office publie des nouvelles et des promotions. Votre adresse e-mail ne sera pas utilisée à d'autres fins, et vous pouvez vous désabonner à tout moment.

Contacter L'entreprise

Envoyer un message à Gesuba town public service and human resource development office:

Partager