DW Amharic

DW Amharic ዶይቼ ቬለ ርዕሰ ጉዳዮችን በፊስ ቡክ ያወያያል።
Telegram : t.me/dw_amharic
WhatsApp : https://t1p.de/2gg5u

Netiquette: https://www.dw.com/en/dw-netiquette-policy/a-5300954

የህዳር 24 ቀን 2018 ዓ.ም. አርዕስተ ዜናአሜሪካን የጉዞ እገዳ የጣለችባቸውን የ19 ሀገራት ዜጎችን የጥገኝነት ማመልከቻዎች ለጊዜው መቀበል ማቆሟን አስታወቀች። እገዳው የግሪን ካርድ እና...
03/12/2025

የህዳር 24 ቀን 2018 ዓ.ም. አርዕስተ ዜና
አሜሪካን የጉዞ እገዳ የጣለችባቸውን የ19 ሀገራት ዜጎችን የጥገኝነት ማመልከቻዎች ለጊዜው መቀበል ማቆሟን አስታወቀች። እገዳው የግሪን ካርድ እና የዜግነት ማመልከቻዎችንና ተያያዥ ውሳኔዎች ያካትታል።
የሩስያ ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ለሰላም ፍላጎት ያላቸው እያስመሰሉ ነው በማለት አውሮጳውያን ሲወቅሱ ፑቲን አውሮጳች ሩስያን ከተነኮሱም ከአውሮጳ ጋር ጦርነት ለመግጠም ዝግጁ እንደሆኑ አስጠንቅቀዋል።
የሦስት ቀናት ጉብኝት ለማድረግ ዛሬ ለንደን ለገቡት የጀርመን ፕሬዝዳንት ፍራንክ ቫልተር ሽታይንማየር እና ለባለቤታቸው ኤልከ ቡዩድንቤንደር ደማቅ አቀበላል ተደረገላቸው።

የህዳር 24 ቀን 2018 ዓ.ም. የዓለም ዜና አሜሪካን የጉዞ እገዳ የጣለችባቸውን የ19 ሀገራት ዜጎችን የጥገኝነት ማመልከቻዎች ለጊዜው መቀበል ማቆሟን አስታወቀች። እገዳው የግሪን ካርድ እና የ.....

ኢትዮጵያ ከ22 ዓመት በኋላ በአዳጊዎቿ ለአፍሪቃ ዋንጫ አለፈችየኢትዮጵያ ዕድሜያቸው ከ17 ዓመት በታች ብሔራዊ የእግር ኳስ ተጨዋቾች ከ22 ዓመታት በኋላ ለአፍሪቃ ዋንጫ ማለፍ ችለዋል ። ቡድ...
03/12/2025

ኢትዮጵያ ከ22 ዓመት በኋላ በአዳጊዎቿ ለአፍሪቃ ዋንጫ አለፈች

የኢትዮጵያ ዕድሜያቸው ከ17 ዓመት በታች ብሔራዊ የእግር ኳስ ተጨዋቾች ከ22 ዓመታት በኋላ ለአፍሪቃ ዋንጫ ማለፍ ችለዋል ። ቡድኑ ማለፉን ያረጋገጠው ማክሰኞ ኅዳር 23 ቀን፣ 2018 ዓ.ም የኬንያ አቻውን አዲስ አበባ ውስጥ 3 ለ0 ድል ካደረገ በኋላ ነው ። ፌዴሬሽኑ ይህ አጋጣሚ ከእጁ እንዳይወጣ ብዙ ሊሠራ እንደሚገባ ተገልጧል ።

የኢትዮጵያ ዕድሜያቸው ከ17 ዓመት በታች ብሔራዊ የእግር ኳስ ተጨዋቾች ከ22 ዓመታት በኋላ ለአፍሪቃ ዋንጫ ማለፍ ችለዋል ። ቡድኑ ማለፉን ያረጋገጠው ማክሰኞ ኅዳር 23 ቀን፣ 2018 ዓ.ም የኬንያ ....

የካፒታል ገበያ አገልግሎት አቅራቢዎች “እባካችሁ በተሰጣችሁ ፈቃዶች ላይ አትተኙባቸው”አራት የኢንቨስትመንት ባንኮችን ጨምሮ የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለሥልጣን ፈቃድ የሰጣቸው የካፒታል ገበያ...
03/12/2025

የካፒታል ገበያ አገልግሎት አቅራቢዎች “እባካችሁ በተሰጣችሁ ፈቃዶች ላይ አትተኙባቸው”

አራት የኢንቨስትመንት ባንኮችን ጨምሮ የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለሥልጣን ፈቃድ የሰጣቸው የካፒታል ገበያ አገልግሎት አቅራቢዎች ቁጥር 13 ደርሷል። በአዲስ በባ በመካሔድ ላይ በሚገኘው የካፒታል ገበያ ጉባኤ የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ብሩክ ታዬ “እባካችሁ በተሰጣችሁ ፈቃዶች ላይ አትተኙባቸው” ሲሉ መክረዋል።

አራት የኢንቨስትመንት ባንኮችን ጨምሮ የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለሥልጣን ፈቃድ የሰጣቸው የካፒታል ገበያ አገልግሎት አቅራቢዎች ቁጥር 13 ደርሷል። በአዲስ በባ በመካሔድ ላይ በሚገኘ....

የሱዳን ቀውስ፦ ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ጫና ማሳደር ይችል ይሆን?ምንም እንኳን በዩናይትድ ስቴትስ የቀረበው የተኩስ አቁም ጥሪ በሱዳን ተቀባይነት ባያገኝም፣ ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ግን ደም ...
03/12/2025

የሱዳን ቀውስ፦ ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ጫና ማሳደር ይችል ይሆን?

ምንም እንኳን በዩናይትድ ስቴትስ የቀረበው የተኩስ አቁም ጥሪ በሱዳን ተቀባይነት ባያገኝም፣ ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ግን ደም አፋሳሹን ግጭት አስቁሞ የሰብአዊ ርዳታ እንዲቀላጠፍ ጫና ሊፈጥር ይችል ይሆናል ። ግን ደግሞ ተፋላሚ ኃይላቱ ነፍጣቸውን ለማውረድ ዝግጁ ናቸው?

ምንም እንኳን በዩናይትድ ስቴትስ የቀረበው የተኩስ አቁም ጥሪ በሱዳን ተቀባይነት ባያገኝም፣ ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ግን ደም አፋሳሹን ግጭት አስቁሞ የሰብአዊ ርዳታ እንዲቀላጠፍ ጫና ....

ሩስያ የሰላም ዕቅዱን ሙሉ በሙሉ አልተቀበለችውምከውይይቱ በኋላ ከክሬምሊን የወጣው መግለጫ ፕሬዝዳንት ፑቲን የሰላም እቅዱን እንዳለ ባይቀበሉትም ግን ደግሞ በሙሉ እንዳልተቃወሙትና ቀጣይ ውይይ...
03/12/2025

ሩስያ የሰላም ዕቅዱን ሙሉ በሙሉ አልተቀበለችውም

ከውይይቱ በኋላ ከክሬምሊን የወጣው መግለጫ ፕሬዝዳንት ፑቲን የሰላም እቅዱን እንዳለ ባይቀበሉትም ግን ደግሞ በሙሉ እንዳልተቃወሙትና ቀጣይ ውይይቶች የሚያስፈልጉት መሆኑን የሚገልጽ ነው።

ከውይይቱ በኋላ ከክሬምሊን የወጣው መግለጫ ፕሬዝዳንት ፑቲን የሰላም እቅዱን እንዳለ ባይቀበሉትም ግን ደግሞ በሙሉ እንዳልተቃወሙትና ቀጣይ ውይይቶች የሚያስፈልጉት መሆኑን የሚገልጽ ....

የፌደራል የጀርመን ፕሬዘደንት ፍራንክ ቫልተር ሽታይንማየር ጉብኝትሽታይንማየር ከብሪታኒያው ጠቅላይ ሚንስትር ጋር የነበራቸውን ውይት ካጠናቀቁ በኋላ ወደ ዊንዝር ቤተመንግስት በማቅናት በንጉስ ...
03/12/2025

የፌደራል የጀርመን ፕሬዘደንት ፍራንክ ቫልተር ሽታይንማየር ጉብኝት

ሽታይንማየር ከብሪታኒያው ጠቅላይ ሚንስትር ጋር የነበራቸውን ውይት ካጠናቀቁ በኋላ ወደ ዊንዝር ቤተመንግስት በማቅናት በንጉስ ቻርልስና ንግስት ካሜላ ልኡል ዊሊያምና ልእልት ካትሪን በታሪካዊው የንጉሣዊ መኖሪያ ቤት በቅዱስ ጊዮርጊስ አዳራሽ ውስጥ በተዘጋጀላቸው የራት ግብዣ ላይ ለመገኘት ወደ ዊንዘር ቤተመንግስት እቅንተዋል።

ሽታይንማየር ከብሪታኒያው ጠቅላይ ሚንስትር ጋር የነበራቸውን ውይት ካጠናቀቁ በኋላ ወደ ዊንዝር ቤተመንግስት በማቅናት በንጉስ ቻርልስና ንግስት ካሜላ ልኡል ዊሊያምና ልእልት ካትሪን ...

በዓለማችን እያደገ የሄደው የጦር መሣሪያ ምርት ፣ ንግድና ስጋቱየጀርመን ኩባንያዎች በጦር መሣሪያ ሽያጩ ስኬታማዎቹ ናቸው። በ2024 የጀርመን የጦር መሣሪያ ሽያጭ ገቢ በ36 በመቶ ጨምሯል። ...
02/12/2025

በዓለማችን እያደገ የሄደው የጦር መሣሪያ ምርት ፣ ንግድና ስጋቱ

የጀርመን ኩባንያዎች በጦር መሣሪያ ሽያጩ ስኬታማዎቹ ናቸው። በ2024 የጀርመን የጦር መሣሪያ ሽያጭ ገቢ በ36 በመቶ ጨምሯል። SIPRI እንደሚለው የጀርመን የጦር መሣሪያ ሽያጭ ገቢ ያደገው ሀገሪቱ ለዩክሬን በወታደራዊ እርዳታ የሰጠቻቸውን የጦር መሣሪያዎች ለመተካትና የጦር መሣሪያ ክምችቷንም ለማሳደግ ጦር ኃይሉ ባቀረበው ጥያቄ መሠረት ነው።

የጀርመን ኩባንያዎች በጦር መሣሪያ ሽያጩ ስኬታማዎቹ ናቸው። በ2024 የጀርመን የጦር መሣሪያ ሽያጭ ገቢ በ36 በመቶ ጨምሯል። SIPRI እንደሚለው የጀርመን የጦር መሣሪያ ሽያጭ ገቢ ያደገው ሀገሪ....

የሕዳር 23 ቀን 2018 ዓ/ም የዓለም ዜና• የቀድሞው የሰላም ሚንስቴር ምንስትር ዴታ እና የጨፌ ኦሮሚያ አባል አቶ ታዬ ደንደአ አዲስ የተመሰረቱባቸውን ክሶች ተቃወሙ ። • በደቡባዊ ሱዳን ...
02/12/2025

የሕዳር 23 ቀን 2018 ዓ/ም የዓለም ዜና

• የቀድሞው የሰላም ሚንስቴር ምንስትር ዴታ እና የጨፌ ኦሮሚያ አባል አቶ ታዬ ደንደአ አዲስ የተመሰረቱባቸውን ክሶች ተቃወሙ ።
• በደቡባዊ ሱዳን የብሔራዊ ጦር ኃይሉ ሳይፈጽመው አልቀረም በተባለ ጥቃት በትንሹ 40 ያህል ሰዎች ተገደሉ።
• አሜሪካ ይክሬን ውስጥ እየተካሄደ ያለው ጦርነት ፍጻሜ ያገኝ ዘንድ ከሩስያ ጋር ፊት ለፊት ልትነጋገር ነው።
• የኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድን ከ22 ዓመታት ጥበቃ በኋላ ለአፍሪካ ዋንጫ አለፈ።

• የቀድሞው የሰላም ሚንስቴር ምንስትር ዴታ እና የጨፌ ኦሮሚያ አባል አቶ ታዬ ደንደአ አዲስ የተመሰረቱባቸውን ክሶች ተቃወሙ ። • በደቡባዊ ሱዳን የብሔራዊ ጦር ኃይሉ ሳይፈጽመው አልቀ.....

አሜሪካ ሰሞኑን በተገን ጠያቂዎች ላይ ያሳለፈቻቸው ውሳኔዎች አንድምታየአሜሪካ የዜግነት እና የስደተኞች አገልግሎት ለሁሉም የተገን ጥያቄ ውሳኔ መስጠት ማቆሙን ሰሞኑን አስታውቋል።ርምጃው አንድ...
02/12/2025

አሜሪካ ሰሞኑን በተገን ጠያቂዎች ላይ ያሳለፈቻቸው ውሳኔዎች አንድምታ
የአሜሪካ የዜግነት እና የስደተኞች አገልግሎት ለሁሉም የተገን ጥያቄ ውሳኔ መስጠት ማቆሙን ሰሞኑን አስታውቋል።ርምጃው አንድ አፍጋናዊ በዋሽንግተን ዲሲ በብሔራዊ ዘብ አባላት ላይ ተኩስ መክፈቱን ተለትሎ ነው።ከዚህ ውሳኔ ቀደም ብሎ ትራምፕ ከሦስተኛው ዓለም ሀገራት ወደ አሜሪካን የሚሰደዱ ሰዎች በሙሉ በሙሉ እንደሚያስቆሙ ገልፀው ነበር።

የአሜሪካ የዜግነት እና የስደተኞች አገልግሎት ለሁሉም የተገን ጥያቄ ውሳኔ መስጠት ማቆሙን ሰሞኑን አስታውቋል።ርምጃው አንድ አፍጋናዊ በዋሽንግተን ዲሲ በብሔራዊ ዘብ አባላት ላይ ተኩ...

ተቃዋሚዎች ሥጋት ቢጫናቸውም በኢትዮጵያ ሰባተኛ ጠቅላላ ምርጫ ለመሳተፍ እየወሰኑ ነውየኦሮሞ ፌደራላዊ ኮንግረስ በምርጫ ቦርድ ላለመሰረዝ በሰባተኛው አጠቃላይ ምርጫ ለመሳተፍ ቢወስንም በአዲስ ...
02/12/2025

ተቃዋሚዎች ሥጋት ቢጫናቸውም በኢትዮጵያ ሰባተኛ ጠቅላላ ምርጫ ለመሳተፍ እየወሰኑ ነው
የኦሮሞ ፌደራላዊ ኮንግረስ በምርጫ ቦርድ ላለመሰረዝ በሰባተኛው አጠቃላይ ምርጫ ለመሳተፍ ቢወስንም በአዲስ አበባ እና “ጥቂት አካባቢዎች ብቻ” እንደሚሆን አስታውቋል። ጎጎት ለጉራጌ አንድነት እና ፍትሕ ፓርቲ ቢሳተፍም “አጃቢ” መሆን አይፈልግም። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ያዘጋጀው የጊዜ ሰሌዳ ከጸደቀ ከስድስት ወራት በኋላ ድምጽ ይሰጣል።

የኦሮሞ ፌደራላዊ ኮንግረስ በምርጫ ቦርድ ላለመሰረዝ በሰባተኛው አጠቃላይ ምርጫ ለመሳተፍ ቢወስንም በአዲስ አበባ እና “ጥቂት አካባቢዎች ብቻ” እንደሚሆን አስታውቋል። ጎጎት ለጉራጌ ...

02/12/2025

የማክሰኞ ኀዳር 23 ቀን፣ 2018 ዓ.ም የቀጥታ ሥርጭት
ጤና ይስጥልን! እንደምን አላችሁ?
ለአንድ ሰዓት በሚዘልቀው በዕለቱ ሥርጭት ታምራት ዲንሳ የዓለም ዜና ሊያሰማን፥ ጠቅላላ ሥርጭቱን ለመምራት ደግሞ አዜብ ታደሰ በቀጥታው ስቱዲዮ ይገኛል ። የዶይቼ ቬለ የቀጥታ ሥርጭት ከሳተላይት በተጨማሪ በዋናው ድረገጻችን፣ በቴሌግራም እና በዩቲዩብም ይተላለፋል። ማድመጫውን ለወዳጆቻችሁ እያጋራችሁ አብራችሁን ቆዩ።
ትክክለኛውን የዶይቼ ቬለ የዩቲዩብ ና እየቴሌግራም ቻናሎች በሚከተሉት ማገናኛዎች መከተል ትችላላችሁ።
https://www.youtube.com//videos
https://t.me/dw_amharic
dwamharic_newshour

02/12/2025

የማክሰኞ ኀዳር 23 ቀን፣ 2018 ዓ.ም የቀጥታ ሥርጭት
ጤና ይስጥልን! እንደምን አላችሁ?
ለአንድ ሰዓት በሚዘልቀው በዕለቱ ሥርጭት ታምራት ዲንሳ የዓለም ዜና ሊያሰማን፥ ጠቅላላ ሥርጭቱን ለመምራት ደግሞ አዜብ ታደሰ በቀጥታው ስቱዲዮ ይገኛሉ። የዶይቼ ቬለ የቀጥታ ሥርጭት ከሳተላይት በተጨማሪ በዋናው ድረገጻችን፣ በቴሌግራም እና በዩቲዩብም ይተላለፋል። ማድመጫውን ለወዳጆቻችሁ እያጋራችሁ አብራችሁን ቆዩ።
ትክክለኛውን የዶይቼ ቬለ የዩቲዩብ ና እየቴሌግራም ቻናሎች በሚከተሉት ማገናኛዎች መከተል ትችላላችሁ።
https://www.youtube.com//videos
https://t.me/dw_amharic
dwamharic_newshour

Adresse

Kurt-Schumacher-Str. 3
Bonn
53113

Benachrichtigungen

Lassen Sie sich von uns eine E-Mail senden und seien Sie der erste der Neuigkeiten und Aktionen von DW Amharic erfährt. Ihre E-Mail-Adresse wird nicht für andere Zwecke verwendet und Sie können sich jederzeit abmelden.

Service Kontaktieren

Nachricht an DW Amharic senden:

Teilen