16/06/2025
በብድር አቅርቦት እጥረት የተፈተነው የቤት ልማት ዘርፍ
ቤት ገንቢ ድርጅቶች ከግል ባንኮች በቂ ብድር እያገኙ አለመሆኑ መሠረታዊ ችግር እንደሆነበት የኢትዮጵያ የሪል እስቴት አልሚዎች ማሕበር አስታወቀ። በዚህ ወቅት በግል ዘርፉ ያለው የቤት ግንባታ እና ግብይት መቀዛቀዝ የታየበት ሲሆን የቤቶች ዋጋ መናር ለዚህ ምክንያት መሆኑን ማሕበሩ ገልጿል። መንግሥት ለዚህ ዘርፍ መሬት በጨረታ ያቀርብ የነበረ ሲሆን በአዲስ አበባ እስከ 2500 ቤቶችን በአንድ ጊዜ መገንባት ለሚችሉ ድርጅቶች "በድርድር" በማቅረብ ያለውን ከፍተኛ የቤት አቅርቦት ችግር ለማቃለል ማቀዱ ታውቋል።
ቤት ሳይገነቡ መሸጥ፣ በተባለው ጊዜ ቤቶችን ገንብቶ አለማስረከብ፣ የሕዝብን ገንዘብ ሰብስቦ ግንባታ አለመጀመር፣ በየጊዜው የመሸጫ ዋጋ መጨመር፣ ቤትን በውጭ ምንዛሪ አስልቶ በመሸጥ የሚወቀሰው ይህ ዘርፍ በብድር አቅርቦት እና በግንባታ መሬት እጦት መፈተኑ ይነገራል።
ቪዲዮ ዘገባ ፤ ሰለሞን ሙጬ (DW) አዲስ አበባ