DW Amharic

DW Amharic ዶይቼ ቬለ ርዕሰ ጉዳዮችን በፊስ ቡክ ያወያያል።
Telegram : t.me/dw_amharic
WhatsApp : https://t1p.de/2gg5u

Netiquette: https://www.dw.com/en/dw-netiquette-policy/a-5300954

የአውሮፓ ሀገራት ዶናልድ ትራምፕ መጠቅለል ወደሚፈልጓት ግሪንላንድ ወታደሮች እየላኩ ነውየአውሮፓ ሀገራት ወታደሮቻቸውን በአርክቲክ ቀጠና ወደምትገኘው ግሪንላንድ እየላኩ ይገኛሉ። ፈረንሳይ፣ ጀ...
15/01/2026

የአውሮፓ ሀገራት ዶናልድ ትራምፕ መጠቅለል ወደሚፈልጓት ግሪንላንድ ወታደሮች እየላኩ ነው

የአውሮፓ ሀገራት ወታደሮቻቸውን በአርክቲክ ቀጠና ወደምትገኘው ግሪንላንድ እየላኩ ይገኛሉ። ፈረንሳይ፣ ጀርመን፣ ዩናይትድ ኪንግደም፣ ኖርዌይ እና ስዊድን ውስን ቁጥር ያላቸው ወታደሮች ወታደሮች ልከዋል ወይም ለመላክ ዝግጁ መሆናቸውን አስታውቀዋል። ስልታዊ አቀማመጥ ያላት እና በማዕድን የበለጸገችውን የዴንማርክ ግዛት አሜሪካ መጠቅለል ትፈልጋለች።

የአውሮፓ ሀገራት ወታደሮቻቸውን በአርክቲክ ቀጠና ወደምትገኘው ግሪንላንድ እየላኩ ይገኛሉ። ፈረንሳይ፣ ጀርመን፣ ዩናይትድ ኪንግደም፣ ኖርዌይ እና ስዊድን ውስን ቁጥር ያላቸው ወታደ.....

የጥር 7 ቀን 2018 ዓ.ም የዓለም  ዜናበትግራይ ክልል የሚንቀሳቀሱ ስምንት ፓርቲዎች ሀገራዊ ምክክር በክልሉ እንዲካሄድ ለማገዝ ተስማሙ።ሐማስ በአሜሪካ ተነሳሽነት የተጀመረውን የተኩስ  አቁ...
15/01/2026

የጥር 7 ቀን 2018 ዓ.ም የዓለም ዜና
በትግራይ ክልል የሚንቀሳቀሱ ስምንት ፓርቲዎች ሀገራዊ ምክክር በክልሉ እንዲካሄድ ለማገዝ ተስማሙ።

ሐማስ በአሜሪካ ተነሳሽነት የተጀመረውን የተኩስ አቁም ስምምነት ሁለተኛ ክፍል አካል የሆነውን በፍልስጤም ይቋቋማል የተባለውን የባለሙያዎች ኮሚቴ እንደሚቀበለው አስታወቀ። በኮሚቴው ውስጥ ሐማስ አይካተትበትም ተብሏል።

የጀርመን የአየር ትራፊክ ተቆጣጣሪ ባለስልጣን የጀርመን አውሮፕላኖች በኢራን የአየር ክልል እንዳይጠቀሙ አሳሰበ። ባለስልጣኑ ይህን ያሳሰበው የአሜሪካው ፕሬዚደንት ዶናልድ ትራምፕ በኢራን ላይ ወታደራዊ ርምጃ እንደሚወስዱ መዛታቸውን ተከትሎ ነው።

የፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር የ75 ሃገራት ዜጎች የስደተኝነት ቪዛ እንደማይሰጥ አስታወቀ። በዝርዝሩ ከተካተቱት ሐገራት ኢትዮጵያና ኤርትራ ይገኙባቸዋል።

የአውሮፓ ሕብረት አባል ሐገራት ወታደሮቻቸውን የአሜሪካው ፕረዚደንት ዶናልድ ትራምፕ እጠቀልላታለሁ ወዳሏት ግሪንላንድ መላክ ጀመሩ። ወታደሮቻቸውን መላክ ከጀመሩት ውስጥ ጀርመን፣ ፈረንሳይ፣ ኖርዌይና ስዊድን ይገኙባቸዋል።

በትግራይ ክልል የሚንቀሳቀሱ ስምንት ፓርቲዎች ሀገራዊ ምክክር በክልሉ እንዲካሄድ ለማገዝ ተስማሙ። ሐማስ በአሜሪካ ተነሳሽነት የተጀመረውን የተኩስ አቁም ስምምነት ሁለተኛ ክፍል አካ....

በትግራይ የሚንቀሳቀሱ ስምንት ፓርቲዎች ሀገራዊ ምክክር በክልሉ እንዲካሄድ ለማገዝ ተስማሙበትግራይ ክልል የሚንቀሳቀሱ ስምንት ተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች በክልሉ ሀገራዊ ምክክር እንዲከናወን የ...
15/01/2026

በትግራይ የሚንቀሳቀሱ ስምንት ፓርቲዎች ሀገራዊ ምክክር በክልሉ እንዲካሄድ ለማገዝ ተስማሙ

በትግራይ ክልል የሚንቀሳቀሱ ስምንት ተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች በክልሉ ሀገራዊ ምክክር እንዲከናወን የሚያግዝ ጥምረት መመስረታቸውን ገለፁ። ፓርቲዎቹ ይህንን ስምምነታቸውን የሚገልጽ ደብዳቤ ለሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ማስገባታቸውንም ከተጣማሪዎች አንዱ የሆነው ትግራይ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ትዴፓ) ለዶቼ ቬለ አረጋግጧል።

በትግራይ ክልል የሚንቀሳቀሱ ስምንት ተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች በክልሉ ሀገራዊ ምክክር እንዲከናወን የሚያግዝ ጥምረት መመስረታቸውን ገለፁ። ፓርቲዎቹ ይህንን ስምምነታቸውን የሚገል...

በጋምቤላ ክልል መደበኛ ፖሊስ አባላት ትጥቅ በመፍታት ወደ ስልጠና እንዲገቡ ተወሰነግጭት የገጠመው የጋምቤላ ክልል የፖሊስ እና የአድማ ብተና አባላት የጦር መሣሪያ ካስረከቡ በኋላ ወደ የተሐድ...
15/01/2026

በጋምቤላ ክልል መደበኛ ፖሊስ አባላት ትጥቅ በመፍታት ወደ ስልጠና እንዲገቡ ተወሰነ

ግጭት የገጠመው የጋምቤላ ክልል የፖሊስ እና የአድማ ብተና አባላት የጦር መሣሪያ ካስረከቡ በኋላ ወደ የተሐድሶ ሥልጠና እንደሚገቡ የክልሉ የጸጥታ ቢሮ ባልደረባ ተናገሩ። የአድማ ብተና እና የመደበኛ ፖሊስ አባላት የታጠቁትን የጦር መሣሪያ እንዲያስረክቡ የተሰጣቸው ትዕዛዝ ዛሬ ያበቃል።

ግጭት የገጠመው የጋምቤላ ክልል የፖሊስ እና የአድማ ብተና አባላት የጦር መሣሪያ ካስረከቡ በኋላ ወደ የተሐድሶ ሥልጠና እንደሚገቡ የክልሉ የጸጥታ ቢሮ ባልደረባ ተናገሩ። የአድማ ብተና ...

የኢትዮጵያ እና የኤርትራ መንግሥታት ፍጥጫየኢትዮጵያ ፌድራል ፖሊስ የኤርትራ መንግሥት በአማራ ክልል ለሚንቀሳቀሱ የፋኖ ታጣቂዎች የላከው “ከ56 ሺህ በላይ የተለያዩ የጦር መሣሪያ ጥይቶችን” ...
15/01/2026

የኢትዮጵያ እና የኤርትራ መንግሥታት ፍጥጫ

የኢትዮጵያ ፌድራል ፖሊስ የኤርትራ መንግሥት በአማራ ክልል ለሚንቀሳቀሱ የፋኖ ታጣቂዎች የላከው “ከ56 ሺህ በላይ የተለያዩ የጦር መሣሪያ ጥይቶችን” በቁጥጥር ሥር እንዳዋለ አስታውቋል። ፕሬዝደንት ኢሳያስ አፈወርቂ በሀገራቸው ቴሌቭዥን ጣቢያ የተናገሯቸው ጉዳዮችና ፌድራል ፖሊስ ያወጣው መግለጫ የሁለቱ ሀገራት ግንኙነት ያለበትን ደረጃ የሚያሳይ ነው።

የኢትዮጵያ ፌድራል ፖሊስ የኤርትራ መንግሥት በአማራ ክልል ለሚንቀሳቀሱ የፋኖ ታጣቂዎች የላከው “ከ56 ሺህ በላይ የተለያዩ የጦር መሣሪያ ጥይቶችን” በቁጥጥር ሥር እንዳዋለ አስታውቋል....

15/01/2026

ጤና ይስጥልን!
ለአንድ ሰዓት በሚዘልቀው የዕለቱ ሥርጭት ዮሐንስ ገብረእግዚአብሔር የዓለም ዜና ያቀርባል ፤ እሸቴ በቀለ ስርጭቱን ይመራል።
የዶይቼ ቬለ የቀጥታ ሥርጭት ከኢትዮ ሳት በተጨማሪ በፌስቡክ፣ በቴሌግራም እና በዩቲዩብ ይተላለፋል። ማድመጫውን ለወዳጆቻችሁ እያጋራችሁ አብራችሁን ዝለቁ።
ትክክለኛውን የዶይቼ ቬለ የዩቲዩብ እና የቴሌግራም ቻናሎች በሚከተሉት ማስፈንጠሪያዎች ታገኛላችሁ።
https://www.youtube.com//videos
https://t.me/dw_amharic
dwamharic_newshour

ጤና ይስጥልን የስርጭታችን ታዳሚያን ! በዛሬው ስርጭታችን አራት ርዕሰ ጉዳዮች በትንታኔ ይደመጣሉ። እነርሱም :--የኢትዮጵያ እና የኤርትራ መንግሥታት ፍጥጫ-በትግራይ የሚንቀሳቀሱ ስምንት ፓር...
15/01/2026

ጤና ይስጥልን የስርጭታችን ታዳሚያን ! በዛሬው ስርጭታችን አራት ርዕሰ ጉዳዮች በትንታኔ ይደመጣሉ። እነርሱም :-
-የኢትዮጵያ እና የኤርትራ መንግሥታት ፍጥጫ
-በትግራይ የሚንቀሳቀሱ ስምንት ፓርቲዎች ሀገራዊ ምክክር በክልሉ እንዲካሄድ ለማገዝ መስማማታቸው
-በጋምቤላ ክልል በተፈጠረ የጸጥታ ችግር ምክንያት የአድማ ብተና እና የመደበኛ ፖሊስ አባላት የታጠቁትን የጦር መሣሪያ እንዲያስረክቡ የተሰጣቸው ትዕዛዝ ዛሬ ማብቃቱ
-የአውሮፓ ሕብረት አባል ሐገራት ወታደሮቻቸውን የአሜሪካው ፕረዚደንት ዶናልድ ትራምፕ ይገባኛል ወዳነሱባት ግሪንላንድ መላክ መጀመራቸው ናቸው።
ሳምንታዊው የባህል ዝግጅትም እንዲሁ ሰዓቱን ጠብቆ ይቀርባል። ስርጭቱን ለወዳጆቻችሁ እያጋራችሁ አብራችሁን እንድትቆዩ ከወዲሁ ጋብዘናል።

የዶይቼ ቬለ ጦማረ-ዜና (Newsletter) አገልግሎት  ተጠቃሚ ይሁኑ!የተወደዳችሁ የዝግጅታችን ታዳሚያን ከስርጭታችን ውስጥ በየሳምንቱ አንዴ ተመርጦ እንዲላክላችሁ የምትፈልጓቸው ጦማረ ዜና ...
15/01/2026

የዶይቼ ቬለ ጦማረ-ዜና (Newsletter) አገልግሎት ተጠቃሚ ይሁኑ!
የተወደዳችሁ የዝግጅታችን ታዳሚያን ከስርጭታችን ውስጥ በየሳምንቱ አንዴ ተመርጦ እንዲላክላችሁ የምትፈልጓቸው ጦማረ ዜና (Newsletter) ስብስቦችን ለተመዘገባችሁ በቀጥታ በኢሜል አድራሻ መላክ ጀምረናል ።
በመሆኑም ከስር ባለው ማገናኛ ውስጥ ባለው ባዶ ቦታ የኢሜል አድራሻዎን በማስገባት እናንተም የአገልግሎቱ ተጠቃሚ መሆን ትችላላችሁ ። ከስር ቀጥሎ በሰፈረ ክፍት ቦታ ላይ እስማማለሁ የአጠቃቀምደንብ.* የሚለውን በመጫን «ያስገቡ» የሚለውን ሲነኩ በቀላሉ ተመዘገቡ ማለት ነው ። የአዲሱ አገልግሎታችን ተጠቃሚ እንድትሆኑ ተጋብዛችኋል።
የዶይቼ ቬለ ጦማረ-ዜና (Newsletter) አገልግሎት
https://system.promio-connect.com/.../single.../83494https://scontent-fra5-

15/01/2026

ዝምታ ሰባሪ አዳጊ ሴቶች: የሥዕል ጥበበኛዋ ወጣት

ወጣት ዱሬቲ በየነ ነዋሪነቷ በሀዋሳ ከተማ ነው ፡፡ ዱሬቲ ለሥዕል ጥበብ ልዩ ፍቅር እንዳላት ትናገራለች ፡፡ አሁን ላይ በከተማው የመዝናኛ ሥፍራዎችንና ትምህርት ቤቶችን በሥዕል የማስዋብ ሥራ እየሠራች ትገኛለች ፡፡

“ የሥዕል ጥበብ ሥራን ያዳበርኩት ከልጅነቴ ጀምሮ ነው “ የምትለው ወጣቷ ሥዕል በውስጧ ያለውን ችሎታዋን እንድታወጣ ብቻ ሳይሆን የገቢ ምንጭም እየሆናት እንደሚገኝ ትናገራለች ፡፡ የሥዕል ጥበብ የተለያዩ ዘርፎች እንዳሉት የተናገረችው ዱሬቲ የግድግዳ ሥዕሎችንና በትዕዛዝ በምትቀበላቸው የሰዎች ሥዕሎች ላይ ትኩረት አድርጋ እየሠራች እንደምትገኝ ጠቅሳለች ፡፡

ዱሬቲ ራሷን በሥዕል ጥበብ ለማዳበር በሀዋሳ የማሠልጠኛ ትምህርት ቤት ባለመኖሩ በወቅቱ ፍላጎቷን ለሟሟላት እንዳልቻለች ታስታውሳለች ፡፡ በዚህም የተነሳ ወደ አዲስ አበባ በመሄድ የአጭር ጊዜ ሥልጠና መውሰዷል ገልጻለች ፡፡ በሥራዎቿ ዙሪያ ቤተሰቦቿና የአካባቢው ማህበረሰብ ድጋፍ በማድረግ እንደሚያበረታቷት ተናግራለች ፡፡ #ዝምታሰባሪአዳጊሴቶች

ዘገባ: ትንቢት ሰውነት

ቪድዮ: ሸዋንግዛው ወጋየሁ

በትግራይ ክልል የሚንቀሳቀሱ ስምንት ፓርቲዎች ሀገራዊ ምክክር በክልሉ እንዲካሄድ ለማገዝ ተስማሙበትግራይ ክልል የሚንቀሳቀሱ ስምንት ተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች በክልሉ ሀገራዊ ምክክር እንዲከና...
15/01/2026

በትግራይ ክልል የሚንቀሳቀሱ ስምንት ፓርቲዎች ሀገራዊ ምክክር በክልሉ እንዲካሄድ ለማገዝ ተስማሙ
በትግራይ ክልል የሚንቀሳቀሱ ስምንት ተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች በክልሉ ሀገራዊ ምክክር እንዲከናወን የሚያግዝ ጥምረት መመስረታቸውን ገለፁ። ፓርቲዎቹ ይህንን ስምምነታቸውን የሚገልጽ ደብዳቤ ለሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ማስገባታቸውንም ከተጣማሪዎች አንዱ የሆነው ትግራይ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ትዴፓ) ለዶቼ ቬለ አረጋግጧል።
የትግራይ ክልልን ችግር« ለመፍታት ያግዛል» በሚል የተደረገው የፖለቲካ ድርጅቶቹ ጥምረት፤ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ባለፈው ሳምንት በክልሉ ከሚገኙ ፓርቲዎች አመራሮች ጋር ያደረገውን ውይይት ተከትሎ ነው ተብሏል።
የብሔራዊ የምርጫ ቦርድ ህዝባዊ ወያነ አርነት ትግራይ ህወሓትን ከፓርቲ ምዝገባ መሰረዙ ይታወሳል። ይህንኑ ተከትሎ መጭው ሃገራዊ ምርጫ በትግራይ ክልል ስለመደረግ አለመደረጉ ገና በውል አልተለየም። በህወሓት እና በፌዴራል መንግስቱ መካከል የተፈጠረው እስጥ አገባም ገና መፍትሔ አላገኘም። እንደዚያም ኾኖ ግን በትግራይ ክልል የሚንቀሳቀሱት የፖለቲካ ፓርቲዎቹ የክልሉ ችግር "በውይይት እንደሚፈታ" እምነት እንዳለቸው እየገለጹ ነው።
የኢትዮጵያ ሃገራዊ የምክክር ኮሚሽን በትግራይ ክልል በያዝነው የጥር ወር መጨረሻ «የምክክር መድረክ» ለማዘጋጀት ቀጠሮ ይዟል።

የጋምቤላ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የክልሉ መደበኛ እና አድማ ብተና ፖሊሶች ትጥቅ እንዲፈቱ ጥብቅ መመሪያ አስተላለፈ፡፡ በክልሉ ከተፈጠረው የጸጥታ ችግር ጋር ተያይዞ ሁሉም ፖሊሶች እስከ ዛሬ ድረ...
15/01/2026

የጋምቤላ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የክልሉ መደበኛ እና አድማ ብተና ፖሊሶች ትጥቅ እንዲፈቱ ጥብቅ መመሪያ አስተላለፈ፡፡ በክልሉ ከተፈጠረው የጸጥታ ችግር ጋር ተያይዞ ሁሉም ፖሊሶች እስከ ዛሬ ድረስ ትጥቅ እንዲፈቱ የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን አዝዟል። የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ትናንት ረቡዕ በማህበራዊ መገናኛ ገጾቹ ባጋራው እና «ጥብቅ» ማስታወቂያ ባለው ማሳሰቢያው ቀደም ሲል ከክልሉ ኮማንድ ፖስት በተቀመጠው አቅጣጫ መሰረት «ፈርማችሁ ያወጣችሁትን የጦር መሣሪያ ገቢ ያላደረጋችሁ እስከ ጥር 7 ቀን 2018 ዓ/ም 11:00 ሰዓት ድረስ ገቢ እንድታደርጉ» እንድታደርጉ ይላል።
የክልሉ ፖሊስ ከሁለት ቀናት አስቀድሞ ባወጣው መግለጫ በክልሉ የሚገኙ ለሁሉም የፖሊስ አባላት «የተሃድሶ ስለጠና መስጠት አስፈላጊ ሆኖ ተገኝቷል» ብሎ ነበር።
ይህንኑ ተከትሎ በክልሉ በሚገኙ ዞኖች የመደበኛ ፖሊስ አባላት ዳግም ወደ ማስልጠኛ ጣቢያ ሊገቡ መሆኑ ነው የተገለጸው።
የአሁኑ የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ሁሉንም የፖሊስ አባላት ወደ ማሰልጠኛ ካስገባ የክልሉን ጸጥታ ሊከታተልና ሊያስከብር ሥለሚገባዉ አካል ያለው ነገር የለም።
በጋምቤላ ክልል ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ማንነትን መሰረት ያደረጉ ተደ,ጋጋሚ ጥቃቶች መፈጸማቸው እና በርካቶች ህይወታቸውን ማጣታቸውን መዘገባችን ይታወሳል። በዚህ ጥቃት ውስጥ ደግሞ የክልሉ የፖሊስ አባላት ተሳታፊ መሆናቸው መረጋገጡን አንድ ስማቸው እንዳይገለጽ የጠየቁ የክልሉ የጸጥታ ቢሮ ባልደረባ ለዶቼ ቬለ ተናግረዋል።
ሄድ መለስ እያለ ዓመታት የየተሻገረው የጋምቤላ ክልል የጸጥታ ሁኔታ አሳሳቢ እየሆነ መምጣቱን ዶቼ ቬለ በተለዩ ጊዜያት የክልሉን ነዋሪዎች አነጋግሮ ዘግቧል። በክልሉ የሚንቀሳሰው ዓለማቀፉ የድንበር የለሽ ሃኪሞች ቡድንም በግጭቱ በሰላማዊ ሰዎች ላይ የከፋ ሰብአዊ ጉዳት መድረሱን አስታውቆ ነበር። የምሽቱ ዜና መጽሔት ዝርዝሩን ይዟል።

የዩጋንዳ ተቃዋሚ ፓርቲዎች የሀገሪቱ መንግስት የፕሬዚዳንት ዩዌሪ ሙሴቬኒ ከ40 ዓመታት የተሻገረ አገዛዝ ለማራዘም ሲባል ሆን ተብሎ ምርጫው እንዲዘገይ እየተደረገ ነው ሲሉ ከሰሱ። አዛውንቱን ...
15/01/2026

የዩጋንዳ ተቃዋሚ ፓርቲዎች የሀገሪቱ መንግስት የፕሬዚዳንት ዩዌሪ ሙሴቬኒ ከ40 ዓመታት የተሻገረ አገዛዝ ለማራዘም ሲባል ሆን ተብሎ ምርጫው እንዲዘገይ እየተደረገ ነው ሲሉ ከሰሱ። አዛውንቱን ፕሬዚዳንት ከፖፕ የሚዚቃ ሰው ዳግም ባፋጠጠው የዩጋንዳ ምርጫ ዜጎች ድምጻቸውን እየሰጡ ነው።
ነገር ግን በበርካታ የሃገሪቱ አካባቢዎች የድምጽ አሰጣጥ ስነስረዓቱ ቶሎ አለመጀመሩን የገለጹት ተቃዋሚዎች ይህ ሆን ተብሎ የተደረገ እንደሆነ እየገለጹ ነው። መዲናዋ ካምፓላን ጨምሮ የመታወቂያ ወረቀት መለያ ማሽኖች እና የድምጽ መስጫ ሳጥኖች በቶሎ ያልደረሱባቸው አካባቢዎች እንደነበሩ የፈረንሳይ ዜና አገልግልሎት ዘጋቢዎች አረጋግጠዋል።
ዩጋንዳ በምታካሂደው ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ የ81 ዓመቱ አዛውንት ለ7ኛ የስልጣን ዘመን የማሸነፍ ዕድል እንዳላቸው እየተገለጸ ነው። ለዚህ ደግሞ በተለይ የሀገሪቱን መንግስታዊ እና የጸጥታ መዋቅር አጥብቀው መቆጣጠራቸው ሌሎች ዕድል እንዳያገኙ አስችሏቸዋል ነው የተባለው።
ሙዚቀኛው እና በስድስተኛው የዩጋንዳ ምርጫ ብርቱ ተፎካካሪ ሆነው የቀረቡት ሙዚቀኛው ሮበርት ኪያጎላኒ የሙሴቬኒን «አገዛዝ ለማብቃት» ብሎም ሙስናን ለመዋጋት እና በሀገሪቱ « ጠንካራ ለውጥ ለማምጣት » ቃል መግባታቸው ተዘግቧል። ምንም እንኳ ምርጫውን በድል የመወጣታቸው ነገር ባያስተማምንም።
በምርጫው ድምጽ ለመስጠት 21.6 ሚሊዮን ሰዎች ድምጽ ለመስጠት ሲመዘገቡ ሁለቱን ዋነኛ ተቃናቃኞች ጨምሮ ስድስት ሰዎች ለፕሬዘደንትነት ለመወዳደር መመዝገባቸውን የሀገሪቱ የምርጫ ኮሚሽን አስታውቋል።
የዛሬው የድምጽ አሰጣጥ ከመጀመሩ ጥቂት ቀናት አስቀድሞ በዩጋንዳ የኢንተርኔት አገልግሎት መቋረጡ ተመልክቷል። የሀገሪቱ የኮሙኒኬሽን ሚኒስቴር በሀገር ውስጥ የኢንተርኔት አገልግሎት ለሚያቀርቡ ኩባንያዎች «የተዛባ» እና «ሀሰተኛ መረጃዎች ስርጭትን ለመግታት» ኢንተርኔት ማቋረጥ አስፈላጊ ኾኖ መገኘቱን አስታውቆ ነበር። ነገር ግን ለተባለው መረጃ ከመንግስት ወገን ማረጋገጫም ሆነ ማስተባበያ አልቀረበበትም ።

Adresse

Kurt-Schumacher-Str. 3
Bonn
53113

Benachrichtigungen

Lassen Sie sich von uns eine E-Mail senden und seien Sie der erste der Neuigkeiten und Aktionen von DW Amharic erfährt. Ihre E-Mail-Adresse wird nicht für andere Zwecke verwendet und Sie können sich jederzeit abmelden.

Service Kontaktieren

Nachricht an DW Amharic senden:

Teilen