Breaking News In Ethiopia " ሰበር ዜና "

Breaking News In Ethiopia "  ሰበር ዜና " Human Rights, Freedom Of Expression & Rule Of Low ln Ethiopia. Big No For War, Enough With ETHNIC FEDERALISM! Ready To Deal ANY Difference's.......

የፌደራል ገቢ ግብር አዋጅ ፀደቀ።የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፌደራል ገቢ ግብር አዋጅን ለማሻሻል የቀረበውን ረቂቅ አዋጅ አፀደቀ።ረቂቅ አዋጁ በአብላጫ ድምጽ ነው የፀደቀው።ረቂቅ አዋጁ ላይ...
17/07/2025

የፌደራል ገቢ ግብር አዋጅ ፀደቀ።

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፌደራል ገቢ ግብር አዋጅን ለማሻሻል የቀረበውን ረቂቅ አዋጅ አፀደቀ።

ረቂቅ አዋጁ በአብላጫ ድምጽ ነው የፀደቀው።

ረቂቅ አዋጁ ላይ ሰፊ ክርክር ሲነሳበት እንደነበር ይታወቃል። በተለይ የኢትዮጵያ ሰራተኛ ማሕበራት ኮንፌዴሬሽን (ኢሰማኮ) ረቂቅ አዋጁ ላይ የደመወዝ ገቢ ግብር መነሻ ተብሎ የተቀመጠው 2,000 ብር ወደ 8,324 ብር ከፍ እንዲል ፤ አጠቃላይ አዋጁ የኑሮ ውድነቱንና ጫናውን ታሳቢ ባደረገ መልኩ እንዲታረም ሲወተውት ነበር።

ከ0 ጀምሮ 10% ፣ 15% ፣ 20% ፣ 25% ፣ 30% ፣ 35% ይቀጥል የነበርው የግብር ምጣኔም በረቂቅ አዋጁ 10% ከመሃል ወጥቶ ከ0 ጀምሮ ቀጥታ ባከፍተኛው 15% መጀመሩንም ታቃውሞ ነበር።

ሌላው 14,100 በላይ የሚያገኝ ሰው 35% ግብር ይከፍላል በሚለው ላይም ጥያቄ ተነስቶ ነበር።

በአሁኑ የኑሮ ውድነት ሰራተኛው በእያንዳንዱ ነገር በምግብ ዋጋ፣ በሚገዛው እቃ 15% ይጨምራል ይሄ በ35% ላይ ሲደመር 50% ይመጣል፤ 7% የጡረታ አለ ሲደመር 57% ከደመወዙ ላይ ይሄዳል በቀረችው 43% ልጆች ያስተምራል ፣ ምግብ ይበላል ፣ ልብስ ይገዛል ፣ ቤት ይከራያል ምንድነው የሚያደርገው ? የሚል የሰራተኛውን ጥያቄ በማንሳት ረቂቁ እንዲታረም ጠይቆ ነበር።

ሰበር ዜናበአሁን ሰአት በአፋር ክልል የሚገኘው ኤርታሌ እሳተ ገሞራ እየፈፈነዳ ይገኛልተገቢው ጥንቃቄ ይደረግ
15/07/2025

ሰበር ዜና

በአሁን ሰአት በአፋር ክልል የሚገኘው ኤርታሌ እሳተ ገሞራ እየፈፈነዳ ይገኛል
ተገቢው ጥንቃቄ ይደረግ

“በአፋር ክልል የሚገኙ ታጣቂዎች የሚፈጽሙት ማንኛውም ትንኮሳ የፌደራል ወይንም የአፋር ክልል መንግስት ትነኮሳ አደርገን ነው የምንወስደው” - ሌተናል ጀነራል ታደሰ ወረደበአፋር ክልል የሚገኙ...
15/07/2025

“በአፋር ክልል የሚገኙ ታጣቂዎች የሚፈጽሙት ማንኛውም ትንኮሳ የፌደራል ወይንም የአፋር ክልል መንግስት ትነኮሳ አደርገን ነው የምንወስደው” - ሌተናል ጀነራል ታደሰ ወረደ

በአፋር ክልል የሚገኙ የትግራይ ታጣቂዎች የሚፈጽሙት ማንኛውም ትንኮሳ የፌደራል መንግስት ወይንም የአፋር ክልል መንግስት ትነኮሳ አደርገን ነው የምንወስደው ሲሉ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ሌተናል ጀነራል ታደሰ ወረዳ ገለጹ።

የክልሉ የሰማዕታት ኮሚሽን ባዘጋጀው መድረክ ላይ ትላንት ሐምሌ 8 ቀን 2017 ዓ.ም ተገኝተው ንግግር ያደረጉት ሌተናል ጀነራል ታደሰ ወረደ “በዚያ በኩል የሚኖር ምንም አይነት ተነሳሽነት/እንቅስቃሴ እንደ ትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር፣ እዚያ ያሉ ሀይሎች ብቻ አድርጎ አይወስደውም፣ ወይ የፌደራል መንግስት ነው ካልሆነም የአፋር መንግስት ነው ብሎ ነው የሚወስደው” ብለዋል።

“እዛ ካሉት (ነጻ መሬት) ሀይሎች ጋር ያለው ልዩነት መቶ በመቶ መፈታት ያለበት በሰላማዊ መንገድ ነው፤ ነገር ግን ማንኛውም ትንኮሳ ከአፋር ክልል በኩል ከመጣ ወይ የአፋር መንገስት ነው አልያም የፌደራል መንግስቱ ነው ተብሎ የሚወሰድ እንጂ የትግራይ ተወላጆች/ተጋሩ ተደርጎ የሚወሰድ አይደለም” ሲሉም አስታውቀዋል፤ ታጣቂዎች “የውክልና (Proxy) ሀይሎች ሁነው እንዳያገለግሉ የሚቻለንን ሁሉ እናደርጋለን ሲሉ ተደምጠዋል።

Adresse

Schweinfurt
97424

Webseite

Benachrichtigungen

Lassen Sie sich von uns eine E-Mail senden und seien Sie der erste der Neuigkeiten und Aktionen von Breaking News In Ethiopia " ሰበር ዜና " erfährt. Ihre E-Mail-Adresse wird nicht für andere Zwecke verwendet und Sie können sich jederzeit abmelden.

Service Kontaktieren

Nachricht an Breaking News In Ethiopia " ሰበር ዜና " senden:

Teilen