Gursha group

Gursha group ጉርሻ
(479)

21/07/2025

😎😎😎

EBS TV ላይ የበቆሎ አበላል ውዝግብ! 🌽🥄🔪

በየጊዜው በስራዎቹ የምንመሰግነውም ሆነ የምንተቸው EBS TV፣ አሁን ደግሞ በአዲስ ቲክቶክ አቅራቢ ምክንያት አነጋጋሪ ሆኗል!

አዲሱ የዝግጅት አቅራቢ የተጠበሰ በቆሎን እንዴት መብላት እንደሚገባ ሲያስተምሩ ታይተዋል። ይሁን እንጂ፣ በቆሎውን "በማንኪያ ልክ እንደ ፖስታ ነው የሚበላው" በሚል ያሳዩት አበላል ብዙዎችን ግራ አጋብቷል።

የEBS ተከታታዮች ይህን አበላል "ብዙ ልጆች ነገ እኛም እንደ EBS አቅራቢዎች እናድርግ እንዳይሉ እና በቢላ እጃቸውን እንዳይቆርጡ" የሚል ስጋት አሳድሮባቸዋል።

አያይዘውም፣ "EBS አቅራቢዎች ጥርሳቸው እንዳይበላሽ በቆሎ አልግጥም ካሉ አለመጋጥ መብታቸው ነው፤ ይህ ነገር ይታረም" የሚል ጥሪ አቅርበዋል።

እናንተስ ስለ ጉዳዩ ምን ትላላችሁ?

የበቆሎ አበላል በማንኪያ ና በቢ* ይቻላል?

ወይስ አግባብ አይደለም?

ሀሳባችሁን አካፍሉን!

😎😎😎

🌴🌴🌴

21/07/2025

🇺🇸 አሜሪካ ሊሄዱ ነው

የኢትዮጵያ እግር ኳስ ብሄራዊ ቡድን

ሐምሌ 26.2017 ወደ አሜሪካ ሀገር ሄደው
የወዳጅነት ጭዋታ ሊያደርጉ ነው::

ለዚህም 26 የቡድኑ አባላት ተመርጠዋል::

ከዚህ በፊት አንዳንዶቹ ጭዋታው ሳይጀመር በአሜሪካ እንደጠፉ እና አንዳንዶቹ ደሞ White House ፊት ለፊት ልደታቸውን ሲያከብሩም የታዩ መሆኑን እዚሁ ፔጅ ላይ መገለፃችን ይታወቃል::

😎😎😎

🌴🌴🌴

21/07/2025

💔

ነገ በአለልኝ አዘነ ላይ በሞቱ ጥፋተኝነታቸው ያመኑት

* የባለቤቱን እና
* የባለቤቱን የእህት ባል

የጋሞ የከፍተኛውን ፍርድ ቤት የመጨረሻ የፍርድ ውሳኔን ለመስማት ዝግጁ ናችሁ?

አሌ አንተን መመለስ ባንችልም

" ነብስህ ግን ፍትህ " ልታገኝ ነው::

💔

🌴🌴🌴

21/07/2025
21/07/2025

🙏🙏🙏❤️❤️❤️

የአቡነ አረጋዊ ረድኤት እና ምልጃቸው አይለየን !!!

ከዚያች ዕለት ጀምሮ ምድራዊ ኅብስት ፈጽመው አልቀመሱም

አባታቸው ይስሃቅ የሮም ነገሥታት ወገን ስለሆኑ ከነገሥታት ወገን የምትሆን ሚስት ቢትታጭላቸውም እምቢ ብለው ወደ አባ ጳኩሚስ ገዳም ገቡ፡፡ በምንኩስና ስማቸው ዘሚካኤል ተብለው የሚጠሩትና ከተሰዓቱ ቅዱሳን አንዱ የሆኑት አቡነ አረጋዊ፡፡

ገና በትንሽ እድሜያቸው መመንኮስ ቢፈልጉም የንጉሥ ልጅ ስለነበሩ የአባታቸውን ንግስና ወራሽ ይሆናሉ ተብለው በመታሰባቸው፣ ዓለምን ንቀውና ቆርጠው ገዳም መግባታቸውን በተለያዩ ፈተናዎች ካረጋገጡ በኋላ በ14 ዓመታቸው ምንኩስና ሰጧቸው፡፡

ዘሚካኤልም ከእንጦንስና ከመቃርስ ከጳኩሚስም የምንኩስና መንፈሳዊ ሐረግ 4ኛ ትውልድ ሆኑ፡፡ የአባ ዘሚካኤል እናት ንግሥት ዕድናም የልጃቸውን ዜና ሰምተው መንኩሰው የሴቶች ገዳም ገብተዋል፡፡ ተስዓቱ ቅዱሳን በአልአሜዳ ዘመነ መንግሥት በዘሚካኤል መሪነት በ460 ዓ.ም አክሱም ከተማ ሲገቡ እናታቸው ቅድስት ዕድናም ልጃቸውን ተከትለው መጥተዋል፡፡

ከሰንበት በስተቀር እህል የማይቀምሱት እነዚህ ቅዱሳን አባ ዘሚካኤልን የበላይ አድርገው ሾሙትና ስሙንም አረጋዊ አሉት፡፡ ተስዓቱ ቅዱሳን ኢትዮጵያን በኪደተ እግራቸው ባርከዋታል፣ በትምህርታቸው የእምነቷን መሠረት አጽንተውታል፡፡ ለ12 ዓመታትም በፍጹም አንድነት በጸሎት እየተጉ አብረው ከተቀመጡ በኋላ ተለያዩ፡፡ አቡነ አረጋዊ ከሩቅ ሆነው የዳሞን ተራራ ባዩት ጊዜ እጅግ ወደውት ሲጠጉት ረጅሙን ገደል ጫፉ ላይ ለመድረስ መውጫ ቢያጡ ሌሊቱና ቀኑን ሁሉ በጸሎት አሳለፉ፡፡

ከሦስት መዓልትና ሦስት ሌሊት በኋላ ቅዱስ ሚካኤል “እግዚአብሔር ወደ ተራራው ጫፍ የምትወጣበትን ነገር እስኪያዘጋጅልህ ጥቂት ታገስ” ብሏቸው ሁለት ሱባኤ በዚያ ቆዩ፡፡ ከዚያም ቁመቱ ስድሳ ክንድ የሆነ ዘንዶ በቅዱስ ሚካኤል ጥበቃ አስወንጭፏቸው ደብረ ዳሞ ላይ ሲወጡ መስቀላቸውና መጎናጸፊያቸው ያረፈበትና ቅርጽ ዛሬም ድረስ በጠፍጣፋ ድንጋይ ላይ ምልክቱ በግልጽ ይታያል፡፡

አባታችንም ተራራው ላይ እንደወጡ በጸሎት አምላካቸውን በእጅጉ ስላመሰገነበት ቦታው ደብረ ሃሌ ሉያ ተብሏል፡፡ መጠነኛ ቤትም ሠርተው ያመጡትን ታቦት አኖሩት፡፡ ከዚያች ዕለት ጀምሮ ምድራዊ ኅብስት ፈጽመው አልቀመሱም፡፡ መላእክትም ለመሥዋዕት የሚያስፈልጉትን ንዋያተ ቅድሳት፣ ኅብስትና ወይን ከሰማይ ያወርዱላቸው ነበር፡፡

ንጉሡ ዐፄ ገብረ መስቀልም ወደ አቡነ አረጋዊ ሄዱው ተባረኩ፡፡ አሁን በስፍራው የምትገኘውን ቤተክርስቲያንም በሁለት ዓመት ሠርተው የእመቤታችንን ታቦት አስገቡ፡፡ 12 የወርቅና የብር መስቀሎችን ጨምሮ ብዙ ንዋያተ ቅድሳቶችንና ሰጧቸው፡፡ አቡነ አረጋዊም በሰማያዊ ኅብስትና ወይን ቀድሰው አቆረቧቸው፡፡ ጌታችንም ለአቡነ አረጋዊ ተገለጠለትና ቃልኪዳን ሰጣቸው፡፡ የገድልህን መጽሐፍ አምኖ በንጽሕና በቤቱ ያስቀመጠ ምንም አይነት በሽታ በቤቱ አይገባም፡፡

ድንገተኛም የሰውና የእንስሳ ሞት አይደርስበትም፣ የእህል ችግርም አይኖርበትም፡፡ በልባዊ ጥሞና የገድልህን መጽሐፍ የሰማ ያለስንፍና በፍጹም መታመን የንባቡን ኃይለ ቃል ያሰማ እኔ ለችግሩ ሁሉ ፈጥኜ እደርስለታለሁ፣ አንተም የሞት ጥላ አያርፍብህም፣ እንደ ነቢያቶቼ ኤልያስና ሄኖክ ትሰወራለህ እንጂ” ካላቸው በኋላ ወደ ሰማይ ዐረገ፡፡ አቡነ አረጋዊም ደቀ መዝሙራቸው ማትያስን ጠርተው ጌታችን የሰጣቸውን ቃልኪዳን ከገድላቸው ጋር ተጽፎ ለልጅ ልጅ መታሰቢያ እንዲሆን አዘዙት፡፡ ጌታችን እንደነገራቸውም በጥቅምት 14 ቀን ተሰውረዋል፡፡ ቅዱሳን ገዳማውያን ገድልና ትጋታቸው የዘለዓለሙን መንግስት በመናፈቅ ነውና ዘወትር በጸሎት ይተጋሉ፡፡ ገዳማቸውን ስንደግፍ በዓታቸውን ስናጸና በረከታቸው ያድርብናል፡፡

ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም

ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391

ወይም

አቢሲኒያ ባንክ
141029444

የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444

🙏🙏🙏

🌴🌴🌴

21/07/2025

❤️🙏

በዓለም ላይ ሁሉም ነገር ቢደርግለት

* ቢሸለም
* ቢሞገስ

የሚገባው አንድ ልጅ አለ

እሱም ቢኒ የሜሮን ልጅ ነው

እንኳን ደስ ያለህ ወንድማችን ጎደኞችን

ሁሉም ነገር እንዲሳክልህ እና ያስብክው ሁሉ እንዲሆንልህ ምኞታችን ነው::

ፈጣሪም የልጅ ቢኒን ልፋት አይቶ አንድ ቀን እናቱን ሜሮንን ጨርሶ እንዲምርሽ ምኞታችን ነው::

🙏🙏🙏

🌴🌴🌴

21/07/2025

ነብስ ይማር

አሰቃቂ የመሬት ናዳ: 5 የአንድ ቤተሰብ አባላት ህይወታቸውን አጡ!

ጋሞ ዞን፣ ኢትዮጵያ – በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል፣ አሪ ዞን፣ ደቡብ አሪ ወረዳ፣ ኮመር ቀበሌ፣ ሞልሽር ልማት ቡድን ውስጥ ትናንት ምሽት 2፡30 ላይ በደረሰ ከባድ የመሬት ናዳ የአምስት ሰዎች ህይወት ማለፉ ተሰማ። ይህ አሳዛኝ ክስተት የተከሰተው በ13/11/2017 ዓ.ም በጣለው ከፍተኛ ዝናብ ሳቢያ ነው።

የሟቾቹ ማንነት ሲረጋገጥ፣ የአንድ ቤተሰብ ሙሉ አባላት ሲሆኑ፣ ከህፃናት ጨምሮ

* 3 ወንዶች እና
* 2 ሴቶች ናቸው።

በዚህ አደጋ ሶስት የመኖሪያ ቤቶች ከቤት እንስሳት ጋር በናዳው ሙሉ በሙሉ ወድመዋል።
በአሁኑ ወቅት የመንግስት አካላት፣ ቀይ መስቀል እና የአካባቢው ነዋሪዎች የነፍስ ማዳን እና የእርዳታ ስራዎችን በከፍተኛ ሁኔታ እያከናወኑ ይገኛሉ።

የጋሞ ዞን መንግስት በደረሰው አደጋ የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን ገልጿል፤ በሟች ቤተሰቦች ላይም መፅናናትን ተመኝቷል።

ይህ ወቅት የክረምት ወራት በመሆኑ፣ በክልሉ ውስጥ ባሉ ሌሎች ተመሳሳይ የአደጋ ስጋት ያለባቸው አካባቢዎች ቅድመ ጥንቃቄ እንዲደረግ የአካባቢው አስተዳደር አሳስቧል።

የህብረተሰቡም ትኩረት እና ጥንቃቄ እንዲጨምር ጥሪ ቀርቧል።

Via DW

💔

🌴🌴🌴

21/07/2025

ውሸት ነው!

ታደለ ጥበቡ ወደ ፊስቡክ ተመልሷል የተባለው
መረጃ ሀሰት ነው!

በናፍቆት የምንጠብቀው ወንድማችን ታደለ ጥበቡ

አንዳንድ የፌስቡክ ገጾች ስማቸውን ወደ "ታደለ ጥበቡ" በመቀየር፣ እሱ እንደጻፈው አድርገው የተለያዩ ጽሑፎችን እያወጡ ነው።

ይህ ተግባር እውነት ያልሆነ መረጃ በማሰራጨት ህብረተሰቡን ለማደናገር የሚደረግ መሆኑን እንድትገነዘቡ እና እንድትጠነቀቁ እናሳስባለን።

የታደለ ጥበቡ ትክክለኛ የፌስቡክ አካውንት አሁንም እንዳለ ነው፤

ሆኖም የመጨረሻ ፖሰት ያደረገው ሁለት ዓመት ሊሞላው 20 ቀናት ቀርተውትል::

ወደ ፌስቡክ ሲመለስ እኛ ጉርሻዎች ይፋዊ መረጃውን የምናደርስ መሆናችንን ልናረጋግጥላችሁ እንወዳለን።

ስለሆነም፣

ስማቸውን ወደ ታደለ ጥበቡ የቀየሩ ልክ ታደለ ጥበቡ እንደፃፈው አድርገው የሚፅፉ የፌስቡክ ገጾችን እየተበራከቱ ስለመጡ እንድትጠነቀቁ መልዕክት እናስተላልፋለን።

ጉርሻዎች ነን

🌴🌴🌴

21/07/2025

ውሸት ነው!

ስለ አቤል ሙሉጌታ አዲስ አልበም የተሰራጨው መረጃ ሀሰት ነው!

በማህበራዊ ሚዲያ (በቲክቶክ እና ፌስቡክ) ድምፃዊ አቤል ሙሉጌታ አዲሱን አልበሙን አስመልክቶ ተናግሯል እየተባለ የሚሰራጨው መረጃ ከእውነት የራቀ ነው።

አቤል ሙሉጌታ እስካሁን ስለ አዲሱ አልበሙ ምንም የተናገረውም ሆነ ያወራው ነገር የለም።

ጉርሻዎች ራሱን አይተነዋ ድሮ ይሄን ቪዲዮ

ከ5 ዓመታት በፊት ድምፃዊ አቤል ሙሉጌታ ይህን ኮፍያ አድርጎ ስለቀድሞው አልበሙ ሲናገር የነበረውን ቪዲዮ በማህበራዊ ሚዲያ በማሰራጨት "ወደኋላ አልመለስም፣ ስለ አልበሜ የምትሰሙ ስሙት" እንዳለ ተደርጎ እየተሰራጨ ነው።

ይህ በፍፁም ሀሰት ነው።

እኛ ጉርሻ ፔጅ ነን፤

አንዋሽም!
እውነትን መናገር ልማዳችን ነው።

የኢትዮጵያ ህዝብ አብዛኛው የሶሻል ሚዲያ አጠቃቀም ወደ ኋላ የቀረ መሆኑ ይታያል።

እባክዎን መረጃዎችን ከማጋራታችን በፊት ትክክለኛነታቸውን እንፈትሽ።

አቤል ሙሉጌታ እስካሁን ስለ አዲሱ አልበሙ ምንም የተናገረውም ሆነ ያወራው ነገር የለም።

ይሻሻል!

ምን አገባን ልትሉ ትችላላችሁ ግን የቆይ ቪዲዮ ልክ እንደ አሁን ተደርጎ ብዙ ሰው ጋር ተደራሽነቱን ስላየን እንዲሁም ብዙ ልጆች እስይ የእጅህን ነው ያገኘህ እያሉ ስላተመለከትን ነው::

ይህ ጉርሻ ፔጅ ነው::

🙏🙏🙏

🌴🌴🌴

21/07/2025

ቪዲዮው ቲጂ ቻናላችን ላይ አለ::

🤔👇

አርብ እለት ለ3ኛ ጊዜ ትራምፕ ዶናልድ ትራምፕ የታላቁ ህዳሴ ግድብ በአሜሪካ ገንዘብ ተገነባ አሉ

እንዲሁም ለግብፅ አባይ ደሟ፣ ልቧ፣
ሁሉም ነገሯ ነው አሉ::

የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ፣ በግብፅ እና በኢትዮጵያ መካከል ከፍተኛ ውዝግብ የፈጠረውን የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታን አስመልክቶ አስገራሚ መግለጫ ሰጥተዋል።

ትራምፕ ግድቡ አርብ እለት በነበራቸው የእራት ፕሮግራም ላይ "በአብዛኛው በአሜሪካ ገንዘብ" እንደተገነባ ተናግረዋል።

በንግግራቸው ወቅት ትራምፕ፣ ግድቡ ከዓለም ትልቁ ግድቦች አንዱ መሆኑን ጠቅሰው፣ "አንድ ትንሽ ችግር አለው፣ ብዙ ውሃ ወደ አባይ ወንዝ እንዲፈስ አያደርግም" ሲሉ ገልጸዋል።

ይህ ደግሞ ግብፅን እንዳላስደሰተች ገልጸው፣ ግብፅ "ከአባይ ወንዝ እንደምትኖር" እና አባይ

* ደሟ፣
* ልቧ፣
ሁሉም ነገር"

እንደሆነ ተናግረዋል።

ትራምፕ፣ የግድቡን ግንባታ ሂደት በቅርበት ሲከታተሉ እንደነበር በመግለጽ፣ "ይህ ግዙፍ ግድብ ውሃውን ለአባይ ይዘጋዋል?" የሚል ስጋት እንደነበራቸው ተናግረዋል።

በመጨረሻም፣ ግድቡ "በአሜሪካ የገንዘብ ድጋፍ" መገንባቱ "ትንሽ እብደት" እንደሆነ ገልጸው፣

እርስዎ በዚህ ወር ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ለ3ኛ ጊዜ አጀንዳዬ ብሎ በሚገኝበት ስብሰባ ላይ ስለ ህዳሴ ግድብ የተሳሳተ መረጃዎችን ለመንግስታት እየሰጠ ያለውን የትራምፕ አካሄድ እንዴት አያችሁት ?

ሀሳባችሁን አካፍሉን?

🙏🙏🙏

🌴🌴🌴

21/07/2025

አለልኝ አዘነ የ15 ቀን ሙሽራ ነበር

አንድ ቀን ቀርቶትል
የመጨረሻ የፍርድ ውሳኔ ቀን ደርሷል።

ወንድሙ ሲናገር ፣ አለልኝ ከባለቤቱ ጋር ከ9 እስከ 10 ዓመታት በላይ በፍቅር ኖረዋል።

ነገር ግን ባልታሰበ እና በሚዘገንን ሁኔታ፣ ባቀዱት እና ባሰቡት ግድያ ወንድማችንን አጥተነዋል።

ሲሞት ገና የ15 ቀን ሙሽራ ነበር።

ሚስቱም የልጅነት ፍቅሩ የነበረች ሲሆን፣
ካገባትም ገና 15 ቀኑ ነበር።

"ከቤተሰቡ በላይ በሚወዳት፣ 'ወልደን ከብረን አብረን እንኖራለን' ባላት በገዛ ሚስቱ እቅድ እና በሚስቱ እህት ባል፣ ላይመለስ ከእኛ ተወስዷል" ሲል ወንድሙ በሐዘን ተናግሯል።

ይህ አሰቃቂ ድርጊት የ15 ቀን ሙሽራ የነበረውን ወንድማችንን ህይወት ቀጥፏል።

የዚህን አሳዛኝ ክስተት ገዳዬቹ ግድያውን ያመኑ ሲሆን ነገ በዚህ ስዓት በጋሞ ከፍተኛው ፍርድ ቤት የፍርድ ውሳኔ ይሰጣል::

አለልኝ ገና የ15 ቀን ሙሽራ ነበር

💔

🌴🌴🌴

Adresse

Zwickau

Benachrichtigungen

Lassen Sie sich von uns eine E-Mail senden und seien Sie der erste der Neuigkeiten und Aktionen von Gursha group erfährt. Ihre E-Mail-Adresse wird nicht für andere Zwecke verwendet und Sie können sich jederzeit abmelden.

Teilen

Our Story

Gursha Group Is Ethiopian Media Company Which Is Based In Germany. We are Providing Ethiopian Dramas, Ethiopian Movies, Ethiopian TV Show To Our Beloved Fans.