20/12/2025
የስፖርት ዜና፡
መድፈኞቹ ወደ መሪነቱ ተመልሰዋል!
ኤቨርተን 0-1 አርሰናል :- ጎል ዮኬሬሽ (27' P)
አርሰናል ከሜዳው ውጪ ተጉዞ ኤቨርተንን 1 ለ 0 በሆነ ውጤት በማሸነፍ ወሳኝ 3 ነጥብ ይዞ ተመልሷል።
በውጤቱም ማንቸስተር ሲቲ ለሰዓታት ተቆጣጥሮት የነበረውን የሊጉን መሪነት አርሰናል ዳግም ተረክቧል።
* አዲሱ ፈራጅ ቪክቶር ዮኬሬሽ የተገኘውን የፍፁም ቅጣት ምት በብቃት ከመረብ በማሳረፍ ለቡድኑ ብቸኛዋንና የድል ግብ አስቆጥሯል።
መድፈኞቹ ነጥባቸውን በማሳደግ በሊጉ አናት ላይ ተቀምጠዋል።
*አርሰናል የኤቨርተንን ተደጋጋሚ ጥቃት በመቋቋም መረቡን ሳያስደፍር (Clean Sheet) መውጣት ችሏል።
⚽️⚽️⚽️
🌴🌴🌴