Gursha group

Gursha group ጉርሻ
(492)

10/09/2026

አሁን በዚህ ሰዓት እና ደቂቃ ውብ ሀገራችን 2019 አዲስ ዓመትን ተቀብላለች!

እንኳን ለ2019 አዲስ ዓመት በሰላም በጤና በሰላም አደረሳችሁ!

ዓለም በራሷ መንገድ በምትጓዝበት በዚህ ዘመን፣ የራሳችን በሆነውና ከምድር ሁሉ ለየት ባለው ውብ የ፲፫ (13) ወራት የዘመን አቆጣጠራችን ሌላ አዲስ ምዕራፍ፣ አዲስ ተስፋ እና አዲስ ብርሃን ይዘን ለመቀበል በቅተናል።

ኢትዮጵያዊነት የራሱ የሆነ ልዩ ውበት፣ መከባበርና ፍቅር አለው። ይህ አዲስ ዓመት ለሁላችንም፦

* የታሰቡ ህልሞች የሚሳኩበት
* የተዘጉ ደጆች የሚከፈቱበት
* የጤና፣ የደስታ እና የትልቅ ስኬት ዓመት እንዲሆንልዎ የጉርሻ ፔጅ ቤተሰቦች ከልብ እንመኛለን!

በዓሉ የሰላም፣ የፍቅርና የምህረት ይሁንልን!

መልካም አዲስ ዓመት!

ጉርሻ page

🌴🌴🌴

10/09/2026
10/09/2026

የ2018 የእንቁጣጣሽ ሎተሪ የ20 ሚሊዮን ብር ዕጣ ቁጥር 2302203 ሆኖ ወጣ::

የኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት የ2018 ዓ.ም የእንቁጣጣሽ ሎተሪ ዕጣ በዛሬው ዕለት (ጳጉሜን 5 ቀን 2018 ዓ.ም) በህዝብ ፊት በይፋ ማውጣቱን አሳውቋል።

በዚህም መሰረት የ20,000,000 (ሃያ ሚሊዮን) ብር የ1ኛ ዕጣ ባለቤት የሚያደርገው ቁጥር 2302203 ሆኖ ወጥቷል።

ዋና ዋና የዕጣ ቁጥሮች ዝርዝር፡

1ኛ ዕጣ (20,000,000 ብር)፦ 2302203

2ኛ ዕጣ (10,000,000 ብር)፦ 1057413

3ኛ ዕጣ (5,000,000 ብር)፦ 0829516

4ኛ ዕጣ (2,000,000 ብር)፦ 2161591

©️የኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት

ጉርሻ page

🌴🌴🌴

10/09/2026
10/09/2026

እንኳን ለ2019 ዓ.ም ለአዲሱ ዓመት ዋዜማ አደረሳችሁ፣አደረሰን🙏

በአዲሱ ዓመት እናታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የጎደለንን ትሙላልን፣ከክፉ ነገር ከልላ የልባችንን መልካም መሻት ትፈጽምልን🙏

ነቢየ እግዚአብሔር ኢሳይያስ በትንቢቱ ኢሳ 7፡14 "ድንግል ትጸንሳለች፤ ወንድ ልጅም ትወልዳለች" ብሎ የተናገረላት ያቺ ድንግል በዚህች ዕለት ተወለደች፡፡ ይህች ቀን ልበ አምላክ ክቡር ዳዊት በመዝ 44÷9 "የወርቅ ልብስ ተጎናጽፋ ንግሥቲቱ በቀኝህ ትቆማለች" ብሎ የተናገረላት እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የተገኘችባት ናት፡፡ ቅዱስ ዮሐንስም በራዕይ 12÷1 "ፀሐይን የተጎናጸፈች፣ ጨረቃን የተጫማች፣ አስራ ሁለት የክዋክብት አክሊል በራሷ ላይ ያላት" ብሎ የመሰከረላት የብርሃን እናቱ ድንግል ማርያም የተወለደችባት ቀን ናት፡፡ የእርስዋም ልደት እንደ እንግዳ ደራሽ እንደ ውኃ ፈሳሽ ድንገት የተከሰተ ሳይሆን አስቀድሞ በትንቢት፣ በምሳሌና በራዕይ የሰውን ልጅ ድኅነት በጉጉት ሲጠባበቁ ለነበሩ ቅዱሳን ሲገለጽ የነበረ መሆኑን ቅዱስ መጽሐፍ እንዲህ ያስረዳናል፡፡

በኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ግንቦት አንድ ቀን (የግንቦት ልደታ) የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ልደት የሚከበርበት ዕለት ነው፡፡ ይህ ዕለት ቅዱስ ኤፍሬም በውዳሴ ማርያም ‹‹የመመኪያችን ዘውድ፣ የንጽሕናችንም መሰረት›› ያላት ወላዲተ አምላክ ድንግል ማርያም የተወለደችበት ነው፡፡ ጠቢቡ ንጉስ ሰሎሞን በመኃልይ 4÷8 "ንዒ እምሊባኖስ መርዓት ንዒ እምሊባኖስ፡ ሙሽራዬ ሆይ ከሊባኖስ ከእኔ ጋር ነይ፡፡" ብሎ እንደተናገረ በኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መጻሕፍት መሰረት የእመቤታችን የትውልድ ስፍራ ሊባኖስ የተባለው ተራራማ ሀገር ነው፡፡

ቅድስት ድንግል ማርያም ግንቦት 1 ቀን በ15 ዓ.ዓ ቅድመ ልደተ ክርስቶስ በሊባኖስ ተራራ ተወልዳለች፡፡ ኢትዮጵያዊው ሊቅ ቅዱስ ያሬድ ስለእመቤታችን ልደት "ማርያምሰ ተኀቱ እምትካት ውስተ ከርሱ ለአዳም ከመ ባሕርይ ጸዓዳ/ ማርያም ግን ከጥንት ጀምሮ በአዳም ባሕርይ ውስጥ እንደ ነጭ ዕንቁ ታበራለች፡፡ በማለት እርሷ በደፈረሰው ዓለም በንጽሕና፣ በቅድስናና በድንግልና ስታበራ እንደነበርና ኋላም የዓለም ብርሃን የሆነውን ኢየሱስ ክርስቶስን መውለዷን አመስጥሮ ተናግሯል።

ኢትዮጵያዊ ቄርሎስ የተባለው የነገረ ማርያም ሊቅ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ ሰሎሞን እመቤታችን በሊባኖስ እንደምትወለድ አስቀድሞ ሰሎሞን ስለእመቤታችን የተናገረውን ቃል መፈጸሙን ሲያመሰጠር "የአናብስት ልጅ አልኩሽ፡፡ ሙሽራዪት ሆይ ከሊባኖስ ተራራ ነዪ፤ ከአንበሶች ጒድጓድ ወጥተሽ ነዪ፤ ከምርጥ ነገድነት የተነሣ ከሚመካ ወገን የመወለድሽ ዜና እጅግ ግሩም ነው፡፡" ይላል፡፡ እመቤታችንም በሊባኖስ ተራራ እንድትወለድ ምክንያት የሆነው በማሕፀን ሳለች የአርሳባንን ልጅ ዓይን በማብራቷና ሳሚናስ የሚባለውን የጦሊቅን ልጅ ከሞት በማስነሳቷ አይሁድ በቅናት ተነሳስተውባቸው ስለነበር ሐናና ኢያቄም ወደ ሊባኖስ ተራራ እንዲሄዱ ታላቁ መልአክ ቅዱስ ገብርኤል ለኢያቄም ተገልጾ ስለነገራቸው እንደሆነ የቤተ ክርስቲያን መጻሕፍት ያስረዳሉ፡፡ ስለታላቅ መንፈሳዊ ተልዕኮ ሲባል ከሚያውቁት ቦታ መራቅን፣ ከለመዱት ቀዬ መሰደድን ከእመቤታችን የተረዱት ገዳማውያንም ዓለምን ንቀው ስሟን ስንቅ አድርገው ይመንናሉ። ገዳማቸውን ስንደግፍ ፣ በዓታቸውን ስናጸና የበረከታቸው ተሳታፊ እንሆናለን።

ድጋፍ ለማድረግ:-
ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም

ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391

ወይም

አቢሲኒያ ባንክ
141029444

ለበለጠ መረጃ:-
09 38 64 44 44/0918077957

🙏🙏🙏

🌴🌴🌴

10/09/2026

አቶ ክርስቲያን ታደለን ጨምሮ ከ600 በላይ የፖለቲካ እስረኞች በምህረት መለቀቃቸው ተገለጸ::

በተለያዩ ከባድ የወንጀል ክሶች ተመስርቶባቸው በእስር ላይ ይገኙ የነበሩ ከ600 በላይ ተጠራጣሪዎችና ተፈራጅ እስረኞች በመንግስት ምህረት ተደርጎላቸው መፈታታቸውን የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ይፋ አደረገ።

ከእስር ከተለቀቁት መካከል የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል የነበሩት አቶ ክርስቲያን ታደለ እንደሚገኙበት የተገለጸ ሲሆን፣ ህገ-መንግስታዊ ስርዓቱን በመናድ፣ በሽብርተኝነትና በሌሎች ከባድ ወንጀሎች ተከሰተው ፍርድ ቤት ሲመላለሱና የእስር ቅጣታቸውን ሲፈጽሙ የነበሩ ናቸው ተብሏል።

ኮሚሽኑ እንዳስታወቀው ከሆነ፣ ላለፉት አምስት ወራት ከፌደራል መንግስት ባለስልጣናት ጋር ሲያካሂድ የቆየውን ተከታታይ የምክክርና የድርድር ሂደቶች ተከተሎ በተደረሰበት መግባባት መሰረት እስረኞቹ ከቤተሰቦቻቸው ጋር እንዲቀላቀሉ ተደርጓል።

በተጨማሪም የኮሚሽኑ ተወካዮች በማረሚያ ቤቶች በአካል በመገኘት ከሚፈቱት ግለሰቦች ጋር ውይይት ማድረጋቸውንና የድርድሩን ውጤት የሚያስጠብቅ አቋም ላይ መደርሱን ገልጸዋል።

©️ኢሰመኮ

ጉርሻ page

🌴🌴🌴

Adresse

Zwickau

Telefon

004915210290031

Webseite

Benachrichtigungen

Lassen Sie sich von uns eine E-Mail senden und seien Sie der erste der Neuigkeiten und Aktionen von Gursha group erfährt. Ihre E-Mail-Adresse wird nicht für andere Zwecke verwendet und Sie können sich jederzeit abmelden.

Verknüpfungen

Teilen