27/02/2026
በ2013 ዓ/ም የትግራይ ሐይሎች በስልጣን ላይ ያለውን አገዛዝ በመናቅ በተለመደው የውጊያ ስልት በመግጠማቸው ለሽንፈት ተዳርገዋል፡፡ በሁለቱም በኩል የደረሰው ጉዳት ቀላል ባይሆንም የቴክኖሎጅ ብልጫ የነበረው አገዛዙ ሊያሸንፍ ችሏል፡፡
አሁንም ቢሆን አገዛዙ የያዘውን መሳሪያ ወይም መቃወሚያ ይዘናል በሚል ለመጠፋፋት የተለመደው መፎካከርና ውረድ እንውረድ መባባሉ ቀጥሏል፡፡
አገዛዙ የአፍሪካ መንግሰታት ሊኖሩት የማይቻል በርካታ ከባድ መሳሪያ ሊኖረው ይችላል፡፡ ለምሳሌ ቢ83 የተባለ ቦምብ ቢኖረው 10 ኪሎ ሜትር ራዲየስ የሚሸፍን ቦታወችን በአንድ ጊዜ ድምጥማጡን ያጠፋል፡፡ ይህም ማለት 314 ስኩየር ኪሎሜትሮችን የሚሸፍን ቦታ ነው፡፡ ይህ የቦታ ስፋት ማለት ከአብዛኞቹ የምስራቅ አፍሪካ ከተሞች የበለጠ ቦታ ይሸፍናል ማለት ነው፡፡በአንድ አቅጣጫ ተሰባስበህ ገጠምከው ማለት ተመቸው ማለት ነው፡፡በአጭር ጊዜ በአንድ አቅጣጫ ሰብስቦ ያውድምሃል ማለት ነው፡፡
ለኢትዮጵያ መንግሰት፤ለኤርትራ መንግስት እና ለሁሉም ሐይሎች ቁጭ ብላችሁ ተነጋገሩና ችግሩን ፍቱ፡፡
የኤርትራ መንግሰትም ለማይጠቀምበት ወደብ አላስፈላጊ ዋጋ መክፈል የለበትም፡፡ የኤርትራ መንግስት በሰጥቶ መቀበል መርህ ተደራደርና ጥቅምህን አስከብር፡፡
የትግራ ሐይሎች ከኤርትራ መንግስት ጋር በመሆን ተገንጥላችሁ አገር ለመሆን እና ከኤርትራ ጋር በመዋሃድ አገር ለመሆን የሚታሰብ መንገድ አዋጭ አይሆንም፡፡ ሰሞኑን በወልቃትና በራያ ላይ የተሰጠው ውሳኔ ስትፈልጉት የነበረው ውሳኔ የተሰጠ ሲሆን እንደ ሐገር በጋራ መጠቀም ሲቻል ራሳችሁንም ሆነ አገሪቱን ዋጋ ማስከፈል የለባችሁም፡፡ ፋኖ የመደራደር ክህሎት በመጨመር ውጤት ማምጣት ትችላላችሁ፡፡
ሁሉም ጉዳይ በንግግርና በሰላማዊ በሰላማዊ መንገድ የማያልቅ ከሆነ የሚደርሰው እልቂት ከዚህ በፊት ከሆነው ሁሉ የከፋ ነው፡፡
ለሁሉም ልቦና ፈጣሪ እንዲሰጠው ፈጣሪ የጠጠረውን ልባችሁን ያሟሟው፡፡
EWUNETU