Debrebirhan Press

Debrebirhan Press ሰለ እውነትና ፍትህ ይታገላል

በ2013 ዓ/ም የትግራይ ሐይሎች በስልጣን ላይ ያለውን አገዛዝ በመናቅ በተለመደው የውጊያ ስልት በመግጠማቸው ለሽንፈት ተዳርገዋል፡፡ በሁለቱም በኩል የደረሰው ጉዳት ቀላል ባይሆንም የቴክኖሎጅ...
27/02/2026

በ2013 ዓ/ም የትግራይ ሐይሎች በስልጣን ላይ ያለውን አገዛዝ በመናቅ በተለመደው የውጊያ ስልት በመግጠማቸው ለሽንፈት ተዳርገዋል፡፡ በሁለቱም በኩል የደረሰው ጉዳት ቀላል ባይሆንም የቴክኖሎጅ ብልጫ የነበረው አገዛዙ ሊያሸንፍ ችሏል፡፡
አሁንም ቢሆን አገዛዙ የያዘውን መሳሪያ ወይም መቃወሚያ ይዘናል በሚል ለመጠፋፋት የተለመደው መፎካከርና ውረድ እንውረድ መባባሉ ቀጥሏል፡፡

አገዛዙ የአፍሪካ መንግሰታት ሊኖሩት የማይቻል በርካታ ከባድ መሳሪያ ሊኖረው ይችላል፡፡ ለምሳሌ ቢ83 የተባለ ቦምብ ቢኖረው 10 ኪሎ ሜትር ራዲየስ የሚሸፍን ቦታወችን በአንድ ጊዜ ድምጥማጡን ያጠፋል፡፡ ይህም ማለት 314 ስኩየር ኪሎሜትሮችን የሚሸፍን ቦታ ነው፡፡ ይህ የቦታ ስፋት ማለት ከአብዛኞቹ የምስራቅ አፍሪካ ከተሞች የበለጠ ቦታ ይሸፍናል ማለት ነው፡፡በአንድ አቅጣጫ ተሰባስበህ ገጠምከው ማለት ተመቸው ማለት ነው፡፡በአጭር ጊዜ በአንድ አቅጣጫ ሰብስቦ ያውድምሃል ማለት ነው፡፡
ለኢትዮጵያ መንግሰት፤ለኤርትራ መንግስት እና ለሁሉም ሐይሎች ቁጭ ብላችሁ ተነጋገሩና ችግሩን ፍቱ፡፡
የኤርትራ መንግሰትም ለማይጠቀምበት ወደብ አላስፈላጊ ዋጋ መክፈል የለበትም፡፡ የኤርትራ መንግስት በሰጥቶ መቀበል መርህ ተደራደርና ጥቅምህን አስከብር፡፡

የትግራ ሐይሎች ከኤርትራ መንግስት ጋር በመሆን ተገንጥላችሁ አገር ለመሆን እና ከኤርትራ ጋር በመዋሃድ አገር ለመሆን የሚታሰብ መንገድ አዋጭ አይሆንም፡፡ ሰሞኑን በወልቃትና በራያ ላይ የተሰጠው ውሳኔ ስትፈልጉት የነበረው ውሳኔ የተሰጠ ሲሆን እንደ ሐገር በጋራ መጠቀም ሲቻል ራሳችሁንም ሆነ አገሪቱን ዋጋ ማስከፈል የለባችሁም፡፡ ፋኖ የመደራደር ክህሎት በመጨመር ውጤት ማምጣት ትችላላችሁ፡፡
ሁሉም ጉዳይ በንግግርና በሰላማዊ በሰላማዊ መንገድ የማያልቅ ከሆነ የሚደርሰው እልቂት ከዚህ በፊት ከሆነው ሁሉ የከፋ ነው፡፡
ለሁሉም ልቦና ፈጣሪ እንዲሰጠው ፈጣሪ የጠጠረውን ልባችሁን ያሟሟው፡፡

EWUNETU

በ2013 ዓ/ም የትግራይ ሐይሎች በስልጣን ላይ ያለውን አገዛዝ በመናቅ በተለመደው የውጊያ ስልት በመግጠማቸው ለሽንፈት ተዳርገዋል፡፡ በሁለቱም በኩል የደረሰው ጉዳት ቀላል ባይሆንም የቴክኖሎጅ...
26/02/2026

በ2013 ዓ/ም የትግራይ ሐይሎች በስልጣን ላይ ያለውን አገዛዝ በመናቅ በተለመደው የውጊያ ስልት በመግጠማቸው ለሽንፈት ተዳርገዋል፡፡ በሁለቱም በኩል የደረሰው ጉዳት ቀላል ባይሆንም የቴክኖሎጅ ብልጫ የነበረው አገዛዙ ሊያሸንፍ ችሏል፡፡
አሁንም ቢሆን አገዛዙ የያዘውን ድሮን እና መሰል መሳሪያ ወይም መቃወሚያ ይዘናል በሚል ለመጠፋፋት የተለመደው መፎካከርና ውረድ እንውረድ መባባሉ ቀጥሏል፡፡

አገዛዙ የአፍሪካ መንግሰታት ሊኖሩት የማይቻል በርካታ ከባድ መሳሪያ ሊኖረው ይችላል፡፡ ለምሳሌ ቢ83 የተባለ ቦምብ ቢኖረው 10 ኪሎ ሜትር ራዲየስ የሚሸፍን ቦታወችን በአንድ ጊዜ ድምጥማጡን ያጠፋል፡፡ ይህም ማለት 314 ስኩየር ኪሎሜትሮችን የሚሸፍን ቦታ ነው፡፡ ይህ የቦታ ስፋት ማለት ከአብዛኞቹ የምስራቅ አፍሪካ ከተሞች የበለጠ ቦታ ይሸፍናል ማለት ነው፡፡በአንድ አቅጣጫ ተሰባስበህ ገጠምከው ማለት ተመቸው ማለት ነው፡፡በአጭር ጊዜ በአንድ አቅጣጫ ሰብስቦ ያውድምሃል ማለት ነው፡፡
ለኢትዮጵያ መንግስት፤ለኤርትራ መንግስት እና ለሁሉም ሐይሎች ቁጭ ብላችሁ ተነጋገሩና ችግሩን ፍቱ፡፡
የኤርትራ መንግስትም ሆነ ሕዝብ ለማይጠቀምበት ወደብ አላስፈላጊ ዋጋ መክፈል የለበትም፡፡ የኤርትራ መንግስት በሰጥቶ መቀበል መርህ ተደራደርና ጥቅምህን አስከብር፡፡

የትግራይ ሐይሎች ከኤርትራ መንግስት ጋር በመሆን ተገንጥላችሁ አገር ለመሆን እና ከኤርትራ ጋር በመዋሃድ አገር ለመሆን የሚታሰብ መንገድ አዋጭ አይሆንም፡፡ ሰሞኑን በወልቃትና በራያ ላይ የተሰጠው ውሳኔ ስትፈልጉት የነበረው ውሳኔ የተሰጠ ሲሆን እንደ ሐገር በጋራ መጠቀም ሲቻል ራሳችሁንም ሆነ አገሪቱን ዋጋ ማስከፈል የለባችሁም፡፡ ፋኖ የመደራደር ክህሎት በመጨመር ውጤት ማምጣት ትችላላችሁ፡፡

ሁሉም ጉዳይ በንግግርና በሰላማዊ መንገድ የማያልቅ ከሆነ የሚደርሰው እልቂት ከዚህ በፊት ከሆነው ሁሉ የከፋ ነው፡፡ በስልጣን ላይ ያለውን አገዛዝ መናቅ እጅግ ውድና ከፍተኛ ዋጋ ያስከፍላል፡፡

ለሁሉም ልቦና ፈጣሪ እንዲሰጠው ፈጣሪ የጠጠረውን ልባችሁን ያሟሟው፡፡

EWUNETU

በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ ለጎንደር ዩኒቨርሲቲ ስጦታ አበረከቱ!!በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር አስራት አጸደወይንን...
23/01/2026

በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ ለጎንደር ዩኒቨርሲቲ ስጦታ አበረከቱ!!

በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር አስራት አጸደወይንን በኤምባሲያቸው ተቀብለው ባነጋገሩበት ወቅት ለዩኒቨርሲቲው የመጻሕፍት ስጦታ አበርክተዋል።
አምባሳደሩ ያበረከቱት ስጦታ የቀድሞው የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ሃሪ ትሩማንን ታሪክና ስራዎች የሚዘክሩ መጻሕፍት ሲሆኑ፣ ይህም በሁለቱ አካላት መካከል ያለውን የቆየ አጋርነት የሚያጠናክር መሆኑ ተገልጿል። ስጦታው በተለይም እ.ኤ.አ በ1950ዎቹ በፕሬዝዳንት ትሩማን ዘመን የተጀመረውን ታሪካዊ ግንኙነት እውቅና ለመስጠት የታለመ ነው።
ጎንደር ዩኒቨርሲቲ በቅርቡ ቤተ-መጽሐፍቱን በፕሬዝዳንት ሃሪ ትሩማን ስም ለመሰየም ለወሰነው ውሳኔ አምባሳደር ማሲንጋ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። ይህ እርምጃ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን የትምህርትና የባህል ትብብር ይበልጥ እንደሚያጎላው ተመልክቷል።
በተጨማሪም አምባሳደሩ የጎንደር ዩኒቨርሲቲ የተመሰረተበትን 70ኛ ዓመት እንዲሁም ለዘመናዊ ሕክምና መሰረት የሆነው የማስተማሪያ ሆስፒታሉ የተቋቋመበትን 100ኛ ዓመት በዓል በማስመልከት የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።
የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ከአሜሪካ መንግሥት ጋር ባለው የረጅም ዘመን ግንኙነት በተለይም በጤና እና በትምህርት ዘርፎች በርካታ የልማት ስራዎችን በጋራ ሲያከናውን መቆየቱ ይታወሳል።

ቤተ-መጽሐፍቱን በፕሬዝዳንት ሃሪ ትሩማን ስም ለመሰየም ለወሰነው ውሳኔ አምባሳደሩ ምስጋና አቅርበዋል።በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ለጎንደር ዩኒቨርሲቲ የመጽሐፍት ስጦታ አበረከቱ  | በኢት...
22/01/2026

ቤተ-መጽሐፍቱን በፕሬዝዳንት ሃሪ ትሩማን ስም ለመሰየም ለወሰነው ውሳኔ አምባሳደሩ ምስጋና አቅርበዋል።

በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ለጎንደር ዩኒቨርሲቲ የመጽሐፍት ስጦታ አበረከቱ
| በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ ለጎንደር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር አስራት አጸደወይንን በኤምባሲው ተቀብለው አነጋግረዋል።
አምባሳደሩ በዚሁ ወቅት የቀድሞው የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ሃሪ ትሩማንን ታሪክና ስራዎች የሚዘክሩ መጽሐፍትን ለዩኒቨርሲቲው በስጦታ አበርክተዋል።
ይህ ስጦታ በዩኒቨርሲቲውና በአሜሪካ መካከል ያለውንና እ.ኤ.አ በ1950ዎቹ በፕሬዝዳንት ትሩማን ዘመን የተጀመረውን የቆየ አጋርነት እውቅና ለመስጠት የታለመ መሆኑ ተገልጿል።
ዩኒቨርሲቲው በቅርቡ ቤተ-መጽሐፍቱን በፕሬዝዳንት ሃሪ ትሩማን ስም ለመሰየም ለወሰነው ውሳኔም አምባሳደሩ ምስጋና አቅርበዋል።
አምባሳደር ማሳንጋ የጎንደር ዩኒቨርሲቲ የተመሰረተበት 70ኛው ዓመት እና ከዩኒቨርሲቲው ምስረታ ቀድሞ የተቋቋመውና ለዘመናዊ ሕክምና መሰረት የሆነው የማስተማሪያ ሆስፒታሉ 100ኛ ዓመት በዓል በማስመልከት የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።

ሐኪሙ ዩቱዩበር የነጻነት ወርቅነህን ማረፍ ተከትሎ በሰራው ዜና ያገኘውን ገንዘብ ምን ላድርገው የሚል ጥያቄ አቅርቧል ? አስተያየታችን እንዲደርሰው አድርጉ።ይሄ ልጅ በጣም በሳል ነው። በዛ ላ...
20/01/2026

ሐኪሙ ዩቱዩበር የነጻነት ወርቅነህን ማረፍ ተከትሎ በሰራው ዜና ያገኘውን ገንዘብ ምን ላድርገው የሚል ጥያቄ አቅርቧል ?

አስተያየታችን እንዲደርሰው አድርጉ።

ይሄ ልጅ በጣም በሳል ነው። በዛ ላይ ደግሞ እጅግ ሲበዛ ቅን ነው። ለረጅም አመታት የሚሰራቸውን አይቻለሁ። አንድም ጊዜ ዩቱዩብ ገንዘብ ለማግኘት የውሸት ዜና ሲሰራ አላየሁትም። ሰወች በተሳሳተ ዜና በደል ሲደርስባቸው እውነቱን በማስረጃ እና በሐሳብ ይሞግታል። የህክምና ዶክተርም ነው። ራሱን በትምህርትም አብቅቷል። ወደ ፊት ሐገራችን ላይ ትልቅ ስራ ይሰራሉ ብየ ከምጠብቃቸው ሰወች አንዱ ነው። ዛሬም ያቀረበው ሃሳብ ትልቅነቱን የሚያሳይ ነው። በነጻነት ማረፍ በሰራው ዘገባ ምክንያት ያገኘውን ገንዘብ ምን ላድርገው ሃሳብ ስጡ ብሎ ያቀረበው የልጁን በጎ እና አርቆ አሳቢነት ያሳያል። በእኔ ሃሳብ ከዚህ ልጅ በጎ ጅምር ተነስተን ''ነጻነት ወርቅነህ ፋውንዴሽን'' ቢቋቋም እና በጎ ስራ በስሙ ቢሰራ ብየ አስባለሁ። ወንድም ቴወድሮስ ተክለአረጋይም የነጻነትን ስም በጎ ተግባር እንዲሰራበት ውስጥህ ያሰበ ይመስለኛል እና ግፋበት። ፋውንዴሽኑ ቢቋቋም አንድ ያዘነ ሰው ብቻ ሳይሆን ብዙ ያዘኑ ሰወችን እንዲስቁ ማድረግ ይቻላል።
ያቀረበው ቪዲዮ ከስር በኮሜንት መስጫው ይገኛል።

@ተመስገን አምሀ

8  ስምንት ጠቃሚ ወርቃማ ሕጎች ለልጆች እንሆ1- ለልጅህ የሚጠይቀውን ሁሉ ከመስጠት ተቆጠብ።  የሚፈልገውን ሁሉ የማግኘት መብት እንዳለው አምኖ ያድጋልና።  2-ልጃችሁ የስድብ ቃላትን ሲናገ...
01/09/2023

8 ስምንት ጠቃሚ ወርቃማ ሕጎች ለልጆች እንሆ

1- ለልጅህ የሚጠይቀውን ሁሉ ከመስጠት ተቆጠብ። የሚፈልገውን ሁሉ የማግኘት መብት እንዳለው አምኖ ያድጋልና።

2-ልጃችሁ የስድብ ቃላትን ሲናገር ከመሳቅ ተቆጠቡ። ክብር ማጣት/ክብር አለመስጠት መዝናኛ እንደሆነ እያሰበ ያድጋል።

3- በመጥፎ ባህሪው ሳይነቀፍ ሊያሳየው ለሚችለው መጥፎ ባህሪ ቸልተኛ መሆንን ያስወግዱ። በህብረተሰብ ውስጥ ምንም አይነት ህግጋት እንደሌለ በማሰብ ያድጋል።

4- ልጅዎ የሚያበላሽቦትን ማንኛውንም ነገር ከማንሳት ይቆጠቡ። ለኃላፊነቱ ሌሎች ኃላፊነት መውሰድ እንዳለባቸው በማመን ያድጋል።

5- ማንኛውንም ፕሮግራም በቲቪ እንዲመለከት አትፍቀድ። በልጅነት እና በአዋቂነት መካከል ምንም ልዩነት እንደሌለ በማሰብ ያድጋል።

6- ለልጅዎ የጠየቀውን ገንዘብ ሁሉ ከመስጠት ይቆጠቡ። ገንዘብ ማግኘት ቀላል እንደሆነ በማሰብ ያድጋል እናም ለመስረቅ ወደ ኋላ አይልም።

7- ጎረቤቶቹን፣ መምህራኑን እና ፖሊሶችን ሲበድል ሁል ጊዜ እራስዎን ከጎኑ ከማድረግ ይቆጠቡ። የሚሠራው ሁሉ ትክክል ነው፣ የተሳሳቱት ሌሎች ናቸው ብሎ በማሰብ ያድጋልና።

8- ወደ ጸሎት ቤት ስትሄድ ብቻውን እቤት ውስጥ እንዳትተወው አለበለዚያ እግዚአብሔር እንደሌለ እያሰበ ያድጋል።

ስለ ሻደይ፣ አሸንድዬ፣ ሶለል ምን ያህል ያውቃሉ ?የሻዳይ፣ አሸንድዬ እና ሶለል ባህል ዓመታዊ ክብረ በዓል በአማራ ክልል የሚከበር በዓል ነው።በዋግ ሹሞች መዲና ሰቆጣና አካባቢዋ ሻደይ፣ በቆ...
22/08/2023

ስለ ሻደይ፣ አሸንድዬ፣ ሶለል ምን ያህል ያውቃሉ ?

የሻዳይ፣ አሸንድዬ እና ሶለል ባህል ዓመታዊ ክብረ በዓል በአማራ ክልል የሚከበር በዓል ነው።

በዋግ ሹሞች መዲና ሰቆጣና አካባቢዋ ሻደይ፣ በቆቦ አካባቢ ሶለል እና በላስታ እና በአብዛኛው የክልሉ አካባቢዎች አሸንድዬ በሚል የሚከበረ የልጅ አገረዶች ጨዋታ በዓል ነው።

በዓላቱ አማራ ክልል ባለብዙ ዘርፍ የተፈጥሮ እና ሰው ሰራሽ ሀብት ባለቤት መሆኑን ፣ የተለያዩ ቋንቋዎች እና ባሕላዊ ትውፊቶች ያሉት፣ ሕዝቦች በመተሳሰብ በመፈቃቀር እና በአንድነት የሚኖሩበት መሆኑን የሚያሳዩ ናቸው።

የሻደይ፣ አሸንድዬ፣ ሶለል በዓል የአዲስ አመት መምጣቱን ተከትሎ የሚከበር ብስራት ነው።

ልጃገረዶች ከክረምት መግባት ጋር ተያይዞ የሚከሰቱ ውጣ ውረዶችን አልፈው ብሩህ ዘመን እየመጣ መሆኑን የሚያበስሩበት፣ እጮኛ የሚያጩበት፣ ከአቻዎቻቸው ጋር የሚጨፍሩበት እና የሚጫወቱበት ባሕላዊ ጨዋታ ነው።

በተጨማሪ እናቶች እና ህጻናት ያለ ልዩነት ሚሳተፉበትም ነው።

በዓላቱ በህዝባዊ አንድነት የሚያከብሩ፣ የመተሳሰብ፣ የፍቅር እና አብሮ የመኖር እሴትን ለትውልድ ማስተላለፊያ ጠንካራ ገመድ ናቸው።

ለውጭ ሀገራት ብርቅ በመሆኑም የገቢ ምንጭም ነው።

እነዚህ በዓላት በተለይም ባለፉት አመታት በአማራ ክልል በነበረው ጦርነት እና አለመረጋጋት እንዲሁም በዓለም አቀፉ ወረርሽኝ ኮቪድ-19 ምክንያት በሚፈለገው ልክ በተሟላ ሁኔታ አልተከበሩም።

ዘንድሮም በዓሉ በተቃረበበት ወቅት በክልሉ ሰላም ደፍርሶ ፣ ንፁሃን ተገድለው፣ በርካቶች ተጎድተው አጠቃላይ ቀውስ በመፈጠሩ እንዲሁም ክልሉ ባአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ስር በመውደቁ ድባቡ እንደከዚህ ቀደሙ የደመቀ አይደለም።

በነዚህ በዓላት በተለይ ከሰሜኑ ጦርነት በፊት በርካታ ቱርስቶች ወደ ክልሉ ይጎርፉ የነበረ ሲሆን በጦርነቱ ምክንያት እንቅስቃሴ ሁሉ ተዳክሞ ነበር ፤ ከወራት በፊት በተገኘው አንፃራዊ ሰላም የቱሪስት እንቅስቃሴ ትንሽ የመነቃቃት ነገር ቢፈጠርም ዳግም በፀጥታ ችግር እና ጦርነት ወደ ክልሉ የሚደረግ የቱሪስት እንቅስቃሴ እጅግ ተዳክሟል።

ፎቶ ፦ ፋይል

የእመቤታችን ፀሎትና ልመና የመድኃኒታችን የምህረት ቃል ኪዳን በኛ በልጆቿ ላይ ይድረስ 🙏
18/08/2023

የእመቤታችን ፀሎትና ልመና የመድኃኒታችን የምህረት ቃል ኪዳን በኛ በልጆቿ ላይ ይድረስ 🙏

በአዲስ አበባ የቅዱስ ገብርኤል ክብረ በዓል ⛪🛐የሚከበርባቸው 50 ገዳማትና አድባራት!!፩) መንበረ መንግሥት ግቢ ቅዱስ ገብርኤል ገዳም፤ በ1889 ዓ.ም. የተመሠረተ፤፪) አስኮ ቅዱስ ገብርኤ...
25/07/2023

በአዲስ አበባ የቅዱስ ገብርኤል ክብረ በዓል ⛪🛐
የሚከበርባቸው 50 ገዳማትና አድባራት!!

፩) መንበረ መንግሥት ግቢ ቅዱስ ገብርኤል ገዳም፤ በ1889 ዓ.ም. የተመሠረተ፤
፪) አስኮ ቅዱስ ገብርኤል፤
፫) ጎፋ መካነ ሕያዋን ቅዱስ ገብርኤል፤
፬) ደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል (ብሥራተ ገብርኤል)
፭) ቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል
፮) ደብረ ገነት ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ.
፯) ኮተቤ ደብረ ልዑል ዳግማዊ ቁልቢ ቅዱስ ገብርኤል በ.ክ.
፰) ደብረ ገነት ፉሪ ዕንቊ ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ.
፱) ምሥራቀ ፀሐይ ቅዱስ ገብርኤል ቅድስት አርሴማና አቡነ አዳም ቤ.ክ.
፲) ደብረ ምሕረት ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ.
፲፩) መካነ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ.
፲፪) አለም ባንክ ደብረ ራማ ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ.
፲፫) አየር ጤና አንቀጸ ብርሃን ኪዳነ ምሕረት ቤ.ክ. (በድርብነት ይከብራል)
፲፬) ደብረ በረከት ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ.
፲፭) ደብረ ዕንቊ ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ.
፲፮) ጋራ ኦዳ ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ.
፲፯) አንቆርጫ ደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ.
፲፰) ጉራራ ምሥራቀ ፀሐይ ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ቤ.ክ. (በድርብነት ይከብራል)
፲፱) ፈረንሳይ ደብረ ፀሐይ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ.ክ. (በድርብነት ይከብራል)
፳) አቃቂ ፈለገ ግዮን ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ.
፳፩) ኤረር ጎሮ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ.
፳፪) ቦሌ ሃራብሳ ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ.
፳፫) ቦሌ ቡልቡላ ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ.
፳፬) መካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤ.ክ. (በድርብነት ይከብራል)
፳፭) ብርሃናተ ዓለም ቅዱስ ጴጥሮስ ወጳውሎስ (የቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ. በድርብነት በውስጥ አለ)
፳፮) ቦሌ ደብረ ገነት ቅዱስ ጊዮርጊስና ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ.
፳፯) ቦሌ ኆኅተ ብርሃን ቅድስት ማርያም ቤ.ክ. (በድርብነት ይከብራል)
፳፰) ቦሌ መንበረ ብርሃን ቅዱስ እግዚአብሔር አብ ቤተ ክርስቲያን (በድርብነት ይከብራል)
፳፱) ደብረ ገሊላ አማኑኤል ቤ.ክ. (በድርብነት ይከብራል)
፴) ጀሞ ደብረ ኀይል ቅዱስ ገብርኤልና ቅድስት አርሴማ ቤ.ክ.
፴፩) አቃቂ ጃቲ መካነ ሕይወት ኪዳነ ምሕረት ቤ.ክ. (በድርብነት ይከብራል)
፴፪) ቃሊቲ መካነ ብርሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ.
፴፫) የካ አባዶ ገብርኤል ቤ.ክ.
፴፬) ኮልፌ ደብረ ፀሐይ አቡነ ተክለ ሃይማኖትና ቅዱስ ገብርኤል
፴፭) ኮልፌ ደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ ቤ/ክ (በድርብነት ይከብራል)
፴፮) ደብረ መዊዕ ቅዱስ ሚካኤል ቤ.ክ. (አዲሱ ሚካኤል) (በድርብነት ይከብራል)
፴፯) ካራ ቆሬ ደብረ በረከት ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ.
፴፰) ድልበር መካነ ጎልጎታ መድኀኔዓለም (በድርብነት ይከብራል)
፴፱) አዲስ አምባ ደብረ ገነት ቅድስት ኪዳነ ምሕረትና ደብረ ፍስሐ ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ (አዲስ ሰፈር)
፵) ደብረ ቀራንዮ መድኀኔ ዓለም ስር የሚገኘው ሙት አንሳ ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ.
፵፩) መንበረ ልዑል ገብርኤልና ማርያም ቤ.ክ.፤
፵፪) አየርጤና ደብረ ብሥራት ገብርኤልና አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቤ.ክ.
፵፫) ቱሉ ዲምቱ ደብረ መዊዕ ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ.
፵፬) ቀበና ምዕራፈ ጻድቃን አቡነ ተክለ ሃይማኖትና ቅ/ገብርኤል ቤ.ክ.
፵፭) መጠሊ ደብረ አሮን ፍልፍል ዋሻ ቅዱስ ገብርኤልና አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤ.ክ.
፵፮) ቂሊንጦ ደብረ ብሥራት ገብርኤልና ማርያም፤
፵፯) ደብረ ፍስሐ መካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤ.ክ. (በድርብነት ይከብራል)፡፡
፵፰) አንቀጸ ምሕረት (ራስ ካሣ) ቅዱስ ሚካኤል፤ (በድርብነት ይከብራል)
፵፱) ደብረ ዕንቊ ልደታ ለማርያም፤ (በድርብነት ይከብራል)
፶) ቦ

በ40 ዓመቷ በጨጓራ ካንሰር ከመሞቷ በፊት በዓለም ታዋቂው ዲዛይነር እና ደራሲ “ክሪስዳ ሮድሪጌዝ” እንዲህ ስትል ፅፋለች። 1. ጋራዥ ውስጥ የአለማችን ውድ መኪና ነበረኝ፣ አሁን ግን በዊልቸ...
24/07/2023

በ40 ዓመቷ በጨጓራ ካንሰር ከመሞቷ በፊት በዓለም ታዋቂው ዲዛይነር እና ደራሲ “ክሪስዳ ሮድሪጌዝ” እንዲህ ስትል ፅፋለች።

1. ጋራዥ ውስጥ የአለማችን ውድ መኪና ነበረኝ፣ አሁን ግን በዊልቸር መንቀሳቀስ አለብኝ።

2. ቤቴ ሁሉንም አይነት ብራንድ ያላቸው ልብሶች፣ ጫማዎች እና ውድ እቃዎች ይሸጣል፣ አሁን ግን ሰውነቴ በሆስፒታሉ በተዘጋጀ ትንሽ ጨርቅ ተጠቅልሏል።

3. በባንክ ውስጥ ብዙ ገንዘብ አለኝ። አሁን ግን ከዚህ መጠን ምንም አልጠቀመኝም።

4. ቤቴ እንደ ቤተ መንግስት ነበር አሁን ግን በሆስፒታል ውስጥ በሁለት አልጋዎች ተኝቻለሁ።

5. ከባለ አምስት ኮከብ ሆቴል ወደ ባለ አምስት ኮከብ ሆቴል. አሁን ግን በሆስፒታል ውስጥ ከአንድ ላብራቶሪ ወደ ሌላ በመንቀሳቀስ ጊዜዬን አሳልፋለሁ

🦋 በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎችን ፊርማ ሰጥቻለሁ ነገርግን በዚህ ጊዜ የሕክምና መዝገቦች የእኔ ፊርማ ናቸው።

እ.ኤ.አ. . ፀጉሬን ለመስራት ሰባት ፀጉር አስተካካዮች ነበሩኝ ፣ አሁን ግን - በራሴ ላይ አንድ ፀጉር የለኝም።

፨ በግል ጄት ላይ፣ የትኛውም ቦታ መብረር እችላለሁ፣ አሁን ግን ወደ ሆስፒታል በር ለመራመድ ሁለት እርዳታዎች ያስፈልጉኛል።

፨ ምንም እንኳን ብዙ ምግቦች ቢኖሩም, አሁን የእኔ አመጋገብ በቀን ሁለት ጽላቶች እና ምሽት ላይ ጥቂት የጨው ውሃ ጠብታዎች ናቸው.

ይህ ቤት፣ ይህ መኪና፣ ይህ አውሮፕላን፣ ይህ የቤት ዕቃ፣ ይህ ባንክ፣ ብዙ ዝናና ዝና፣ አንዳቸውም አይመጥኑኝም። ከእነዚህ ውስጥ አንዳቸውም አያዝናኑኝም.

የቴሌግራም ቻናላችንን ተቀላቅለው መሰል መረጃዎች በፍጥነት ያግኙ
https://t.me/GhionMaleda
https://t.me/GhionMaleda

የአርሲ ዩኒቨርሲቲ ለጀግናው አትሌታችን ቀነኒሳ በቀለ የክብር ዶክትሬት ዛሬ ይሰጠዋል፡፡ቀነኒ ኬኛ!! መኩሪያችን!
22/07/2023

የአርሲ ዩኒቨርሲቲ ለጀግናው አትሌታችን ቀነኒሳ በቀለ የክብር ዶክትሬት ዛሬ ይሰጠዋል፡፡
ቀነኒ ኬኛ!! መኩሪያችን!

Dirección

Madrid

Página web

Notificaciones

Sé el primero en enterarse y déjanos enviarle un correo electrónico cuando Debrebirhan Press publique noticias y promociones. Su dirección de correo electrónico no se utilizará para ningún otro fin, y puede darse de baja en cualquier momento.

Contacto La Empresa

Enviar un mensaje a Debrebirhan Press:

Compartir