Debrebirhan Press

Debrebirhan Press ሰለ እውነትና ፍትህ ይታገላል

ታማኝ በየነ የሕይወት ዘመን ጀግና የሚባል ሽልማት ሊሰጠው የሚገባ ሰው ነው።እዚህ አሜሪካ የሚኖሩ "አክቲቪስት ነን" የሚሉ እንከፎች በሆነ ባልሆነው የታማኝን ስም የሚጠሩትን ያህል የፈጣሪን ...
07/07/2025

ታማኝ በየነ የሕይወት ዘመን ጀግና የሚባል ሽልማት ሊሰጠው የሚገባ ሰው ነው።

እዚህ አሜሪካ የሚኖሩ "አክቲቪስት ነን" የሚሉ እንከፎች በሆነ ባልሆነው የታማኝን ስም የሚጠሩትን ያህል የፈጣሪን ስም ቢጠሩ በምድርም በሰማይም ተጠቃሚ ይሆኑ ነበር።

"ታማኝ ለተጎዱ ሰዎች ለምን ገንዘብ አይሰበስብም? ታማኝ ለምን ለቤተክርስቲያን gofundme አይከፍትም? ታማኝ ለምን የተቃውሞ ሰልፍ አይጠራም? ታማኝ ለምን የድጋፍ ሰልፍ አይጠራም? ታማኝ ለምን ሰልፍ ላይ አልተገኘም? ታማኝ ለምን ለአማራ አይታገልም? ታማኝ ለምን መንግስትን አልተቸም? ታማኝ ለምን ድምፁን ያጠፋል?" የሚሉ ማለቂያ የሌላቸውን የመሀይም ጥያቄዎች በየጊዜው እያነሱ ሲጃጃሉ እኮ ከታማኝ ጋር ውል የተፈራረሙ ነው የሚመስሉት።

ማይክ ስለያዘ ብቻ የማንም ደንቆሮ እየተነሳ ሲዘባርቅ ማየት እንዴት ያማል! ኸረ ሰው ይታዘበናል በሉ። ታማኝ ለዚች አገር የከፈለው መስዋዕትነትና ያበረከተው አስተዋፅኦ ሀብት ሆኖ ቢመነዘር ኖሮ ለአስር ትውልድ ይበቃ ነበር። ግን ምን ዋጋ አለው አገሪቱ ውለታ ቢስ ትውልድ ነው የፈጠረችው። አድር ባዩና የድል አጥቢያ አርበኛው ሁሉ በአገኘው አጋጣሚ እየተነሳ በእሱ ላይ አፉን ይከፍታል።

አባዬ .. ትልቅን ሰው በመዝለፍ ትልቅነት አይገኝም። የራስህን ስራ ሰርተህ ለመታወቅ ሞክር። ታማኝ የራሱ ህይወት አለው። እሱ ፈጣሪ አይደለም በጠራህው ቦታ ሁሉ የሚገኘው። እንደማንኛውም ሰው ያመነበትንና የተመቸውን ነገር በመረጠው ጊዜ የማድረግ መብት አለው። ምን ማድረግ እንዳለበት አንተ አትነግረውም! ውጤት ላያስገኝልህ ነገር ድድብናህንም አደባባይ አታውጣው!

ይቺ መከረኛ አገር ግን ስንቱን ደነዝ ነው የፈጠረችው? የማይረጥቡ አሳዎች!

በጋዜጠኛ ኃይሌ ሙሉ
ከአመት በፊት የተከተበች ስትሆን ለማስታወስ የተለጠፈ ነው።

ወይ የታማኝ በየነ አበሳ!እዚህ አሜሪካ የሚኖሩ "አክቲቪስት ነን" የሚሉ እንከፎች በሆነ ባልሆነው የታማኝን ስም የሚጠሩትን ያህል የፈጣሪን ስም ቢጠሩ በምድርም በሰማይም ተጠቃሚ ይሆኑ ነበር።...
06/07/2025

ወይ የታማኝ በየነ አበሳ!

እዚህ አሜሪካ የሚኖሩ "አክቲቪስት ነን" የሚሉ እንከፎች በሆነ ባልሆነው የታማኝን ስም የሚጠሩትን ያህል የፈጣሪን ስም ቢጠሩ በምድርም በሰማይም ተጠቃሚ ይሆኑ ነበር።

"ታማኝ ለተጎዱ ሰዎች ለምን ገንዘብ አይሰበስብም? ታማኝ ለምን ለቤተክርስቲያን gofundme አይከፍትም? ታማኝ ለምን የተቃውሞ ሰልፍ አይጠራም? ታማኝ ለምን የድጋፍ ሰልፍ አይጠራም? ታማኝ ለምን ሰልፍ ላይ አልተገኘም? ታማኝ ለምን ለአማራ አይታገልም? ታማኝ ለምን መንግስትን አልተቸም? ታማኝ ለምን ድምፁን ያጠፋል?" የሚሉ ማለቂያ የሌላቸውን የመሀይም ጥያቄዎች በየጊዜው እያነሱ ሲጃጃሉ እኮ ከታማኝ ጋር ውል የተፈራረሙ ነው የሚመስሉት።

ማይክ ስለያዘ ብቻ የማንም ደንቆሮ እየተነሳ ሲዘባርቅ ማየት እንዴት ያማል! ኸረ ሰው ይታዘበናል በሉ። ታማኝ ለዚች አገር የከፈለው መስዋዕትነትና ያበረከተው አስተዋፅኦ ሀብት ሆኖ ቢመነዘር ኖሮ ለአስር ትውልድ ይበቃ ነበር። ግን ምን ዋጋ አለው አገሪቱ ውለታ ቢስ ትውልድ ነው የፈጠረችው። አድር ባዩና የድል አጥቢያ አርበኛው ሁሉ በአገኘው አጋጣሚ እየተነሳ በእሱ ላይ አፉን ይከፍታል።

አባዬ .. ትልቅን ሰው በመዝለፍ ትልቅነት አይገኝም። የራስህን ስራ ሰርተህ ለመታወቅ ሞክር። ታማኝ የራሱ ህይወት አለው። እሱ ፈጣሪ አይደለም በጠራህው ቦታ ሁሉ የሚገኘው። እንደማንኛውም ሰው ያመነበትንና የተመቸውን ነገር በመረጠው ጊዜ የማድረግ መብት አለው። ምን ማድረግ እንዳለበት አንተ አትነግረውም! ውጤት ላያስገኝልህ ነገር ድድብናህንም አደባባይ አታውጣው!

ይቺ መከረኛ አገር ግን ስንቱን ደነዝ ነው የፈጠረችው? የማይረጥቡ አሳዎች!

በጋዜጠኛ ኃይሌ ሙሉ
ከአመት በፊት የተከተበች ስትሆን ለማስታወስ የተለጠፈ ነው።

አርቲስት ታማኝ በዬነና ቤተሰቡ ለተጎዳ ኢትዮጵያዊ ያልደረሱለት የለም።ከእነዚህም መካከል ፋሲል ደሞዝ አንዱ ነው።ይህን ሁሉ እረስቶ ግን የታላቁን ታማኝ በየነና ቤተሰቡን ስም አጥፍቷል።ፋሲል ...
06/07/2025

አርቲስት ታማኝ በዬነና ቤተሰቡ ለተጎዳ ኢትዮጵያዊ ያልደረሱለት የለም።ከእነዚህም መካከል ፋሲል ደሞዝ አንዱ ነው።ይህን ሁሉ እረስቶ ግን የታላቁን ታማኝ በየነና ቤተሰቡን ስም አጥፍቷል።ፋሲል ይሔን ያክል እብደት ውስጥ መግባቱ የሚያሳዝን እና ነውረኛ ድርጊት ነው፡፡ ይህን አምኖ ፋሲል ደሞዝ ይቅርታ ይጠይቃል ብዬ አምናለሁ!

@ጉዛራ ጎርጎራ ጎንደር

የሽዋ 38ቱ  ነገሥታት! በሽዋ ነገሥታት ጊዜ የኢትዮጵያ የግዛት ክልል ቀይ ባሕር፣ የአደን ባሕረ ሰላጤ፣ ሕንድ ውቅያኖስ እና ላይ ኛው የአባይ ሸለቆ /ነጭ አባይ/ እንደሚያዋስኑት የታወቀ ሲ...
27/05/2025

የሽዋ 38ቱ ነገሥታት!

በሽዋ ነገሥታት ጊዜ የኢትዮጵያ የግዛት ክልል ቀይ ባሕር፣ የአደን ባሕረ ሰላጤ፣ ሕንድ ውቅያኖስ እና ላይ ኛው የአባይ ሸለቆ /ነጭ አባይ/ እንደሚያዋስኑት የታወቀ ሲሆን፤ በውስጧ ያሉት የእስልምናና የክርስትና እንዲሁም የሌሎች ሃይማኖት ተከታይ ሕዝቦች በማዕከላዊው መንግሥት ስር ተጠቃለው የሚተዳደሩ፣ ነገር ግን ላለመገብርና ራስ ገዝ ለመሆን የንጉሥ ነገሥት መንግሥቱን ሲወጉ የነበሩ አሉ።

በሽዋ ነገሥታት የነገሡት ስምና ዓ. ም👇

1/ አፄ ይኩኑ አምላክ (ከ1253_1268 ዓ. ም)

2/ አፄ አግብዓ ጽዮን (ከ1268_1277)

3/ አፄ ፅንፈ አርዕድ (ከ1277_1278)

4/ አፄ ሕዝበ አሠግድ (ከ1278_1279)

5/ አፄ ቅድመ አሠግድ (ከ1279_1280)

6/ አፄ ጃን አሠግድ (ከ1280_1281)

7/ አፄ ስበዓ አሠግድ (ከ1281_1282)

8/ አፄ ውድም አርዕድ (ከ1282_1297)

9/ አፄ ዓምደ ጽዮን 1ኛ (ከ1297_1327)

10/ አፄ ሰይፈ አርዕድ (ከ1327_1355)

11/ አፄ ውድም አስፈሬ (ከ1355_1365)

12/ አፄ ዳዊት (ከ1365_1395)

13/ አፄ ቴዎድሮስ 1ኛ (ከ1395_1399)

14/ አፄ ይስሐቅ (ከ1399_1414)

15/ አፄ እስክንድያስ (እስክንድር) (ከ1414_1414 በወራት ነው የነገሠው)

16/ አፄ ሕዝብናኝ (ከ1414_1418)

17/ አፄ በድልናኝ (ከ1418_1419)

18/ አፄ ዓምደ እያሱ "ዳዊት" (ከ1419_1426)

19/ አፄ ዘርዓ ያዕቆብ (ከ1426_1460)

20/ አፄ በእደ ማርያም (ከ1460_1470)

21/ አፄ እስክንድር (ከ1470_1486)

22/ አፄ ዓምደ ጽዮን 1ኛ (ከ1486_1487)

23/ አፄ ናኦድ (ከ1487_1500)

24/ አፄ ልብነ ድንግል (ከ1500_1532)

25/ አፄ ገላውዲዎስ (ከ1532_1551)

26/ አፄ ሚናስ (ከ1551_1555 ዓ. ም)

በሸዋ ብቻ ንጉሥ የሆኑ ናቸው እኒህ:- አቤቶ ያዕቆቦች ይባላሉ!🥰

27/ አቤቶ ያዕቆብ

28/ አቤቶ ሥግው ቃል

29/ አቤቶ ነጋሲ(ነጋሲ ክርስቶስ)

30/ አቤቶ ስብስቴ(ሰብስቲያኖስ)

31/ መርድ አዝማች አብየ

32/ መርድ አዝማች አምሀየስ (አመኃ ኢየሱስ)

33/ መርድ አዝማች አስፋ ወሰን

34/ መርድ አዝማች ወሰን ሰገድ

35/ ንጉሥ ሣህለ ስላሴ

36/ ንጉሥ ኀይለ መለኮት

እንደገና ሙሉ ኢትዮጵያን ያስተዳደሩ!

37/ ንጉሠ ነገሥት ዘኢትዮጵያ አፄ ምኒልክ (እምዬ)

38/ ንጉሠ ነገሥት አፄ ኃይለ ሥላሴ (ጃንሆይ)

ጥይት በጀበርና _ ዝናር ተንተርሶ፣
ሽዋ ሰው ይሰራል _ እንደ እግዜር አፍርሶ።

✍️ Abreham Amelework Demeke

❝እኔ ኢትዮጵያዊያንን አላምንም ከራሴ ጀምሮ። በጭንብል ተሸፍነን የምንኖር ህዝቦች ነን። ለሰው የምናሳየው ገፅታና እውነተኛው ባህሪያችን የተለያዩ ናቸው። እንደ ተረታችን ፣ ስነ ፅሁፋችንና ን...
28/03/2025

❝እኔ ኢትዮጵያዊያንን አላምንም ከራሴ ጀምሮ። በጭንብል ተሸፍነን የምንኖር ህዝቦች ነን። ለሰው የምናሳየው ገፅታና እውነተኛው ባህሪያችን የተለያዩ ናቸው። እንደ ተረታችን ፣ ስነ ፅሁፋችንና ንግግራችን ባህርያችንም ሰምና ወርቅ ነው ...❞
**
❝በዚህ ላይ ደግሞ ክፉውና በጎውን ነገር አንዱን ከሌላው ለይተን የምናይበት መለኪያ የለንም ፤ የማንኛውም ነገር መሠረታዊ መለኪያችን የግል ጥቅማችን ነው። ለዚህም ነው ተንኮል የሚበዛው፤ መተማመን የሌለው፤ የወዳጅነት ወይም የጓደኝነት ትርጉሙ የማይታወቀው ፤ ሀሜት አሉባልታና እርስ በዕርስ መበላላት የሚበዛው። ኢትዮጵያዊያን ስንባል የምናውቀው መርህ አንድ ብቻ ነው ፤ የግል ጥቅም! ከራስ በላይ ነፋስ ፤ እኔ ከሞትኩ ሰርዶ አይብቀል... ሰውን ማመን ቀብሮ ፥ ይሉታል ከነተረቱ። የሚያሳዝን ነው...❞
**
❝ለግል ጥቅማችን የሚበጅ ከሆነ እንዋሻለን። ስንዋሽ ህሊናችንን ቅንጣት ታህል አይቆረቁረንም። እንዴት አድርጎ ለግል ጥቅም የተገዛ ህሊና ሊቆረቁረው ይችላል ?❞
**

❝ለተንኮል አንመለስም የምንሸርበው ተንኮል ጓደኛን፤ ወዳጅን ፤ የስጋ ዘመድን አይለይም ቅናት ባህላችን ነው። ❞
**
❝ምግባር የሚባለውን ነገር በአፍ ካልሆነ በቀር በተግባር አናውቀውም። በአጠቃላይ ክፉውንና በጎውን ለይቶ የሚያይ ህሊና የለንም፤ ያስተማረንም የለም። የተማርነው ነገር ቢኖር በአደባባይ ሰው መስሎ መታየትን ነው፤ ሰው መሳይ በሸንጎ ይሉ የለም? በአደባባይ ሁሉም ጨዋ፣ ልበ ሙሉ፣ ጀግና፣ አትንኩኝ ባይ፣ ኩሩና ቅን፣ በጎ አሳቢና ታማኝ፣ አስተዋይና ትሁት ነው። በአደባባይ የምናጠልቀው ጭንብል ይህ ነው። በግል ኑሮአችን ግን ከስብቅ ፣ ከምቀኝነት ፣ ከተንኮል፣ ከቅናት ፣ ለውሸት፣ ከአሉባልታና ከሀሜት፣ ለግል ጥቅም ለመልከስከስና ለመልፈስፈስ ከፍርሃትና ከአድርባይነት ርቀን አንገኝም። መለያ ባህርያችን ግብዝነት ነው። የግብዝነት ጭንብል አጥልቀን ነው የምንኖረው። ያለ ጭንብል እናስቀይማለን... ወይም እናምራለን፤ አይታወቅም። ያለ ጭንብል ታይተን አናውቅማ!❞

🔸 በዓሉ ግርማ ፥ የቀይ ኮከብ ጥሪ ፥ ገፅ 234

ከነ ሙሉ ክብሩ የሚኖር እንቁ ሰው !! በዘመናት አንዴ የተገኘ !!
16/02/2025

ከነ ሙሉ ክብሩ የሚኖር እንቁ ሰው !! በዘመናት አንዴ የተገኘ !!

ቴዲ አፍሮ እስካሁን ለሐገሩ እና ለሕዝቡ የከፈለው ቢመነዘር ለአስር ትውልድ ይበቃል።ሰወች ከራሳቸው ጋር ሲጋጩ የሚጋጩት ሰው-ቴዲ
08/02/2025

ቴዲ አፍሮ እስካሁን ለሐገሩ እና ለሕዝቡ የከፈለው ቢመነዘር ለአስር ትውልድ ይበቃል።

ሰወች ከራሳቸው ጋር ሲጋጩ የሚጋጩት ሰው-ቴዲ

ተንኮልና ምቀኝነትን መጸየፍ አለብን !!"..የምንኖርባት ጊዜ ከዘላለማዊ ህይወት ላይ ተቀንሳ በቅንፍ ውስጥ የተቀመጠች በጣም ትንሽ ጊዜ ናት.." በዚች ጊዜ ውስጥ በህይወታችን ስንኖር መረዳዳ...
25/03/2024

ተንኮልና ምቀኝነትን መጸየፍ አለብን !!

"..የምንኖርባት ጊዜ ከዘላለማዊ ህይወት ላይ ተቀንሳ በቅንፍ ውስጥ የተቀመጠች በጣም ትንሽ ጊዜ ናት.." በዚች ጊዜ ውስጥ በህይወታችን ስንኖር መረዳዳትን ፤ መተባበርንና መቀራረብን መልመድ አለብን።

ተንኮልና ምቀኝነትን መጸየፍ አለብን።

በየመጠለያው ቤታቸው ፈርሶ በሀዘን እና ረሃብ ለሚሰቃዩ ዜጎች፣ በክፉዎች እየተሳደደች ለምትገኝ ቅድስት ቤተክርስቲያን፣ በሰላም እጦት ምክንያት መውጣት መግባት ለቸገራቸው ወገኖች፣በጦርነት ምክ...
12/09/2023

በየመጠለያው ቤታቸው ፈርሶ በሀዘን እና ረሃብ ለሚሰቃዩ ዜጎች፣ በክፉዎች እየተሳደደች ለምትገኝ ቅድስት ቤተክርስቲያን፣ በሰላም እጦት ምክንያት መውጣት መግባት ለቸገራቸው ወገኖች፣በጦርነት ምክንያት ቤተሰባቸው ለተበተነ፣በማንነታቸው በየቦታው ለሚገደሉ እና ለሚፈናቀሉ ኢትዮጲያውያን ሁሉ አዲሱ አመት የእረፍት ፣ የሰላም እና የነፃነት ያርግላቸው። ሀገራችንን ሰላም ያርግልን።
#መልካምአዲስዓመት

‹‹ እንደ ምኒልክ  አይነት ሩህሩህ የለም›› ታየ ቦጋለ፡፡  ስለ ኢትዮጵያና ስለ ኢትዮጵያዊነት መሥማት ልቡ የወደደ ሁሉ ይከተላቸዋል፡፡ ኢትዮጵያን የሚወድ ሁሉ ይወዳቸዋል፡፡ ኢትዮጵያዊነት ...
07/09/2023

‹‹ እንደ ምኒልክ አይነት ሩህሩህ የለም›› ታየ ቦጋለ፡፡

ስለ ኢትዮጵያና ስለ ኢትዮጵያዊነት መሥማት ልቡ የወደደ ሁሉ ይከተላቸዋል፡፡ ኢትዮጵያን የሚወድ ሁሉ ይወዳቸዋል፡፡ ኢትዮጵያዊነት ጠላቱ የሆነ ደግሞ አምርሮ ይጠላቸዋል፡፡

ባገኙት አጋጣሚ በደረሱበት ሁሉ ስለ ኢትዮጵያና ስለ ኢትዮጵያዊነት ይናገራሉ፡፡ ይመሰክራሉ፡፡ የኢትዮጵያዊያንን ታሪክ በእውነት ሚዛን ይመዝናሉ፡፡ ወገንተኝነታቸው ለእውነት ነው የታሪክ መምሕሩና የመራራ እውነት ደራሲው ታዬ ቦጋለ፡፡

ከዘመናት በፊት በዘመነችው፣ ከቀደሙት በፊት በቀደመችው ፣ የታሪክ ሀብታም በሆነችው ኢትዮጵያ ይመካሉ፡፡

ምኒልክና እውነተኛ ፌደራሊዝም ስርዓትን በተመለከተ ከአብመድ ጋርቀ ቆይታ አድርገዋል፡፡

ምኒልክ ሶስት አይነት የዘመቻ ምዕራፍ ነበሯቸው ነው ያሉት፡፡ የመጀመሪያው የሸዋ ንጉሥ በነበሩበት ወቅት የሸዋ አማራና የሸዋ ኦሮሞ የጦር አበጋዞቻቸውን ይዘው በሰላማዊ መንገድ ግዛቶቻቸውን አስፍተው ነበር፡፡ በእነዚህ ሰላማዊ ዘመቻዎቻቸው ጅማን ጨምሮ በርካታ አካባቢዎችን ይዘዋል፡፡

በእነዚህ ቦታዎች ሁሉ ገዥ የመደቡት የአካባቢውን ተወላጆች ነው፡፡ ትክክለኛ የሆነውን ፌደራሊዝም የጀመሩና አሁን ላይ የብሔር ፌደራሊዝም የሚባለውን እሳቸው እስከ ታች ድረስ በተግባር ያሳዩ መሆናቸውን ነው የተናገሩት፡፡ ዜጎች በቋንቋቸው እንዲተዳደሩ ያደርጉ እንደነበርም ተናግረዋል፡፡

ሁለተኛው ዘመቻቸው ደግሞ የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት ከሆኑበት ጊዜ እስከ አድዋ ጦርነት ባለው ጊዜ ነበር፡፡ በዘመቻቸው አብዛኛውን ቦታ የያዙት በሰላማዊ መንገድ መሆኑን ነው የተናገሩት፡፡

ሶስተኛው የዘመቻ ምዕራፍ ደግሞ ከአድዋ ድል በኋላ እንደነበር አንስተዋል፡፡ የምኒልክ ዘመቻ አንድም ኢትዮጵያዊያንን በጋብቻ የማስተሳሰር፤ ሌላኛው በየአካባቢው ራሱን እንዲያስተዳድር የማድረግ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡

ትህነግ የሚመካበትና አሁን ላይ ያለው ፌደራሊዝም ግን የይስሙላህ መሆኑን ነው ያመላከቱት፡፡ እንደፈለገ የሚያሽከረክርበት ፌደራሊዝም ነው ያሉት የታሪክ ምሁሩ የምኒልክ ፌደራሊዝም እውነተኛ፣ በጣም ዘመናዊ፣ በዚያ ዘመን ውስጥ ሊታሰብ የማይችል የፌደራሊዝም ስርዓት ነበር ብለዋል፡፡

ምኒልክ አፍሪካን ወራሪዎች እየገቡባት እንደሆነ ያውቁ ስለ ነበር ከወገኖቻቸው ጋር ከመጋጨት ይልቅ በዙሪያቸው ጠላት እንዳለ በመናገር በፍቅር ለመኖር ጥረት ያደርጉ እንደነበርም ነው የተናገሩት፡፡

ያለፉት ሶስት አስርት ዓመታት የኢትዮጵያ ታሪክ ችግሩ በፈጠራ የተመሰረተና የኦነግን፣ የወያኔንና ኢትዮጵያን ለማፍረስ የሚፈልጉትን ሰዎች ዓላማ የያዘ መሆኑን ነው የታሪክ ምሁሩ ያስረዱት፡፡
‹‹እንደ ምኒልክ አይነት ሩህሩህ የለም›› ሲሉም ስለ ምኒልክ የሚወራው የሀሰት ትርክት መሆኑን ነው የተናገሩት፡፡ ከሰው መሀል አልቆ ሲያስገዛህ በሰው መጨከን አይገባም፣ ለሰው ሲያዝኑ እግዚአብሔር እድሜ ይሰጣል፣ የሚሉት ምኒልክ የባርያ ንግድ የሚባለውን ተግባርና አስተሳሰብ አጥብቀው ይቃወሙ እንደነበርም ተናግረዋል፡፡

ምኒልክ አይደለም ለወዳጅ ለካዳቸውና ሊገድላቸው ለተዘጋጄ ጭምር ይቅርታ የሚያደርጉ ሰው እንደነበሩም ተናግረዋል፡፡ ትልቅ ቁም ነገራቸውና ትልቅ ራዕያቸው ከዘመን የቀደመ መሆኑንም ነግረውኛል፡፡ ምኒልክ ሕዝቤ በባዶ እግሩ እየሄደ እኔ በጫማ አልሄድም ብለው የወርቅ ጫማቸውን አውልቀው በባዶ እግራቸው የሚሄዱ መሪ እንደነበሩም ምሁሩ አስታውሰዋል፡፡

ምኒልክ የስልጣኔ አውራና ጠቢብ ናቸው ያሉት አቶ ታዬ ቦጋለ ስለ እሳቸው የሚወራው በሙሉ ለፖለቲካ ፕሮፓጋንዳ ካልሆነ በስተቀር እንደዚያ አይነት ሥነ ልቦና ያላቸው አይነት ሰው አልነበሩም ብለዋል፡፡

ኢትዮጵያዊያን በአንድነታቸው እንዲቀጥሉ የማያግባቡ ትርክቶች ሲኖሩ በማቆምና የሌላው ዓለም ተሞክሮ ምን ይመስላል የሚለውን ማዬት ተገቢ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡ በትምህርት ዓለማ መሄድና ሁሉንም ሰው በእኩል ማዬት ተገቢ እንደሆነም ጠቅሰዋል። ወደሰፈር ከመውረድ በአንድነታችን ላይ መስራት እንደሚገባንም ነው ያሳሰቡት፡፡

የሰው ልጅ ለእንስሳት መብት በሚቆምበት ዘመን ያልተፈለገ ነገር ውስጥ መግባት እንደማይገባም አሳስበዋል፡፡ ውይይት፣ አዳዲስ ስርዓተ ትምህርት መቅረፅ፣ ቀናነትን፣ ሰውነትን መያዝ፣ በእምነት መራመድ፣ በዘመናት ውስጥ የነበረንን መስተጋብር ማንሳት ይገባልም ብለዋል፡፡

መገናኛ ብዙኃን ታላላቅ የታሪክ አዋቂዎችን በማቅረብ ሰውን ከብዥታ ማውጣት እንደሚገባቸውም ተናግረዋል፡፡ ‹‹ዓለም የምትጠፋው ከመጥፎዎች እኩይ ድርጊት ይልቅ በመልካሞች ዝመታ ነው›› እንዲሉ መልካሞች ዝም እንዳይሉ ማድረግ ይገባልም ብለዋል፡፡

ኢትዮጵያን ኢትዮጵያ ተነካች በተባለበት ሁሉ አብሮ በሚወድቀው በመከላከያ ሠራዊት ውስጥ እንያት፤ እኛ የአንድ እናት ልጆች ነን፤ ሰው በሞራል፣ በሃይማኖትና በሰውነት መኖር መቻል አለበትም ብለዋል፡፡

ሰው ሰው መሆኑን ቢያውቅና ለምን ዓላማ እንደተፈጠረ ቢገነዘብ፣ እመነት ቢኖረውና በእመነቱ ህግጋት ቢሄድ፣ በኢትዮጵያዊነት ሥነ ምግባርና ሞራል ታንፆ ቢያድርግና የሚያደረግው ድርጊት ውጤቱ ምንድን ነው የእኔን ማሕበረሰብ ይጠቅማል ወይ የሚለውን ቢረዳ መልካም እንደሆነም ተናግረዋል፡፡

እንደ ኢትዮጵያ አንድ ላይ መታገል እንደሚገባም መክረዋል፡፡ ወደዚህ ምድር ፈልጎ የመጣ የለም፤ ወደዚህ ምደር ሌላውን ጠልቶ ሌላውን ፈልጎ የመጣ ሰው ባለመኖሩ ሰውነቱን ልናከብረው እንጂ ልንጠላው አይገባም ነው ያሉት የታሪክ ምሁሩና የመራራ እውነት ደራሲው ታየ ቦጋለ፡፡

በታርቆ ክንዴ

መንገደኛ የተሰኘ የአገር አቋራጭ የአውቶብስ ትኬት መቁረጫ ሲስተም ይፋ ሆኗል።ሲስተሙ የአውቶብስ ቲኬት ለመቁረጥ የሚባክነውን ጊዜ ያስቀራል ተብሏል። ከታች የተያያዘውን ሊንክ ከጎግል ስቶር በ...
06/09/2023

መንገደኛ የተሰኘ የአገር አቋራጭ የአውቶብስ ትኬት መቁረጫ ሲስተም ይፋ ሆኗል።

ሲስተሙ የአውቶብስ ቲኬት ለመቁረጥ የሚባክነውን ጊዜ ያስቀራል ተብሏል።
ከታች የተያያዘውን ሊንክ ከጎግል ስቶር በማውረድ በሞባይልዎ እና በኮምፒውተርዎ መጠቀም ይችላሉ።
ጊዜ እና እንግልት ይቀንስልዎታል።

Mengedegna - Ethiopia bus ticket booking system in English, Amharic and Oromifa.

Mengedegna is an online bus booking application that helps internet users to reserve and purchase bus tickets across Ethiopia using their phones or computers through the bus reservation system. It is multilingual (English, Amharic and Afaan Oromoo) and works with most bust operators in Ethiopia. The app was developed by Walia Technologies PLC with the goal of establishing a safe and simple bus reservation system. The app's main purpose is to help users reserve and purchase bus tickets utilizing an online system with just a few clicks of your phone that eliminating the need to queue at a counter to buy a bus ticket. Customers can also use this simple app to check the availability and types of buses, as well as the departure time online. The application is integrated with TeleBirr and PayPal for quick payment, and it also allows customers to cancel and reschedule their reservations at any time. With our dedicated customer service, the application is available at all times, 24 hours a day.

Our mission is to transform Ethiopia's bus transportation system from an offline to a digitized and modern system, as well as to establish a user-friendly, easy-to-use system for the state's transportation sector. This application will provide hassle-free bus ticketing transporation system and play a huge role in digitizing Ethiopia’s Bus ticketing system.

https://play.google.com/store/apps/details?id=com.waliatech.mengedegna

"..የምንኖርባት ጊዜ ከዘላለማዊ ህይወት ላይ ተቀንሳ በቅንፍ ውስጥ የተቀመጠች በጣም ትንሽ ጊዜ ናት.." በዚች ጊዜ ውስጥ በህይወታችን ስንኖር መረዳዳትን ፤ መተባበርንና መቀራረብን መልመድ ...
04/09/2023

"..የምንኖርባት ጊዜ ከዘላለማዊ ህይወት ላይ ተቀንሳ በቅንፍ ውስጥ የተቀመጠች በጣም ትንሽ ጊዜ ናት.." በዚች ጊዜ ውስጥ በህይወታችን ስንኖር መረዳዳትን ፤ መተባበርንና መቀራረብን መልመድ አለብን።

Dirección

Madrid

Página web

Notificaciones

Sé el primero en enterarse y déjanos enviarle un correo electrónico cuando Debrebirhan Press publique noticias y promociones. Su dirección de correo electrónico no se utilizará para ningún otro fin, y puede darse de baja en cualquier momento.

Contacto La Empresa

Enviar un mensaje a Debrebirhan Press:

Compartir