Debrebirhan Press

Debrebirhan Press ሰለ እውነትና ፍትህ ይታገላል

የሁለቱ ፍቅረኛሞች ኃኪሞች ህልፈት ከሆስፒታል ከውስጥ የተገኜ ልዩ እና እውነተኛ መረጃ እነሆ !! ዶ/ር አቤኔዘር ጌታቸው እና ሜሮን ደምሌ በጎንደር ሆሰፒታል በትምህርት እና በስራ ላይ የነበ...
18/12/2025

የሁለቱ ፍቅረኛሞች ኃኪሞች ህልፈት ከሆስፒታል ከውስጥ የተገኜ ልዩ እና እውነተኛ መረጃ እነሆ !!

ዶ/ር አቤኔዘር ጌታቸው እና ሜሮን ደምሌ በጎንደር ሆሰፒታል በትምህርት እና በስራ ላይ የነበሩ ሲሆን በተቋሙ ውስጥ በነበሩበት ወቅት ፍቅረኛሞች ነበሩ፡፡
የሚያውቋቸው ሁሉ የነበራቸውን መቀራረብ እና መዋደድ ደስ የሚል እንደነበረ ይናገራሉ፡፡ ነገር ግን ዶ/ር ሜሮን ባጋጠማት የማይድን ህመም ምክንያት በተደጋጋሚ ጊዜ ለዶ/ር አቤኔዘር የራሱን ህይወት እንዲኖር እና ህይወቱን እንዲያስተካክል በተደጋጋሚ ስትነግረው እንደነበረ ጓደኞቻቸው ይናገራሉ፡፡
ዶ/ር ሜሮን ለረጅም ጊዜያት በህክምና ብትረዳም ህመሙ ለውጥ ሊያመጣ አለመቻሉ ቢታወቅም በርከት ላሉ ቀናት ሆስፒታል ውስጥ ገብታ ተኝቶ መታከም ሲደረግላት ቢቆይም ለውጥ ሊመጣ አልቻለችም፡፡ ዶ/ር ሜሮን ከ3 ዓመት በላይ የቆየ ህመም Systemic Lupus Erythematosus (SLE) እና (Acute liver failure) ነበረባት። አዲስ አበባ እና የተለያዮ ሆስፒታሎች እና ጎንደር ሆስፒታል ስትታከም ቆይታ ታሕሳስ 3 እንድትተኛ ተደረገ። ዶ/ር አቤኔዘርም በሆስፒታሉ ውስጥ ሲከታተላት እና ሲያሳክማት የቆየ ሲሆን ምሳ ከውጭ አምጥቶ ቀን ከተኛችበት አብልቷት ነበረ፡፡ እገዛ በሚያደርግላት ወቅትም የራሱን ህይወት እንዲመራ እና እንደማትድን ስትነግረው እንደነበር ጓደኞቻቸው ተናግረዋል፡፡
በዚህ ሁኔታ ውስጥ እንዳሉ ዶ/ር አቤኔዘር ከጓደኛው ጋር አምሽቶ ራሴን ስላመመኝ Tramadol ልግዛ ብሎ ከአንድ ጓደኛው ጋር ሂዶ 10 ፍሬ ገዝቶ ገባ፡፡ በእለቱም ማታ ላይ ከእናቱ ጋር ሲያወራ እንዳመሸ ከቤተሰብ ተሰምቷል፡፡ በማግስቱ ከሥራ በመቅረቱ ተደውሎለት ስልክ ባለማንሳቱ አብሮት የተከራየው ዶ/ር አበባው የተባለ ጓደኛው ተደወለለት፡፡ጓደኛውም ቤቱ ሂዶ ክፍሉን ሲያንኳኳ አልከፈት በማለቱ በሩን ከፍቶ ሲገባ ተሸፋፍኖ ተኝቶ ተመለከተው። ሲጠራው አቤት ስላላለው ትከሻውን እየነካ ለመቀስቀስ ሞከረ ስላልነቃለት ብርድ ልብሱን ሲገልጠው አረፋ አየ፤ ከዛ የልብ ትርታውን ሲያዳምጠው እንደሞተ አረጋገጠ፡፡ ደ/ር አበባውም ጉዳዩን ለፖሊስና ለባልደረባዎቹ ነግሮ ፖሊስ እያጣራው ይገኛል፡፡ ሚኒሊክ ሆስፒታልም የአስከሬን ምርመራ ታህሳስ 5 ተደርጎለታል፣ ውጤቱ እየተጠበቀ ነው። አካላዊ ጉዳት ምንም የደረሰበት እንደሌለ ተረጋግጧል፡፡

ዶ/ር ቃልኪዳን ደምሌ (እሕቷ) እና ወ/ሮ የቆየ በዛብህ (እናቷ) እያስታመሟት እያለ ዶር ሜሮን ታህሳስ 6 አረፈች። ቀብሯም ታሕሳስ 8 በትውልድ ቦታዋ ደ/ማርቆስ ከተማ ተፈጽሟል

በዚህ ዘመን በካንሰር፤በኩላሊት፤በጉበት፤ እና በስኳር የሚያልፈው ወገን እየበዛ የመጣ ጊዜ ላይ እንገኛለን፡፡ ነገሮችን በማወቅም ሆነ ባለማወቅ ወዳልሆነ አቅጣጫ ለመውሰድ የሚደረጉ የክፋት ጥንስሶችን ሕብረተሰቡ በአስተውሎት ሊያያቸው ይገባል፡፡

ፈጣሪ ነብሳቸውን በገነት ያኑርልን፡፡

ታማኝ በየነ የሕይወት ዘመን ጀግና የሚባል ሽልማት ሊሰጠው የሚገባ ሰው ነው።እዚህ አሜሪካ የሚኖሩ "አክቲቪስት ነን" የሚሉ እንከፎች በሆነ ባልሆነው የታማኝን ስም የሚጠሩትን ያህል የፈጣሪን ...
07/07/2025

ታማኝ በየነ የሕይወት ዘመን ጀግና የሚባል ሽልማት ሊሰጠው የሚገባ ሰው ነው።

እዚህ አሜሪካ የሚኖሩ "አክቲቪስት ነን" የሚሉ እንከፎች በሆነ ባልሆነው የታማኝን ስም የሚጠሩትን ያህል የፈጣሪን ስም ቢጠሩ በምድርም በሰማይም ተጠቃሚ ይሆኑ ነበር።

"ታማኝ ለተጎዱ ሰዎች ለምን ገንዘብ አይሰበስብም? ታማኝ ለምን ለቤተክርስቲያን gofundme አይከፍትም? ታማኝ ለምን የተቃውሞ ሰልፍ አይጠራም? ታማኝ ለምን የድጋፍ ሰልፍ አይጠራም? ታማኝ ለምን ሰልፍ ላይ አልተገኘም? ታማኝ ለምን ለአማራ አይታገልም? ታማኝ ለምን መንግስትን አልተቸም? ታማኝ ለምን ድምፁን ያጠፋል?" የሚሉ ማለቂያ የሌላቸውን የመሀይም ጥያቄዎች በየጊዜው እያነሱ ሲጃጃሉ እኮ ከታማኝ ጋር ውል የተፈራረሙ ነው የሚመስሉት።

ማይክ ስለያዘ ብቻ የማንም ደንቆሮ እየተነሳ ሲዘባርቅ ማየት እንዴት ያማል! ኸረ ሰው ይታዘበናል በሉ። ታማኝ ለዚች አገር የከፈለው መስዋዕትነትና ያበረከተው አስተዋፅኦ ሀብት ሆኖ ቢመነዘር ኖሮ ለአስር ትውልድ ይበቃ ነበር። ግን ምን ዋጋ አለው አገሪቱ ውለታ ቢስ ትውልድ ነው የፈጠረችው። አድር ባዩና የድል አጥቢያ አርበኛው ሁሉ በአገኘው አጋጣሚ እየተነሳ በእሱ ላይ አፉን ይከፍታል።

አባዬ .. ትልቅን ሰው በመዝለፍ ትልቅነት አይገኝም። የራስህን ስራ ሰርተህ ለመታወቅ ሞክር። ታማኝ የራሱ ህይወት አለው። እሱ ፈጣሪ አይደለም በጠራህው ቦታ ሁሉ የሚገኘው። እንደማንኛውም ሰው ያመነበትንና የተመቸውን ነገር በመረጠው ጊዜ የማድረግ መብት አለው። ምን ማድረግ እንዳለበት አንተ አትነግረውም! ውጤት ላያስገኝልህ ነገር ድድብናህንም አደባባይ አታውጣው!

ይቺ መከረኛ አገር ግን ስንቱን ደነዝ ነው የፈጠረችው? የማይረጥቡ አሳዎች!

በጋዜጠኛ ኃይሌ ሙሉ
ከአመት በፊት የተከተበች ስትሆን ለማስታወስ የተለጠፈ ነው።

ወይ የታማኝ በየነ አበሳ!እዚህ አሜሪካ የሚኖሩ "አክቲቪስት ነን" የሚሉ እንከፎች በሆነ ባልሆነው የታማኝን ስም የሚጠሩትን ያህል የፈጣሪን ስም ቢጠሩ በምድርም በሰማይም ተጠቃሚ ይሆኑ ነበር።...
06/07/2025

ወይ የታማኝ በየነ አበሳ!

እዚህ አሜሪካ የሚኖሩ "አክቲቪስት ነን" የሚሉ እንከፎች በሆነ ባልሆነው የታማኝን ስም የሚጠሩትን ያህል የፈጣሪን ስም ቢጠሩ በምድርም በሰማይም ተጠቃሚ ይሆኑ ነበር።

"ታማኝ ለተጎዱ ሰዎች ለምን ገንዘብ አይሰበስብም? ታማኝ ለምን ለቤተክርስቲያን gofundme አይከፍትም? ታማኝ ለምን የተቃውሞ ሰልፍ አይጠራም? ታማኝ ለምን የድጋፍ ሰልፍ አይጠራም? ታማኝ ለምን ሰልፍ ላይ አልተገኘም? ታማኝ ለምን ለአማራ አይታገልም? ታማኝ ለምን መንግስትን አልተቸም? ታማኝ ለምን ድምፁን ያጠፋል?" የሚሉ ማለቂያ የሌላቸውን የመሀይም ጥያቄዎች በየጊዜው እያነሱ ሲጃጃሉ እኮ ከታማኝ ጋር ውል የተፈራረሙ ነው የሚመስሉት።

ማይክ ስለያዘ ብቻ የማንም ደንቆሮ እየተነሳ ሲዘባርቅ ማየት እንዴት ያማል! ኸረ ሰው ይታዘበናል በሉ። ታማኝ ለዚች አገር የከፈለው መስዋዕትነትና ያበረከተው አስተዋፅኦ ሀብት ሆኖ ቢመነዘር ኖሮ ለአስር ትውልድ ይበቃ ነበር። ግን ምን ዋጋ አለው አገሪቱ ውለታ ቢስ ትውልድ ነው የፈጠረችው። አድር ባዩና የድል አጥቢያ አርበኛው ሁሉ በአገኘው አጋጣሚ እየተነሳ በእሱ ላይ አፉን ይከፍታል።

አባዬ .. ትልቅን ሰው በመዝለፍ ትልቅነት አይገኝም። የራስህን ስራ ሰርተህ ለመታወቅ ሞክር። ታማኝ የራሱ ህይወት አለው። እሱ ፈጣሪ አይደለም በጠራህው ቦታ ሁሉ የሚገኘው። እንደማንኛውም ሰው ያመነበትንና የተመቸውን ነገር በመረጠው ጊዜ የማድረግ መብት አለው። ምን ማድረግ እንዳለበት አንተ አትነግረውም! ውጤት ላያስገኝልህ ነገር ድድብናህንም አደባባይ አታውጣው!

ይቺ መከረኛ አገር ግን ስንቱን ደነዝ ነው የፈጠረችው? የማይረጥቡ አሳዎች!

በጋዜጠኛ ኃይሌ ሙሉ
ከአመት በፊት የተከተበች ስትሆን ለማስታወስ የተለጠፈ ነው።

አርቲስት ታማኝ በዬነና ቤተሰቡ ለተጎዳ ኢትዮጵያዊ ያልደረሱለት የለም።ከእነዚህም መካከል ፋሲል ደሞዝ አንዱ ነው።ይህን ሁሉ እረስቶ ግን የታላቁን ታማኝ በየነና ቤተሰቡን ስም አጥፍቷል።ፋሲል ...
06/07/2025

አርቲስት ታማኝ በዬነና ቤተሰቡ ለተጎዳ ኢትዮጵያዊ ያልደረሱለት የለም።ከእነዚህም መካከል ፋሲል ደሞዝ አንዱ ነው።ይህን ሁሉ እረስቶ ግን የታላቁን ታማኝ በየነና ቤተሰቡን ስም አጥፍቷል።ፋሲል ይሔን ያክል እብደት ውስጥ መግባቱ የሚያሳዝን እና ነውረኛ ድርጊት ነው፡፡ ይህን አምኖ ፋሲል ደሞዝ ይቅርታ ይጠይቃል ብዬ አምናለሁ!

@ጉዛራ ጎርጎራ ጎንደር

የሽዋ 38ቱ  ነገሥታት! በሽዋ ነገሥታት ጊዜ የኢትዮጵያ የግዛት ክልል ቀይ ባሕር፣ የአደን ባሕረ ሰላጤ፣ ሕንድ ውቅያኖስ እና ላይ ኛው የአባይ ሸለቆ /ነጭ አባይ/ እንደሚያዋስኑት የታወቀ ሲ...
27/05/2025

የሽዋ 38ቱ ነገሥታት!

በሽዋ ነገሥታት ጊዜ የኢትዮጵያ የግዛት ክልል ቀይ ባሕር፣ የአደን ባሕረ ሰላጤ፣ ሕንድ ውቅያኖስ እና ላይ ኛው የአባይ ሸለቆ /ነጭ አባይ/ እንደሚያዋስኑት የታወቀ ሲሆን፤ በውስጧ ያሉት የእስልምናና የክርስትና እንዲሁም የሌሎች ሃይማኖት ተከታይ ሕዝቦች በማዕከላዊው መንግሥት ስር ተጠቃለው የሚተዳደሩ፣ ነገር ግን ላለመገብርና ራስ ገዝ ለመሆን የንጉሥ ነገሥት መንግሥቱን ሲወጉ የነበሩ አሉ።

በሽዋ ነገሥታት የነገሡት ስምና ዓ. ም👇

1/ አፄ ይኩኑ አምላክ (ከ1253_1268 ዓ. ም)

2/ አፄ አግብዓ ጽዮን (ከ1268_1277)

3/ አፄ ፅንፈ አርዕድ (ከ1277_1278)

4/ አፄ ሕዝበ አሠግድ (ከ1278_1279)

5/ አፄ ቅድመ አሠግድ (ከ1279_1280)

6/ አፄ ጃን አሠግድ (ከ1280_1281)

7/ አፄ ስበዓ አሠግድ (ከ1281_1282)

8/ አፄ ውድም አርዕድ (ከ1282_1297)

9/ አፄ ዓምደ ጽዮን 1ኛ (ከ1297_1327)

10/ አፄ ሰይፈ አርዕድ (ከ1327_1355)

11/ አፄ ውድም አስፈሬ (ከ1355_1365)

12/ አፄ ዳዊት (ከ1365_1395)

13/ አፄ ቴዎድሮስ 1ኛ (ከ1395_1399)

14/ አፄ ይስሐቅ (ከ1399_1414)

15/ አፄ እስክንድያስ (እስክንድር) (ከ1414_1414 በወራት ነው የነገሠው)

16/ አፄ ሕዝብናኝ (ከ1414_1418)

17/ አፄ በድልናኝ (ከ1418_1419)

18/ አፄ ዓምደ እያሱ "ዳዊት" (ከ1419_1426)

19/ አፄ ዘርዓ ያዕቆብ (ከ1426_1460)

20/ አፄ በእደ ማርያም (ከ1460_1470)

21/ አፄ እስክንድር (ከ1470_1486)

22/ አፄ ዓምደ ጽዮን 1ኛ (ከ1486_1487)

23/ አፄ ናኦድ (ከ1487_1500)

24/ አፄ ልብነ ድንግል (ከ1500_1532)

25/ አፄ ገላውዲዎስ (ከ1532_1551)

26/ አፄ ሚናስ (ከ1551_1555 ዓ. ም)

በሸዋ ብቻ ንጉሥ የሆኑ ናቸው እኒህ:- አቤቶ ያዕቆቦች ይባላሉ!🥰

27/ አቤቶ ያዕቆብ

28/ አቤቶ ሥግው ቃል

29/ አቤቶ ነጋሲ(ነጋሲ ክርስቶስ)

30/ አቤቶ ስብስቴ(ሰብስቲያኖስ)

31/ መርድ አዝማች አብየ

32/ መርድ አዝማች አምሀየስ (አመኃ ኢየሱስ)

33/ መርድ አዝማች አስፋ ወሰን

34/ መርድ አዝማች ወሰን ሰገድ

35/ ንጉሥ ሣህለ ስላሴ

36/ ንጉሥ ኀይለ መለኮት

እንደገና ሙሉ ኢትዮጵያን ያስተዳደሩ!

37/ ንጉሠ ነገሥት ዘኢትዮጵያ አፄ ምኒልክ (እምዬ)

38/ ንጉሠ ነገሥት አፄ ኃይለ ሥላሴ (ጃንሆይ)

ጥይት በጀበርና _ ዝናር ተንተርሶ፣
ሽዋ ሰው ይሰራል _ እንደ እግዜር አፍርሶ።

✍️ Abreham Amelework Demeke

❝እኔ ኢትዮጵያዊያንን አላምንም ከራሴ ጀምሮ። በጭንብል ተሸፍነን የምንኖር ህዝቦች ነን። ለሰው የምናሳየው ገፅታና እውነተኛው ባህሪያችን የተለያዩ ናቸው። እንደ ተረታችን ፣ ስነ ፅሁፋችንና ን...
28/03/2025

❝እኔ ኢትዮጵያዊያንን አላምንም ከራሴ ጀምሮ። በጭንብል ተሸፍነን የምንኖር ህዝቦች ነን። ለሰው የምናሳየው ገፅታና እውነተኛው ባህሪያችን የተለያዩ ናቸው። እንደ ተረታችን ፣ ስነ ፅሁፋችንና ንግግራችን ባህርያችንም ሰምና ወርቅ ነው ...❞
**
❝በዚህ ላይ ደግሞ ክፉውና በጎውን ነገር አንዱን ከሌላው ለይተን የምናይበት መለኪያ የለንም ፤ የማንኛውም ነገር መሠረታዊ መለኪያችን የግል ጥቅማችን ነው። ለዚህም ነው ተንኮል የሚበዛው፤ መተማመን የሌለው፤ የወዳጅነት ወይም የጓደኝነት ትርጉሙ የማይታወቀው ፤ ሀሜት አሉባልታና እርስ በዕርስ መበላላት የሚበዛው። ኢትዮጵያዊያን ስንባል የምናውቀው መርህ አንድ ብቻ ነው ፤ የግል ጥቅም! ከራስ በላይ ነፋስ ፤ እኔ ከሞትኩ ሰርዶ አይብቀል... ሰውን ማመን ቀብሮ ፥ ይሉታል ከነተረቱ። የሚያሳዝን ነው...❞
**
❝ለግል ጥቅማችን የሚበጅ ከሆነ እንዋሻለን። ስንዋሽ ህሊናችንን ቅንጣት ታህል አይቆረቁረንም። እንዴት አድርጎ ለግል ጥቅም የተገዛ ህሊና ሊቆረቁረው ይችላል ?❞
**

❝ለተንኮል አንመለስም የምንሸርበው ተንኮል ጓደኛን፤ ወዳጅን ፤ የስጋ ዘመድን አይለይም ቅናት ባህላችን ነው። ❞
**
❝ምግባር የሚባለውን ነገር በአፍ ካልሆነ በቀር በተግባር አናውቀውም። በአጠቃላይ ክፉውንና በጎውን ለይቶ የሚያይ ህሊና የለንም፤ ያስተማረንም የለም። የተማርነው ነገር ቢኖር በአደባባይ ሰው መስሎ መታየትን ነው፤ ሰው መሳይ በሸንጎ ይሉ የለም? በአደባባይ ሁሉም ጨዋ፣ ልበ ሙሉ፣ ጀግና፣ አትንኩኝ ባይ፣ ኩሩና ቅን፣ በጎ አሳቢና ታማኝ፣ አስተዋይና ትሁት ነው። በአደባባይ የምናጠልቀው ጭንብል ይህ ነው። በግል ኑሮአችን ግን ከስብቅ ፣ ከምቀኝነት ፣ ከተንኮል፣ ከቅናት ፣ ለውሸት፣ ከአሉባልታና ከሀሜት፣ ለግል ጥቅም ለመልከስከስና ለመልፈስፈስ ከፍርሃትና ከአድርባይነት ርቀን አንገኝም። መለያ ባህርያችን ግብዝነት ነው። የግብዝነት ጭንብል አጥልቀን ነው የምንኖረው። ያለ ጭንብል እናስቀይማለን... ወይም እናምራለን፤ አይታወቅም። ያለ ጭንብል ታይተን አናውቅማ!❞

🔸 በዓሉ ግርማ ፥ የቀይ ኮከብ ጥሪ ፥ ገፅ 234

ከነ ሙሉ ክብሩ የሚኖር እንቁ ሰው !! በዘመናት አንዴ የተገኘ !!
16/02/2025

ከነ ሙሉ ክብሩ የሚኖር እንቁ ሰው !! በዘመናት አንዴ የተገኘ !!

ቴዲ አፍሮ እስካሁን ለሐገሩ እና ለሕዝቡ የከፈለው ቢመነዘር ለአስር ትውልድ ይበቃል።ሰወች ከራሳቸው ጋር ሲጋጩ የሚጋጩት ሰው-ቴዲ
08/02/2025

ቴዲ አፍሮ እስካሁን ለሐገሩ እና ለሕዝቡ የከፈለው ቢመነዘር ለአስር ትውልድ ይበቃል።

ሰወች ከራሳቸው ጋር ሲጋጩ የሚጋጩት ሰው-ቴዲ

Dirección

Madrid

Página web

Notificaciones

Sé el primero en enterarse y déjanos enviarle un correo electrónico cuando Debrebirhan Press publique noticias y promociones. Su dirección de correo electrónico no se utilizará para ningún otro fin, y puede darse de baja en cualquier momento.

Contacto La Empresa

Enviar un mensaje a Debrebirhan Press:

Compartir