18/12/2025
የሁለቱ ፍቅረኛሞች ኃኪሞች ህልፈት ከሆስፒታል ከውስጥ የተገኜ ልዩ እና እውነተኛ መረጃ እነሆ !!
ዶ/ር አቤኔዘር ጌታቸው እና ሜሮን ደምሌ በጎንደር ሆሰፒታል በትምህርት እና በስራ ላይ የነበሩ ሲሆን በተቋሙ ውስጥ በነበሩበት ወቅት ፍቅረኛሞች ነበሩ፡፡
የሚያውቋቸው ሁሉ የነበራቸውን መቀራረብ እና መዋደድ ደስ የሚል እንደነበረ ይናገራሉ፡፡ ነገር ግን ዶ/ር ሜሮን ባጋጠማት የማይድን ህመም ምክንያት በተደጋጋሚ ጊዜ ለዶ/ር አቤኔዘር የራሱን ህይወት እንዲኖር እና ህይወቱን እንዲያስተካክል በተደጋጋሚ ስትነግረው እንደነበረ ጓደኞቻቸው ይናገራሉ፡፡
ዶ/ር ሜሮን ለረጅም ጊዜያት በህክምና ብትረዳም ህመሙ ለውጥ ሊያመጣ አለመቻሉ ቢታወቅም በርከት ላሉ ቀናት ሆስፒታል ውስጥ ገብታ ተኝቶ መታከም ሲደረግላት ቢቆይም ለውጥ ሊመጣ አልቻለችም፡፡ ዶ/ር ሜሮን ከ3 ዓመት በላይ የቆየ ህመም Systemic Lupus Erythematosus (SLE) እና (Acute liver failure) ነበረባት። አዲስ አበባ እና የተለያዮ ሆስፒታሎች እና ጎንደር ሆስፒታል ስትታከም ቆይታ ታሕሳስ 3 እንድትተኛ ተደረገ። ዶ/ር አቤኔዘርም በሆስፒታሉ ውስጥ ሲከታተላት እና ሲያሳክማት የቆየ ሲሆን ምሳ ከውጭ አምጥቶ ቀን ከተኛችበት አብልቷት ነበረ፡፡ እገዛ በሚያደርግላት ወቅትም የራሱን ህይወት እንዲመራ እና እንደማትድን ስትነግረው እንደነበር ጓደኞቻቸው ተናግረዋል፡፡
በዚህ ሁኔታ ውስጥ እንዳሉ ዶ/ር አቤኔዘር ከጓደኛው ጋር አምሽቶ ራሴን ስላመመኝ Tramadol ልግዛ ብሎ ከአንድ ጓደኛው ጋር ሂዶ 10 ፍሬ ገዝቶ ገባ፡፡ በእለቱም ማታ ላይ ከእናቱ ጋር ሲያወራ እንዳመሸ ከቤተሰብ ተሰምቷል፡፡ በማግስቱ ከሥራ በመቅረቱ ተደውሎለት ስልክ ባለማንሳቱ አብሮት የተከራየው ዶ/ር አበባው የተባለ ጓደኛው ተደወለለት፡፡ጓደኛውም ቤቱ ሂዶ ክፍሉን ሲያንኳኳ አልከፈት በማለቱ በሩን ከፍቶ ሲገባ ተሸፋፍኖ ተኝቶ ተመለከተው። ሲጠራው አቤት ስላላለው ትከሻውን እየነካ ለመቀስቀስ ሞከረ ስላልነቃለት ብርድ ልብሱን ሲገልጠው አረፋ አየ፤ ከዛ የልብ ትርታውን ሲያዳምጠው እንደሞተ አረጋገጠ፡፡ ደ/ር አበባውም ጉዳዩን ለፖሊስና ለባልደረባዎቹ ነግሮ ፖሊስ እያጣራው ይገኛል፡፡ ሚኒሊክ ሆስፒታልም የአስከሬን ምርመራ ታህሳስ 5 ተደርጎለታል፣ ውጤቱ እየተጠበቀ ነው። አካላዊ ጉዳት ምንም የደረሰበት እንደሌለ ተረጋግጧል፡፡
ዶ/ር ቃልኪዳን ደምሌ (እሕቷ) እና ወ/ሮ የቆየ በዛብህ (እናቷ) እያስታመሟት እያለ ዶር ሜሮን ታህሳስ 6 አረፈች። ቀብሯም ታሕሳስ 8 በትውልድ ቦታዋ ደ/ማርቆስ ከተማ ተፈጽሟል
በዚህ ዘመን በካንሰር፤በኩላሊት፤በጉበት፤ እና በስኳር የሚያልፈው ወገን እየበዛ የመጣ ጊዜ ላይ እንገኛለን፡፡ ነገሮችን በማወቅም ሆነ ባለማወቅ ወዳልሆነ አቅጣጫ ለመውሰድ የሚደረጉ የክፋት ጥንስሶችን ሕብረተሰቡ በአስተውሎት ሊያያቸው ይገባል፡፡
ፈጣሪ ነብሳቸውን በገነት ያኑርልን፡፡