Guge Zuma

Guge Zuma Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Guge Zuma, Digital creator, Adama.

ሁሉም በራሱ ባህል አልባሳት ይዋባሉ🙏ታሪካዊ እውነታው ይህ ነው
28/04/2026

ሁሉም በራሱ ባህል አልባሳት ይዋባሉ🙏
ታሪካዊ እውነታው ይህ ነው

የኮንሶ ዞን ከፍተኛ ፍ/ቤት የሙስና ወንጀል ክስ መዝገብን መርምሮ በተከሳሾች ላይ የመጨረሻ የቅጣት ውሳኔ አስተላለፈ፣‎‎የዞኑ ከፍተኛ ፍ/ቤት በዛሬው ዕለት በዋለው ችሎት ሁለት ተከሳሾች ጥፋ...
27/04/2026

የኮንሶ ዞን ከፍተኛ ፍ/ቤት የሙስና ወንጀል ክስ መዝገብን መርምሮ በተከሳሾች ላይ የመጨረሻ የቅጣት ውሳኔ አስተላለፈ፣

‎የዞኑ ከፍተኛ ፍ/ቤት በዛሬው ዕለት በዋለው ችሎት ሁለት ተከሳሾች ጥፋተኛ በተባሉበት የመንግስትን የሥራ ኃላፊነት በማይመች አኳኋን መምራት እና የሙስና ወንጀል በተሻሻለው የቅጣት አወሳሰን መመሪያ ቁጥር 3/2017 መሠረት ደረጃ የወጣለት መሆኑን ፍ/ቤቱ አስታውቋል።

‎ፍ/ቤቱ የወንጀሉን ድርጊት ፈጽመዋል ያላቸው 1ኛ ተከሳሽ አቶ ዳዊት ገበየሁ ዱባና የዞኑ የቀድሞ ዋና አስተዳዳሪ፤ 2ኛ ተከሳሽ አቶ ገደኖ ካዋይታ በዞኑ ግብርና መምሪያ የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ጽ/ቤት የቀድሞ ኃላፊ ሲሆኑ፤ በመመሪያው አንቀፅ 98(4) እና (5) መሰረት የስልጣን ደረጃቸው መካከለኛ በመሆኑ፣ ተከሳሾቹ ለግል ጥቅማቸው ያዋሉት የመንግስትና የህዝብ ሀብት ብር 3,702,466.67 (ሶስት ሚሊዮን ሰባት መቶ ሁለት ሺህ አራት መቶ ስልሳ ስድስት ብር ከስልስ ሰባት ሳንቲም) የሚገመት መሆኑን፣ የተገኘው ጥቅምና በህዝብ ላይ የደረሰው ጉዳት ከፍተኛ መሆኑን እንደዚሁም ተከሳሾቹ ወንጀሉን የፈፀሙበት ዓላማ ከባድ መሆኑን ግምት ውስጥ በማስገባት ለወንጀሉ ደረጃ አውጥቷል።

‎በዚህም መሠረት ፍ/ቤቱ ተከሳሾቹ እያንዳንዳቸው በ15 ዓመት ጽኑ እስራትና በ50,000 ብር የገንዘብ መቀጮ እንዲቀጡ መነሻ ቅጣት የወሰነ ሲሆን፤ ተከሳሾቹ "የወንጀል ድርጊቱን በጋራ ፈፅመዋል" በሚል ቅጣቱ እንዲከብድ በዐቃበ-ሕግ በኩል የተነሳውን የቅጣት ማክበጃ ተከትሎ ተከሳሾቹ ከዚህ በፊት የስነ-ምግባር ችግር ወይም የወንጀል ሪከርድ የሌላቸው በመሆኑ፣ ሁለቱም የቤተሰብ አስተዳዳሪ በመሆናቸውና ለረዥም ጊዜያት መንግስትንና ህዝብን ያገለገሉ በመሆናቸው፤ በተለይ 1ኛ ተከሳሽ "እምርታ" የተሰኘ የበጎ አድራጎት ማህበር መስራችና ስራ አስኪያጅ የነበሩ መሆናቸውን ግምት ውስጥ በማስገባት ለእያንዳንዳቸው ሶስት ሶስት የቅጣት ማቅለያ ምክንያቶች ቀርበዋል።

‎በዚህም መሠረት 1ኛ ተከሳሽ አቶ ዳዊት ገበየሁ በፖሊስ ቁጥጥር ስር ከዋሉበት ከሰኔ 25 ቀን 2017 ዓ/ም ጀምሮ በ13 ዓመት ጽኑ እስራትና በብር 20,000 (በሃያ ሺህ ብር) የገንዘብ መቀጮ እንዲቀጡ፤ እንደዚሁም 2ኛ ተከሳሽ የሆኑት አቶ ገደኖ ካዋይታ በፖሊስ ቁጥጥር ስር ከዋሉበት ከመስከረም 14 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በ13 ዓመት ጽኑ እስራትና በብር 20,000 (በሃያ ሺህ ብር) የገንዘብ መቀጮ እንዲቀጡ የመጨረሻ የቅጣት ውሳኔ ተላልፏል።

‎በሌላ በኩል ተከሳሾቹ ለግል ጥቅማቸው ያዋሉትን የህዝብ ንብረት የዋጋ ግምት እንዲመልሱ በኢ.ፌ.ዲ.ሪ. የወንጀል ህግ አንቀጽ 101 መሰረት በክስ 2 ስር በፍትሐ ብሔር የተከሰሱበትን ብር 3,702,466.67 (ሶስት ሚሊዮን ሰባት መቶ ሁለት ሺህ አራት መቶ ስልሳ ስድስት ብር ከ ስልስ ሰባት ሳንቲም) ለመንግስት በጋራ እንዲመልሱ ተወስኗል።

‎ይህ በእንዲህ እንዳለ ፍ/ቤቱ 1ኛ ተከሳሽ አቶ ዳዊት ገበየሁ በዚሁ ፍ/ቤት በሌላ የወንጀል መዝገብ ከየካቲት 12 ቀን 2018 ዓ.ም በዋለው ችሎት በ7 ዓመት ጽኑ እስራትና በ5,000 ብር የገንዘብ መቀጮ እንዲቀጡ የተወሰነ ሲሆን፤ ለግል ጥቅማቸው ያዋሉትን ግምቱ ብር 472,500 (አራት መት ሰባ ሁለት ሺህ አምስት መቶ ብር)
‎የሆነ ንብረት ለመንግስት እንዲከፍሉ የተወሰነ በመሆኑ በወ/መ/ህ/ሥ/ሥ/ቁጥር 186 መሰረት ሁለቱም የወንጀል ቅጣቶች ሲደመሩ ተከሳሹ በ20 ዓመት ጽኑ እስራትና በ25,000 ብር የገንዘብ መቀጮ እንዲቀጡ ውሳኔ ተላልፏል።

‎መረጃው
‎የኮንሶ ዞን መንግስት ኮሚኒኬሽን ነው

ትብብር ፓርቲ ኢሕአፓ በሕግ ይጠየቀ አለ‼️ኢህአፓ፣ መኢአድ፣ አማራ ግዮናዊ እና እናት ፓርቲ በመዋሃድ ትብብር በሚል መጠሪያ የጋራ እንቅስቃሴ መጀመራቸው ቢታወቅም፣ በኢህአፓ ግራ የተጋባ አካ...
22/04/2026

ትብብር ፓርቲ ኢሕአፓ በሕግ ይጠየቀ አለ‼️

ኢህአፓ፣ መኢአድ፣ አማራ ግዮናዊ እና እናት ፓርቲ በመዋሃድ ትብብር በሚል መጠሪያ የጋራ እንቅስቃሴ መጀመራቸው ቢታወቅም፣ በኢህአፓ ግራ የተጋባ አካሄድ ምክንያት ጥምረቱ ለከፍተኛ ውጥረት መዳረጉ ተጋለጠ።

የትብብሩ የምርጫ ጉዳዮች ኃላፊ በሰጡት መግለጫ፣ አንዳንድ የኢህአፓ ሰዎች ከጥምረቱ የጋራ አቋም ውጭ አጥር ላይ ተንጠልጥለው የራሳቸውን መግለጫ እየሰጡ መሆኑንና ይህም በሕግ ሊያስጠይቃቸው እንደሚገባ አስታውቀዋል።

ትብብሩን የመሠረቱት ፓርቲዎች በአንድ ዓላማ ለመጓዝ ቢስማሙም፣ የኢህአፓ አመራሮች ግን ግልጽ ያልሆነና የተወላዳ ስልት እየተከተሉ መሆኑ ታውቋል።

22/04/2026
በከበረው ህዝብ ላይ ለጥቅሙ ሲል ክህደት የፈጸመው ቡንካሾ ሀንጌ (ቡንኬ)‎‎👉 ቡንካሾ ሀንጌ በፖለቲካው ገጽታ ውስጥ አወዛጋቢ እና  ለግል ጥቅም አቅጣጫዎችን እያማረጠ ተከታዮቹን የካደ  አስ...
20/03/2026

በከበረው ህዝብ ላይ ለጥቅሙ ሲል ክህደት የፈጸመው ቡንካሾ ሀንጌ (ቡንኬ)

‎👉 ቡንካሾ ሀንጌ በፖለቲካው ገጽታ ውስጥ አወዛጋቢ እና ለግል ጥቅም አቅጣጫዎችን እያማረጠ ተከታዮቹን የካደ አስቸጋሪ ግለሰብ ነው! በለውጡ ጅምር አከባቢ ከባድ የመደመር መንግስት አቀንቃኝ የብልጽግና ደጋፊ ነበር። ይህ ሀቅ ከማንም የራቀ አይደለም። ህዝብን ከቆላ እስከ ደጋ ከ70 ኪ.ሜ ርቀት በባዶ እግሩ ወደ ወረዳ ከተማዎች መተው ብልጽግና (መደመር) እንዲሰብኩ ታምራዊ ድራማ ሰርቷል! በተለይ ለአብነት ገረሴ-ቦንኬ ህዝብን ያላሰራው ድራማ የለም! በተለይ በለውጡ ግዜ ህዝብ በባዶ ሆድ እየተጓዘ መንገድ ላይም አድሮ የሱን ሴራ ሰልፍ ተካፍሏል።

‎👉ህዝቡን ለክፉኛ ያታለለው ይህ ግለሰብ የክቡር መሪያችን የዶ/ር አብይ አህመድ ስዕል ያሉበትን የመደመር ካራባት፣ ቲ-ሸርት፣ ኮፍያ፣ በራሪ ወረቀቶችና መፈክሮችን በርሜል ላይ ወተው 'ገረሴ ዛላ ሜዳ' ላይ በውድ ዋጋ ሸጧል። ግርግር ለቀጣፊ ይመቻል እንደተባለው ብዙ ገንዘብ ከግብረአበሮቹ ጋራ አጭዶ ገብቷል። የገጠሩን ወጣት በባዶ ሆድ ለሳምንታት ከተማ እየጠራ " ማይክ ይዞ በከፍተኛ ድምጽ ተደምረናል በሉ እያለ የቀድሞ አመራሮችን "እነሱ ጽንፈኛ 'ጋዴፓ' ናቸው" በማለት በወጣቱ አስኮንኗል። በአመራሩና በአመራር ዘመድ ላይ ያልተገባ ትንኮሳና ዛቻ አስተባብሯል። ወጣቱ ሰላማዊ ስለሆነ እንጂ እንደ ቡንካሾማ ቢሆን ብዙ ደም ፈሶ ነበር።

‎👉ከግዜ በኋላ በ6ኛው አገራዊ ምርጫ ላይ ይህንን ህዝብ ክዶ ወደ ህወሓት አመራሮች ትግራይ በመሄድ ዳጎስ ያለ ገንዘብ በመቀበል የዶ/ር አብይ መንግስትን ለመቃወም በቅቷል። በምርጫው ግዜ የፖለቲካ ማንነቱን ቀይሮ ስትራቴጂካዊ የጥቅም መረብ በመዘርጋት ተከታዩን ህዝብ በተሰላ ቀመር በማታለል በጅምር ላይ ሲያሳድድ የነበረውን "ጋዴፓ" ፓርቲ መሪ ነኝ ብሎ ለ6ኛው አገራዊ ምርጫ ለመወዳደር ሲቀርብ በሴራ ስራው የተናደደ ህዝብ አንድም ድምጽ ሳይሰጥ በምርጫው ወቅት ከጨዋታ ውጭ አድርጎታል። ክብር ለህዝብ ይሁን ብለን ታዝበን አልፈናል።

‎👉ይሁን እንጂ ከዚህ አወሳሳቢ ድርጊት ትምህርት ያልወሰደው አሁን በ7ኛው አገራዊ ምርጫ የምርጫ ጊዜ በጀት ተጠቃሚ ሱሰኛው አቶ ቡንኬ (ቡንካሾ ሀንጌ) አሁንም መልኩን ቀይሮ በፍጹም ሌላ ፓርቲ መሪ ሆኖ ብቅ ብሏል። ይህ ድንገተኛ ለውጥ ብዙ የመጀመሪያ ደጋፊዎቹን ግራ እንዲጋቡ እና እንዲደናገጡ አድርጓቸዋል። ምናልባት ይህ ለቡንኬ ልምዱ ነው! ብዙም መደንገጥ አያስፈልግም!

‎👉ቡንካሾ ሀንጌን በተለይ የሚያስጨንቀው የሚለዋወጠው ባህርይ ብቻ ሳይሆን ዛሬ አንጠልጥሎ በሚዞረው ቦርሳ ውስጥ የሚከተው የብር መጠንና የግል ጥቅምነው።

‎👉በዚህም እና በብዙ ምክንያት፣ የቡንካሾ የፖለቲካ ጉዞ ወጥነት ማጣትና ዕድል ማጣት ሕዝቡ በሱ ላይ ያለውን እምነት እንዴት ሊሸረሽር እንደሚችል የማስጠንቀቂያ ምሳሌ ሆኖ ያገለግላል።

‎ይቀጥላል!

ጋዴፓ ካይሜ ካይሜ…ጋዴፓ ፓርቲ ሆይ ወዴት ነህ?አንድ ዘመን የጋሞ ሕዝብ ድምፅ ነኝ ብለህ ተነስተህ የነበርህ ፓርቲ፤ ዛሬ ግን የራስህን እሴት ትተህ የሌሎች ፕሮፖጋንዳ አጨብጫቢ ሆነህ ትታያለ...
28/02/2026

ጋዴፓ ካይሜ ካይሜ…

ጋዴፓ ፓርቲ ሆይ ወዴት ነህ?

አንድ ዘመን የጋሞ ሕዝብ ድምፅ ነኝ ብለህ ተነስተህ የነበርህ ፓርቲ፤ ዛሬ ግን የራስህን እሴት ትተህ የሌሎች ፕሮፖጋንዳ አጨብጫቢ ሆነህ ትታያለህ። የጋሞ ሕዝብ የሰላም ተምሳሌትነት፣ የክብር ባህልና የአንድነት መንፈስ እንዲጠነክር ማስተማር ሲገባህ፤ ተመልሰህ የሌሎችን አጀንዳ መደገፍ ጀመርህ።

ጋዴፓ ሆይ፣ የተመሰረትህበትን አላማ አትርሳ። ለጋሞ ሕዝብ ጥቅም ልትቆም ነበር፤ የሕዝብን መብት ልትጠብቅ ነበር፤ የክልሉን ሰላምና ልማት ልትገነባ ነበር። ነገር ግን ዛሬ የምታሳየው እርምጃ ከእነዚህ ፍጹም ተቃራኒ ነው። የጋሞን እሴት ማስተማር ሲችሉ ለፍርፋሪ ለቀማ ራሳቸውን መሸጥ የመረጡ መሪዎች ማፈሪያዎች ናቸው ። ይህ ለሕዝብ ክብር አይገባም!
የፖለቲካ ፓርቲ ታላቅ ሀብት የሕዝብ እምነት ነው። እምነት ግን በአጨብጫቢነት አይገኝም፤ በተግባር እንጂ። ሕዝብ የሚፈልገው ግልፅ አቋም ነው፤ የሚፈልገው የእሴት ቆራጥነት ነው፤ የሚፈልገው ለሕዝብ ጥቅም የማይታጠፍ አመራር ነው። ራስን ለጊዜያዊ ጥቅም መሸጥ ግን የታሪክ እፍረት ነው።

ጋዴፓ ካይሜ ካይሜ ማለት አሁን አይደል?

ዛሬ ጊዜው የመምረጥ ጊዜ ነው፤ በእሴት ላይ መቆም ወይስ በጥቅም ላይ መውደቅ? ታሪክ ተመዝግቧል፤ ሕዝብ ይፈርዳል!

ድንቅ ክስተት ከጋሞ ሰማይ ስር — የሰላም ምልክት በመድረኩ ላይ ታየዛሬ በጋሞ ዞን በተካሄደው የየጋሞ ዞን ባህል፣ ቅርስ ጥበቃ እና ክብካቤ ማህበር ምስረታ ማጠቃለያ ሥነ-ስርዓት ላይ አስደና...
18/02/2026

ድንቅ ክስተት ከጋሞ ሰማይ ስር — የሰላም ምልክት በመድረኩ ላይ ታየ

ዛሬ በጋሞ ዞን በተካሄደው የየጋሞ ዞን ባህል፣ ቅርስ ጥበቃ እና ክብካቤ ማህበር ምስረታ ማጠቃለያ ሥነ-ስርዓት ላይ አስደናቂ ክስተት ተመዝግቧል።

የጋሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዶ/ር ደምሴ አድማሱ መድረኩ ላይ ማጠቃለያ ንግግር በሚያቀርቡበት ወቅት፣ በአናታቸው ላይ እርግብ በማረፍ ተሳታፊዎችን በግርምት አስደነቀች። በተለይም እርግብ እንደ ሰላም ምልክት በሚታወቀው ባህላዊ እና መንፈሳዊ ትርጉም መሠረት፣ የተገኙት እንግዶች ይህን ክስተት “የጋሞ ሰላምነት እና ተባባሪነት ምልክት” እውነታነቱ ምስክር ነው ሲሉ ብለዋልለ።

ሥነ-ስርዓቱ በባህላዊ ዝግጅቶች፣ በቅርስ አቀራረብ እና በማህበራዊ ቃል-ኪዳኖች የተቀናጀ ሲሆን፣ ክስተቱ የቀኑን ትርጉም በልዩ መልኩ አጠናክሮታል። በተሳታፊዎች አስተያየት፣ ይህ ድንቅ ክስተት አዲሱ ማህበር ለባህልና ቅርስ ጥበቃ የሚያደርገውን ጉዞ በሰላምና በተስፋ እንዲጀምር የሚያመለክት መሆኑ ተጠቅሷል።

ከጋሞ ሰማይ ስር የታየው ይህ ምልክታዊ ክስተት ለብዙዎች የማይረሳ ታሪካዊ ቀን ሆኖ ተቀምጧል።

ለጋሞ ህዝብ ካለው ንቀት የተነሳ እስካሁን ይቅርታ መጠየቅ አልፈለገም Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)  ገጹን unfollow እና ሪፖርት በማድረግ የጋሞ ህዝብ አንድነቱን ሊያሳይ ይ...
11/02/2026

ለጋሞ ህዝብ ካለው ንቀት የተነሳ እስካሁን ይቅርታ መጠየቅ አልፈለገም Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) ገጹን unfollow እና ሪፖርት በማድረግ የጋሞ ህዝብ አንድነቱን ሊያሳይ ይገባል!!!!

04/02/2026

ለ300 ክፍለ ዘመናት ስካሄድ የነበረውን Atlantic slave trade ተሳታፊ ያልሆነች ብቸኛው ብሔር ጋሞ መሆን ታሪክ ያስረዳል።

Address

Adama

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Guge Zuma posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share