
26/08/2025
በክልሉ ያለው ፍትሓዊነት ጥያቄ ይህንን ይመስላል፡፡
በዲላ ክላስተር ያለውን አደረጃጀት፣ የምዝበራ እና ዝርፊያ ቡድን መመልከት በቂ ነው፡፡ ይህንን ይዞ ወደ ክልል ለመግባት ነው እያሰፈሰፉ ያሉት
አቶ ገብረመስቀል ጫላ ወደ ፓርቲ አመራርነት ከመጡ ወዲህ ዶክተር መርሁን በምክትል ር/መስተዳድር ማዕረግ የዝርፊያ እና ሠራ ቡድኑን እየመሩ በርካታ የዘረፋ እና የመዝበራ ተግባር በማከናወን ላይ ይገኘል፡፡
ለዚህም የሚሆነውን የዝምበራ አሰላለፍ የክልሉ ግብርና ቢሮ ውስት የፋይናንስ ዘርፍ፣ ንብረት አስተዳደር፣ ኦዲተር እና አጽዳቂ ቡድን ከወላይታ በማደራጀት ሌሎችን አፈናቅለው በምትካቸው በውክልና በማስከመጥ እየሰሩ ይገኛሉ፡፡
አስቀድመን በክልሉ ግብርና ቢሮ ያለውን የአመራር አሰላለፍ እንመልከት
• የቢሮ ኃላፊና ምክትል ር/መስተዳድር ዶክተር መርሁን
• የቀድሞ ወላይታ ዞን ዋና አስተዳደሪዎቹ ጰጥሮስ ወልደማሪያም ቡናና ቅመማቅመም፣
• ሳሙኤል ፎላ ደግሞ ህብረት ስራ ኮሚሽነር
• አቶ አድማሱ አወቀ የእርሻ ዘርፍ ኃላፊ
• አቶ ማርቆስ ዘውገ ምክትልና የፋይናንስና አስተዳደር ዘርፍ ኃላፊ
• የእንስሳት ጤና ግብኣት አቅርቦት ዘርፍ ዶ/ር አዲሱ ኢዮብ
ሆነው በአንድ ቢሮ ውስጥ ማናጅመንትም፣ ፋይናንስም ኦዲተርም ሆነው ከማገልገል በተጨማሪ በቢሮው ውስጥ ከወላይታ ውጪ የሆኑ ዳይሬክክሬቶችን ላይ የሚፈጽሙትን ኢፍትሃዊነት ቀጥለን እንመልከት፡፡
ወ/ሮ አያልነሽ የተባለች LFSDP እንስሳት እና አሳ ሴክተር ሚደግፍ በ100 ሚሊዮን የሚቆጠር ሃብት የሚያንቀሳቅስ ፕሮጀክት አስተባባሪ ናት፡፡
ይህቺ ሴት በዘርፉ በቦታው ረጅም ዓመት የሰራችና በወላይታ፣ ጌዴኦ፣ ደቡብ ኦሞ፣ ጋሞ እና ጎፈ ፍትሃዊ በሆነ መንገድ ድንቅ ተግባራትን ስታከናውን ነበረች፡፡
ደ/ር መርሁን በምክትል ር/መስተዳድር ማዕረግ ሆኖ ከመጣ ወዲህ የፕሮጀክት አስተባባሪዋን በማንሳፈፍ በምትኳ የወላይታ ተወላጁን ዶ/ር አዲሱን ፈራሚ በማድረግ በክልሉ የዓሳ ዝርያ ለማሻሻል እና ምርማነት ለማረጋገጥ የተመደበውን በጀት ለባለውለታው ገብረመስቀል ጫላ፣ ፍሬዜር እና መሰል ሙሰኛ ስራ አስፈጻሚዎች በየሳምንቱ አበል በማመላለስ እና በዕቃ ግዢ መልክ ሚሊዮን ብር እያጓዙ ነው፡፡
የዘረፋ ቡድኑ ደቡብ ኦሞ፣ ጎፋ፣ ጋሞ እና ጌዴኦ የተጀመሩ የእንስሳት ማሻሻያ ፕሮጀክት እና የመንግስት በጀት በማጠፍ እቃ ተገዝቷል እያሉ ለግል ጥቅማቸው እያዋሉ ሲሆን በተለይ ለጡት አባቱ አቶ ገብረመስቀል ጫላ ከተለያዩ ፕሮጀክቶች የነዳጅና አበል በሳምንት 200 ሺህ ብር እየተላከለት ይገኛል፡፡ ይህንንም አድርሰው ከእጅ መንሻ ጋር የሚሰጡት ቡድኖች ከቢሮው አበልና ነዳጅ ተሞልቶላቸው ነው፡፡
ለዚህ ምዝበራ ከለላ የሚሰጠውን የወላይታ ሰው ኦዲተር አድርጎ በውክልና ሰጥቷል፡፡ በተመሳሳይም ንብረት ተገዝተዋል እያሉ ባዶ ሰነድ ላይ እንዲፈርም ሲያስገድዱት አሻፈረኝ ያለውን አቶ አምባዬ የተባለ የዳውሮ ዞን ተወላጅ በማንሳት በምትኩ ወላይታ ተወላጅ አቶ ግርማን አስቀምጠው ዝርፊያውን አጧጥፈውታል፡፡
ይህ ለወላይታ ህዝብ የልማት ጥያቄ ደንታ የለለው የአረካ ማፊያ ቡድን በተደራጀበት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ቢሮ ከወላይታ ውጪ አንድም ባለሙያ በዳይሬክቶሬት ደረጃ የለም፡፡
አንድ ፋይናንስ ላይ እየሰራ የሚገኘውን ከወላይታ ብሐር ውጪ የሆነ ግለሰብን የስም ማትፋት ዘመቻ በማድረግ የወላይታ ተወላጅ ለመተካት አሰፍስፈው እየሰሩ ነው፡፡
በሹመት የተቀመጡ የጋሞ እና ሌሎች ብሔር ተወላጆችን በቢሮው ኃላፊ ቀጥተኛ ጣልቃ ገብነት እና የስርቆት ሰንሰለት ከስራ ውጪ አድርጓል፡፡
ርዕሰመስተዳድር ለመሆን የሚደረገው ሩጫ ምን እና በምን መልኩ እንደሆነ ተመልክታችኋል።
እውነት ያሸንፋል!