ARSI POST

ARSI POST ፖለቲካዊ ማህበራዊእና ባህለዊ ይዘቶች በስፋት የሚዘገብበት ከእውነት እና ከተበዳይ ህዝብ ጎን የሚቆም የህዝብ አይን የህዝብ ጆሮ የህዝብ ድምፅ ነው !!!

ይድረስ ለኢትዮዽያ ህዝብአንድ አንድ መረጃዎች እንደሚያመላክቱን በትምህርት ደረጃቸው ብቁ ያልሆኑ የጤና ባለሞያዎች አላግባብ በሆነ መንገድ ከጤና ጣቢያ ወደ ትልልቅ ሆስፒታል ተዘዋውረው እንዲሰ...
20/05/2025

ይድረስ ለኢትዮዽያ ህዝብ

አንድ አንድ መረጃዎች እንደሚያመላክቱን በትምህርት ደረጃቸው ብቁ ያልሆኑ የጤና ባለሞያዎች አላግባብ በሆነ መንገድ ከጤና ጣቢያ ወደ ትልልቅ ሆስፒታል ተዘዋውረው እንዲሰሩ እየተደረጉ እንደሚገኙ ነው።

በዚህ መሀል ለሚፈጠረው የህክምና ስህተት ተጠያቂ የሚሆነው ማነው? አዘዋዋሪው አካል እንዲሁም ተዘዋዋሪው ባለሞያው ነዋ።

የአስተዳደር መግለጫዎች ሆስፒታል ያለምንም መስተጓጐል ስራ ቀጥሏል ይላሉ። የኢትዮዽያ ጤና ተቋሞች አደለም ይሄ ሁላ ባለሞያ ስራ አቁሞ በደህና ጊዜውም መስተጓጐል የወትሮ ልምዱ ነው ። ይሄን ደግሞ ሆስፒታል የታከመ፣ ሰው የጠየቀ ከምንም በላይ ደግሞ ሰው ያስታመመ ያውቀዋል። የውሸት መግለጫውን ለማን እንዳሰቡት ፈጣሪ ይወቀው። ነገሩን ያጤኑትም አይመስል።

የላቤን ላግኝ ፣ ልጆቼን ላስተምር ፣ ተቋሙ ይሟላ ፣ በስራ ቦታዬ ደህንነቴ ይጠበቅልኝ ያለን ባለሞያ ጥያቄ ከመመለስ ይልቅ እንደምትመለከቱት ነገሩን ወዳልተፈለገ አቅጣጫ እየወሰዱትም ይገኛሉ።

የኢትዩዽያ ህዝብ ሆይ በሀገራችሁ በተሟላ ተቋም እና በብቁ የጤና ባለሞያ የመታከም መብት አላችሁ!! በዚህ ሰሞን የጤና ባለሞያ አለ ብሎ የተቀበላችሁ ማንኛውም የመንግስት ሆስፒታል ውስጥ የሚሰራ ማንኛውም የጤና ባለሞያ አቅጣጫ እንኳን በቅጡ ማመላከት ካልቻለ “ለመሆኑ እዚህ ነው የምትሰራው?” ብለህ ጠይቀው ። አካባቢህ ላለ ሌላ የሆስፒታል ተጠቃሚም አሳውቅ ። የጤና ባለሞያውን አሰራር እና ተግባር በህብረት በማድፈጥ ተከታተሉ። ለሚፈጠር ማንኛውም የህክምና ስህተት ተጠያቂ ይሆናልና የፎቶም መረጃ ያዙ!!

ስነምግባር ጠፍቷልና ብቻህን አትጋፈጥ። አብሮህ ካለው ሰው ጋር በህብረት ተረጋግተህ መብትህን ጠይቅ። በሆስፒታል ጥበቃም አካላዊ እርምጃ ከተወሰደ የቪዲዮ ማስረጃ ሰብስቡ!!

ለተፈጠረባችሁ እንግልት ከልብ እናዝናለን። ከፈጣሪ ጋር በቅርብ ጊዜ በተሻሻለ የህክምና ስርዐት ዳግመኛ እንገናኛለን!!

Share Share Share‼️

©️EHPM
BBC News Amharic ARSI POST

ዜና ሹመት  | የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ ለ23 ካቢኔ አባላት ሹመት ሰጡ።ርዕሰ መስተዳድሩ የካቢኔ አባላት ሹመት የሰጡት የክልሉ ምክር ቤት በቀን 13/12/...
31/08/2023

ዜና ሹመት

| የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ ለ23 ካቢኔ አባላት ሹመት ሰጡ።

ርዕሰ መስተዳድሩ የካቢኔ አባላት ሹመት የሰጡት የክልሉ ምክር ቤት በቀን 13/12/2015 ባካሄደው መስራች ጉባኤ በተሰጠው ውክልና መሰረት ትላንት ማምሻውን የካቢኔ አባላትን ሹመት ሰጥቷል።

በዚህም መሰረት:-

1 አቶ አክሊሉ ለማ የትራንስፖርት እና መንገድ ልማት ቢሮ ኃላፊ
2 አቶ ቢረጋ ብርሃኑ የኢንተርፕራይዝ ልማትና ሥራ ዕ/ፈ/ ቢሮ ኃላፊ
3 ወ/ሮ ካሰች ኤልያስ የሴቶችና ህፃናት ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ
4 ዶ/ር እንዳልካቸው ጌታቸው ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ
5 ዶ/ር ቦጋለ ቦሼ የፕላን ቢሮ ኃላፊ
6 አቶ ብርሃኑ ዘውዴ የከተማና እና መሠረተ ልማት ቢሮ ኃላፊ
7 ወ/ሮ አለምነሽ ደመቀ የገቢዎች ቢሮ ኃላፊ
8 አቶ ግዛቴ ጊጄ የደንና አካባቢ ጥበቃ ልማት ቢሮ ኃላፊ
9 ዶ/ር ዋኖ ዋሎሌ የሠራተኛ እና ማህበራዊ ጉዳዮች ቢሮ ኃላፊ
10 አቶ ሀ/ማሪያም ተስፋዬ የግብርና ቢሮ ኃላፊ
11 አቶ አብዩት ደምሴ የቴክኒካና ሙያ ትምህርት ሥልጠና ቢሮ ኃላፊ
12 አቶ ተፈሪ አባተ የፋይናንስ ቢሮ ኃላፊ
13 አቶ ታረቀኝ ሀብቴ የመስኖና ቆላማ አከባቢ ልማት ቢሮ ኃላፊ
14 አቶ ንጋቱ ዳንሳ የፐቢሊክ ሠርቪስ እና ሰዉ ሃብት ልማት ቢሮ ኃላፊ
15 አቶ ተካልኝ ጋሎ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ቢሮ ኃላፊ
16 አቶ አቤነዘር ተረፈ የፍትህ ቢሮ ኃላፊ
17 አቶ ገለቦ ጎልቶሞ ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ ኃላፊ
18 ዶ/ር ኦንጋዬ ኦዳ የኢንቨስትመንት ቢሮ ኃላፊ
19 ወ/ሮ ሰናይት ሰለሞን የመንግሥት ኮሚዩኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ
20 አቶ አርሻሎ አርካል የወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ኃላፊ
21 ወ/ሪት ፍሬህይወት ዱባለ የባህልና ቱሪዝም ቢሮ ኃላፊ
22 አቶ እንዳሻው ሽብሩ የጤና ቢሮ ኃላፊ
23 አቶ ወገኔ ብዙነህ የሠላምና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ

ሆነው ተሹመዋል።

መረጃው የክልሉ መንግስት ኮ/ጉ/ቢሮ ነው

የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ምክትል ቴክኒክ ዳይሬክተር ከአውስትራሊያ ሳትመለስ ቀረች።የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የቴክኒክ ክፍል ምክትል ቴክኒክ ዳይሬክተር እና የሴቶች ልማት ባለሙያ ...
29/08/2023

የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ምክትል ቴክኒክ ዳይሬክተር ከአውስትራሊያ ሳትመለስ ቀረች።

የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የቴክኒክ ክፍል ምክትል ቴክኒክ ዳይሬክተር እና የሴቶች ልማት ባለሙያ አልማዝ ፍስሀ አውስትራሊያ መጥፏቷ ታውቋል።

ለትርታ ስፖርት ውስጥ አዋቂዎች ባደረሱት መረጃ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት አቶ ኢሳያስ ጅራ ፣ የጽ/ቤት ሀላፊው አቶ ባህሩ ጥላሁን እና የሴቶች ልማት ባለሙያዋ አልማዝ ፍስሀ ከሴቶች የአለም ዋንጫ ፍፃሜ ጋር ተያይዞ ወደ አውስትራሊያ ተጉዘው እንደነበር ይታወሳል።

ይሁን እንጂ የፌዴሬሽኑ ምክትል ቴክኒክ ዳይሬክተር እና የሴቶች ልማት ባለሙያ አልማዝ ፍስሀ ይህንን አጋጣሚ በመጠቀም አውስትራሊያ መቅረቷ ታውቋል። ከዚህ ቀደም ባለሙያዋ በፌዴሬሽኑ እገዳ ተጥሎባት እንደነበርና በደል ተፈፅሞብኛል ማለቷ አይዘነጋም። በፌዴሬሽኑ ወደ አሜሪካ ተጉዞ የነበረው የቀድሞው ቴክኒክ ዳይሬክተር ቴዎድሮስ ፍራንኮ፣ እንዲሁም በአሜሪካ የብሄራዊ ቡድን ጉዞ ወቅት ትጥቅ ያዥ እና የቡድኑ ወጌሻ መጥፋታቸው ይታወሳል።

ምንጭ፦ ትርታ ስፖርት

ኡጋንዳ "የሞቱ ምዕራባውያን" ልብስ ሀገር ውስጥ እንዳይገባ እግድ ጣለችየኡጋንዳው ፕሬዝደንት ዮሪ ሙሰቨኒ የሀገር ውስጥ የጨርቃጨርቅ ኢንዱስትሪዎችን እድገት ያቀጭጫሉ ያሏቸውን "የሞቱ ምዕራባ...
27/08/2023

ኡጋንዳ "የሞቱ ምዕራባውያን" ልብስ ሀገር ውስጥ እንዳይገባ እግድ ጣለች

የኡጋንዳው ፕሬዝደንት ዮሪ ሙሰቨኒ የሀገር ውስጥ የጨርቃጨርቅ ኢንዱስትሪዎችን እድገት ያቀጭጫሉ ያሏቸውን "የሞቱ ምዕራባውያን" ልብሶች ወደ ሀገር ውስጥ እንዳይገቡ እገዳ ጥለዋል።

ኡጋንዳ ከፍተኛ መጠን ያለው ያገለገለ ልብስ ስታስገባ የቆየች ሲሆን የዋጋ ቅናሽ ስላላቸው በተወሰኑ በተጠቃሚዎች ዘንድ ተመራጭ ናቸው።

ፕሬዝደንት ሙሰቨኒ"እነዚህ ለሞቱ ሰዎች የሚሆኑ ናቸው። ነጭ ሰው በሚሞትበት ጊዜ፣ ልብሶቹን ይሰበስቡና ወደ አፍሪካ ይልኳቸዋል" ሲሉ ተናግረዋል።

የቫግነር አዛዥ የቭጌኒ ፕሪጎዢን በሞት ጥላ ሥር ነበር?   | ባለፈው ሰኔ ወር በሞስኮ ላይ ወታደራዊ አመጽ ካካሄደ ጀምሮ የቭጌኒ ፕሪጎዢን በሩሲያውያን ዘንድ በቅርቡ ሟች እንደሆነ ተደርጎ ...
26/08/2023

የቫግነር አዛዥ የቭጌኒ ፕሪጎዢን በሞት ጥላ ሥር ነበር?

| ባለፈው ሰኔ ወር በሞስኮ ላይ ወታደራዊ አመጽ ካካሄደ ጀምሮ የቭጌኒ ፕሪጎዢን በሩሲያውያን ዘንድ በቅርቡ ሟች እንደሆነ ተደርጎ ይገለጽ ነበር።

በቅጥረኛ ቡድኑ መሪ በሕይወት የመቆያ ጊዜን በተመለከተ አስተያየት የሰጡት የአሜሪካው የስለላው ተቋም (ሲአይኤ) ዳይሬክተር ዊሊያም በርንስ “እኔ ፕሪጎዢንን ብሆን ኖሮ፣ የምግብ ቀማሸን አላቃጥልም ነበር” ብለዋል የፑቲን የቀድሞ ምግብ አብሳይ (ሼፍ) የነበረው ፕሪጎዢን ሊገደል እንደሚችል በመጠቆም።

ፕሪጎዢን ተሳፍሮበት የነበረው አውሮፕላን ተከስክሶ ሕይወቱ ማለፉ የተነገረውም ዳይሬክተሩ አስተያየቱን ከሰጡ ከአንድ ወር በኋላ ነው።

ፕሪጎዢንን ያሳፈረው አውሮፕላን በበረራ ላይ እያለ እንዲከሰከስ መደረጉ ሆነ ተብሎ በክሬምሊን የተፈፀመ በቀል መሆኑ ከተረጋገጠም ክስተቱን በሩሲያ ታሪክ የተፈፀመ “ልዩ የሆነ ወታደራዊ ኦፕሬሽን” ያደርገዋል።

የቀድሞው ፍርደኛ፣ ምግብ አብሳይ (ሼፍ) የነበረው እና በኋላ ላይ የቅጥረኛ ወታደሮች አዛዥ የነበረው ፕሪጎዢን፣ በቫግነር ቅጥረኛ ጦር ውስጥ እና ከዚያም ባሻገር በርካታ አድናቂዎች ነበሩት።

ከሁለት ወር በፊት ለ24 ሰዓታት ብቻ ለቆየው አመጽ ወደ ደቡባዊ የሩሲያ ከተማ ሮስቶቭ ኦን ዶን ሲያቀና ሕዝቡ ያደረገለትን ደማቅ አቀባበል በርካቶች ተመልክተዋል።

ይሁን እንጂ በሞስኮ በርታ ባላንጣዎች ነበሩት። ይህም በተደጋጋሚ እና በግልጽ ትችት ሲሰነዘርባቸው በነበሩት በሩሲያ ጦር የላይኛው የሥልጣን እርከን ላይ ባሉ ባለሥልጣናት በይበልጥ ታይቷል።

ፕሪጎዢንን ለሞት ለዳረገው ስህተት ያበቃውም እንደ አውሮፓውያኑ ሰኔ 23 በሞስኮ ላይ አመጹን ሲያስነሳ የፕሬዝዳንት ፑቲንን ቀይ መስመር መተላለፉ ሊሆን እንደሚችል ተነግሯል።

በዚያን ወቅት ፕሪጎዢን ምንም እንኳን ፑቲንን በስም ባይጠቅስም ሩሲያ የካቲት 2022 ላይ በዩክሬን ላይ ለከፈተችው ወረራ በይፋ የተሰጡትን ምክንያቶች በመተቸት ክሬምሊንን አስቆጥቷል።

ሩሲያውያን እንደተታለሉ እና በደካማ አመራር ምክንያት ልጆቻቸው በዩክሬን ጦርነት እየሞቱ እንደሆነ ተናግሮ ነበር።

ይህም በሩሲያ ባለሥልጣናት ዘንድ ቁጣን የፈጠረ ሲሆን ፑቲን የዚያኑ ዕለት ያስተላለፉት የቪዲዮ መልዕክትም መራር ነበር።

ፑቲን በመልዕክታቸው ፕሪጎዢን በሞስኮ ላይ ያስነሳውን አመጽ “ክህደት እና ከጀርባ እንደመወጋት ነው” ብለውታል።

ቭላድሚር ፑቲን ደግሞ በባህሪያቸው ከሃዲዎችንም ሆነ ተቃዋሚዎቻቸውን ይቅር የሚሉ ሰው አይደሉም።

ከዚህ ቀደም የቀድሞው የሩሲያ የደኅንነት መኮንን የነበረው እና ኋላ ላይ ተቃዋሚ የሆነው አሌክሳንደር ሊትቪኔንኮ፣ ፖሎኒየም 210 በተባለ ራዲዮአክቲቭ ከተመረዘ በኋላ በሕመም ሲሰቃይ ቆይቶ በ2006 በለንደን ሆስፒታል ሕይወቱ አልፏል።

በእርሱ ላይ የተካሄደው ምርመራም ከሩሲያ መንግሥት ቤተ ሙከራ የወጣ ነው የተባለ አደገኛ የተባለውን ንጥረ ነገር ነፍሰ ገዳዮች ከሩሲያ በማምጣት እንደመረዙት ድምዳሜ ላይ ደርሷል።

ይሁን እንጂ ሞስኮ በጉዳዩ ላይ እጇ እንደሌለበት የገለጸች ሲሆን፣ ሁለቱ ተጠርጣሪዎች ለፍርድ እንዲቀርቡ ለማድረግ አልፈቀደችም።

ከዚያም የሩሲያ ደኅንነት ኤጀንሲ የቀድሞ መኮንን እና በኋላ ላይ ከድቶ ዩናይትድ ኪንግደም የነበረው ሰርጌይ ስክሪፓል እንደ አውሮፓውያኑ 2018 ከሴት ልጁ ዩሊያ ጋር ለጥቂት ከሞት ተርፈዋል።

በሩሲያ ውስጥም ተቺዎችን እና ባለሃብቶችን ጨምሮ የሞት ጽዋን በድንገት የተጎነጩ ጥቂቶች አይደሉም። በአንዳንድ ሁኔታዎችም ከፎቅ ላይ በመውደቅ ሕይወታቸው ያለፉ ሰዎችም አሉ።

ፕሬዝዳንት ፑቲን ተቀናቃኝ

አቶ አረጋ ከበደ * የአማራ ክልል ርእሰ መሥተዳድር ሆነው ተሾሙ የአማራ ክልል ምክር ቤት 6ኛ ዙር፤ 2ኛ ዓመት የሥራ ዘመን፤ 1ኛ አስቸኳይ ጉባኤ በባሕር ዳር እየተካሄደ ነው፡፡ ምክር ቤቱ ...
25/08/2023

አቶ አረጋ ከበደ

* የአማራ ክልል ርእሰ መሥተዳድር ሆነው ተሾሙ

የአማራ ክልል ምክር ቤት 6ኛ ዙር፤ 2ኛ ዓመት የሥራ ዘመን፤ 1ኛ አስቸኳይ ጉባኤ በባሕር ዳር እየተካሄደ ነው፡፡

ምክር ቤቱ የክልሉን ወቅታዊ የፀጥታ ሁኔታ ማዕከል አድርጎ ሲመክር ውሏል፡፡ ከውይይቱ በኋላ በክልሉ ወጥ የሆነ ሪፎርም ተግባራዊ ማድረግ እንደሆነ የጋራ መግባባት ላይ ደርሷል፡፡

የክልሉ ርእሰ መስተዳድር ይልቃል ከፋለ (ዶ.ር) ያቀረቡትን የመልቀቂያ ጥያቄ የተቀበለው ምክር ቤቱ በምትካቸው አቶ አረጋ ከበደን የክልሉ ርእሰ መሥተዳድር በማድረግ ሹሟል፡፡

“የጥይት እሩምታ በላያችን ላይ አርከፈከፉብን” ወደ ሳዑዲ ለመግባት የሞከሩ ኢትዮጵያውያን----------------------------------------------------------------...
25/08/2023

“የጥይት እሩምታ በላያችን ላይ አርከፈከፉብን” ወደ ሳዑዲ ለመግባት የሞከሩ ኢትዮጵያውያን
------------------------------------------------------------------------------------------------------
“በተደጋጋሚ ተኮሱብን። መቼም ቢሆን በማላስበው መንገድ የተገደሉ ሰዎች አይቻለሁ። በስፍራው 30 ሰዎች ሲገደሉ ተመለከትኩ። አንዲት ቋጥኝ ድንጋይ ስር ተኝቼ ተደበቅኩኝ። ሰዎች በዙሪያዬ የተኙ መስሎም ተሰማኝ። የተኙ የመሰሉኝ ሰዎች አስከሬኖች እንደሆኑ ያወቅኩት ቆይቼ ነው። ስነቃም ብቻዬን ነበርኩ” በማለት ከሳዑዲ የድንበር ጠባቂዎች ግድያ ያመለጠች የ14 ዓመቷ ታዳጊ ሃምዲያ ተናግራለች።
የሃምዲያ ታሪክ ሂዩማን ራይትስ ዋች ባወጣው ከየመን ወደ ሳዑዲ አረቢያ ለማቋረጥ ሲሞክሩ በሳዑዲ ድንበር ጠባቂዎች በጅምላ የተገደሉ ኢትዮጵያውያን ስደተኞችን አሰቃቂ ሁኔታ በያዘው ሪፖርት ውስጥ ተካቷል።
ተቋሙ በመቶዎች የሚቆጠሩ በአብዛኛው ኢትዮጵያውያን ስደተኞች ላይ የተፈጸመውን የጅምላ ግድያ በሰብዓዊነት ላይ የሚፈጸም ወንጀል እንደሆነም ባወጣው ዘርዘር ያለ ሪፖርት ጠቅሷል።
ስደተኞቹ በጦርነት እየታመሰች ካለችው የመን ወደ ሳዑዲያ አረቢያ ሊያቋርጡ ሲሞክሩ ነው በጠባቂዎቹ በአስከፊ ሁኔታ እንደተገደሉ የሰፈረው።
ስደተኞቹ ለቢቢሲ እንደተናገሩት በተተኮሰባቸው ጥይት ቆስለው እግራቸው የተቆረጡ እንዲሁም አስከሬኖች በመንገድ ላይ ተረፍርፍርፈው ማየታቸውን ነው።
ሳዑዲ አረቢያ እነዚህን ስልታዊ ግድያዎች መፈጸማቸውን አስመልክቶ ከዚህ ቀደም በሰጠችው ምላሽ ውድቅ አድርጋ ነበር።
ሂውማን ራይትስ ዋች የጅምላ ግድያውን የያዘውን ሪፖርት ‘ዘይ ፋየርድ ኦን አስ ላይክ ሬይን’ “ጥይት እንደ ዝናብ በላያችን ላይ አዘነቡብን’ የሚል ርዕስ ሰጥቶታል።
ሪፖርቱ የመን ከሳዑዲ አረቢያ ጋር በምትዋሰንበት ድንበር ላይ የሳዑዲ ፖሊስ እና ወታደሮች ጥይት እና ተቀጣጣይ ፈንጂዎችን ጭምር በመጠቀም በጅምላ በአሰቃቂ ሁኔታ እንደገደሏቸው የስደተኞችን ምስክርነት ይዟል።
ቢቢሲ ያናገራቸው ስደተኞችም ወደ ሳዑዲ ለመሻገር የሞከሩ በአብዛኛው ኢትዮጵያውያን ስደተኞች የነበሩበትን አሸባሪ ሁኔታ ተናግረዋል። ሴቶች እና ህጻናትም በቅርብ ርቀት በጥይት ተተኩሶባቸው ተገድለዋል።
“ተኩስ አያባራም፣ ዝም ብሎ ይተኮስ ነበር” ሲል የ21 ዓመቱ ሙስጠፋ ሶፊያ መሐመድ ለቢቢሲ ተናግሯል።
እሱን ጨምሮ 45 ስደተኞች ባለፈው ዓመት ሐምሌ ወር ላይ ድንበሩን ተሻግረው ወደ ሳዑዲ ለመግባት የሞከሩ ሲሆን የተወሰኑትም መገደላቸውን ያስረዳል።
“እንደተተኮሰብኝ እንኳን አላስተዋልኩም። ነገር ግን ለመራመድ ስሞክር እግሬ የለም” ሲልም ተናግሯል።
ለሦስት ወራት ያህል ጥምን፣ ረሃብን፣ መታረዝን፣ ድካምን ተቋቁመው ነበር እዚህ የደረሱት።
ይባስ ብሎም በየመን እና ኢትዮጵያውያን ሕገወጥ አዘዋዋወሪዎች እጅ ስቃይ እና መከራም አይተዋል።
BBC News Amharic

የዋግነር ቡድን መሪ የቭጌኒ ፕሪጎዢን እና የቡድን አጋሮቹ በአውሮፕላን አደጋ ህይወታቸው ማለፉ ተሰማ     በሩሲያ የሚገኘው የዋግነር ቡድን መሪ የቭጌኒ ፕሪጎዢን እና የቡድን አጋሮቹ በአውሮ...
25/08/2023

የዋግነር ቡድን መሪ የቭጌኒ ፕሪጎዢን እና የቡድን አጋሮቹ በአውሮፕላን አደጋ ህይወታቸው ማለፉ ተሰማ

በሩሲያ የሚገኘው የዋግነር ቡድን መሪ የቭጌኒ ፕሪጎዢን እና የቡድን አጋሮቹ በአውሮፐላን አደጋ ህይወታቸው ማለፉን መገናኛ ብዘሁን እየዘገቡ ነው፡፡

የሩሲያ አቪየሽን ባለስልጣናትን ጠቅሶ ቢቢሲ እንደዘገበው የታጣቂው ዋግነር ቡድን መሪው የቭጌኒ ፕሪዢንን ጨምሮ 10 የቡድንኑ አባላት የያዘች የግል አውሮፕላን በምዕራብ ሩሲያ ኩዙኪኖ በተባለች መንደር አቅራቢያ ተከስክሳለች፡፡

የሩሲያ ባለስልጣናት የተከሰተውን የአውሮፕላን አደጋ ምክንያት ለማወቅ ምርምራ መጀመራቸውም ተገልጿል፡፡

በአካባቢው የነበሩ የአይን እማኞች ÷ በአካባቢው ሁለት የፍንዳታ ድምፅ መስማታቸውን እና የ’ቅጥረኛ ተዋጊ ቡድኑን’ አባላት የያዘችው አውሮፕላን ከፍንዳታው በኋላ መከስከሷን ለቢቢሲ አስረድተዋል፡፡

ይሁን እንጅ የዋግነር ቡድን አባላትን በያዘቸው አውሮፕላን ላይ ጥቃት ተፈፅሟል ለማለት በቂ ማስረጃ የለም ነው የተባለው።

ፕሪጎዢን ለመጨረሻ ጊዜ በአፍሪካ ውስጥ በውል ባልታወቀ አንድ ቦታ ላይ እንደሚገኝ በተንቀሳቃሽ ምስል ታይቶ እንደነበር ቢቢሲ በዘገባው አስታውሷል፡፡

በ19ኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና አሸናፊ አትሌቶች ስንት ይከፈላቸዋል? | በሃንጋሪ ቡዳፔስት እየተካሄደ ባለው የ19ው የዓለም የአትሌቲክስ ሻምፒዮና ለአትሌቶች በግለሰብ እና በቡድን ደረ...
25/08/2023

በ19ኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና አሸናፊ አትሌቶች ስንት ይከፈላቸዋል?

| በሃንጋሪ ቡዳፔስት እየተካሄደ ባለው የ19ው የዓለም የአትሌቲክስ ሻምፒዮና ለአትሌቶች በግለሰብ እና በቡድን ደረጃ የሚከፈለው የገንዘብ ሽልማት ከዚህ ቀደም ከነበሩት የተሻለ መሆኑን ነው የወርልድ አትሌቲክስ መረጃ የሚያመለክተው፡፡

በሻምፒዮናው በግልም ሆነ በቡድን ከ1 እስከ 8 የሚወጡ አትሌቶች ሽልማት ይበረከትላቸዋል፡፡

ከዚህ በተጨማሪም የዓለም ክብረ ወሰን ለሰበረ/ች አትሌት ተጨማሪ ሽልማት ይበረከታል፡፡

በሻምፒያናው በግል አሸናፊ ለሆኑ
• ለ1ኛ ደረጃ 70 ሺህ የአሜሪካ ዶላር
• ለ2ኛ ደረጃ 35 ሺህ የአሜሪካ ዶላር
• ለ3ኛ ደረጃ 22 ሺህ የአሜሪካ ዶላር
• ለ4ኛ ደረጃ 16 ሺህ የአሜሪካ ዶላር
• ለ5ኛ ደረጃ 11 ሺህ የአሜሪካ ዶላር
• ለ6ኛ ደረጃ 7 ሺህ የአሜሪካ ዶላር
• ለ7ኛ ደረጃ 6 ሺህ የአሜሪካ ዶላር
• ለ8ኛ ደረጃ 5 ሺህ የአሜሪካ ዶላር

በሻምፒያናው በቡድን አሸናፊ ለሆኑ

• ለ1ኛ ደረጃ 80 ሺህ የአሜሪካ ዶላር
• ለ2ኛ ደረጃ 40 ሺህ የአሜሪካ ዶላር
• ለ3ኛ ደረጃ 20 ሺህ የአሜሪካ ዶላር
• ለ4ኛ ደረጃ 16 ሺህ የአሜሪካ ዶላር
• ለ5ኛ ደረጃ 12 ሺህ የአሜሪካ ዶላር
• ለ6ኛ ደረጃ 8 ሺህ የአሜሪካ ዶላር
• ለ7ኛ ደረጃ 6 ሺህ የአሜሪካ ዶላር
• ለ8ኛ ደረጃ 4 ሺህ የአሜሪካ ዶላር

በተጨማሪም የዓለም ክብረ ወሰን ለሰበረ/ች አትሌት ተጨማሪ አንድ መቶ ሺህ ዶላር እንደሚበረከት ተገልጿል፡፡

የከተማ አስተዳደሩ የተለያዩ የአመራር ሽግሽግ በማድረግ አዳዲስ ሹመቶችን እና ምደባ ሰጠ   | የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በ2015 ባደረገው ግምገማ የተገኙ ውጤታማ ጥንካሬዎችንና ድክመቶ...
24/08/2023

የከተማ አስተዳደሩ የተለያዩ የአመራር ሽግሽግ በማድረግ አዳዲስ ሹመቶችን እና ምደባ ሰጠ

| የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በ2015 ባደረገው ግምገማ የተገኙ ውጤታማ ጥንካሬዎችንና ድክመቶችን መለየቱን አስታውቋል::

ከዚህም በመነሳት ጠንካራ ስራዎቹን የበለጠ ለማላቅ ፣ የተቋማት ሪፎርምን አጠናክሮ ለማስቀጠል እና ብልሹ አሰራሮችን ለማረም ከከተማ እስከ ወረዳ 280 አመራሮችንና 5442 የመንግስት ሰራተኞችን ተጠያቂ ማድረጉን ገልጿል::

በሌላ በኩል የከተማ አስተዳደሩ የተለያዩ የአመራር ሽግሽግ ያደረገ ሲሆን አዳዲስ ሹመቶችን እና ምደባም ሰጥቷል::

በዚህም መሰረት በከተማ ማዕከል ደረጃ የተሰጡ ሹመቶች:-

1. አቶ ሲሳይ ጌታቸው ኦበራ - የመሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ

2. ወ/ሮ ልዕልቲ ግደይ ረዳ - በቢሮ ኃላፊ ደረጃ የህብረት ስራ ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር

3. ወ/ሮ ሙሉእመቤት ታደሰ ረታ- በቢሮ ኃላፊ ደረጃ የምግብና መድሃኒት አስተዳደርና ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር

4. ወ/ሮ ሽታዬ መሃመድ አህመድ- በቢሮ ኃላፊ ደረጃ የምገባ ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር

5. አውራሪስ ከበደ በቀለ- የግንባታ ፈቃድና ቁጥጥር ባለስልጣን

6. ዶ/ር ኢ/ር እሸታየሁ ክንፉ ተስፋዬ- በቢሮ ኃላፊ ደረጃ የስትራቴጂክ ፕሮግራሞች ማኔጅመንት ጽ/ቤት ኃላፊ

7. አቶ በላይ ታደለ ዞዴ- በቢሮ ኃላፊ ደረጃ የከንቲባ የፕሮጀክቶች ክትትል አማካሪ

8. አቶ ተስፋዬ ኦሜጋ ፋልታሞ- በቢሮ ኃላፊ ደረጃ የስፖርት ትምህርትና ስልጠና ዘርፍ ኃላፊ

9. አቶ ሞላ ንጉስ ፈንታቢል - በቢሮ ኃላፊ ደረጃ የአፈ ጉባኤ አማካሪ

10. አቶ ተክሌ ዲዶ ሙራስ- በቢሮ ኃላፊ ደረጃ የአፈጉባኤ የህግ አማካሪ

11. አቶ መላኩ ታምሩ ተሰማ- በቢሮ ኃላፊ ደረጃ በፐብሊክ ሰርቪስ የሰው ሃብት ልማትና አስተዳደር ዘርፍ ኃላፊ

12. ወ/ሮ ፍቅርተ አበራ መኮንን- በቢሮ ኃላፊ ደረጃ የፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሃብት አስተዳደር ቢሮ የማስፈፀም አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ

13. አቶ ከበደ ካሳ ማሞ- በቢሮ ኃላፊ ደረጃ የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማዕከል የስትራቴጂክ ስራ አመራር ዘርፍ አስተባባሪ

14. ዶ/ር ሚኤሳ ኤሌማ ሮቤ- በቢሮ ኃላፊ ደረጃ የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማዕከል የኮሙኒኬሽን ዘርፍ አስተባባሪ

15. አቶ ሃፍታይ ገ/እግዚአብሄር አለማየሁ- በቢሮ ኃላፊ ደረጃ የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማዕከል የዴሞክራሲ ባህል ዘርፍ አስተባባሪ

16. ወ/ሮ ጸዳለች ሚካኤል አደም- በቢሮ ኃላፊ ደረጃ የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማዕከል የሃብት አስተዳደር ዘርፍ አስተባባሪ

17. አቶ ዳርዳር ብርሃኑ ወልደአብ- በቢሮ ኃላፊ ደረጃ የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማዕከል የልዩ ፅ/ቤት ኃላፊ

18. አቶ ሚደቅሳ ከበደ ዳዲ- የሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ ምክትል ኃላፊ

19. ወ/ሮ ታጋይቱ አባቡ ወርቂ- በትምህርት ቢሮ ስርዓተ ትምህርት ዘርፍ ምክትል ኃላፊ

20. አቶ ደስታ መርጋ ገረሱ- የመሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ የመሬት ዝግጅትና ማስተላለፍ ዘርፍ ኃላፊ

21. አቶ ሞሊቶ አባይነህ ኢርካሎ- መሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ አገልግሎት ማሻሻል ዘርፍ ኃላፊ

22. አቶ ከድር አደም በዳሶ- የስትራቴጂክ ፕሮግራሞች ማኔጅመንት ጽ/ቤት አማካሪ

የክፍለከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚዎች

1. ወ/ሮ አይዳ አወል- የአዲስከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ

2. አቶ ታረቀኝ ገመቹ ያደታ- የለሚኩራ ክፍለከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ

3. አቶ አበበ ተቀባ ምህረቱ- የአራዳ ክፍለከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ

4. አቶ ወልዴ ወገሴ ናኦ- የጉለሌ ክፍለከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ

ፕላምፒነት1.ፕላምፒነት ማለት፡-ከፍተኛ የሆነ ሀይል ሰጭ ወይም በፕሮቲን የበለፀገ፤ የለውዝ ምርት ላይ ተመስርቶ የተዘጋጀ ሆኖ በውስጡም የተለያዩ ቫይታሚኖች እና ማዕድናት ያሉት ሲሆን በከፍተ...
24/08/2023

ፕላምፒነት

1.ፕላምፒነት ማለት፡-ከፍተኛ የሆነ ሀይል ሰጭ ወይም በፕሮቲን የበለፀገ፤ የለውዝ ምርት ላይ ተመስርቶ የተዘጋጀ ሆኖ በውስጡም የተለያዩ ቫይታሚኖች እና ማዕድናት ያሉት ሲሆን በከፍተኛ ሁኔታ በምግብ እጥረት ለተጎዱ ህፃናት የሚሰጥ የምግብ ምርት ነው፡፡
ፕላምፒነት ጥቅም፡-
1. በከፍተኛ ሁኔታ የምግብ እጥረት ምክንያት ለሚከስት የመቀንጨርና ሌሎች ተያያዥ የጤና ችግሮች የተከስተባቸው ህፃናትን ለማከም እንዲሁም ራህባቸውን ለማስታገስ፣ የክብደት መጠናቸውን ለማሻሻልና ምርቱ ካለው የተመጣጣኑ የምግብ ይዘት አኳያ ህፃናት በፍጥነት ጤናቸውን ለማሻሻል ይረዳል፡፡
ፕላምፒነት ምርትና ስርጭት፡-
1. የምርቱ ምንጮች፡-
1.ኛ፡-ከሀገር ውስጥ አምራች ድርጅቶች
2.ኛ፡- በእርዳታ ከውጭ ሀገር የሚመጣ ሲሆን እነዚህ ምርቶች በአጣዳፊ የምግብ እጥረት የተጎዱ ህፃናትን ለማከም የሚውሉ እንደ ፕላምፒነት፤ RUSF እና RUTF ያሉ አልሚ ምግቦች የተጎዱትን ህፃናት ለማከም የሚውሉ መድሐኒቶች እንጂ ማንኛውም ህብረተሰብ የሚጠቀማቸው ምግቦች አይደሉም፡፡
 ምርቱ በምግብ እጥረት ለተጎዱ ህፃናት የሚቀርበው ሙሉ በሙሉ በነፃ ነው፡፡
 ምርቱን ችግር የሌለባቸው የህብረተሰብ ከፍሎች መጠቀም የለባቸውም፡፡
 ምርቱ በምንም አይነት መንገድ ለሽያጭ አገልግሎት መዋል የለበትም፡፡
ከዚህ ውጭ በሆነ መንገድ ይህን ምርት በገበያ ለሽያጭ ሲያውሉ ቢገኝ በህግ የሚያስጠይቅ ስለሆነ ህብረተስቡም ይህንን አውቆ በሱቅ ውስጥ እና በተለያዩ መንገዶች የሚሸጡት በህገወጥ መንገድ ተሰርቀው በመሆኑ ይህንን ባለመግዛት፤ ባለመሸጥ እና በአቅራቢያው ላሉ ጤና ተቆጣጣሪዎች እና ለህግ አካላት በመጠቆም ምርቱ ለተጎጂ ህጻናት እንዲደርስ እናግዝ፡፡

ዘገባው የኢትዮጽያ ምግብ እና መሀኒት ፈንድ ነው

የዋግነሩ አዛዥ የቨግኒ ፕሪጎዢን ህይወቱ ሳያልፍ እንዳልቀረ ተገለጸየሩሲያው ቅጥረኛ ወታደራዊ ቡድን አዛዥ የቨግኒ ፕሪጎዥን ይጓዙበት የነበር አውሮፕላን ተከስክሷል የተባለ ሲሆን የአዛዡ ህይወ...
23/08/2023

የዋግነሩ አዛዥ የቨግኒ ፕሪጎዢን ህይወቱ ሳያልፍ እንዳልቀረ ተገለጸ

የሩሲያው ቅጥረኛ ወታደራዊ ቡድን አዛዥ የቨግኒ ፕሪጎዥን ይጓዙበት የነበር አውሮፕላን ተከስክሷል የተባለ ሲሆን የአዛዡ ህይወት ሳያልፍ እንዳልቀረ አርቲ ዘግቧል።

አዛዡ ከሌሎች መንገደኞች ጋር በመሆን በግል አውሮፕላን እየተጓዙ እያለ በተፈጠረ አደጋ የሰዎች ህይወት አልፏል ተብሏል።

ፕሪጎዢን ባሳለፍነው ሀምሌ በሩሲያ ጦር ላይ አምጸው የሀገር ክህደት ወንጀል ክስ ተመስርቶባቸው ነበር።

በኋላም ከፕሬዝዳንት ፑቲን ጋር በተደረገ ድርድር ክሱ ውድቅ ሲደረግ አዛዡም ወደ ቤላሩስ መኮብላቸው ይታወሳል።

የቨግኒ ከሰሞኑ አፍሪካን ነጻ እያወጣን ነው ሲሉ አነጋጋሪ ቪዲዮ አሰራጭተው ነበር

Address

Adama

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ARSI POST posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share