ARSI POST

ARSI POST ፖለቲካዊ ማህበራዊእና ባህለዊ ይዘቶች በስፋት የሚዘገብበት ከእውነት እና ከተበዳይ ህዝብ ጎን የሚቆም የህዝብ አይን የህዝብ ጆሮ የህዝብ ድምፅ ነው !!!

እሷ የ24 ዓመት ወጣት ነበረች። ከኮሌጅ ትምህርቷን እንዳጠናቀቀች ነበር።እሱ የ3 ወር ህፃን ነበር። ከአንድ ሆስፒታል ውጪ በካርቶን ሳጥን ውስጥ ተጥሎ የተገኘው እንዲህ ከሚል ማስታወሻ ጋር ...
15/07/2025

እሷ የ24 ዓመት ወጣት ነበረች። ከኮሌጅ ትምህርቷን እንዳጠናቀቀች ነበር።
እሱ የ3 ወር ህፃን ነበር። ከአንድ ሆስፒታል ውጪ በካርቶን ሳጥን ውስጥ ተጥሎ የተገኘው እንዲህ ከሚል ማስታወሻ ጋር ነበር፦
"ይቅርታ አድርጉልኝ። እባካችሁ ውደዱት።"
ማንም ሊወስደው አልመጣም።
ቤተሰብም ሆነ ወገን አልጠየቀውም። ምንም የስልክ ጥሪ አልነበረም... ዝምታ ብቻ።
በዜና ላይ "ህፃኑ ኤልያስ" ብለው ሰየሙት። ነገር ግን ሁሉም ሰው መጨረሻው የመንግስት የህፃናት ማሳደጊያ ውስጥ እንደሚሆን ገምቶ ነበር።
ከእሷ በቀር።
ራሄል እናት የመሆን ምንም እቅድ አልነበራትም። እሷ በሆስፒታሉ የህፃናት ማቆያ ክፍል በበጎ ፈቃደኝነት ታገለግል ነበር።
ነገር ግን ለመጀመሪያ ጊዜ እቅፍ ስታደርገው፣ ጥቃቅን እጆቹ ጣቷን አጥብቀው ያዙና ሊለቋት አልቻሉም።
ልቧም አልለቀቀውም።
የጉዲፈቻ ተቋሙ "ገና ወጣት ነሽ፣ ብቻሽን ነሽ፣ ልምድም የለሽም" አሏት።
እሷም እንዲህ አለቻቸው፦
"ባል ላይኖረኝ ይችላል። ገንዘብም ላይኖረኝ ይችላል። ነገር ግን ፍቅር አለኝ። እሱ ደግሞ ከምንም ነገር በላይ የሚያስፈልገው ይሄንን ነው።"
ኤልያስን በጉዲፈቻ ወሰደችው።
የእሷ ነጭ ቆዳና የእሱ ጠይም ሉጫ ፀጉር የብዙዎችን አይን ይስብ ነበር።
የሰዎችን ሹክሹክታ ትሰማ ነበር፦
"በፍፁም ልጇ አይመስልም!"
"አመት እንኳን አትቆይም።"
"ሲያድግ ይጠላታል።"
ነገር ግን ነፋስና ዝናብ ሲበረታ እንዴት ተጠግቷት ከእቅፏ እንደማይወጣ አላዩም።
ወይም ደግሞ የፒያኖ ትምህርቱን ክፍያ ለመሸፈን ብቻ ሶስት ስራዎችን እንደምትሰራ አላወቁም።
ወይም ለመጀመሪያ ጊዜ "እማዬ" ብሎ ሲጠራት እንዴት በእንባ እንደታጠበችም አላዩም።
ጀግንነትን፣ የመኝታ ሰዓት ታሪኮችን እና ወሰን የሌለውን ፍቅር እየመገበች አሳደገችው።
ዓመታት ነጎዱ።
ኤልያስም ቁመናው ገዝፎ፣ ደግና ብሩህ አዕምሮ ያለው ወጣት ሆነ።
18 ዓመት ሲሞላውም በነፃ የትምህርት ዕድል የሃርቫርድ ዩኒቨርሲቲ ገባ።
በምረቃው የእራት ግብዣ ላይ መድረክ ላይ ወጥቶ እንዲህ አለ፦
"ሰዎች ሁልጊዜ 'እውነተኛ እናትህ ወዴት ናት?' እያሉ ይጠይቁኝ ነበር።
መልሱ ይኸውላችሁ፤ እሷ እዚች ጋር ናት።
ማንም ያልፈለገኝን እኔን የመረጠችኝ ሴት።
ስም፣ ቤትና የወደፊት ተስፋ የሰጠችኝ።
እሷ ምናልባት አልወለደችኝም ይሆናል...
ነገር ግን ህይወቴን አትርፋለች።"
በክፍሉ ውስጥ የነበሩት ሁሉ አለቀሱ።
ራሄልም እንባዋን መቆጣጠር አቃታት።
ኤልያስ ግን ፈገግ ብሎ በጆሮዋ እንዲህ ሲል ሹክ አላት፦
"እማዬ፣ አሁንም እጄን እንደያዝሽልኝ ነው። እኔም በፍፁም አልለቅሽም።"

(ከማሕበራዊ ሚዲያ የተገኘ)

ይድረስ ለኢትዮዽያ ህዝብአንድ አንድ መረጃዎች እንደሚያመላክቱን በትምህርት ደረጃቸው ብቁ ያልሆኑ የጤና ባለሞያዎች አላግባብ በሆነ መንገድ ከጤና ጣቢያ ወደ ትልልቅ ሆስፒታል ተዘዋውረው እንዲሰ...
20/05/2025

ይድረስ ለኢትዮዽያ ህዝብ

አንድ አንድ መረጃዎች እንደሚያመላክቱን በትምህርት ደረጃቸው ብቁ ያልሆኑ የጤና ባለሞያዎች አላግባብ በሆነ መንገድ ከጤና ጣቢያ ወደ ትልልቅ ሆስፒታል ተዘዋውረው እንዲሰሩ እየተደረጉ እንደሚገኙ ነው።

በዚህ መሀል ለሚፈጠረው የህክምና ስህተት ተጠያቂ የሚሆነው ማነው? አዘዋዋሪው አካል እንዲሁም ተዘዋዋሪው ባለሞያው ነዋ።

የአስተዳደር መግለጫዎች ሆስፒታል ያለምንም መስተጓጐል ስራ ቀጥሏል ይላሉ። የኢትዮዽያ ጤና ተቋሞች አደለም ይሄ ሁላ ባለሞያ ስራ አቁሞ በደህና ጊዜውም መስተጓጐል የወትሮ ልምዱ ነው ። ይሄን ደግሞ ሆስፒታል የታከመ፣ ሰው የጠየቀ ከምንም በላይ ደግሞ ሰው ያስታመመ ያውቀዋል። የውሸት መግለጫውን ለማን እንዳሰቡት ፈጣሪ ይወቀው። ነገሩን ያጤኑትም አይመስል።

የላቤን ላግኝ ፣ ልጆቼን ላስተምር ፣ ተቋሙ ይሟላ ፣ በስራ ቦታዬ ደህንነቴ ይጠበቅልኝ ያለን ባለሞያ ጥያቄ ከመመለስ ይልቅ እንደምትመለከቱት ነገሩን ወዳልተፈለገ አቅጣጫ እየወሰዱትም ይገኛሉ።

የኢትዩዽያ ህዝብ ሆይ በሀገራችሁ በተሟላ ተቋም እና በብቁ የጤና ባለሞያ የመታከም መብት አላችሁ!! በዚህ ሰሞን የጤና ባለሞያ አለ ብሎ የተቀበላችሁ ማንኛውም የመንግስት ሆስፒታል ውስጥ የሚሰራ ማንኛውም የጤና ባለሞያ አቅጣጫ እንኳን በቅጡ ማመላከት ካልቻለ “ለመሆኑ እዚህ ነው የምትሰራው?” ብለህ ጠይቀው ። አካባቢህ ላለ ሌላ የሆስፒታል ተጠቃሚም አሳውቅ ። የጤና ባለሞያውን አሰራር እና ተግባር በህብረት በማድፈጥ ተከታተሉ። ለሚፈጠር ማንኛውም የህክምና ስህተት ተጠያቂ ይሆናልና የፎቶም መረጃ ያዙ!!

ስነምግባር ጠፍቷልና ብቻህን አትጋፈጥ። አብሮህ ካለው ሰው ጋር በህብረት ተረጋግተህ መብትህን ጠይቅ። በሆስፒታል ጥበቃም አካላዊ እርምጃ ከተወሰደ የቪዲዮ ማስረጃ ሰብስቡ!!

ለተፈጠረባችሁ እንግልት ከልብ እናዝናለን። ከፈጣሪ ጋር በቅርብ ጊዜ በተሻሻለ የህክምና ስርዐት ዳግመኛ እንገናኛለን!!

Share Share Share‼️

©️EHPM
BBC News Amharic ARSI POST

Address

Adama

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ARSI POST posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share