ዓለም ከተማ ፖስት /Alem ketema's post

ዓለም ከተማ   ፖስት /Alem ketema's post Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from ዓለም ከተማ ፖስት /Alem ketema's post, News & Media Website, Adama.

18/03/2025

የመኑ ታጣቂ ቡድን ሃውቲ በአሜሪካ የጦር መርከብ ላይ ጥቃት መፈጸሙን ገለጸ።

ጥቃቱ 53 የመናውያን ለሞቱበት የቅዳሜው የአሜሪካ የአየር ድብደባ አጻፋ መሆኑንም ነው ያስታወቀው።

በኢራን ድጋፍ እንደሚደረግለት የሚታመነው ሃውቲ ባወጣው መግለጫ በቀይ ባህር በምትገኘውና አውሮፕላን ተሸካሚዋ "ዩኤስኤስ ሃሪ ቱርማን" መርከብ ላይ በ24 ስአት ውስጥ ሁለት ጊዜ ጥቃት ማድረሱን ጠቁሟል።

ቡድኑ በመርከቧ ላይ ጥቃት ለማድረስ 18 ሚሳኤሎችና ድሮኖች መጠቀሙን ያስታወቀ ሲሆን፥ ዋሽንግተንም በየመን የአየር ጥቃቷን መቀጠሏ ተገልጿል።

ተጨማሪ ያንብቡ፦ https://bit.ly/4bv1tb7

15/03/2025

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት(ተመድ) ባለሙያዎች እስራኤል በጋዛው ጦርነት ወቅት የሴቶችን የጤና ተቋማት በስልት በማውደም በፍልስጤማውያን ላይ የዘር ማጥፋት ተግባር ማካሄዷንና ጾታዊ ጥቃትን እንደጦርነት ስትራተጂ መጠቀሟን በትናንትናው እለት ባወጡት ሪፖርት ገልጸዋል።

የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታኔያሁ "እድሎአዊና ጸረ-ጽዮናዊ" ነው በማለት የሪፖርቱን ግኝት ውድቅ አድርገውታል።

" ተመድ ሽብርተኛው ሀማስ በፈጸማችው በሰብዓዊነት ላይ የተፈጸሙ ወንጀሎችና የጦር ወንጀሎች ላይ ከማተኮር ይልቅ እስራኤል በሀሰተኛ ክስ በድጋሚ ማጥቃትን መርጧል" ብለዋል ኔታንያሁ ባወጡት መግለጫ።

"የእስራኤል ባለስልጣናት የወሊድ መጠንን ለመቀነስ ያለሙ ክልከላዎችን በመጣል ጭምር የፍልስጤማውያንን የወሊድ አቅም በማዳከም በሮም ስታቱና በጀኖሳይድ ኮንቬንሽን የዘር ማጥፋት ተግባር ውስጥ አንዱ የሆነውን ተግባር ፈጽመዋል" ሲል ምስራቅ እየሩሳሌምንና እስራኤልን ጨምሮ በእስራኤል በተወረሩ ቦታዎች ላይ ምርመራ ያደረገው የተመድ ነጻ አለምአቀፍ ኮሚሽን በሪፖርቱ ገልጿል።

https://bit.ly/43J3BtJ

01/03/2025
እቴጌ ጣይቱ  - ብርሃን ዘኢትዮጵያ በውጫሌ ውል ጣሊያን አምታች ቋንቋ በመጠቀም ኢትዮጵያን ቀኝ ለመግዛት እየተዘጋጀች መሆኑ እንዲታወቅ እና ውሉ ፈርሶ ኢትዮጵያ ለማይቀረው ጦርነት እንድትዘጋ...
28/02/2025

እቴጌ ጣይቱ - ብርሃን ዘኢትዮጵያ

በውጫሌ ውል ጣሊያን አምታች ቋንቋ በመጠቀም ኢትዮጵያን ቀኝ ለመግዛት እየተዘጋጀች መሆኑ እንዲታወቅ እና ውሉ ፈርሶ ኢትዮጵያ ለማይቀረው ጦርነት እንድትዘጋጅ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ካበረከቱ ግለሰቦች መካከል እቴጌ ጣይቱ ብጡል ዋና እንደነበሩ ታሪክ ይናገራል፡፡ በወቅቱ እቴጌ ጣይቱ የሚከተለውን አስደናቂ ንግግር አድርገው ነበር፡፡

"እኔ ሴት ነኝ ጦርነት አልወድም፡፡ ግን እንዲህ ዓይነቱን ውል ከምቀበል ጦርነትን እመርጣለሁ። . . . የዛሬ ሳምንትም አድርገው፤ በዚህ ለአንተ የሚደነግጥ የለም። ሂድ የፎከርክበትን አሁኑኑ አድርገው። እኛም የመጣውን እንመልሰዋለን። እግሩን ለጠጠር ደረቱን ለጦር ሰጥቶ ሀገሩን የሚያድን ሰው የሌለ እንዳይመስልህ። ደሙን አፍስሶ ለሀገር መሞት ጌጥ ነው እንጂ ሞት አይባልም።"

እቴጌ ጣይቱ በድንቅ ንግግራቸው እንደገለጹትም ጣሊያን ኢትዮጵያን በወረረች ጊዜ እሳቸውን ጨምሮ “እግሩን ለጠጠር ደረቱን ለጦር” ለመስጠት የተዘጋጀ ሕዝብ ዓድዋ ድረስ ዘምቶ የሀገሩን ነጻነት እና አንድነት አስጠብቆ በድል ተመልሷል፡፡

24/12/2024
የመጀመሪያ ዙር የቻን አፍሪካ ዋንጫ ማጣርያውን በሊቢያ ያደረገው የኢትዮጵያ ብሄራዊ ብድን በሱዳን አቻው ሁለት ለ ባዶ በሆነ ውጤት ተሸንፏል ።የመልስ ጨዋታውም እሮብ ታህሳስ 16 የሚደረግ ይ...
23/12/2024

የመጀመሪያ ዙር የቻን አፍሪካ ዋንጫ ማጣርያውን በሊቢያ ያደረገው የኢትዮጵያ ብሄራዊ ብድን በሱዳን አቻው ሁለት ለ ባዶ በሆነ ውጤት ተሸንፏል ።
የመልስ ጨዋታውም እሮብ ታህሳስ 16 የሚደረግ ይሆናል

Address

Adama

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ዓለም ከተማ ፖስት /Alem ketema's post posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share