ዓለም ከተማ ፖስት /Alem ketema's post

ዓለም ከተማ   ፖስት /Alem ketema's post Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from ዓለም ከተማ ፖስት /Alem ketema's post, News & Media Website, Adama.

 ***************************1- ግንቦት 20 ቀን 1946 ዓ.ም ከሐዋርድ ዩኒቨርሲቲ በሕግ የክብር ዶክተሬት ድግሪ2- ግንቦት 25 ቀን 1946 ዓ.ም ከኮሎምቢያ ዩኒቨርሲቲ በ...
25/07/2025


***************************
1- ግንቦት 20 ቀን 1946 ዓ.ም ከሐዋርድ ዩኒቨርሲቲ በሕግ የክብር ዶክተሬት ድግሪ
2- ግንቦት 25 ቀን 1946 ዓ.ም ከኮሎምቢያ ዩኒቨርሲቲ በሕግ
3- ግንቦት 28 ቀን 1946 ዓ.ም ከሞንትሪያል ዩኒቨርሲቲ የክብር ዶክተሬት
4- ግንቦት 30 ቀን 1946 ዓ.ም ከሚቺጋን ዩኒቨርሲቲ የሕግ የክብር ዶክተሬት ድግሪ
5- ግንቦት 1946 ዓ.ም ከመክጊል ዩኒቨርሲቲ የሕግ የክብር ዶክተሬት ድግሪ
6- ሐምሌ 16 ቀን 1946 ዓ.ም ከኬምብሪጅ ዩኒቨርሲቲ የሕግ የክብር ዶክተሬት ድግሪ
7- ሐምሌ 29 ቀን 1946 ዓ.ም ከአቴና ብሔራዊና ካፓዲስትሪን ዩኒቨርሲቲ በፍልስፍና የክብር ዶክተሬት ድግሪ
8- 1946 ዓ.ም አትላንታ ጆርጂያ ከሚገኘው ሞርሐውስ ኮሌጅ የሕግ የክብር ዶክተሬት ድግሪ
9- ጥቅምት 10 ቀን 1947 ዓ.ም ከኢክስፎርድ ዩኒቨርሲቲ የሕግ የክብር ዶክተሬት ድግሪ
10- ከቦን ዩኒቨርሲቲ በእርሻ የክብር ዶክተሬት ድግሪ
11- ሕዳር 4 ቀን 19 49 ዓ.ም ከባናራስ ሂንዱ ዩኒቨርሲቲ የሥነ-ጽሑፍ ዶክተሬት ድግሪ
12- ሐምሌ 5 ቀን 1951 ዓ.ም ከሞስኮ ዩኒቨርሲቲ በሕግ የክብር ዶክተሬት ድግሪ
13- ሐምሌ 8 ቀን 1951 ዓ.ም ከፕራግ ከቻርልስ ዩኒቨርሲቲ በሕግ የዶክተሬት ድግሪ
14- ህዳር 27 ቀን 1952 ዓም ከላይቤሪያ ዩኒቨርሲቲ በሕግ የክብር ዶክተሬት ድግሪ
15- መስከረም 22 ቀን 1956 ዓ.ም ከጆርጅ ታውን ዩኒቨርሲቲ በሥነ-ጽሑፍ የክብር ዶክተሬት ድግሪ
16- መስከረም 18 ቀን 1957 ዓ.ም ከሩማኒያ ከቡካሬስት ዩኒቨርሲቲ የሕግ የክብር ዶክተሬት ድግሪ
17- መስከረም 30 ቀን 1959 ዓ.ም ከሊባኖስ ዩኒቨርሲቲ የሀገሪቱ ፕሬዘዳንት ቻርልስ ሄሉ ባሉበት ክብር ዶክትሬት
18- ሚያዚያ 24 ቀን 1960 ዓ.ም ከታይላንድ ከተማስት ዩኒቨርሲቲ የህግ የክብር ዶክተሬት ድግሪ
19- ግንቦት 9 ቀን 1960 ዓም ከምዕራብ አውስትራሊያ ዩኒቨርሲቲ በሕግ የክብር ዶክተሬት ድግሪ
20- ግንቦት 13 ቀን 1960 ዓም ከደቡብ ኮሪያ ዩኒቨርሲቲ የህግ ዶክሬት ድግሪ
***********

[ በአፍሪካ ብቸኛው ተወዳዳሪያቸው፣ ኔልሰን ማንዴላ ናቸው። አልበርት ኤነስታይን በአጠቃላይ 17 የክብር ዶክትሬቶች ያገኘ ሲሆን፣ ከፍተኛው ቁጥር 32 በዴቪድ አቴንበርግ የተያዘ ነው። ]

( የመረጃ ምንጭ ስብስብ ከአጼ ኃ/ሥላሴ የታሪክ መጻሕፍት )

ድንቅና አስተማሪ አባባሎች!!‎ ================‎1. ‹‹የዘጠኝ ወር እርጉዝ በማግባት በአንድ ወር የራስህን ልጅ ልትወልድ አትችልም›› ‎‎2. ‹‹ዛሬ ዛፍ ጥላ ስር የምንቀመጠው የ...
25/07/2025

ድንቅና አስተማሪ አባባሎች!!
‎ ================
‎1. ‹‹የዘጠኝ ወር እርጉዝ በማግባት በአንድ ወር የራስህን ልጅ ልትወልድ አትችልም››

‎2. ‹‹ዛሬ ዛፍ ጥላ ስር የምንቀመጠው የሆነ ጊዜ ላይ የሆነ ሰው ዛፉን ስለተከለው ነው፡፡››

‎3. ‹‹ዝናህን ለመገንባት ሃያ ዓመት ይወስድብሃል፡፡ ዝናህን ለማበላሸት ግን ሃያ ደቂቃ በቂህ ነው፡፡ ይሄን ጉዳይ ካሰብክ ነገሮችን በተለያየ መንገድ ታከናውናቸዋለህ፡፡››

‎4. ‹‹ባልገባህ ቢዝነስ ላይ ኢንቨስት አታድርግ››

‎5. ‹‹ስጋት ወይም ፈተና የሚመጣው የምትሰራውን ባለማወቅ ነው፡፡››

‎6. ‹‹በአንድ ገቢ ብቻ ጥገኛ አትሁን፡፡ ሁለተኛ የገቢ ምንጭ ፍጠር››

‎7. ‹‹በአሜሪካ ቢዝነስ ቁጭ ብሎ ማሰብ ያልተለመደ ነው፡፡ እኔ ግን ብዙ ጊዚዬን የማጠፋው ቁጭ ብዬ በማሰብ ነው፡፡

‎8. ‹‹በጣም አስፈላጊው ኢንቨስትመንት በራስህ ላይ የምታደርገው ነው፡፡››

‎9. ‹‹የማትፈልገውን የምትገዛ ከሆነ የምትፈልገውን ወዲያው ትሸጣለህ፡፡››

‎10. ‹‹ከመጥፎ ሰው ጋር ጥሩ ውል ማሰር አትችልም፡፡

‎11. ‹‹ደስተኛ ሰዎች የሚደሰቱት ምርጥ ነገር ስላላቸው አይደለም፡፡ እነሱ የሚደሰቱት ያላቸውን ነገር አክብረውና ወደው ስለያዙ ነው፡፡

‎12. ‹‹በመኝታህ ሰዓት ገንዘብ ለማግኘት አስበህ አዲስ መላ ካልፈጠርክ እስክትሞት ትሰራለህ፡፡

‎13. ‹‹አጥፍተህ የቀረህን አትቆጥብ፡፡ ከቁጠባ በኋላ የተረፈህን አጥፋ፡፡››

‎14. ‹‹ብዝሃነት ወይም ሁለገብ ዕውቀት ከመሐይምነት ይከላከላል፡፡

‎15. ‹‹ታማኝነት በጣም ውዱ ስጦታ ነው፡፡ ይሄን ስጦታ ከርካሽ ሰዎች አትጠብቅ፡፡››

‎16. ‹‹ያልተለመደ ከሆነ ሰዎች ብዙ ጊዜ ትክክለኛውን ነገር ከመስራት ሊያስቆሙህ ይሞክራሉ፡፡

‎17. ‹‹በዓለም ላይ ሐይል ያለው ምንም ቅድመ ሁኔታ የሌለው ፍቅር ነው፡፡

‎18. ‹‹ሁልጊዜም ሐብት ማግኛ ምርጡ መንገድ ለራስህ ዋጋ መስጠት ነው፡፡

‎19. ‹‹አነባለሁ፣ አነባለሁ፣ አነባለሁ! በቀን ውስጥ ከአምስት እስከ ስድስት ሰዓት ድረስ አነባለሁ፡፡››

‎20. ‹‹ብዙ በተማርክ ቁጥር ብዙ ታገኛለህ። ››

19/07/2025

🚹?? 🚺🚺

✅ ድንግልናን ከማስወሰድ በላይ ስልክን መሰረቅ በጣም የሚያስቆጭበት ትውልድ

✅ ሴቶች ከHIV ይልቅ እርግዝናን የፈሩበት አስነዋሪ ትውልድ

✅ I Phone መያዝ ተምሮ ከመመረቅ በላይ የሚደሰትበት ትውልድ

✅ ሴቶች እምብርትንና ጡትን በአደባባይ እንደ ከተማ ህንፃ እዩኝ እዩኝ እያሉ ለዲያቢሎስ የተማረኩበት ትውልድ

✅ ፍቅር በዋጋ ሴክስ በነፃ የሆነበት አሳፋሪ ትውልድ

✅ እውነት ተዳፍኖ ውሸትና ክህደት እውነት መስሎ የታየበት አፀያፊ ዘመን

✅ ህዝቡ ከፈጣሪ ይልቅ አሸባሪ ፣ ገዳይና ሌባን የሚፈራበት አስቀያሚ ዘመን

✳ ገንዘብ ከቤተሰብና ከጉደኛ በላይ የተወደደበት ርካሽ ትውልድ

✳ በፍቅረኛ ላይ ሌላ ካልደረቡ "ፋራ" ተብሎ ሰውን
የሚሳደቡበት ትውልድ

✳ ሰው ሞልቶ ተርፎ ብቻን እንዲኖሩ ያስገደደ አሳዛኝ
ዘመን

✳ ለፍቅር መታመን ፣ ለፍቅር መሰደድ ፣ ለፍቅር መሰቃየትና መሞት እንደ ሞባይል game የተቆጠረበት ቅስም ሰባሪ ትውልድ

✳ ባልና ሚስት የማይተማመኑበት መሽቶ ላይነጋ የጨለመ ዘመን

✳ ወንዶች ሱሪን ዝቅ አድርጎ መታጠቅ ስልጣኔ መስሏቸው ለሰይጣን የሰገዱበት የተረገመ ትውልድ

✳ ሴቶች እምብርትንና ጡትን በአደባባይ እንደ ከተማ ህንፃ እዩኝ እዩኝ እያሉ ለዲያቢሎስ የተማረኩበት ትውልድ

✳ አለባበስ ታይቶ የሰውን ማንነት በአብረቅራቂ ነገርና በአይን ብቻ የሚገምት ትውልድ

🙏 ወደ ፈጣሪ ቦታ ሲከድ ስልክና ኤርፎን ይዞ የሚሄድ ትውልድ

ካነበቡ በውሃላ ሼር ያድርጉ፡፡

ፔጁን follow እያረጋችሁ

18/03/2025

የመኑ ታጣቂ ቡድን ሃውቲ በአሜሪካ የጦር መርከብ ላይ ጥቃት መፈጸሙን ገለጸ።

ጥቃቱ 53 የመናውያን ለሞቱበት የቅዳሜው የአሜሪካ የአየር ድብደባ አጻፋ መሆኑንም ነው ያስታወቀው።

በኢራን ድጋፍ እንደሚደረግለት የሚታመነው ሃውቲ ባወጣው መግለጫ በቀይ ባህር በምትገኘውና አውሮፕላን ተሸካሚዋ "ዩኤስኤስ ሃሪ ቱርማን" መርከብ ላይ በ24 ስአት ውስጥ ሁለት ጊዜ ጥቃት ማድረሱን ጠቁሟል።

ቡድኑ በመርከቧ ላይ ጥቃት ለማድረስ 18 ሚሳኤሎችና ድሮኖች መጠቀሙን ያስታወቀ ሲሆን፥ ዋሽንግተንም በየመን የአየር ጥቃቷን መቀጠሏ ተገልጿል።

ተጨማሪ ያንብቡ፦ https://bit.ly/4bv1tb7

15/03/2025

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት(ተመድ) ባለሙያዎች እስራኤል በጋዛው ጦርነት ወቅት የሴቶችን የጤና ተቋማት በስልት በማውደም በፍልስጤማውያን ላይ የዘር ማጥፋት ተግባር ማካሄዷንና ጾታዊ ጥቃትን እንደጦርነት ስትራተጂ መጠቀሟን በትናንትናው እለት ባወጡት ሪፖርት ገልጸዋል።

የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታኔያሁ "እድሎአዊና ጸረ-ጽዮናዊ" ነው በማለት የሪፖርቱን ግኝት ውድቅ አድርገውታል።

" ተመድ ሽብርተኛው ሀማስ በፈጸማችው በሰብዓዊነት ላይ የተፈጸሙ ወንጀሎችና የጦር ወንጀሎች ላይ ከማተኮር ይልቅ እስራኤል በሀሰተኛ ክስ በድጋሚ ማጥቃትን መርጧል" ብለዋል ኔታንያሁ ባወጡት መግለጫ።

"የእስራኤል ባለስልጣናት የወሊድ መጠንን ለመቀነስ ያለሙ ክልከላዎችን በመጣል ጭምር የፍልስጤማውያንን የወሊድ አቅም በማዳከም በሮም ስታቱና በጀኖሳይድ ኮንቬንሽን የዘር ማጥፋት ተግባር ውስጥ አንዱ የሆነውን ተግባር ፈጽመዋል" ሲል ምስራቅ እየሩሳሌምንና እስራኤልን ጨምሮ በእስራኤል በተወረሩ ቦታዎች ላይ ምርመራ ያደረገው የተመድ ነጻ አለምአቀፍ ኮሚሽን በሪፖርቱ ገልጿል።

https://bit.ly/43J3BtJ

01/03/2025
እቴጌ ጣይቱ  - ብርሃን ዘኢትዮጵያ በውጫሌ ውል ጣሊያን አምታች ቋንቋ በመጠቀም ኢትዮጵያን ቀኝ ለመግዛት እየተዘጋጀች መሆኑ እንዲታወቅ እና ውሉ ፈርሶ ኢትዮጵያ ለማይቀረው ጦርነት እንድትዘጋ...
28/02/2025

እቴጌ ጣይቱ - ብርሃን ዘኢትዮጵያ

በውጫሌ ውል ጣሊያን አምታች ቋንቋ በመጠቀም ኢትዮጵያን ቀኝ ለመግዛት እየተዘጋጀች መሆኑ እንዲታወቅ እና ውሉ ፈርሶ ኢትዮጵያ ለማይቀረው ጦርነት እንድትዘጋጅ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ካበረከቱ ግለሰቦች መካከል እቴጌ ጣይቱ ብጡል ዋና እንደነበሩ ታሪክ ይናገራል፡፡ በወቅቱ እቴጌ ጣይቱ የሚከተለውን አስደናቂ ንግግር አድርገው ነበር፡፡

"እኔ ሴት ነኝ ጦርነት አልወድም፡፡ ግን እንዲህ ዓይነቱን ውል ከምቀበል ጦርነትን እመርጣለሁ። . . . የዛሬ ሳምንትም አድርገው፤ በዚህ ለአንተ የሚደነግጥ የለም። ሂድ የፎከርክበትን አሁኑኑ አድርገው። እኛም የመጣውን እንመልሰዋለን። እግሩን ለጠጠር ደረቱን ለጦር ሰጥቶ ሀገሩን የሚያድን ሰው የሌለ እንዳይመስልህ። ደሙን አፍስሶ ለሀገር መሞት ጌጥ ነው እንጂ ሞት አይባልም።"

እቴጌ ጣይቱ በድንቅ ንግግራቸው እንደገለጹትም ጣሊያን ኢትዮጵያን በወረረች ጊዜ እሳቸውን ጨምሮ “እግሩን ለጠጠር ደረቱን ለጦር” ለመስጠት የተዘጋጀ ሕዝብ ዓድዋ ድረስ ዘምቶ የሀገሩን ነጻነት እና አንድነት አስጠብቆ በድል ተመልሷል፡፡

28/02/2025
24/12/2024
የመጀመሪያ ዙር የቻን አፍሪካ ዋንጫ ማጣርያውን በሊቢያ ያደረገው የኢትዮጵያ ብሄራዊ ብድን በሱዳን አቻው ሁለት ለ ባዶ በሆነ ውጤት ተሸንፏል ።የመልስ ጨዋታውም እሮብ ታህሳስ 16 የሚደረግ ይ...
23/12/2024

የመጀመሪያ ዙር የቻን አፍሪካ ዋንጫ ማጣርያውን በሊቢያ ያደረገው የኢትዮጵያ ብሄራዊ ብድን በሱዳን አቻው ሁለት ለ ባዶ በሆነ ውጤት ተሸንፏል ።
የመልስ ጨዋታውም እሮብ ታህሳስ 16 የሚደረግ ይሆናል

Address

Adama

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ዓለም ከተማ ፖስት /Alem ketema's post posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share