Dhugaan ni iyyiti

19/04/2026

ንጉስ ነጃሺ አክሱምና ዉቅሮ
✅✅✅✅✅✅✅✅

በአሕመዲን ጀበል፥ክፍል አንድ
🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴

ይህ ጹሑፍ በትግራይ ጦርነት ጊዜ የነጃሺ መስጂድ ላይ ጥቃት በተፈጸመ ጊዜ ተጽፎ በሦስት ተከታታይ ክፍሎች በኔ በአሕመዲን ጀበል የፌስቡክ ገጽ እእና የግል ፕሮፋይል ላይ በጃኑዋሪ 2፥ 2021 ተለጥፎ ነበር። ዛሬም በድጋሚ ሦስቱ ክፍሎች በተከታታይ ይቀርባል። መልካም ንባብ።

🎁🎁🎁🎁🎁🎁🎁🎁🎁🎁🎁🎁🎁

ነቢዩ (ሶ.ዐ.ወ) በእምነት ነጻነት፣ እጦት ጭቆናና መከራ ከባልደረቦቻቸው መከላከል እንደማይችሉ ሲገነዘቡ ወደ ሐበሻ ምድር እንዲሰደዱ መከሯቸው። እንዲህም አሏቸው፡-

‹‹ወደ ሐበሻ ተሰደዱ፤ በእርሷ አንድ ንጉሥ አለ። ከእርሱ ፊት ማንም ተበዳይ አይሆንም። … (ስለዚህ ተሰደዱ)፤ አላህ ካላችሁበት ሁኔታ አውጥቶ ድል እስክንጎናጸፍ ድረስ…፡፡››(ሙሐመድ ጦይብ ኢብን ሙሐመድ ኢብን ዩሱፍ፣ ኢትዮጵያ እና ኢስላም (ትርጉም)፣ ነጃሺ ማተሚያ ቤት፣ ገጽ 9)

ሰሀቦችም በሁለት ዙር ተሰደው ወደ ኢትዮጵያ-አክሱም መጡ፡፡በንጉስ ነጃሺ ዘንድ ነጻነትን ተጎናጸፉ፡፡ የነቢዩ ሙሐመድ (ሶ.ዐ.ወ) ባልደረቦች በሐበሻ የገጠማቸውን ሁኔታ እንዲህ ሲሉ መስክረዋል፡-

‹‹ሐበሻ ገባን። መልካም ጎረቤቶችንም አገኘን። በሃይማኖታችን ምክንያት የሚደረግብን ተፅእኖ አልነበረም። አላህንም በሰላም መገዛት ጀመርን። አንድም ችግርና መከራ አላጋጠመንም። የምንጠላውን ነገር አልሰማንም።››

(አህመዲን ጀበል፣ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች ከ615-1700 የጭቆናና የትግል ታሪክ፣2003፣ገጽ 35)

መናገሻ ከተማውን አክሱም ከተማ አድርጎ ይመራ የነበረው ንጉስ ነጃሺ በኢስላም ኃይማኖት ታላቅ ስፍራ ከሚሰጣቸው ስብዕናዎች መካከል አንዱ ነው፡፡ ለሙስናና የስጦታ ድለላ ሳይታለል የእምነት ነጻነትን ጨምሮ ሙሉ ነጻነትና ጥገኝነትን ለነቢዩ ሙሐመድን(ሰ.ዐ.ወ) ባልደረቦች በመስጠቱና በኃላ ላይም ኢስላምን ተቀብሎ ኦክቶበር/ኖቬምበር 630 (ረጀብ ወር 9ኛ ዓ.ሂ.) ሲሞት የርሱን ሞት መልዓኩ ጂብሪል ሲነግራቸው ለርሱ ነቢዩ(ሰ.ዐ.ወ) ለሞቱ ሙስሊሞች ላይ የሚሰገደውን ሰላትን ሰግደዋል፡፡

(ኢማሙ ጦበሪ፣ ታሪኽ አል ሩሱል ወል ሙሉክ፣ ጥራዝ 3፣ ገጽ 81፤ ኢብኑ ከሲር፣ አል-ቢዳያ ወኒሃያ፣ ጥራዝ 3፣ ገጽ 99፤ ኢብኑል አሲር፣ አል-ካሚል ፊ ታሪኽ፣ ጥራዝ 1፣ ገጽ 347)

አላህም ንጉሥ ነጃሺ ኢስላምን መቀበሉን በማረጋገጥ የሚከተለውን የቁርኣን አንቀጽ አወረደ፡-

وَإِنَّ مِنْ أَهْلِ الْكِتَابِ لَمَنْ يُؤْمِنُ بِاللَّهِ وَمَا أُنْزِلَ إِلَيْكُمْ وَمَا أُنْزِلَ إِلَيْهِمْ خَاشِعِينَ لِلَّهِ لَا يَشْتَرُونَ بِآيَاتِ اللَّهِ ثَمَنًا قَلِيلًا أُولَئِكَ لَهُمْ أَجْرُهُمْ عِنْدَ رَبِّهِمْ إِنَّ اللَّهَ سَرِيعُ الْحِسَابِ (سورة : آل عمران آية: 199)

ከመጽሐፉ ሰዎች መካከል አላህን ፈሪዎች፣ በአላህ አናቅጽትም ጥቂትን ዋጋ የማይሸምቱ ሆነው በአላህ የሚያምኑ፣ ወደ እናንተ የተወረደውንም ወደነርሱ የተወረደውንም (እውነት የሚቀበሉ) ወገኖች በእርግጥ ይገኛሉ። እነርሱ ከጌታቸው ዘንድ (የላቀ) ምንዳ ተዘጋጅቶላቸዋል። አላህ ምርመራው ፈጣን ነው። (ቁርኣን፣ዓሊ ኢምራን፣ 3፡199)

(ይህ የቁርኣን ጥቅስ የወረደው በነጃሺ ምክንያት መሆኑን በርካታ የኢስላም ሊቃውንት በመጽሐፍቶቻቸው አብራርተዋል። ለምሳሌ፡- ኢብኑ ከሲር፣ ተፍሲር አል ቁርአን አል ዓዚም፣ ጥራዝ 3፣ ገጽ 199፤ ኢማሙ ጦበሪ፣ ጃሚዑል

Iraan Karaa Bishaanii Hormuuz Irra Deebiin CufteMootummaan Iraan karaa bishaanii daldala addunyaatiif murteessaa ta'e, K...
19/04/2026

Iraan Karaa Bishaanii Hormuuz Irra Deebiin Cufte

Mootummaan Iraan karaa bishaanii daldala addunyaatiif murteessaa ta'e, Karaa Hormuuz (Strait of Hormuz), irra deebiin cufuu ishee beeksisteetti.

Tarkaanfiin kun kan fudhatame erga mariin nagaa Paakiistaan, magaalaa Islamaabaaditti adeemsifamaa ture walii-galtee malee xumuramee booda, Ameerikaan uggura bishaanii (Naval Blockade) dooniiwwan Iraan irratti labsite kaasuuf eeyyamtuu dhabuu isheetiin wal qabateeti.
Sababni ijoon Iraan karaa kana irra deebiin akka cuftu taasise tarkaanfii haaloo ba'uuti.

Iraan uggura Ameerikaan dooniiwwan ishee irra keesse akka "cabsa walii-galtee dhukaasa dhaabuutti" waan fudhatteef, hanga uggurri kun guutummaatti hin kaafamnetti, dooniin daldalaa fi boba'aa biyya kamiyyuu karaa Hormuuz akka hin qaxxaamurre dhorkiteetti. Akka gabaasa humna waraanaa Iraanitti (IRGC), tarkaanfiin kun deebii kallattii dhiibbaa dinagdee fi waraanaa Ameerikaa irraa dhufeef kenname dha.

Taateen kun dinagdee addunyaa, keessattuu gabaa boba'aa (Oil Market) irratti jeequmsa guddaa uumeera. Boba'aan addunyaa harki 20% fi gaaziin uumamaa (LNG) harki guddaan karaa kana waan darbuuf, cufamuun Hormuuz gatiin boba'aa akka malee akka dabalu taasisaa jira.

Pirezidaantiin Ameerikaa Donaald Tiraamp gama isaaniin uggurri bishaanii dooniiwwan Iraan irratti godhamu akka itti fufu ibsuun isaanii, waldhabdeen kun dhihootti akka hin qabbanoofne agarsiisa.

dhugaan ni iyyit

17/10/2025
10/10/2025

"የእስላም መንግሥት" ፕሮፓጋንዳ ⁉️
(በዐብዱልጀሊል ሸኽ ዐሊ ካሣ)
★★★//💢//★★★

በሰው ልጆች ታሪክ ውስጥ ታላላቅ ጥፋቶች የሚጀምሩት በጦር መሣሪያ ግጭት ሳይሆን፣ ቃላትን በማጣመም እና የጋራ እውነታን በመሸርሸር ነው። በአማራ ክልል እየተካሄደ ያለው ግጭት፣ ከስሩ ካለው ውስብስብ የፖለቲካ ይዘት ባሻገር፣ የዚህ አደገኛ ክስተት ህያው ማሳያ ሆኗል።

በገልለተኛ አካሎች በተደጋጋሚ በተደረገ ጥናት እና ደታ ስብሰባ የእስላም መንግሥት ትርክት በአማራ ክልል በገጠሩ ማህበረሰብ ውስጥ በሰፊው ይገኛል።

የፌደራል መንግሥትን "የእስላም መንግሥት" ብሎ የሚፈርጀው ፕሮፓጋንዳ፣ ቀላል የፖለቲካ መፈክር ሳይሆን፣ አንድን ማህበረሰብ ከስር መሰረቱ ለመበታተን እና በአናሳው የህብረተሰብ ክፍል ላይ የሚፈጸምን ማንኛውንም ዓይነት ጥቃት ህሊናዊ እና ሞራላዊ ቅቡልነት ያለው ለማድረህ በጥንቃቄ የተቀረጸ ሥነ-ልቦናዊ መሣሪያ ነው።

💢ከፖለቲካ ጥያቄ ወደ ህልውና ስጋት፡ የፕሮፓጋንዳው ስልት

የዚህ ፕሮፓጋንዳ የመጀመሪያው እና ዋነኛው ስኬት፣ የችግሩን ምንነት ከፖለቲካዊ ወደ ኃይማኖታዊ የህልውና ትግል መቀየሩ ነው። በፖለቲካ ሳይንስ "የህልውና ስጋት ፈጠራ" (Securitization Theory ) በመባል የሚታወቀው ይህ ስልት፣ አንድን ጉዳይ ከመደበኛው የፖለቲካ ውይይት እና የህግ ማዕቀፍ አውጥቶ፣ የአገርንና የማንነትን ህልውና የሚፈታተን አጣዳፊ አደጋ አስመስሎ ያቀርባል። "የእስላም መንግሥት" የሚለው ትርክት፣ መንግሥትን ብቻ ሳይሆን እስልምናን ራሱን እንደ ህልውና ስጋት በመፈረጅ፣ ማንኛውም የመንግሥት ተቃውሞ ከእስልምና ስጋት ጋር እንዲያያዝ ያደርጋል።

ይህ ከተሳካ በኋላ፣ ማንኛውም አይነት የመከላከያ እርምጃ፣ የጅምላ እስርን፣ የንብረት ውድመትንና የሰብዓዊ መብት ጥሰትን ጨምሮ፣ ተገቢና አስፈላጊ መስሎ መታየት ይጀምራል። በዚህ በተመረዘ የአስተሳሰብ መስክ ውስጥ፣ በአማራ ክልል የሚኖረው ሲቪል ሙስሊም ዜጋ፣ ከፖለቲካ አቋሙ ተለይቶ፣ "የሥርዓቱ ወኪል" እና የእስልምና ተምሳሌት ተደርጎ ይወሰዳል። በዚህም ምክንያት መስጊዱ "የጠላት ምሽግ"፣ ንግድ ቤቱ "የሴራ ማዕከል"፣ ጎረቤቱ ደግሞ "የውስጥ ባንዳ" ተደርጎ ይፈረጃል።

ይህ የውጭ ስጋት ፈጠራ፣ ከሰው ልጅ ጥልቅ ሥነ-ልቦናዊ ፍላጎት ጋር የተቆራኘ ነው። በማህበራዊ ሳይኮሎጂ "የማህበራዊ ማንነት ንድፈ-ሐሳብ" (Social Identity Theory ) እንደሚያስረዳው፣ ሰዎች ማንነታቸውንና ክብራቸውን ከሚጋሩት "የእኛ" ቡድን ጋር በማያያዝ ይገነባሉ። በቀውስ ወቅት፣ ይህ "የእኛ" የሚለው ስሜት ሲጠናከር፣ ከቡድኑ ውጪ ያሉት "እነሱ" እንደ ባዕድና እንደ ጠላት የመታየት እድላቸው በከፍተኛ ሁኔታ ይሰፋል።

"የእስላም መንግሥት" የሚለው ትርክት፣ "የአማራ ክርስትያን" የሚለውን የጋራ ማንነት በማጠናከር፣ ሙስሊሙን ማህበረሰብ እንደ ታሪካዊና ህልውናዊ ስጋት ያቀርባል። ይህ ሂደት "የውስጠ-ቡድን ወገንተኝነት" (in-group favoritism) እንዲፈጠር በማድረግ፣ በ"እነሱ" ላይ የሚፈጸም ጥቃት፣ ለ"እኛ" ህልውና የሚከፈል መስዋዕትነት እና እንደ ጀግንነት የሚቆጠር የሞራል ተግባር ሆኖ እንዲታይ የአስተሳሰብ ለውጥ ያመጣል። ይህ ዓይነቱ የፖለቲካ ስልት፣ ልሂቃን የፖለቲካና የኢኮኖሚ ጥቅማቸውን ለማስጠበቅ ሲሉ ኃይማኖትን እንደ መሣሪያ በመጠቀም ህዝብን በቀላሉ የሚያሰባስቡበት የ"ኢንስትሩመንታሊዝም" (Instrumentalism ) ጽንሰ-ሀሳብ ዓይነተኛ ማሳያ ነው።

💢የማህበራዊ መዋቅር መፍረስ እና የጥፋት አዙሪት

እንዲህ አይነቱ ሥነ-ልቦናዊ ክፍፍል፣ ማህበራዊ መዋቅሩን ያፈርሳል። ለማህበረሰብ ህልውና ወሳኝ የሆነው እና በሰዎች መካከል ያለው የመተማመን፣ የትብብርና የግንኙነት መረብ በጥላቻ ትርክት ይሸረሸራል። የጥላቻ ፕሮፓጋንዳው ይህንን ትስስር ሲያፈርስ፣ በአማራ ክልል ለዘመናት አብሮ የኖረ ጎረቤት በጥርጣሬ መተያየት ይጀምራል፤ የጋራ ገበያ የፍርሃት ቀጠና ይሆናል፤ የኃይማኖት ተቋማት የሰላም ማዕከል መሆናቸው ቀርቶ፣ የጥላቻ መስበኪያና የጥቃት ዒላማ ይሆናሉ። አንዴ መተማመን ከጠፋ፣ ህብረተሰቡ እርስ በእርሱ ወደሚበላላበት የScapegoating አዙሪት ውስጥ ይገባል። የጦርነቱ፣ የኢኮኖሚ ውድቀቱ እና የፖለቲካ አለመረጋጋቱ የፈጠረው ብስጭትና ጭንቀት፣ በቀላሉ ሊለይ በሚችለውና ራሱን መከላከል በማይችለው አናሳው ሙስሊም ማህበረሰብ ላይ ይላከካል።

ከዚህም በላይ የእርስ በእርስ ግጭት ተለዋዋጭነት (civil-war microdynamics ) ላይ የተደረጉ ጥናቶች እንደሚያሳዩት፣ እንዲህ ያለው ሀገራዊ ትርክት አንዴ ከተስፋፋ በኋላ፣ ግለሰቦች የግል ቂማቸውን፣ የንብረት ክርክራቸውን እና ሌሎች የአካባቢ ግጭቶችን በዚህ ትልቅ የኃይማኖት ሽፋን ስር በማስገባት የግል ጥቃቶችን ይፈጽማሉ። ይህም ማለት፣ በሁለት ጎረቤቶች መካከል የነበረ የመሬት ክርክር፣ አንደኛው ወገን ሌላኛውን "የመንግስት ሰላይ" ወይም "የጅሃዳዊያን ተላላኪ" በማለት በመወንጀል ወደ ህይወት ማጥፋት ሊያድግ ይችላል።

💢በአማራ ክልል ሙስሊሞች ላይ የደረሰው ተጨባጭ ጉዳት

ይህ የጥላቻ ትርክት በአማራ ክልል ሙስሊሞች ላይ ያስከተለው ጉዳት ንድፈ-ሀሳባዊ ብቻ ሳይሆን በየቀኑ የሚኖሩት መራራ እውነታ ነው፦

1️⃣ ማግለል እና ጥርጣሬ፡ የተራ ሙስሊሞች ፖለቲካቸው ምንም ይሁን ምን “የሥርዓቱ ወኪሎች” ተብለው እንደ Fifth column ተደርገው ይወሰዳሉ። ይህ እንግልት፣ የታማኝነት ፈተናዎች እና ኢኮኖሚያዊ ወይም አስተዳደራዊ መገለልን አስከትሏል። ሙስሊም ነጋዴዎች ከገበያ እየተገፉ ነው፣ ንብረታቸው እየተዘረፈና እየወደመ ነው።

2️⃣ የጸጥታ ኃይሎች ከመጠን ያለፈ እርምጃ፡ ፖሊስ እና ሚሊሻዎች በጋራ ቅጣት ላይ ያተኩራሉ፦ በሙስሊም አካባቢዎች ላይ ያነጣጠሩ የፍተሻ ኬላዎች፣ የጅምላ እስራት፣ መገለል እና የንብረት መውረስ የተለመደ ሆኗል።

3️⃣ በሕዝብ ደረጃ የሚፈጸም ዓመፅ እና መለያየት፡ በውሸት ወሬዎችና የሞራል ሽብር ግርግር ይነሳል፦ በመስጊዶች እና በሱቆች ላይ ጥቃት ይሰነዘራል፣ የግዳጅ ማፈናቀል ይፈጸማል፣ እንዲሁም ሰፈሮችን "በማጥራት" ስም የኑፋቄ ክፍፍል ይፈጠራል።

4️⃣ ፖለቲካዊ መብትን ማሳጣት፡ ፓርቲዎች እና ማህበራት ሙስሊም አባላትን ያስወጣሉ፤ የመንግሥት ሠራተኞች ወደ ጎን ይገፋሉ፤ የአካባቢው መገናኛ ብዙኃን ሰብአዊነትን የሚያዋርዱ አገላለጾችን እንደ ተለመደ ነገር ያቀርባሉ።

💥ዓለም አቀፍ የታሪክ ማሳያዎች ከቦስኒያ እስከ መካከለኛው አፍሪካ

የአማራ ክልል ሰማይ ስር እየተፈጸመ ያለው ድርጊት፣ በሌሎች ሀገራት የታየው የጥላቻ ፖለቲካ አደገኛ ማስተጋባት ነው።

🩸 ቦስኒያ (1992–1995): የሰርብ ብሔርተኞች አዲሱን የቦስኒያ መንግሥት "እስላማዊ ሪፐብሊክ" ተብሎ እንዲፈረጅ በማድረግና ሙስሊሞችን "ጽንፈኞች" በማለት በሰፊው ፕሮፓጋንዳ ነዝተዋል። ይህ በቦስኒያክ ሙስሊሞች ላይ የዘር ማጽዳት ለመፈጸም እንደ ህጋዊ ሽፋን አገልግሏል። ልክ ዛሬ በአማራ ክልል እንደሚሰማው፣ በወቅቱ "ሙስሊም ጎረቤትህን አትመን፣ ነገር ግን መሳሪያህን አዘጋጅ" የሚሉ መፈክሮች ይሰሙ ነበር።

🩸መካከለኛው አፍሪካ ሪፐብሊክ (2013–2014): በዋናነት ሙስሊሞችን ያቀፈው የሴሌካ አማጺ ቡድን ስልጣን መያዙን ተከትሎ፣ ፀረ-ባላካ የተባሉ የክርስቲያን ሚሊሻዎች "መንግሥትን መቃወም" የሚለውን መፈክር በፍጥነት ወደ "ሙስሊምን መቃወም" በመቀየር በመላ ሀገሪቱ በሚገኙ ሙስሊም ሲቪሎች ላይ አሰቃቂ እልቂትና ማፈናቀል ፈጽመዋል። ይህም "ፀረ-ሥርዓት" ትግል በቀላሉ እንዴት "ፀረ-ሙስሊም" ዘመቻ እንደሚሆን ቁልጭ አድርጎ ያሳያል።

ይህ ታሪካዊ ንድፍ እንደሚያሳየው፣ አንዴ የፖለቲካ ትግል የኃይማኖት መልክ ከያዘ፣ የመጀመሪያው ሰለባ የሚሆነው በሩቅ ያለው የፖለቲካ ሥርዓት ሳይሆን በአቅራቢያ የሚኖረው ንጹሕ አናሳ ዜጋ ነው።

👂ሊመጣ የሚችለው የከፋ ጥፋት

ይህ አደገኛ አካሄድ ካልተገታ፣ በአማራ ክልል ሙስሊሞች ላይ ሊያስከትል የሚችለው ጉዳት እጅግ የከፋ ነው።

🩸 በመካከለኛ ጊዜ: ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ መለያየት (ghettoization) ሊፈጥር ይችላል። ሙስሊሙ ማህበረሰብ ከኢኮኖሚው መዋቅር በመገፋት የራሱን ትይዩ ኢኮኖሚ ለመፍጠር ይገደዳል፣ ይህም የረጅም ጊዜ መገለልን ያባብሳል። የተማረውና ሀብት ያፈራው የህብረተሰብ ክፍል ከክልሉ ሊሰደድ ይችላል (brain drain), ይህም የክልሉን ምሁራዊና ኢኮኖሚያዊ አቅም ያዳክማል።

🩸በረጅም ጊዜ: ይህ መከፋፈል በቀላሉ የማይሽር ታሪካዊ ጠባሳ በመተው በቀልንና ጥርጣሬን በትውልዶች መካከል ሊዘራ ይችላል። የኃይማኖት መቻቻል ባህል ሙሉ በሙሉ በመሸርሸር፣ የክልሉ ማህበራዊ መዋቅር ሊጠገን በማይችልበት ደረጃ ሊጎዳ ይችላል።

"የእስላም መንግሥት" የሚለው ፕሮፓጋንዳ በአማራ ክልል የፈጠረው ቀውስ፣ የቃላት ኃይል ምን ያህል ገዳይ ሊሆን እንደሚችል የሚያሳይ ህያው ምስክር ነው። ጥቃቱ የዘፈቀደ ሳይሆን፣ የጥላቻ ትርክት የፈጠረው ሥርዓታዊ እና አመክንዮአዊ ውጤት ነው። ይህንን አጥፊ አዙሪት ለመስበር၊ የፖለቲካ၊ የኃይማኖት እና የማህበረሰብ መሪዎች ይህንን የውሸት ትርክት በግልጽና በድፍረት ሊያወግዙ ይገባል። የተሸረሸረውን ማህበራዊ መተማመን መልሶ ለመገንባትና የህግ የበላይነትን ለማስፈን የሚደረገው ጥረት፣ የክልሉን ብቻ ሳይሆን የሀገሪቱን ህልውና የሚወስን ይሆናል።

ጥናቶች እንደሚያሳዩት፣ እንዲህ ያለውን አዙሪት ለመስበር እንደ ጥቅጥቅ ያሉ የሃይማኖት ተቋማት የንግድ እና የሲቪክ መረቦች (civic interdependence ) እና የጥላቻ ንግግርን በጋራ የሚያወግዙ የልሂቃን ስምምነቶች (elite pacts ) ያሉ መፍትሄዎች ወሳኝ ናቸው።

የመጨረሻው ጥያቄ፣ አንድ ማህበረሰብ በውስጡ ያሉትን አናሳዎች እንደ ህልውናው አካል ሲመለከትና እንደ ስጋት ሲፈርጅ መካከል ያለውን የህሊና ወሰን የት ላይ ያሰምራል የሚለው ነው።

መልሱ፣ የመጪውን ትውልድ እጣ ፈንታ ይወስናል።

07/10/2025

ሙስሊም ሁሉ ስልጤ ከመሰላችሁ እኔም ስልጤ ነኝ።☺️

07/10/2025

Address

Adama

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Dhugaan ni iyyiti posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Dhugaan ni iyyiti:

Shortcuts

Share

Category