GADAA Media ገዳ ሚድያ

GADAA Media  ገዳ ሚድያ Oduu Ammee ሰበር ዜናዎች

በህዳር ወር 2015 ዓ.ም (እ.ኤ.አ. ህዳር 2022) በፕሪቶሪያ፣ ደቡብ አፍሪካ የተፈረመው የሰላም ስምምነት ዋነኛ ዓላማ በኢትዮጵያ መንግሥት እና በህወሓት መካከል የተፈጠረውን ግጭት በዘላ...
10/12/2025

በህዳር ወር 2015 ዓ.ም (እ.ኤ.አ. ህዳር 2022) በፕሪቶሪያ፣ ደቡብ አፍሪካ የተፈረመው የሰላም ስምምነት ዋነኛ ዓላማ በኢትዮጵያ መንግሥት እና በህወሓት መካከል የተፈጠረውን ግጭት በዘላቂነት መፍታት ነበር። የዚህ ስምምነት አንዱ ዋና ምሰሶ እና ሁለቱም ወገኖች የገቡት ቁልፍ ቃል የኢትዮጵያን ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሕገ መንግሥትና ህግጋትን ማክበር የሚለው ነው።

ይህ ድንጋጌ ሰላምን የማስፈን ሂደቱ በህግ የበላይነት ስር እንዲሆን የሚያረጋግጥ ሲሆን፣ ስምምነቱ ሁሉንም የሀገሪቱን ክልሎች የሚገዛውን ማዕከላዊ ህጋዊ ማዕቀፍ እውቅና ይሰጣል።

ሆኖም፣ ህወሓት ከስምምነቱ በኋላ ባሉት ጊዜያት ከዚህ ሕገ መንግሥታዊ ግዴታ በተቃራኒ የሚቆሙ ተግባራትንና አቋሞችን በተደጋጋሚ ሲያንጸባርቅ እንደነበር ይታወቃል። የሕገ መንግሥቱን ማዕከላዊነት ችላ ማለት ወይም መቃወም የሰላም ስምምነቱን መንፈስ የሚሸረሽር ከመሆኑም በላይ፣ በሰላም ግንባታው ሂደት ውስጥ ዋና ፈተና ነው።

ከኅዳር 23 ቀን ወዲህ አንድም በማርበርግ ቫይረስ የተያዘ ሰው የለም፡፡የኢፌዴሪ የጤና ሚኒስቴር በየዕለቱ የማርበርግ ቫይረስን በተመለከተ መረጃዎችን እየሰጠ ይገኛል፡፡ በዚህም መሠረት ኅዳር ...
09/12/2025

ከኅዳር 23 ቀን ወዲህ አንድም በማርበርግ ቫይረስ የተያዘ ሰው የለም፡፡

የኢፌዴሪ የጤና ሚኒስቴር በየዕለቱ የማርበርግ ቫይረስን በተመለከተ መረጃዎችን እየሰጠ ይገኛል፡፡ በዚህም መሠረት ኅዳር 23 ቀን 2018 ዓ.ም ከተደረጉ 221 ምርመራዎች መካከል በአንድ ሰው ላይ ከመገኘቱ በቀር እስከዛሬ ባሉት ስድስት ቀናት ተጨማሪ አንድም ሰው በቫይረሱ መያዙ አልተረጋገጠም፡፡

ኅዳር 23 ቀን ቫይረሱ እንዳለበት የተረጋገጠውም ሰው አስቀድሞ በቫይረሱ መያዙ ከተረጋገጠ ሰው ጋር ንክኪ የነበረውና በልይቶ ማቆያ የነበረ መኾኑ በወቅቱ ተገልጧል፡፡ ከኅዳር 24 እስከ 29/2018 ዓ.ም ባሉት ቀናት ለ642 ሰዎች የላቦራቶሪ ምርመራ እንደተደረገም መረጃዎች ያመለክታሉ፡፡
ይሁን እንጅ ከእውነታዉ የራቀ ስጋት ለመፍጠር ወደ ኢትዮጵያ የጉዞ ክልከላዎች የሚመስሉ ማስጠንቀቂያዎችን እያወጡ ነው፡፡ ኢትዮጵያ ለዜጎቿም፣ ለእንግዶቿም ጤና የምትጨነቅ፣ የዓለም ጤና ድርጅት ምክረ ሐሳቦችን መሠረት በማድረግ ወቅታዊ የጤና መረጃዎችን በግልጽ ለሕዝብ የምታጋራ ኃላፊነት የሚሰማት ሀገር ናት፡፡ ከዚህ እውነታ በመራቅ በፈጠራ አሉቧልታ በሕዝባችን ላይ ስጋት ማስተጋባት፣ ወደ ኢትዮጵያ የሚመጡ መንገደኞችንም ጥርጣሬ እንዲገባቸው ለማድረግ መጣር የሚጠበቅ ተግባር አይደለም፡፡

ኋላ ቀሩ የህውሃት ቡድን  በሰሜኑ ጦርነት ከተሸነፈ በኋላ ወደ ሰላማዊ ድርድር ቢመጣም፣ በሰላም ስምምነቱ ሙሉ አተገባበር ላይ የሚያሳየው መዘግየት፣ በወሰን ላይ የሚፈጥረው ውዝግብ እና የፖለ...
09/12/2025

ኋላ ቀሩ የህውሃት ቡድን በሰሜኑ ጦርነት ከተሸነፈ በኋላ ወደ ሰላማዊ ድርድር ቢመጣም፣ በሰላም ስምምነቱ ሙሉ አተገባበር ላይ የሚያሳየው መዘግየት፣ በወሰን ላይ የሚፈጥረው ውዝግብ እና የፖለቲካ አቋሙ የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ሥርዓት ሰላማዊና ዘላቂ መረጋጋት እንዳይኖረውና ከኢትዮጵያ ህገመንግስት በተቃራኒው በመቆም አሁንም ድረስ ሁከት ለምፍጠር እየሰራ ይገኛል ።

08/12/2025
ኢትዮጵያ ውስጥ ሌላ ኢትዮጵያዩኒቨርሲቲዎች የቀለም ትምህርት የሚገበይባቸው ማእከላት ብቻ አይደሉም፡፡ ባህል ከዘመናዊነት፣ ሃይማኖት ከነባራዊ እውነት፣ ፖለቲካ ከንድፈ ሐሳብ እየተገናኙ የወጣቶ...
08/12/2025

ኢትዮጵያ ውስጥ ሌላ ኢትዮጵያ

ዩኒቨርሲቲዎች የቀለም ትምህርት የሚገበይባቸው ማእከላት ብቻ አይደሉም፡፡ ባህል ከዘመናዊነት፣ ሃይማኖት ከነባራዊ እውነት፣ ፖለቲካ ከንድፈ ሐሳብ እየተገናኙ የወጣቶችን የሕይወት ምሕዋር የሚገሩበት የመስተጋብር ቦታ ጭምር እንጅ፡፡ ተማሪዎች ወደ ዩኒቨርሲቲ እስኪገቡ ድረስ በአብዛኛዉ አንድ ዓይነት ባህል እና ማኅበራዊ ሕይወት የሚታይበት አካባቢ ይቆያሉ፡፡ ወደ ዩኒቨርሲቲ ሲገቡ ግን የተለየ የሕይወት ዓውድ ይጠብቃቸዋል፡፡ የቋንቋ፣ የሃይማኖት፣ የባህል፣ የሥልጣኔ ወ.ዘ.ተ ልዩነት ካላቸው ጓደኞቻቸው ጋር ይገናኛሉ፡፡

በዚህ ጊዜ የብዝኃነትን ጣዕም በተግባር ማጣጣም ይጀምራሉ፡፡ የቋንቋ፣ የባህል፣ የሥልጣኔ፣ የፖለቲካዊ አመለካከት ወስተጋብር ውጤቶችን በገቢር በዩኒቨርሲቲ ጓደኞቻቸው ያገኛሉ፡፡ ተማሪዎች ከተለያዩ አካባቢዎች ስለሚመጡ የአንዱ ተማሪ መገለጫ ለሌላኛዉ እንግዳ የመኾን ዕድላቸው ሰፊ ነው፡፡ እነዚህ ተማሪዎች በአንድ ክፍል አብረው እየተማሩ፣ በአንድ የመኝታ ክፍል ውስጥ እየኖሩ የሕይወት ልምዳቸውን ይጋራሉ፡፡ አንዱ የሌላዉን ባህል፣ እሴት፣ አመለካከት በቅርበት ይረዳል፤ የራሱንም ያስረዳል፡፡ ብዝኃነት በተግባር የሚኖር የዕለት ከዕለት ሕይወት ይኾናል፡፡
ዛሬ እያከበርን የምንገኘው የኢትዮጵያ ብሔሮች ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ቀን ደግሞ በዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ ብዝኃነት አጊጦ የሚታይበት ነው፡፡ ተማሪዎች የየመጡባቸዉን አካባቢዎች አልባሳትና መዋቢያዎች ተጠቅመው ራሳቸዉን ይገልጻሉ፡፡ በየቋንቋቸዉ ኅብረ ዝማሬዎችንና ኪነ ጥበባዊ ሥራዎችን ያቀርባሉ፡፡ አንዱ ሌላዉን ለማየት ጉጉቱ ይልቃል፡፡ ዩኒቨርሲቲዎችም ይህንኑ ዓውድ በጉጉት ይጠብቁታልና ኢትዮጵያን በግቢያቸው ውስጥ ለማየት ምቹ ዓውድ ይፈጥራሉ፤ ኢትዮጵያውያን የበለጠ እንዲተዋወቁና ብዝኃነትን እንዲኖሩ በገቢር ያሳያሉ፡፡
በዩኒቨርሲቲዎች በየዓመቱ የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ቀንን በድምቀት ማክበርና ኅብረ ብሔራዊነትን ማስረጽ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶታል፡፡ ዘንድሮም "ዴሞክራሲያዊ መግባባት ለኅብረ ብሔራዊ አንድነት" በሚል መሪ መልእክት በዩኒቨርሲቲዎች 20ኛዉ የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ቀን እየተከበረ ነው።
ኅዳር 29 ቀን የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ቀን እየተባለ የሚከበረው የኢፌዴሪ ሕገ መንግሥት የጸደቀበትን ቀን ምክንያት በማድረግ ሕገ መንግሥታዊ አስተምህሮን ለማስረጽ ነው፡፡ በዓሉ ከ1998 ዓ.ም ጀምሮ በየዓመቱ በመላው ኢትዮጵያ እየተከበረ ይገኛል፡፡ ሕገ መንግሥቱ ኢትዮጵያውያን ኅብረ ብሔራዊ አንድነታቸዉን በማጽናት አንድ የጋራ የፖለቲካ እና ኢኮኖሚ ማኅበረሰብ ለመገንባት የገቡት ቃል ኪዳን መገለጫ ነው፡፡

በህዝብና በመንግስት እምነት አላግባብ በሚጠቀሙ ነጋዴዎች ላይ ጠንካራ የመንግስት እርምጃ አስፈላጊነትየንግድ ስርዓቱ ከሙስናና ከብልሹ አሰራር የጸዳ እንዲሆን እና የኢኮኖሚው እድገት ፍትሐዊ በ...
08/12/2025

በህዝብና በመንግስት እምነት አላግባብ በሚጠቀሙ ነጋዴዎች ላይ ጠንካራ የመንግስት እርምጃ አስፈላጊነት
የንግድ ስርዓቱ ከሙስናና ከብልሹ አሰራር የጸዳ እንዲሆን እና የኢኮኖሚው እድገት ፍትሐዊ በሆነ መንገድ እንዲሰራጭ ለማድረግ፣ መንግስት የህዝብና የመንግስትን እምነት በሚያጠፉ ነጋዴዎች ላይ ሳይዘገይ ጠንካራ እርምጃ መውሰድ ይገባዋል። ይህ የዜጎችን ደህንነት ለማስጠበቅ እና የሀገርን ኢኮኖሚያዊ መረጋጋት ለማረጋገጥ መሠረታዊ ጉዳይ ነው።
የህዝብን ጥቅም ለግል ጥቅም ሲሉ በሚጎዱ ነጋዴዎች ላይ ጠንካራ እና አስተማሪ ቅጣት መጣል፣ ይህም ሌሎች ተመሳሳይ ወንጀል እንዳይፈጽሙ ማስጠንቀቂያ ይሆናል።

07/12/2025

የሰላም ስምምነት አካል አይደለንም የሚሉ አካላት የጠላት አጀንዳ ተሽካሚ ናቸው።

የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያዎች እና የዶላር አቅርቦትየኢትዮጵያ መንግሥት ባካሄዳቸው ዋና ዋና የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያዎች መካከል አንዱ ገበያ-መር (Market-Based) የውጭ ምንዛሬ ሥርዓትን ተ...
04/12/2025

የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያዎች እና የዶላር አቅርቦት
የኢትዮጵያ መንግሥት ባካሄዳቸው ዋና ዋና የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያዎች መካከል አንዱ ገበያ-መር (Market-Based) የውጭ ምንዛሬ ሥርዓትን ተግባራዊ ማድረግ ነው። ይህ የፖሊሲ ለውጥ፣ ባንኮች የውጭ ምንዛሪ የሚገዙበትንና የሚሸጡበትን ዋጋ ከደንበኞች ጋር በመደራደር እንዲወስኑ የሚፈቅድ ሲሆን፣ ይህም የውጭ ምንዛሪ ዋጋ በገበያው ውስጥ ባለው ፍላጎትና አቅርቦት ላይ የተመሠረተ እንዲሆን ያስችላል።

መንግሥት የጥቁር ገበያውን ለመግታት እና ሕገወጥ የዶላር ግብይቶችን ለመቆጣጠር በርካታ ተግባራዊ እርምጃዎችን እየወሰደ ይገኛል።

የሕገወጥ አሰራር መከላከልና ለመቆጣጠር መንግስት

የባንክ አካውንት እገዳዎች: ብሔራዊ ባንክ ሕገወጥ የዶላር ዝውውርና ግብይት ላይ የተሰማሩ ግለሰቦች እና ድርጅቶች የባንክ አካውንቶች እንዲታገዱ በማድረግ ላይ ይገኛል። ይህ እርምጃ ሕገወጥ የገንዘብ ዝውውርን የሚያካሂዱ አውታሮችን ለመበተን ያለመ ነው።

የመረጃ መረብ ዘመቻዎች: የጥቁር ገበያ ተዋናዮችን በክትትልና በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ሥራዎች እየተከናወኑ ነው።

የውጭ ምንዛሪ አጠቃቀም ሥርዓት፡ የውጭ ምንዛሪን በተመለከተ ባንኮች የሚያስከፍሉትን ክፍያዎች ግልፅ፣ ተወዳዳሪ እና ምቹ ለማድረግ ማሻሻያዎች እየተደረጉ ነው።

የ2018 ዓ.ም የምርጫ  አስቻይ ሁኔታዎችየኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ (መርሐ ግብርን ጨምሮ) የ2018 ዓ.ም. ምርጫ ቅድመ ዝግጅትን በንቃት እያካሄደ መሆኑን የሚጠቁሙ ሁኔታዎች አሉ።የቦር...
04/12/2025

የ2018 ዓ.ም የምርጫ አስቻይ ሁኔታዎች

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ (መርሐ ግብርን ጨምሮ) የ2018 ዓ.ም. ምርጫ ቅድመ ዝግጅትን በንቃት እያካሄደ መሆኑን የሚጠቁሙ ሁኔታዎች አሉ።

የቦርዱ ተቋማዊ አቅም ማጎልበት፡ ቦርዱ በቅርብ ዓመታት በተደረጉት ለውጦች እና ማሻሻያዎች ምክንያት ገለልተኝነቱ እና ተዓማኒነቱ ተሻሽሏል ተብሎ ይታሰባል (በተለይ ከ2011 ዓ.ም. በኋላ በተቋቋመበት አዲስ አዋጅ መሰረት)።

የቴክኖሎጂ አጠቃቀም፡ ቦርዱ እንደ ዕጩ ምዝገባ እና ታዛቢዎች ምዝገባ ባሉ ሂደቶች ውስጥ ዘመናዊ የኦንላይን ሲስተሞችን እየተጠቀመ ነው። ይህ አሰራር ቅልጥፍናን ከማምጣቱም በላይ የመረጃዎችን ትክክለኛነት ለማረጋገጥ ይረዳል።

የባለድርሻ አካላት ተሳትፎ፡ ለፓርቲዎች፣ ለሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች እና ለሴት ፖለቲከኞች የማሰልጠኛ እና የምክክር መድረኮችን ማዘጋጀቱ አካታችነትን ለማረጋገጥ ያለውን ቁርጠኝነት ያሳያል።

የፕላን ዝግጅት፡ ቦርዱ ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ዝርዝር፣ ሊለካ የሚችል እና ከጊዜ ጋር የተጣጣመ ዕቅድ (Plan) እያዘጋጀ መሆኑ፣ ሂደቱን በህጋዊው የጊዜ ገደብ ውስጥ ለማስፈጸም ያለውን ዝግጁነት ያመለክታል።

ማጠቃለያ

በአጠቃላይ፣ የኢትዮጵያ ያለፉት ምርጫዎች ተሞክሮዎች የሚያሳዩት ምርጫ የማካሄድ ልምድና ጥረት ከባድ የሆኑ የጤናም ሆነ የደህንነት ፈተናዎችን ለመሻገር የቻለ መሆኑን ነው። በዚህም መሰረት፣ የ2018 ዓ.ም. ምርጫ ቅድመ ዝግጅት በዘመናዊ አሰራር እና በተሻሻለ የቦርድ አቅም እየተመራ መሆኑን ከግምት ውስጥ ስናስገባ፣ ምርጫውን የሚያስተጓጉል የገዘፈ ምክንያት እንደሌለ መገመት ይቻላል። ቀደም ሲል የነበሩ ልምዶች ለአሁኑ ሂደት የማይናወጥ መሠረት ናቸው

ሰላም በዘላቂነት  እንዲሰፍን  በመደገፍ  ተሳትፏቸውን  አጠናክረው  እንደሚቀጥሉ የጎንደር ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ።የጎንደር ከተማ አስተዳደርና የማዕከላዊ ጎንደር ዞን የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ...
04/12/2025

ሰላም በዘላቂነት እንዲሰፍን በመደገፍ ተሳትፏቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ የጎንደር ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ።

የጎንደር ከተማ አስተዳደርና የማዕከላዊ ጎንደር ዞን የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ያዘጋጁትና ታላቅ የሰላም ጥሪን ያነገበ ሕዝባዊ ሰልፍ በጎንደር ከተማ እየተካሄደ ነው።

የሀገር ሽማግሌዎችና የሃይማኖት አባቶችን ጨምሮ ሌሎችም ነዋሪዎች በድጋፍ ሰልፉ በመሳተፍ ላይ ናቸው።

የድጋፍ ሰልፉ ተሳታፊ ነዋሪዎች ሰላም በዘላቂነት እንዲሰፍን በመደገፍ ተሳትፏቸውን እንደሚያጠናክሩና ሰላምን መስበካቸውን እንደሚቀጥሉ የሚገልጹ የተለያዩ መልዕክቶችን እያስተላለፉ ነው።

ከመልዕክቶቹም ቤተ እምነቶች ሰላምን ማስፈን ተቀዳሚ ተግባራቸው ነው፣የሰላምና የመከባበር ባሕልን ለማስቀጥል የሃይማኖት ተቋማት ሚና የማይተካ ነው፣ሀይማኖታዊ እሴቶቻችን የአብሮነትና የጥንካሬያችን መሰረቶች ናቸው የሚሉ ይገኙበታል።

04/12/2025

The Guardian በቅርቡ ያወጣው ዘገባ
የኢትዮጵያን ገጠር እውነታ የሚገልጽ አይደለም።

በ The Guardian የሚቀነቀነው "የድል ዜና" እና መሬት ላይ ያለው "የተስፋ መቁረጥ እውነት" ለሰማይ እና ለምድር የራቁ ናቸው።

ዛሬ ጫካው በድል ዜና ሳይሆን በተስፋ መቁረጥ ጩሀት ተሞልቷል። እንደነ ማስረሻ ሰጤ ያሉ የቡድኑ ቁልፍ ሰዎች ሳይቀሩ የትግሉ አቅጣጫ መጥፋቱን ተረድተው ወደ ሰላም ጎዳና እየመጡ ነው።

ታጣቂው እርስ በእርስ እየተናከሰ አላማው ጠፍቶበት እና ተስፋ ቆርጦ በቡድን እየከዳ ዓለም አቀፍ ሚዲያዎች ግን ስለሌለ "የመብረቅ ጥቃት" ያወራሉ። ይህ የጋዜጠኝነት ውድቀት ብቻ ሳይሆን እየሞተ ላለ እንቅስቃሴ የውሸት ኦክስጅን ለመስጠት የሚደረግ ከንቱ ጥረት ነው። እውነቱ ግን እንደ ፀሐይ ፈጥጦ ወጥቷል፤ የቡድኑ ጊዜ አልቋል!

የጠቅላይ ሚንስትር ዶ/ር ዐብይ አህመድ የህዳር ወር ዲፕሎማሲያዊ ስኬት የጠቅላይ ሚንስትር ዶ/ር ዐብይ አህመድ  በኢትዮጵያ የውጭ ግንኙነት እና ዲፕሎማሲ መስክ በህዳር ወር ቁልፍ ስኬቶችን አ...
03/12/2025

የጠቅላይ ሚንስትር ዶ/ር ዐብይ አህመድ የህዳር ወር ዲፕሎማሲያዊ ስኬት

የጠቅላይ ሚንስትር ዶ/ር ዐብይ አህመድ በኢትዮጵያ የውጭ ግንኙነት እና ዲፕሎማሲ መስክ በህዳር ወር ቁልፍ ስኬቶችን አስመዝግበዋል። እነዚህም
* በG20 በመሳተፍ ቁልፍ እና ገንቢ አገራዊና አህጉራዊ ይዘት ያላቸውን መልክቶች አስተላልፈዋል ከተለያዩ አገራት መሪዎችም ጋር የሁለትዮሸ ውይይት አድርገዋል

* የindonesia እና የ singapore መሪዎችን ተቀብለው አነጋግረዋል
በጥቅሉ በህዳር ወር
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቀጣናው ሰላምና መረጋጋት ላይ ያተኮሩ ንቅናቄዎችን በማካሄድ በአፍሪካ ቀንድ ሀገራት መካከል ያለውን ትብብር ለማጠናከር ጥረት አድርገዋል።

በውጭ ጉዳይ ግንኙነት ሀገሪቱን ከፍ የማድረግ ስራዎችን ተከትሎ፣ ከዓለም አቀፍ አጋሮች እና ተቋማት ጋር የኢኮኖሚ እና የልማት ድጋፍን በማስገኘት ረገድ ውጤታማ ነበሩ።

ከውጭ ወታደራዊ አመራሮች ጋር በቀጠናዊ የጸጥታ ጉዳዮች ላይ የተደረጉ ውይይቶች የሀገሪቱን የዲፕሎማሲ አቅም ያጠናከሩ ነበሩ። ለምሳሌ በወቅቱ የዩናይትድ ስቴትስ የአፍሪካ እዝ አዛዥን የመሳሰሉ ከፍተኛ ባለስልጣናትን አግኝተው ነበር።

Address

Adama

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when GADAA Media ገዳ ሚድያ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share