GADAA Media ገዳ ሚድያ

GADAA Media  ገዳ ሚድያ Oduu Ammee ሰበር ዜናዎች

ሰበር ዜናየአማራ ህዝብ ፋኖን ጠልቷል ስንል በምክንያት ነው!የሰሜን ጎንደር ዞን ጭልጋ ወረዳ ነዋሪዎች ከጀግናው መከላከያ ሰራዊት ጋር በመተባበር በየጥሻው ተደብቆ ሲተናኮል የነበረውን ሽፍታው...
17/10/2025

ሰበር ዜና
የአማራ ህዝብ ፋኖን ጠልቷል ስንል በምክንያት ነው!
የሰሜን ጎንደር ዞን ጭልጋ ወረዳ ነዋሪዎች ከጀግናው መከላከያ ሰራዊት ጋር በመተባበር በየጥሻው ተደብቆ ሲተናኮል የነበረውን ሽፍታውን ፋኖ በዚህመልኩ ማርኳል ቀሪዎቹም ላይመለሱ ተደምስሰዋል።
ክብር ለሃገር መከላከያ ሰራዊት!
የጭልጋ ወረዳ ነዋሪዎች እናመሰግናለን!

የደንባራው ታደሰ ወረደ ጉዞ ወደ ዝግ መንገድ።ታደሰ አንዴ አለምን ይዤ ሞንጀሪኖና ደብረፅዮንን አባርሬ፣ ጌታቸው አሰፋን አስሬ ሪፎርም አመጣለሁ ይላል። ይህን እንኳ ለአሜሪካኖችም ነግሮ አሳብ...
17/10/2025

የደንባራው ታደሰ ወረደ ጉዞ ወደ ዝግ መንገድ።
ታደሰ አንዴ አለምን ይዤ ሞንጀሪኖና ደብረፅዮንን አባርሬ፣ ጌታቸው አሰፋን አስሬ ሪፎርም አመጣለሁ ይላል። ይህን እንኳ ለአሜሪካኖችም ነግሮ አሳብቀውበታል። ዞር ብሎ ደሞ ዓለም ዕድል ካገኘ የደመኮርን ያህል ፋታ ሳይሰጥ ይገለብጠኛል ይላል።
ከ2015 ጀምሮ ተፈናቃይ እንዳይመለስ በዋናነት ያሰናከሉት እሱ፣ ከዚያ በመቀጠልና በእርሱ ተፅዕኖም ፍሰሃ ማንጁስ ሆነው እያለ ተፈናቃይ አለመመለሱ ችግር ነው ይላል። አዲስ አ ሶበባ ሲሄድ ደመኮር አደናቀፈኝ ታገሱኝ፣ ሳምንታት ስጡኝ ይልና ትግራይ ሲመለስ ደመኮርን ሰብስቦ የፌደራል መንግስት እናንተ እንደለመዳችሁት እግር ከጎተታችሁ እራሴ መልሳለሁ ብሏልና ፈጥናችሁ ተፈናቃዩን የህወሃት ሰርተፊኬት ካልተሟላ አንሄድም እንዲል አሳምነዉ፣ እኔም ካቢኔ ሰብስቤ ተፈናቃዩ እምቢ ስላለ የህወሃትን ሰርተፊኬት በመመለስ ችግሩን በቅድሚያ እንፍታ እላለሁ እያለ ያሳድማል። ሲሻም ደሞ እኔ ሳላውቀው አንድም ተፈናቃይ አይመለስም ይላል። በስተ መጨረሻም ከሁለቱን ሳይሆን ቀርተዋል።

ጀ-WAR በአሁን ሳዓት "ቄሮ ከእ" ብለው መቀስቀስ የሚችለው ቄሮ የተባለው ሁለተኛ ልጁን ብቻ ነው።የኦሮሞ ህዝብ ማሳመፅ እንደሚችል እና እንደማይችል ለማየት ጥቀቅን የሰፈር ውሬዎችን ሳይቃር...
17/10/2025

ጀ-WAR በአሁን ሳዓት "ቄሮ ከእ" ብለው መቀስቀስ የሚችለው ቄሮ የተባለው ሁለተኛ ልጁን ብቻ ነው።

የኦሮሞ ህዝብ ማሳመፅ እንደሚችል እና እንደማይችል ለማየት ጥቀቅን የሰፈር ውሬዎችን ሳይቃር በማህበራዊ ትስስር ገፁ ስያሰራጭ ቆይቷል። ነገር ግን ትኩረት የሚሰጠው ሰው ጠፋ።

ጀዋር ምቾት ውስጥ ሲሆን የትም አልሄድም፣ ከህዝብ ጋር እኖራለው፣ እዚሁ እሞታለው ብሎ የነበረ ቢሆንም፣ ማኖ ነክቶ ከታሰረ በኃላ ግን ጥሎት እንደሄደ ያየ የኦሮሞ ወጣት እና የኦሮሞ ህዝብ ዝም ብሎታል። በአሁን ሳዓት ቄሮ የተባለው ጃዋር የወለደው ልጅ ራሱ "ቄሮ ከኢ" ብለው ልጁ "Dad" ለምን? ብለው አሳማኝ ምክንያት ይጠይቃል።

ስለዚህ ጀዋር ያለው ብቸኛ ህልም ከፋኖ ጋር አረት ኪሎ መግባት ነው። ጃዋር ህልሙ ህልም ብቻ ሆኖ የሚቀር ቢሆንም፣ ፋኖን አረት ኪሎ ማስገባት አላማ እንዳለው ሰሞኑን ባወጣቸው የትንታኔ ጽሁፎች ገልጿል። ይህንን አላማ እውን ለማድረግ ያቀደው በአንድ ባኩል የኦሮሞን ሃይል በማጥፋት እና በሌላ ባኩል አይሳካለትም እንጂ መንግስትን ማዳከም ነበር።

የእሱ ትንተና መደምደሚያ ይህ ስርዓት መፍረስ አለበት ነው። እሺ ተሳክቶለት ይፈርሳል እንበልና፣ ማነው ጀዋርን እንኳን መጣክልን ብለው ልቀበል የሚችል? ጀዋር ከለውጡ በፊትም፣ ከለውጡ በኃላም በጠመንጃ መታገል የለብንም ብለው ሸኔን ሲቃወም ስለነበር ሸኔ ጋር ተቀባይነት የለውም። የኦሮሞ ህዝብም እንዳይደግፈው ኦሮሚያ ውስጥ በጀ-WAR ምክንያት በተለያዩ ግዜ ደም ፈሷል፣ አሁን ለእሱ መሞት የሚፈልግ ወጣት የለም።

ጀዋር ኦሮሞ ፈርስት በሚል ፕሬፖጋንዳ ምክንያት ሌሎች ብሔሮች በጥርጣሬ አይን እንዲያዩት ሆኗል። ስለዚህ ጀዋር በእልህ እና በቅናት መንፈስ ኢትዮጵያን መበጥበጥ ይፈልጋል እንጂ ምንም የማድርግ አቅም እንደሌለው በደንብ ገብቶታል።

17/10/2025

Tadese wrede

🇪🇹🇮🇳  የኢትዮጵያ እና የሕንድ የጋራ የመከላከያ ትብብር ያለበትን ደረጃ የሚገመግም የምክክር መድረክ በሕንድ ዋና ከተማ ኒውዴሊ ተካሂዷል የኢትዮጵያ እና የሕንድ የጋራ የመከላከያ ትብብር ሥ...
16/10/2025

🇪🇹🇮🇳 የኢትዮጵያ እና የሕንድ የጋራ የመከላከያ ትብብር ያለበትን ደረጃ የሚገመግም የምክክር መድረክ በሕንድ ዋና ከተማ ኒውዴሊ ተካሂዷል የኢትዮጵያ እና የሕንድ የጋራ የመከላከያ ትብብር ሥምምነት አፈጻጸምን የሚገመግም የምክክር መድረክ በሕንድ ዋና ከተማ ኒውዴሊ በዛሬው እለት የተካሄደ ሲሆን መድረኩን የኢፌዲሪ መከላከያ የውጭ ግንኙነት ዋና ዳይሬክተር ሜጀር ጄኔራል ተሾመ ገመቹ እና የሕንድ መከላከያ ዓለምአቀፍ ትብብር ፀሐፊ አሚታባህ ፕራሳድ በጋራ መርተውታል።የሁለቱ ሃገራት የመከላከያ ተቋማት የስልጠና፣ የሕክምናና የመከላከያ ኢንዱስትሪ ትብብር ያለበት ደረጃ በጥልቀት የተገመገመ ሲሆን ሁለቱ ሃገራት የተፈራረሙትን ወታደራዊ የጋራ መግባቢያ ሥምምነት (MOU) ውጤታማ ለማድረግ በቀጣይ መሰራት ባለባቸው ጉዳዮች ዙሪያ የጋራ መግባባት ላይ ተደርሷል። India and Ethiopia today held their inaugural Joint Defence Cooperation (JDC) meeting in New Delhi, co-chaired by JS (IC) Shri Amitabh Prasad and Maj Gen Teshome Gemechu. The delegations reviewed ongoing defence cooperation and explored new avenues in training, joint exercises, medical collaboration, and defence industry engagement, further strengthening the framework established under the Defence Cooperation MoU signed earlier this year. 🇮🇳🤝🇪🇹

"መጪውን ትውልድ ከማንነቱና ከኩራቱ አፍልሶ፤ ከቤቱና ከቀዬው ስቦ፤ ከሀገሩና ከመንደሩ ገፍትሮ፤ ሌላ ሀገር ደጅ እንዲጠና ያደረገውን ሕመም እንዴት እናክመው?" #የመደመርትውልድ
15/10/2025

"መጪውን ትውልድ ከማንነቱና ከኩራቱ አፍልሶ፤ ከቤቱና ከቀዬው ስቦ፤ ከሀገሩና ከመንደሩ ገፍትሮ፤ ሌላ ሀገር ደጅ እንዲጠና ያደረገውን ሕመም እንዴት እናክመው?"
#የመደመርትውልድ

መማር መብት እንጂ ስጦታ አይደለም። ማንም ሰው ልጅን የመማር እድልን የመንፈግ ሞራልም ሆነ መለኮታዊ ስልጣን የለውም። እያንዳንዱ የተወለደ ልጅ የመፃፍ፣ የማንበብ፣ የማለም እና የማደግ እድል...
15/10/2025

መማር መብት እንጂ ስጦታ አይደለም።

ማንም ሰው ልጅን የመማር እድልን የመንፈግ ሞራልም ሆነ መለኮታዊ ስልጣን የለውም። እያንዳንዱ የተወለደ ልጅ የመፃፍ፣ የማንበብ፣ የማለም እና የማደግ እድል ማግኘት አለበት።

የምግብ ሉዓላዊነት ጉዞን የሚያፋጥነው ፋብሪካ  *********************************ኢትዮጵያ የምትገነባው የአፈር ማዳበሪያ ፋብሪካ ሀገሪቱ ከማዳበሪያ አቅርቦት ጋር ተያይዞ ሊ...
15/10/2025

የምግብ ሉዓላዊነት ጉዞን የሚያፋጥነው ፋብሪካ
*********************************
ኢትዮጵያ የምትገነባው የአፈር ማዳበሪያ ፋብሪካ ሀገሪቱ ከማዳበሪያ አቅርቦት ጋር ተያይዞ ሊደርሱባት የሚችሉ ጫናዎችን እንድትቋቋም አቅም የሚሰጣት ነው ሲሉ የግብርና ሚኒስትር አዲሱ አረጋ ገለፁ።
የዓለም ሃገራት ከምግብ ዋስትና ባሻገር የምግብ ሉዓላዊነት አጀንዳን እየከተሉ በመሆናቸው፤ የአፈር ማዳበሪያ ፋብሪካው ሉዓላዊነትን የሚያረጋግጥ ስለመሆኑ ነው የጠቆሙት።
የኦሮሚያ ክልል ግብርና ቢሮ ምክትል ኃላፊ በርሳ ፈይሳ በበኩላቸው፤ የመንግስት እና ሕዝብ የረጅም ጊዜ ጥያቄ የነበረውን የማዳባሪያ አቅርቦት ለማሳደግ ቁርጠኛ እርምጃ መወሰዱ ምርታማነትን የሚያሳልጥ ስለመሆኑ ነው የተናገሩት።
የአፈር ማዳበሪያ ፋብሪካው እየጨመረ የመጣውን የአርሶ አደሩን ፍላጎት የሚያረካ እና የምግብ ዋስትናን የሚያረጋገጥ ነው ያሉት ደግሞ የሲዳማ ክልል እርሻና የተፈጥሮ ሀብት ልማት ቢሮ ኃላፊ መምህሩ ሞኬ ናቸው።
በሌላ በኩል የአፈር ማዳበሪያ ፋብሪካው ፕሮጀክት መጀመር አዲስ ተስፋ የፈጠረባቸው አርሶ አደሮች፤ ይህ ጅማሮ ለተሻለ ምርታማነት ተነሳሽነትን እንደፈጠረላቸው ተናግረዋል።
አክለውም የአፈር ማዳበሪያ ፋብሪካው በሕዳሴ ግድብ ላይ ያየነውን የመንግስት ቁርጠኝነት ይበልጥ ያረጋገጠ ነው ብለዋል።

በትግራይ ክልል ውጥረት ነግሰዋልየትግራይን ጊዜያዊ አስተዳደር አፍርሰው ክልላዊ መንግሥት የመሆን ከፍተኛ ንቅናቄ የጀመሩት ጀኔራል ምግበ ኃይለ፣ ዮሀንስ ወልደ ጊዮርጊስ (ጆን መዲድ) እና ፍሰ...
14/10/2025

በትግራይ ክልል ውጥረት ነግሰዋል

የትግራይን ጊዜያዊ አስተዳደር አፍርሰው ክልላዊ መንግሥት የመሆን ከፍተኛ ንቅናቄ የጀመሩት ጀኔራል ምግበ ኃይለ፣ ዮሀንስ ወልደ ጊዮርጊስ (ጆን መዲድ) እና ፍሰሐ ኪዳኑ (ማንጁስ) የሚመሩት ባህላዊ ጄኔራሎች፣ በትግራይ ክልል ከፍተኛ ሁከትና ብጥብጥ እየፈጠሩ ነው። ይህ እርምጃ የትግራይን የራስን ዕድል በራስ የመወሰን ጥያቄ የሚያኮላሽ፣ በብዙ መስዋዕትነት የተገኘውን የፕሪቶሪያን የሰላም ስምምነት የሚንድ ከመሆኑም በላይ፣ ክልሉን ለዘመናት ወደኋላ በሚጎትትና ህዝቡን ወደ ባሰ ድቀትና ሰቆቃ በሚከት ተግባር ተወግዟል።

የታጣቂዎቹ ተቃውሞ መቀጠል የክልሉን ዘላቂ ሰላም እና መረጋጋት አደጋ ላይ ጥሎ የጦርነት ደመና ዳግም እንዲያንዣብብ ከፍተኛ ስጋት አሳድሯል።ትግራይን ለዘመናት የማድቀቅ አላማ አንግበው ሲንቀሳቀሱ የነበሩት ጄኔራል ምግበ እና ሌሎች ባህላዊ ጄኔራሎች አሁንም ክልሉን ወደ ባሰ ጥፋት ሊጨምሩ እንቅስቃሴ ጀምረዋል።

ምግበ ኃይለን፣ ጆን መዲድን እና ማንጁስን ጨምሮ በአመራሮች የሚመራው ይህ የታጣቂ ቡድን፣ ጊዜያዊ አስተዳደሩን ለመጣል እና ከፍተኛ ሁከትና ብጥብጥ ለመፍጠር እየሞከረ ነው። ይህ አደገኛ እርምጃ የትግራይን ህዝብ ከሰላም ርቆ ወደ ስቃይና ውድቀት የሚወስድ በመሆኑ የፕሪቶሪያን ስምምነት ለመጠበቅ ለሚደረገው ጥረት ትልቅ አደጋ ደቅኗል።"

መቀሌ የሚገኙ  ታጣቂዎች ዓመፅ አስነስተዋል የሃውልቲ  የነ መንጆሪኖ ቢሮዎችን ከባዋል ፣  መንገዶችን ዘግተዋል  ሻዕቢያዎቹ  የነ ስብሃት ቤተሰቦች  ለጥቅማቸው ለ50 ዓመታት  እንደፈለጉ ከ...
14/10/2025

መቀሌ የሚገኙ ታጣቂዎች ዓመፅ አስነስተዋል
የሃውልቲ የነ መንጆሪኖ ቢሮዎችን ከባዋል ፣ መንገዶችን ዘግተዋል
ሻዕቢያዎቹ የነ ስብሃት ቤተሰቦች ለጥቅማቸው ለ50 ዓመታት እንደፈለጉ ከአካል እስከ ነፍስ ሲያስገብሯቸው የነበሩ ወጣት ታጣቂዎች ዛሬ "በቃ" በሚል አምርረው ወተዋልና TPFም ሆነ የፌድራል መንግስት አስፈላጊውን ድጋፍ ሊያደርጉላቸው ይገባል። የህውሃት ሻዕቢያ አገዛዝ ለአንዴና ለመጨረሻ ግዜ ከኢትዮጵያ ምድር መወገድ አለበት ።

የአፍሪካ የዲፕሎማሲ ማዕከል፡ ኢትዮጵያ!አየህ ልዩነቱ! ትላንት የአስመራው መሪ የሱዳኑን ጦር ጄነራል ሲያገኙ፣ ዛሬ ደግሞ የኢትዮጵያው መሪ የሶማሊያን ፕሬዝዳንት በአዲስ አበባ ተቀብለው በቀጠ...
12/10/2025

የአፍሪካ የዲፕሎማሲ ማዕከል፡ ኢትዮጵያ!
አየህ ልዩነቱ! ትላንት የአስመራው መሪ የሱዳኑን ጦር ጄነራል ሲያገኙ፣ ዛሬ ደግሞ የኢትዮጵያው መሪ የሶማሊያን ፕሬዝዳንት በአዲስ አበባ ተቀብለው በቀጠናዊ ሰላምና ትብብር ላይ መከሩ። አንደኛው ወገን በችግርና በጦርነት ውስጥ ካሉ ወገኖች ጋር ሲገናኝ፣ ኢትዮጵያ ግን የቀጠናውን የወደፊት የጋራ ብልጽግና ከጎረቤት መሪ ጋር ትቀርጻለች። አዲስ አበባ የችግሮች መፍቻ እንጂ የችግሮች መስሪያ ቦታ አይደለችም። ልዩነቱ ይሄ ነው! ኢትዮጵያ የምስራቅ አፍሪካ የፖለቲካ ማዕከል መሆኗን በድርጊት እያስመሰከረች ነው። 😉

#ኤርትራ #ሱዳን #ኢሳይያስአፈወርቂ #ካሚልኢድሪስ #አፍሪካ #አስመራ #ከርቱም #ኤርትራሱዳን #አፍሪካውያን #የጂዮፖሊቲካ

New

የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ ቀለማት ትርጉም …18ኛው የሰንደቅ ዓላማ ቀን በነገው ዕለት በመላ ሀገሪቱ በተለያዩ ሁነቶች ይከበራል፡፡ቀኑ “ሰንደቅ ዓላማችን ለኢትዮጵያ ታላቅ የከፍታ ዘመን ብሥራት...
12/10/2025

የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ ቀለማት ትርጉም …
18ኛው የሰንደቅ ዓላማ ቀን በነገው ዕለት በመላ ሀገሪቱ በተለያዩ ሁነቶች ይከበራል፡፡
ቀኑ “ሰንደቅ ዓላማችን ለኢትዮጵያ ታላቅ የከፍታ ዘመን ብሥራት፣ ለብሔራዊ አንድነታችን፣ ለሉዓላዊነታችንና ለኢትዮጵያ ሕዳሴ” በሚል መሪ ሃሳብ ነው የሚከበረው፡፡
በኢፌዲሪ ሕገ መንግስት መሰረት የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ ቀለማት እና በሰንደቅ ዓላው መሀል ላይ የሚገኘው ዓርማ ትርጉም ምንድን ነው?
1. አረንጓዴው ቀለም፡- የሥራ፣ የልምላሜና የዕድገት ምልክት ነው፡፡
2. ቢጫው ቀለም፡- የተስፋ፣ የፍትሕና የእኩልነት ምልክት ነው፡፡
3. ቀዩ ቀለም ፡- ለነፃነትና ለእኩልነት መስፈን የሚደረግ የመስዋዕትነትና የጀግንነት ምልክት ነው፡፡
እንዲሁም በሰንደቅ ዓላማው መሀል ላይ የሚገኘው ዓርማ ትርጉም ከታች እንደሚከተለው ቀርቧል፡፡
1. ክብ የሆነው፡- ሰማያዊ መደብ ሰላምን ያመለክታል፡፡
2. ቀጥታና እኩል የሆኑት መስመሮች፡- የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች እንዲሁም የሐይማኖቶችን እኩልነት ያመለክታሉ፡፡
3. ቀጥታና እኩል ከሆኑት መስመሮች የተዋቀረው ኮከብ፡- የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች በመፈቃቀድ የመሠረቱትን አንድነት ያመላክታል፡፡
4. ቢጫ ጨረሩ ደግሞ ፡- በመፈቃቀድ አንድነት ለመሰረቱት ብሔር፣ ብሔረሰቦች የፈነጠቀውን ብሩህ ተስፋ ይጠቁማል፡፡

Address

Adama

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when GADAA Media ገዳ ሚድያ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share