GADAA Media ገዳ ሚድያ

GADAA Media  ገዳ ሚድያ Oduu Ammee ሰበር ዜናዎች

በአረንጓዴ አሻራ ዓለምን የሚያስደምም ስራ እየሰራን ነው - ከንቲባ አዳነች የአዲስ አበባ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር ዓለምን የሚያስደምም ስራ እየሰራን ነው አሉ፡፡ከ...
31/07/2025

በአረንጓዴ አሻራ ዓለምን የሚያስደምም ስራ እየሰራን ነው - ከንቲባ አዳነች

የአዲስ አበባ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር ዓለምን የሚያስደምም ስራ እየሰራን ነው አሉ፡፡

ከንቲባ አዳነች አቤቤ በአንድ ጀንበር 700 ሚሊየን ችግኞችን የመትከል መርሐ ግብር ላይ አረንጓዴ አሻራቸውን አኑረዋል፡፡

ከንቲባዋ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፥ አረንጓዴ አሻራ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥና አዲስ አበባን አረንጓዴ ለማልበስ እንዲሁም ለነዋሪዎቻችን ምቹ ለማድረግ ትልቅ ጠቀሜታ አለው፡፡

ማህበረሰባችን በጋራ ተስማቶ ከሰራቸው ስራዎች መካከል የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር አንዱ ነው ያሉት ከንቲባዋ፥ ሁላችንም በተባበረ ክንድ ችግኞቻችን በመትከል ታሪክ ልንሰራ ይገባል ሲሉ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡

በአንድ ጀንበር 700 ሚሊየን ችግኞች የመትከል መርሐ ግብር በመላው ኢትዮጵያ እየተካሄደ ይገኛል፡፡

Get ready👌👌
29/07/2025

Get ready👌👌

እርሶስ ተዘጋጅተዋል??
28/07/2025

እርሶስ ተዘጋጅተዋል??

Ethiopia food systems summit
26/07/2025

Ethiopia food systems summit

  ታሪካዊ አሻራችንን ለማሳረፍ እንዘጋጅ! ፟ቀረው
25/07/2025

ታሪካዊ አሻራችንን ለማሳረፍ እንዘጋጅ!

፟ቀረው

የጎርፍ ፖለቲካ ማህበራዊ ሚዲያውን አጨናንቆታል🥸  ጎርፍ እንኳን እኛ 3ኛው አለም ውስጥ ያለነውን ቀርቶ እጅግ ሠልጥነዋል በተባሉት ትልልቅ አገሮች ጭምር የተከሰትና ወደፊትም ሊከሰት የሚችል ...
24/07/2025

የጎርፍ ፖለቲካ ማህበራዊ ሚዲያውን አጨናንቆታል🥸

ጎርፍ እንኳን እኛ 3ኛው አለም ውስጥ ያለነውን ቀርቶ እጅግ ሠልጥነዋል በተባሉት ትልልቅ አገሮች ጭምር የተከሰትና ወደፊትም ሊከሰት የሚችል የተፈጥሮ አደጋ መሆኑ የታወቀ እውነት ነው::

አንዳንድ አውርቶ አደሮች ይህን በአለም ላይ የተከሰተ እና ወደፊትም ሊከሰት የሚችል የተፈጥሮ አደጋ መሆኑን ልቦናቸው እያወቀ በከተማችን እና በሀገራችን የተሰሩ አስደናቂ ልማቶችን ለማጠልሸት ሲሞክሩ .....🧐 ፋራ! ብለን ፈገግ ብለን እናያቸዋለን😂

Jawar Mohammed ሰርተህ ብላ!!

ኢትዮጵያን ከፍ የማድረግ ጉዞ እንደቀጠለ ነው!!ኢትዮጵያችን ከፍ ብላ እና በልፅጋ እንድትታይ አንድነታችንን በወንድማማችነት መርህ ላይ መገንባቱ ጠቅሞናል። አንድነታችን በመጠናከር ልማቶችን አ...
23/07/2025

ኢትዮጵያን ከፍ የማድረግ ጉዞ እንደቀጠለ ነው!!
ኢትዮጵያችን ከፍ ብላ እና በልፅጋ እንድትታይ አንድነታችንን በወንድማማችነት መርህ ላይ መገንባቱ ጠቅሞናል። አንድነታችን በመጠናከር ልማቶችን አየፈጠን ሀገራችን በሁሉም ከፍ እንድትል መድረግ ነው!!እኛ ኢትዮጵያን ከተባበርን ዓለምን የሚቀይር አቅም በውስጣችን አለ።የሀገራችንን ፖለቲካ በወንድማማችነት መርህ ላይ በመመስረት ሀገራችንን በማንም የማትደፈር ኩሩ ህዝብ እንዳላት ለዓለም ማሳየት ከእያንዳንዱ ዜጋ ይጠበቃል!

የኢትዮጵያ ልጆችና ወዳጆች በጎ ዜናዋን ለማብሰር ስንሽቀዳደም የኢትዮጵያ ጠላቶችና የጠላቶቿ ተለላኪ የሆኑ ባንዳዎች 24/7 የሟርት ዜና የሚያንበለብሉላት እናት ሃገሬ ኢትዮጵያ ፈተናዎችን በድ...
22/07/2025

የኢትዮጵያ ልጆችና ወዳጆች በጎ ዜናዋን ለማብሰር ስንሽቀዳደም የኢትዮጵያ ጠላቶችና የጠላቶቿ ተለላኪ የሆኑ ባንዳዎች 24/7 የሟርት ዜና የሚያንበለብሉላት እናት ሃገሬ ኢትዮጵያ ፈተናዎችን በድል እየቀየረች ወደፊት እየገሰገሰች ትገኛለች።

በፈረንጆች 2024/25 የበጀት ዓመት ኢትዮጵያ $32.1 ቢሊዮን የውጭ ምንዛሬ ገቢ ስታገኝ ከባለፈው የበጀት ዓመት ገቢ ማለትም ከ 2023/24 አኳያ ሲታይ የ $7.4 ቢሊዮን ዶላር ጭማሪ አሳይቷል። ኢትዮጵያ በፈረንጆች 2023/24 ያገኘችው አጠቃላይ የውጭ ምንዛሬ $24.7 ነበር።

═══════❁🇪🇹❁══════
ኢትዮጵያ ተስፋ አላት !!

ሰበር መረጃ!!የቀይ ባህር አፋር ዲሞክራሲያዊ ድርጅት በዳንካሊያ ክልል በቀይ ባህር አፋር ተወላጆች ላይ በኤርትራ መንግስት እየደረሰ ያለውን መንግስታዊ ድጋፍ እና የሽብር ዘመቻ ለአለም አቀፉ...
22/07/2025

ሰበር መረጃ!!

የቀይ ባህር አፋር ዲሞክራሲያዊ ድርጅት በዳንካሊያ ክልል በቀይ ባህር አፋር ተወላጆች ላይ በኤርትራ መንግስት እየደረሰ ያለውን መንግስታዊ ድጋፍ እና የሽብር ዘመቻ ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ እንዲያውቅ ይህን አስቸኳይ ጥሪ አቅርቧል። መግለጫዉ ከታች ተያይዟል👇

ኢትዮጵያ ተስፋ አላት የምንለው በትክክልም ተስፋ ስላላት ነው። ዓለምአቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በያዝነው የፈረንጆች ዓመት የኢትዮጵያ ጥቅል ሃገራዊ ምርት በ 6.6% ያድጋል የሚል ትንበ...
15/07/2025

ኢትዮጵያ ተስፋ አላት የምንለው በትክክልም ተስፋ ስላላት ነው።

ዓለምአቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በያዝነው የፈረንጆች ዓመት የኢትዮጵያ ጥቅል ሃገራዊ ምርት በ 6.6% ያድጋል የሚል ትንበያውን ሲያስቀምጥ የኢትዮጵያ መንግስት ደግሞ የእድገት ምጣኔውን 8.4% ለማድረግ ግብ ጥሎ 24/7 ያለእረፍት እየሰራ ነው።

═══════❁🇪🇹❁═══════
ኢትዮጵያ ተስፋ አላት !!

  ሰኔ 30 በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ  ቅዱስ ገብርኤል ቤተ-ክርስቲያን አካባቢ፤ ከቀኑ 11፡45 ላይ  የ10 እና የ7 ዓመት ዕድሜ ያላቸው ህፃን ለህፃናቱ ወላጅ እናት ለወ/ሮ ሃዊ ዮሴፍ ስ...
15/07/2025


ሰኔ 30 በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ቅዱስ ገብርኤል ቤተ-ክርስቲያን አካባቢ፤ ከቀኑ 11፡45 ላይ የ10 እና የ7 ዓመት ዕድሜ ያላቸው ህፃን ለህፃናቱ ወላጅ እናት ለወ/ሮ ሃዊ ዮሴፍ ስልክ በመደወል ህጻናቱን ማገቱንና 10 ሚሊዮን ብር ካልተሰጠው ልጆቹን እንደሚገድላቸው ይዝታል ወንጀለኞች በደወሉት ስልክ የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት የክትትል አባላት ቀንና ሌሊት ባደረጉት እልህ አስጨራሽ ሥራ፤ አጋቹን እና ሌሎች ተባባሪዎቹን ሐምሌ 5 ቀን 2017 ዓ/ም

ሁለቱንም ህጻናት በአዳማ ከተማ ልዩ ቦታው ቦሌ ሶሌ ሰፈር እየተባለ ከሚጠራ አካባቢ ታግተው ከተቀመጡበት ቤት ጉዳት ሳይደርስባቸው አስለቅቆ ከቤተሰቦቻቸው ጋር እንድያገናኙ ለአዲስ አበባ ፖሊስ ክትትል ብድን መሪ ኮማንደር ማርቆስ አስረክበዋል በነገራችን ለይቶ ትናንትና ይሄ ዜና የአዲስ አበባ ፖሊስ እንደሰራ ተደርገው ነበር የዘገበው ስራው ግን በብሔራዊ መረጃ ደህንነት የተሰራ እንጂ በአዲስ አበባ ፖሊስ የተሰራ አይደለም ፖሊስ የሰራው ነገር ብኖር የኦፐሬሽን ቀን ድገፍ መስጠት ብቻ ነበር ሀቁን ለባለቤት መስጠት ተገቢ ነው።

ለሽብር ተልዕኮ የተመለመሉ 82 የአይ ኤስ አባላት በቁጥጥር ስር ዋሉአዲስ አበባ፣ ሐምሌ 8፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ለሽብር ተልዕኮ የተመለመሉ 82 የአይ ኤስ አባላት በቁጥጥር ስር ዋሉ መዋ...
15/07/2025

ለሽብር ተልዕኮ የተመለመሉ 82 የአይ ኤስ አባላት በቁጥጥር ስር ዋሉ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 8፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ለሽብር ተልዕኮ የተመለመሉ 82 የአይ ኤስ አባላት በቁጥጥር ስር ዋሉ መዋላቸውን የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት አስታወቀ፡፡

አገልግሎቱ ለፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን በላከው መግለጫ እንዳመለከተው፥ በፑንትላንድ የሚንቀሳቀሰው የአይ ኤስ የሶማሊያ ክንፍ በተለያዩ ሀገራት እንዲሁም በኢትዮጵያ ለመስፋፋትና የሽብር ቡድኑን ሴሎች ለመመስረት የሚያደርገውን ጥረት በተመለከተ የመረጃ ስምሪትና ጥናት ሲደረግ ቆይቷል፡፡

በተለይም በኢትዮጵያ የሽብር መረብ ለመዘርጋት የሚያደርገውን ሙከራ በተመለከተ ከጅምሩ በመረጃና በማስረጃ ተደግፎ ጥብቅ ክትትል ሲያደርግ መቆየቱንም አገልግሎት መስሪያ ቤቱ ገልጿል፡፡

የሥጋት ደረጃውን በተመለከተ በየጊዜው ባከናወናቸው ግምገማዎች ተጋላጭነትን የሚያስከትሉና ወደ ብሔራዊ ደኅንነት ሥጋት የሚያድጉ ተጨባጭ ግኝቶች መለየታቸውንም ጠቁሟል፡፡

የተከናወነውን ተጨባጭ መረጃና ማስረጃ የማጠናቀር ሂደት ተከትሎ የሽብር ቡድኑ በፑንትላንድ አሰልጥኖ ወደ ተለያዩ የኢትዮጵያ አካባቢዎች ያሰማራቸው 82 ተጠርጣሪዎች ተለይተው ከፌዴራል ፖሊስና ከክልል የጸጥታ አካላት ጋር በመተባበር በቁጥጥር ስር ውለዋል፡፡

ከቡድኑ ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት ያላቸውና ሁለንተናዊ ድጋፍ ሲያደርጉ የነበሩ ተጠርጣሪዎች መካተታቸውን የጠቀሰው መግለጫው፥ በተለይ በዓለምአቀፍ የሽብር ቡድኑ በመረጃ ክንፍ የተደራጁ እንዲሁም በፋይናንስና በሎጀስቲክ እገዛ ሲያደርጉ የነበሩ ግለሰቦች በሕግ ቁጥጥር ስር መዋላቸውን አመልክቷል፡፡

የሽብር ቡድኑ የጥፋት ተልዕኮውን ለማስፋፋትና ምልመላ ለማከናወን የሃይማኖት ተቋማትንና ሃይማኖትን እንደ ሽፋን እንደሚጠቀምም ነው አገልግሎት መሥሪያ ቤቱ በመግለጫ ያመለከተው፡፡

የሕዝብን አንድነትና ተከባብሮ የመኖር እሴት የሚሸረሽሩ ብሎም ለአመጽና ሁከት የሚያነሳሱ አስተምህሮዎችን ለማስፋፋት ሙከራ ሲደረግ እንደነበር በተጨባጭ ማስረጃ መረጋገጡንም አስታውቋል፡፡

ተጠርጣሪዎቹ በአዲስ አበባ፣ በኦሮሚያ ክልል ሸገር ከተማ፣ አዳማ፣ ሃሮማያ፣ ሻሸመኔ፣ ባሌ፣ጅማና ሻኪሶ ከተማ ዙሪያ እንዲሁም በአማራ ክልል ከሚሴ አካባቢ፣ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ስልጤ ዞንና ሃላባ ቁሊቶ ከተማ፤ በሶማሌ ክልል ጅግጅጋ ከተማና በሐረሪ ክልል በቁጥጥር ውለዋል፡፡

ግለሰቦቹን ለመያዝ በተደረገው ስምሪት በየአካባቢው የሚገኘው ኅብረተሰብ ከደኅንነትና ከጸጥታ አካላት ጋር በመተባበር ያሳየው ተሳትፎ በመልካም አርዓያነት የሚጠቀስ ነው ብሏል፡፡
የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት በመግለጫው እንዳስታወቀው፥ በቁጥጥር ስር ያልዋሉ የሽብር ቡድኑ አባላት ላይ የሚደረገው ክትትል ተጠናክሮ ይቀጥላል፡፡

ኅብረተሰቡም በየአካባቢው ሰላምን የሚያደፈርሱና ስጋት ሊፈጥሩ የሚችሉ አጠራጣሪ ሁኔታዎችን ሲመለከት አንደ ሁልጊዜው ለሚመለከታቸው የደኅንነትና የጸጥታ አካላት ጥቆማውን በማቅረብ የዜግነት ግዴታውን እንዲወጣ አገልግሎቱ ጥሪ አቅርቧል፡፡

Address

Adama

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when GADAA Media ገዳ ሚድያ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share