16/10/2025
🇪🇹🇮🇳 የኢትዮጵያ እና የሕንድ የጋራ የመከላከያ ትብብር ያለበትን ደረጃ የሚገመግም የምክክር መድረክ በሕንድ ዋና ከተማ ኒውዴሊ ተካሂዷል የኢትዮጵያ እና የሕንድ የጋራ የመከላከያ ትብብር ሥምምነት አፈጻጸምን የሚገመግም የምክክር መድረክ በሕንድ ዋና ከተማ ኒውዴሊ በዛሬው እለት የተካሄደ ሲሆን መድረኩን የኢፌዲሪ መከላከያ የውጭ ግንኙነት ዋና ዳይሬክተር ሜጀር ጄኔራል ተሾመ ገመቹ እና የሕንድ መከላከያ ዓለምአቀፍ ትብብር ፀሐፊ አሚታባህ ፕራሳድ በጋራ መርተውታል።የሁለቱ ሃገራት የመከላከያ ተቋማት የስልጠና፣ የሕክምናና የመከላከያ ኢንዱስትሪ ትብብር ያለበት ደረጃ በጥልቀት የተገመገመ ሲሆን ሁለቱ ሃገራት የተፈራረሙትን ወታደራዊ የጋራ መግባቢያ ሥምምነት (MOU) ውጤታማ ለማድረግ በቀጣይ መሰራት ባለባቸው ጉዳዮች ዙሪያ የጋራ መግባባት ላይ ተደርሷል። India and Ethiopia today held their inaugural Joint Defence Cooperation (JDC) meeting in New Delhi, co-chaired by JS (IC) Shri Amitabh Prasad and Maj Gen Teshome Gemechu. The delegations reviewed ongoing defence cooperation and explored new avenues in training, joint exercises, medical collaboration, and defence industry engagement, further strengthening the framework established under the Defence Cooperation MoU signed earlier this year. 🇮🇳🤝🇪🇹