Ermias Ze Anathoth

Ermias Ze Anathoth Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Ermias Ze Anathoth, Digital creator, Addis Ababa.

ገብረ ሥላሴ፤ የሥላሴ ባሪያ

ꍟꂦ꓄ꉓ ✝️ - ȶɦɛ ȶʀʊɛ քǟȶɦ օʄ ʟɨɢɦȶ

ወለነሰ ተሣየጠነ ክርስቶስ እመርገማ ለኦሪት በዘወድአ በእንቲአነ ወጾረ መርገማ እስመ ከመዝ ይቤ መጽሐፍ “ርጉም ውእቱ ኵሉ ዘስቁል ዲበ ዕፅ።” ገላ ፫፥፲፫

“በእንጨት የሚሰቀል ሁሉ የተረገመ ነው ተብሎ ተጽፎአልና ክርስቶስ ስለ እኛ እርግማን ሆኖ ከሕግ እርግማን ዋጀን” ገላትያ 3፥13

25/12/2025

I would like to extend my heartfelt Christmas greetings to all Christians living in South and West Africa, as well as to Christians all over the world, who celebrate the Feast of the Nativity of our Savior Jesus Christ on December 25 each year.

Just as on the day of the Lord’s birth, when angels and humankind - heaven and earth - were united in joy and praise (Luke. 2-13), so too today, as Christians who are called by His holy name (Acts. 3-16) and who serve as ambassadors of Christ, let us leave behind the time we have spent in division and hostility. Let us proclaim the song of peace (2-14). And just as the world was delivered from darkness through the Lord’s birth (Matthew. 4፥16), by remembering His holy Nativity, let us strive for good works and fill our world with the true joy of Christ.

May God bless us all.

Merry Christmas!

+Abba Henok Archbishop

ለቤተ አእላፍ ወ  #አእላፋት የምለውደብተራ በአማን ነጸረ እንደጻፉት፩. የትራንስፖርት አቅርቦት ቢመቻችና ዝማሬው ከማኅሌት ሰዓት ቀደም ብሎ ቢጠናቀቅ ጥሩ ነው። ዝማሬው ላይ ያመሹት ልጆች ከ...
19/12/2025

ለቤተ አእላፍ ወ #አእላፋት የምለው
ደብተራ በአማን ነጸረ እንደጻፉት

፩. የትራንስፖርት አቅርቦት ቢመቻችና ዝማሬው ከማኅሌት ሰዓት ቀደም ብሎ ቢጠናቀቅ ጥሩ ነው። ዝማሬው ላይ ያመሹት ልጆች ከቅዳሴ እንዳይቀሩ። ቅዳሴው መንፈቀ ሌሊት ስለሚጀምር። በተግባርም ወጣቶች ለማስቀደስ በድካም ሲቸገሩና በቅዳሴው ሳሳ ብለው ስላየሁ።

፪. ሁሉንም ትችት በአንድ ሚዛን አትመዝኑት። የሚወሰደውን ውሰዱ። እስክትነጥሩ እሳቱ ይነዳል። በሕግ ቋንቋ ገና Probation period ላይ ናችሁ።

፫. ከቤተ ክርስቲያን መዋቅር ተናበቡ። ከነድክመቱና ከነቅሬታችን መዋቅሩን ማክበር ግድ ነው።

፬. አገልግሎታችሁ የምስጋና ጊዜ ከመጨመር በቀር የትኛውንም መደበኛ የቅዳሴና ውዳሴ አገልግሎት አይተካም። ይሄን አታጡትም።

፭. ጸልዩ። በግልም በማኅበርም ስለአገልግሎታችሁ መቃናት ጸልዩ። አባቶችንም በጸሎት ርዱን በሉ።

#ምርቃት :- ታናናሾቼ ስለምትበዙ ልመርቅ፥ አገልግሎታችሁን ለበረከት ያድርግላችሁ። የልብ ቅንነታችሁን ተመልክቶ ለሀገራችን ምሕረቱን ይላክልን። አሜን።

#ማስታወሻ:- በዚህ ጉዳይ በተከታታይ ለሁለት ዓመታት በቂ ንትርክ ስላደረግሁ ለተጨማሪ ምልልስ አቅምም ፍላጎትም የለኝም።

“በክፋታቸው እውነትን ዐፍነው በሚይዙ፣ በዐመፃቸውና በክፋታቸው ሁሉ ላይ የእግዚአብሔር ቍጣ ከሰማይ ይገለጣል” ሮሜ 1፥18
28/11/2025

“በክፋታቸው እውነትን ዐፍነው በሚይዙ፣ በዐመፃቸውና በክፋታቸው ሁሉ ላይ የእግዚአብሔር ቍጣ ከሰማይ ይገለጣል” ሮሜ 1፥18



የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቃለ ዓዋዲ (የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ አቋቋም ሥርዓት አንቀጽ 2(ሀ)) የሰበካ ጉባኤን አባላት አደረጃጀት በግልጽ አስቀምጧል። ጉባኤው ቤተክርስቲያንን በዕውቀታቸው፣ በጉልበታቸው፣ በሀብታቸውና በአገልግሎታቸው የሚረዱ ካህናት፣ ምእመናንና የሰንበት ት/ቤት ወጣቶች ስብስብ ነው። ይህ የሥርዓት መሠረት ለምርጫው ሕጋዊነት ወሳኝ ነው።

የእንጦጦ መንበረ ስብሐት ቅድስት ሥላሴ ቤተክርስቲያን አስተዳደር አካል ይህን መሠረታዊ መርህ በመጣስ ኅዳር 14 ቀን 2018 ዓ.ም. ያደረገው ምርጫ ትክክል ያልሆነና ሕገወጥ ያደረጉት ጠንካራና ተጨባጭ ማስረጃዎች የሚከተሉት ናቸው።

#ክፍል ፩፡ (Procedural Violations)
1.1.
የሕግ ጥሰት: ቃለ ዓዋዲው የሚያመለክተው ሰበካ ጉባኤ የሁሉም ምእመናን ስብስብ መሆኑን ነው።

✍️የተፈጸመው ጥፋት: ምርጫው ከመድረሱ በፊት ስለሰበካ ጉባኤ አስፈላጊነትና ጥቅም ለጠቅላላው ምእመናን በቂ የግንዛቤ ማስጨበጫ (ማስተማሪያ/ቅስቀሳ) ሥራ አልተሰራም። በተለይም በደብሩ የሚገኙ ካህናት የንስሐ ልጆቻቸውን ለምርጫው እንዲያዘጋጁና እንዲያነሳሱ ምንም ዓይነት የተቀናጀ ሥራ አለመሥራቱ፣ የምርጫው ዓላማ የግለሰብ ፍላጎት እንጂ ሰፊ የምእመናን ተሳትፎ አለመሆኑን ያሳያል።

1.2.
የሕግ ጥሰት: ምእመናን የመምረጥና የመመረጥ መብታቸው እንዲከበር ማድረግ የአስመራጭ ኮሚቴው ዋና ተግባር ነው።

✍️የተፈጸመው ጥፋት: ለምዝገባ የተመደቡ አካላት የአካባቢውን ምእመናን በአግባቡ ባለማስተናገድ (ሆን ተብሎ ቢሮዎችን ዝግ በማድረግ)፣ በርካታ ምእመናን መመዝገብ ሳይችሉ ተመልሰዋል። ይህ ድርጊት የተመረጡ ግለሰቦች ብቻ እንዲመዘገቡ በማሰብ በሕዝብ ተሳትፎ ላይ ሆን ተብሎ የተፈጸመ እንቅፋት ነው።

1.3.
የሕግ ጥሰት: ሰበካ ጉባኤ በማኅበርና በጉባኤ የሚገለገለውን ምእመን ያጠቃልላል።

✍️የተፈጸመው ጥፋት: በአጥቢያው የሚገኙ በርካታ እድሮችና ሌሎች መንፈሳዊ ማኅበራት ለምርጫው በአግባቡ አልተጠሩም፣ ወይም የተሳትፎ መረጃ አልተሰጣቸውም። የደብሩ አስተዳደር እድሮችን የሚጠራው ለመቃብር ጽዳት ብቻ ነው የሚል ጥያቄ ምእመናን እንዲያነሱ መደረጉ፣ አስተዳደሩ የሰበካ ጉባኤን ምንነትና አስፈላጊነት እንዴት እንደሚመለከተው ያሳያል።

#ክፍል ፪፡
(Ethics & Canonical Violations)
2.1.
የሕግ ጥሰት: ምርጫ ምስጢራዊ፣ ፍትሐዊና ከማንኛውም ጫና ነፃ መሆን አለበት።

✍️የተፈጸመው ጥፋት: የምርጫው ዋዜማ ለተለያዩ አካላት "እገሌን ምረጡ" በሚል ጥሪ የድጋፍ ቅስቀሳ ሲደረግ ማምሸቱ ግልጽ የምርጫ ሥነ-ምግባር ጥሰት ነው። በተለይም ዕድሜያቸው ላልደረሱ ሕፃናት ሁሉ የምርጫ ካርድ በገፍ ሲታደል መታየቱ፣ የምርጫውን ሕጋዊነትና ፍትሐዊነት ሙሉ በሙሉ ያሳጣዋል።

2.2.
የሕግ ጥሰት: አስመራጭ ኮሚቴ በገለልተኝነትና በፍትሐዊነት መመሥረት አለበት።

✍️የተፈጸመው ጥፋት: አስመራጭ ኮሚቴው የተመሠረተው ዕድሉን ቀድመው ለተመረጡ ሰዎች ቅድሚያ በመስጠት ነው። ከምርጫው ቀን በፊት በተደረገ ምክክር የተወሰኑ ግለሰቦችን ይዞ የመምጣት ድርጊት መፈጸሙ ምርጫው ከመደረጉ በፊት ውጤቱ አስቀድሞ ተወስኗል የሚለውን ጥርጣሬ አጠናክሮታል።

2.3.
የሕግ ጥሰት: የደብሩ አስተዳዳሪ ማንኛውንም ምእመን በአድልዎ መመልከት አይችሉም።

✍️የተፈጸመው ጥፋት፦ ዋና አስተዳዳሪው በምርጫ ዕለት "ከቅጥር ካህናትና ዲያቆናት ውጪ ሌላ ዲያቆን የለም፣ ማኅበርም የለም። ከዚህ ውጪ መምረጥ ይችላል፤ መመረጥ አይችልም።" ማለታቸው፣ የአጥቢያውን ማኅበራት መብትና ሕልውና የካደ፣ ሆን ተብሎ የማኅበረ ዲያቆናት ማኅበርን ጨምሮ ሌሎች ማኅበራትን ከምርጫው ውጪ ለማድረግ የተደረገ ሕገወጥ ሙከራ ነው።

2.4. #የሰንበት
የቃለ ዓዋዲ መጣስ: ቃለ ዓዋዲው ከሰንበት ት/ቤት የሚመረጡ አባላት ዕድሜያቸው ከ18-35 ዓመት መሆን እንዳለበት ያዛል።

✍️የተፈጸመው ጥፋት: በዕለቱ የተመረጡት ግለሰብ ዕድሜያቸው በቃለ ዓዋዲው ከተቀመጠው በላይ መሆኑ ግልጽ ማስረጃ ነው። ሰንበት ት/ቤቱ ይህንን ግለሰብ እንዲመርጥ መደረጉ "ሰው አጥቶ ነው ወይስ የተለየ ነገር አለ?" የሚለውን የሙስና እና የሥርዓት መጣስ ጥርጣሬ ያጭራል።


(Conclusion and Call for Action)
ከላይ በተዘረዘሩት የሂደት ጥሰቶች፣ የማጭበርበር ተግባራት እና የቃለ ዓዋዲ አንቀጾች ግልጽ መጣስ ምክንያት፣ በእንጦጦ መንበረ ስብሐት ቅድስት ሥላሴ ቤተክርስቲያን የተደረገው የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ምርጫ ሕጋዊ ያልሆነ፣ ፍትሐዊ ያልሆነ እና መሻር ያለበት ነው ብለን እንፈርጃለን።



✍️እኛ ማኅበረ ዲያቆናት የተመሠረትነው የአብነት ት/ቤቶችን በማቋቋም፣ የቤተ ክርስቲያናችንን ተደራሽነት በማስፋትና የተቸገሩ አብያተ ክርስቲያናትን በመደገፍ የመንፈሳዊ አገልግሎት ዓላማዎችን ለማሳካት ነው።

ስለሆነም ከላይ በዝርዝር በተቀመጡት ምክንያቶች ሕገ ወጥ ነው ብለን የፈረጅነው የሰበካ ጉባኤ ምርጫ በሚመለከተው የበላይ አካል ተሽሮ ሕገ ቤተ ክርስቲያኑ በሚፈቅደው መልኩ የሕዝብ ተሳታፊነት ያለበት ምርጫ እንዲደረግ እንጠይቃለን ።

21/11/2025

"ነገር ግን በእውነት ጽሑፍ የተጻፈውን እነግርሃለሁ በዚህም ነገር ከአለቃችሁ ከሚካኤል በቀር ማንም የሚያጸናኝ የለም።” ዳን ፲፥፳፩

"... ፍጡነ ይርከበነ ሣህልከ እግዚኦ፤ አቤቱ ይቅርታህ ፈጥኖ ይደረግልን" ቅ.ዲዮስቆሮስ ቁ-፸ተገድሎ የማያልቀው ሕዝብ ዛሬም በአርሲ መከራና ስቃይ ውስጥ ይገኛል። አቤቱ ጌታ ሆይ ማረን 😢
09/11/2025

"... ፍጡነ ይርከበነ ሣህልከ እግዚኦ፤ አቤቱ ይቅርታህ ፈጥኖ ይደረግልን" ቅ.ዲዮስቆሮስ ቁ-፸

ተገድሎ የማያልቀው ሕዝብ ዛሬም በአርሲ መከራና ስቃይ ውስጥ ይገኛል።

አቤቱ ጌታ ሆይ ማረን 😢

08/11/2025

"ጽንዕት በድንግልና ሥርጉት በቅድስና እመቤታችን ይህች ሰንበት የመከራችን ፍጻሜ ትሆን ዘንድ ለምኚልን።" 🌹

ሰላም ሰላም ለልደትከ እንግዳእምነ ማርያም ድንግል ውስተ ቤተልሔም ዘይሁዳሠራዬ ኃጢአት ክርስቶስ ወመቅለሌ ዕፁብ ዕዳልደትከ ሶበ ተሰምዐ ለኢየሩሳሌም በዐውዳሰብዓ ጢሮስ ለንግሥከ አወፈዩ ጋዳ ...
07/11/2025

ሰላም ሰላም ለልደትከ እንግዳ
እምነ ማርያም ድንግል ውስተ ቤተልሔም ዘይሁዳ
ሠራዬ ኃጢአት ክርስቶስ ወመቅለሌ ዕፁብ ዕዳ
ልደትከ ሶበ ተሰምዐ ለኢየሩሳሌም በዐውዳ
ሰብዓ ጢሮስ ለንግሥከ አወፈዩ ጋዳ

ተዝካረ ልደቱ ለእግዚእነ ወመድኃኒነ ኢየሱስ ክርስቶስ

እንኳን አደረሰን !

… ምሕረትህ በቶሎ ታግኘን፥ እጅግ ተቸግረናልና። 💔😢🥺
05/11/2025

… ምሕረትህ በቶሎ ታግኘን፥ እጅግ ተቸግረናልና። 💔😢🥺

“የባሪያዎችህንም በድኖች ለሰማይ ወፎች መብል አደረጉ፥ የጻድቃንህንም ሥራ ለምድር አራዊት፤” መዝሙር 79፥2

…. ምሕረትህ በቶሎ ታግኘን፥ እጅግ ተቸግረናልና።

"አሳዳጆቻችን በአንገታችን ላይ ናቸው፤ እኛ ደክመናል ዕረፍትም የለንም።" ሰቆ ኤርምያስ 5:5
04/11/2025

"አሳዳጆቻችን በአንገታችን ላይ ናቸው፤ እኛ ደክመናል ዕረፍትም የለንም።" ሰቆ ኤርምያስ 5:5

ሰላም ዕብል ለአክናፊከ ስድስቱ፤ዘመንገለ የማን ሠለስቱ፤ወመንገለ ፀጋም ሠለስቱ ተክለሃይማኖት ወልድከ በረከተከ ይፈቱ፤ሶበ ኀሠሠከ ጊዜ ኀደጎ ዕለቱ፤ለረድኤቱ ክንፈከ አስተፋጥን ሎቱ።እናንተ የ...
02/11/2025

ሰላም ዕብል ለአክናፊከ ስድስቱ፤
ዘመንገለ የማን ሠለስቱ፤
ወመንገለ ፀጋም ሠለስቱ ተክለሃይማኖት ወልድከ በረከተከ ይፈቱ፤
ሶበ ኀሠሠከ ጊዜ ኀደጎ ዕለቱ፤
ለረድኤቱ ክንፈከ አስተፋጥን ሎቱ።

እናንተ የምድር ጨው ናችሁ (ማቴ 5፥13) እንዳለ ጌታ ዓለምን ካለማመን ወደ ማመን የመለሱ ሐዲስ ሐዋርያ የጣዖታትን ቤት በቃለ እግዚአብሔር መዶሻ ያፈረሱ አቢያተ ክርስቲያናትን በወንጌል መሠረት ያነፁ ቅዱስ አባታችን ተክለሃይማኖት ረድኤት በረከታቸው አይለየን !

የጻድቁ በረከት ይጠብቀን

💚💛❤ አሜን 💚💛❤

ማኅበረ ሐዋርያት ሰባክያን ….
02/11/2025

ማኅበረ ሐዋርያት ሰባክያን ….

ማኅበሩ በዛሬው ዕለት ባደረገው ጠቅላላ ጉባኤ ከግማሽ ሚሊዮን ብር በላይ ለ 2018 ዓ.ም ሐምሌ ቅዱስ ገብርኤል በዓል ማክበሪያ ከአባላቱ መሰብሰብ ችሏል !

ጥቅምት 23 ቀን 2018 ዓ.ም

ማኅበረ ዲያቆናት ዘሽሮሜዳ ሥላሴ በዛሬው ዕለት ባካሄደው 7ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ በተለያዩ የቤተ ክርስቲያናችን የአገልግሎት ጉዳዮች ላይ መክሯል።

በዚህም በገጠራማ የሀገሪቱ ክፍሎች የሚገኙ የተቸገሩ አብያተ ክርስቲያናትን እንዲሁም የአብነት ትምህርት ቤቶችን ከዚህ ቀደሙ በተሻለ ሁኔታ መደገፍ የሚችልበትን አቅጣጫ ያስቀመጠ ሲሆን በደቡብ ኢትዮጵያ ለሚያገለግሉ አንድ የአብነት መምህር የአንድ ዓመት ደመወዝ አጽድቋል።

ማኅበራችን በ 2017 ዓ.ም በጀት ዓመት በደብራችን የአብነት ትምህርት ቤት ለማስገንባት ብዙ እንቅስቃሴዎችን ያደረገ ቢሆንም በተለያዩ ችግሮች ምክንያት ዕቅዱን ሳያሳካ ቀርቷልተ

እንደሚታወቀው ከ 2012 ዓ.ም. ጀምሮ በደብራችን መከበር በተጀመረው የሐምሌ ቅዱስ ገብርኤል በዓል ማኅበሩ ታላላቅ የአብነት መምህራንን በመጋበዝ ሥርዓተ ማኅሌቱ ይትበሃሉን ጠብቆ በታላቅ ድምቀት እንዲከበር በኃላፊነት ሲሠራ ቆይቷል።

በዛሬው ዕለትም ለሐምሌ 2018 ዓ.ም ቅዱስ ገብርኤል በዓል ማክበሪያ ከአባላቱ ከግማሽ ሚሊዮን ብር በላይ ለማግኘት ተችሏል።

ኢንኅድግ ማኅበረነ !

29/10/2025

“ስለ አንተ ቀኑን ሁሉ እንገደላለን፥ እንደሚታረዱ በጎች ተቆጠርን።” ሮሜ ፰፥፴፮

በአርሲ ሀገረ ስብከት በኖኖ ጃዊ ቀበሌ ፲፬ ኦርቶዶክሳውያን በአሰቃቂ ሁኔታ መገደላቸው ተሰምቷል።

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ አብዝተን እየተለማመድነው የመጣነው የኦርቶዶክሳውያን ሞት ሊበቃ እና የሰው ልጆች ሁሉ የመኖር ሰብዓዊ መብት ሊረጋገጥ ይገባል።

በአካባቢው የሚገኙ ባለድርሻ አካላት በተደጋጋሚ በአማኙ ላይ የሚሰነዘረውን ጥቃት ሊያስቆሙ እና መፍትሔ ሊያበጁለት ይገባል።

ለወደፊቱም ቢሆን እንደ ቤተ ክርስቲያን የሚጠበቁብንን በርካታ ሥራዎች አለመሥራታችን ትውልዱን ዋጋ እያስከፈለው እንዳይኖር ጥንቃቄ በተሞላበት መልኩ መሥራት የሚገባን አያሌ ተግባራት መኖራቸውን መዘንጋት የለብንም።

በግፍ ለተገደሉ ወገኖቻችን ዕረፍተ ነፍስን ያድልልን፤ ለቤተሰቦቻቸው አጽናኝ ቅዱስ መንፈስን ይላክላቸው።

እግዚአብሔር ኢትዮጵያን ይባርክ !

Address

Addis Ababa

Telephone

+251910193560

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ermias Ze Anathoth posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Ermias Ze Anathoth:

Share