Ermias Ze Anathoth

Ermias Ze Anathoth Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Ermias Ze Anathoth, Digital creator, Addis Ababa.

በልባችን ይገባና የኃጢአትን መሠረት ያጠፋ ዘንድ የሚቻለው፤ የሰው ልጆች ወዳጅ መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በደጅ ቆሞአል። በቤተ ፋጌ ዓለም በተራራው ዲያብሎስ አጠገብ የምንገኝ እኛን ከማዕ...
05/04/2026

በልባችን ይገባና የኃጢአትን መሠረት ያጠፋ ዘንድ የሚቻለው፤ የሰው ልጆች ወዳጅ መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በደጅ ቆሞአል። በቤተ ፋጌ ዓለም በተራራው ዲያብሎስ አጠገብ የምንገኝ እኛን ከማዕሠረ ኃጢአት ይፈታ ዘንድ ወዳጆቹን ልኳል። ልዑል የሆነው ዘንባባ ብቻ የሚቀርብለት አይደለም በእሳት የማይቃጠል ሌቦች ቆፍረው የማይሰርቁት ሰማያዊ ሀብት በደጁ ያለ ነው።

የሆሣዕናው ንጉሥ እንደ ኢዩ የሚያልፍ ጨርቅ የምናነጥፍለት አይደለም የልባችንን በር የምንከፍትለት ነው፤ እንደ እስራኤል ንጉሥ በሰዎች አንደበት ብቻ የሚመሰገን አይደለም ሕጻናትና መላእክት የሚያመሰግነት ነው።

በክብር የመጣው ንጉችን አህያይቱንና ውርንጫዋን አልናቃቸውም፣ ታዲያ እንዴት እኛን ይጠየፈናል? በሰው ዘንድ ብንናቅም በክብር ጌታ ዘንድ ክቡራን ነን፤ በኃጢአት ብንወድቅም የሚያነሳን አባት አለን፤ በሆሣዕና አክብሮ በአርብ በሚሰቅል ዓለም መጽናኛችንና መተማመኛችን በልባችን ቤተ መቅደስ የምናከብረው፤ አንጽሖት እንዲያደርግልን በእልልታና በምስጋና ወደ ሰውነታችን ቤተ መቅደስ የምንጠራው የሆሣዕናው ጌታ የእኛ የተናቅነው መነሻችን፣ ከምንፈራው መደበቂያችን፣ ከጨለማ መውጫ ብርሃናችን ክርስቶስ ኢየሱስ ነው ደግሞ ካለፈው ዓመት ላይ ወደ ልባቸው ቢመለሱ ብሎ አንድ ዓመት የንስሐ እድሜ ጨምሮ ለዚህ አደረሰን ክብር ለስሙ ይሁን !

+ ብፁዕ አቡነ ሄኖክ ሊቀ ጳጳስ እንደጻፉት እንኳን ለበዓለ ሆሣዕና በሰላምና በጤና አደረሰን አደረሳችሁ !

31/03/2026
“የማታስተውሉ የገላትያ ሰዎች ሆይ፥ በዓይናችሁ ፊት ኢየሱስ ክርስቶስ እንደ ተሰቀለ ሆኖ ተሥሎ ነበር፤ ለእውነት እንዳትታዘዙ አዚም ያደረገባችሁ ማን ነው?” ገላትያ 3:1
19/03/2026

“የማታስተውሉ የገላትያ ሰዎች ሆይ፥ በዓይናችሁ ፊት ኢየሱስ ክርስቶስ እንደ ተሰቀለ ሆኖ ተሥሎ ነበር፤ ለእውነት እንዳትታዘዙ አዚም ያደረገባችሁ ማን ነው?” ገላትያ 3:1

"በመቃብር ያሉቱ ሁሉ ድምፁን የሚሰሙበት ሰዓት ይመጣል" ዮሐንስ ፭፥ ፳፰ትንሣኤን ተስፋ በማድረግ ከመጽናናት በቀር አንድም ቃል ሊያወጡለት የማይቻል መሪር ሐዘን። እግዚአብሔር መጽናናቱን ያድ...
17/03/2026

"በመቃብር ያሉቱ ሁሉ ድምፁን የሚሰሙበት ሰዓት ይመጣል" ዮሐንስ ፭፥ ፳፰

ትንሣኤን ተስፋ በማድረግ ከመጽናናት በቀር አንድም ቃል ሊያወጡለት የማይቻል መሪር ሐዘን።

እግዚአብሔር መጽናናቱን ያድለን !

15/03/2026

The Indian Malankara Orthodox Church and the Ethiopian Orthodox Tewahedo Church in Stoke-on-Trent, United Kingdom, held a meeting to discuss working together in the area.

Fr. Happy Jacob, the Vicar of St. John the Baptist Indian Orthodox Church, warmly welcomed the delegation.

Dn. Ermias (Jeremiah) and Mr. Daniel represented St. Rufael and Abune Echege Yohannes Ethiopian Orthodox Tewahedo Church. They met with the main Vicar and the Trustees of the church.

During the discussion, they explored ways to work together and made plans for proper collaboration as Oriental Orthodox Churches in the region.

" … ሁሉም ከንቱ ነው" መክ ፫፥፲፱
10/03/2026

" … ሁሉም ከንቱ ነው" መክ ፫፥፲፱

08/03/2026

“ወይትነሥኡ ምዉታን መቅድመ እለ ሞቱ በሃይማኖተ ክርስቶስ፤ … በክርስቶስ የሞቱትም አስቀድመው ይነሣሉ" ፩ ተሰ ፬፥፲፮

የመምህር ዘለዓለም ወንድሙን ዕረፍት የሰማነው በታላቅ ሀዘን ነው።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ካሏት ዕንቁ የወንጌል መምህራን መካከል ግንባር ቀደም የሆነው መምህር ዘለዓለም፤ በቃሉ ብቻ ሳይሆን በሕይወቱም ጭምር ወንጌልን ሕይወት አድርጎ የኖረ ወንድም ነው።

መምህር ዘለዓለም የመንግስቱን ወንጌል ከገጠር እስከ ከተማ፣ ከሀገር ውስጥ እስከ ባሕር ማዶ የሰበከ፤ ለአገልግሎት የማይደክም፣ ለቤተክርስቲያን የሚቀና፣ ለሰዎች አብነት የሚሆን፣ የበጎ ሥራ ባለቤት፣ የእግዚአብሔርን ትዕዛዛት ፈጻሚ፣ በሁሉ ዘንድ የተወደደ ጸጋ እግዚአብሔር የበዛለት ሐዋርያ ነበር።

"ለእኔ ሕይወት ክርስቶስ ሞትም ጥቅም ነውና" (ፊልጵ ፩፥፳፩) እንዳለ ቅዱስ ጳውሎስ መ/ር ዘለዓለም ዘመኑን ሁሉ ሲሰብከው ከኖረው አምላኩ ጋር ሕይወት ስላለው ሞትን መሸጋገሪያና መጠቀሚያ አድርጎ ለዘለዓለም ዕረፍትና ሕይወት ተጠርቶ መንገዱን ከአባቶቻችን ጋር ወደላይ አድርጓል።

ከምንም በላይ ሊያጽናናን የሚገባው ነገር "በመበስበስ ይዘራል ባለመበስበስ ይነሳል፤ በውርደት ይዘራል በክብር ይነሳል ... " (፩ ቆሮ ፲፭፥፵፭) በተባለው የሐዋርያው ቃል መሠረት የመምህር ዘለዓለም መጠራት ለክብር ትንሣኤ በመሆኑ ነው።

ለመላው ኦርቶዶክሳውያን፣ ለመ/ር ዘለዓለም ቤተሰቦች ወዳጅ ዘመዶች ሁሉ ጌታ አጽናኝ ቅዱስ መንፈስን እንዲልክ እየተመኘሁ የወንድማችንን ወልደ ሰማዕትን ነፍስ በአብርሃም በይስሐቅ በያዕቆብ ዕቅፍ ያሳርፍልን።

+ አባ ሄኖክ ሊቀ ጳጳስ

01/03/2026
14/02/2026

"ሥሉስ ቅዱስ ቅረቡኒ ለተሣህሎ"

"ከመዝኑ እንከ መሪር ውእቱ ሞት፤ በውኑ ሞት እንደዚህ መራራ ነውን?" ፩ ሳሙ ፲፭፥፴፪እጅግ ሩኅሩኅ፣ ደግ ሁሉን ወዳድ እና ጸሎተኛው ወንድሜ እና አባቴ ብእሴ እግዚአብሔር ብፁዕ አቡነ ዕንባ...
26/01/2026

"ከመዝኑ እንከ መሪር ውእቱ ሞት፤ በውኑ ሞት እንደዚህ መራራ ነውን?" ፩ ሳሙ ፲፭፥፴፪

እጅግ ሩኅሩኅ፣ ደግ ሁሉን ወዳድ እና ጸሎተኛው ወንድሜ እና አባቴ ብእሴ እግዚአብሔር ብፁዕ አቡነ ዕንባቆም ከዚህ ዓለም ድካም ማረፋቸውን የሰማሁት በታላቅ ሀዘን ነው።

በተለይም በዚህ ወቅት ብፁዕ አቡነ ዕንባቆምን ማጣት እጅግ አስቸጋሪ ነው፤ ሐዋርያው "በሕይወት ሆነን ብንኖር ለጌታ እንኖራለንና፥ ብንሞትም ለጌታ እንሞታለን፤ እንግዲህ በሕይወት ሆነን ብንኖር ወይም ብንሞት የጌታ ነን" (ሮሜ ፲፬፥፰) እንዳለ ብፁዕነታቸው በዘመናቸው ሁሉ ራሳቸውን ለክርስቶስ ሰጥተው በሕይወት ኖረው የክርስቶስ መሆናቸውን ያስተማሩን ሲሆን ዛሬም በዕረፍታቸው የክርስቶስ መሆናቸውን መመልከት ይቻላል።

ብፁዕ አቡነ ዕንባቆም በተለይም በደቡብ ኦሞ ሀገረ ስብከት በነበራቸው አገልግሎት በርካታ ነፍሳት የሥላሴን ልጅነት እንዲያገኙ ያደረጉት አስተዋጽኦ ቀላል አልነበረም፤ እንዲሁም በሌሎች አህጉረ ስብከትና በኢየሩሳሌም ገዳማትም ጭምር የሰጡት አገልግሎት ሰፊና ዘርፈ ብዙ ነበር።

የብፁዕነታቸው የመጨረሻዎቹ የአገልግሎት ጊዜያት በሕመምና በተለያዩ ጉዳዮች ታጥሮ የነበረ መሆኑ ልባችንን የሚያቆስል ክስተት ቢሆንም ከብዙ ድካምና ያልተቋረጥ አገልግሎት በኋላ በክርስቶስ የሞቱትም አስቀድመው ይነሳሉ ( ፩ ተሰ ፬፥፮) በሚለው የተስፋ ቃል ትንሣኤ ሙታንን ተስፋ በማድረግ በክርስቶስ ኢየሱስ ዕቅፍ ከዚህ ዓለም ድካም አርፈዋል።

ለመላው የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት፣ በኢየሩሳሌም ገዳማት ለሚኖሩ አባቶችና እናቶች፣ ለምእመናንና ምእመናት እንዲሁም ለብፁዕነታቸው ወዳጅ ዘመዶች ሁሉ መጽናናትን እንመኛለን።የብፁዕነታቸው በረከት አይለየን !

+ አባ ሄኖክ
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን
የደቡብና ምዕራብ አፍሪካ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ

ጥር ፲፰ ቀን ፳፻፲፰ ዓ.ም
ጆሐንስበርግ፤ደቡብ አፍሪካ

በቦስትዋና ጋቦርኔ የሚገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ልጆች ያሳነጹት የመጀመሪያው የሊቀ ሰማዕታት ቅዱስ ጊዮርስ ቤተ ክርስቲያን ተባርኮ ቅዳሴ ቤቱ በድምቀት ተከብሮአል።ብፁ...
25/01/2026

በቦስትዋና ጋቦርኔ የሚገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ልጆች ያሳነጹት የመጀመሪያው የሊቀ ሰማዕታት ቅዱስ ጊዮርስ ቤተ ክርስቲያን ተባርኮ ቅዳሴ ቤቱ በድምቀት ተከብሮአል።

ብፁዕ አቡነ ሄኖክ በቦስትዋና ሐዋርያዊ ጉብኝት እያደረጉ የሚገኙ ሲሆን በባስተላለፉት መልእክት የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ለአፍሪካ ብርሃን በመሆን በርካቶችን ወደ መንግስቱ ለመጥራት እና ፍጥረት ሁሉ የወንጌልን ቃል እንዲሰማ ለማድረግ የምታደርገው ጥረት በየሀገራቱ በሚቋቋሙ አብያተ ክርስቲያናት ፈጻሚነት የሚደረግ እንቅስቃሴ በመሆኑ የአብያተ ክርስቲያናት መታነጽ ለስብከተ ወንጌል ተደራሽነት መሠረት የሚጥል ነው ብለዋል።

ብፁዕነታቸው ጨምረውም በስደት ያሉ በተለይም በአፍሪካ ሀገራት የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ክርስቲያኖች ጥንካሬያቸው እና ለሀይማኖታቸው ያላቸው ቁርጠኝነት ዘወትር ሲያስደንቀን ይኖራል ሲሉ ገልጸዋል።

"አማናዊ ፀሐይ" 😍 ተክለሃይማኖት 😍
01/01/2026

"አማናዊ ፀሐይ"

😍 ተክለሃይማኖት 😍

Address

Addis Ababa

Telephone

+251910193560

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ermias Ze Anathoth posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Ermias Ze Anathoth:

Share