Zebidar Media/ ዘቢዳር ሚዲያ

Zebidar Media/ ዘቢዳር ሚዲያ ሀገራዊ፣ አካባቢያዊ እና የጉራጌን ህዝብ ባህል ቋንቋ ኢኮኖሚ ፣ ፖለቲካ ፣ ማህበራዊ እንዲሁም ሁለንተናዊ ጉዳዮች የምንጦምርበት ገጽ ነው።
(1)

በፌደራል መንገዶች ባለስልጣን የሚሰራው የወልቂጤ ከተማ መንገድ እና ጎን ለጎን የሚሰራው የኮሪደር ስራ ግንባታ አለመፋጠን ከተማውን ለከፍተኛ የትራፊክ መጨናነቅ እና አዋራ ዳርጎታል። አሽከርካ...
07/10/2025

በፌደራል መንገዶች ባለስልጣን የሚሰራው የወልቂጤ ከተማ መንገድ እና ጎን ለጎን የሚሰራው የኮሪደር ስራ ግንባታ አለመፋጠን ከተማውን ለከፍተኛ የትራፊክ መጨናነቅ እና አዋራ ዳርጎታል። አሽከርካሪዎች፣ እግረኞችና የንግድ ተቋማት ላይ ጫናው በግልፅ ይታያል።

ሌላው የሚስተዋለው ችግር እየተሰራ ያለው መንገድ ጥበት ነው። መንገዱ የወደፊቱ ይቅርና የአሁኑ የከተማው የትራፊክ ፍሰት እንኳን በአግባቡ ማስተናገድ የሚችል አይደለም። የመንገድ አካፋይ መሰራቱ ጥሩ ቢሆንም የመንገዱ ጥበት ግን ገና ከወዲሁ ችግሩ አፍጦ እየታየ ነው። የከተማው አስተዳደር ከመንገዶች ባለስልጣን ጋር በመሆን ከወዲሁ መፍትሄ ቢያበጅ የተሻለ ይሆናል!

የከተማው ነዋሪ ወይም ተመላላሽ ከሆኑ አስተያየትዎን ያካፍሉን።

Zebidar Media/ ዘቢዳር ሚዲያ

መስከረም 15/2018 በጉራጌ ዞን ፖሊስ መምሪያ ላይ የተፈፀመውን ጥቃት በዋናነት ካቀናበሩት መካከል ይህ ሴፉ የሚባለው ከመከላከያ ሰራዊት ተመላሽ ይገኝበታል።  እስካሁን በቁጥጥር ስር አልዋ...
07/10/2025

መስከረም 15/2018 በጉራጌ ዞን ፖሊስ መምሪያ ላይ የተፈፀመውን ጥቃት በዋናነት ካቀናበሩት መካከል ይህ ሴፉ የሚባለው ከመከላከያ ሰራዊት ተመላሽ ይገኝበታል። እስካሁን በቁጥጥር ስር አልዋለም! ሴፉና መሰሎቹ የሰራዊቱን ክቡር መለዮና ካኪ የፀጥታ ኃይሎችን ለመግደልና መሳሪያዎች ለመዝረፍ ተጠቅመዋል።
Zebidar Media/ ዘቢዳር ሚዲያ

እልባት የሚሻው የጊቤ ሸለቆ የታጣቂዎች እንቅስቃሴ….መስከረም 15/2018 የጉራጌ ዞን ፖሊስ መምሪያ በልዩ ወረዳው ሽ‍ፍቶች በተፈፀመበት ጥቃት በጥበቃ ላይ የነበሩ ፖሊሶች ገድለው መሳሪያ ግ...
07/10/2025

እልባት የሚሻው የጊቤ ሸለቆ የታጣቂዎች እንቅስቃሴ….

መስከረም 15/2018 የጉራጌ ዞን ፖሊስ መምሪያ በልዩ ወረዳው ሽ‍ፍቶች በተፈፀመበት ጥቃት በጥበቃ ላይ የነበሩ ፖሊሶች ገድለው መሳሪያ ግምጃ ቤት ውስጥ የነበሩ በርካታ መሳሪያዎች መዘረፋቸው መዘገባችን ይታወሳል። በዘረፋውና ግድያው የተሳተፉት በሙሉ የልዩ ወረዳው ወንበዴዎች መሆናቸው ዘቢዳር ተዓማኒ ምንጮችን ይዛ ስትዘግብ ቆይታለች። ካስፈለገ እስከነ ፎቶአቸው ማውጣት ይቻላል።

ገዳይ ዘራፊዎች በአካባቢው ከሚንቀሳቀሱ ታጣቂ ቡድኖች ጋር ግንኙነት ሳይፈጥሩ እንዳልቀሩ እና በህገ ወጥ የመሳሪያ ዝውውር እና ሽብር ተግባር ሳይሰማሩ እንዳልቀሩ ሙያዊ አስተያየት ማጋራታችን ይታወሳል።

ይኸው አሁን ከወልቂጤ ጅማ የሚወስደው መንገድ በተለይም ጊቤ በረሃ ላይ እገታ እና ዘረፋ እየተፈፀመ እንደሆነ በሰፊው እየተሰማ ነው። በዚህ አካባቢ የሚንቀሳቀሱ ፅንፈኛ ኃይሎች መኖራቸውና በወልቂጠ‍ኤ ከተማ የተለያዩ ተቋማት ላይ በተደጋጋሚ የሚፈፀሙ የፀጥታ ኃይሎች ግድያና የጦር መሳሪያዎች ዘረፋ ከዚህ ውንብድና ጋር የተያያዘ እንደሆነ ጉዳዩን በቅርበት የሚከታተሉ ወገኖች ይገልፃሉ።

የመስከረም 15ቱ የጉራጌ ዞን ፖሊሶች ግድያና ዘረፋ በዋናነት ካቀናበሩት መካከል የተወሰኑት እስካሁን በቁጥጥር ስር አለመዋላቸው ዘቢዳር ሚዲያ ከፀጥታ ምንጮች ሰምታለች።

የጉራጌ ዞን አስተዳደር ከአዋሳኝ የኦሮሚያ መዋቅሮች ጋር ተባብሮ ይህንን በመንገደኞች ላይ የተደቀነ አደጋ ለመቅረፍ ሊንቀሳቀስ ይገባል።


Zebidar Media/ ዘቢዳር ሚዲያ

የወልቂጤ ዩኒቨረሲቲ ቡታጅራ ካምፓስ በዛሬው እለት በይፋ ስራ  ይጀምራል።Zebidar Media/ ዘቢዳር ሚዲያ
05/10/2025

የወልቂጤ ዩኒቨረሲቲ ቡታጅራ ካምፓስ በዛሬው እለት በይፋ ስራ ይጀምራል።

Zebidar Media/ ዘቢዳር ሚዲያ

ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻዉ ጣሰዉ (ዶ/ር ) የተለያዩ ሹመቶችን ሰጡ፣የማዕከላዊ  ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻዉ ጣሰዉ (ዶ/ር ) የተለያዩ ሹመቶችን  በሸግሽግና አዳዲስ ሹመቶችን ...
03/10/2025

ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻዉ ጣሰዉ (ዶ/ር ) የተለያዩ ሹመቶችን ሰጡ፣

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻዉ ጣሰዉ (ዶ/ር ) የተለያዩ ሹመቶችን በሸግሽግና አዳዲስ ሹመቶችን ሰጥተዋል።
በዚህም መሠረት፦
1/ ዶ/ር ባዩሽ ተስፋዬ - ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ ሀላፊ
2/ ወይዘሮ ቀመሪያ ረሺድ - የገቢዎች ቢሮ ሀላፊ
3/ አቶ ዳንኤል ዳምጣው - የፕላንና ልማት ቢሮ ሀላፊ
4/ ኢንጂነር ሸሪፍ ሀሰን - በካቢኔ ማዕረግ - የውሃ ስራዎች ስራ አስኪያጅ
5/ አቶ ደስታ ተስፋዬ - በምክትል ቢሮ ሀላፊ ማዕረግ የትምህርት ቢሮ ጽህፈት ቤት ሀላፊ
6/ አቶ ራህማቶ ቦካ - የትምህርት ጥራትና ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር በቢሮ ኃላፊ ማዕረግ
7/ ኢ/ር አንድነት ወንባርጋ - በምክትል ቢሮ ሃላፊ ማዕረግ - የማረሚያ ቤቶች አስተዳደር ኮሚሽነር
8/ ዶ/ር በፍቃዱ ገብረሃና - የፖሊሲ ጥናት ምርምር ምክትል ዳይሬክተር
9/ ዶ/ር ተስፋዬ አጋፋሪ - በምክትል ቢሮ ሀላፊ ማዕረግ የኢንቬስትመንትና ኢንዳስትሪ ልማት ቢሮ ማካሪ
10/ ወ/ሮ ወጋሜ ጴጥሮስ- - በቢሮ ሀላፊ ማዕረግ- የዴሞክራሲ ሰርዓት ማስተባበሪያ ማዕከል - ሀብት ልማትና አሰተደደር ዘርፍ ሀላፊ
11/ ወ/ሮ ስምረት ሳሙኤል - በቢሮ ሀላፊ ማዕረግ- በዴሞክራሲ ሰርዓት ማስተባበሪያ ማዕከል ስትራቴጂክ ፕላንና ቴክኖሎጂ ዘርፍ ሀላፊ

12/ አቶ አንዳለ ወልደሚካሄል- በምክትል ቢሮ ሃላፊ ማዕረግ- የሰላምና ጸጥታ ቢሮ ፣ የሀይማኖት ጉዳዮች ዘርፍ ሀላፊ
13/ ኢ/ር ምትኬ አሰፋ - በምክትል ቢሮ ሃላፊ ማዕረግ-- የውሃ ስራዎች ምክትል ስራ አስኪያጅ
14 አቶ ሸረፋ ሌገሶ- በምክትል ቢሮ ሃላፊ ማዕረግ- የሰላምና ጸጥታ ቢሮ አማካሪ
15/ አቶ መላኩ ብርሃኔ- የንግድና ገበያ ልማት ቢሮ - ምክትልና ንግድ ዘርፍ

16/ አቶ መስቀሉ መንጃ- - የሰለም ጸጥታ ምክትል ቢሮ ሀላፊ ፣የመረጃ አሰባሰብ / አቅ/ አስ/ምላሽ አሰጣጥ ዘርፍ
17/ አቶ እያሱ ሻንቆ - የፍትህ ቢሮ ምክትል ሀላፊ
18/ ወ/ሮ በቱላ አብዳላ ፤- - በምክትል ቢሮ ሃላፊ ማዕረግ -ፍትህ ቢሮ አማካሪ
19/ አቶ ኑሪ ከድር ጸረ ሙስና ስነ ምግባር ኮሚሺን ምክትል ኮሚሽነር
20/ አቶ ገብሬ አስፋው - የፍትህ አካላት ማሰልጠኛና የህግ ምርምር ማዕከል ምትል ዳይሬክር
21 ወይዘሮ ታየች ሞላ- በምክትል ቢሮ ሀላፊ ማዕረግ- በትም/ ስልጠና ጥ/ቁ/ባለስልጣን የሙያ ብቃት ማረጋገጫ ዘረፍ
22 አቶ ተክል አሼቦ - በምክትል ቢሮ ሃላፊ ማዕረግ - የህብረት ስራ ምክትል
23/ አቶ ተስፋዬ ኤርሲዶ- በምክትል ቢሮ ሀላፊ ማዕረግ- የኢትዮጵያ ታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ የህዝብ ተሳትፎ ማስተበባሪያ ጽ/ ቤት/ ሀላፊ
24/ አቶ ሱልጣን አሊ-- በወጣቶችና ስፖርት ቢሮ የወጣት ዘርፍ ሀላፊ
24/አቶ ሁሴን ሳኒ- - በምክትል ቢሮ ሀላፊ ማዕረግ- ሳይንስና ኢንፎ፣ ቴክ/ ቢሮ አማካሪ
25/ አቶ አቢቲ አንሴቦ - አመራር አካዳሚ ምክትል
26/ አቶ ደስታ ዶሌቦ- ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ - ገበያ ልማት ዘርፍ
27/ አቶ አብረሃም ዓለሙ - መንግስት ኮሙኒኬሽን ቢሮ ምክትል ሀላፊ
28/ አቶ አብዱል ባር ኡስማን - መንግስት ኮሙኒኬሽን ቢሮ ምክትል ሀላፊ
29/ አቶ ሀይሉ ማቲዮስ - በምክትል ቢሮ ሀላፊ ማዕረግ - ሚሊሻ ሃላፊ
30/ አቶ መሀመድ ኑር ሳሊሃ- በምክትል ቢሮ ሀላፊ ማዕረግ- ባህልና ቱሪዝም ቢሮ - ቱሪዝም ዘርፍ ሀላፊ
31/ አቶ አዳነ ብሩ - ትምህርት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ሃላፊ-በመምሪያ ሀላፊ ማዕረግ
32/ ዶ/ር ፈላቀች ተ/ማሪያም- በቢሮ ሀላፊ ማዕረግ - የፕላንና ልማት ቢሮ ምክትል
33/ አቶ ንጉሴ መኪ- - በምክትል ቢሮ ሀላፊ ማዕረግ- የንግድና ገበያ ልማት ቢሮ አማካሪ
34/ አቶ ታደሰ ዋጄቦ- - በምክትል ቢሮ ሀላፊ ማዕረግ- የትም/ትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን አማካሪ
35/ አቶ በሩክ ቡናሮ- ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ ህዝብ ግንኙነት- በመምሪያ ሀላፊ ማዕረግ
36/ አቶ አብድልራህማን አህመድ - በምክትል ቢሮ ሀላፊ ማዕረግ - በዴምክራሲ ግንባታ ማዕከል - የትም/ት ተቋማት ክትትል ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር

መረጃው የክልሉ መንግስት ኮሚኒኬሽን ነው

Zebidar Media/ ዘቢዳር ሚዲያ

የወልቂጤ ከተማ አስተዳደር የኢሬቻ በዓልን ለማክበር ከተማውን አቋርጠው ለሚሄዱ ወንምና እህት የኦሮሞ ብሔረሰብ ተወላጆች የእንኳን ደህና መጣችሁ አቀባበል እያደረገ ይገኛል። የከተማው ነዋሪዎች...
03/10/2025

የወልቂጤ ከተማ አስተዳደር የኢሬቻ በዓልን ለማክበር ከተማውን አቋርጠው ለሚሄዱ ወንምና እህት የኦሮሞ ብሔረሰብ ተወላጆች የእንኳን ደህና መጣችሁ አቀባበል እያደረገ ይገኛል። የከተማው ነዋሪዎች፣ወጣቶችና አመራሮች በተገኙበት ለእንግዶች ደማቅ አቀባበል እና ሽኝት እየተደረ ነው። መሰል ማህበረሰባዊ መስተጋብሮች ሊበረታቱ ይገባል።

ዘቢዳር ሚዲያ በዓሉን ለሚያከብሩ በሙሉ መልካም በዓል ይመኛል!
Zebidar Media/ ዘቢዳር ሚዲያ

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር  እንዳሻው  ጣሰው (ዶ/ር ) ከምስራቅ ጉራጌ ዞን ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች እና የዞኑ ተወላጅ ከሆኑ  የክልል አመራሮች ጋር በቡታጅራ ከተማ ላይ በ...
29/09/2025

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር ) ከምስራቅ ጉራጌ ዞን ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች እና የዞኑ ተወላጅ ከሆኑ የክልል አመራሮች ጋር በቡታጅራ ከተማ ላይ በተፈጠረው የፀጥታ ችግር ላይ ውይይት አካሂደዋል።

የተፈጠረው የፀጥታ ችግር የከተማውን የእድገት ደረጃ ዝቅ የሚያደርግ እና የዞኑን ማህበረሰብ የማይመጥን ስለመሆኑ መግለፃቸውና በከተማዋ የተፈጠረው የፀጥታ ችግር በአጭር ግዜ ውስጥ በፀጥታ አካላት እና በሰላም ወዳዱ ህዝብ ርብርብ በቁጥጥር ስር መዋሉ ገልፀዋል።

በተፈጠረው የፀጥታ ችግር የተሳተፉ አካላትን በህግ ቁጥጥር ስር ማዋል መጀመሩና በድርጊቱ የተሳተፉ አካላት ላይ ህግ የማስከበር ስራው ተጠናክሮ እንደሚቀጥል መግለፃቸው የምስራቅ ጉራጌ ዞን መንግስት ኮሙኒኬሽን ዘግቧል።
Zebidar Media/ ዘቢዳር ሚዲያ

29/09/2025

ከጉራጌ ዞን አስተዳደር ሰላምና ፀጥታ መምሪያ የተሰጠ መግለጫ!!

መስከረም 18/2018 ዓ•ም (ወልቂጤ)

በጽንፈኞች እኩይ ተግባር ሰላምችንን የማጽናት ጅምሮች ከቶውንም አይደናቀፉም ።

በዞናችን በወልቂጤ ከተማ አስተዳደር ፤ ባለፉት ዓመታት ውዝፍ ያልተፈቱ የመልካም አስተዳደር ችግሮች ፤ ለግጭትና አለመረጋጋት መንስኤ በመሆን ለከተማዋ ልማት እና ለህዝቦች አብሮነት ደንቃራ ሆኖ ለዜጎች ሰላም እና ደህንነት ስጋት ፈጥሮ ቆይቷል።

የክልላችን መንግስት ለሕዝቦች አብሮነት፣ ወንድማማችነት ፤ እንዲሁም ለዜጎች ሰላም፣ ደህንነትና ብልጽግና ፤ካለው አስተሳስብና ባህሪ በመነሳት ፤ ለሰላም ስንኮፍ የሆኑትን ጉዳዮች በጥናት ምላሽ በመስጠት ፤ ሕዝቡ በሙሉ አቅሙ ወደ ልማት እንዲመለስ እየሰራ ይገኛል።

ሆኖም ይህንን ሁኔታ የማይዋጥላቸው ጥቂት ግጭት ናፋቂዎች ሂደቱን ለማደናቀፍ የተለያዩ የግድያና የዘረፋ ወንጀሎችን ሲፈጽሙ ቆይቷል ። እየፈጸሙም ይገኛሉ።

መስከረም 15/2018 በዞናችን ፖሊስ መምሪያ ፤ የመከላከያ ሰራዊታችን ዮኒፎርም በመልበስ እና የሰራዊት አባል መስሎ ከቅጥር ግቢ ዘልቆ በመግባት፤ በከፈቱት ተኩስ ፤ በዕለቱ ስራ ላይ የነበሩ ሁለት የፖሊስ አባላት ገድለው አንድ አባል አቁስሏል ።

ይህ ድርጊት እጅግ አሳዛኝ ፤ በመንግስትና በሕዝብ ላይ የተቃጣ ጥቃት ነው።

የተሰውት ሰማዕታት፤ በስነ ምግባራቸው ሆነ በተግባራቸው ምስጉን የነበሩ ፤ ሕዝባዊ ውግንና የነበራቸው የሕዝብ ልጆች ነበሩ ።

መላው የዞናችን የጸጥታ ተቋማት አመራሮችና አባላት በወንድሞቻችን ድንገተኛ መስዋዕትነት የተሰማንን ሃዘን እየገለጽን ለቤተሰብቻቸው ለዘመድ ወዳጆቻቸው መጽናናትን እንመኛለን።

ፖሊስ ከሁሉም የጸጥታ አካላት በመቀናጀት ወንጀለኞችን ለሕግ የማቅረቡ ተግባር አጠናክሮ የሚቀጥል ሲሆን ።መላው ሕዝባችን በተለይም ወጣቶች ፖሊስ የጀመረውን የሕግ የበላይነት በማረጋገጥ ሰላምችንን የማጽናቱ ተግባር የማይቀለበስና ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን ተገንዝቦ፤ በተለመደው ትዕግስ ከጸጥታ አካላት ጎን እንድትቆሙ በአክብሮት እንጠይቃለን።

የጉራጌ ዞን ሰላምና ጸጥታ መምሪያ!!

መስከረም 18/2018 ዓ•ም

ወልቂጤ

ከቡታጅራ ከተማ አስተዳደር የተሰጠ መግለጫ‎=============================‎መስከረም 18/2018 ዓ/ም‎በትናንትናው ዕለት ማምሻ ላይ እንዲሁም በዛሬው ዕለት ጠዋት የከተማችን ...
29/09/2025

ከቡታጅራ ከተማ አስተዳደር የተሰጠ መግለጫ
‎=============================
‎መስከረም 18/2018 ዓ/ም
‎በትናንትናው ዕለት ማምሻ ላይ እንዲሁም በዛሬው ዕለት ጠዋት የከተማችን ህዝብ የማይመጥን አስነዋሪና አሳፋሪ ተግባር ማንንም ሊወክሉ በማይችሉ የተደራጁ አካላት በቡታጀራ ከተማ በተወሰኑ መንደሮች ላይ ብጥብጥና ረብሻ ተፈፅሞ የነበረ ቢሆንም በፀጥታ ሀይሎቻችን ብሎም በሰላም ወዳዱ ማህበረሰብ አማካይነት ማስቆም ተችሏል። የተፈጠረው አስነዋሪ ድርጊት የህይወትና የአካል ጉዳት አስከትሏል።

በዚህም ከተማ አስተዳደሩ የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን እየገለፅን በተፈጠረው ብጥብጥና ረብሻ ህይወታቸውን ላጡ ነብሳቸውን በገነት እንዲያኖርልን ከልብ እየተመኘን ለቤተሰቦቻቸው እና ወዳጅ ዘመዶቻቸው መፅናናትን እንመኛለን።

‎የህዝባችንን የቆየ አብሮነትና አንድነትን እንዲሁም የከተማችን በተለይም የሰላም ሰገነትና አብነት ተብላ የምትጠራው ከቡታጅራ ከተማችን አኳያ የተፈጠረው ችግር የተፈፀመው የብጥብጥና ሁከት ተግባር ፍፁም ቡታጅራን የሚመጥን አይደለም።

‎ስለሆነም የቡታጅራ ከተማ አስተዳደር ችግሩን ለመፍታት ከሰላምና ልማት ወዳዱ ህዝባችን ጋር እና ከሚመለከታቸው አካላት ጋር እየመከርንበት መሆኑ ታውቆ የአካባቢያችን ብሎም የቡታጅራ ከተማን ሰላምና ፀጥታ ወደነበረበት ለመመለስ ህዝቡ ከፀጥታ መዋቅሮቻችን ጋር በመተባበር እንዲሰራ ጥሪያችንን እናቀርባለን ።

‎ የቡታጅራ ከተማ አስተዳደር
Zebidar Media/ ዘቢዳር ሚዲያ

ትላንት መስከረም 17/2018 ጀምሮ በቡታጅራ ከተማ በነዋሪዎችና በፀጥታ ኃይሎች መካከል የተፈጠረው ግጭት ዛሬም ቀጥሎ የዋለ ሲሆን በንብረትና በሰዎች ላይ ጉዳት ደርሷል። ለዛሬ ተቀጥሮ የነበ...
28/09/2025

ትላንት መስከረም 17/2018 ጀምሮ በቡታጅራ ከተማ በነዋሪዎችና በፀጥታ ኃይሎች መካከል የተፈጠረው ግጭት ዛሬም ቀጥሎ የዋለ ሲሆን በንብረትና በሰዎች ላይ ጉዳት ደርሷል። ለዛሬ ተቀጥሮ የነበረው ውይይትም ከተጀመረ በኋላ መበተኑ ተሰምቷል። በአሁን ሰዓት የመከላከያ ሰራዊት በከተማው ገብቶ ነገሮች አንፃራዊ መረጋጋት እያሳዩ ነው። የተዘጉ መንገዶችም እየተከፈቱ ናቸው። ሰላም!
Zebidar Media/ ዘቢዳር ሚዲያ

ከታች በፎቶ የተገለፁት አባት አቶ ደሳለኝ ተክሌ ይባላሉ የትውልድ አካባቢያቸው በምሁር አክሊል ወረዳ   አካባቢ ነው። ዕድሜ ከ55–60 ዓመት  ይሆናሉ። (ረቡዕ) በቀን 14/01/ 2018 ዓ...
28/09/2025

ከታች በፎቶ የተገለፁት አባት አቶ ደሳለኝ ተክሌ ይባላሉ የትውልድ አካባቢያቸው በምሁር አክሊል ወረዳ አካባቢ ነው። ዕድሜ ከ55–60 ዓመት ይሆናሉ። (ረቡዕ) በቀን 14/01/ 2018 ዓ.ም ከሠዓት በኋላ ከ10:00 ጀምሮ ከቤት እንደወጡ አልተመለሱም።

ቤተሰብ ከጠፉበት ዕለት ጀምሮ በማፈላለግ ላይ ቢሆንም ማግኘት ግን አልተቻለም። ስለሆነም ሁሉም እንዲያፈላልግ በጭንቀት ውስጥ ያለው ቤተሰብ እባካችሁ ድረሱልን፤ አፋልጉን እያለ ይገኛል❗️

👉 እኚህ አባትን በየትኛውም አካባቢ ያየ ከስር በተቀመጡት ቁጥሮች በመደወል እንዲያሳውቅ ቤተሰባቸው በትህትና ይጠይቃል።
0991450296 (ቢተው ደሳለኝ)
0911750024 (ክፍሌ ቸገን)
ደውለው ቢያሳውቁን ወሮታውን እንከፍላለን።
መረጃው እንዲዳረስ ‼

27/09/2025

ቡታጅራ Developing….

በምስራቅ ጉራጌ ዞን ቡታጅራ ከተማ በፖሊስ እና በወጣቶች መካከል ግጭት መፈጠሩ ተሰምቷል። የግጭቱ መንስኤ ነገ በሴራና አዳራሽ ይካሄዳል ከተባለና በስናኖ ሴራ ላይ ትኩረት ካደረገ መድረክ ጋር እንደሆነ የአካባቢው ምንጮቻችን ይገልፃሉ። መድረኩ ይካሄዳል አይካሄድም በሚል የተፈጠረ አለመግባባት ወደ ግጭት ማምራቱ ተሰምቷል።

ሰላም ለጉራጌ! ሰላም ለቀጠናው! ሰላም ለሐገራችን! ዝርዝር መረጃ የምናደርስ ይሆናል!
Zebidar Media/ ዘቢዳር ሚዲያ

Address

Bole Road, Wereda 17
Addis Ababa

Telephone

+251977961254

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Zebidar Media/ ዘቢዳር ሚዲያ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Zebidar Media/ ዘቢዳር ሚዲያ:

Share