Ayu Zehabesha- አዩዘሀበሻ

Ayu Zehabesha- አዩዘሀበሻ "መረጃ ህይወት ነው"
(1)

አዲስ ፍጥጫ‼️ኢራን በትናንትናው ዕለት የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስቴር እና የእስራኤል መከላከያ ሚኒስቴርን ጨምሮ አጠቃላይ አስር ከፍተኛ ወታደራዊ እና ፖለቲካዊ አመራሮችን ለመግደል ማቀዷን ስም...
12/08/2025

አዲስ ፍጥጫ‼️
ኢራን በትናንትናው ዕለት የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስቴር እና የእስራኤል መከላከያ ሚኒስቴርን ጨምሮ አጠቃላይ አስር ከፍተኛ ወታደራዊ እና ፖለቲካዊ አመራሮችን ለመግደል ማቀዷን ስም ዝርዝራቸውን ይፋ አድርጋለች።
ይህን ተከትሎ እስራኤል ከኢራን ሊመጣ ከሚችል ጥቃት እራሷን ለመከላከል ከፍተኛ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑንና የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስቴር ቤንጃሚን ኔታንያሁ ሁሉም የጦር አመራሮች እና የሞሳድ የስለላ ድርጅት ዝግጁ ሆኖ እንዲጠብቅ ትዕዛዝ ማስተላለፋቸውን የእስራኤል ሚዲያዎች ዘግበዋል።
በኢራን ከሚገደሉ ስም ዝርዝር ውስጥ የሚገኙት የእስራኤል መከላከያ ሚኒስቴር "የኢራኑን መሪ አያቶላህ አልካሜኒ ከተደበቁበት ጥልቅ ዋሻ(Bunker)ሲወጡ ሰማዩን እንዲመለከቱና ማንኛውንም ድምፅ በትኩረት እንዲያዳምጡ እመክራለሁ፣የቀዩ ሰርግ ደጋሾች(Israel air force & Mossad) ዛሬም አሉ"ሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል።
ኢራን በቅርቡ 40 የሚጠጉ J-10C የተባለ የቻይና ስውር ተዋጊ አውሮፕላን መረከቧ የሚታወስ ነው።
(አዩዘሀበሻ)
‎======================
💎⬇️⬇️⬇️👇👇👇👇👇👇
የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s

የታሪፍ ማሻሻያው ይቀጥላል‼️የኤሌክትሪክ ሽያጭ ዋጋ ማስተካከያ ለቀጣይ 3 አመታት ይቀጥላል ተባለ።የኤሌክትሪክ ሽያጭ ዋጋ ማስተካከያ በእቅዱ መሰረት ለቀጣይ ሶስት አመታት እንደሚቀጥል የኢትዮ...
11/08/2025

የታሪፍ ማሻሻያው ይቀጥላል‼️
የኤሌክትሪክ ሽያጭ ዋጋ ማስተካከያ ለቀጣይ 3 አመታት ይቀጥላል ተባለ።
የኤሌክትሪክ ሽያጭ ዋጋ ማስተካከያ በእቅዱ መሰረት ለቀጣይ ሶስት አመታት እንደሚቀጥል የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሃይል አስታዉቋል ፡፡

የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ እንደተናገሩት ተቋሙ ከአስር ዓመታት በላይ የታሪፍ ማሻሽያ ሳያደርግ በከፍተኛ ብድር የኃይል ተደራሽነትን የሚያሳድጉ የኃይል መሰረተ ልማት ስራዎችን ሲያከናውን ቆይቷል ብለዋል ፡፡

ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ይህንን ያሉት ነሐሴ 1/2017 ዓ.ም በተቋሙ የ2017 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸምና በ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ ዙሪያ ለመገናኛ ብዙኃን በሰጡት መግለጫ ላይ ነው።

በዚህም ተቋሙ የህልውና አደጋ ውስጥ በመግባቱ በመንግሥት በኩል የሀገር ውስጥ ዕዳ ጫና ስረዛ እንደተደረገለት አስታውሰዋል፡፡

በተጨማሪም ተቋሙ የፋይናንስ ቁመናውን ለማሻሻል፣ የኃይል ሽፋንን ለማሳደግ እና የኦፕሬሽንና የፕሮጀክት ወጪዎችን ለመሸፈን በጥናት ላይ ተመስርቶ የታሪፍ ማሻሻያ መተግበሩን ዋና ስራ አስፈፃሚዉ ተናግረዋል፡፡

የታሪፍ ማሻሽያው በየሩብ ዓመቱ ተከፋፍሎ በቀጣዮቹ ሦስት ዓመታት ተግባራዊ የሚደረግ መሆኑን ኢንጂነር አሸብር አንስተዋል ፡፡

የታሪፍ ማሻሻያው ከጎረቤት ሀገራት አንፃር ሲታይ አሁንም እጅግ ዝቅተኛና የተቋሙን ወጪ መሸፈን የማይችል መሆኑን ገልፀዋል፡፡
Ethio Fm
‎======================
💎⬇️⬇️⬇️👇👇👇👇👇👇
የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s

አረብ ኢምሬትስ ማሳሰቢያ ሰጠች‼️የሱዳን ወታደራዊ መሪ ጄኔራል አልብሩሀን የሀሰት መረጃ ማሰራጨታቸውን እንዲያቆሙ ዩናይትድ አረብ ኤመሬትስ ማሳሰቢያ ሰጠች፡፡ የዩናይትድ አረብ ኤመሬትስ የውጭ...
10/08/2025

አረብ ኢምሬትስ ማሳሰቢያ ሰጠች‼️
የሱዳን ወታደራዊ መሪ ጄኔራል አልብሩሀን የሀሰት መረጃ ማሰራጨታቸውን እንዲያቆሙ ዩናይትድ አረብ ኤመሬትስ ማሳሰቢያ ሰጠች፡፡ የዩናይትድ አረብ ኤመሬትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዛሬ ባወጣው መግለጫ ‹‹ለሱዳን ህዝብ ሰላም፣ መረጋጋትና የወደፊት ህይወት መልካሙን እንመኛለን›› በማለት ጀምሯል፡፡

ሲቀጥልም ይህ የእርስ በእርስ ጦርነት ከተጀመረ አንስቶ ‹‹ተኩስ አቁም እንዲደረግ፣ ሰላማዊ ሰዎች እንዲጠበቁና በሁሉም ተፋላሚ አካላት ለተፈፀሙ ወንጀሎች ተጠያቂነት እንዲኖር›› ያላሰለሰ ጥሪ ሲያቀርብ መቆየቱን ጠቅሷል፡፡ አሁንም ቢሆን ከሁለቱም ተፋላሚ አካላት በላይ ለሱዳን ህዝብ የሚጠቅም ሰላማዊ መፍትሄ ማምጣት ተገቢ ነው የሚል እምነት እንዳለውም አስታውቋል፡፡

መግለጫው ሲቀጥልም ‹‹በዚህ ጦርነት ተሳታፊ ከሆኑት አካላት አንዱ የሆነውና የፖርት ሱዳን መንግስት የሚባለው ሀይል ግን በዩናይትድ አረብ ኤመሬትስ ላይ መሰረት የሌለው ወቀሳና ፕሮፖጋንዳ ማሰራጨቱን ቀጥሎበታል›› ካለ በኋላ እንዲህ አይነቱ ድርጊት ግጭቱን ለማቆምና መረጋጋት እንዲሰፍን ለማድረግ የሚደረገውን ጥረት እንደሚጎዳው አስረድቷል፡፡

መግለጫው ጨምሮም ‹‹እንዲህ አይነት የሀሰት ወሬዎችን እየፈጠሩ ማሰራጨት የሽንፈት ምልክት ነው›› በማለት በጄኔራል አልብሩሀን መንግስት ላይ ጠንካራ ትችት አቅርቧል፡፡ የሌተና ጄኔራል አልብሩሀን መንግስት ከተጠያቂነት ለመሸሽና ጦርነቱን ለማራዘም ይህንን እንደሚያደርግ ገልፆ ከዚህ እንዲቆጠብ ማሳሰቢያ ሰጥቷል፡፡
‎======================
💎⬇️⬇️⬇️👇👇👇👇👇👇
የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s

የአስር ብር እጥረት‼️ዝርዝር አስር ብር እጥረት በመከሰቱ በገበያው ላይ ተፅዕኖ እየፈጠረ መሆኑን የአዩዘሀበሻ ቤተሰቦች ጥቆማ አድርሰዋል።ዝርዝር አስር ብር ለማግኘት ወደ ባንክ ቤት ቢሄዱም ...
10/08/2025

የአስር ብር እጥረት‼️
ዝርዝር አስር ብር እጥረት በመከሰቱ በገበያው ላይ ተፅዕኖ እየፈጠረ መሆኑን የአዩዘሀበሻ ቤተሰቦች ጥቆማ አድርሰዋል።
ዝርዝር አስር ብር ለማግኘት ወደ ባንክ ቤት ቢሄዱም አስር ብር ማተም መቆሙንና ዝርዝር አስር ብር የለም ብለው መልሰውናል ብለዋል።
በዚህ ምክንያት ዝርዝር የአስር ብር እጥረት ምክንያት በገበያው ላይ መልስ ለመመለስ ተቸግረናል ብለዋል።
አዩዘሀበሻ
‎======================
💎⬇️⬇️⬇️👇👇👇👇👇👇
የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s

ድልድዩ በጎርፍ ተወሰደ‼️በአማራ ክልል ከአዲስ አበባ-ደብረማርቆስ-ባህርዳር በሚወስደዉ መንገድ በጊደብ ወንዝ ላይ የተሰራዉ ድልድይ በጎርፍ ተወሰደ‼️የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የደብረማር...
10/08/2025

ድልድዩ በጎርፍ ተወሰደ‼️
በአማራ ክልል ከአዲስ አበባ-ደብረማርቆስ-ባህርዳር
በሚወስደዉ መንገድ በጊደብ ወንዝ ላይ የተሰራዉ ድልድይ በጎርፍ ተወሰደ‼️

የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የደብረማርቆስ መንገድ ጥገና ዲስትሪክት ተገጣጣሚ ድልድይ በፍጥነት በመንገንባት ለአገልግሎት ለማብቃት እየሰራ መሆኑን ገልጿል።

ድልድዩ በጎርፍ የተወሰደዉ ነሐሴ 3/2017 ሌሊት ጮቄ አካባቢ በጣለዉ ከባድ ዝናብ በተፈጠረ ጎርፍ ነዉ። ድልድዩ ጥዋት አካባቢ እንደተወሰደ የአካባቢዉ ነዋሪዎች ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የደብረማርቆስ መንገድ ጥገና ዲስትሪክት ስለጉዳዩ ጠይቀናቸዉ ችግሩ መከሰቱን ገልጸዉ ተገጣጣሚ ድልድይ ለመስራት የሚያስፈልጉ ቁሳቁሶችን በዛሬዉ እለት ከአዲስ አበባ መጫን መጀመራቸዉን ገልጸዉልናል።

የጌደብ ወንዝ በአማኑኤል ከተማ አስተዳደር የዉላ ቀበሌ አካባቢ የሚገኝ ወንዝ ነዉ።

በተመሳሳይ በዚሁ ወንዝ ላይ የአንጎት በለምና ቀበሌ ነዋሪዎችን ከአማኑኤል ከተማ ጋር የሚያገናኝ የብረት ድልድይ በጎርፍ ተወስዷል።
#አዩዘሀበሻ
‎======================
💎⬇️⬇️⬇️👇👇👇👇👇👇
የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s

በድጋሚ አጠቁኝ:-ቢሮው‼️የትግራይ ሰላምና ፀጥታ ቢሮ በትናንትናው ዕለት መግለጫ ሰጥቷል።በአፋር የሚንቀሳቀሱ ታጣቂዎች በሰራዊታችን ላይ ለሁለተኛ ጊዜ ጥቃት ፈፅመዋል ብሏል።አንዳንድ የ ቡድን...
09/08/2025

በድጋሚ አጠቁኝ:-ቢሮው‼️
የትግራይ ሰላምና ፀጥታ ቢሮ በትናንትናው ዕለት መግለጫ ሰጥቷል።
በአፋር የሚንቀሳቀሱ ታጣቂዎች በሰራዊታችን ላይ ለሁለተኛ ጊዜ ጥቃት ፈፅመዋል ብሏል።
አንዳንድ የ ቡድን አመራሮች የትግራይን የጸጥታ ሃይሎች እና የወጣቶቻችንን ጠንካራ አደረጃጀት ለማዳከም አልፎ ተርፎም ለማደናቀፍ አላማ አድርገው እየሰሩ ነው ብሏል። የትግራይ ተቃዋሚ ሃይሎችን ያዳክማል እና ይከፋፍላል ብለው ያመኑባቸውን የተለያዩ ሴራዎች ሲቀሰቅሱ ቆይተዋል።
ነገር ግን ይህ የክህደት አጀንዳ አሁን የጀመሩት ሳይሆን ሁሉም የትግራይ ህዝብ እንደሚያውቀው በጊዜያዊ አስተዳደር ስም ያገኙትን ከፍተኛ የስልጣን ጫፍ ትግራይን ሲገዙ ስልጣናቸውን ተጠቅመዋል። የትግራይ ህዝብ ለማንነቱና ለህልውናው የከፈለውን መስዋዕትነት ንስሀ እንዲገባ የመንግስት በጀት መድበው እየሰሩ ነው። አላማቸውም የትግራይን ህዝብ አንድነት ለማደፍረስ እና የተቃውሞ ሀይላችንን ለማዳከም ነው።
አሁን ቤተሰቦቻቸውን በአውሮፓ, በአሜሪካ አስፍረዋል፣እነሱም ሸራተን ላይ ሰፈሩ < የትግራይ ወጣቶች ተነሱ ወደ አፋር ሂድ በማለት ሌት ተቀን ቅስቀሳ እያካሄዱ ነው ብሏል።
እንደሚባለው ; ጌቶቻቸውን ለማስደሰት ሲታገሉ ቆይተዋል; ማንም ታጋይም ሆነ ወጣት የእነዚህን አሳፋሪ ሰዎች ቃል ሰምቶ ከህዝባዊ አላማው እንደማያፈነግጥ በልባቸው ያውቃሉ።
ከጥቅሙ ጋር የሚዋጋ ህዝብም ሆነ ጦር የለንም።
ይህ ብቻ አይደለም በትግራይ ተወላጆች መካከል የተፈጠረውን አለመግባባት በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ብዙ ጥረት እያደረግን ሲሆን በሌላ በኩል በአፋር ክልል የሚያንቀሳቅሷቸውን ታጣቂዎች በመጠቀም እርስ በርስ የመጠፋፋት ፕሮጀክታቸውን ለማሳካት በሠራዊታችን ላይ ተደጋጋሚ ጥቃት እየፈፀሙ ይገኛሉ። ዛሬ ለሁለተኛ ጊዜ ከአፋር ክልል ጠብታብ ከሚባል ልዩ ቦታ በደደርባ አቅራቢያ በሚገኘው የጦራችን ክፍል ላይ በተከፈተ ተኩስ አንድ ተዋጊ ተሰውቶብናል። ለሰማዕቱ ቤተሰቦች እና ጓዶች መፅናናትን እንመኛለን። ይህ በእኛ በትግራይ ተወላጆች መካከል ደም የሚያፈሰው እኩይ ተግባር በአስቸኳይ እንዲቆም እንጠይቃለን። ይህ አጥፊ ተግባር ከቀጠለ ይህንን በሚመሩና በሚያስተባብሩ አካላት ላይ ትምህርታዊ እርምጃ እንወስዳለን"ብሏል።
(አዩዘሀበሻ)
‎======================
💎⬇️⬇️⬇️👇👇👇👇👇👇
የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s

አስገራሚ መረጃ‼️በሆድዋ ውስጥ ሌላ ፅንስ የያዘች ህጻን ተወለደች‼️በህንድ ሃገር በሆድዋ ውስጥ ሌላ ጽንስ የያዘች ህጻን መወለዷ እየተዘገበ ነው። በሆድዋ ውስጥ ሌላ ሕፃን ይዛ ተወለደች የሚ...
09/08/2025

አስገራሚ መረጃ‼️
በሆድዋ ውስጥ ሌላ ፅንስ የያዘች ህጻን ተወለደች‼️
በህንድ ሃገር በሆድዋ ውስጥ ሌላ ጽንስ የያዘች ህጻን መወለዷ እየተዘገበ ነው።

በሆድዋ ውስጥ ሌላ ሕፃን ይዛ ተወለደች የሚለው ያልተለመደ ክስተት እውነት መሆኑን የጤና ባለሙያዎች አስታውቀዋል።

ይህ ክስተት fetus in fetu በመባል የሚታወቅ ሲሆን፣ በአለም ላይ እጅግ በጣም አልፎ አልፎ የሚከሰት ነው ተብሏል።

በህንድ ሃገር ግን ከሌሎች ሃገራቶች በበለጠ እየተከሰተ ነው ተብሏል።

ይህ ሁኔታ አንድ ፅንስ ገና በማህፀን ውስጥ ሳለ በሌላው መንታ ፅንስ ሆድ ውስጥ ሲፈጠር ሊከሰት የሚችል ነው ተብሏል።

በህክምና ታሪክ ውስጥ እስካሁን የተመዘገቡት የዚህ አይነት ክስተቶች ከ200 እንደማይበልጡም ተጠቁሟል።

ይህንን ዘገባ ያሰራጨው ዘ ታይምስ ኦፍ ኢንዲያ ሲሆን የህክምና ባለሙያዎች ይህ ሁኔታ እውነት መሆኑን እና ከዚህ በፊትም ተመዝግቦ እንደነበር አስገንዝበዋል ነው የተባለው።

ይህ አይነቱ ክስተት ከተከሰተ በኋላ በቀዶ ጥገና አማካኝነት በሆድ ውስጥ ያለው ፅንስ እንዲወጣ እንደሚደረግ ተመላክቷል።
‎======================
💎⬇️⬇️⬇️👇👇👇👇👇👇
የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s

ጠቅላይ ሚኒስትሩ አግደውታል‼️ጠቅላይ ሚኒስትሩ የንግድ ባንክን አዲስ ሎጎ አገዱ‼️የንግድ ምልክቱን ለመቀየር 600 ሚሊየን ብር መድቦ ሲሰራ የነበረው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በመጨረሻው ሰአት...
09/08/2025

ጠቅላይ ሚኒስትሩ አግደውታል‼️
ጠቅላይ ሚኒስትሩ የንግድ ባንክን አዲስ ሎጎ አገዱ‼️
የንግድ ምልክቱን ለመቀየር 600 ሚሊየን ብር መድቦ ሲሰራ የነበረው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በመጨረሻው ሰአት አዲሱን ሎጎ ይፋ የማድረግ እቅዱን ሰርዟል።

በምክንያት የተጠቀሰው ጠቅላይ ሚኒስተር አብይ አህመድ ስለ አዲሱ ሎጎ መተዋወቅ መረጃውን ከቀናት በፊት ከሰሙ በሀኋላ በሰጡት ትእዛዝ ነው።

አዲሱ ሎጎ ፈጠራ የጎደለው ነው የሚሉት ተቺዎች ጠቅላይ ሚኒስትሩም ላሳለፉት ውሰኔ ይሄንኑ በምክንያት ጠቅሰው፤ ምልክቱ የኢትዮጵያን ፊደል አለማካተቱ በተጨማሪ ምክንያት ጠቅሰዋል ሲል ሪፖርተር ነው የዘገበው።

ከቅረብ ጊዜ ወዲህ ከፍተኛ ሃብት እየመደቡ የፋይናንስ ተቋማት የንግድ ምልክቶቻቸውን እየቀየሩ እና እያሻሻሉ ተስተውለዋል።

ሆኖም የሚያስተዋውቋቸው ምልክቶች ከፍተኛ ትችትን ከማስተናገድ አልዘለሉም።

ግዙፍ መንግስታዊ የፋይናንስ ተቋም የኢኮኖሚ ማሻሻያውን ተከትሎ ስር ነቀል ለውጥ እያደረገ መሆኑ ይታወሳል።

አሁን ያለው የንግድ ምልክቱ ለበርካታ አስርት አመታት ሲጠቀምበት የኖረ ነው።
‎======================
💎⬇️⬇️⬇️👇👇👇👇👇👇
የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s

ደብረብርሃን‼️በደብረብርሃን ከተማ አንዳንድ ክፍለከተሞች ከሰሞኑ ውሃ ሳይበከል አይቀርም፣ከዚህ ጋር በተያያዘ አዋቂዎችን ጨምሮ በተለይ ልጆቻችን እየታመሙብን ነው የሚሉ በርካታ ጥቆማዎች አድር...
09/08/2025

ደብረብርሃን‼️
በደብረብርሃን ከተማ አንዳንድ ክፍለከተሞች ከሰሞኑ ውሃ ሳይበከል አይቀርም፣ከዚህ ጋር በተያያዘ አዋቂዎችን ጨምሮ በተለይ ልጆቻችን እየታመሙብን ነው የሚሉ በርካታ ጥቆማዎች አድርሰውናል።
ይህን ጥቆማ መሰረት በማድረግ አዩዘሀበሻ የደብረብርሃን ከተማ አስተዳደር ውሃና ፍሳሽ አገልግሎት ስራ አስኪያጅ ወይዘሪት መሰረት መንገሻን አነጋግሮ ተከታውን ምላሽ ሰጥተዋል።
ሃላፊዋ በደብረብርሃን ምንም አይነት የውሃ ብክለት ያልተከሰተ መሆኑን ጠቁመው ከሁሉም የከተማዋ አካባቢዎች የውሃ ናሙና (sample) እየተወሰደና ጥራቱ እየተረጋገጠ ለተጠቃሚዎች እንደሚደርስ ገልፀዋል።
በዛሬው ዕለትም ከተለያዩ የከተማዋ አካባቢዎች የውሃ ናሙና መወሰዱን እና ውጤቱ ከ 24 በኋላ እንደሚታይ የገለፁ ሲሆን የውሃ ብክለት ተከስቷል የሚለው ውሸት ነው ብለዋል። ከውሃው ጣዕም መቀየር ጋር ተያይዞ ያለው የውሃ ማከሚያ ክሎሪን እንጂ ውሃ ተበክሎ አይደለም ብለዋል።
ወቅቱ ክረምት እንደመሆኑ መጠን ለበሽታ አምጪ ተዋህሲያን የመጋለጥ እድላችን ሰፊ በመሆኑ በተለይ የአካባቢ ንፅህናን እና የምንመገባቸውን ምግቦች ንፅህና መጠበቅ አስፈላጊ መሆኑን ጠቁመዋል።
‎======================
💎⬇️⬇️⬇️👇👇👇👇👇👇
የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s

የመሬት መንቀጥቀጥ‼️ትናንት ነሐሴ 2/2017 ዓ.ም አርብ ለቅዳሜ አጥቢያ ከለሊቱ 7:19 አካባቢ በሬክተር ስኬል 4.6 የተመዘገበ በመላው አዲስ አበባና በሌሎች አካባቢዎች ከበድ ያለ የመሬት...
09/08/2025

የመሬት መንቀጥቀጥ‼️
ትናንት ነሐሴ 2/2017 ዓ.ም አርብ ለቅዳሜ አጥቢያ ከለሊቱ 7:19 አካባቢ በሬክተር ስኬል 4.6 የተመዘገበ በመላው አዲስ አበባና በሌሎች አካባቢዎች ከበድ ያለ የመሬት መንቀጠጥቀጥ ተከስቷል።
የመሬት መንቀጥቀጥ መነሻ(Epicenter) ቦታው በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ከደብረሲና ከተማ ደቡብ ምስራቅ አቅጣጫ 54 ኪሎሜትር ርቀት ላይ መሆኑን መረጃዎች ይጠቁማሉ።
ይህን ተከትሎ በሸዋሮቢት፣ በደብረሲና፣በደብረብርሃን፣በአጣዬ፣ በመላው አዲስ አበባ በጅጅጋ እንዲሁም በሌሎች አካባቢዎች ንዝረቱ እንደተሰማቸው ከአካባቢው ነዋሪዎች የደረሰን ጥቆማ ያመላክታል።
(አዩዘሀበሻ)
‎======================
💎⬇️⬇️⬇️👇👇👇👇👇👇
የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s

በመቀሌ ጥብቅ ፍተሻ‼️ህወሃትን በመቃወም ራሱን "የትግራይ የሰላም ሃይል - ነፃ መሬት ትግራይ (T.P.F)" ብሎ የሚጠራውና በመቀሌ ከተማ ውስጥ በህቡእ እንቅስቃሴ እያደረገ መሆኑን የገለጸው...
08/08/2025

በመቀሌ ጥብቅ ፍተሻ‼️
ህወሃትን በመቃወም ራሱን "የትግራይ የሰላም ሃይል - ነፃ መሬት ትግራይ (T.P.F)" ብሎ የሚጠራውና በመቀሌ ከተማ ውስጥ በህቡእ እንቅስቃሴ እያደረገ መሆኑን የገለጸው ቡድን፣ ከቀናት በፊት በመቀሌ በራሪ ወረቀት በመበተን ለመላው የመቀሌ ወጣቶችና ለትግራይ ሰራዊት አባላት ትግሉን እንዲያቀጣጥሉና እንዲቀላቀሉ አስቸኳይ ጥሪ ማቅረቡ ይታወሳል።
ይህን ተከትሎ በመቀሌ ከተማ በተለይ በመግቢያ በሮች እና ኬላዎች ላይ ዛሬ ከሰዓት በኋላ ጀምሮ በክልሉ ፖሊስ ጥብቅ ፍተሻ እየተደረገ መሆኑን የደረሰን መረጃ ያመላክታል።
(አዩዘሀበሻ)
‎===================
💎⬇️⬇️⬇️👇👇👇👇👇👇
የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s

አካውንት ማገድ ተጀምሯል‼️በሕገ-ወጥ የውጭ ምንዛሪ የወንጀል ተግባር ላይ የተሰማሩ ተጠርጣሪዎች የባንክ ሂሳብ ታገደ‼️በሕገ-ወጥ የውጭ ምንዛሪ የወንጀል ተግባር ላይ የተሰማሩ 138 ተጠርጣሪ...
08/08/2025

አካውንት ማገድ ተጀምሯል‼️
በሕገ-ወጥ የውጭ ምንዛሪ የወንጀል ተግባር ላይ የተሰማሩ ተጠርጣሪዎች የባንክ ሂሳብ ታገደ‼️
በሕገ-ወጥ የውጭ ምንዛሪ የወንጀል ተግባር ላይ የተሰማሩ 138 ተጠርጣሪዎች የባንክ ሂሳብ መታገዱን የፋይናንስ ደኅንነት አገልግሎት ገለጸ፡፡

አገልግሎቱ ለኤኤምኤን በላከው መግለጫ ሕጋዊና መደበኛ የባንክ ስርዓትን ወደ ጎን በመተው በህገ-ወጥ እና ትይዩ ገበያ የውጭ ምንዛሪ ወንጀል ላይ የተሰማሩ 138 ዋነኛ ተጠርጣሪዎች የገንዘብ እንቅስቃሴ እንዲታገድ ተደርጓል ብሏል፡፡

የውጭ ምንዛሪ አገልግሎት በሕጋዊና መደበኛ የባንክ ሥርዓት በኩል እንዲከናወን በግልጽ የተቀመጠ መሆኑን ያወሳው መግለጫው፤ በሕገ-ወጥ መንገድ የምንዛሪ አገልግሎት ላይ የተሰማሩት ላይ ጠንካራ የሕግ ተጠያቂነት የሚያስከትል መሆኑን አስገንዝቧል፡፡

ከዚሁ ጋር በተያያዘ በወንጀል ድርጊቱ ላይ ተሰማርቶ መገኘት የንብረት መወረስን ጨምሮ በከፍተኛ ጽኑ እስራት የሚያስቀጣ በመሆኑ የንግዱ ማህበረሰብ መደበኛ የባንክ ስርዓትን እንዲጠቀም በመንግስት በኩል ማሳሳቢያ ሲሰጥ ቆይቷል ብሏል።

ሆኖም ግን አንዳንድ የንግድ ድርጅቶችና ግለሰቦች ህገ-ወጥ የውጭ ምንዛሪ ወንጀልን እንደ መደበኛ የንግድ ስራ በመያዝ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ በመሆናቸው ክትትል ሲደረግባቸው ቆይቷል ሲል ገልጿል።

በዚሁ መሠረት ክትትል ተርጎ የተደረሰባቸው እና በህገ-ወጥ የውጭ ምንዛሪ ላይ የተሰማሩ 138 ዋነኛ ተጠርጣሪዎች የገንዘብ እንቅስቃሴ እንዲታገድ ተደርጓል፡፡
ብሄራዊ ባንክ የውጪ ምንዛሪ ለማግኘት መደበኛ የባንክ ስርዓትን የማይጠቀሙ ግለሰቦችንም ሆነ ነጋዴዎች ላይ እርምጃ መውሰድ እንደሚጀመር ማሳወቁ ይታወሳል።
አዩዘሀበሻ
‎===================
💎⬇️⬇️⬇️👇👇👇👇👇👇
የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ayu Zehabesha- አዩዘሀበሻ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Ayu Zehabesha- አዩዘሀበሻ:

Share