Ayu Zehabesha- አዩዘሀበሻ

Ayu Zehabesha- አዩዘሀበሻ "መረጃ ህይወት ነው"

Update‼️ተደብቀው የነበሩት ነዳጅ የጫኑ ቦቴዎች ተያዙ‼️የአፋር ክልል ንግድ ቢሮ እና የክልሉ ጸጥታ አካላት ባደረጉት ርብርብ ነዳጅ ጭነው በየቦታው ተደብቀው የነበሩ ቦቴዎች ከተደበቁበት ...
05/01/2025

Update‼️
ተደብቀው የነበሩት ነዳጅ የጫኑ ቦቴዎች ተያዙ‼️
የአፋር ክልል ንግድ ቢሮ እና የክልሉ ጸጥታ አካላት ባደረጉት ርብርብ ነዳጅ ጭነው በየቦታው ተደብቀው የነበሩ ቦቴዎች ከተደበቁበት እንዲወጡ መደረጉ ተገለጸ፡፡

አዲስ አበባን ጨምሮ ለተለያዩ ክልሎች የሚጓጓዝን ነዳጅ ይዘው በአፋር ክልል ሰርዶ አድማስ በሚባል ቦታ በየጥሻው የተደበቁ ቦቴዎች በፀጥታ አካላት አሰሳ መያዛቸውን የነዳጅ እና ኢነርጂ ባለስልጣን አስታውቋል፡፡

በአሁኑ ሠዓትም የክልሉ ንግድ ቢሮ ለተሽከርካሪዎቹ እጀባ እንዲሰጥ በማድረግ ወደ የመዳረሻቸው እንዲንቀሳቀሱ ተደርጓል መባሉን የባለስልጣኑ መረጃ አመላክቷል፡፡

“በወሩ መጨረሻ የነዳጅ ዋጋ ክለሳ ይሠራል” በሚል ያልተጨበጠ ተስፋ ነዳጁን ይዘው የተደበቁት እነዚህ አሽከርካሪዎች ያለአግባብ ስለሚያገኙት ትርፍ ብቻ ቅድሚያ መስጠታቸውን ባለስልጣኑ ገልጿል፡፡

በየክልል ከተሞች የነዳጅ ማደያዎችን በማድረቅ እጥረት በመፍጠር ሕብረተሰቡን የማጉላላት ሥራን መሥራታቸውንም ጠቁሟል፡፡

የፈፀሙት ሕገ-ወጥ ተግባር በተጨባጭ መረጋገጡን የገለጸው ባለስልጣኑ÷ መንግሥት ለሕብረተሰቡ ተጠቃሚነት ሲል በድጎማ የከፈለውን የነዳጅ ወጪ እንዲሸፍኑ ይደረጋል፤ ከምርት መሰወር ጋር በተያያዘም በሕግ ተጠያቂ ይደረጋሉ ብሏል፡፡
#አዩዘሀበሻ
=======================
💎⬇️⬇️⬇️👇👇👇👇👇
የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s

"እየተፋፈርን ስለሆነ ነው እንጂ ማንም ኑሮን እየተቋቋመው (Afford) እያደረገ አይደለም፡፡ከሁለትና ሦስት ዓመት በፊት 10 እና 15 ሺህ ደመወዝ የሚያገኙት ሠራተኞች ጥሩ ነበሩ፡፡አሁን ግ...
05/01/2025

"እየተፋፈርን ስለሆነ ነው እንጂ ማንም ኑሮን እየተቋቋመው (Afford) እያደረገ አይደለም፡፡ከሁለትና ሦስት ዓመት በፊት 10 እና 15 ሺህ ደመወዝ የሚያገኙት ሠራተኞች ጥሩ ነበሩ፡፡አሁን ግን 30 ሺህ እና 40 ሺህ ብር ደመወዝ የሚያገኙት ጥሩ ደረጃ ላይ ናቸው አልልም፡፡ የቤት ኪራይ:የትምህርት ቤት ክፍያው:የኑሮ ውድነት ሰማይ ወጥቷል"።
አትሌት ሻለቃ ኃይሌ ገብረ ሥላሴ
ለሪፖርተር ጋዜጣ
=======================
💎⬇️⬇️⬇️👇👇👇👇👇
የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s

ነዳጅ‼️ከጅቡቲ ነዳጅ ጭነው በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ሰበብ እየፈጠሩ በርካታ ቦቲዎች መቆማቸውን ጥቆማ ደርሶኛል። ለአብነት ያለ በቂ ምክንያት ጭፍራ ላይ በርካታ ቦቲዎች ቆመዋል። ነዳጅ ጭነ...
05/01/2025

ነዳጅ‼️
ከጅቡቲ ነዳጅ ጭነው በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ሰበብ እየፈጠሩ በርካታ ቦቲዎች መቆማቸውን ጥቆማ ደርሶኛል። ለአብነት ያለ በቂ ምክንያት ጭፍራ ላይ በርካታ ቦቲዎች ቆመዋል። ነዳጅ ጭነው በየመንገዱ የቆሙ በርካታ ናቸው ብለዋል። ለዚህ መነሻው ደግሞ ከመጪው ወር ጀምሮ የነዳጅ ዋጋ ላይ ማሻሻያ ይደረጋል በሚል ነው ብለዋል።
አንድ የአዩዘሀበሻ ቤተሰብ ከሰመራ ከተማ የላከልን👇
"እኔ ያለሁት ሰመራ ከተማ ነው በነዳጅ ምክንያት ብዙ መኪኖች በየሄድኩባቸው ከተሞች ብዙ መኪኖች እንደቆም አይቻለሁ ፣ሰመራ ሎጌያ፣ሚሌ ላይ ታች ሚሌ ፣ድቸቱ-----ሰማራ ባለው ነዳጅ ማደያ በሙሉ ነዳጅ የለም በጣም ትንሽና ለአደጋ ግዜ በሚመስል መልኩ ሰመራ ኤርታእሌ ነዳጅ ማደያ ማታ ላይ ሲሰጥ ተመልክቻለሁ ለመሆኑ ይህን የሚቆጣጠር መ/ቤት ምን ይሰራል?"
አዩዘሀበሻ
=======================
💎⬇️⬇️⬇️👇👇👇👇👇
የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s

04/01/2025

"አሁን በዚህ ሰዓት ከምሽቱ 5:05 በድጋሜ ከፍተኛ ንዝረት ነበር"የአዲስ አበባ ነዋሪዎች
የዛሬው 5.0 በሬክተር ስኬል ተመዝግቧል።

በየቀኑ🙄❗❗ዛሬም ታህሳስ 26, 2017 ከመሸ 1:38 ላይ የመሬት መንቀጥቀጥ አዲስ አበባ ላይ ተከስቷል። ጀሞ፣ጣፎ፣ኮየፈጬ የሚኖሩ የአዩዘሀበሻ ቤተሰቦች ንዝረቱን መስማታቸውን ገልፀዋል።===...
04/01/2025

በየቀኑ🙄❗❗
ዛሬም ታህሳስ 26, 2017 ከመሸ 1:38 ላይ የመሬት መንቀጥቀጥ አዲስ አበባ ላይ ተከስቷል። ጀሞ፣ጣፎ፣ኮየፈጬ የሚኖሩ የአዩዘሀበሻ ቤተሰቦች ንዝረቱን መስማታቸውን ገልፀዋል።
=======================
💎⬇️⬇️⬇️👇👇👇👇👇
የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s

ከአንድ ታካሚ ሆድ 57 ብረታ ብረቶች ወጡ‼️   | ‎በሣውላ አጠቃላይ ሆስፒታል ከሁለት ሰዓት በላይ በፈጀ ቀዶ ሕክምና ከአንድ ታካሚ ሆድ 57 ብረታ ብረቶች ወጡ።‎‎ታኅሳስ 26/2017 ዓ....
04/01/2025

ከአንድ ታካሚ ሆድ 57 ብረታ ብረቶች ወጡ‼️
| ‎በሣውላ አጠቃላይ ሆስፒታል ከሁለት ሰዓት በላይ በፈጀ ቀዶ ሕክምና ከአንድ ታካሚ ሆድ 57 ብረታ ብረቶች ወጡ።

‎ታኅሳስ 26/2017 ዓ.ም በጎፋ ዞን ሣውላ አጠቃላይ ሆስፒታል ከሁለት ሰዓት በላይ በፈጀ ቀዶ ሕክምና ከአንድ የ25 ዓመት ታካሚ ሆድ 57 ብረታ ብረቶች ወጡ።

‎በቀዶ ሕክምናው 28 ሚስማር፣ 8 ብሎን እና ሌሎች የተለያዩ ብረታ ብረቶች መውጣታቸው ተጠቅሷል፡፡

‎የአንጀት ቀዶ ሕክምናው ከ2 ሰዓት በላይ የፈጀ እንደነበረም የሆስፒታሉ መረጃ ያመላክታል።

‎የቀዶ ሕክምናው በስኬት መጠናቀቁን የሆስፒታሉ አጠቃላይ ቀዶ ሕክምና ሐኪም ዶ/ር ጌታነህ በላይ ገልጸዋል።

=======================
💎⬇️⬇️⬇️👇👇👇👇👇
የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s

በጎንደር የሰዓት ገደብ እንቃስቃሴ ላይ ማሻሻያ ተደረገ‼️በጎንደር ከተማ በነበረው በፀጥታ ችግር ምክንያት በሰው እና በተሽከርካሪ እንቅስቃሴ ላይ ተጥሎ የነበረው የሰዓት እላፊ ገደብ የተሻሻለ...
04/01/2025

በጎንደር የሰዓት ገደብ እንቃስቃሴ ላይ ማሻሻያ ተደረገ‼️
በጎንደር ከተማ በነበረው በፀጥታ ችግር ምክንያት በሰው እና በተሽከርካሪ እንቅስቃሴ ላይ ተጥሎ የነበረው የሰዓት እላፊ ገደብ የተሻሻለ ሲሆን በዚህም የሰዓት ገደቡ ወደ አራት ሰዓት ከፍ ብሏል።ከነገ ጀምሮ ተግባራዊ ይሆናል ተብሏል።
የተፈቀደላቸው ባጃጆች እስከ ምሽት አራት ሰዓት መስራት የሚችሉ ሲሆን ሌሎች ባጆጆች ደግሞ በቀደመው የሰዓት ገደብ እስከ 12 ስዓት ብቻ መንቀሳቀስ እንደሚችሉ ተገልጿል።
#አዩዘሀበሻ
=======================
💎⬇️⬇️⬇️👇👇👇👇👇
የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s

ጉዳት ደረሰ‼️ሰሞኑን እየተከሰተ ያለው የመሬት መንቀጥቀጥ በአፋር ክልል በከሰም የስኳር ፋብሪካ ሠራተኞች ህንፃ እና ማሽኖች ላይ ከፍተኛ ጉዳት ማድረሱን የፋብሪካው ሰራተኞች ለአዩዘበሀሻ ገል...
04/01/2025

ጉዳት ደረሰ‼️
ሰሞኑን እየተከሰተ ያለው የመሬት መንቀጥቀጥ በአፋር ክልል በከሰም የስኳር ፋብሪካ ሠራተኞች ህንፃ እና ማሽኖች ላይ ከፍተኛ ጉዳት ማድረሱን የፋብሪካው ሰራተኞች ለአዩዘበሀሻ ገልፀዋል።
አዩዘሀበሻ
=======================
💎⬇️⬇️⬇️👇👇👇👇👇
የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s

በመሬት መንቀጥቀጥ 80,000 ሰዎች ተጠቂ ሆነዋል‼️ሰሞኑን የተከሰተውን የመሬት መንቀጥቀጥ ተከትሎ ለጉዳት የተጋለጡ 80,000 የሚጠጉ ዜጎችን ከአካባቢው በማራቅ ለማስፈር ከፍተኛ ርብርብ እ...
04/01/2025

በመሬት መንቀጥቀጥ 80,000 ሰዎች ተጠቂ ሆነዋል‼️
ሰሞኑን የተከሰተውን የመሬት መንቀጥቀጥ ተከትሎ ለጉዳት የተጋለጡ 80,000 የሚጠጉ ዜጎችን ከአካባቢው በማራቅ ለማስፈር ከፍተኛ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን መንግሥት አስታውቋል።
=======================
💎⬇️⬇️⬇️👇👇👇👇👇
የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s

የመሬት መንቀጥቀጥ በሬክተር ስኬል ከፍ ማለት እና ሊያስከትል የሚችለው ጉዳት‼️💥    ከ4.0 በታች፡-አነስተኛ ነው፤ ትንሽ ብቻ ነው የሚሰማው። የሚሰማን ንዝረት አንድ መኪና ባጠገባችን ሲያ...
04/01/2025

የመሬት መንቀጥቀጥ በሬክተር ስኬል ከፍ ማለት እና ሊያስከትል የሚችለው ጉዳት‼️
💥 ከ4.0 በታች፡-

አነስተኛ ነው፤ ትንሽ ብቻ ነው የሚሰማው። የሚሰማን ንዝረት አንድ መኪና ባጠገባችን ሲያልፍ የሚሰማንን ንዝረት ያህል ነው።

💥 ከ4.0 - 4.9፡-

ጉዳቱ አብዛኛውን ጊዜ አነስተኛ ቢሆንም በቀላሉ ሊወድቁ የሚችሉ እቃዎችን ሊጥል ይችላል። መስታወት ሊሰበር ይችላል።

💥 ከ5.0 - 5.9፡-

መጠነኛ ነው። በደንብ ባልተገነቡ ሕንፃዎች እና የእንጨት ስራ ውጤቶች ላይ ጉዳት ሊያደርስ ይችላል።

💥 ከ6.0 - 6.9፡-

ንዝረቱ ጠንከር ይላል። ህዝብ በሚበዛባቸው አካባቢዎች በተለይም አሮጌ ወይም በደንብ ባልተገነቡ ህንፃዎች ላይ ከፍተኛ ጉዳት ሊያደርስ ይችላል።

💥 ከ7.0 - 7.9፡-

የህንፃ መሰረቶችን በመሰባበር የህንፃ መደርመስን ሊያስከትል ይችላል፣ በመሬት ውስጥ የተቀበሩ የመሰረተ ልማት ዝርጋታዎችን ሊሰባብር ይችላል።

💥 8.0-8.9
ከፍተኛ ውድመት ያስከትላል፣ድልድዮች ይፈራርሳሉ፣ትናንሽ ነገሮች ብቻ ሊተርፉ/ቆመው/ ልናይ ይችላሉ።
9.0 በላይ
ሙሉ ለሙሉ ከፍተኛ ውድመት ያስከትላል። የመሬት መንቀጥቀጥ ሞገዱን/seismic wave/ በአይናችን ማየት እንችላለን።
✍አዩዘሀበሻ
=======================
💎⬇️⬇️⬇️👇👇👇👇👇
የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s

ኢትዮጵያ ከ64 ዓመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ከፍተኛ የተባለ የመሬት ተከሰተ‼️ለሊት ላይ 9:53 ደቂቃ ላይ የተከሰተው የመሬት መንቀጥቀጥ በደሴ፣ኮምቦልቻ፣ ደብረብርሃን፣ቡራዩ፣አዳማ፣አዲስአባ...
04/01/2025

ኢትዮጵያ ከ64 ዓመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ከፍተኛ የተባለ የመሬት ተከሰተ‼️
ለሊት ላይ 9:53 ደቂቃ ላይ የተከሰተው የመሬት መንቀጥቀጥ በደሴ፣ኮምቦልቻ፣ ደብረብርሃን፣ቡራዩ፣አዳማ፣አዲስአባባ..በሌሎች አካባቢዎች ከፍተኛ ንዝረት መሰማቱን ጠቅሰው በንዝረቱ ምክንያት ጠረንቤዛ ላይ የነበረ ፎቶ ወድቆ እንደተሰበረባቸው የአዩዘሀበሻ ቤተሰቦች ገልፀዋል።
ይህ የመሬት መንቀጥቀጥ በሬክተር ስኬል 5.8 ሆኖ የተመዘገበ ሲሆን ይህ በኢትዮጵያ ታሪክ ከፍተኛው ነው። የዛሬው ንዝረቱ ከባድ በመሆኑ ብዙ ሰዎችን ከእንቅልፍ ቀስቅሷል። ኢትዮጵያ ከፍተኛ የተባለ የመሬት መንቀጥቀጥ ያስተናገደችው በ1953 ዓ.ም ነበር።
አዩዘሀበሻ
=======================
💎⬇️⬇️⬇️👇👇👇👇👇
የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s

እሳት‼️ Amazing🙀🙀በአፋር ክልል ዱለቻ ወረዳ ሰንጋቶ ቀበሌ ዶፈን ተራራ ላይ ጠዋት ጀምሮ ጭስ እየወጣበት የነበረው ቦታ አሁን በምስሉ እንደምትመለከቱት እሳት 🔥እየወጣበት ይገኛል ሲሉ የ...
03/01/2025

እሳት‼️ Amazing🙀🙀
በአፋር ክልል ዱለቻ ወረዳ ሰንጋቶ ቀበሌ ዶፈን ተራራ ላይ ጠዋት ጀምሮ ጭስ እየወጣበት የነበረው ቦታ አሁን በምስሉ እንደምትመለከቱት እሳት 🔥እየወጣበት ይገኛል ሲሉ የአፋር የመረጃ ምችጮቼ ጠቁመዋል። ከአንድ ሰዓት በፊት 2:01 ደቂቃ ላይ የተከሰተው የመሬት መንቀጥቀጥ መነሻው (epicenter) እዚሁ አካባቢ ነው። የመሬት መንቀጥቀጥ የከፋ ጉዳት ሊያደርስ የሚችለው በዋናነት በመነሻው(Epicenter) አካባቢ ስለሆነ እንዲሁም ምን ሊከሰት እንደሚችል ለመገመት አዳጋች ስለሆነ ለአካባቢው ህዝብ ተገቢውን ትኩረት መስጠት ያስፈልጋል።
አዩዘሀበሻ
=======================
💎⬇️⬇️⬇️👇👇👇👇👇
የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s

እንቅጥቅጡ ቀጥሏል‼️ከደቂቃዎች በፊት 2:01 ደቂቃ ላይ በደሴ፣በደብረብርሃን እንዲሁም በአዲስ አበባ(አያት)፣አዳማ፣ድሬዳዋ ከበድ ያለ የመሬት መንቀጥቀጥ ንዝረት መሰማቱን የአዩዘሀበሻ ቤተሰቦ...
03/01/2025

እንቅጥቅጡ ቀጥሏል‼️
ከደቂቃዎች በፊት 2:01 ደቂቃ ላይ በደሴ፣በደብረብርሃን እንዲሁም በአዲስ አበባ(አያት)፣አዳማ፣ድሬዳዋ ከበድ ያለ የመሬት መንቀጥቀጥ ንዝረት መሰማቱን የአዩዘሀበሻ ቤተሰቦች ገልፀዋል።
የመሬት መንቀጥቀጡ በሬክተር ስኬል 5.5 ሲሆን ጥልቀቱ ደግሞ 10km ሆኖ ተመዝግቧል። የመሬት መንቀጥቀጡ መነሻው(epicenter) በአፋር ዱለቻ አቅራቢያ ዛሬ ጠዋት እሳተገሞራ የፈነዳበት ዶፈን ተራራ አካባቢ ነው።
አዩዘሀበሻ
=======================
💎⬇️⬇️⬇️👇👇👇👇👇
የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s

ገደሉት❗❗ይህ አሽከርካሪ ጥላሁን ይባላል የአይሱዙ ሾፌር ነው በዛሬው ዕለት በ 25/04/2017 በኦሮሚያ ክልል በወለንጪቲ እና መተሀራ መሀከል ልዩ ቦታው ሀሪቦና የሚባል ቦታ ላይ የታጠቁ ወ...
03/01/2025

ገደሉት❗❗
ይህ አሽከርካሪ ጥላሁን ይባላል የአይሱዙ ሾፌር ነው በዛሬው ዕለት በ 25/04/2017 በኦሮሚያ ክልል በወለንጪቲ እና መተሀራ መሀከል ልዩ ቦታው ሀሪቦና የሚባል ቦታ ላይ የታጠቁ ወንበዴዎች ገድለውታል :: በአካባቢው ሾፌር በተደጋጋሚ ሾፌሮች ረዳቶች ተሳፋሪዎች ቢታገቱ ቢገደሉም ቦታውን ለማስጠበቅ የሚደረግ ጥረት ባለመኖሩ ማንም ዘራፊ እንዳሻው እንዲፈነጭ በርን ከፍቷል ::
እዚሁ አካባቢ በዚሁ ዕለት 3 ተሽከርካሪዎች መቃጠላቸውን ሌሎች በጥይት መመታታቸው ይታወቃል።
=======================
💎⬇️⬇️⬇️👇👇👇👇👇
የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s

 ❗ ተከፍቷል‼️ጠዋት ጀምሮ በአማራ ክልል ከአዲስ አባባ ደሴ...በዋናው መንገድ ደብረሲና አካባቢ ልዩ ስሙ ሾላሜዳ በሚባል ቦታ የተኩስ ልውውጥ መቀስቀሱን ተከትሎ ለተወሰነ ሰዓታት የትራንስፖ...
03/01/2025

❗ ተከፍቷል‼️
ጠዋት ጀምሮ በአማራ ክልል ከአዲስ አባባ ደሴ...በዋናው መንገድ ደብረሲና አካባቢ ልዩ ስሙ ሾላሜዳ በሚባል ቦታ የተኩስ ልውውጥ መቀስቀሱን ተከትሎ ለተወሰነ ሰዓታት የትራንስፖርት እንቅስቃሴ ተስተጓጉሎ የነበረ ቢሆንም ከቀኑ 8:30 ጀምሮ መንገዱ መከፈቱን ምንጮቼ ገልፀዋል። በየመንገዱ ቆመው የነበሩ መኪኖችም ጉዞ መጀመራቸውን ገልፀውልኛል(አዩዘሀበሻ)።
=======================
💎⬇️⬇️⬇️👇👇👇👇👇
የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s

መንገድ ዝግ ነው‼️ዛሬ ማለትም አርብ ታህሳስ 25/04/2017 ዓ.ም ከአዲስአበባ  ደሴ ያለዉ መስመር ዝግ መሆኑን የደረሰኝ መረጃ ያመላክታል።ከአዲስአበባ የሄዱት ባሶች ጣርማ በር አካባቢ ቆ...
03/01/2025

መንገድ ዝግ ነው‼️
ዛሬ ማለትም አርብ ታህሳስ 25/04/2017 ዓ.ም ከአዲስአበባ ደሴ ያለዉ መስመር ዝግ መሆኑን የደረሰኝ መረጃ ያመላክታል።
ከአዲስአበባ የሄዱት ባሶች ጣርማ በር አካባቢ ቆመዋል፣ ምንም አይነት እንቅስቃሴ የለም ብለዋል።
ለዚህ መነሻው ከደብረሲና ዝቅ ብሎ ሾላ ሜዳ በሚባል አካባቢ ጠዋት ጀምሮ በከባድ መሳሪያ የታገዘ የተኩስ ልውውጥ መኖሩን ተከትሎ የትራንስፖርት እንቅስቃሴ መቆሙን ምንጮቼ ገልፀዋል።
[አዩዘሀበሻ]
=======================
💎⬇️⬇️⬇️👇👇👇👇👇
የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s

ከላይ የሚታየው ዛሬ 25/4/2017 ዓ.ም በአፋር ክልል በ  #ገቢረሱ ዞን  #ዱላሳ ወረዳ  #ሰጋቶ ቀበሌ ዳግም በመሬት መንቀጥቀጥ ምክንያት የተከሰተ ጪስ ሲሆን እስካሁን የተረጋገጠ ነገር ...
03/01/2025

ከላይ የሚታየው ዛሬ 25/4/2017 ዓ.ም በአፋር ክልል በ #ገቢረሱ ዞን #ዱላሳ ወረዳ #ሰጋቶ ቀበሌ ዳግም በመሬት መንቀጥቀጥ ምክንያት የተከሰተ ጪስ ሲሆን እስካሁን የተረጋገጠ ነገር ባይኖርም እሳተገሞራ ሳይሆን እንዳልቀረ የአዩዘሀበሻ ምንጮች ጠቁመዋል።
=======================
💎⬇️⬇️⬇️👇👇👇👇👇
የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s

500 ኪ.ግ የሚመዝን የጋለ ብረት  #ከሰማይ መውደቁ ተነገረ‼️በአጎራባቿ ኬንያ 500 ኪሎ ግራም ሊመዝን የሚችል ብረት ከሰማይ ወድቋል ነው የተባለው። ቀለበታማ ብረቱ የወደቀው ሙኩኩ በተሰኘ...
03/01/2025

500 ኪ.ግ የሚመዝን የጋለ ብረት #ከሰማይ መውደቁ ተነገረ‼️
በአጎራባቿ ኬንያ 500 ኪሎ ግራም ሊመዝን የሚችል ብረት ከሰማይ ወድቋል ነው የተባለው።

ቀለበታማ ብረቱ የወደቀው ሙኩኩ በተሰኘች መንደር እንደሆነ የተገለጸ ሲሆን ብረቱ የ2 ነጥብ 5 ሜትር ስፋት ወይም ዲያሜትር ያለው መሆኑ ተመላክቷል።

የኬንያ ስፔስ ኤጀንሲ ብረቱ በስፔስ ላይ ከሚገኙ ሮኬቶች ተገንጥሎ የወደቀ ሊሆን እንደሚችል አስታውቋል።
=======================
💎⬇️⬇️⬇️👇👇👇👇👇
የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ayu Zehabesha- አዩዘሀበሻ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Ayu Zehabesha- አዩዘሀበሻ:

Videos

Share