Biruh Entertainment

Biruh Entertainment Biruh Entertainment is Ethiopian social media New Media channel and website News. Documentary Tourism Travel Entertainment Information and more Video everyday

BIRUH ENTERTAINMENT
Ethiopian social media New Media channel and website News.

ሙያዊ ውይይት “ ” ሁሉም እንዲታደም ተጋብዟል!  #ቅዳሜ፣  ፣ 2017 ዓ.ም 8፡00 ሰዓት ይጀምራልአወያይ÷ ሔኖክ አየለ አቅራቢዎች÷•  ቤዛ ኃይሉ•  ሙሴ አበባየሁ ጌትነትአዘጋጅ:- የኢት...
17/03/2025

ሙያዊ ውይይት “ ”

ሁሉም እንዲታደም ተጋብዟል!

#ቅዳሜ፣ ፣ 2017 ዓ.ም
8፡00 ሰዓት ይጀምራል

አወያይ÷ ሔኖክ አየለ

አቅራቢዎች÷
• ቤዛ ኃይሉ
• ሙሴ አበባየሁ ጌትነት

አዘጋጅ:- የኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ የብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደ ሥላሴ የሥነ ጥበባት ማዕከል

አድራሻ፦ ቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል አካባቢ (በንግድ ባንክ ጉለሌ ቅርንጫፍ በኩል ገባ ብሎ)፡፡

ትራንስፖርት፡ ከፒያሳ/ማስታወቂያ አካባቢ 7፡30 ላይ የሚነሳ ትራንስፖርት ተዘጋጅቷል፡፡-

ለበለጠ መረጃ እና መገኘትዎን ለማረጋገጥ የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ፡፡
https://t.me/+VZQIhKm-NoAwYjM0

በራሳችሁ ለምትመጡ አድራሻው፤ Ethiopian Academy of Sciences
ጎግል ማፕ፡ https://maps.app.goo.gl/GwKfjcwg1jmqsfG76
በፒያሳ በኩል ከመጡ ከቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል አለፍ እንዳሉ ወደ ቀኝ የሚታጠፈውን ሁለተኛውን ቀጭን የአስፓልት መንገድ ይዘው 500 ገባ ይላሉ፤ በውንጌት በኩል የሚመጡ ከሆነ መድሐኒያለም ትምህርት ቤትን እንዳለፉ በሚያገኙት የመጀመሪያው ቀጭን የአስፓልት መንገድ ወደ ግራ ታጥፈው 500 ሜትር ገባ ይላሉ፡፡

አዝናኙ ሲዝናና ሚዲያ ካፕ የ13 ዓመታ ጉዞ
10/03/2025

አዝናኙ ሲዝናና ሚዲያ ካፕ የ13 ዓመታ ጉዞ

"ከትዳር በላይ"100 ዓመት ያለፈው የቲአትር ታሪካችን ዛሬ ያለበት ሁኔታ ያሳስባል።"ከትዳር በላይ"የተቀዛቀዘውን ቲአትር በእጅጉ ሊያነቃቃ መምጣቱን ሰሞኑን ያለው የጥበብ ቤተሰቦች ርብርብ ያ...
28/02/2025

"ከትዳር በላይ"
100 ዓመት ያለፈው የቲአትር ታሪካችን ዛሬ ያለበት ሁኔታ ያሳስባል።
"ከትዳር በላይ"የተቀዛቀዘውን ቲአትር በእጅጉ ሊያነቃቃ መምጣቱን ሰሞኑን ያለው የጥበብ ቤተሰቦች ርብርብ ያሳየናል።
እየተዝናናን( እየሳቅን) ልናየው የተዘጋጀው ይህ ኮሜዲ ቲአትር በርካታ ባለሙያዎችን አሳትፏል።
በነገራችን ላይ ጸሐፊ ተውኔቱ፣ አዘጋጁ ፣ፕሮዲዩሰሯ መርጠው የሚሠሩና የሚሳካላቸው ባለሙያዎች ናቸው።

በከፍተኛ ዝግጅት የተሰናዳው ይህ ኮሜዲ ቲአትር በግል የሚሠሩ እና በቲአትር ቤት ቅጥር ሆነው የሚሠሩ ተዋናያን ተጣምረውበታል።


በተለያዩ የመድረክ፣ የፊልም እና የቴሌቭዥን ምርጥ ሥራዎቿ የምትታወቀው ተዋናይት መስከረም አበራ ፕሮዲዩስ አድርገዋለች። ጸሐፊ ተውኔት ቴዎድሮስ ተ/አረጋይ ተጽፎ በዳግማዊ ዓመለወርቅ ፈይሳ የተዘጋጀው "ከትዳር በላይ" የተሰኘው ኮሜዲ ቴያትር ዝነኞቹ ተዋንያን ሽዋፈራው ደሳለኝ ፣መስከረም አበራ ፣ ቸርነት ፍቃዱ ፣መዓዛ ገ/ሕይወት ፣ የማታወርቅ ታደሰ ተሳትፈውበታል።

በመግለጫው እንደተገለጸው ከትዳር በላይ ኮሜዲ ቲአትርየ ለሙያው መደረግ የሚገባውን ሥነ ምግባር በመከተል የተሠራ በመሆኑ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ደፍረው ሂስ እንዲሠሩበት ተጋብዝዋል። ቲአትሩ በአዲስ መልክና በተሻለ መልኩ በመሠራቱ ከፍተኛ ወጪ ወጥቶበታል።

በተጨማሪም የትያትሩ ጽሑፍ በተደጋጋሚ ታርሞ ለ2 ወር የተጻፈና በአዲስ አበባ የባህል ማዕከልና ዓለም ሲኒማ 3ወር ልምምድ እንደተደረገበትም ተገልጿል።

ከትዳር በላይ ኮሜዲ ቴያትር የኮሜዲ ዘውግ ያለው ሲሆን ሳቅ የሚያስጭር ብቻ ሳይሆን ቁምነገርም የሚጨበጥበት እንደሆነ ተነግሯል።

የትያትሩ መግቢያ 1000 ብር ሲሆን ይህ ዋጋ ግን ለምርቃቱ ጊዜ ብቻ እንደሆነ ተገልጿል።

በተጨማሪም ትያትሩን በተለያዩ የሀገራችን ከተሞች ለማሳየት እቅድ ተይዟል።
በቅርብም ሚያዚያ ላይ እስራኤል ሀገር እንደሚታይ ተነግሯል።
ቲኬቱ ሁሉ በእጄ መተግበሪያ የሚገኝ ሲሆን VIP ከ5000 ብር በላይ መግዛት እንደሚችሉ የተገለጸ ሲሆን ከ50 ወንበሮች መካከል የተወሰኑት መሸጣቸውን እየተመለከትን ነው።
እናም VIP ካርዱን ለማግኘት +251 922 541776 እና +251 713 927054 ላይ በመደወል መግዛት ይቻላል።
ለሁሉም ባለሙያዎች ከፍተኛ ክብር ይገባቸዋል።

አባይ ቴሌቭዥን መቅደስ ደበሳይን አሰፈረመ!ተወዳጇ የቴሌቪዥን ፕሮግራም አቅራቢ መቅደስ ደበሳይ ዓባይ ቴሌቪዥንን በይፋ ተቀላቀለች፡፡በመዝናኛው ዘርፍ የቴሌቪዥን ፕሮግራም በኢትዮጵያ ውስጥ ተወ...
24/02/2025

አባይ ቴሌቭዥን መቅደስ ደበሳይን አሰፈረመ!

ተወዳጇ የቴሌቪዥን ፕሮግራም አቅራቢ መቅደስ ደበሳይ ዓባይ ቴሌቪዥንን በይፋ ተቀላቀለች፡፡

በመዝናኛው ዘርፍ የቴሌቪዥን ፕሮግራም በኢትዮጵያ ውስጥ ተወዳጅነትን ካተረፉ የመዝናኛ ዝግጅት አቅራቢዎች መካከል ስሟ የሚጠራው መቅደስ ደበሳይ ዓባይ ቲቪ በይፋ ተቀላቅላለች፡፡

በቴሌቪዥን የመዝናኛ መሰናዶ የተመልካቾችን ቀልብ በሚስብ ድንቅ አቀራረብ ላለፉት ዓመታት አድናቆት የተቸራት መቅደስ ዓባይ ቴሌቪዥንን በመቀላቀሏ የተሰማትን ደስታ ገልጻለች፡፡

ዝነኛዋ የቴሌቪዥን ፕሮግራም አቅራቢ መቅደስ ዓባይ ቴሌቪዥንን መቀላቀሏን ይፋ ስታደርግ ከቴሌቪዥን ጣቢያው ስራ አስኪያጅ አቶ ግሩም ይልማ ጋር የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርማለች፡፡

በስምምነት ስርዓቱ ላይ ንግግር ያደረገጉት የዓባይ ቴሌቪዥን ስራ አስኪያጅ አቶ ግሩም ይልማ ‹‹ስርጭት ከጀመረ ሶስት ዓመታትን ያስቆጠረው ዓባይ ቴሌቪዥን በእነዚህ ጥቂት ዓመታት ሰፊ ህዝብ ጋር በመድረስ ተወዳጅነትን በማትረፍ ትልቅ ስኬት ላይ ደርሷል›› ብለዋል፡፡

‹‹ዓባይ ቴሌቪዥን አሁንም በተጨማሪ ከፍታ ለመምጣት በርካታ እንቅስቃሴዎችን እያደረገ ባለበት በዚህ ወቅት ከመቅደስ ጋር በመገናኘታችን እጅግ በጣም ደስተኛ ነን›› ሲሉም አቶ ግሩም አክለዋል፡፡

ዝነኛዋ የቴሌቪዥን ፕሮግራም አቅራቢ መቅደስ ደበሳይ በበኩሏ ‹‹ተወዳጁ ዓባይ ቴሌቪዥን በቤተሰባዊነት ስሜት ስለተቀበለኝና ይህንን ስምምነት ስላደረግኩ በጣም ደስ ብሎኛል፡ ስለተማመናችሁብኝ ከልቤ አመሰግናለሁ›› ብላለች፡፡
Abbay TV

Pandora Dubai 🇦🇪VIP ትኬት በ400,000ብር!በፈረንጆቹ አቆጣጠር በጃንዋሪ 16 በፖንዶራ ዱባይ የሚዘጋጀው የስመጥሩ ድምፃዊ ኤፍሬም ታምሩ የሙዚቃ ዝግጅት የVIP ቦታ 24 ሰዓት ባ...
11/01/2025

Pandora Dubai 🇦🇪
VIP ትኬት በ400,000ብር!

በፈረንጆቹ አቆጣጠር በጃንዋሪ 16 በፖንዶራ ዱባይ የሚዘጋጀው የስመጥሩ ድምፃዊ ኤፍሬም ታምሩ የሙዚቃ ዝግጅት የVIP ቦታ 24 ሰዓት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ በኢትዮጵያውያን የሙዚቃ ዝግጅት ታሪክ በዱባይ ሪከርድ በሆነ ዋጋ ብር 400,000 ተሽጦ ማለቁ አነጋጋሪ ሆኗል::

አርቲስት መሀሙድ አህመድ  (  የክቡር ዶክተር)  ካሁን ቀደም ያልተሰሙ የህይወቱን ገጽታዎች አካቶ የተሰናዳው መጽሀፉ ትላንት ጥር 1 ቀን 2017 ዓ.ም በማሪዮት ሆቴል ለምረቃ በቅቷል።ለዝግ...
11/01/2025

አርቲስት መሀሙድ አህመድ ( የክቡር ዶክተር) ካሁን ቀደም ያልተሰሙ የህይወቱን ገጽታዎች አካቶ የተሰናዳው መጽሀፉ ትላንት ጥር 1 ቀን 2017 ዓ.ም በማሪዮት ሆቴል ለምረቃ በቅቷል።

ለዝግጀት 10 ዓምታትን የወሰደው መጽሐፉ፣ የክቡር ዶክተር አርቲስት መሀሙድ አህመድ ካሁን ቀደም ያልተሰሙ የህይወቱን ገጽታዎችን የያዘ ሆኖ የተሰናዳ ስለመሆኑ ደራሲው ወሰን ደበበ ማንደፍሮ ተናግሯል።

የክቡር ዶክተር አርቲስት መሀሙድ አህመድ ላለፉት 63 ዓመታት በሙዚቃው ዓለም ያሳለፋቸዉን ውጣ ውረዶች፣ የቤተሰብ የኋላ ታሪክና የወዳጅ ጓደኞቹን እንዲሁም የሙያ ባልደረባዎቹን ምስክርነት አካቶ የያዘው የሕይወት ታሪክ መፅሐፍ በጋዜጠኛና ደራሲ ወሰን ደበበ ማንደፍሮ ተዘጋጅቶ በንብ ኢንተርናሽናል ባንከ አማካኝነት ታትሞ ለንባብ ተዘጋጀቶዋል።

ንብ ባንክ በ3.5 ሚሊዮን ብር ሕትመቱን ስፖንሰር ማደርጉ ተገልጿል።

ኢንጂነር ቢጃናይ እና ዶ/ር ሐውለት አሕመድ 500 መጽሐፍትን በ2.5 በሚሊዮን ብር ገዝተዋል፣ የሰንሻይን ሪል ስቴት ባለቤት አቶ ሳሙኤል ታፈሰ በበኩላቸው በ500 ሺ ብር 100 መጽሐፍትን ገዝተዋል።

ታላቁ የፊልም ሰው. . .EBS ቅዳሜ መዝናኛ ከሚሶ ነጋያ ጀምሮ በርካታ የሙዚቃ ክሊፖችን ዳይሬክት በማድረግ የምናውቀውን ስንታየሁ ሲሳይን እንግዳ አድርጎ አቅርቦ ነበር ።በአሁን ጊዜ ያለበት...
06/10/2024

ታላቁ የፊልም ሰው. . .
EBS ቅዳሜ መዝናኛ ከሚሶ ነጋያ ጀምሮ በርካታ የሙዚቃ ክሊፖችን ዳይሬክት በማድረግ የምናውቀውን ስንታየሁ ሲሳይን እንግዳ አድርጎ አቅርቦ ነበር ።
በአሁን ጊዜ ያለበት አሳዛኝ የኑሮ ፈተናንም ለህዝብ አድርሷል ።
https://youtu.be/VuwCj7pCom8?si=1bomNf_L-F0FALjf

Wasihune Tesfaye ተከታዩን ፅሁፍ ስለ ስንታየሁ አጋርቷል ።

ታላቁ የፊልም ሰው. . ...
ከጥቂት ጊዜያት በፊት ፡ ቦሌ ላይ ፡ በዘመናዊ ካሜራዎችና ፡ የስቱዲዮ እቃዎች የተሞላ የትልቅ ስቱዲዮ ባለቤት የነበረ ፡ ልጆቹን ዘመናዊ ትምህርት ቤት ያስተምር የነበረ. . በኢትዮጵያ ውስጥ ቁጥር አንድ የፊልም ዳይሬክተር ..ስንታየሁ ሲሳይን የሚያክል ሰው . ህይወት ጋደል ብላበት የቤት ኪራይ የሚከፍለው አጥቶ ሲቸገር አስባችሁታል ?....
መኪናውን ሽጦ ፡ ከሰው ተበድሮ ፡ እንደምንም ብሎ ልጆቹን ለማስተማር ሞክሮ በመጨረሻ ግን አቅቶት የዚህ ጎበዝ ልጅ. ልጆቹ የትምህርት ቤት የሚከፍሉት አጥተው. .. በዚህ ዘመን እቤት ለመዋል ሲገደዱ. .ማሰብ ይከብዳል ።
...ግን ምን ይደረግ ህይወት አንዳንዴ ፊቷን ታዞር የለ ፡ ስንታየሁንም የገጠመው ይሄ ነገር ነው ።
ስንታየሁ ሲሳይን የሚያክል ታላቅ ባለሙያ በዚህ መልኩ ህይወት ከብዶት ሰው ፊት ሲቆም ያሳዝናል ። .....
ይህ ታላቅ የጥበብ ሰው በውጭ ሀገር ቢሆን ፡ ቪዲዮዎቹን የሚቀርፀው በራሱ ሄሊኮፕተር ይሆን ነበር ። አልሆነም ። ስንታየው ፡ ዛሬ የኛን ድጋፍ የሚፈልግበት ጊዜ ላይ ነው ። ይህ ጎበዝ ሰው ዳግም በእግሩ ቆሞ የተለመዱ ስራዎችን እንዲያበረክት የወገን እገዛ ይፈልጋል ። ...
ለተባበረ ወገን ስንታየሁን ወደቀድሞ ከፍታው ላይ እንዲሆን ማገዝ ቀላል ነው ። አለሁ እንበለው ፡ አነሰ በዛ ሳንል ተባብረን የምንጥላት እያንዳንዷ ጠጠር ፡ ይህንን ታላቅ ባለሙያ ዳግም ወደካሜራው መመለስ ይችላል ።
1000351511285 - ስንታየሁ ሲሳይ CBE...
ከጥቂት ጊዜያት በፊት ፡ ቦሌ ላይ ፡ በዘመናዊ ካሜራዎችና ፡ የስቱዲዮ እቃዎች የተሞላ የትልቅ ስቱዲዮ ባለቤት የነበረ ፡ ልጆቹን ዘመናዊ ትምህርት ቤት ያስተምር የነበረ. . በኢትዮጵያ ውስጥ ቁጥር አንድ የፊልም ዳይሬክተር ..ስንታየሁ ሲሳይን የሚያክል ሰው . ህይወት ጋደል ብላበት የቤት ኪራይ የሚከፍለው አጥቶ ሲቸገር አስባችሁታል ?....
መኪናውን ሽጦ ፡ ከሰው ተበድሮ ፡ እንደምንም ብሎ ልጆቹን ለማስተማር ሞክሮ በመጨረሻ ግን አቅቶት የዚህ ጎበዝ ልጅ. ልጆቹ የትምህርት ቤት የሚከፍሉት አጥተው. .. በዚህ ዘመን እቤት ለመዋል ሲገደዱ. .ማሰብ ይከብዳል ።
...ግን ምን ይደረግ ህይወት አንዳንዴ ፊቷን ታዞር የለ ፡ ስንታየሁንም የገጠመው ይሄ ነገር ነው ።
ስንታየሁ ሲሳይን የሚያክል ታላቅ ባለሙያ በዚህ መልኩ ህይወት ከብዶት ሰው ፊት ሲቆም ያሳዝናል ። .....
ይህ ታላቅ የጥበብ ሰው በውጭ ሀገር ቢሆን ፡ ቪዲዮዎቹን የሚቀርፀው በራሱ ሄሊኮፕተር ይሆን ነበር ። አልሆነም ። ስንታየው ፡ ዛሬ የኛን ድጋፍ የሚፈልግበት ጊዜ ላይ ነው ። ይህ ጎበዝ ሰው ዳግም በእግሩ ቆሞ የተለመዱ ስራዎችን እንዲያበረክት የወገን እገዛ ይፈልጋል ። ...
ለተባበረ ወገን ስንታየሁን ወደቀድሞ ከፍታው ላይ እንዲሆን ማገዝ ቀላል ነው ። አለሁ እንበለው ፡ አነሰ በዛ ሳንል ተባብረን የምንጥላት እያንዳንዷ ጠጠር ፡ ይህንን ታላቅ ባለሙያ ዳግም ወደካሜራው መመለስ ይችላል ።
1000351511285 - ስንታየሁ ሲሳይ CBE

Saturday afternoon infotainment show with magazine format; lifestyle, tea time guests, book review, music, cooking segment, and many more…, every Saturday at...

መጠሪያዬ የቬሮኒካ አዳነ የሙዚቃ አልበም  መለቀቂያዉ ቀን ተራዘመ ።ኪነት ኢንተርቴመንት የድምጻዊት ቬሮኒካ አዳነ መጠሪያዬ የተሰኘው የመጀመሪያ አልበም በቀጣይ ሳምንት እንደሚለቀቅ በዛሬው እ...
19/08/2024

መጠሪያዬ የቬሮኒካ አዳነ የሙዚቃ አልበም መለቀቂያዉ ቀን ተራዘመ ።

ኪነት ኢንተርቴመንት የድምጻዊት ቬሮኒካ አዳነ መጠሪያዬ የተሰኘው የመጀመሪያ አልበም በቀጣይ ሳምንት እንደሚለቀቅ በዛሬው እለት በሀያት ሪጀንሲ ሆቴል በተሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ተገልጿል።

መጠሪያዬ አልበም 12 ሙዚቃዎች ያሉት ሲሆን አልበሙን ስርቶ ለማጠናቀቅ 3 ዓመት ፈጅቷል አልበሙ ላይ ሁለት የሙዚቃ ቪዲዮዎች በአሜሪካ አትላንታ ተሰርተዋል፡፡

ይህ አልበም አጠቃላይ ከስድስት ሚሊየን ብር በላይ ወጪ የወጣበት ሲሆን የአልበሙ ሙሉ በሙሉ ወጪ በድምጻዊት ቬሮኒካ አዳነ ፕሮዲዩስ የተደረገ ሲሆን አልበሙን በማኔጅመንት ኪነት ኢንተርቴይመንት ማኔጅ አደርጎቷል፡፡

ይህ አልበም ዞጃክ ወርልድ ዋይድ የተስኘ አለም አቀፍ የሙዚቃ ካምፓኒ ጋር በ160,000 ዶላር በመላው አለም ለማከፋፈል ከአርቲስቷ ጋር ተስማምተዋል።

ዞዳክ ወርልድ ዋይድ መቀመጫውን በአሜሪካ ፍሎሪዳ ያደረገ ሲሆን በተለያዩ አለማት ማለትም ሜክሲኮ ፣ ኢንዶኒዢያ ፣ ጀማይካ እና ኬንያ ቅርንጫፎች ያሉት ሲሆን ይህ ካምፓኒ የኢትዮጵያን አልበም ሲገዛ የመጀመሪያው ነው፡፡

መጠሪያዬ የተሰኘው አልበም የፊታችን ነሀሴ 23 ቀን 2016 ዓ.ም በቬሮኒካ አዳነ ዩቲዩብ ቻናል ፣ በካሴት የቴሌግራም ቻናል እና በሁሉም አለም አቀፍ የሙዚቃ መተግበሪያዎች ላይ ይለቀቃል፡፡

ድምጻዊት ቬሮኒካ አዳነ ሙዚቃው ነሐሴ 14 ቀን 2016 ዓ.ም ይለቀቅ የነበረ ቢሆንም በህጻን ሔቨን ላይ የደረሰውን ጥቃት ምክንያት በማድረግ አንድ ሳምንት መራዘሙን ድምጿዊቷ ገልጻለች።

በዓይነቱ ልዩ የሆነ "ጥቁር አደይ"  የተሰኘ ፊልም ለእይታ ሊበቃ እንደሆነ ተገለፀበዓይነቱ ልዩ የሆነ "ጥቁር አደይ"  የተሰኘ ፊልም ለእይታ ሊበቃ እንደሆነ  የፊልሙ አዘጋጆች ዛሬ ሰኔ25 ...
02/07/2024

በዓይነቱ ልዩ የሆነ "ጥቁር አደይ" የተሰኘ ፊልም ለእይታ ሊበቃ እንደሆነ ተገለፀ
በዓይነቱ ልዩ የሆነ "ጥቁር አደይ" የተሰኘ ፊልም ለእይታ ሊበቃ እንደሆነ የፊልሙ አዘጋጆች
ዛሬ ሰኔ25 ቀን /2016 ዓ.ም በቬልቪው ሆቴል በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ አስታውቀዋል።

👉ይህ ፊልም በ www.Netflix.com ሊታይ እንደሚችል ተጠቁሟል።

በበርካታ የአማርኛ ፊልሞች በደራሲነትና በአዘጋጅነት እንዲሁም ለበርካታ ስመጥር ድምፃዊያኖች ግጥምና ዜማ በምሥራት የሚታወቀው ፍፁም ካሣሁን የተዘጋጀው "ጥቁር አደይ " የተሰኘው ልብ አንጠልጣይ ፊልም ሐምሌ10 ቀን 2016ዓ.ም በሸራተን አዲስ ሆቴል ከቀኑ 10፡00 ሰዓት ጀምሮ በቀይ ምንጣፍ በልዩ ሁኔታ የፊልም ባለሙያዎችን ባከበረ በደማቅ ሥነ ሥርዓት ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች፣ አምባሳደሮች፣ ታዋቂ ግለሰቦች፣ ባለሀብቶች፣ አርቲስቶች፣ የመገናኛ ብዙሀን
ባለሙያዎችና የኪነ ጥበብ አፍቃሪያን በተገኙበት በታላቅ ድምቀት ይመረቃል።

የዚህ "ጥቁር አደይ" ፊልም :-
👉ደራሲ ፍፁም ካሳሁን
👉ዳሬክተር ፍፁም ካሳሁን
👉ካሜራ ጳውሎስ ፀጋዬ
👉ኤዲተር ያዕቆብ ና ቤተልሔም

ተዋንያን:-
👉ኤደን አይሸሹም፣ካሣሁን ፍስሐ(ማንዴላ)፣ናታን ጌታቸው፣ነቢዩ እንድሪስ፣ሚኪ ተስፋዬ ፣ሜሮን አብርሃም ፣የአብሥራ ሺመክት፣ማሕተመ ኃይሉ በአጠቃላይ በትወና 180 የሚደርሱ ተዋንያን ተሳትፈውበታል ።

👉የፊልሙ እርዝማኔ=1:50 ደቂቃ
👉ፊልሙ የሚፈጀው ጊዜ =3 ዓመት
👉ፊልሙ የወጣበት ወጪ=6.7 ሚሊየን ብር
👉ፕሮዲዩሰር =ሕሊና ደረጄ

ጥቁር አደይ የተሰኘወ ፊልም ይፍቱስራ የምትባል ወጣት ሴት ከከተማ ግርግር እና ብልጭልጭ አለም ወጥታ የግብርና ሥራን በመምረጥ ሲዳማ ክልል በሚገኝ ቤተሰቦቿ በሰጧት መሬት ላይ የግብርና ስራ በመሰራት ህይወቷን እየገፋች ባለችበት ጊዜ ቢልልኝ የተባለ ወጣት በ ፍቅርሽ ተይዣለሁ የኔ መሆን አለብሽ በማለት በህይወቷ ላይ ጣልቃ በመግባት ህይወቷን ሲያከብደወ እንዲሁም በዙሪያዋ ያሉ ሰዎችንም በመግደል ህይወቷን ሲያከብደዉ ይታያል። ይህንንም ፈተና ለማለፍ የምቴድበትን ከባድ መንገድ በግሩም የትወና ጥበብ እና የቀረፃ ጥበብ የሚያሳይ ፊልም ነዉ።

ለዚህ ፊልም ለእይታ እንዲበቃ አስተዋፅኦ ያደረጉ
👉አብርሃም ግዛው ኢንተርቴይመንት
👉ስንቅ ማልት
👉አሃዱ ባንክ
👉በረከት ገበሬዋ(የቀረፃ ቦታ በመተባበር ) ናቸው።

በ18 ቢሊየን ብር በአዲስ አበባ በ11 ክፍለ ከተማ የአርቲስቶች መንደር ሊገነባ ነው!   | በኢትዮጵያ ያለውን የኪነ-ጥበብ እድገት ከዚህ በፊት ከነበረው ሁኔታዎች በተሻለ ሁኔታ ለመስራት እ...
19/10/2023

በ18 ቢሊየን ብር በአዲስ አበባ በ11 ክፍለ ከተማ የአርቲስቶች መንደር ሊገነባ ነው!
| በኢትዮጵያ ያለውን የኪነ-ጥበብ እድገት ከዚህ በፊት ከነበረው ሁኔታዎች በተሻለ ሁኔታ ለመስራት እንዲቻል መንግስትን፣ ባለሀብቶችን የተቀረውን ህዝብ በማስተባበር ሦስት ዋና ዋና ተግባራትን ለመስራት ታስቧል፡፡
እነሱም የጥበብ ውለታ የጋራ የመኖሪ መንደር፤ የጥበብ ውለታ ኢንተርናሽናል ት/ቤት፤ የጥበብ ውለታ የመመጋቢያ የመዝናኛ ማዕከል በማስገንባት የጥበብ ቤተሰብ ከልመና እና ከችግር የሚወጣበትን ስራ ለመስራት እንቅስቃሴ እየተደረግ እንደሆነ ዛሬ ጥቅምት 02/2016 ዓም በቤስት ዌስተርን ፔርል አዲስ ሆቴል በተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ ተገልጻል፡፡
የጥበብ ውለታ ሦስቱም ዓላማ በአዲስ አበባ ባሉት በ11 ክፍለ ከተማ ላይ ተግባራዊ እንዲሆን የሚሰራ ሲሆን የቤቱን ብቻ ብንመለከት 990 የጥበብ ሰዎች የቤት ባለቤት የሚሆኑበትን እድል የሚፈጥር ይሆናል ተብሏል፡፡
በአንድ ክፍለ ከተማ ላይ የጥበብ ውለታ የጋራ የመኖሪያ መንደር ሲገነባ 90 አርቲስቶችን የቤት ባለቤት የሚያደርግ ሲሆን 500,000,000 (አምስት መቶ ሚሊየን) ብር ወጪ ያስፈልጋል ለጥበብ ውለታ ኢንተርናሽናል ት/ቤት 700,000,000/ ሰባት መቶ ሚሊዮን ብር ይፈልጋል፤ የጥበብ ውለታ የመመጋቢያ የመዝናኛ ማዕከል ደግሞ 600,000,000/ ስድስት መቶ ሚሊየን ብር ያስፈልጋል፡፡
በአጠቃላይ የጥበብ ውለታ ዓላማን ለማሳካት በአንድ ክፍለ ከተማ ላይ 18,000,000,000 (አስራ ስምንት ቢሊየን) ብር የሚያስፈልግ መሆንን እንደሚያስፈልግ ነው በመግለጫው የተገለጸው፡፡
ይህን የጥበብ ውለታ ዓላማን ለማሳካት የታሰቡ እንቅስቃሴዎች የተጀመሩ ሲሆን በአሁኑ ወቅት የተለያዩ አርቲስቶችን የያዘ ቡድን በእንግሊዝ ሀገር የሚገኝ ሲሆን በዛም ለጥበብ እንሮጣለን የሚል ሩጫ ፕሮግራም፤ የጥበብ ውለታ የእራት ፕሮግራም እና በጎ ፈንድ ሚ ገቢ ማሰባሰብ እንደሚደረግ ነው የተገለጸው፡፡

Address

Kirkos
Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Biruh Entertainment posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share