Lemi kura wereda 06 proseperity page

Lemi kura wereda 06 proseperity page የሚዲያ ተደራሸነትን ለማረጋገጥ

"መደበኛ ህዋስ ውይይት ለተሻለ ተቋም ግንባታ"በወረዳችን የሚገኙ የብልጽግና ፓርቲ የሁሉም ማህበራዊ መሰረት የሚገኙ ህዋሳቶች ወርሀዊ መደበኛ የህዋስ ውይይት እየተደረገ ይገኛል።በለሚ ኩራ ወረ...
05/01/2025

"መደበኛ ህዋስ ውይይት ለተሻለ ተቋም ግንባታ"

በወረዳችን የሚገኙ የብልጽግና ፓርቲ የሁሉም ማህበራዊ መሰረት የሚገኙ ህዋሳቶች ወርሀዊ መደበኛ የህዋስ ውይይት እየተደረገ ይገኛል።

በለሚ ኩራ ወረዳ 06 የብልጽግና ፓርቲ የመኖሪያ ፣የቢሮ ፣የጥቃቅን፣የትምህርት ቤት፣የወጣት ሊግ ፣የሴት ሊግ ፣ተቋማቶች በሚገኙበት ቀጠናና በተቋማቸው በየህዋሶቻቸው ወርሀዊ ውይይት በሚዲያ አጠቃቀም ዙሪያና የኮር ሚና በሚል አጀንዳ በሳል ውይይቶች እየተደረጉ ይገኛል።

በውይይቱ ሚዲያ ህዝብ ጋር ለመድረስ ትልቅ በቀጣይ አቅም እንዳለውና ለበጎ ስራ ሚዲያን በመጠቀም ፓርቲያችን የሰራቸውን ስራዎች በሰፊው ተደራሽ ማድረግ እንደሚገባ ተግባቦት መፍጠር ተችሏል።

ለሚ ኩራ ወረዳ 6 ፓርቲ ሚዲያ
ታህሳስ 26/2017 ዓ ም

ፕሬስ ሪሊዝለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለገና በአል በሰላም አደረሳችሁ።🎄🎄🎄🎄🎄🎄🎄🎄🎄🎄🎄🎄🎄🎄🎄🎄🎄🎄🎄🎄🎄🎄🌲🌲🌲🌲🌲🌲በለሚ ኩራ ወረዳ 6 አስተዳደር ገና በዓልን ምከንያት በማድ...
05/01/2025

ፕሬስ ሪሊዝ

ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለገና በአል በሰላም አደረሳችሁ።
🎄🎄🎄🎄🎄🎄🎄🎄🎄🎄🎄🎄🎄🎄
🎄🎄🎄🎄🎄🎄🎄🎄🌲🌲🌲🌲🌲🌲
በለሚ ኩራ ወረዳ 6 አስተዳደር ገና በዓልን ምከንያት በማድረግ ዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ ለሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች የማዕድ ማጋራት ፕሮግራም እንደሚካሄድ ተገለፀ፡

የገናን በአል ምክንያት በማድረግ በነገው እለት 28/04/2017 ዓ/ም ከተለያዩ በጎ አድራጊ ድርጅቶች እና ግለሰቦች ጋር በመተባበር በወረዳዉ ዉስጥ ለሚገኙ 3500 በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙና አቅመ ደካማ የሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎችን ማእድ ለማጋራት የቅድመ ዝግጅት ስራውን ማጠናቀቁን የለሚ ኩራ ወረዳ 6 የህብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ዘውዴ ውብሸት ገልጸዋል ።

ድጋፉ የበዓል መዋያ የዘይት ፤የዱቀት እና እንቁላልን ጨምሮ የተለያዩ ግበዓቶች እንደሆኑ ነዉ ተገልጿዋል ፡፡

በተጨማሪም ለበአሉ የታደሱ የአቅመ ደካማ ቤቶቾ በነገው እለት ርክክብ እንደሚደረግ ሀላፊው ጨምረው ገልጸዋል።

መልካም በአል
ለሚ ኩራ ወረዳ 6 ፓርቲ ሚዲያ

 /ቤት_ግንባታ_አሁናዊ_የግንባታ_ሂደት_በፎቶ
03/01/2025

/ቤት_ግንባታ_አሁናዊ_የግንባታ_ሂደት_በፎቶ

የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 06 ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በዛሬው እለት የቢሮ ሙህራን  የታህሳስ ወር ህዋስ ውይይት አካሄደ::   የህዋስ ውይይቶቹ ለፓርቲ ተቋም ግንባታ ከፍተኛውን...
03/01/2025

የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 06 ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በዛሬው እለት የቢሮ ሙህራን የታህሳስ ወር ህዋስ ውይይት አካሄደ::

የህዋስ ውይይቶቹ ለፓርቲ ተቋም ግንባታ ከፍተኛውን ድርሻ ይወሰዳሉ በህዋስ ውይይት የፓርቲ እሳቤዎችን በማስረጽ የሚያጋጥሙ ችግሮችን በጋራ በመወያየትና የአባላትን አቅም በመገንባት እንዲሁም የጋራ ትርክትን ለማስረጽ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያበረክታል::በተደረገው የቢሮ ሙሁራን ህዋስ ውይይት በየማህበራዊ መሠረታቸው ተወያይተዋል።



ታህሳስ 25/2017 ዓ/ም
👉የለሚ ኩራ ወረዳ 06 ፓርቲ ሚዲያ

በክፍለ ከተማ ደረጃ የተዋቀረው የሱፐርቪዥን ቡድን በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 6 ፓርቲ ጽ/ቤት ምዘና ማካሄድ ጀመረ።የሱፐርቪዥን ቡድኑ ዛሬ በውሎው የወረቀት ስራዎችን ምልከታ ሲያደርግ ውሏ...
02/01/2025

በክፍለ ከተማ ደረጃ የተዋቀረው የሱፐርቪዥን ቡድን በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 6 ፓርቲ ጽ/ቤት ምዘና ማካሄድ ጀመረ።

የሱፐርቪዥን ቡድኑ ዛሬ በውሎው የወረቀት ስራዎችን ምልከታ ሲያደርግ ውሏል።

የለሚ ኩራ ወረዳ 6 ፓርቲ ሚዲያ
ታህሳስ 24/2017 ዓ.ም

"ገዢ ትርክትን ማስረፅ"በሚል መሪ ሀሳብ ከማህበረሰብ አንቂዎች ጋር የገፅ ለገፅ የተግባቦት ውይይት ተካሄደ።"ገዢ ትርክትን ማስረፅ"  በሚል መሪ ሀሳብ በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ የገፅ ለገፅ የ...
31/12/2024

"ገዢ ትርክትን ማስረፅ"በሚል መሪ ሀሳብ ከማህበረሰብ አንቂዎች ጋር የገፅ ለገፅ የተግባቦት ውይይት ተካሄደ።

"ገዢ ትርክትን ማስረፅ" በሚል መሪ ሀሳብ በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ የገፅ ለገፅ የተግባቦት መድረክ በብልፅግና ፓርቲ የህዝብ ግንኙነትና ሚዲያ ዘርፍ ከክፍለ ከተማና ከወረዳ የማህበረሰብ አንቂዎች ጋር ውይይት አካሄደ።

የለሚ ኩራ ክ/ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ የሚዲያና ህዝብ ግንኙነት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ግዛቸዉ ገ/ሚካኤል እንደ ገለፁት የውይይቱ ዋና ዓላማ በገዢ ትርክትና ህብረ ብሄራዊ አንድነትን በማጠናከር በሀገር ግንባታ ሂደት የማህበረሰብ አንቂዎች ጉልህ ሚና አላየዉ፣በተለይም የአስተሳሰብና የሀሳብ አንድነት በማምጣት የሀገራችንን እድገትና ልማት በማስመዘገብ ሁለንተናዊ ብልፅግናን ማረጋገጥ ሲሆን ሀገራዊ እሳቤዎች በአግባቡ በመገንዘብ አሰባሳቢ ሀሳቦችን ከፍ በማድረግ ህብረ ብሔራዊ ወንድማማችነትና እህትማማችነት ማረጋገጥ እንደሆነ ገልፀዋል።

አቶ ግዛቸዉ አክለዉም ገዥ ትርክትን በሚገባ ለመስረፅና ህብረ ብሄራዊነትን ለማጠናከር ከማህበረሰብ አንቂዎች ጋር በተደረገ ውይይት ከነጠላ ትርክት ይልቅ የወል እውነትና ትርክትን የሚያጠናክር ማህበረሰብ አንቂ ህብረ ብሄራዊት የሆነች ኢትዮጵያን ለመገንባት በሚደረገው በሀገር ግንባታ ሂደት ጎልህ ድርሻ እንዳለው የተመላከተ ገንቢ ውይይት የተደረገ መሆኑን ገልፀዋል።

በማጠቃለያዉም በውይይቱ ውጤታማ ህብር ብሄራዊነትን ለማጠናከር የመደመር ትውልድ ገዥ ትርክትን በተገቢው ያሰረፀ ውይይት መደረጉን ተሳታፊዎች ገልፀዋል ።

ለሴት አመራሮች የውሳኔ ሰጭነት እና የአመራርነት ሚና ስልጠና ተሰጠ፡የለሚ ኩራ ክ/ከተማ  ሴቶች ህጻናትና ማህበራዊ ጉዳይ ጽ/ቤት የሴት አመራሮችን አቅም ለማጎልበት   በሴቶች ውሳኔ ሰጭነት ...
31/12/2024

ለሴት አመራሮች የውሳኔ ሰጭነት እና የአመራርነት ሚና ስልጠና ተሰጠ፡

የለሚ ኩራ ክ/ከተማ ሴቶች ህጻናትና ማህበራዊ ጉዳይ ጽ/ቤት የሴት አመራሮችን አቅም ለማጎልበት በሴቶች ውሳኔ ሰጭነት እና የአመራር ብቃት ስልጠና መሰጠቱ ተገልጿል፡፡

በመድረኩ ላይ ተገኝተው የማጠቃለያ ንግግር ያደረጉት የለሚ ኩራ ክ/ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት አደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ የሆኑት ወ/ሪት ወይንሸት አስናቀ ስልጠናው ጥሩ መነሳሳና ቁጭትን የሚያጭር ነው ያሉ ሲሆን የሰለጠነውን ስልጠና ወደ ተግባር ቀይረን በህይወታችን ተግባራዊ ማድረግ ያስፈልጋል ብለዋል፡፡

የለሚ ኩራ ክ/ከተማ ሴቶች ህጻናትና ማህበራዊ ጉዳይ ጽ/ቤት ኃላፊ የሆኑት ወ/ሮ ሙሉ እመቤት ስራህ ብዙ የሴቶችን የአመራርና የውሳኔ ሰጭነት አቅም ለማጎልበት ከተቀመጡ የልማትና የለውጥ ፓኬጆች አንዱ የሴቶችን ውሳኔ ሰጭነትና የአመራር ብቃት ማሳደግ መሆኑን ገልጸው በሴቶች ውሳኔ ሰጭነት እና የአመራር ሚና ዙሪያ ከወረዳ እስከ ክ/ከተማ ለሚገኙ ሴት አመራሮች ስልጠና መሰጠቱን ተናግረዋል፡፡

ወ/ሮ ሙሉእመቤት ሴቶች የሀገር ዋልታና መሰረት በመሆናቸው በተለያየ ደረጃ በሚገኙ የአመራርነት ማዕቀፎች ማሳተፍ እና የአመለካከት ለውጥ ማምጣት ሲቻል መሆኑን ገልጸው ሴቶች ከቤተሰብ ጀምሮ በየትኛውም የስልጣን ደረጃ መሳተፍ እንዳለባቸው ተናግረዋል፡፡

የለሚ ኩራ ክ/ከተማ ወረዳ 6 ኢንስፔክሽንና ስነ_ምግባር ኮሚሽን  ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ፅ/ጽ/ቤት በመገኘት የፓርቲ ስራዎች ያሉበትን ደረጃ ምልከታ አደረገ።ምልከታው የድጋፍና ክትትል ሲሆን የ2...
30/12/2024

የለሚ ኩራ ክ/ከተማ ወረዳ 6 ኢንስፔክሽንና ስነ_ምግባር ኮሚሽን ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ፅ/ጽ/ቤት በመገኘት የፓርቲ ስራዎች ያሉበትን ደረጃ ምልከታ አደረገ።

ምልከታው የድጋፍና ክትትል ሲሆን የ2017 በጀት አመት የውስጠ ፓርቲ ተግባራት የፖለቲካና አደረጃጀት ስራዎች ያሉበትን ደረጃ በመገምገም በቀሪ ስራዎች ትኩረት ሊደረግባቸው የሚገቡ ተግባራትን መለየት እና በክፍተት የሚታዩ ጉዳዮች በፍጥነት እንዲታረሙ ለማገዝ እና ጥንካሬዎችን ለማስቀጠል የሚያግዝ መሆኑን ኢንስፔክሽን ቡድኑ አሳውቋል ።

የወረዳው ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ሙሉቀን ቸኮል ጠንካራ ድጋፍ ፣ ክትትል እና ምዘና ማካሔድ ጠንካራ ተቋምን ለመገንባት የሚያደርገው አስዋጽኦ ጉልህ በመሆኑ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት እና በቀጣይ እንደ ወረዳችን የተገኙ ክፍተቶችን ፈጥኖ ለማረም በጋራ እንሰራለን ሲሉ ገልፀዋል።

ታህሳስ 21/2017ዓ.ም
ለሚ ኩራ ወረዳ 6 ፓርቲ ሚዲያ

የጉለሌ ክ/ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ፅ/ቤት የሚዲያና ህዝብ ግንኙነት ዘርፍ ለለሚኩራ አቻ ክፍለ ከተማ  ዘርፍ በተሰሩ ስራዎች ዙሪያ ልምዱን አካፈላ።የልምድ ልውውጡን በማስመልከት ገለፃ ያደረ...
29/12/2024

የጉለሌ ክ/ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ፅ/ቤት የሚዲያና ህዝብ ግንኙነት ዘርፍ ለለሚኩራ አቻ ክፍለ ከተማ ዘርፍ በተሰሩ ስራዎች ዙሪያ ልምዱን አካፈላ።

የልምድ ልውውጡን በማስመልከት ገለፃ ያደረጉት
የጉለሌ ክ/ከተማ ብልፅግና ፓርቲ የሚዲያና ህዝብ ግንኙነት ዘርፍ ኃላፊ የሆኑት አቶ ጤናው አለማየሁ፣ ባለፉት 6 ወራት የፓርቲን እሳቤ ከማስረፅ አኳያ የስራ አካባቢውን ምቹ ከማድረግ ጀምሮ ተሞክሮ እስከመቀመር ድረስ ውጤታማ ስራዎች እንደተሰሩ ገልፀዋል፡

ለተልዕኮ መሳካት የአመራሩ፣ የአባሉና የበጎ ማህበር ሰብ አንቂዎች ተሳትፎ የጎላ ሚና እንደነበረው የጠቀሱት አቶ ጤናው ፣ የፓርቲውን ገፅታ ለመገንባት የተሰሩ የብራንዲንግ ስራዎች ፣ ስልጠናዎች ፣ የንቅናቄ ተግባራትና ፓርቲና ህዝብን ለማቀራረብ የተሰሩ ስራዎች የቅንጅ ውጤት መሆኑን በስፋት አብራርተዋል።

የመረጃ አያያዝን የማዘመን፣ ፓርቲውን በብራንዲንግ አጉልቶ የማስተዋወቅ፣ ዲጂታል ላይብረሪ የማደራጀት፣ ከላይ እስከ ታች ወጥ የኮሙኒኬሽን አግባብ በመዘርጋት አበረታች ስራዎች መሠራታቸውን የገለፁት አቶ ጤናው ፣ የእያንዳንዱ ተግባራትን ናሙና በማሳየት ያላቸውን የካበተ ልምድ አካፍለዋል።

የለሚኩራ ክፍለ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ፅ/ቤት የሚዲያና ህዝብ ግንኙነት ዘርፍ ሃላፊ አቶ ገዛቸው ገ/ሚካኤል ባጭር ስዓት ባዩት ነገር ላይ መደሰታቸውን የገለፁ ሲሆን ለለሚኩራ ልምድ የሚሆኑ በርካታ ስራዎች መኖራቸውንና በቀጣይ ወደ ክ/ከተማና ወረዳ በመውሰድ የማስፋት ስራ እንደሚሰራ ገልፀዋል። ሃላፊው በሰጡት ተጨማሪ ሃሳብ በቀጣይም በጋራ ጉዳዮች ላይ በትብብር ለመስራት ያላቸውን ቁርጠኝነት ገልፀዋል::

 #ማስታወቂያ #የልማታዊ ሴፍትኔትን በተመለከተበለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 06 አስተዳደር  የስራ ክህሎት ጽ/ቤት በማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ አማካኝነት በቀጥታ ድጋፍና በአካባቢ ልማት ተጠቃሚ ...
27/12/2024

#ማስታወቂያ
#የልማታዊ ሴፍትኔትን በተመለከተ

በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 06 አስተዳደር የስራ ክህሎት ጽ/ቤት በማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ አማካኝነት በቀጥታ ድጋፍና በአካባቢ ልማት ተጠቃሚ የሚሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎችን በስትሪንግ ኮሚቴ ለይቶ አጽድቋል።

እነዚህ የተለዩ የህዝረተሰብ ክፍሎች ላይ ህብረተሰቡ ሀሳብ እንዲሰጥ ግልፅ አሰራር ለመከተል በሁሉም ቀጠናዎች የማስተቸት ስራ የተሰራ ሲሆን ስም ዝርዝራቸዉ በቀን 16/04/2017 ዓ.ም በወረዳው በሚገኙ በሁሉም ክላስተር በሚታይ ቦታ የተለጠፈ በመሆኑ ማንኛዉም ቅሬታ ያለዉ አካል በወረዳው ለተቋቋሙ የቅሬታ ኮሚቴ በአካል በመቅረብ ከነገ ታህሳስ19/2017 ጀምሮ ለተከታታይ 5ቀናት ቢሮ ቁጥር 8 ቅሬታ ኮሚቴ ቅሬታ ማቅረብ የሚቻል መሆኑን ፅ/ቤቱ ገልጿል።

የለሚ ኩራ ወረዳ 6 ፓርቲው ሚዲያ
ኮሙኒኬሽን ፅ/ቤት

ታህሳስ 18/2017

 /ቤት_የአካል_ብቃት_እንቅስቃሴ_ፕሮግራም_ተደረገለሚ ኩራ ወረዳ 06 ፓርቲ ሚዲያታህሳስ 18/2017 ዓ.ም የአካል ብቃት እንቅስቃሴ  አላማም  በት/ቤቶች ስፖርትን ባህሉ ያደረገ ማህበረሰብ ...
27/12/2024

/ቤት_የአካል_ብቃት_እንቅስቃሴ_ፕሮግራም_ተደረገ

ለሚ ኩራ ወረዳ 06 ፓርቲ ሚዲያ
ታህሳስ 18/2017 ዓ.ም

የአካል ብቃት እንቅስቃሴ አላማም በት/ቤቶች ስፖርትን ባህሉ ያደረገ ማህበረሰብ ለመፍጠር እየተሰራ ያለውን ስራ ለማበረታታት ሲሆን በመርሀ ግብሩ ላይም የለሚ ኩራ ክ/ከተማ ወረዳ 06 ወጣቶችና ስፖርት ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ታደሰ ዌሊሳ ተገኝተዋል።

ኃላፊው ባስተላለፉት መልእክት ማለዳ በመውጣት የአካል ብቃት እንቅስቃሴ በማድረግ ጤናችሁን ለመጠበቅ የምታደርጉት ጥረት ስፖርትን በወረዳችን ባህል እንድናደርግ
ጤናው የተጠበቀ አምራች በአካልና በአእምሮ የዳበረ ማህበረሰብ ለመፍጠር የሚረዳ እንደሆነ አንስተው በቀጣይም የዚህ አይነት ፕሮግራም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል በመልዕክታቸው አስተላልፈዋል።

በመርሀ ግብሩም መምህራን፣ ተማሪዎች ፣ የት/ት ባለድርሻ አካላት የተሳተፉበት እንደነበር ታውቋል።

የብልፅግና የሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባላት በአዲስ አበባ የተገነቡትን  አጠቃላይ የልማት ሥራዎችን ጉብኝት በምስል:-
26/12/2024

የብልፅግና የሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባላት በአዲስ አበባ የተገነቡትን አጠቃላይ የልማት ሥራዎችን ጉብኝት በምስል:-

  አመራሩ_ምልከታ_ተደረገበለሚ ኩራ ክ/ከተማ ወረዳ 06 አስተዳደር ከከተማዋ የተለያዩ አከባቢዎች በኮሪደር ልማት ተነስተው የቦታ እጣ ላነሱ ዜጎች ምትክ መሬት ርክክብ እየተደረገ እንዳለ የለ...
26/12/2024

አመራሩ_ምልከታ_ተደረገ

በለሚ ኩራ ክ/ከተማ ወረዳ 06 አስተዳደር ከከተማዋ የተለያዩ አከባቢዎች በኮሪደር ልማት ተነስተው የቦታ እጣ ላነሱ ዜጎች ምትክ መሬት ርክክብ እየተደረገ እንዳለ የለሚ ኩራ ክ/ከተማ ወረዳ 06 ኮር አመራሮች በቦታው ተገኝተው ምልከታ አድርገዋል።

አዲስ አበባን እንደ ስሟ ውብ አበባ ለማድረግ መሰረተ ልማት ከማሟላት በተጨማሪ የሰው ህይወትን ለማሻሻል እና የነዋሪዎችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የከተማ አስተዳደሩ ትልቅ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ እንዳለ የሚታወቅ ነው ።።

ለሚ ኩራ ወረዳ 06 ፓርቲ ሚዲያ
ታህሳስ 17/2017

 #የፎቶ አውደርእይ ተካሄደየለሚኩራ ክ/ከተማ ወረዳ 6 ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት አዘጋጅነት በ2017 በጀት አመት በወረዳ አስተዳደሩ የተሰሩ አበይት ተግባራትን በፎቶ በማቀናጀት ለእይታ አብቅቷል።አ...
26/12/2024

#የፎቶ አውደርእይ ተካሄደ

የለሚኩራ ክ/ከተማ ወረዳ 6 ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት አዘጋጅነት በ2017 በጀት አመት በወረዳ አስተዳደሩ የተሰሩ አበይት ተግባራትን በፎቶ በማቀናጀት ለእይታ አብቅቷል።

አውደርዩን ያስጀመሩት የለሚ ኩራ ክ/ከተማ ወረዳ 06 አስተዳደር ዋና ስራ አስፈፃሚ ሲስተር ግሩም ንጉሴ እና የብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሙሉቀን ቸኮል ሲሆኑ የፎቶ አውደርዩ የተሰሩ ስራዎችን አጉልቶ የሚያወጣና ገላጭ እንደሆነ ተናግረዋል ።

በአውደርዩ የለሚኩራ ክ/ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ሚድያ ኃላፊ አቶ ግዛቸው ገ/ሚካኤል፣ የወረዳው ኮር አመራሮች፣አጠቃላይ አመራር እንዲሁም የሚድያ ሰራዊቶች የተሳተፉ ሲሆን ለቀጣዮቹ 2 ቀናት ለእይታ ክፍት ሆኖ እንደሚቀጥል ታውቋል።

ለሚኩራ ወረዳ 6 ፓርቲ ሚዲያ
17/4/2017

የማህበራዊ ሚዲያን ለሀገር ግንባታ እንጠቀም፨በለሚ  ኩራ ክ/ከተማ ወረዳ 06 አስተዳደር በፓርቲ ሚዲያና በኮሙኒኬሽን ፅ/ቤት አዘጋጅነት ለአመራሩና  ለሚዲያ ሰራዊት  አባላት የአቅም ግንባታ ...
26/12/2024

የማህበራዊ ሚዲያን ለሀገር ግንባታ እንጠቀም፨

በለሚ ኩራ ክ/ከተማ ወረዳ 06 አስተዳደር በፓርቲ ሚዲያና በኮሙኒኬሽን ፅ/ቤት አዘጋጅነት ለአመራሩና ለሚዲያ ሰራዊት አባላት የአቅም ግንባታ ስልጠና ተሰጠ።

"ፓለቲካዊ የህዝብ ግንኙነትና ሚዲያ አጠቃቀም"በሚል ርእስ ስልጠናውን በተጋባዥነት ተገኝተው የሰጡት የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ፓርቲ ሚዲያ ዘርፍ ሀላፊ የሆኑት አቶ ግዛቸው ገ/ሚካኤል ሲሆኑ የስልጠናው አላማ አመራሩና የሚዲያ ሰራዊቱ አለም አቀፍ የሚዲያ ሁኔታውንና ወቅቱን በመረዳት ራሳቸውን በንባብ፣ከራሳቸው ተሞክሮ በፍጥነት በመማር ራሳቸውን ለተልዕኳቸው በፍጥነት ማብቃት እንዲችሉና የማህበራዊ ሚዲያን ተጽእኖ በመረዳት ሚዲያውን ለበጎ አላማ እንዲጠቀሙ ለማስቻል ነው ብለዋል፡፡ እንዲሁም የአመራሩንና የሚዲያ ሰራዊቶችን አቅም ማጎልበት ፣ሁሉም የሚዲያ ሰራዊት የሚዲያ ተሳትፎ ወደ ተቀራራቢ ደረጃ ለማምጣትና ባለድርሻ አካላት በኮሙኒኬሽንና በፓርቲ ሚዲያ ፅህፈት ቤት የሚተገበሩ ተግባራትን በቅርበት እንዲያውቁ ለማድረግ ያለመ ነው።

በስልጠናው ላይ የወረዳው አስተባባሪዎችና ጠቅላላ አመራሮች እንዲሁም የሚዲያ ሰራዊቶች ተሳትፈዋል።

በስልጠናው ላይ መልእክታቸውን ያስተላለፉት የወረዳው ዋና ስራ አስፈጻሚ ሲስተር ግሩም ንጉሴ እንዳሉት አመራሩና በጎ የሚዲያ ሰራዊት አንቂዎች ወቅቱን የዋጀ ፈጣን እና ተአማኒነት ያለው መረጃ ለማህበረሰቡ ለማሰራጨት ከወረዳው ጎን ሆኖ በንቃት መሳተፍ እንደሚገባ አሳስበዋል።አክለውም አመራሩና ሁሉም የሚዲያ አንቂ አባላት ለሚሰራጭ መረጃ የመረጃ ምንጭ በመሆን ማህበሰቡን ከሀሰተኛ መረጃ በመከላከል ረገድ የተሰሩ ስሳዎችን ለህብረተሰቡ ተደራሽ ከማድረግ ረገድ ኃላፊነቱን ሊወጣ ይገባል ብለዋል።

የወረዳው ብልጽግና ቅ/ጽ/ቤት ሀላፊ የሆኑት አቶ ሙሉቀን መቸኮል በበኩላቸው ማህበራዊ ሚዲያን ስንጠቀም በእውቀት በክህሎትና በሀላፊትነት ስሜት በመጠቀም ለበጎ አላማ ማዋል ተገቢ መሆኑን ገልጸው በዋነኝነትም ለዚህ ዓላማ መሳካት የአባሉ ሚና ከፍተኛ በመሆኑ ያለንን እምቅ አቅም በበጎ መንገድ በመጠቀም ሚዲያን የወል እውነትን ለማፅኛ ማድረግ ይገባናል ብለዋል ።

በስልጠናው በማህበራዊ ሚዲያ አጠቃቀም በአዎንታዊ መንገድ በመጠቀምና ጥቅሙንና እያስከተለ ያለውን ጉዳት በማስገንዘብ ሁሉም አካል የሚጠበቅበትን ሀላፊነት እንዲወጡ ግንዛቤ ተፈጥሯል ።

ለሚ ኩራ ወረዳ 06 ፓርቲ ሚዲያ
ታህሳስ /2017

 በለሚ ኩራ ክ/ከተማ ወረዳ 06 አስተዳደር መደበኛ የመንግስት እና የፓርቲ ስራዎች አፈፃፀም ከአጠቃላይ አመራር ጋር ተገመገመ ።የለሚ ኩራ ክ/ከተማ ወረዳ 06 ዋና ስራ አስፈፃሚ ሲ/ር ግሩም...
25/12/2024



በለሚ ኩራ ክ/ከተማ ወረዳ 06 አስተዳደር መደበኛ የመንግስት እና የፓርቲ ስራዎች አፈፃፀም ከአጠቃላይ አመራር ጋር ተገመገመ ።

የለሚ ኩራ ክ/ከተማ ወረዳ 06 ዋና ስራ አስፈፃሚ ሲ/ር ግሩም ንጉሴ እና የለሚ ኩራ ክ/ከተማ ወረዳ 06 ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሙሉቀን ቸኮል የስራ አፈፃፀም ግምገማውን የመሩት ሲሆን የወረዳ አጠቃላይ አመራር ተገኝተዋል ።

በአፈፃፀም ግምገማው የፀጥታ ስራ፣ስራ እድል ፈጠራ፣ የሌማት ትሩፋት፣ የማዕድ ማጋራት እና መደበኛ የፓርቲ ስራዎች በውይይት በስፋት ተገምግመዋል ።

ለሚ ኩራ ወረዳ 06 ፓርቲ ሚዲያ
ታህሳስ 16/2017

 #ማስታወቂያ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የለሚ ኩራ ክ/ከተማ የመሬት ይዞታ ምዝገባ እና መረጃ ጽ/ቤት በወረዳ 06 ከታህሳስ 10/2017ዓ.ም ጀምሮ እስከ ግንቦት15/2017ዓ.ም ድረስ ...
25/12/2024

#ማስታወቂያ


በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የለሚ ኩራ ክ/ከተማ የመሬት ይዞታ ምዝገባ እና መረጃ ጽ/ቤት በወረዳ 06 ከታህሳስ 10/2017ዓ.ም ጀምሮ እስከ ግንቦት15/2017ዓ.ም ድረስ የመሬት ይዞታ ማረጋገጥ ስራ ለማከናወን በከተማ አስተዳደሩ አውጇል።

በመሆኑም በቀጣይ በሚወጣው የይዞታ ማረጋገጫ የሰፈር ፕሮግራም መሰረት ባለይዞታዎች በወረዳ በመገኘት በተዘጋጀ የማመልከቻ ቅፅ መሰረት ሞልታለችሁ የይዞታ ይረጋገጥልኝ ከ21/04/2017 ጀምሮ ጥያቄ ማቅረብ የምትችሉ መሆኑን እናሳስባለን ።

ለሚ ኩራ ወረዳ 06 ፓርቲ ሚዲያ
ታህሳስ 16/2017

 በለሚ ኩራ ክ/ከተማ ወረዳ 06 አስተዳደር በወረዳ አስተዳደሩ ግቢ ሲለማ የነበረ የሽንኩርት ምርት ወቅቱ ደርሶ ለሽያጭ እየቀረበ ነው።ዝቅተኛ የኑሮ ሁኔታ ላይ ለሚገኙ የወረዳው ነዋሪዎች የወ...
24/12/2024



በለሚ ኩራ ክ/ከተማ ወረዳ 06 አስተዳደር በወረዳ አስተዳደሩ ግቢ ሲለማ የነበረ የሽንኩርት ምርት ወቅቱ ደርሶ ለሽያጭ እየቀረበ ነው።

ዝቅተኛ የኑሮ ሁኔታ ላይ ለሚገኙ የወረዳው ነዋሪዎች የወረዳው አስተዳደር እና የከተማ ግብርና ፅ/ቤት የቦታ፣የዘር፣የውሀና መሰል ግብአቶችን በሟሟላት ለመስራት ፍላጎት ያላቸውን በመለየት የከተማ ግብርናንና የሌማት ትሩፋት ስራዎችን ለምግብ ዋስትና መረጋገጥ እና የኑሮ ውድነትን በማረጋጋት ጉልህ ሚና እንዳላቸው ግንዛቤ በመፍጠር በበጋም ሆነ በክረምት ከአመት እስከ አመት እንዲሰራ እየተደረገ እንዳለ በዛሬው እለት ፅ/ቤታችን በአስተዳደሩ ግቢ ባደረገው ቅኝት ተመልክቷል።

የሚሸምት ብቻ ሳይሆን የሚያመርት ዜጋ እንዲፈጠር የግንዛቤ ፈጠራ በ24ቱ ብሎኮች እየተሰራ እንዳለና ሞዴል የሆነና ስታንዳርድ ባስጠበቀ መልኩ እንዲተገበር የሚመለከታቸው አካላት ተቀናጅተው እየሰሩ እንዳለ ተመልክተናል።

ለሚ ኩራ ክ/ከተማ ወረዳ 06 ፓርቲ ሚዲያ
ታህሳስ 15/2017

ለበለጠ የመረጃ ተደራሽነት
👉https://t.me/LkW6communication👉https://www.instagram.com/lemikurawereda6communication
👉https://x.com/wereda66394/status/1868980154686755115?t=j0kbo-iQZxtdVzHFyfBOGQ&s=08
👉https://youtube.com/watch?v=At7crYR81kA&si=9VK-HBV5kL6qvWgK
👉https://vm.tiktok.com/ZMkFToWTG/

Address

Addis Ababa

Telephone

+251913661757

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Lemi kura wereda 06 proseperity page posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Lemi kura wereda 06 proseperity page:

Videos

Share