20/07/2026
አስደሳች ዜና👉 ህክምና
ሐምሌ 13/2018
ጅማ ዩኒቨርሲቲ
**************
ለጅማና አካባቢዋ ነዋሪዎች በሙሉ
የጅማ ዩኒቨርሲቲ የዓይን ህክምና ትምህርት ክፍል ODA Research and Development Association ከተባለዉ ግብረሰናይ ድርጅት ጋር በመተባበር ከሐምሌ 27 እስከ ነሐሴ 2፣ 2018 በጅማ ዩኒቨርሲቲ የህክምና ማዕከል ነፃ የዓይን ሞራ ቀዶ ህክምና ዘመቻ ያደርጋል፡፡
ስለሆነም ካሁን በፊት በምርመራ የተረጋገጠ የዓይን ሞራ ችግር ያለባችሁና ቀዶ ህክምና በመጠባበቅ ላይ የምትገኙ ሰዎች ቀደም ብላችሁ ወደ ጅማ ዩኒቨርሲቲ የህክምና ማዕከል የዓይን ህክምና ክፍል በመቅረብ እንድትመዘገቡና የዕድሉ ተጠቃሚ እንድትሆኑ ጥሪ እናደርጋለን፡፡
በማህበረሰብ ውስጥ ነን !