Gamo Media Center GMC

Gamo Media Center GMC Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Gamo Media Center GMC, Media/News Company, Addis Ababa.

የደቡቧ ኮከብ ብርብር ማርያም= የኦሪትና የሀዲስ ኪዳን ማህተም~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~የደቡቧ የአጥቢያ ኮከብ በመባል የምትታወቀው ብርብር ደብረ ማርያም ገዳም የምትገኘው በጋሞ ዞ...
30/01/2025

የደቡቧ ኮከብ ብርብር ማርያም= የኦሪትና የሀዲስ ኪዳን ማህተም
~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~

የደቡቧ የአጥቢያ ኮከብ በመባል የምትታወቀው ብርብር ደብረ ማርያም ገዳም የምትገኘው በጋሞ ዞን በምዕራብ ዓባያ ወረዳ ቦላ ሔራ ቀበሌ ልዩ ስሙ ደጋ ብርብር እየተባለ በሚጠራው ከፍተኛ ቦታ ላይ ነው፡፡

ደብረ ማርያም ብርብር ገዳም ቀደም ሲል በኦሪት ቤተ መቅደስ የተተከለችው ከጌታችንና መድሃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ቅድመ ልደት 400 ዓመት አካባቢ ነበር።

በሀገራችን ኢትዮጵያ መሥዋዕተ ኦሪት ከሚሰዋባቸው ትምህርተ ብሉይ ከሚሰጥባቸው አክሱም ጽዮን፣ ተድባብ ማርያም፣ መርጡለ ማርያምና ጣና ቂርቆስ አብያተ መቃድስ ጋር በኦሪቱ ሥርዓትና በምኩራብ በአይሁድ ደንብ ትተዳደር ነበር።

በዘመነ ሐዲስ በአምስተኛው መቶ ክፍለ ዘመን አጋማሽ ላይ ደግሞ የቤተ መቅደስዋን የጥንት ታሪክና ዝና የሚያውቁት አጼ ገብረ መስቀል ብርብር በተባለችው ቤተ መቅደስ ሥርዓት ሐዲስ ዘመንን የሚመለከት ታቦት ገብቶ ሊወደስባትና ሊቀደስባት እንደሚገባ አስበው በታቦተ ማርያም ስም ቅዱስ ያሬድ እና ጻድቁ አቡነ አረጋዊን ታቦተ ማርያምን አስይዘው በአያሌ ሠራዊት ታጅበው ከአክሱም ጽዮን በብዙ ጉዞና ድካም ወደ ቦታው ደረሱ።

ግንቦት 21 ቀን ጻድቁ አቡነ አረጋዊ ቤተ መቅደሱን በሜሮን አክብረው ታቦተ ማርያምን አስገብተው ቅዳሴ ቤቷን አከበሩ።

በዚህ መሠረት አገልግሎቷን ከኦሪት እስከ ሐዲስ ኪዳን ስትቀጥል የደቡብ ኢትዮጵያ የሃይማኖት ማዕከል
በመባል የምትገለጸው ጥንታዊቷ ደብረ ማርያም ብርብር ገዳም በየዘመኑ የቤተክርስቲያናችን ላይ የሚነሱ አጽራረ አብያተ _ ክርስቲያናት ታሪኳን ለማጥፋት ቢጥሩም በተለያዩ ጊዜያት የተለያዩ ድንቅ ተዓምራትን በማድረግ ለዚህ ትውልድ ደርሳለች።

አናኒያንና አዛሪያን የሚባሉ ሊቃነ ካህናት ታቦተ ጽላቱን ከኢየሩሳሌም ቀይ ባህርን አሻግረው ከአክሱም ታቦተ ፅዮን ጋር እንዳመጧት ይነገራል፡፡
ብርብር ማርያም በምትባለው የታሪክ የእውነት የመመረጥ እና የበረከት ዶሴ ውስጥ በምኩራብ ስርዓት በዘመነ ኦሪት ከነበሩት ከሊቃ ካህኑ ሳዶቅ ልጅ ካህኑ አዛርያስ እስከ ጉባኤ ኒቂያ አዘጋጅ ከሆነው የንግስት እሌኒ ልጅ ንጉስ ቆስጢንጢኖስ ድረስ በድምቀት ጎልተው ይነበባሉ።

በኢትዮጽያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ታሪክ የመጀመርያው ሊቀጻጳስ ከሆኑት ከአቡነ ከሳቴ ብርሃን (ፍሬምናጦስ ) እስከ ከሳቱ ቅዱሳን አካል ከሆኑት አቡነ አረጋዊ ድረስ በእዚህች ገዳም በረከት አፈስው ሱባኤ ይዘው ፀሎትና ቡራኪያቸውን አስቀምጠው ለትውልድ አልፈዋል።

የዜማው ሊቅ ስውሩ አባታችን ቅዱስ ያሬድ በመላእክት ጣዑመ ዜማ በሰማያውያን ለዛ በእዚህች ገዳም የምስጋና መሰዋት ዘርግቶ አልፎባታል።
በእዚህች ገዳምን ፃዲቁ አባታችን አቡነተክለሐይማኖት መንበረ አድርገዋት የወንጌል ዘርን በደቡብ ኢትዮጽያ ውስጥ ዘርተዋል።

ከኢዛና ሳይዛና እስከ አፄ ልብነድንግል፤ከአፄ ገብረመስቀል እስከ አፄ ዘርያዕቆብ ፤ ከአፄ ምኒልክ እስከ ጃንሆዬ ድረስ እጅ መንሻ እና መባ ለደቡቧ ኮከብ ለሆነችው ለብርብር ማርያም ሰጥተዋታል በረከት አፍሰውባታል።
በሀገር ላይ መከራ እና ወረራ ተከስቶ ጠላቶች በተነሱበት ጊዜ ከታቦተ ጽዮን እስከ ግማደ መስቀል በእዚህች ገዳም ሰንብተው ህዝቡን ባርከው ምድሯን ቀድሰው አልፈዋል።

እንግዲህ የእዚህች ገዳም ስም የደቡቧ ኮከብ ርዕሰ አድባራት ወገዳማት ሰማያዊት ጽዮን ብርብር ማርያም ትባላለች።

በህገ ኦሪት ከክርስቶስ ልደት 800 ዓመት በፊት በደብተረ ደንኳን በሊቀ ካህኑ ሳዶቅ ልጅ ካህኑ አዛርያስ ህገ እግዚአብሔር ተዘርግቶባታል።
በ1440 ዓ.ም አፄ ዘርዓ-ያዕቆብ ከትግራይ፣በ530 ዓ.ም አፄ ልብነ-ድንግል እንዲሁም በ1961 ዓ.ም ግርማዊ ቀዳማዊ አፄ ኃይለሥላሴ ወደ ቤተ-ክርስቲያኗ በመምጣት መሳለማቸውና ድጋፍ እንዲሆን የሰጧቸው የተለያዩ ንዋዬ ቅድሳትን በገዳሟ ይገኛሉ።

የብርብር _ ማርያም ገዳም ከጋሞ ዞን ርዕሰ ከተማ አርባምንጭ 67 ኪ.ሜ ርቀት እንዲሁም ከምዕራብ አባያ ወረዳ ከተማ ብርብር 82 ኪ.ሜ ርቀት ላይ ትገኛለች፡፡
ከተለያዩ የሀገሪቱ አከባቢዎች የሚጡ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት ተከታይ ምዕመናን አዘውትረው ፀሎት የሚያደርሱበት ስፍራ ነው፡፡

ጥንታዊና ታሪካዊ የሆኑ በርካታ ንዋየ ቅድሳትና መንፈሳዊ ቅርሶች ያቀፈች ገዳም ናት።
በዚህች ገዳም በርካታ ሀገርንና ህዝብን ሊጠቅሙ የሚችሉ የባህልና የቅርስ ማስረጃዎች ይገኛሉ።
ይህንንም ከግምት በማስገባት የኢፌድሪ ቅርስ ጥናትና ጥበቃ ባለስልጣን በሀገር ቅርስነት መዝግቦ በተለያዩ ጊዜያቶች እየተንከባከባትም ይገኛል።

የገዳሟ የቅርስ ይዘትን ስንመለከት ፦ በርካታ የብራና መፃህፍት፣ ከነገሥታት የተበረከቱ ጥንታዊ መፅሐፍት ፣ የቅዳሴ መስቀሎችና ሌሎች ቅርሶች ይገኛሉ።
የዚህችን ገዳም ታሪካዊነት ከሚያሳዩ የቁም ማስረጃዎች ዋና ዋናዎቹ ገዳሟ በአካባቢው የጋሞ ቤት አሰራር መሠረት የተሰራ ሲሆን የህንጻው ባህላዊ የቤት አሰራርም ጥበብ አሁን ላይ ይዘቱን እንደጠበቀ ይገኛል፡፡

የብርብር ማርያም ገዳም በአሁኑ ወቅት በጥሩ ሁኔታ ላይ ብትሆንም ቅርሶቹ የሚገኙበት ሁኔታ ካላት ውድ ዘመን ተሻጋሪ ሀብት አንጻር ለአደጋ የተጋለጠ በመሆኑ ከትውልድ ወደ ትውልድ እንዲተላለፍ ዘመናዊ ቤተ-መዘክር ሊገነባለት ይገባል።
አክሱም ጽዮንን ተሳልመው ይሆናል፤ጣና ቂርቆስን ረግጠው ሊሆን ይችላል፤ከተድባባ እና መርጦለማርያምንም በረከት ቢያፍሱም መልካም ነው።

ነገር ግን ብርብር ማርያም የምትባል አንድ ደቡቧዊር የህገ ኦሪትና ህገ ወንጌል ግምጃ ቤት በጋሞዎች መንደር አለች።

እሷ ትቀራችዋለች። ይሳለሟት፤ይርገጧት። በረከትና ቃልኪዷኗ ነፍስን አንጽቶ ስጋን የሚያከብር ነው።

ጥንታዊቷ የብርብሯ ማርያም እንዲህ ደምቃ ከብራለች***የደቡቧ ኮከብ ፣ ህገ ኦሪት እና ህገወንጌል የተፈጸመባት የሁለት ኪዳኖች ማዕከል፣ የቅዱሳን አባቶች መካን የሆነችው የደቡቧ ደማቅ ገዳም ...
29/01/2025

ጥንታዊቷ የብርብሯ ማርያም እንዲህ ደምቃ ከብራለች
***

የደቡቧ ኮከብ ፣ ህገ ኦሪት እና ህገወንጌል የተፈጸመባት የሁለት ኪዳኖች ማዕከል፣ የቅዱሳን አባቶች መካን የሆነችው

የደቡቧ ደማቅ ገዳም የሆነችው የታሪክ እና የእውነት ማማ....የብርብሯ ማርያም ዛሬ እንዲህ ደምቃ በዓለ አስተርዮን አክብራ ውላለች።

እግዚአብሔር ይመስገን !!!

የአስትርዮ በዓል በጨንቻ ከተማ በድምቀት  ተከብሮ ዉሏል
29/01/2025

የአስትርዮ በዓል በጨንቻ ከተማ በድምቀት ተከብሮ ዉሏል

በዓለ አስተርዮ በጨንቻ ይመኔ ቅድስት ድንግል ማርያም ገዳም በድምቀት ተከበረ አርባ ምንጭ (ጋሞ ቴቪ) ጥር 21 / 2017 ዓ.ም. በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን በጋሞ ዞን ጨን...
29/01/2025

በዓለ አስተርዮ በጨንቻ ይመኔ ቅድስት ድንግል ማርያም ገዳም በድምቀት ተከበረ

አርባ ምንጭ (ጋሞ ቴቪ) ጥር 21 / 2017 ዓ.ም.

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን በጋሞ ዞን ጨንቻ ከተማ በይመኔ ቅድስት ድንግል ማርያም ገዳም ዓመታዊው የአስተርዮ (መገለጥ) ማርያም በዓል ዛሬ በደማቅ ሀይማኖታዊ ስነስርዓት ተከብሯል።

በክብረ በዓሉ ላይ ጋሞ ዞንን ጨምሮ ከተለያዩ አከባቢዎች የመጡ የኦርቶዶክስ ክርስትና እና ሌሎችም ሀይማኖቶች ተከታዮች ታድመዋል።

እንዲሁም የሶስት ወረዳዎች ቤተክህነት ሥራ አስኪያጅ እና የኃይማኖት ፎረም ሰብሳቢ ሊቀብርሃናት ዳዊት መርዕድ እና የጨንቻ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ደመላስ ንጉሴ ተገኝተዋል።

እነሆ የበዓሉን አከባበር በፎቶ።

በጋሞ ዞን ሠላምበር ከተማን በጋራ እናልማ~~~~~~~~~~~~የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳደር የተከበሩ  አቶ ጥላሁን ከበዴ ለሠላምበር ከተማ የመንገድ ዳር መብራት ዝርጋታ ፕሮጀክት የ...
29/01/2025

በጋሞ ዞን ሠላምበር ከተማን በጋራ እናልማ
~~~~~~~~~~~~
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳደር የተከበሩ አቶ ጥላሁን ከበዴ ለሠላምበር ከተማ የመንገድ ዳር መብራት ዝርጋታ ፕሮጀክት የመጀመሪያ ዙር 15,000 ብር ገቢ አድርገዋል 🙏🙏🙏🙏🙏

የተከበሩ አቶ ጥላሁን ከበደ ለሠላምበር ከተማ መንገድ ዳር ዝርጋታ ፕሮጀክት ላበረከቱት አስተዋጽዖ በልማት ወዳዱ ሕዝባችን ስም ሠላምበር ከተማ አስተዳደር መንግስት አመስግነዋል።

!!

#እርስዎስ??

🙏በጋሞ ዞን ሠላምበር ከተማ የመንገድ ዳር መብራት ዝርጋታ ፕሮጀክትን ይደግፉ!!


1000641559548

ከ3 ሺህ ዓመት በላይ ባስቆጠረችውና የኦርት መስዋዕት ከተሰዋባቸዉ ጥቂት ከሀገራችን ክፍሎች መካከል የአባ ባህርይ ዘብሔሬ ጋሞዋ የብርብር ማርያም ገዳም  የአስትርዮ በዓል በድምቀት  እየተከበ...
29/01/2025

ከ3 ሺህ ዓመት በላይ ባስቆጠረችውና የኦርት መስዋዕት ከተሰዋባቸዉ ጥቂት ከሀገራችን ክፍሎች መካከል የአባ ባህርይ ዘብሔሬ ጋሞዋ የብርብር ማርያም ገዳም የአስትርዮ በዓል በድምቀት እየተከበረ ይገኛል።

የእምነቱ ተከታዮች ፣ የሀገር ዉስጥ እና የዉጭ ሀገራት ጎብኝዎች በበዓሉ ታድመዋል።

😳😳😳 #በጅማ ከተማ ለልማት ተነሺዎች ነዋሪዎች የተሰሩ መኖሪያ ቤቶች‼️ፎቶ፤ ከኦሮሚያ ፕሬዚዳንት ጽሕፈት ቤት
28/01/2025

😳😳😳

#በጅማ ከተማ ለልማት ተነሺዎች
ነዋሪዎች የተሰሩ መኖሪያ ቤቶች‼️

ፎቶ፤ ከኦሮሚያ ፕሬዚዳንት
ጽሕፈት ቤት

 ጥንታዊቷ ከተማ ጨንቻ ነገ ትደምቃለች የጌታችን እናት የእመቤታችን ድንግል ማርያም በዓለ አስተርዕዮ በድምቀት ይከበራል። እንደ ከዚህ ቀደሙ ሁሉ ከተማው ይባረካል❤ ምዕመኑ በዝማሬ ያመሰግናል...
28/01/2025



ጥንታዊቷ ከተማ ጨንቻ ነገ ትደምቃለች የጌታችን እናት የእመቤታችን ድንግል ማርያም በዓለ አስተርዕዮ በድምቀት ይከበራል።

እንደ ከዚህ ቀደሙ ሁሉ ከተማው ይባረካል❤ ምዕመኑ በዝማሬ ያመሰግናል 🙏 ከተማው በህዝበ ክርስትያኑ ማዕበል ይጥለቀለቃል❤

ሰላም ያድርሰን🙏❤

በጋሞ ዞን ምዕራብ ዓባያ ወረዳ በነገው ዕለት ጥር 21/2017 ዓ.ም  የሚከበረውን የብርብር ማሪያም ገዳም ዓመታዊ ክብረ በዓል ቅድመ ዝግጅት በማድረግ ከተለያዩ የሀገሪቱ አከባቢዎች የሚመጡ ...
28/01/2025

በጋሞ ዞን ምዕራብ ዓባያ ወረዳ በነገው ዕለት ጥር 21/2017 ዓ.ም የሚከበረውን የብርብር ማሪያም ገዳም ዓመታዊ ክብረ በዓል ቅድመ ዝግጅት በማድረግ ከተለያዩ የሀገሪቱ አከባቢዎች የሚመጡ እንግዶችን ለመቀበል በመጠባበቅ ላይ ይገኛሉ ።

ጥር 20/2017ዓ.ም
(ምዕራብ ዓባያ ወረዳ መ.ኮሚዩኒኬሽን )

በህገ ወጥ መንገድ በግለሰቦች ቤትና ድርጅቶች የተከማቸ ቤንዚንና ናፍጣ በቁጥጥር ሥር መዋሉን የጋሞ ዞን ፖሊስ መምሪያ አስታወቀአርባምንጭ ፣ጥር 21/2017 ዓ.ም(ጋሞ ዞን መ/ኮሚዩኒኬሽን)፦...
28/01/2025

በህገ ወጥ መንገድ በግለሰቦች ቤትና ድርጅቶች የተከማቸ ቤንዚንና ናፍጣ በቁጥጥር ሥር መዋሉን የጋሞ ዞን ፖሊስ መምሪያ አስታወቀ

አርባምንጭ ፣ጥር 21/2017 ዓ.ም(ጋሞ ዞን መ/ኮሚዩኒኬሽን)፦ የጋሞ ዞን ፖሊስ አዛዥ ኢንስፔክተር ደበበ ኦንቶ እንደገለፁት ነዳጁ በቁጥጥር ሥር ሊዉል የቻለዉ ከላንቴ ቀበሌ አንስቶ እስከ ምዕራብ አባያ ወረዳ ሀመሳ ወሰን ባለዉ የዞኑ ፀጥታ ግብረ ሀይል ከምዕራብ አባያ ወረዳ ፖሊስ ጋር ባደረገዉ የተቀናጀ ልዩ ኦፕሬሽን ሥራ መሆኑን ጠቅሰዋል።

በተካሄደው ኦፕሬሽንም 24 በርሜል ቤንዚን፣ 11 በርሜል ናፍጣ ፣ 4 ባለ 20 ሊትር ጀርካን ቤንዚን፣ 18 ባለ 20 ሊትር ጀርካን ናፍታ ፣158 ሊትር በሀይላንድ የተቀዳ ቤንዚን በግለሰቦች እጅ ተከማችቶና ሊዘዋወር የተዘጋጀ ከፉራ ፣ ከቆላ ባራናና ከዋጅፎ አካባቢዎች መያዙን ተናግረዋል።

በቀጣይም ይህን አይነት ህገ ወጥና በአጭር ለመክበር የሚደረግን ህገ ወጥ የንግድ ዝውውርን ለመከላከል በየአከባቢው የሚገኘው የህብረተሰብ ክፍሎች ከመንግስትና ከፖሊስ ጎን ሆኖ ጥቆማ እንዲሰጥ የተለመደ ትብብራቸውን እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል ።

መረጃው የጋሞ ዞን ፖሊስ መምሪያ ነው

Local market in Gamo,South Ethiopia 🇪🇹    መልካም ቀንዳዉሮ ባና ዳዉሮ ባና . . .:::Ten unknown Facts About  1. The first film ever m...
27/01/2025

Local market in Gamo,South Ethiopia 🇪🇹






መልካም ቀን
ዳዉሮ ባና ዳዉሮ ባና . . .
:
:
:

Ten unknown Facts About

1. The first film ever made was "Roundhay Garden Scene" in 1888, directed by French inventor Louis Le Prince.

2. The first Hollywood film was "The Squaw Man" in 1911, directed by Oscar Apfel and Cecil B. DeMille.

3. The first 3D film was "The Power of Love" in 1922, directed by Nat G. Deverich and Harry K. Fairall.

4. The first film with sound was "The Jazz Singer" in 1927, directed by Alan Crosland.

5. The longest film ever made was "Ambian" in 2016, directed by Anders Weberg, with a runtime of 720 hours.

6. The highest-grossing film of all time is "Avengers: Endgame" in 2019, directed by Anthony and Joe Russo.

7. The most Academy Awards won by a single film is 11, achieved by "Ben-Hur" in 1959, "Titanic" in 1997, and "The Lord of the Rings: The Return of the King" in 2003.

8. The first film to feature a computer-generated image (CGI) was "Westworld" in 1973, directed by Michael Crichton.

9. The first film to use motion capture technology was "The Lord of the Rings: The Fellowship of the Ring" in 2001, directed by Peter Jackson.

10. The highest-paid actor of all time is Keanu Reeves, with a salary of $250 million for "The Matrix" trilogy.

Where nature's charm and comfort blend seamlessly.
27/01/2025

Where nature's charm and comfort blend seamlessly.

ልብ በሉበወላይታ ዞን መቀመጫ ያደረጉ Excellency Center እና Wolaita Times ሚዲያ የፖለቲካ ገበያ ለመፍጠር ሽረ ጉድ ስሉ እያየን ነው።የጌዴኦ ምሁራን በሀሳብ የሚያምኑ እንጂ...
26/01/2025

ልብ በሉ

በወላይታ ዞን መቀመጫ ያደረጉ Excellency Center እና Wolaita Times ሚዲያ የፖለቲካ ገበያ ለመፍጠር ሽረ ጉድ ስሉ እያየን ነው።

የጌዴኦ ምሁራን በሀሳብ የሚያምኑ እንጂ በፌክ ሚዲያ ሀሳባቸውን የሚያባክኑ አይደለም

እንደ ጅራፍ ራሱ ፕሮፓጋንዳ አፈልቆ ራሱ መልሶ መጮህ ትልቅ ውድቀት ነው። መቀመጫ ወላይታ አደርገህ በራስህ አይን ስር በርካታ ብልሽቶች እያሉ ሳይተቹ የሌለውን እንዳለው አደርገው ኩንቱ ሩጫ መሮጥ መልሶ ያስታዝባል።

የጌዴኦ ምሁራን በሀሳብ የሚያምኑ ፤በጣም የበሰሉና ፤ጤናማ ህብረት ያሉ ናቸው። ስለዚህ የራስህን የፖሎቲካ ጥቅም ለማሳካት ፤በስም ጌዴኦ የፖሎቲካ ገበያ መፍጠር አይቻልም ።

ጌዴኦ በሁሉም መስክ በሚባልበት ደረጃ የጉብኝት መስክ ሆናለች ። ደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የሚመሩትን ልጆች በጋሞና በጌዴኦ በማነጣጠር የሰራ ፖሎቲካ በመዘርጋት የምታደርጉትን እንቅሰቃሴ የማታቆሙ ከሆነ ማን ይህ ተግባር የሚትመሩ እንድሆነ በስም ዝርዝር እናወጣለን ።

25/01/2025

ሁላችንም አጥፍተናል። ደም ተቃብተናል። ደም መፋሰስ ይበቃናል: የታየኝ ነገር አለ እያለ ነው። Divine Interventioኗ ተተካች ማለት ነው?

25/01/2025
KEHAZ Agro Services PLC. 🌴🌱🎋🍃ከሀዝ የግብርና ድጋፍ አገልግሎት ኃ.የተ.የግ.ማ💼 ምርትና አገልግሎቶች 🍀የግብዓት አቅርቦት፤ (ማዳበሪያ፣ ምርጥ ዘር፣ ፀረ-ተባይና ፀረ-ነፍሳት፣...
25/01/2025

KEHAZ Agro Services PLC. 🌴🌱🎋🍃
ከሀዝ የግብርና ድጋፍ አገልግሎት ኃ.የተ.የግ.ማ

💼 ምርትና አገልግሎቶች

🍀የግብዓት አቅርቦት፤ (ማዳበሪያ፣ ምርጥ ዘር፣ ፀረ-ተባይና ፀረ-ነፍሳት፣ የእርሻና የመስኖ መሣሪያዎችን፣ እና ሌሎችም)።

🍀 የአፈር ለምነት ምርመራ (Soil-Fertility-Test)፤ በዘመናዊ መሣሪያዎች በመታገዝና በብቁ ባለሙያዎች የአፈር ለምነት ምርመራና የተስማሚነት ምዘና አገልግሎቶችን እንሰጣለን፤ የእርሻ አፈር ለምነት ዝርዝር መረጃና የባለሙያ ምክረ-ሀሳቦችን ደንበኞች በሚገባቸው ቋንቋ ሪፖርት እናቀርባለን)።

🍀ድጋፍና ማማከር፤ የረዥም ጊዜ ልምድና ብቃት ባላቸው የግብርና ባለሙያዎች :—
🌱በእርሻ መሬት አያያዝ፣
🌱በሰብል አስተዳደርና ምርታማነት፣
🌱በመስኖ አሠራሮች፣
🌱በተባይ ቁጥጥር እንዲሁም በኬሚካሎች አጠቃቀምና አተገባበር፣
🌱በአፈር ለምነት አጠባበቅ፣
🌱በምርት አሰባሰብና አያያዝ፣
እንዲሁም በሌሎችም የግብርና ተግባራት ላይ በዘላቂነት እናማክራለን። በእርሻ ቦታዎች በመገኘትም የድጋፍና የሥራ አመራር አገልግሎቶችን እንሰጣለን)።

💥ይጎብኙን! ከፍተኛ ልምድና ብቃት ካላቸው የግብርና ባለሙያዎች ጋር ስለ እርሻዎ ይወያዩ፤ ዘመናዊ መፍትሔዎችን ያግኙ!!

💥 አድራሻችን፤ አርባምንጭ - ሲቀላ፣ በወጋገን ባንክ ወደ ውስጥ በሚወስደው መንገድ 200ሜትር ገባ ብሎ፣ ወይም በመናኸሪያ መውጫ በኩል ወደ ውስጥ በሚወስደው መንገድ 200ሜትር ገባ ብሎ ሙሉጌታ ህንፃ ላይ ያገኙናል።

🌞 ለበለጠ መረጃ
👉ስልክ፤ 0985950190/0916873260
👉ኢሜይል፤ [email protected]

እንበርታ! እናምርት! ... ይትረፍረፍ!
Let's flourish together!! Let's make surplus!

በእኛው መፍትሔ!
Our Own Solutions!!
-------------------------------------

KEHAZ Agro Services PLC 🍀🌿

💼Product and services

👉 Supply of agricultural resources; (fertilizers, improved (Laboratory-developed) seeds, pesticides and insecticides, farm and irrigation equipment, and more).

👉 Support and consulting; (With long-term experienced and qualified agricultural experts - we consult on farmland management, crop management and productivity, irrigation systems, pest control and the use and application of agro chemicals, soil fertility care, harvest and logistics management, as well as other agricultural activities; we also provide support and management services by visiting farms).

👉 Soil fertility test. (With the help of modern tools, we provide soil fertility testing and conformity assessment services by qualified experts).

💥 Our address: Arbaminch - Sikella, you can find us at the Mulugeta building, 200 meters from the road leading from Wegagen Bank, or 200 meters across the road leading from the Car-Station exit.

🌞 For more information
phone 0985950190
email; [email protected]

🚶‍♂️Visit us; Discuss your farm works with highly experienced and qualified agricultural experts!!

Let's flourish together!!
Our Own Solutions!!

#ግብርናችን
#ደቡብኢትዮጵያ
#አርባምንጭ






#ከሀዝ

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Gamo Media Center GMC posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Videos

Share