Gamo Media Center GMC

Gamo Media Center GMC Peace for the world
(1)

ክቡር አቶ ጥላሁን ከበደ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ልማት አርበኛ~~~~~~~~~~ክቡር አቶ ጥላሁን ከበደ፣ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር፣ ኢትዮጵያ ውስጥ ከኦሮሚያ እና አማራ ክልሎች...
18/08/2025

ክቡር አቶ ጥላሁን ከበደ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ልማት አርበኛ
~~~~~~~~~~
ክቡር አቶ ጥላሁን ከበደ፣ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር፣ ኢትዮጵያ ውስጥ ከኦሮሚያ እና አማራ ክልሎች በመቀጠል በህዝብ ብዛት ሦስተኛ የሆነውን ይህን አዲስ ክልል በብቃት እየመሩ ይገኛሉ። የአቶ ጥላሁን አመራር ክልሉን ወደተሻለ ልማትና ብልጽግና ለማሸጋገር ወሳኝ ሚና እየተጫወተ ነው።

* ልማታዊ አስተዋፅኦዎች

በአቶ ጥላሁን ከበደ በሳል መሪነት በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የህዝቡን ኑሮ ለማሻሻል የሚያስችሉ በርካታ የልማት ስራዎች ተከናውነዋል። በእርሻ፣ በጤና፣ በትምህርት እና በመሠረተ ልማት ዘርፎች ትኩረት በመስጠት፣ ክልሉን ከድህነት አዙሪት ለማውጣት እና የህዝቡን አቅም ለማሳደግ ጉልህ አስተዋፅዖ አበርክተዋል። በርካታ የገጠር መንገዶች ተገንብተዋል፣ አዳዲስ የጤና ተቋማት ተከፍተዋል፣ እና የትምህርት ተደራሽነት እንዲጨምር ሰፊ ስራዎች ተከናውነዋል። እነዚህ ሁሉ ጥረቶች የህዝቡን ተጠቃሚነት ከፍ ያደረጉ ሲሆን፣ ክልሉ በፍጥነት እያደገ እንዲሄድ መሠረት ጥለዋል።

* የፖለቲካ ብቃት እና አስተዳደር

አቶ ጥላሁን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን በመምራት ረገድ ያሳዩት የፖለቲካ ብቃትና አስተዋይነት የሚደነቅ ነው። ክልሉ በርካታ ብሔር ብሔረሰቦችን የያዘ በመሆኑ፣ የህዝቦችን ሰላምና አንድነት መጠበቅ ትልቅ ጥበብ የሚጠይቅ ፀጋ ነው። አቶ ጥላሁን የህዝቦችን እኩልነት በማረጋገጥ፣ የጋራ መግባባትን በማስፈን እና ሁሉንም አካላት ያሳተፈ የልማት እቅድ በመንደፍ፣ የክልሉን ሰላምና መረጋጋት ማስጠበቅ ችለዋል። ይህም ለክልሉ ቀጣይነት ያለው እድገትና ልማት ወሳኝ መሠረት ነው።

ክቡር አቶ ጥላሁን ከበደ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልን በልማት እና በፖለቲካዊ ብቃት በመምራት፣ ለክልሉ ህዝቦች ብሩህ ተስፋ እየፈነጠቁ ይገኛሉ። የእርሳቸው አመራር ለሌሎች ክልሎችም መልካም ተሞክሮ ሊሆን የሚችል ሲሆን፣ ለኢትዮጵያ አጠቃላይ እድገትም ትልቅ አስተዋፅዖ አለው።
Tilahun Kebede

18/08/2025

Abiy Ahmed Ali
Berhanu Zewdie Zeta

18/08/2025

የወንድማችን ደም ፈሶ መቅረት የለበትም!💔😭
በግፍ የተገደለው ልደቱ አየነው (አቢ) ጓደኞቼ እና የሚያውቁት ፍትህ ለወንድማችን በማለት ጠይቀዋል!

18/08/2025

❤❤

አርባምንጭ ከተማ እግርኳስ ክለብ አጥቂውን አሸናፊ ተገኝን ለተጨማሪ የውድድር ዓመት የሚያቆየውን ውል ለማደስ ከተጫዋቾቹ ጋር ከስምምነት ላይ ደርሷል ።Arba Minch City F.C
18/08/2025

አርባምንጭ ከተማ እግርኳስ ክለብ አጥቂውን አሸናፊ ተገኝን ለተጨማሪ የውድድር ዓመት የሚያቆየውን ውል ለማደስ ከተጫዋቾቹ ጋር ከስምምነት ላይ ደርሷል ።

Arba Minch City F.C

 ! በቡርጂ ዞን በሶያማ ዙሪያ ወረዳ ነደሌ ቀበሌ በሰላማዊ መንገድ በገዛ ማሳው ላይ በፅንፈኛ ኃይሎች በተገደለው አርሶ አደር ሞት ሐዘን ተሰምቶናል።ዛሬ ነሐሴ 12/2017 ዓ/ም በቡርጂ ዞን...
18/08/2025

!
በቡርጂ ዞን በሶያማ ዙሪያ ወረዳ ነደሌ ቀበሌ በሰላማዊ መንገድ በገዛ ማሳው ላይ በፅንፈኛ ኃይሎች በተገደለው አርሶ አደር ሞት ሐዘን ተሰምቶናል።

ዛሬ ነሐሴ 12/2017 ዓ/ም በቡርጂ ዞን በሶያማ ዙሪያ ወረዳ ነደሌ ቀበሌ በሰላማዊ መንገድ በገዛ ማሳው ላይ የነበረውን ሰላማዊ አርሶ አደር ከኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ጉጂ ዞን በኩል የመጡ የታጠቁ የጥፋት ኃይሎች በፈፀሙት አስነዋሪ እኩይ ተግባር ህይወቱ ባለፈው የነደሌ ቀበሌ ም/ሊቀመንበር አቶ በለጠ በዙ ሞት እንደ ቡርጂ ዞን መንግስት የተሰማን ሀዘን ጥልቅ ነው።

ሠላም ወዳዱና ታታሪው የቡርጂ ህዝብ በአዝመራ ወቅት ሀገር አማን ነው ብሎ እርሻዉን ሲያርስ የነበረን አርሶ አደር በራሱ ማሳ ላይ በየጊዜው እየመጡ መግደል እጅግ በጣም ጸያፊና አሳዛኝ ስለሆነ የቡርጂ መንግስት ይህንን እኩይ ተግባር አምርሮ ያወግዛል።

የቡርጂ ዞን መንግስት የህዝቡን ሠላምና ልማት አደናቃፊ የሆኑ የጥፋት ኃይሎችን ተከታትሎ እርምጃ ይወሰድ ዘንድ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመሆን አስፈላጊዉን ክትትል የሚያደርግ መሆኑን ይገልጻል።

የዞናችን ህዝብ ሰርቶ አዳሪ ሠላም ወዳድ ህዝብ በመሆኑ በህዝባችን ላይ የሚቃጡ የአጥፊዎች አፀያፊ ተግባር በዘላቂነት እንዲቆምና የሚመለከታቸውም አካላት ወንጀለኛውን ተከታትለው ለህግ እንዲያቀርቡ የዞኑ መንግስት ይጠይቃል።

የዞኑ መንግስትም በህዝባችን ላይ እየደረሰ ያለውን አስከፊ የጠላት ስራ እንዲቆም ከምንጊዜውም በላይ ትኩረት ሰጥቶ እንደሚሰራ ለተከበረው ህዝባችን እያሳሰብን ወቅቱ የአዝመራ ስለሆነ ሕዝባችን ከምንጊዜውም በላይ ከአጥፊዎች ሰለባ ራሱን እየጠበቀና ጥንቃቄ እያደረገ እርሻዉን እንዲዘራና የተለየ የጠላት እንቅስቃሴ ሲመለከት ቅድመ ጥቆማ እንዲሰጠን እናሳስባለን።

በመጨረሻም የቡርጂ ዞን መንግስት በንፁሁ አርሶ አደር መገደል የተሰማዉን ጥልቅ ሐዘን እየገለፀ ለወዳጅ ዘመዶቹ እና ለመላው የቡርጂ ሕዝብ መጽናናትን ይመኛል።

የቡርጂ ዞን አስተዳደር
ነሐሴ 12/2017 ዓ/ም
ቡርጂ-ሶያማ

እንደሚታወቀው አብዛኛው የኢትዮጵያ ህዝብ የሚኖረው በገጠር ሲሆን አኗኗሩ ግን  አስቸጋሪ የሚባል የተበታተነ ለልማትና ለመሰረተ ልማት ለንፅህና  በማይመች ነው፤  በመሆኑም   በቀጣይ  መላው ...
18/08/2025

እንደሚታወቀው አብዛኛው የኢትዮጵያ ህዝብ የሚኖረው በገጠር ሲሆን አኗኗሩ ግን አስቸጋሪ የሚባል የተበታተነ ለልማትና ለመሰረተ ልማት ለንፅህና በማይመች ነው፤ በመሆኑም በቀጣይ መላው የኢትዮጵያን የገጠር ህዝብ አኗኗር ሚያዘምኑ እነኚህን የመሳሰሉ በወጪ ቆጣቢ ማቴሪያሎች በጥናትና በጥራት የተሰሩ ሳምፕል የገጠር ኮሪዶር ፕሮጀክቶች በመሰራት ላይ የሚገኙ ሲሆን በእውነቱ እነዚህ ስራዎች በእጅጉ ሊበረታቱ በዘመቻና በቋሚነት በመላው ኢትዮጵያ በቅንነት ሊሰራበት የሚገባ ቅዱስ ሃሳብ ነው።

የገጠር ኮሪዶር ....የገጠሩ ህዝባችን እርሻውም በሜካናይዝድ ዘመናዊ መንገድ በጋራ በክላስተር ታርሶ የታረሰው ተሰብስቦ በጋራ ስቶርና ፕሮሰስ ተደርጎ የደላላ ሲሳይ ሳይሆን ትርፋማ ሚሆንበት ፤ መኖሪያው ከተበታተነ አከባቢ በአንድ መንደር መብራት ውሃ ወዘተ ተሟልቶለት ከዋና መንገድ ሳይርቅ የእርሻና የመኖሪያ መንደሩ በጋራ የሚዘምንበት ወሳኝ የሁላችንንም መረዳትና ጥረት ሚጠይቅ ፕሮጀክት ነው ።

ኢትዮጵያዊነት Ethiopiawinet

ከጌዴኦ ምድር ሠላምን እንሻማGedeo TV
18/08/2025

ከጌዴኦ ምድር
ሠላምን እንሻማ
Gedeo TV

ከመስከረም ጀምሮ ለሠራተኛው ተጨማሪ የደመወዝ ማሻሻያ ለማድረግ መንግሥት ወሰነ አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 12፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ከመስከረም 2018 ጀምሮ ለመንግሥት ሠራተኛው ተጨማሪ የደመወ...
18/08/2025

ከመስከረም ጀምሮ ለሠራተኛው ተጨማሪ የደመወዝ ማሻሻያ ለማድረግ መንግሥት ወሰነ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 12፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ከመስከረም 2018 ጀምሮ ለመንግሥት ሠራተኛው ተጨማሪ የደመወዝ ማሻሻያ ለማድረግ መንግሥት ወስኗል፡፡

የፌደራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ባወጣው መግለጫ፤ መንግሥት የዜጎችን የኑሮ ሁኔታ ለማሻሻል የሀገር ዐቅም የሚፈቅደውን ርምጃ እየወሰደ ነው ብሏል፡፡

በዚህም ለመንግሥት ሠራተኛው ተጨማሪ የደመወዝ ማሻሻያ ለማድረግ መንግሥት መወሰኑን አስታውቋል፡፡

በማሻሻያው ዝቅተኛው የመንግሥት ሠራተኛ ደመወዝ ከብር 4 ሺህ 760 ወደ ብር 6 ሺህ እንዲያድግ ይደረጋል ነው ያለው።

ከፍተኛው የመንግሥት ሠራተኛ ደመወዝ ከብር 21 ሺህ 492 ወደ ብር 39 ሺህ እንዲያድግ ይደረጋል ብሏል።

የዲግሪ ተመራቂ መነሻ ደመወዝ ከብር 6 ሺህ 940 ወደ ብር 11 ሺህ 500 የሚሻሻል መሆኑን ገልጿል።

ከሲቪል ሰርቪስ ውጭ በተለያዩ ዘርፎች የተሠማሩ የመንግሥት ሠራተኞች ደመወዝም ማሻሻያ እንደሚደረግበት አስታውቋል።

ይህ የደመወዝ ማስተካከያ ከ160 ቢሊዮን ብር በላይ ተጨማሪ በጀት ጠይቋል ያለው ኮሚሽኑ፤ ይሄም ለደመወዝ የሚወጣውን ጠቅላላ ዓመታዊ የመንግሥት ወጪ 56ዐ ቢሊዮን ብር ያደርሰዋል ብሏል።

የፌደራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽንን ሙሉ መግለጫ ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ፦https://www.fanamc.com/archives/299145

ከእንጦጦ አራት ኪሎ አዲስ አበባ!
17/08/2025

ከእንጦጦ አራት ኪሎ አዲስ አበባ!

17/08/2025

የሠላም ተምሳሌት ክልል
ደቡብ ኢትዮጵያ
Gamo ArbaMinch

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Gamo Media Center GMC posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share