ሮሃ ሚዲያ ROHA MEDIA

ሮሃ ሚዲያ ROHA MEDIA የፌስቡክ ገፃችንን ላይክ በማድረግ እለታዊ መረጃዎችን ይከታተሉ!

20/09/2025

"ፋኖ ዞን እና ወረዳ ተቆጠጠረ የሚሉትን ጥቃቅን ዜናዎችን መስማት ብቻ መቆም አለበት" ፋኖ አበበ ሙላት

በዛሬው እለት አፋህድ የአንድነት ጉባዔ ሊያዘጋጅ ነው!

መስከረም 10 ቀን 2018 ዓ.ም (ሮሃ ቴቪ)

የአማራ ፋኖ ህዝባዊ ድርጅት አፋኃድ መስከረም 11 እና 12 ቀን 2018 ዓ.ም ታላቅ የሆነ የአንድነት ጉባዔ ሊያዘጋጅ ነው። ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታ ለአንድነቱ እየሰራን ነው ያለው ፋኖ ኢንጂነር ኢያሱ አበራ የዚህ ታላቅ የአንድነት ጉባዔ ዋናው አላማ አንድነትን ማጠናከር መሆኑን ገልፆ የአማራ ህዝብ እና ሀገር የሚድኑት እኛ አንድ መሆን መተባበር ስንችል ነው በማለት ለሀገር ድህነት አንድነቱ ያለውን ጠቀሜታ ገልጿል።

ፋኖ ኢንጂነር ኢያሱ አክሎም መሬት ላይ ባለ ሀቅ እና እውነታን መሰረት በማድረግ ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ እና ለትግሉ ደጋፊዎች አሁን ያለውን ነባራዊ ሁኔታ በግልፅ ከማስረዳትም ባሻገር በአማራ ፋኖ በኩል ያሉትን ፖለቲካዊ እና ወታደራዊ እንቅስቃሴዎች ለማሳወቅ ጉባኤው እንደተዘጋቸ አሳውቋል።

በትግሉ ውስጥ የነበሩ ችግሮችንና ቅራኔዎችን የምናስወግድበት ብሎም ስለ አንድነት ሁላችንም በጋራ የምንዘምርበት አንድ አይነት የትግል መስመር ላይ እያለን ነገር ግን ለተለያየ አላማ እንደምንታገል አድርጎ ለተመልካች እንድንታይ ያደረገንን ልዩነት ሰባብረን በአንድነተት ለአንድነት የምንዘምርበት አብሮነታችንን የምናጠነክርበት ልዩ ጉባዔ ነው በማለት የገለፀው ደግሞ ፋኖ አበበ ሙላት ነው።

አክሎም ህዝባችን እና ዓለም አቀፉ ማሕበረሰብ የሚፈልገው በጋራ ቆመን በጋራ ታግለን አንድ ወጥ የሆነ አማራዊ ድርጅት መስርተን በአንድ መርህ እና አቋም ላይ ሆነን እንድንታገልለት እና በአገዛዙ የሚደርስበትን ጫና እንዲሁም በገፍ የሚፈሰው እንባውን እንድናብስለት ነው የሚፈልገው ብሏል።

ከዚህ ቀደም በተለያዩ መድረኮች አንድነታችንን ማጠናከር አለብን የሚል በርካታ ንግግሮች ሲደረጉ ቆይተዋል ያለ ሲሆን ይህንን ለየት የሚያደርገው ሁሉንም አይነት አስተሳሰብ እና አመለካከት በአንድ መድረክ ላይ ሀሳብና አስተያየት የሚሰጥበት ሲሆን ከሀሳብ በዘለለ ደግሞ ሁሉም ለተግባራዊነቱ የሚተባበሩበት መድረክ ነው በማለት ስለ ጉባዔው አስረድቷል።

ህዝባችን ፋኖ ዞን እና ወረዳ ተቆጠጠረ የሚሉትን ጥቃቅን ዜናዎችን ሳይሆን መስማት ያለበት የተወዛወዘውን ስርዓተ ቢስ አገዛዝ እስከወዲያኛው ገርስሶ ለሁላችንም መልካም የሆነውን ብስራት ነው መስማት ያለበት በማለት ከሮሃ ቴቪ ጋር ባደረጉት ቆይታ አሳውቀዋል።

ከመርሐ ግብሩ በኋላ በመድረኩ ላይ የተለያዩ ሀሳብ እና ንግግር ያደረጉት አካላት በአማራ ህዝብ ላይ የሚደርሰው ሰቆቃ ሀላፊነት ስላለበት ሁሉም ለተግባራዊነቱ ላይ መትጋት አለበት ብሏል።

በመጨረሻም ፋኖ አበበ ሙላት በመልእክቱ ከጥፋት ሁሉ ጥፋት የታሪክ ተወቃሽ መሆን ነው ያለ ሲሆን በእኛ አንድ አለመሆን ምክንያት በታሪክ ላይ ጥቁር ጠባሳ እንዳናሳርፍ እና የታሪክ ተወቃሽ እንዳንሆን ሁላችንም በጋራ ሆነን ሁሉም የሚመለከተው አካል በአንድነት ለአንዴ እና ለመጨረሻ ጊዜ ተባብረን ጨቋኙን ስርዓት መቅበር ያስፈልጋል በማለት ሀሳቡን ቋጭቷል።

በመርሐ ግብሩ ላይ ጥሪ የተደረገላቸው ትላልቅ ተቋማት አጋዥ ድርጅቶች የአፋህድ የውጪ ኮሚቴዎች የድርጅቱ ከፍተኛ አመራሮች እና ተጋባዥ ሚዲያዎች የሚገኙ ይሆናል።

ሙሉውን ቃለ ምልልስ ለመከታተል👇👇👇
https://youtu.be/jT4diXwwr7o?si=RkKRwaJODAQ9lMx5

የዩቱዩብ ቻናልን
https://www.youtube.com/channel/UCDXU7RuIQc0xRKJyP0ZTZaQ

- page 👇
https://www.facebook.com/rohamedia2022/?ref=pages_you_manage

Telegram Channel 👇
👉 https://t.me/rohatv1

#ሮሃ ቴቪ tiktok
https://www.tiktok.com/?_t=ZM-8yvAZcRGkoq&_r=1

የዓለም ባንክ እና አይኤምኤፍ ለኢትዮጵያ ከባድ ማስጠንቀቂያ ሰጡ! መስከረም 9 ቀን 2018 ዓ.ም (ሮሃ ቴቪ) አገዛዙ በተለያየ የሀገራችን ቦታዎች ስልጣኑን ለማስጠበቅ ከሚያስጨርሳቸው የደሀ ...
19/09/2025

የዓለም ባንክ እና አይኤምኤፍ ለኢትዮጵያ ከባድ ማስጠንቀቂያ ሰጡ!

መስከረም 9 ቀን 2018 ዓ.ም (ሮሃ ቴቪ)

አገዛዙ በተለያየ የሀገራችን ቦታዎች ስልጣኑን ለማስጠበቅ ከሚያስጨርሳቸው የደሀ ልጆች በተጨማሪ ከዓለም አቀፍ አበዳሪ ተቋማት እና ሀገራት ኢትዮጵያን አስይዞ ለከተማ ልማት በሚል ሰበብ የማይከፍለውን ገንዘብ እየተበደረ መሆኑ የአደባባይ ሀቅ ነው።

የዓለም ባንክ እና አይ ኤም ኤፍ በጋራ አዲስ ግምገማ በማድረግ በኢትዮጵያ ኢኮኖሚ እይታ ላይ ከባድ ማስጠንቀቂያ የሰጡ ሲሆን ሀገሪቱ ያሉባትን የውጭ ብድር የመመለስ አቅሟ "ዘላቂነት የለውም" በማለት መንግስት ቀድሞውንም በእዳ ጭንቀት ውስጥ መሆኑን አረጋግጧል።

በሁለቱም ተቋማት ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች የፀደቀው ዘገባው “የኢትዮጵያ ዕዳ የመክፈል አቅም ዘላቂነት የሌለው ነው ተብሎ የሚገመገመው በዋናነት ከወጪ ንግድ ጋር በተያያዙ የውጭ ዕዳ አመላካቾች ላይ በመጣስ እና በደካማ ዕዳ የመሸከም አቅም ላይ የተመሰረተ ነው” ብሏል።

በጋራ ትንታኔው መሰረት መንግስት በG20 የጋራ ማዕቀፍ በመጋቢት 2025 ከኦፊሴላዊው አበዳሪዎች ጋር በመርህ ደረጃ ስምምነት ላይ ደርሷል።በ2027/28 የአይኤምኤፍ መርሃ ግብር ሲያበቃ የዕዳ አያያዝን በተመለከተ የመግባቢያ ስምምነት በቅርቡ ይጠበቃል።

የዕዳ አገልግሎት ግዴታዎች ከወጪ ንግድ የሚገኘውን ገቢ እና የመንግስት ገቢን እየበለጡ በመሆናቸው ኢትዮጵያ ካልተሳኩ መልሶ ማዋቀር እና ማሻሻያዎች ጫናዎች እንደሚኖሩባት ሪፖርቱ አስጠንቅቋል።

ከ2021 ጀምሮ የኢትዮጵያ ህዝባዊ እና በህዝባዊ ዋስትና ያለው ብድር ከጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት (GDP) ድርሻ ቢቀንስም፣ ይህ የሆነው በአብዛኛው በስም እድገት እና ከዋና አበዳሪዎች አዳዲስ ክፍያዎች በመታገዱ ነው። ሪፖርቱ እነዚህ ውድቀቶች በታህሳስ 2024 በሀገሪቱ 1 ቢሊዮን ዶላር ዩሮቦንድ ላይ በነባሪነት የተገለፀውን ደካማ ሁኔታን እንደሚሸፍኑ ያስጠነቅቃል።

የገንዘብ ሚኒስትሩ አህመድ ሺዴ በሐምሌ ወር ለፓርላማ አባላት እንደተናገሩት ኢትዮጵያ 3.5 ቢሊዮን ዶላር የዕዳ እፎይታ ለማግኘት በምታደርገው ጥረት ከአበዳሪ ሀገራት ጋር የዕዳ ማሻሻያ ድርድር እያደረገች እንደሆነ ገልፀው ነበር።

የአለም ባንክ እና አይ ኤም ኤፍ የቅርብ ጊዜ ሪፖርት ኢትዮጵያ ከችግር የምትወጣበት መንገድ በውጪ ዕዳ ቅነሳ፣ የፊዚካል ማሻሻያ እና የኤክስፖርት ልዩነት ላይ የተመሰረተ እንደሆነ አስጠንቅቋል።

"የዕዳ አያያዝን በተሳካ ሁኔታ ማጠናቀቅ እና የማሻሻያ አጀንዳዎችን ተግባራዊ ማድረግ የእዳ ዘላቂነት ወደነበረበት እንዲመለስ እና ከዕዳ ጭንቀት ለመውጣት ያስችላል" ሲል የጋራ ግምገማው ገልጿል.

አምራች የሆነውን ማህበረሰብ በጦርነት አቆርቁዞ እንኳንስ የአበዳሪዎቹን እዳ ሊከፍል ለዜጎቹ በቂ የእለት ጉርስ ማደል የማይች ህሊና ቢስ አገዛዝ እራሱን እንደማያውቅ ህፃን ልጅ በብልጭልጭ ነገሮች በመከበብ ሀገሪቷ ላይ ለውጥ አመጣሁ በማለት የሚለፈልፍ ካፈርኩ አይመልሰኝ በማለት በፓርላማ ጭምር ለማኝነቱን ጥሮ ግሮ ያመጣው ይመስል በአደባባይ የሚያውጀው ወራዳው የሀገር መሪ ተብዬው ግለሰብ በዚው እንቅስቃሴው የሚቀጥል ከሆነ የሀገሪቷ መፃዒ እጣ ፈንታ ምን ሊሆን እንደሚችል መገመት አስቸጋሪ አይሆንም።

የዩቱዩብ ቻናልን
https://www.youtube.com/channel/UCDXU7RuIQc0xRKJyP0ZTZaQ

- page 👇
https://www.facebook.com/rohamedia2022/?ref=pages_you_manage

Telegram Channel 👇
👉 https://t.me/rohatv1

#ሮሃ ቴቪ tiktok
https://www.tiktok.com/?_t=ZM-8yvAZcRGkoq&_r=1

ብልጽግና ሊወረኝ እያኮበኮበ  ነው ስትል ኤርትራ አስታወቀች !መስከረም 9 ቀን 2018 ዓ.ም (ሮሃ ቴቪ) አብይ አሕመድ የመደመር መንግስት የተሰኘውን የቅዠት አዲስ መጽሀፋ ባስመረቁበት ወቅት...
19/09/2025

ብልጽግና ሊወረኝ እያኮበኮበ ነው ስትል ኤርትራ አስታወቀች !

መስከረም 9 ቀን 2018 ዓ.ም (ሮሃ ቴቪ)
አብይ አሕመድ የመደመር መንግስት የተሰኘውን የቅዠት አዲስ መጽሀፋ ባስመረቁበት ወቅት ስለ ባህር በር ጉዳይ ባደረገበት ንግግር በፍጹም ኢትዮጵያ መውጫ መግቢያ በሯን ዝግ አይሆንም፣ ባህር በሩ ይመጣል እናሳካዋለን› ሲሉ ተደምጠዋል፡፡

ይኽን ተከትሎም የብልፅግና የሚዲያ ሰራዊት ከግድቡ ወደ ወደቡ የሚል ዘመቻ ሲያደርጉ የቆዩ ሲሆን ይኽን መፈክርም በተለያዩ ከተሞች የንግድ ተቋማት በተለይም በደሴ ከተማ በባነር ካልሰቀላችሁ የሚል ንትርክ ውስጥ ሰንብተዋል።

ለዚህ የአብይ ንግግር ኤርትራ በማስታወቂያ ሚኒስትሩ በኩል እንደተለመደው የተቃውሞ መልስ ሰጥቷል፡፡

የማስታወቂያ ሚኒስትሩ አቶ የማነ በኤክስ ገፃቸው ባሰራጩት መልእከት፣ ብልጽግና ሉአላዊነታችንን ለመጣስ እያኮበኮበ ነው በማለት ከሰዋል፡፡ የብልጽግና ባለሥልጣናት ዘምተውብናል ሲሉ የወነጀሉት ሚኒስትሩ፤ የብልጽግና ባለሥልጣናት በባለቤትነት የሚቆጣጠሩት የባህር በር ለማግኘት ያላቸውን መሻት አጠናክረው ቀጥለዋል ብለዋል፡፡

የዩቱዩብ ቻናልን
https://www.youtube.com/channel/UCDXU7RuIQc0xRKJyP0ZTZaQ

- page 👇
https://www.facebook.com/rohamedia2022/?ref=pages_you_manage

Telegram Channel 👇
👉 https://t.me/rohatv1

#ሮሃ ቴቪ tiktok
https://www.tiktok.com/?_t=ZM-8yvAZcRGkoq&_r=1

የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል (አፋብኃ) በአማራ ክልል በጦርነት ለተጎዱና ለተፈናቀሉ ዓለማቀፍ የሰብዓዊ ድጋፍ ማሰባሰቢያ ቴሌቶን ይፋ ስለማድረግ!የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል (አፋብኃ) ማዕከላዊ ...
18/09/2025

የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል (አፋብኃ) በአማራ ክልል በጦርነት ለተጎዱና ለተፈናቀሉ ዓለማቀፍ የሰብዓዊ ድጋፍ ማሰባሰቢያ ቴሌቶን ይፋ ስለማድረግ!

የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል (አፋብኃ) ማዕከላዊ ኮማንድ በአማራ ሕዝብ ላይባለፉት 28 ወራት የአብይ አህመድ አገዛዝ በከፈተው ጦርነት ምክንያት ህጻናት ወላጅ አልባ ሁነዋል፣ ሽማግሌዎች ያለ ጧሪ ቀባሪ ቀርተዋል፣ የህክምና ተቋማትና መሰል የመሰረተ ልማቶች ወድመዋል። አፋብኃ በጦርነቱ ለተጎዱና ለተፈናቀሉ የሚውል የሰብዓዊ ድጋፍ ለማሰባሰብና ለማድረስ ለአራት ቀናት የሚካሄድ ዓለማቀፍ የቴሌቶን ፕሮግራም ለማካሔድ በዝግጅት ላይ ይገኛል።

የድጋፍ ማሰባሰቢያ ቴሌቶን የሚዘጋጀው የተለያዩ ባለድርሻ አካላት በሚሳተፉበት ኮሚቴ ሲሆን፣ ዝግጅቱ ከሁለት ወራት በኋላ በአሜሪካ ሃገርበሚከበረው የTHANKS GIVING በዓል ወቅት ከኖቬምበር 27 እስከ 30፣ 2025 ዓ/ም (እአአ) ይሆናል።

በቴሌቶን ዝግጅቱ ከ10 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር በላይ _ ለማሰባሰብ ታቅዷል።

በዚህ የወገን ደራሽ ድጋፍ ማሰባሰቢያ ዝግጅት ላይ ለአማራ ሕዝብ ህልውና የሚቆረቆር ወገን ሁሉ እንዲሳተፍና እንዲረባረብ አፋብኃ የአክብሮት ጥሪ ያቀርባል።

የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል

የዩቱዩብ ቻናልን
https://www.youtube.com/channel/UCDXU7RuIQc0xRKJyP0ZTZaQ

- page 👇
https://www.facebook.com/rohamedia2022/?ref=pages_you_manage

Telegram Channel 👇
👉 https://t.me/rohatv1

#ሮሃ ቴቪ tiktok
https://www.tiktok.com/?_t=ZM-8yvAZcRGkoq&_r=1

ቀኝ ጌታ ዮፍታሄ ንጉሴ 6ኛ ክፍለ ጦር በሜካናይዝድ መሳሪያ ያሰለጠናቸውን የመጀመሪያ ዙር ሰልጣኞች አስመረቀ።/ሮሃ ቴቪ /መስከረም 8ቀን 2018 ዓ.ምየአፋብኃ ምዕራብ ቀጠና ቴዎድሮስ ዕዝ ቀ...
18/09/2025

ቀኝ ጌታ ዮፍታሄ ንጉሴ 6ኛ ክፍለ ጦር በሜካናይዝድ መሳሪያ ያሰለጠናቸውን የመጀመሪያ ዙር ሰልጣኞች አስመረቀ።

/ሮሃ ቴቪ /መስከረም 8ቀን 2018 ዓ.ም

የአፋብኃ ምዕራብ ቀጠና ቴዎድሮስ ዕዝ ቀኝ ጌታ ዮፍታሄ ንጉሴ 6ኛ ክፍለ ጦር በሜካናይዝድ መሳሪያ ያሰለጠናቸውን የመጀመሪያ ዙር ሰልጣኞች በዛሬው ዕለት አስመርቋል።

በጥቂት የነፍስ ወከፍ መሳሪያ የተጀመረው ከመሳሪያ ይልቅስ የስነ ልቡና ትጥቅን አንግቦ በተፈጥሮ የአማራነት የጀግንነትና የድል አድራጊነት ልዩ ስጦታ ታጅቦ ድቡልቡል ድንጋይ እየወረወረ እስከ አፍንጫው የታጠቀውን የጅል ስብስብ መሳሪያውን ከነፍስ ወከፍ እስከ ሜካናይዝድ መሳሪያ እየተረከበ ዛሬ ላይ የደረሰበት የግዝፍና እና የኃይልነት ደረጃ ደርሷል ሲል ክፍለ ጦሩ መረጃውን አድርሶናል።

በሁለት ሳምንታት ውስጥ እንኳን ትጥቁን ቀበቶውን እንዲያወልቅ በድቡልቡል ደናቁርቶች የተዛበት ጀግናው የአማራ ፋኖ በጥቂት ጊዜያት ውስጥ አያሌ የጁላን ሠራዊት በመደምሰስ ፣አያሌዎቹንም በመማረክ ሌሎችንም በመሳብ ጨፍጫፊው ሠራዊት አለኝ የሚለውን የጦር መሳርያ ከጥቂት ሜካናይዝዶች በስተቀር በመረከብ ሕልውናውን ከማከበር አልፎ አጠቃላይ በቀጠናው ተጽዕኖ ፈጣሪ ኃይል ወደሆነበት ደረጃ ከፍ ብሏልም ብሏል።

አክሎም ዛሬ ላይም ዘመናዊ ሠራዊት በመገንባት፣ ለሠራዊቱም በየዘርፉ ሥልጠናዎችን በመስጠት ግዙፍ የሆነ ተቋም እየመሠረተ እንደሚገኝም ክፍለ ጦሩ አስታውቋል።

በዚህም መሠረት የአፋብኃ ምዕራብ ቀጠና ቴዎድሮስ ዕዝ ቀኝ ጌታ ዮፍታሄ ንጉሴ 6ኛ ክፍለ ጦር ለዘርፉ ትኩረት በመስጠት ከየብርጌዱ የተውጣጡ የመጀመሪያ ዙር የሚካናይዝድ መሳርያ ሰልጣኞችን በበቂ ሁኔታ በማሰልጠን በዛሬው ዕለት አስመርቋል።

በስልጠና መርሐ ግብሩ የሞርተር፣ የአርፒጅ፣ የጸረ ታንክና ሌሎችም የቡድን መሳሪያ ስልጠና የተሰጠ ሲሆን ተመራቂዎች በቂ እውቀት እንዳገኙ የክፍለ ጦሩ ስልጠና መምሪያ ኃላፊ ፶ አለቃ ቁሜ አዲስ ገልጿል።

በምረቃው የአፋብኃ ቴዎድሮስ ዕዝ አመራሮችና የክፍለ ጦሩ አመራሮች የተገኙ ሲሆን በተለይም ይህ በአይነቱ የመጀመሪያ የሆነው የስልጠና ፕሮግራም ተሳታፊ በመሆናቸው ለሰልጣኞቹ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።

ቀጣዩ የትግል ምዕራፋችን የሚካናይዝዱን ክንድ የሚፈልግ መሆኑን የጠቀሱት አመራሮቹ ስልጠናው ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ገልጸው ሰልጣኞቹ በስልጠና ቆይታቸው ባካበቱት ልምድ አደራቸውን እንዲወጡና ለሌችም እንዲያካፍሉ ገልጸዋል።

የዩቱዩብ ቻናልን
https://www.youtube.com/channel/UCDXU7RuIQc0xRKJyP0ZTZaQ

- page 👇
https://www.facebook.com/rohamedia2022/?ref=pages_you_manage

Telegram Channel 👇
👉 https://t.me/rohatv1

#ሮሃ ቴቪ tiktok
https://www.tiktok.com/?_t=ZM-8yvAZcRGkoq&_r=1

ኢትዮጵያ ኢንተርኔትን በተደጋጋሚ በመዝጋት ከአፍሪካ በአንደኛ ደረጃ መቀመጧን ጥናት አመለከተ! /ሮሃ ቴቪ/መስከረም 8ቀን 2018 ዓ.ም ኢትዮጵያ ኢንተርኔትን በተደጋጋሚ በመዝጋትና የኢንተርኔ...
18/09/2025

ኢትዮጵያ ኢንተርኔትን በተደጋጋሚ በመዝጋት ከአፍሪካ በአንደኛ ደረጃ መቀመጧን ጥናት አመለከተ!

/ሮሃ ቴቪ/መስከረም 8ቀን 2018 ዓ.ም

ኢትዮጵያ ኢንተርኔትን በተደጋጋሚ በመዝጋትና የኢንተርኔትን ነጸነት በመገደብ ከአፍሪካ በአንደኛ ደረጃ ላይ መቀመጧን በብሉምስበሪ አሳታሚ ላይ የታተመ የጥናት መጽሐፍ አመላከተ።

“የኢንተርኔት መዘጋት በአፍሪካ” በሚል ርእስ በፊሊሽያ አንቶኒዮ እና ቶኒ ሮበርትስ የተጠናውና መቀመጫውን በዩናይትድ ኪንግደም ባደረገው ብሉምስበሪ አሳታሚ ድርጅት ላይ በመጸሐፍ መልክ ታትሞ የወጣው ጥናት በአውሮፓውያኑ አቆጣጠር ከ2016 እስከ 2024 በአህጉረ አፍሪካ በሀገራት የተፈጸመውን የኢንተርኔት መዘጋት ገምግሟል።

በዚህም በአውሮፓውያኑ አቆጣጠር ከ2016 እስከ 2024 ባሉት በለፉት ዘጠኝ ዓመታት 193 የኢንተርኔት መዘጋት በአፍሪካ አህጉር መመዝገቡን ገልጿል።

በተጠቀሱት ዘጠኝ ዓመታት ውስጥ በተፈጸሙ የኢንተርኔት መዘጋት ድግግሞሽ መጠኖች ሀገራትን በደረጃ ያስቀመጠው ጥናቱ ኢትዮጵያን በእነዚህ ዓመታት ውስጥ ሰላሳ ጊዜ ኢንትርኔት የዘጋች በሚል ከ55ቱ የአፍሪካ ሀገራት በአንደኛ ደረጃ አስቀምጧታል።

በእርስ በእርስ ጦርነት እየታመሰች የምትገኜው ጎረቤት ሀገር ሱዳን በተጠቀሱት ዓመታት ውስጥ 21 ጊዜ ኢንተርኔትን በመዝጋት በአፍሪካ በሁለተኛ ደረጃ ስትቀመጥ፤ እንደዚሁ ባለፉት ዓመታት በሰላም እጦትና በግጭት ውስጥ ያለችው ሰሜን አፍሪካዊቷዓ ሀገር አልጀሪያ ደግሞ 14 ጊዜ ኢንተርኔትን በመዝጋት በሦስተኛ ደረጃ ተቀምጣለች።

ባለፉት ዘጠኝ ዓመታት በአህጉሪቱ የተፈጸመው የኢንተርኔት መዘጋት ሁኔታና የድግግሞሽ መጠኑ ከሀገር ሀገር ከፍተኛ ልዩነት የሚታይበት መሆኑንም የጥናቱ ውጤት አመላክቷል።

በዚህም ምንም እንኳዓን በብዙዎቹ የአፍሪካ ሀገራት የኢንተርኔት መዘጋት የነበረ መሆኑን የጠቆመው ጥናቱ፤ በዚያው ልክ ደግሞ በ14 የአፍሪካ ሀገራት ውስጥ አንድም የኢንተርኔት መዘጋት አለመመዝገቡን፤ በሌሎች 14 ሀገራት ደግሞ የኢንተርኔት መዘጋት የገጠመው አንድ፣ አንድ ጊዜ ብቻ መሆኑን አስታውሷል።

በአህጉሪቱ የተፈጸመው የኢንተርኔት መዘጋት ክስተት በመጠንና በድግግሞሽ ብቻ ሳይሆን ለድርጊቱ መፈጸም መንስኤ በሆኑ ገፊ ምክንያቶች ጭምርም ሰፊ ልዩነት የሚታይበት መሆኑን ጥናቱ አመላክቷል።

የመንግሥታት ሕዝባዊ አመጽን መፍራት፣ በሀገራቱ ውስጥ የሚኖሩ ግጭቶችና ጦርነቶች፥ ምርጫን ተከትለው ሊቀሰቀሱ የሚችሉ አመጾች፥ የፈተና መሰረቅንና መጭበርበርን ለማስቀረትና የፖለቲካ ተቃውሞን ለማፈን የሚወሰዱ ሴንሰርሽፖች ባለፉት ዘጠኝ ዓመታት በአህጉሪቱ ለተፈጸሙ የኢንተርኔት መዘጋትና በኢንተርኔት ነጻነት ላይ ለተፈጸሙ ገደቦች ዋነኛ መንስኤ ሆነው መለየታቸውንም ጥናቱ ገልጿል።

ኢትዮጵያን በተመለከተም የኢንተርኔት መዘጋት በተለይም በግጭትና በጦርነት ወቅት ሊኖረው የሚችለው ውጤትና በዜጎች ሰብአዊና ዲሞክራሲያዊ መብቶች ላይ ሊያስከትል የሚችለው ተጽእኖና በጥናቱ መካተቱን አዲስ ማለዳ ዘግቦታል።

የዩቱዩብ ቻናልን
https://www.youtube.com/channel/UCDXU7RuIQc0xRKJyP0ZTZaQ

- page 👇
https://www.facebook.com/rohamedia2022/?ref=pages_you_manage

Telegram Channel 👇
👉 https://t.me/rohatv1

#ሮሃ ቴቪ tiktok
https://www.tiktok.com/?_t=ZM-8yvAZcRGkoq&_r=1

"ስንጠብቅ የነበረው ይህንን ውጤት ነው" ትምህርት ምኒስቴርየትምህርት ሚንስተርው ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በዛሬው እለት የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤትን በተመለከተ በሰጡት መግለጫ 91.1% ...
14/09/2025

"ስንጠብቅ የነበረው ይህንን ውጤት ነው" ትምህርት ምኒስቴር

የትምህርት ሚንስተርው ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በዛሬው እለት የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤትን በተመለከተ በሰጡት መግለጫ 91.1% ተማሪዎችን መጣላቸውን ገልፀው ይህንንም በኩራት " ስንጠብቅ የነበረው ይህንን ውጤት ነው " በማለት ንግግር አድርገዋል።

በ2017 ዓ/ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከተፈተኑት 585,879 ተማሪዎች መካከል 48,929 ተማሪዎች 50 በመቶ አምጥተው አልፈዋል። ይህም 8.4 በመቶ ነው።
በ2016 ዓ/ም ከ674,823 ተማሪዎች ያለፉት 36,409 ወይም 5.4 በመቶ ነበሩ በማለት የተፈታኞችን ውጤት ገልፀዋል።

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ በ2017 ዓ/ም ተማሪዎች ስላስመዘገቡት ውጤት የተሰማቸውን ሲገልፁ "ስንጠብቅ ያነበረው ይህንን ውጤት ነው። የመጀመሪያ ሾክ ነበር ከዛ ግን በራሱ ውጤት የሚያልፍ ተማሪ እየመጣ ነው።የፈተና ስርአታችን ሊያመጣው የሚፈልገው ውጤት እየመጣ ነው ትክክለኛው መስመር መሆኑን የተረዳንበት ነው።ይህንን ሃገር የሚጠበቅበት ቦታ ለማድረስ ለእዛ የሚበቃ ትውልድ እያፈራን ነው። በእዚሁ እንዲቀጥል ነው የምንሰራው በማለት ተናግረዋል ።

የተለያዩ የሀገራችን ክፍሎች በብልፅግናው መር ስርዓት አስፈፃሚነት ጦርነቶች ያለ እረፍት በሚቀጣጠሉበት ወቅት ተማሪዎች አይደለም በአግባቡ ለመማር ወጥቶ መግባት ስጋት በልቶ ማደር ቅንጦት በሆነበት ሁኔታ ብሔራዊ ፈተናን ሰጥቼ ይሄንን ያህል ተማሪ ፈተናውን አልፏል የተቀሩት ደግሞ ወድቀዋል ብሎ መግለጫ መስጠት በራሱ ያለንበትን የሞራል ዝቅጠት እና የአስተሳሰብ ባዶነትን የሚያሳይ ነው።

ከስር መሰረቱ ፈርሶ በአዲስ መልክ መገንባት የሚገባውን ስርዓተ ትምህርት ለተማሪዎች መመዘኛ በማድረግ የከሸፈ ትውልድ ለማፍራት የሚሯሯጠው ሚንስትር ተጠሪውን ብርሃኑን ነጋን ጨምሮ ጀሌዎቹ ቢፈተኑ የማያልፉትን ፈተና ለተማሪዎች በመስጠት በእርሱ ፈተና የወደቁትን ተማሪዎች ለብልፅግናው መር ስርዓት ማስፈፀሚያ ተላላኪ መከላከያ ለማድረግ ጠንክሮ እየሰራ ይገኛል።

አንድም ዩኒቨርስቲ ገንብቶ የማያቀው ያገዛዙ ሥርዓት ዩኒቨርስቲዎችን ባዶውን እያስቀረ አክሎም የጦር ካምፕ ሲያደርጋቸው በአንጻሩ የመከላከያ ሰራዊቱን እያዘመንኩ ነው ሲል ደጋግሞ ይስተዋላል።

የዩቱዩብ ቻናልን
https://www.youtube.com/channel/UCDXU7RuIQc0xRKJyP0ZTZaQ

- page 👇
https://www.facebook.com/rohamedia2022/?ref=pages_you_manage

Telegram Channel 👇
👉 https://t.me/rohatv1

#ሮሃ ቴቪ tiktok
https://www.tiktok.com/?_t=ZM-8yvAZcRGkoq&_r=1

Address

Addis Ababa

Telephone

+251920603569

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ሮሃ ሚዲያ ROHA MEDIA posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to ሮሃ ሚዲያ ROHA MEDIA:

Share