ሮሃ ሚዲያ ROHA MEDIA

ሮሃ ሚዲያ ROHA MEDIA የፌስቡክ ገፃችንን ላይክ በማድረግ እለታዊ መረጃዎችን ይከታተሉ!
(1)

የኦፓል ማዕድን ዋሻ የተናደባቸው ማዕድን አውጭዎች አፅም ስርዓተ ቀበራቸው ተፈፀመ።ሮሃ ቴቪ ኅዳር 8 ቀን 2018 ዓ.ምበአማራ ክልል ደቡብ ወሎ ዞን ደላንታ ወረዳ ባሳለፍነው ዓመት ጥር 30 ...
17/11/2025

የኦፓል ማዕድን ዋሻ የተናደባቸው ማዕድን አውጭዎች አፅም ስርዓተ ቀበራቸው ተፈፀመ።

ሮሃ ቴቪ ኅዳር 8 ቀን 2018 ዓ.ም

በአማራ ክልል ደቡብ ወሎ ዞን ደላንታ ወረዳ ባሳለፍነው ዓመት ጥር 30 ቀን 2016 ዓ.ም ኦፓል በማውጣት ላይ ሳሉ ዋሻ ተንዶባቸው ሊገኙ ያልቻሉት ስመንት ወጣቶች ከ 20 ወራት በኋላ በዋሻ ውስጥ አፅማቸው መገኘቱን መዘገባችን የሚታወስ ሲሆን በዛሬው እለትም ስርዓተ ቀበራቸው ተፈፅሟል።

በደላንታ ወረዳ በተለምዶ ቆቅ ውኃ እየተባለ በሚጠራ አካባቢ ጥር 30 ቀን 2016 ዓ.ም ሌሊት የኦፓል ማዕድን በቁፋሮ ለማውጣት ሲሞክሩ የነበሩ በርካታ ወጣቶች የቆፈሩት አለት ተንዶ ህወታቸውን ማትረፍ እና 8ቱ ደግሞ ሳይገኙ መቅረታቸው የሚታወስ ነው።

ከአመት በኋላ ባሳለፍነው ሳምንት ህዳር 4 ቀን 2018 ዓ/ም በአካባቢው ኦፖል በማውጣት ላይ የነበሩ ወጣቶች አፅማቸው በዋሻ ውስጥ ማግኘታቸውን ቢቢሲን ዋቢ አድርገን መዘጋባችን የሚታወስ ሲሆን ይህንንም ተከትሎ ህዳር 4 ቀን ከማለዳው 12:00 ጀምሮ የአፀም ማውጣት ስራው ተጀምሮ የ8 ወጣቶች አፅም ወጥቶ ወዳጅ ዘመዶቻቸው በተገኙበት በወገልጤና ርዕሰ አድባራት ሐመረኖህ ቅድስት ኪዳነምህረት ቤተክርስቲያን የፍትሃተ ፀሎት ተደርጎ ስርዓተ ቀብራቸው ተፈፅሟል ተብሏል።

ላለፉት 13 አመታት የኦፓል ማዕድን ቁፋሮ ሲደረግበት የቆየው ዋሻ ከ750 ሜትር በላይ ርዝመት ያለው ሲሆን በደረሰበት የመናድ አደጋ በውስጡ የቀሩ ሰዎችን ለማውጣት በወቅቱ ከ80 ሜትር በላይ ቁፋሮ መደረጉ ይታወሳል። ከ20 ወራት በኋላ አጽማቸው ሲገኝም ሰራተኞቹ ቁፋሮ እያደረጉ በነበሩበት የዋሻ ክፍል ተዘግቶባቸው በህይወት ለቀናት እንደቆዩና እሚደርስላቸው በማጣታቸው አሟሟታቸውም በረሀብ ምክንያት እንደሆነም ምንጮች ተገኝተዋል። አፅማቸውም በአንድ አንድ ሜትር ርቀት እንደተገዘ ሆኖ ተዘጋጅተው እንደተገኙም ተገልጿል። መጨረሻ የሞተው ብቻ ገለል ብሎ በዛው ህይወቱ አልፎ ተገኝቷል። በሥነ ሥርዓት በአንድ አንድ ሜትር ርቀት አስቀምጧቸዋል። በረሃብ ነው የሞቱት" ይላሉ። የማኅበሩ ሊቀ መንበር አቶ ተስፋዬ "እነሱ ያሉበት እና የሚቆፍሩበት ቦታ ውስጥ አልተናደም፤ ከእነሱ ወደታች ያለው ክፍል ነው የተናደው እና የተዘጋው መውጫ አጥተው ነው፤ አቅጣጫው በጣም ከባድ ስለሆነ ነው መውጣት ይችሉ ነበር። የተገኙበት ሁኔታ ልጆቹ ውሃ እየጠጡ እንደቆዩ የሚያስረዳ ነው። ዋሻው ውስጥ ውሃ ስላለ ውሃ ለማግኘት የቆፈሩትን ሁሉ አግኝተነዋል" ሲሉ ተናግረዋል።።

ከ20 ወራት በፊት በደላንታ በማዕድን ቁፋሮ ዋሻ ውስጥ ተደርምሶባቸው የቀሩት ሰራተኞች በዋሻው በህይወት እያሉ ሚደርስላቸው አተው  በረሀብ ምክንያት እንደሞቱ ተረጋጋጠ! ሮሃ ቴቪ ኅዳር 6 ቀ...
15/11/2025

ከ20 ወራት በፊት በደላንታ በማዕድን ቁፋሮ ዋሻ ውስጥ ተደርምሶባቸው የቀሩት ሰራተኞች በዋሻው በህይወት እያሉ ሚደርስላቸው አተው በረሀብ ምክንያት እንደሞቱ ተረጋጋጠ!

ሮሃ ቴቪ ኅዳር 6 ቀን 2018 ዓ.ም

በአማራ ክልል ደቡብ ወሎ ዞን ደላንታ ወረዳ የኦፓል ማዕድን ቁፋሮ ላይ እያሉ ዋሻ የተናደባቸው ስምንት ግለሰቦች ከአንድ ዓመት አስር ወራት በኋላ አጽማቸው መገኘቱ ተገልጿል።

ሰራተኞቹ ቁፋሮ እያደረጉ በነበሩበት የዋሻ ክፍል ተዘግቶባቸው በህይወት ለቀናት እንደቆዩና እሚደርስላቸው በማጣታቸው አሟሟታቸውም በረሀብ ምክንያት እንደሆነም ምንጮች ተገኝተዋል ነው የተባለው።

የማኅበሩ ሊቀመንበር አቶ ተስፋዬ አጋዥ ለቢቢሲ የማዕድን ቆፋሪዎቹ አስክሬን የተገኘበተን ሁኔታ ሲያብራሩ "በአንድ አንድ ሜትር ርቀት ነው ያገኟቸው። ተዘጋጅተው ነው የተገኙት። መጨረሻ የሞተው ብቻ ገለል ብሎ ተገኝቷል። በሥነ ሥርዓት በአንድ አንድ ሜትር ርቀት አስቀምጧቸዋል። በረሃብ ነው የሞቱት" ይላሉ።

አቶ ተስፋዬ አክለውም "እነሱ ያሉበት እና የሚቆፍሩበት ቦታ ውስጥ አልተናደም፤ ከእነሱ ወደታች ያለው ክፍል ነው የተናደው እና የተዘጋው መውጫ አጥተው ነው፤ አቅጣጫው በጣም ከባድ ስለሆነ መውጣት ይችሉ ነበር።

የተገኙበት ሁኔታ ልጆቹ ውሃ እየጠጡ እንደቆዩ የሚያስረዳ ነው። ዋሻው ውስጥ ውሃ ስላለ ውሃ ለማግኘት የቆፈሩትን ሁሉ አግኝተነዋል" ሲሉ አስረድተዋል።

ከማዕድን ቆፋሪዎቹ አስክሬን መገኘት በኋላ ምን እንደተሰማቸው የተጠየቁት አስር አለቃ ተስፋዬ "ጉዳቴን እኔ ራሴ አውቀዋለሁ። ስሜቱ እንዳለ ሁኖ ፈጣሪ ባዘዘው ቀን አስክሬኑን አግኝተን ወደ ቤተክርስቲያን አስቀምጠናል" ብለዋል።

የማኅበሩ ሊቀምንበር አቶ ተስፋዬም በተመሳሳይ የቅርብ ዘመዳቸው ዋሻ ውስጥ ተቀብሮ እንደነበር ለቢቢሲ ገልጸው፤ "ምን ዋጋ አለው መውጣት ባለመቻላቸው በጣም ከባድ ስሜት ነው የተሰማኝ። ዙሮ ዙሮ ወደ ቤተክርስቲያን መምጣታቸው ጥሩ ነው" ሲሉ ለቢቢሲ ስሜታቸውን አጋርተዋል።

አስር አለቃ ተስፋዬ ልጃቸው የተቀበረባቸው እህታቸው ያሳለፏቸውን ሁለት ዓመት የሚጠጉ ጊዜያት፤ "ማንም የማይቀንሰው ትልቅ ስቃይ" ሲሉ ይገልጹታል። "ምንም አማራጭ እስከ ሌለው ድረስ ደግሞ አግኝታ ያለውን ነገር ቤተ ክርስቲያን መቅበሯ ለዘመድም ሆነ ለእሷ የዘላለም እሳት ከሚሆን ቁርጡን አውቃ ተቀመጠች። ቢያንስ ዘመዷ ጋር ቀበረችው እስካሁን ጫካ ውስጥ ነበር" ሲሉ ያክላሉ።

የዩቱዩብ ቻናልን
https://www.youtube.com/channel/UCDXU7RuIQc0xRKJyP0ZTZaQ

- page 👇
https://www.facebook.com/rohamedia2022/?ref=pages_you_manage

Telegram Channel 👇
👉 https://t.me/rohatv1

#ሮሃ ቴቪ tiktok
https://www.tiktok.com/?_t=ZM-8yvAZcRGkoq&_r=1

ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ የአገዛዙን ሻለቃ መሪው በቁጥጥር ስር አዋለ!በአፋብኃ ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ ግዙፉ ላስታ ጄኔራል አሳምነው ፅጌ ኮር ስር ተከዜ ክፍለ ጦር መረጃን ...
15/11/2025

ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ የአገዛዙን ሻለቃ መሪው በቁጥጥር ስር አዋለ!

በአፋብኃ ምስራቅ አማራ ቀጠና ምኒልክ ዕዝ ግዙፉ ላስታ ጄኔራል አሳምነው ፅጌ ኮር ስር ተከዜ ክፍለ ጦር መረጃን በማነፍነፍ የ61ኛ ክፍለ ጦር የ2ኛ ሻለቃ ምክትል መሪ የሆነው መቶ አለቃ በእውቀቱ ምስጋናው ከድልብ ወደ ግዳን ወረዳ ሙጃ ማርያም ከተማ በሚወስደው መንገድ ዴንሳ ከተማ ላይ በተከዜ ክፍለ ጦር ፋኖዎች ህዳር 04/2018 ዓ.ም አመሻሽ ላይ በቁጥጥር ስር ሊዉል ችሏል።

ይህ ግለሰብ ላስታ ወረዳ ኩልመስክ ከተማ ላይ ከዚህ በፊት ስምንት ንፁሃንን የረሸነና ያስረሸነ፣የብዙ ወጣቶችን አካል ያጎደለ፣የአባውራ ሴቶችን የደፈረ፣ህዝባዊ መድረክ ላይ በይፋ ኩልመስክ ከተማን ጥቁር አለብሳታለሁ እያለ ማህበረሰቡ ላይ ግልፅ የስነ ልቦና ጫና ያደርስ የነበረ፣ከነጋዴው ብሎም ከማህበረሰቡ ሙስና የሚቀበልና የግል ጥቅሙን የሚያግበሰብስና ፍፁም ስነ ምግባር የጎደለው ጥቁር አማራ ነበርም ተብሏል።

የአርበኛ ጌትነት መሳፍንትን መስዋዕትነት አስመልክቶ ከዋርካው ምሬ ወዳጆ የተላለፈ መልዕክት!ዘመናትን ተሻግሮ የመጣውን የአማራ ህዝብ ግፍና በደል ለማስቆም ህዝቡንና መላ ቤተሰቡን አስተባብሮ ...
11/11/2025

የአርበኛ ጌትነት መሳፍንትን መስዋዕትነት አስመልክቶ ከዋርካው ምሬ ወዳጆ የተላለፈ መልዕክት!

ዘመናትን ተሻግሮ የመጣውን የአማራ ህዝብ ግፍና በደል ለማስቆም ህዝቡንና መላ ቤተሰቡን አስተባብሮ ሲታገል የኖረው የትግል አባታችን አርበኛ መሳፍንት ተስፉ ዛሬም የዘመናት ግፉ ወደ ዘር ማጥፋት አድጎ የህልውና አደጋ ውስጥ የገባውን የአማራ ህዝብ ለመታደግ እየተደረገ ባለው ተጋድሎ ከባድ ዋጋ እየከፈለ ይገኛል::

በዚህ መራር ዋጋ እየተከፈለበት ባለ ትግል ጥቅምት 29/2018 ዓ.ም በሰሜን ጎንደር ዞን ዳባት ወረዳ አጅሬ የተሰኘች ታዳጊ ከተማ የሰሜን አምባራስ ክፍለጦር አዛዥና የራስ አሞራው 3ኛ ኮር አስተዳደር ሃላፊ የሆነው አርበኛ ጌትነት መሳፍንት ተስፉ መስዋዕትነት የከፈለ ሲሆን በዚህም ከባድ ሃዘን እንደተሰማኝ ለመግለፅ እወዳለሁ::

ትግላችን እስከቀራኒዮና አባታችን አርበኛ መሳፍንት ተስፉ እስከ ቤተሰብዎ ለአማራ ሕዝብ በደማቅ የደም ቀለም እየተጻፈ ነውና ትውልድ በጀግንነትና ለአማራ ሕዝብ የተከፈለ እውነተኛ አማራነት ነውና ለእሱ በግሌ አመሰግናለሁ ማለት እወዳለሁ። ይህ መስዋዕትነት የአንድ ጀግና መስዋዕትነት ብቻ ሳይሆን ለአማራነት ዋጋ መክፈል ምን ማለት እንደሆነ በሕይወት እያሉ ህያው ምስክር ነዎት!

የአማራ ፋኖ የጀመረውን የህልውና ትግል አጠናክሮ ይቀጥላል፣ የወንድማችን አርበኛ ጌትነት መሳፍንት ተስፉና በአውደ ውጊያ በወደቁ ጀግኖቻችን ዘመቻ አውጀን የአብይ አህመድን አገዛዝ ድባቅ እንደምንመታው ወደ ድልና ነጻነትም እንደምንሸጋገር ከምስራቅ አማራ ቀጠና ሁኜ ይሄን መልዕክት ሳስተላልፍ በታላቅ ቁርጠኝነትና ቁጭት ሁኜ መሆኔን መግለጽ እፈልጋለሁ።

በመጨረሻም ለአርበኛ መሳፍንት ተስፉ፣ ቤተሰቦቹ፣ እና መላው የትግል ጓዶቹ ልባዊ መጽናናትን እመኛለሁ።

ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን
የአፋብኃ ማዕከላዊ ኮማንድ አባል እና የምኒልክ ዕዝ ሰብሳቢ ዋርካው ምሬ ወዳጆ

ከአርበኛ ኃብቴ ወልዴ መንግሥቴ የተላለፈ የሀዘን መግለጫ       ሕዳር 01/2018ዓ.ም የአርበኛ ጌትነት መሳፍንት ድንገተኛ መስዕዋትነት መፅናናቱን እየተመኘሁ እልፍ ጀግኖችን ተክቶ በማለፉ...
10/11/2025

ከአርበኛ ኃብቴ ወልዴ መንግሥቴ የተላለፈ የሀዘን መግለጫ
ሕዳር 01/2018ዓ.ም

የአርበኛ ጌትነት መሳፍንት ድንገተኛ መስዕዋትነት መፅናናቱን እየተመኘሁ እልፍ ጀግኖችን ተክቶ በማለፉ ኩራት ይሰማናል!!

መስዕዋትነት የነበረና ያለ ወደፊትም የሚኖር መራር እውነት ቢሆንም ከልጅነት እስከ እውቀት የረጅም ዘመን የአርበኝነት ግንባታ ተክለ ቁመናው የተገነባው ነበልባሉ ወንድሜ ታማኙ ጓዴ አርበኛ ጌትነት መሳፍንት የአባ ድፈን ክንድ እንዲህ በከሃዲ ከኃላ ተመተህ በአፍላ የአገልግሎት ዘመንህ ትጎልብናለህ ብለን አስበን አናውቅም ነበርና መስዕዋትነትህን ስሰማ ጥልቅ ሀዘንና ቁጭት ተሰምቶኛል።

የራስ አሞራው 3ኛ ኮር አስተዳደር ኃላፊና የሰሜን አምባራስ ክ/ጦር ዋና አዛዥ በመሆን በጥንካሬ እየታገለና እያታገለ የነበረው ጌትነት መሳፍንት በአያሌ ግንባሮች ተዋግቶ በድል ያጠናቀቀ ማርኮ የታጠቀና ያስታጠቀ ያደራጀና በስነ ምግባር ምሳሌ ሁኖ የመራ ጀግናችን የአባ ድፈን ክንድ ጌትነት መሳፍንት በስራ ተልዕኮ በተሰማራበት ከመቶ በላይ ጠላት በተደመሰሰበት የአጅሬ ግንባር ህያው ሁኖ ሊወድቅ ቢገደድም እልፍ ጌትነቶችን ተክቶ ያለፈ ህያው ጀግናችን በመሆኑ ኩራት ይሰማናል።

ወንድማለም ጌች በጠላት ላይ የወጠንናቸው የትግል ዕቅዶቻችንን ሁሉ ገቢራዊነት በቁርጠኝነትና በማስተዋል ለመስራት ዝግጁ መሆኔን አረጋግጥልኻለሁ።

ጉምቱው አርበኛ አባታችን ጀግናው አርበኛ መሳፍንት ተስፉ እና መላው ቤተዘመድና የትግሉ ቤተሰብ በአርበኛው ወንድማችን ህልፈት መፅናናቱን እንዲሰጠን እመኛለሁ።

አርበኛ ኃብቴ ወልዴ መንግሥቴ
የአፋብኃ ሴንትራል ኮማንድ ኮሚቴ አባል እና
የሰሜን አማራ ቀጠና በላይ ዕዝ ዋና ሰብሳቢ
ሕዳር 01/2018 ዓ.ም
ሰሜን አማራ ቀጠና /ኢትዮጵያ

የአማራ ሳይንሳዊ ኮንፈረንስ‼
07/11/2025

የአማራ ሳይንሳዊ ኮንፈረንስ‼

"መሞት በቃን አንሙት ማለት ፖለቲካ አይደለም" ብፁዕ አቡነ ናትናኤልሮሃ ቴቪ ጥቅምት 27 ቀን 2018 ዓ.ም ብፁዕ አቡነ ናትናኤል የመድኃኒዓለም ክብረ በዓል ላይ በመገኘት በወቅታዊ ጉዳይ ላ...
06/11/2025

"መሞት በቃን አንሙት ማለት ፖለቲካ አይደለም" ብፁዕ አቡነ ናትናኤል

ሮሃ ቴቪ ጥቅምት 27 ቀን 2018 ዓ.ም

ብፁዕ አቡነ ናትናኤል የመድኃኒዓለም ክብረ በዓል ላይ በመገኘት በወቅታዊ ጉዳይ ላይ መልዕክትን አስተላልፈዋል።

ብፁዕነታቸው መቼ ነው ደም መፍሰስና እልቂት የሚቆመው? ነፃነት እንፈልጋለን ! የሰው ልጆች ደም በከንቱ መፍሰስ መቆም አለበት። ነጻነትን መፈለግ ፣ ሰላምን መሻት፣ እረፍት መፈለግ አንሙት ማለት ፖለቲካ አይደለም ሰብአዊነት ነው መሞት በቃን ! ሲሉ በምሬት ተናግረዋል።

አክለውም ለምዕመኑ "ደከመን ህዝቡም በኛ ፈረደ እናንተም ወቀሳችሁን:: እውነት አላችሁ:: ሲሉ ገልፀዋል።

እኛን ማን ይስማን ሞትን ተለማመድነው ስንቶቻችን ስንታረድ ስንቶቻችን ስናልቅ ነው ሚቆመው? ሞት ሰለቸን ደም መፍሰስ በቃን ሀገሪቱ እረፍት ያስፈልጋታል ብለዋል ብፁዕነታቸው።

የዩቱዩብ ቻናልን
https://www.youtube.com/channel/UCDXU7RuIQc0xRKJyP0ZTZaQ

- page 👇
https://www.facebook.com/rohamedia2022/?ref=pages_you_manage

Telegram Channel 👇
👉 https://t.me/rohatv1

#ሮሃ ቴቪ tiktok
https://www.tiktok.com/?_t=ZM-8yvAZcRGkoq&_r=1

“በድርጅታዊ ማዕከላዊነት የኅልውና ትግላችንን ዓላማ እናሳካለን!!!”ከአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል (አፋብኃ)በላይ ዘለቀ ዕዝ በጉባኤ መቋጫ ላይ የተሰጠ የአቋም መግለጫየአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል ...
04/11/2025

“በድርጅታዊ ማዕከላዊነት የኅልውና ትግላችንን ዓላማ እናሳካለን!!!”

ከአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል (አፋብኃ)
በላይ ዘለቀ ዕዝ በጉባኤ መቋጫ ላይ የተሰጠ የአቋም መግለጫ

የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል (አፋብኃ) በላይ ዘለቀ ዕዝ ከመስከረም 23 እስከ ጥቅምት 07/2018 ዓ.ም ዓመታዊ የሥራ አሥፈጻሚ ጉባኤውን አድርጓል። የጀመርነው የኅልውና ትግል ከያዝነው ነባራዊ እውነት ባሻገር፣ ብርቱ መረዳትን፣ ክህሎትንና ልዩ ልዩ የትግል ስልተ መንገዶችን መንደፍንም ጭምር አጥብቆ ይሻል። በውይይት ፖለቲካዊ አቅም ያድጋል፣ በውይይት የሃሳብ ልዩነቶች ይገራሉ/ይታረቃሉ፣ በውይይት ጓዳዊ መስተጋብሮች ይዳብራሉ፣ በውይይት አዳዲስ የአሠራር መንገዶች ይቀየሳሉ።

ከምንም በላይ ደግሞ ልዩልዩ ሥልጠናዎችን በጋራ መውሰድ አንድም መስጠት የአረዳድ ልዩነቶችን ለማጠበብ ያግዛል። በዚህ መሠረት የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል (አፋብኃ) በላይ ዘለቀ ዕዝ አመራሮች ለጋራ ትግል፣ ለጋራ ዓላማና ግብ በጋራ መምከርና መሰልጠን በማስፈለጉ ይህ ታሪካዊ ጓባኤ ተዘጋጅቶ በተሳካ መንገድ ተጠናቋል።

ጉባኤው ቀጠናችን ላይ የሚገኙትን አስቸጋሪ ሰንሰለታማ ተራሮችንና ቁልቁለቱን በማቆራረጥ ከሃያ ቀናት በላይ ጉዞን በጠላት መካከል አቆራርጠን የመከርንበት፣ አቅጣጫዎችን ያስቀመጥንበት፣ የጋራ መገነዛዘቦችን የፈጠርንበት ትልልቅ ውሳኔዎችን ያሳለፍንበት ታሪካዊ ጉባኤ ነው።

የዚህ ታሪካዊ ጉባኤ መሪ ቃል “በድርጅታዊ ማዕከላዊነት የኅልውና ትግላችንን ዓላማ እናሳካለን” የሚል ሲሆን ድርጅታዊ ማዕከላዊነት አሁን ላይ ያለውን የተበታተነ ኃይል፣ የተበታተነ ሃሳብ፣ የተበታተነ አደረጃጀትን በአማራነት እሴት አንድም በአማራነት አስተሳሰብና በመታገያ ጉዳያችን አይለወጤ ነገረ ጉዳይ አማካይነት የሚከናወን ቁልፍ እሳቤ ነው።

የኅልውና ትግላችን እድገቱ፣ የአደረጃጀትና የኃይል ግንባታ ስፉህነቱ፣ የጠላት ደካማና ተለዋዋጭ የአጥፊነት መንገዱ፣ የቀጠናው መልክዓ ፖለቲካዊ ተለዋዋጭ እንቅስቃሴው፣ የዓለም አቀፍ ግዙፍ ተቋማት ሥርዓቱ ላይ ያላቸው አተያይን በተሟላ መንገድ ማስተካከል የሚቻለው ወጥ የሆነ ማዕከላዊነቱን የጠበቀ ተቋማዊ አንድም ድርጅታዊ አሠራርን ማሳደግና ማከበር ሲቻል እንደሆነ በጽኑ እናምናለን።

ድርጅታዊ ማዕከላዊነት ተቋማዊ መርኅና አሠራር ከላይ ወደ ታች፣ በአንጻሩ በድርጅት ጥላ ሥር የሚገኙ አሓዶች፣ ግለሰቦች ከታች ወደ ላይ የሚያከናውኗቸው የሠመሩ ተግባቦቶች እንዲፈጠሩ ጉልህ ሚና ይጫወታል። በዚህ ሂደት ውስጥ ድርጅታዊ አሠራሮች፣ ህግና ደንቦች፣ ነባራዊ እውነት፣ ዘመን ዘለል ልሂቅነት፣ ዓለምአቀፍ አሠራርን ያማከለ ምክንያታዊነት፣ ለህዝብ ጥቅምና ለወል ዓላማ መስዋዕት ከፋይነት ማጠንጠኛ ቁልፍ ጉዳዮቹ ናቸው። ድርጅታዊ ማዕከላዊነት እኔነትን ይጠየፋል በአንጻሩ በእኛነት፣ በአብሮነት፣ በአንድነትና በአንድ ተቋማዊ አሠራር ተገዥነት የሚጓዙት የአሠራር መሠረት ነው። ለዚህ መሰሉ አሠራር በላይ ዘለቀ ዕዝ የሥራ አስፈጻሚ ጉባኤ አባላትና መላው የዕዛችን የሠራዊቱ አመራሮችና አባላት የሚያምኑበትን፣ የሚያሸንፉበትን፣ ጠላትን የሚነቅሉበትን፣ የሕዝባችንን ዘለቄታዊ ኅልውና የምናረጋግጥበትን በማዕከላዊ አንድ አሠራርነት፦ አንድ አመራርነት፣ አንድ ግን የጋራ ውሳኔ ሰጭነት፣ የጋራ ጠላት ላይ ማበር መተባበርነት፣ አንድ ተቋም መፍጠርነት፣ በአማራነት አንድ መሆንነት ላይ ትኩረታችን፣ ውይይትና ሥልጠናችንን ማድረግ ችለናል።

በጥቅሉ የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል (አፋብኃ) በላይ ዘለቀ ዕዝ በጉባኤው መቋጫ ላይ የሚከተሉትን ሦስት የአቋም መግለጫዎች በማውጣት ጉባኤውን ቋጭቷል።

የአብይ አሕመድ አረመኔያዊ አገዛዝ ባለፉት ሰባት ዓመታት በመላው አገሪቱ አማራዊ ማንነት ያላቸውን አካላት ያለ አንዳች ምክንያት እንደ አውሬ እያደነ በጅምላ በአሰቃቂ ሁኔታ መግደሉ፣ ከቀያቸው ማፈናቀሉ፣ ሃብት ንብረታቸውን ማውደሙ ገሐደ የወጣ ሐቅ ነው። ከምንም በላይ ደግሞ ባለፉት ሁለት ዓመታት ክልላችን ውስጥ ጦር አዝምቶ ያልፈጸመው አረመኔያዊ ድርጊት የለም።

ሕዝባችንንም በጅምላ በአየር ኃይልና በሜካናይዝድ ጦር ጨፍጭፏል፣ ዓለምአቀፋዊ የጦር ወንጀልም ፈጽሟል። እንዲሁም ለማኅበራዊ፣ ምጣኔሃብታዊና ፖለቲካዊ ቀውስ ሕዝባችንን ዳርጎታል። በዚህ ሥርዓታዊ አውዳሚነት ሂደት ውስጥ የፋኖ መካች ትግልና እንቅስቃሴ ባይኖር ኖሮ ግፍና መከራው በመቶዎች እጥፍ ሊጨምር በቻለ ነበር። ስለሆነም በመንግሥትነት ጭምብል የሚነግደው ይህ ወንጀለኛ ሥርዓት በአጭር ጊዜ እንዲወገድ የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል (አፋብኃ) ማእከላዊነትን ጠብቀን የትግል መንገዳችንን ሥልታዊነት (Strategize) አድርገን ለመታገል ያለንን ጽኑ አቋም እንገልጻለን።

የኅልውና ትግላችንን የገጠመው የኃይል እጥረት ሳይሆን ያለንን ሰፊ ኃይል በአንድ አስተባብሮና አቀናጅቶ ጠላት ላይ አለመተባበር እንደሆነ የታመነ ጉዳይ ነው። ባለፉት ሁለት ዓመታት ውስጥ አጠገብ ካለ ወንድም ይልቅ ሩቅ ላለ አካል ከፍተን የሰጠነው ጆሯችን ብዙ ዋጋ አስከፈለን። የአንድ አማራዊ ማንነት ባለቤቶች ሆነን፣ አንድ ጠላት ኖሮን፣ አንድ ዓይነት ሞት ተደግሶልን እኛ ለምን አንድ መሆን ተሳነን ካልን ቁጭ ብለን መነጋገር አለመቻላችን ካልሆነ ሌላ ምክንያት የለንም።

“መለያየት ሞት ነው” እንዳለ ባለቅኔው መለያዬት ለተደገሰልን ሥርዓታዊ የሞት ድግስ ራስን ማዘጋጀት ነው፣ መለያየት የሕዝብን ሰቆቃ ማራዘሚያ መንገድና ጸረ ሕዝብነት ነው፣ መለያዬት ልሂቅነት ሳይሆን የዘመናችን የአላዋቂነት ጥግ ነው፣ መለያዬት በድርጅታዊ ማዕከላዊነት አለመጓዝና ትልቁን ዓላማና ግብ መዘንጋት ነው።

ስለሆነም ማሸነፊያ መንገዳችን የሕዝብን እንባ ማበሻ መሃረባችን፣ የተደበቀም የተገለጠም የጠላት አሠራርና እቅድን ማርከሻ ፍኖታችን፣ በኅልውና ትግላችን ስም በሕዝብ ላይ የሚቀልዱ ባለግል ፍላጎት አጋች፣ ሌባ ዘራፊና ተላላኪ ባንዳዎች ማጥሪያ ወንፊታችን አንድነት ብቻ ነው። ይህንን ቅዱስ ተግባር ለማከናወን ቁጭ ብሎ “እውነትን፣ እውቀትን፣ ፍጹም መተማመንን” ማእከል አድርጎ መነጋገር መቻል እንደሆነ በጽኑ እናምናለን። ለዚህ ተግባራዊ ሥራ ደግሞ የበላይ ዘለቀ እዝ እስከ መጨረሻው ድረስ ተጉዞ የማሸነፊያ ቁልፍ የሆነው አንድነት እንዲመጣ ያለንን ጽኑ አቋም እንገልጻለን።

በአፍሪካውያን ብቻ ሳይሆን በመላው ዓለም ታፍራና ተከብራ የምትኖረውን ታላቋን ሃገር ኢትዮጵያን ፖለቲካዊ ተደማጭነቷን፣ ታሪካዊ ልዕልናዋን በማኮሰስ፣ በውስጥ ዓለምአቀፍ የጦር ወንጀል እየፈጸመ፣ በቀጠናው ሃገሪቷን ወደ ጦርነት አዙሪት ውስጥ ለማስገባት እየተደረጉ ያሉ የጦርነት ነጋሪት ጉሰማ አካሄድ የሥርዓቱን የፖለቲካ ዲፕሎማሲ ድህነት ፍንትው አድርጎ የሚያሳይ ጉዳይ ነው።

የምሥራቅ አፍሪካ መልክዓ ፖለቲካ በየቀኑ መልኩንና ገጽታውን እየለዋወጠ የሚገኘውም በግንባር ቀደምትነት በብልጽግና ተናካሽ የፖለቲካ አካሄድ እንደሆነ ለማንም የተሰወረ አይደለም። ይኸው የምሥራቅ አፍሪካ ቀጠና በርካታ የተፈጥሮ ሃብቶች ያሉት፣ የበርካታ ፖለቲካዊ፣ ምጣኔ ሃብታዊ፣ ማኅበራዊና መሰል የባህል፣ የቋንቋ፣ የእምነት እንዲሁም የሥነ ልቡና ተጋሪነት ያለው በመሆኑ አብሮ የመልማት፣ ሥነ ምኅዳራዊ ተጋሪነትና ተጠቃሚነት ያለው መሆኑን እንኳን የሚያስብበት ፖለቲካዊ መርኅና ስሪት የሌለው የቀጠናው ጸረ-ሰላም ኃይል መሆኑን በዓለም አደባባይ እያሳየ የሚገኝ በመሆኑ ይህንን እኩይ እብሪተኛ ቡድን እስካልተወገደ ድረስ በውስጥም በቀጠናውም ሠላም መስፈን እንደማይችል በጽኑ እናምናለን።

ስለሆነም በውስጥ የሃገሪቱ ሁሉንአቀፍ ቀውስ እንዲስተካከል በውጭ ቀጠናዊ ቀውሱ እንዲስተካከል ቀውስ ጠማቂውን በተባበረ ክንድ ማስወገድ ቁልፉ ተግባራችን እንደሆነ ያለንን ጽኑ አቋም እንገልጻለን።

ኅልውናችን በተባበረ ክንዳችን!!!
ከአማራ ፋኖ ብሔራዊ ኃይል (አፋብኃ) በላይ ዘለቀ ዕዝ

ይኼንን ጽሑፍ ቁጭ ብለህ እያነበብህ ያለኸው በዚህ ሰዓት ምሥራቅ አርሲ ገጠር ውስጥ ስላልተገኘህ ብቻ ነው:: በዚህች ቅጽበት በሥጋት ውስጥ ሆነው "ከአሁን አሁን ምን ይመጣብን ይሆን?" እያሉ...
04/11/2025

ይኼንን ጽሑፍ ቁጭ ብለህ እያነበብህ ያለኸው በዚህ ሰዓት ምሥራቅ አርሲ ገጠር ውስጥ ስላልተገኘህ ብቻ ነው:: በዚህች ቅጽበት በሥጋት ውስጥ ሆነው "ከአሁን አሁን ምን ይመጣብን ይሆን?" እያሉ ያሉ የኦሮሚያ ምእመናን ቁጥራቸው ብዙ ነው:: ከቀናት በፊት የተገደሉትን ተናግረን ሳናበቃ አሁን ደግሞ ሌላ ቦታ አምስት እንደተገደሉ እየሰማን ነው::

ሰሞኑን ከሁለት ሺህ ዓመታት በፊት ሔሮድስ ስላሳደዳት እመቤታችን "ሰቆቃወ ድንግል" እያልን እያዘንን ነው:: ከሰይፍ ልጅዋን ማስጣል ያልቻለች የአርሲዋን እናትስ እንዴት ዝም እንበላት? ይህንን የማያቆም ሞት ዜና ሰምተን ወደ ጉሮሮአችን የሚወርድ ምግብና መጠጥ የምንተኛውም እንቅልፍ የለም:: የእነርሱ ሞት የእኛ ሞት ነው:: የእነርሱ መቁሰል የእኛ ቁስል ነው:: የቦታ ለውጥ እንጂ በእነርሱ የደረሰው በእኛም ሊደርስ ይችላል::

ቤተ ክርስቲያን ምሕላ እንድታውጅ ፣ ለተሠዉት ተገቢውን ክብር እና ጸሎተ ፍትሐት እንድታደርግ እንጠብቃለን:: ቤተ ክርስቲያን በየትኛውም ቦታ የንጹሐን ደም ዳግመኛ እንዳይፈስስ እንደ ራሔል ዕንባዋን የምትረጭበት ጊዜ አሁን ነው::

የቤተ ክርስቲያን አስተዳደር ትኩረት ያልሠጠውን ችግር ሌላ አካል ሊጨነቅበት አይችልም:: ስለዚህ ቤተ ክርስቲያን በአስተዳደራዊ መዋቅርዋ መንግሥት ተገቢውን እርምጃ እንዲወስድ በሙሉ ትኩረት የምትሠራበት ጊዜም አሁን ነው:: ቅዱስ ሲኖዶስ በዚህ ዓይነት ጊዜ የሚያሳየው ምላሽ ከሌለ ሌላ ቀን ቢጣራ የማይሰማውን ቤተ ክርስቲያን አልባ ክርስቲያን በራሱ ላይ ይፈጥራል:: ሐዋርያዊትዋ ቤተ ክርስቲያንም በክህነት የማትመራ የመሆን አደጋ ይገጥማታል:: ክህነት ከሌለ ደግሞ ቤተ ክርስቲያንም ምሥጢራትም የሉም::

ኦርቶዶክሳውያን ምእመናንም ይህንን ጊዜ ለመካሰስ ፣ አባቶችን ለመሳደብ ፣ አንዱ ሌላውን ለማስጠቆርና ለመናቆር ሳይሆን ለጸሎት ለምሕላና ለሰብአዊ ሥራና መሬት ላይ ቢወርዱ ችግሮችን የሚፈቱ ዘላቂ መፍትሔዎች ላይ በትብብር ለመሥራት ምክንያት ብናደርገው የተሻለ ነገር ማምጣት እንችላለን::

የሌላ እምነት ተከታዮች ሆነው ይህ በኦርቶዶክሳውያን ላይ ብቻ ሳይሆን በኢትዮጵያውያን ላይ የተቃጣ ጥቃት ብለው ጉዳዩን በተቋምም በግልም ያወገዙ ሰዎችን እናከብራለን:: "ይበላችሁ" ብለው የተሳለቁትን እና በክፉ ቀን ክፋታቸውን ላሳዩን ደግሞ እውነተኛ ማንነታቸውን ስላሳዩን እያመሰገንን "አቤቱ፥ በኢየሩሳሌም ቀን የኤዶምን ልጆች አስብ፦ “እስከ መሠረትዋ ድረስ አፍርሱ አፍርሱ፡” ያሉአትን" ብለን ለሰማያዊው ዳኛ ሠጥተናቸዋል:: መዝ. 137:7






©Henok Haile

Address

Addis Ababa

Telephone

+251920603569

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ሮሃ ሚዲያ ROHA MEDIA posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to ሮሃ ሚዲያ ROHA MEDIA:

Share