ሮሃ ሚዲያ ROHA MEDIA

ሮሃ ሚዲያ ROHA MEDIA የፌስቡክ ገፃችንን ላይክ በማድረግ እለታዊ መረጃዎችን ይከታተሉ!
(1)

29/06/2025

የህወሃት ወታደራዊ ትርዒት

ህወሃት ከፍተኛ ባለስልጣናቱ በተገኙበት ወታደራዊ ትርኢት አሳየ

ህወሃት በትናንትናው እለት በላላይ ቆራሮ ወረዳ የተሰራ ሃውልትን ባስመረቀበት ወቅት ከፍተኛ አመራሮቹ ተገኝተዋል ፣ ወታደራዊ ትርኢቶች ተካሂደዋል፡፡
በዚህም የድርጅቱ ሊቀመንበር ደብረጽዮን ገ/ሚካኤል ፣ አማኑኤል አሰፋ ፣ ፈትለወርቅ ገብረ እግዛቤር/ ሞንጆሪና ፣ የሰላምና ጸጥታ ሃላፊው ፍስሃ ኪዳኑ / ማንጁስ/ ተገኝተዋል፡፡
በመድረኩ ላይም ከዐቢይ መንግስት ጋር የገቡበትን ፍጥጫ የሚጠቁሙ ንግሮችን አድርገዋል፡፡ የክልሉ ሰላምና ጸጥታ ቢሮ ሃላፊው ፍሰሃ ማንጁስ “የተከፋፈለች ትግራይን ለልጆቻችን አናስተላልፍም” ሲሉም በክልሉ ከእነ ጌታቸው ረዳ ጋር የገቡበትን የአካባቢያዊ ክፍፍል አንስተዋል፡፡
ደብረጽዮን ገብረሚካኤልና አማኑኤል አሰፋም በመድረኩ ላይ ንግግር አድርገዋል፡፡
በቦታው ከተሰራው የሀውልት ምርቃት ጎን ለጎን ሀውልቱ በተመረቀበት ቦታ አካባቢ እነ ደብረጽዮን የኮማንዶ ወታደራዊ ትርዒት አሳይተዋል።
ይህ የኮማንዶ ወታደራዊ ትርኢትም ህወሃትና ብልጽግና ከ2013 ጥቅምት 24 በፊት ወደ ነበራቸው ግንኙነት እየተመለሱ መሆናቸውን የሚጠቁም ነው፡፡
በዚያን ወቅት ተመሳሳይ ወታደራዊ ትርኢቶችን አዲስ አበባም መቀሌም በተመሳሳይ ያስተናግዱ እንደነበር ይታወሳል፡፡
አሁንም የቃላት ጦርነቶችን ያካተቱ ወታደራዊ እንቅስቃሴዎችና ትርኢቶች ያንን ጦርነት መልሰው እንዳያመጡ የሚል ስጋት ፈጥሯል፡፡
በሌላ በኩል ደግሞ የዐቢይ አማካሪ ሚንስትሩ አቶ ጌታቸው ረዳ፥ " የትግራይ ህዝብ አሁንም ከህልውና አደጋ አልወጣም " ብለዋል።
" ችግሮቻችንን በውጭ ምክንያቶች እያሳበብን ከመኖር ውስጣችን በደምብ በመፈተሽ የተወሳሰቡ ችግሮቻችን መፍታት እንችላለን " ሲሉ የገለጹት በአዲስ አበባ የትግራይ እድሎችና ፈተናዎች በሚል በተዘጋጀ መድረክ ላይ ነው።
"ትግራይ ጥቂት አመራሮች ማረምና ማንሳት አቅቷት በከባድ ፈተና ተዘፍቃ ትገኛለች ፤ ይህንን ከባድ ፈተና ለመወጣትና ለማለፍ ወጣቶችን ወደ መሪነት ማምጣት ይጠበቅበታል " ብለዋል።
"በአሁኑ ሰዓት ትልቅ የህልው አደጋ ለተጋረጠበት የትግራይ ህዝብ ስለ ዴሞክራሲና ልማት ማውራት ቅንጦት ነው" በማለት አክለዋል።
ጌታቸው በትግራይ ስለዲሞክራሲና ልማት ማውራት ቅንጦት ነው ቢሉም ይህን ማውራት በሌሎች አካባቢዎችስ ከቅንጦት በላይ አይደለም ወይ ብሎ የጠየቃቸው የለም፡፡
ምክንያቱም በመላው ኢትዮጵያ በአሁኑ ሰዓት ስለ ዲሞክራሲና ልማት ማውራት ቅንጦት ከሆነ ሰነባብቷል፡፡

https://t.me/rohatv1

27/06/2025

የብልጽግና ደብዳቤና ኤርትራ

ብልጽግና በኤርትራ ጉዳይ ላይ የጻፈው ደብዳቤና የኤርትራ ምላሽ እያነጋገረ ነው
ኤርትራ፤ የብልጽግናው መንግሥት "ለጦርነት አጀንዳው ድጋፍ ለማሰባሰብ"፤ የከፈተውን "ዲፕሎማሲያዊ ዘመቻ አጠናክሮብኛል" ስትል በመግለጫ መክሰሷን በማለዳው የዜና እወጃችን ወደ እናንተ አድርሰን ነበር።
የኢትዮጵያ መንግሥት "ባለፉት ቀናት" ኤርትራን የሚከስሱ ደብዳቤዎችን ወደ "የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ" እና "የሀገራት መሪዎች ልኳል" በማለትም ወቅሷል።
የኤርትራ መንግሥት ይህንን ክስ በኢትዮጵያ ላይ ያቀረበው ትናንት ሐሙስ ሰኔ 19/2017 ዓ.ም. በማስታወቂያ ሚኒስቴር በኩል ባወጣው መግለጫ ነው።
የብልጽግና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌድዮን ጢሞትዮስ የኤርትራ መንግሥትን በተመለከተ "ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ደብዳቤ ማሠራጨቱን" የመረጃ ምንጮች ጠቁመዋል፡፡
ዘግቦ ነበር።
በማህበራዊ ሚዲያ እየተሰራጨና ለብልጽግና ቅርብ በሆኑ ሚዲያዎች ጭምር እየተዘዋወረ የሚገኘው ደብዳቤው ባለፈው ሳምንት አርብ ሰኔ 13/2017 ዓ.ም. እንደተጻፈ የሚያመለክት ሲሆን፣ በኤርትራ መግለጫ የተጠቀሰውን "ተደጋጋሚ ትኮሳዎችን" የመፈጸም እና "የሉዓላዊነት እና የግዛት አንድነት ጥሰቶችን" የሚመለከት ዓረፍተ ነገር ያካተተ ነው።
የውጭ ጉዳይ በተጨማሪም፤ የኤርትራ መንግሥት "ከህወሓት አንጃ ጋር ትብብር እና ቅንጅት በመፍጠር እንዲሁም ከሌሎች ታጣቂ ኃይሎች ጋር በመተባበር በመጪው የክረምት ወቅት ከፍተኛ ወታደራዊ ጥቃት ለመፈጸም ተዘጋጅተዋል" በማለት እንደወነጀለ በደብዳቤው ላይ ተካትቷል።
የኤርትራ መንግሥት በበኩሉ ትናንት ባወጣው መግለጫ የኢትዮጵያ መንግሥት የጻፈውን ደብዳቤ "የተለመደ ማደናገሪያ" ሲል ጠርቶታል።
"[የዲፕሎማሲ ዘመቻው] ዓለም አቀፉን ማኅበረሰብ ማታለል እና በዚህም ረጅም ጊዜ ሲብላላ ለቆየው የጦርነት አጀንዳው ድጋፍ ማሰባሰብን" ዓላማ ያደረገ ነው በማለት ከስሷል።
መግለጫው፤ "እውነታው ግን የኢትዮጵያ ገዢ ፓርቲ ብልፅግና፤ የኤርትራ ወደቦችን 'በተቻለ መጠን በሕጋዊ መንገድ፣ አስፈላጊ ከሆነም በወታደራዊ መንገድ' ለመውሰድ በሚል ላለፉት ሁለት ዓመታት በግዴለሽት አላስፈላጊ መግለጫዎች እና ተንኳሽ ጦር ሰበቃ ውስጥ እየገባ ነው" ብሏል። የኢትዮጵያ መንግሥት "የጦር መሣሪያዎች ግዢ" ላይ ተሰማርቷል ሲልም አክሏል።
ይህ የኤርትራ መንግሥት መግለጫ የወጣው በአዲስ አበባ እና አሥመራ ባለሥልጣናት አንዳቸው ሌላኛቸውን ዒላማ የያደረጉ ንግግሮችን እያሰሙ ባሉበት በዚህ ወቅት ነው።

https://t.me/rohatv1

Address

Addis Ababa

Telephone

+251920603569

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ሮሃ ሚዲያ ROHA MEDIA posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to ሮሃ ሚዲያ ROHA MEDIA:

Share