Kufa Multimedia

Kufa Multimedia Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Kufa Multimedia, News & Media Website, Addis Ababa.

30/05/2023

ወቅታዊ ሁኔታን በተመለከተ

ከሁለት ወራት ቀደም ብሎ ሸገር ሲቲ ተብሎ በተሰየመው የኦሮሚያ ክልል ውስጥ የሚገኙ በርካታ መስጊዶች ተገቢ ባልሆነ እና በህገወጥ መንገድ መፍረስ መጀመራቸውን ተከትሎ ይህ ህገወጥ የመስጊድ ፈረሳ እስከ አሁንም ድረስ በመቀጠሉ ህዝበ ሙስሊሙን በማስቆጣቱ ዕለተ አርብ ግንቦት 18/2015 በታላቁ አንዋር መስጊድ ህዝበ ሙስሊሙ ተቃውሞ ማሰማቱ ይታወቃል። በዕለቱ በነበረው ተቃውሞ ፖሊስ በሰላማዊ ሰዎች ላይ በወሰደው የኃይል እርምጃ 2 ሙስሊሞች መስዋእትነት ሲከፍሉ በርካታ ሙስሊሞች ለአካል ጉዳት እና ለእስር ተዳርገዋል። በህዝባችን ላይ በደረሰው ጉዳት ነጃሺ ኢስላማዊ ማህበር የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን ይገልፃል። መስዋእትነት የከፈሉ ወንድሞቻችን በጀነተል ፊርደውስ ከነብዩ ሙሐመድ ሶለላሁ ዓለይሂ ወሰለም ጉረቤት እንዲያደርጋቸው አላህን እንማፀናለን።

ማህበረሰባችን ለዚህ የከፋ ጉዳት የተጋለጠው ሀቀኛ፣ ብቁ እና ህዝባዊ ተቀባይነት ያለው መሪ ተቋም የሌለው በመሆኑ እንደሆነ ይታወቃል። በታሪካችን ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ ሙስሊሞች በብዙ መስዋእትነት የሰሯቸው መስጊዶች ከአንድ ተራ መኖሪያ ቤት እኩል ህገወጥ ናቸው ተብለው በኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት እንዲፈርሱ ሲደረግ አሁን ላይ በህገወጥ መንገድ በመፈንቅለ መጅሊስ የሙስሊሙን መሪ ተቋም የተቆጣጠረው ቡድን መስጊዶቹ አንድ ብለው መፍረስ ሲጀምሩ ከማስቆም ይልቅ ዝምታን እና ማድበስበስን በመምረጡ ጉዳዩ ተባብሶ ቁጥራቸው በርካታ የሆኑ መስጊዶች እንዲፈርሱ ትልቁን በር ከፍቷል። ለመስጊዶቹ ጥብቅና በመቆም ህዝብን በማስተባበር ከመፍረስ ሊታደጋቸው ያልቻለው ህገወጡ መጅሊስ ለመስጊዶቹ መፍረስ እና ህዝበ ሙስሊሙ መሪ አልባ እንዲሆን በማድረጉ ረገድ ቅድሚያ ተጠያቂው ነው።

መንግስት የህዝብን ደህንነት የመጠበቅ ኃላፊነት አለበት። ሙስሊሙ ማህበረሰብ የእምነት ተቋማቱ ያለ ምክንያት ሲፈርሱበት ተቆጥቶ በሰላማዊ መንገድ ቅሬታውን ሲገልፅ የፀጥታ አካል ያልተገባ የኃይል እርምጃ በመውሰድ የዜጎችን ህይወት መቅጠፍ እና ለአካል ጉዳት መዳረጋቸው በፍፁም ተገቢ ያልሆነ አካሄድ ከመሆኑ ባሻገር መንግስት የዜጎቹን ደህንነት የመጠበቅ ኃላፊነቱን ያለመወጣት ተግባር ነው። በመሆኑም መንግስት የዜጎችን ህይወትና አካል ከሚቀጥፍ የኃይል ተግባር በመቆጠብ የሙስሊሙን ማህበረሰብ ደህንነት የመጠበቅ ኃላፊነቱን ሊወጣ ይገባል።

በእለቱ አድማ በታኞች ወደ አንዋር መስጊድ ቅጥር ጊቢ ለመግባት ያደረጉት ሙከራ ፍፁም የተሳሳተ እና ሙስሊሙን ማህበረሰብ ከፀጥታ ኃይላት ጋር ወደ ግጭት እንዲገባ ያደረገ ትንኮሳ ነበር። አስለቃሽ ጭስ ወደ መስጊድ ቅጥር ጊቢ መተኮሳቸው እጅግ የተወገዘ ተግባር ነው። የእምነት ተቋማት ሊከበሩ እና ሊታፈሩ፣ በውስጡ የተቀመጡ ምእመናን በሰላም በመስጊዱ ቅጥር ጊቢ ውስጥ የመቆየት እና የአምልኮ ተግባር የመፈፀም ሰብአዊ መብታቸው ሊከበር ይገባል።

መስጊዶቻችን የህልውናችን መሰረት አላህን በብቸኝነት ለማምለክ የምንጠቀምባቸው ተቋሞቻችን እንደመሆናቸው ያለ ምክንያት ሲፈርሱ መመልከት እጅግ ስሜታዊ ያደርጋል። ሆኖም ግን በማህበረሰባችን ላይ የመጣውን ፈተና እንዴት መሻገር አለብን? ምን ብናደርግ ምን እናገኛለን ምን እናጣለን? በምን አይነት አቅጣጫ ነው መጓዝ ያለብን? ፈተናውን ለመጋፈጥ ያለን አቅም ምን ያህል ነው? … ለሚሉ በርካታ ጥያቄዎች መልስ እየሰጠን መጓዝ ከስሜት እና ከተናጠል አካሄዶች በመቆጠብ እንደ ሙስሊም ማህበረሰብ ነገን አሻግረን እያየን ፈተናውን መሻገር ግድ ይሆናል። እንደ አለመታደል ሆኖ መሪ ዑለማኦቻችን ከመሰረቱት ተቋም በታጣቂ ኃይል ተገፍተው በመውጣታቸው እና መጅሊሱን የሚሾፍሩት የአንድ ቡድን ስሜት ብቻ የሚያንፀባርቁ ፅንፈኛ እና ህገወጥ ሰዎች በመሆናቸው ከህወገጡ መጅሊስ ለሙስሊሙ ማህበረሰብ የሚበጅ አቅጣጫ ይኖራል ተብሎ አይታመንም። በኦሮሚያ ክልል መስጊዶች ዛሬም ድረስ እየፈረሱ ቢሆንም ህገወጡ መጅሊስ አፉን ዘግቶ ተለጉሞ ቁጭ በማለቱ ዘላቂ መፍትሄ ከህገወጥ አካል አንጠብቅም።

በመሆኑም በአቅራቢያችን በአካባቢያችን የሚገኙ ዑለማኦቻችን ጋር ምን ይበጀናል? ብሎ በመመካከር
ካልተቀናጀ ከተናጠል እና ከስሜታዊ አካሄድ በመቆጠብ ሙስሊሙ ማህበረሰብ የነፍስ፣ የደም፣ የአካል እና የንብረት መስዋእትነት ተገቢ ባልሆነ መንገድ እንዳይገብር እጅግ የበረታ ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርብናል። በአስተውሎት መራመድ ዛሬ የተፈፀመብን ግፍና መድሎ ነገ በተሻለ ህብረት እና ጥንካሬ እንድንቋቋመው ያስችለናል።

ባለፉት ጊዜያት "ድምፃችን ይሰማ" የተባለው ቡድን በዲን ሽፋን ሙስሊሙን ማህበረሰብ ለድብቅ የፖለቲካ አጀንዳ ሲያታግል እና ተገቢ ያልሆነ መስዋእትነት ሙስሊሙን ማህበረሰብ ሲያስከፍል እንደነበር የብልፅግና መንግስት መምጣትን ተከትሎ "የለውጡ ሃዋሪያ እኛ ነን፣ ዛሬ ለተገኘው ለውጥ ፈር ቀዳጆቹ ነን" እያሉ በወቅቱ የነበረው እንቅስቃሴ የፖለቲካ አጀንዳ ይዞ እንደተንቀሳቀሰ እማኝነታቸውን ሰጥተዋል ዛሬም ድረስ በራሳቸው ላይ እየመሰከሩ ይገኛል። በመሆኑም ካለፈው ስህተት በመማር የሙስሊሙን ወቅታዊ ቁስሎች መነሻ በማድረግ ወደማናውቀው አቅጣጫ ይዘውን ለመጓዝ ለሚፈልጉ ለሚታወቁ እና ለማይታወቁ አካላት ተገዢ ባለመሆን ተደራራቢ ጉዳቶችን ማህበረሰባችን እንዳያስተናግድ ጥንቃቄ ማድረግ የሁላችንም ኃላፊነት ነው። ማንነታቸው የማይታወቁ እና ኃላፊነት የማይወስዱ አካላት በሚያስጀምሩት ተቃውሞዎች ተሳታፊ ባለመሆን ማህበረሰባችንን ከጉዳት እንጠብቅ።

ዕለተ አርብ ግንቦት 18/2015 በአንዋር መስጊድ እና በመርካቶ ዙሪያ ለተገደሉ፣ ቆስለው የአካል ጉዳት ለገጠማቸው እና ለታሰሩ ሰዎች ከጎናቸው በመቆም አስፈላጊውን እገዛ እናድርግላቸው። ብዙ ወጣቶች ቆስለው በህክምና ላይ ናቸው። በርካታ ወጣቶች በጅምላ ታፍሰው ዛሬም ድረስ በእስር ላይ ይገኛሉ። በህመም እና በእስር ላይ የሚገኙ ወጣቶች ከፍተኛ እገዛ ያስፈልጋቸዋልና ጉዳዩ የጋራችን በመሆኑ እንደ ሙስሊም ማህበረሰብ ኃላፊነታችንን እንወጣ። በዚህ አጋጣሚ ከሙስሊም ወንድሞቻቸው ጎን በመቆም አብሮነታቸውን መስዋእትነት በመክፈል ጭምር በጎነታቸውን ላሳዩን ክርስቲያን ወገኖቻችን እጅግ የላቀ ምስጋና እያቀረብን ሙስሊሙ ማህበረሰብ አስፈላጊውን ህክምና እንዲያገኙ ከጎናቸው እንዲሆን ጥሪ እናቀርባለን።

በኦሮሚያ ክልል ውስጥ ሙስሊሙ ማህበረሰብ ላይ እየተፈፀመ ያለውን ግፍ መንግስት በአስቸኳይ እንዲያስቆመው፣ የሙስሊሙ ንብረት የእምነት ተቋማት እና ሰብአዊ መብቶች እንዲከበሩ መንግስት ኃላፊነቱን እንዲወጣ አጥብቀን እንጠይቃለን።

የአዲስ አበባ ሙስሊም ወጣቶች ማሕበር

በአዲሱ የሸገር ከተማ በመንግስት የፈረሱና እየፈረሱ የሚገኙ በርካታ መስጊዶችን ጉዳይ በተመለከተ በዛሬዉ ዕለት በተለያዩ መስጊዶች ድምጻቸዉን ባሰሙ ሙስሊሞች ላይ በተወሰደዉ የሀይል እርምጃ በ...
26/05/2023

በአዲሱ የሸገር ከተማ በመንግስት የፈረሱና እየፈረሱ የሚገኙ በርካታ መስጊዶችን ጉዳይ በተመለከተ በዛሬዉ ዕለት በተለያዩ መስጊዶች ድምጻቸዉን ባሰሙ ሙስሊሞች ላይ በተወሰደዉ የሀይል እርምጃ በደረሰዉ የሞትና የመቁሰል አደጋ የተሰማኝን ጥልቅ ሀዘን እየገለጽኩ ለሞቱት ጀነትን፣ ለቆሰሉት ፈዉስን፣ ለቤተሰቦቻቸዉም መጽናናትን እመኛለሁ፡፡

የተከበሩና የተቀደሱ ቤተዕምነቶችን ቅጽር ጥሶ መግባትና የዕምነት ተቋማትን በዚህ ልክ መዳፈር ከዘመነ-ኢህአዴግ በስተቀር በየትኛዉም የሀገራችን የመንግስት ሥርዓት ታሪክ ተፈጽሞ የማያዉቅ ሲሆን፣ ዉጤቱም ለማንም የማይበጅና በዉስብስብ ፈተናዎች ዉስጥ እያለፈች ባለችዉ ሀገራችን ላይ ተጨማሪ የመከራ ሸክም መጫን በመሆኑ የሚመለከተዉ አካል ነገሩን ቆም ብሎ ሊያጤነዉ ይገባል፡፡

አላህ ሀገራችንን ሠላም ያድርግልን!!!

Ambassador/Ustaz Hasen Taju

https://t.me/hassentaju

ኢና ሊላሂ ወኢና ኢለይሂ ራጂዑን!!💔አሏህ ያሻውን ሰሪ…የወደደውን ፈረደ!ለዓመታት የቀጥባሬን ሐድራ ያጋፈሩት፣የመውሊዱ አበባ የነበሩት፣ የራቲባው ድምቀት፣ የነዝሙ የመደዱ ዘዋሪው… ሸይኽ ሰል...
23/05/2023

ኢና ሊላሂ ወኢና ኢለይሂ ራጂዑን!!💔

አሏህ ያሻውን ሰሪ…የወደደውን ፈረደ!
ለዓመታት የቀጥባሬን ሐድራ ያጋፈሩት፣የመውሊዱ አበባ የነበሩት፣ የራቲባው ድምቀት፣ የነዝሙ የመደዱ ዘዋሪው… ሸይኽ ሰልማን ወደ አኼራ ሒደዋል። የቀጥባሬን መስጂድን ለዘመናት በዒማምነት አገልግለዋል። ሸይኽ ሰልማን ለነፍሳቸው ምቾት እና ዱንያዊ ተድላ ሳይጓጉ፣ ከሼኾች ሐድራ ሳይርቁ ዘውትረው ኺድማቸውን ፈፅመዋል። በሺዎች የሚቆጠሩ ደረሶችን አቅርተዋል። ብዙዎችንም ለትልቅ ዓሊምነት አብቅተዋል። የቃጥባሮች ኮኮከብ ዛሬ ሌሊት ወደ አኼራ ቤታቸው ተሻግረዋል።

ኢናሊላሂ ወኢና ኢለይሂ ራጂዑን!

የሸይኻችን ስርዓተ ቀብር ነገ ማክሰኞ ከዙሁር ሶላት ስግደት በኋለ በቃጥባሬ ሐሪማ ቅጥር ግቢ ይፈፀማል።

መድረስ የቻልን ለቀብር ኹላችንም እንድረስ። ያልቻልነው ደግሞ በያለንበት ዒማማችንን በፋቲሃ እናውሳቸው!!💔

ተተኪያቸውን አላህ አያሳጣን

ኢና ሊላሂ ወኢነ ኢለይሂ ራጂኡን 😥   #የገደባኖ (ወለኔ) ሼህ የሆኑት ሼህ መሀመድ ሼህ ከድር ሼህ አብድሽኩር ወደ አኼራ ሄደዋል አላህ ጀነተል ፍርዶስን ቤታቸውን ያድርገው 🤲
21/05/2023

ኢና ሊላሂ ወኢነ ኢለይሂ ራጂኡን 😥

#የገደባኖ (ወለኔ) ሼህ የሆኑት ሼህ መሀመድ ሼህ ከድር ሼህ አብድሽኩር ወደ አኼራ ሄደዋል አላህ ጀነተል ፍርዶስን ቤታቸውን ያድርገው 🤲

 #ሐይቅሐይቆች ለወሀ^ብያ የሚከፈት ምንም አይነት በር የለም እያሉን ነው!የዛሬው ስብስብ የ*ፖለቲካና የጥቅም አባዜ የተጠናወታቸው ሰዎች ከሚያደርጉት ስብስብ የራቀና የተለየ ነው። ይህ ስብስ...
20/05/2023

#ሐይቅ
ሐይቆች ለወሀ^ብያ የሚከፈት ምንም አይነት በር የለም እያሉን ነው!
የዛሬው ስብስብ የ*ፖለቲካና የጥቅም አባዜ የተጠናወታቸው ሰዎች ከሚያደርጉት ስብስብ የራቀና የተለየ ነው።
ይህ ስብስብ ትክክለኛ አንድነት በነብዩ፣ በሶሐበቶች ብሎም የርሱን አደራ ጠብቀው ባቆዩት የመሻይኾች መንገድ መሆኑን በተግባር የሚያሳይ ስብስብ ነው።

©️ ኩፋ መልቲሚዲያ

የህገወጡ የአዲስ አበባ መጅሊስ ኃላፊ አቶ ሱልጣን አማን የአዲስ አበባን ሙስሊም ሰላም እየነሳ ሽብር እየፈጠረ ነው።ሱልጣን አማን የሚያሰማራቸው ጎረምሶች በታላቁ አንዋር መስጊድ ከ2 አስርት ...
06/05/2023

የህገወጡ የአዲስ አበባ መጅሊስ ኃላፊ አቶ ሱልጣን አማን የአዲስ አበባን ሙስሊም ሰላም እየነሳ ሽብር እየፈጠረ ነው።

ሱልጣን አማን የሚያሰማራቸው ጎረምሶች በታላቁ አንዋር መስጊድ ከ2 አስርት አመታት በላይ ከአሱር ሰላት በኋላ በመስጊዱ ማይክ የሚደረገው ዳእዋ ካልቆመ እርምጃ እንወስዳለን ብለው ሰሞኑን አንዋር መስጊድን የሁከት ማእድ ለማድረግ ከርቀት ቦታ እየተጠራሩ በመምጣት ችግር እየፈጠሩ ሁከት ቀስቃሽ ድርጊቶችን እየፈፀሙ ይገኛል።

በነገው እለት ሚያዝያ 28/2015 በጉለሌ ሙስሊም መቃብር መስራች ሸህ ሀሰን በቱል ስም የሚዘጋጀው ዓመታዊ መውሊድ አይከናወንም በማለት በሱልጣን አማን የሚመራው ህገወጡ መጅሊስ በማዘዙ የሸህ ሀሰን በቱል የልጅ ልጆች ያዘጋጁትን ዓመታዊ መውሊድ ፖሊስ አታደርጉም ብሎ እክል እየፈጠረ ያለበት ተጨባጭ ላይ እንገኛለን።

ይህ ሁሉ እየተፈፀመ ያለው የአዲስ አበባን ሙስሊም ወደ ሁከት በማስገባት ህዝበ ሙስሊሙን ለማጋጨት ሆን ተብሎ የተጠነሰሰ ሴራ ነው። መንግስትና ህዝብ የህገወጡ መጅሊስ መሪ አቶ ሱልጣን አማን እና አጋፋሪው አቶ መሀመድ አባተ የሚፈፅሙትን የሽብር ተግባር የማስቆም ግዴታ አለባቸው። ያ ሳይሆን ቀርቶ በታላቁ አንዋር መስጊድ እና በጉለሌ ሙስሊም መቃብር ግጭት ቢነሳ ለሚፈጠረው ችግር አቀነባባሪዎቹ የህገወጡ መጅሊስ አመራሮች እንደሚሆኑ መታወቅ አለብት።

የአዲስ አበባ ሙስሊም ወጣቶች ማሕበር

ዛሬ ሶለዋት እናብዛ ሱረቱል ካህፍ እንቅራ  🌴 ጁመዓ ሙባረክ 🌴
05/05/2023

ዛሬ ሶለዋት እናብዛ ሱረቱል ካህፍ እንቅራ
🌴 ጁመዓ ሙባረክ 🌴

ፒያሳ በሚገኘው በኑር (በኒ) መስጂድ የሚሰጠው በረመዷን ፆም ምክንያት ተቋርጦ የነበረው የአባታችን የክቡር ዶ/ር ተቀዳሚ ሙፍቲ ሀጅ ዑመር እድሪስ የቁርዐን ተፍሲር ፕሮግራም አላህ ካለ ዛሬ ...
05/05/2023

ፒያሳ በሚገኘው በኑር (በኒ) መስጂድ የሚሰጠው በረመዷን ፆም ምክንያት ተቋርጦ የነበረው የአባታችን የክቡር ዶ/ር ተቀዳሚ ሙፍቲ ሀጅ ዑመር እድሪስ የቁርዐን ተፍሲር ፕሮግራም አላህ ካለ ዛሬ ጁመአ ይጀምራል ።

ፕሮግራሙም በሳምንት አራት ቀን ሰኞ፣ ማክሰኛ፣ ጁመዐ እና ቅዳሜ ከመግሪብ እስከ ኢሻ ይካሄዳል። የእውቀት ማእድ በሚፈስበት ቦታ በመገኘት ተጠቃሚ ይሁኑ ።

"እንደ አይን ብሌን የምንሳሳላቸው መስጂዶቻችን በህገወጡ መጅሊስ አይመለከተኝም ባይነት ፈርሰው ሊያልቁ ነው " በሸገር ከተማ ስም ከ11 በላይ መስጂዶች ፈርሰዋል ሙስሊሞች ተፈናቅለዋል ሙስሊሞ...
04/05/2023

"እንደ አይን ብሌን የምንሳሳላቸው መስጂዶቻችን በህገወጡ መጅሊስ አይመለከተኝም ባይነት ፈርሰው ሊያልቁ ነው "

በሸገር ከተማ ስም ከ11 በላይ መስጂዶች ፈርሰዋል ሙስሊሞች ተፈናቅለዋል ሙስሊሞች ቤታቸው በመፍረሱ ምክንያት ለአክፍሮት ሀይላት ተጋልጠዋል ጠንካራ የተባለው ኡማውን አባት አጣ አባት ይሁነው የተባለው ህገወጡ መጅሊስ ልጓሙ ተይዝዋል!!

በክቡር አባታችን ዶ/ር ተቀዳሚ ሙፍቲ ሀጂ ዑመር እድሪስ አስተዳደር ጊዜም ሆነ ከሳቸው በፊት በነበሩት መጅሊሶች መስጂዶችና ሙስሊሞች እንደዚህ ተሸብረው ተንቀው ተዋርደው አያውቁም

በክቡር አባታችን ጊዜ መስጂዶች ሲፈርሱ ቤትኛውም የሀገሪትዋ ክፍል ለምን ብለው ለኡማው ጥብቅና ይቆሙ ነበር ሞጣ ላይ መስጂድ የተቃጠለ ጊዜ ሸይኽ ቃሲም ታጁዲን ሚድያዎችን የተቹበት ሁኔታ በጎንደሩ ክስተት ክቡር አባታችን ከብት ነው ወይ የምትጠብቁት ብለው መንግስትን የተቹበት ሁኔታ ይታወሳል መሻይኾቻችን ስለሀቅ እንጂ ማጎብደድ እነሱ ጋር ከቶ የለም

ጠንካራ አካታች አቃፊ ተብሎ በተጫነብን በህገወጡ መጅሊስ ጊዜ ዑለማዎች ታስረዋል ኡስታዞች በደህንነት ከመስጂድ ተባረዋል የሴት ሙስሊም ተማሪዎች ሂጃብ ተደፍሯል በመላው አዲስ አበባ ዙርያ ሸገር ሲቲ በሚባለው ከተማ እና ኦሮሚያ ላይ ከ10 መስጂዶች በላይ ዶግ አመድ ሆነው አንዳንድ ለሆድ ያደሩ የመጅሊሱ ተከፋይ አክቲቪስቶች እና መሰሎቻቸው መጅሊስን ለመከላከል የሄዱበት ርቀት ስንት ቢከፈላቸው ነው እንዲህ በዲናቸውን የሚሸቅጡት ለወንበራቸው ዋስትና ያደረጉት እንደዚህ ባለ ሁለት ቢላ የሆኑት የሚለው ግራ አጋቢ ነው

ከሁሉ የሚገርመው የአፍራሾቹ የልብ ባልደረባ ናቸው የሚያስብለው ነገር አቶ አህመዲን ጀበል ኢብራሂም ቱፋ ከመንግስት ጋር እየተወያዩ ነው ብሎ አጀንዳ ለማስቀየር የሄደበት መንገድ እራሱን ኡስታዝ ነኝ ከሚል አካል አይደለም ካድሬ እራሱ እንደዚህ አይነት ቲያትር ይሰራል ተብሎ አይጠበቅም

ሌላው የሚገርመው ነገረ ሀጅ ነው ሀጅን ይህ ህገወጥ ቡድን ህልም ሊያደርገው ይመስላል ካላመሰገናችሁ አያያዜ የበረታ ነው የሚለው የጀሊሉ ንግግርና በእጅ ያለ ወርቅ የሚለው የሀገሬ ሰው አባባል እዚህ ጋር ይሰራል ትላንት 98,000 ብር ሆነ ሀጅና አይወጅብም ያለን አካል ዛሬ 465,000 ብር ሲገባ በሂጅራ ባንክ አስገቡ ተበድራችሁ ሀጅ አድርጉ ሲለን ታዘብን የጭንቅላት ድርቀት ይህ ነው ሀጅ በብድር አቅሙ ላልቻለ ሰው መሄድ እኮ ክልክል ነው

ለምሳሌ አንድ ሰው ተበድሮ ሀጅ ቢያደርግና እዛው ቢሞት ሚስትና ልጅ እዳ እየከፈሉ ሊኖሩ ነው ? ትላንት ዘራፊ እያለ ሲጮኽ የነበር ቡድን በዚህ ያህል ዘረፋ ውስጥ ተዘፍቆ ሲታይ ጉድ ያስብላ ሌላው ህዝቡን ጉድ ያሰኝው እስር ቤት የነበሩ ግለሰቦች በአንድ ጀንበር በከተማችን ውድ የሚባሉ አካባቢዎች ላይ ውድ ህንፃ ሲገዙ ስትመለከት ከሰማይ ወርዶላቸው ካልሆነ በስተቀር የዚሁ የዘረፋ ውጤት እንጂ ሌላ ምንም ሊሆን አይችልም

በተጨማሪም #የበደል #ሱሰኞች

በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ወረዳ 10ልዩ ስሙ ብሔረ ፅጌ ኸውፈላህ ተብሎ በሚጠራው መስጅድ ህገ ወጡ የኢብራሂም ቱፋ እና የሱልጣን አማን ቅጥረኞች የመስጅዱ ዋና ኢማም ሸይኽ አብዱልከሪም በየእለቱ ከመግሪብ አስከ ኢሻዕ የተፍሲር የፊቂህ የሰለዋት ፕሮግራማቸውን በማስቆም ከዚህ ቀደም ከሚሰጡት የደረስ አትሰጡም በማለት ኢማሙን በማመናጨቅ ገፍተዋል የአካባቢው መስሊም ማህበረሰብ ለምን ይሆናል ብሎ ህገ ወጥ ከሱልጣን አማን ቅጥረኞች ጋር በተነሳ ፀብ ቀድሞ ከፖሊስ ጋር የተመሳጠረው ህገ ወጥ የህዝብ ተቀባይነት የሌለው የወሀቢያ ቡድን የመስጅድ አባቶች ወጣቶችን አሳስረዋል አስከ አሁኑ ሰዓት ድረስ ችሎት አልቀረቡም

በተጨማሪም በሲኤም ሲ አል ዒምራን መድረሳ ከ 300 በላይ የአፍተር ስኩል ቂርዓትን ኡስታዞቹን በማባረር በእኛ ካልሆነ(በወሀቢያ )አመለካከት መቅራት የተከለከለ ነው በማለት ተማሪዎችን በትነዋል

ፍትህ ለኸውፈላህ መስጅድ ሙስሊም ማህበረሰብ!!!

በዳዮች ረዳት የላቸውም !!
እውነት ያሸንፋል !!

ዛሬ ምሽት ከ2:30_4:00 የትዊተር ዘመቻ ይኖረናል። ተዘጋጅተን እንጠብቅ፣ ትዊተር ያልከፈተ ይክፈት!
21/02/2023

ዛሬ ምሽት ከ2:30_4:00 የትዊተር ዘመቻ ይኖረናል። ተዘጋጅተን እንጠብቅ፣ ትዊተር ያልከፈተ ይክፈት!

አስቸኳይ ማሳስቢያ !! ህገ ወጡ የአዲስ አበባ መጅሊስ በሱልጣን አማንና በመሀመድ አባተ አማካኝነት በየ ክፍለ ከተማው የሚገኙ መስጂዶችን ለማስበጥበጥ እየሰራ ያለዉን ሴራ በአስቸኳይ ያቁም !...
29/10/2022

አስቸኳይ ማሳስቢያ !!

ህገ ወጡ የአዲስ አበባ መጅሊስ በሱልጣን አማንና በመሀመድ አባተ አማካኝነት በየ ክፍለ ከተማው የሚገኙ መስጂዶችን ለማስበጥበጥ እየሰራ ያለዉን ሴራ በአስቸኳይ ያቁም !!

ይህ መስጂዶች ለግለሰቦች እየሸጠ ያለዉ ህገወጥ ቡድን መስጂዶች ለመንጠቅ የሚመጣ ከሆነ ተቋሞቻችን በደምና በአጥንት የተሰሩ መስጂዶቻችንን ለመጠበቅ የትኛውንም መስዕዋትነት ለመክፈል እንዘጋጅ ሁሉም በየ ክፍለ ከተማው ተዘጋጅቶ መስጂዱን እንዲጠብቅ ከወዲሁ እናሳስባለን !!

እጅግ ሩህሩሕ በጣም አዛኝ በሆነዉ በአላህ ስም !

በህገወጥ መንገድ መጅሊስ የተቆጣጠረዉ ፅንፈኛ ቡድን መጅሊሱ በተቆጣጠረበት ወቅት ህገወጥ መሆኑን ለአለም የተገለጠ ቢሆነም የመሻኢኾቻችን የመሪ ዑለሞቻችን ምክር በመከተልና በመቀበል ሀገራችንም ሙስሊሙ ማህበረሰባችንም ካለበት ነባራዊ ሁኔታ በደረሰብን ሁኔታ ብንከፋም ሀገርንና ህዝብን ወደ መጥፎ ትርምስ እንዳያመራ በማሠብ የዑለሞቻችን ሰላማዊ መንገድ በመከተል ህዝባችንን ለማረጋጋት ችለናል

ሆኖም ህዝባችን ዑለሞቻችን ወጣቱ ሰላም ወዳድ ለሀገር ለህዝብ አሳቢ መሆኑ በተቃራኒው እንደፈሪ እየተቆጠረ ህገወጡ መጅሊስ የመጅሊሱ መንበር ከተቆናጠጠ ጀምሮ በተለይ በህገወጡ የአዲስአበባ መጅሊስ በሱልጣን አማንና መሀመድ አባተ አማካይነት የተለያዩ ሳንካዎችን በመፍጠር ሰላም ማግኘት አልቻለም ይኸዉም በተለያዩ ግዜ እየፈፀማቸው ያሉ ህገወጥ ተግባሮች መመልከት ይቻላል

በተለይ በእነዚህ ሰዎች የሚዘወረዉ የአዲስአበባ መጅሊስ ከቅርብ ግዜ ወዲህ ህዝብ ወደ ሚገለገልባቸዉ የህዝብ መገኛ ተቋማት የሆኑትን መስጂዶች ለመውረድ ምንም አይነት ስልጣን ባይኖረውም ሁሉ ነገር ባለበት እንዲቀጥል የተባለ ቢሆንም ያንን በመተላለፍ ሌላ ህገወጥ አንጃ በየክፍለ ከተማዉ በማዘጋጀትና በማደራጀት የክፍለከተማ አመራር ነን በሚል መስጂዶች ለመቆጣጠር እንቅስቃሴ እያደረገ ሁከት ለመፍጠር እየሰራ ይገኛል

እነዚህ በየክፍለ ከተማዉ በሱልጣን አማንና መሀመድ አባተ የተመራዉ ህገወጥ አደረጃጀት በየክፍለ ከተማዉ የሚገኙ የመስጂድ መሬቶችና ሱቆች የህዝበ ሙስሊሙን ንብረቶች ለመሸጥ ሲሆን በቅርቡም ለግለሰቦች የሸጧቸዉ የህዝበ ሙስሊሙ መስጂዶች ለግለሰብ አሳልፈው መስጠታቸው ዋቢ ማሣያ ነዉ ከሰሞኑ እነዚሁ ህገወጡ የአዲስ አበባ መጅሊስ ያሰማራቸዉ ግለሰቦች በተለያዩ ክፍለ ከተሞች ባሉ መስጂዶች እየዞሩ ወደዚህ መስጂድ ተሹመናል ፣ ኢማም ነኝ አስተዳደር ነኝ ወዘተ በሚል ሰላማዊውን ህዝብ ወደ ሁከት ለማስገባት እየሰሩ እንደሚገኙ ደርሰንበታል

በመሆኑም እኛ ሀገራችን ያለችበት ፖለቲካዊ ኢኮኖሚያዊ ዉጥረት በመረዳት ትዕግስት አድርገን ነገሮች ለማረጋጋት ብንሞክርም በስልጣን የሰከረዉ የሱልጣን አማንና የመሀመድ አባተዉ አንጃ ግን ይህንን ለመቀበል የፈለገ አይመስልም በዚህ መሠረት እኛም ከንግዲህ ለሰፊው ሙስሊም ማህበረሰብ እንላለን ከየትኛውም ክፍለከተማ የሚመጣ ህገወጥ ተላላኪ ተቀባይነት የለዉም ህብረተሰባችን እንዳይቀበል እንላለን ሌላዉ ህዝባችን በመስጂዱ ለመጣ መክፈል ያለብን መስዋዕትነት በጋራ እንደምንከፍል ለማሣሠብ እንወዳለን

በመጨረሻም መስጂዶች ወጣቶች በመደራጀት ተቋማችሁን ከነጋዴው ወሓብያ ለመጠበቅ ተደራጁ ተከላከሉ እያልን በዚህ አጋጣሚ በየትኛውም መስጂዶች ለሚነሱ ነፍስ መጥፋቶች ንብረት ዉድመቶች ለሚከሰተዉ ሁከትም ሆነ የሰላም መደፍረስ ተጠያቂው ህገ ወጡ የአዲስ አበባ መጅሊስ ዉስጥ ቁጭ ብለዉ በማዘዝ እያደራጁ ሁከት የሚጎነጉኑቱ ያሉት አካላት ይሆናል መንግሥትም ከወዲሁ ሊፈጠሩ የሚችሉትን ነገሮች አዉቆ እነዚህን በየ ክፍለ ከተማው መስጂድን የሁከት ማዕከል ለማድረግ የሚንቀሳቀሱ የሁከት አለቆችን በፍጥነት ስርዓት እንድያሲዝ ስንል መልእክት እናስተላልፋለን !!

የአዲስ አበባ ሙስሊም ወጣቶች ማሕበር

 === ✿❀ =====*"ያሲናችን የሸይሆቻችን ያሲን ይሁን!" እንበል
20/07/2022


=== ✿❀ =====
*
"ያሲናችን የሸይሆቻችን ያሲን ይሁን!" እንበል

በእስልምናችን ላይ እየተፈፀመ ያለውን የመንግስት ጣልቃ ገብነት ለማጋለጥ ይህን ፎቶ በፖስትም በኮሜንትም ሼር እናድርገው!
20/07/2022

በእስልምናችን ላይ እየተፈፀመ ያለውን የመንግስት ጣልቃ ገብነት ለማጋለጥ ይህን ፎቶ በፖስትም በኮሜንትም ሼር እናድርገው!

ኢትዮጵያዊያን ሁጃጆች በዶላር ማጣት ምክንያት የሐጅ ጉዟቸው እየተጉላላና ጊዜው እየገፋ ነው።ባንኮች አስፈላጊውን የምንዛሬ ትብብር ሊያደርጉ አልቻሉም።አሁንም ችግሩ ሊቀረፍ ይገባዋል!تأخر ح...
15/06/2022

ኢትዮጵያዊያን ሁጃጆች በዶላር ማጣት ምክንያት የሐጅ ጉዟቸው እየተጉላላና ጊዜው እየገፋ ነው።ባንኮች አስፈላጊውን የምንዛሬ ትብብር ሊያደርጉ አልቻሉም።
አሁንም ችግሩ ሊቀረፍ ይገባዋል!

تأخر حج الحجاج الإثيوبيين بسبب نقص الدولارات. لم تكن البنوك قادرة على التعاون النقدي اللازم.
المشكلة لا تزال بحاجة إلى معالجة.

!

!

!

!

ሼር......

ኮምቦልቻ ህዝቡ በነቂስ ወጥቶ ለ ክቡር ዶክተር ተቀዳሚ ሐጅ ዑመር ኢድሪስ ያለውን ድጋፍ በመግለፅ ላይ ይገኛል:: አላሁ አክበር
05/06/2022

ኮምቦልቻ ህዝቡ በነቂስ ወጥቶ ለ ክቡር ዶክተር ተቀዳሚ ሐጅ ዑመር ኢድሪስ ያለውን ድጋፍ በመግለፅ ላይ ይገኛል::
አላሁ አክበር

በተመሳሳይ ሁኔታ ጂማ የታላቁ አባ ጂፋር ሀገር እንዲህ ነቅሎ ወጥቶ ከክቡር ዶክተር ተቀዳሚ ሐጅ ዑመር ኢድሪስ ጎን መሆኑን እያሳዩ ይገኛሉ ። ትውልዱ ነቅቷል! የውሸት ዘመን አብቅቷል!!አሏሁ...
05/06/2022

በተመሳሳይ ሁኔታ ጂማ የታላቁ አባ ጂፋር ሀገር እንዲህ ነቅሎ ወጥቶ ከክቡር ዶክተር ተቀዳሚ ሐጅ ዑመር ኢድሪስ ጎን መሆኑን እያሳዩ ይገኛሉ ። ትውልዱ ነቅቷል! የውሸት ዘመን አብቅቷል!!

አሏሁ አክበር!

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Kufa Multimedia posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Videos

Share