Afar press

Afar press "ጀነት በእናት እግር ስር ናት! "ረሱል ﷺ❤
(1)

𝖢𝖺𝗅𝗐𝖺𝗒 𝗄𝖾𝖾 𝖼𝖾𝗒𝖺𝗁 𝖺𝖽𝖽𝖺𝗍 𝗍𝖺𝗇 𝗊afar u𝗆𝗆𝖺𝗍𝗍𝖺𝗁 𝗑𝗂𝗊𝖺𝖺𝗆𝖺𝗅 𝗑𝗈𝗇𝗀𝗈𝗅𝗈 𝗒𝖺𝗄𝗄𝖾𝖾𝗇𝗂𝗆𝗂𝗁 𝗍akke gicloh gabah agle taallenim kee qokoltaanam ummaan qafar baxal dirki.kinni

04/10/2025
04/10/2025
ከኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የተሰጠ ወቅታዊ መግለጫ!በአማራ ክልል ደቡብ ወሎ ዞን መካነ ሰላም ከተማ መስከረም 23፣2018 ዓ.ል በመስጂድ ኑር በኢሻ ሰላት ወቅት ወደ መስ...
04/10/2025

ከኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የተሰጠ ወቅታዊ መግለጫ!

በአማራ ክልል ደቡብ ወሎ ዞን መካነ ሰላም ከተማ መስከረም 23፣2018 ዓ.ል በመስጂድ ኑር በኢሻ ሰላት ወቅት ወደ መስጂድ የታጠቁ ኃይሎች በመግባት ሃይማኖታዊ ግዴታቸውን በመወጣት ላይ በነበሩ ፦
1 የመስጂድ ዋና ኢማምና የወረዳው መጅሊስ ም/ሰብሳቢ
2 የመስጂድ አመራሮች
3 የመስጂድ ኻዲሞችን አሰቃቂ እና አረመኔያዊ በሆነ ሁኔታ መግደላቸውን የክልሉ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ም/ቤት አረጋግጦልናል።

እነሱም ሸሂድ ሆነዋል አላህ ጀነተል ፍርዶስ ይወፍቃቸው ።

ጠቅላይ ምክርቤቱ የእምነት ተቋማት የተከበሩ ቦታዎች በመሆናቸው ሊጠበቁ እንጅ እንዲህ አይነት አፀያፊ ተግባር የሚፈፀምባቸው መሆን የለባቸውምና ድርጊቱን በፅኑ ያወግዛል።

መላው የሃይማኖት ተቋማትም በእምነት ቦታዎች የሚደረጉ ትንኮሳዎች እና በእምነት ተከታዮች ላይ የተቃጣ መሰል የጅምላ ግድያ ሊያወግዙና ሊያስቆሙ ይገባል።

ህዝበ ሙስሊሙ ይህንን በሀይማኖት ተቋማት ላይ የተቃጣ አደጋ ለመከላከል መረጃ በመለዋወጥ የሃይማኖት ተቋማትንና አካባቢውን እንዲጠብቅ ጠቅላይ ምክርቤቱ ጥሪውን ያስተላልፋል።

ብዝሃ ሀይማኖት ባለባት ሀገራችን በተለያየ እምነት ውስጥ ያሉ ህዝቦች ለዘመናት ያቆዩተን ሰላማዊ እና መልካም መስተጋብር ሆን ተብሎ ለመናድና ማባሪያ ያጣ ቀውስ ውስጥ እንድንገባ የሚፈልጉ አካላት የፈፀሙት መሆኑን ጠቅላይ ምክርቤቱ ይገነዘባል።

በመጨረሻም ሁሉም ሃይማኖት ተቋማትና መሪዎች ይህ ጉዳይ አብሮ የመኖር እሴት እንዳይሸረሽር ብሎም እንዳያጠፋ ድርጊቱን እንድታወግዙ እንዲሁም በፅኑ እንድትቃወሙ እየጠየቅን መንግስትም ይህንን ተግባር በእምነት ቦታዎችና አባቶች ላይ የፈፀሙት ላይ ህጋዊ እርምጃ እንዲወስድ እንጠይቃለን።

መስከረም 24፣2018 ዓ.ል
የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክርቤት

04/10/2025
04/10/2025
የኤርትራ አመራሮች‼️የኤርትራ የማስታወቂያ ሚኒስቴር ዛሬ ጠንከር ያለ መግለጫ አውጥቷል፡፡ከሰሞኑ horn review "ኢትዮጵያ ለኤርትራ የሰጠችውን የሀገርነት እውቅና ማንሳት አለባት፣ኢትዮጵያ...
04/10/2025

የኤርትራ አመራሮች‼️

የኤርትራ የማስታወቂያ ሚኒስቴር ዛሬ ጠንከር ያለ መግለጫ አውጥቷል፡፡

ከሰሞኑ horn review "ኢትዮጵያ ለኤርትራ የሰጠችውን የሀገርነት እውቅና ማንሳት አለባት፣ኢትዮጵያ የኤርትራን የሀገርነት እውቅና ለማንሳት አለምአቀፍ ህጎች እንዳሉ እንዲሁም የሌሎች ሀገራትን ተሞክሮ በማቅረብ" ረዘም ያለ ፅሁፍ ማሰራጨቱን ተከትሎ የኤርትራ አመራሮችን ክፉኛ ያበሳጨ ይመስላል፡፡

ይህን ተከትሎ የኤርትራው ማስታወቂያ ሚኒስቴር አቶ የማነ ገብረመስቀል "ነጻነታችንን ከኢትዮጵያ በስጦታ አልተረከብንም ኢትዮጵያን አሸንፈን ያገኘነው ነው ብለዋል፡፡ የኤርትራ ሉዓላዊነት እውቀና መሰጠት የነበረበት በ1940 ቢሆንም አሜሪካ እና ሌሎች ሀገራት በቀጠናው የነበራቸው ፍላጎት ሌላ በመሆኑ ሳይሳካ ቀርቷል ብለዋል።

ኢትዮጵያ እንደተባለው የምታደርግ ከሆነ እኛም ከ1952 እስከ 1993 እ.ኤ.አ ኢትዮጵያ ለወሰደችብን ሀብትና ንብረት በቢሊየን ዶላር የሚቆጠር ካሳ እንጠይቃለን ብለዋል፡፡ለዚህም የኢራቅ እና ኩዌትን ታሪክ አጣቅሰዋል፡፡

በፅሁፉ የኢትዮጵያ ሰራዊትን ሲዋጉ በተለይ በመንደፈራ፣በምፅዋና በአሰብ እንዴት እንዳሸነፉና ከኢትዮጵያ በኩል ምን ያህል ሰራዊት እንደተበተነ፣እንደቆሰለ፣እንደሞተ እና እንደተማረከ በቁጥር ለማስቀመጥ ሞክረዋል።

በተያያዘ ዜና ከሰሞኑ የኤርትራ ወታደራዊ አመራሮች ከኢትዮጵያ ጋር በተዋጉባቸው በእያንዳንዱ ግንባር በመሄድ የጦርነቱን ሂደትና አሰላለፍ ምን ይመስል እንደነበር ለሰራዊታቸው አመራሮች እና መኮንኖች የጦርነት ትንታኔ ሲሰጡ ታይተዋል።

አዩዘሀበሻ

04/10/2025

SUBHANALLAH

Love
❤️❤️❤️❤️

የደሴ ከተማ  መጅሊስ በመካነ ሰላሙ የፋኖ ጭፍ'ጨፋ ዙሪያ የሐዘን መግለጫ አውጥቷል።  #ኃይማኖታዊጦርነት
04/10/2025

የደሴ ከተማ መጅሊስ በመካነ ሰላሙ የፋኖ ጭፍ'ጨፋ ዙሪያ የሐዘን መግለጫ አውጥቷል።
#ኃይማኖታዊጦርነት

04/10/2025

ሰላት የጀነት ቁልፍ ናት ራሱል(ﷺ)

𝓢𝓪𝓵𝓵𝓪𝓵𝓵𝓪𝓪𝓱𝓾 𝓐𝓵𝓪𝓱𝓲 𝓦𝓪𝓼𝓼𝓪𝓵𝓵𝓪𝓶♡🥰

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Afar press posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Afar press:

Share