Afar press

Afar press Alcamdulillaah
(1)

𝖢𝖺𝗅𝗐𝖺𝗒 𝗄𝖾𝖾 𝖼𝖾𝗒𝖺𝗁 𝖺𝖽𝖽𝖺𝗍 𝗍𝖺𝗇 𝗊afar u𝗆𝗆𝖺𝗍𝗍𝖺𝗁 𝗑𝗂𝗊𝖺𝖺𝗆𝖺𝗅 𝗑𝗈𝗇𝗀𝗈𝗅𝗈 𝗒𝖺𝗄𝗄𝖾𝖾𝗇𝗂𝗆𝗂𝗁 𝗍akke gicloh gabah agle taallenim kee qokoltaanam ummaan qafar baxal dirki.kinni

19/07/2025

ኒውዮርክ ታይምስ ጋዜጣ “በጋዛ የዘር ፍጅት ወንጀል ተባባሪ” ነው የሚል ክስ ቀረበበት

የአሜሪካው ኒውዮርክ ታይምስ ጋዜጣ፤ “በጋዛ የዘር ፍጅት ወንጀል ተባባሪ” ነው የሚል ክስ የቀረበበት በጸሐፊያን ጥምረት ነው። ጥምረቱ ይህን ክስ ያቀረበው የጋዜጣው ዘገባዎች ላይ ምርመራ በማድረግ ለሕዝብ ባሠራጨው ዶሴ አማካኝነት ነው።

በተለያዩ መገናኛ ብዙኃን በሚሠሩ ጸሐፊያን ጥምረት ረቡዕ ዕለት ይፋ ባደረገው ሠነድ እንደሠፈረው፣ ኒውዮርክ ታይምስ ጋዜጣ ሥልታዊ በሆነ መልኩ እስራኤልን የሚደግፍ እና ፍልስጤማውያንን የሚቃወሙ አድልዎአዊ መረጃዎችን ሲያሠራጭ ቆይቷል። ከባልደረቦቹ መካከል ጋዜጠኞች፣ አዘጋጆች እና ሥራ አስፈፃሚዎችን ጨምሮ ከሃያ በላይ ግለሰቦች ከእስራኤል ደጋፊ የሎቢ ቡድኖች ጋር ትስስር አላቸው።

የኒውዮርክ ታይምስ ዘገባዎች በበርካታ የአሁን እና የቀድሞ የጋዜጣው ባልደረቦችና በእስራኤል ባለሥልጣናት አልያም በሠራዊቱ መካከል ባለው ሠፊ ቁሳዊ፣ የገንዘብ እና ርዕዮተ ዓለማዊ ትስስር ሊብራራ እንደሚችል ማሳያዎች የቀረቡበት መሆኑን ሚድል ኢስት ዐይ ዘግቧል።

በዚህም የጋዜጣው አርታዒዎች እንደ “ዘር ማጥፋት” እና “በወረራ የተያዙ ግዛቶች” የመሳሰሉ አገላለጾችን እንዲያስወግዱ እንዲሁም “ፍልስጤም” ብለው ከመጥራት እንዲታቀቡ ለሪፖርተሮች ነግረዋቸዋል።

በዚህ ተግባር ላይ የሚሣተፉ ሠራተኞች ለወንጀል ፈጻሚዎች ለሚሰጡት ሽፋን በግለሰብም ሆነ በመዋቅራዊ አሠራር ደረጃ ከአለቆቻቸው ድርጎ እንደሚሠፈርላቸው ተጋልጧል። ኒውዮርክ ታይምስ ለፈፀመው የሞያ ሥነ ምግባር ጥሰት ተጠያቂ መደረግ አለበት ያለው ጥምረቱ፣ የጋዜጣው አንባቢዎችም የዚህ ወንጀል ተባባሪ ላለመሆን ደንበኝነታቸውን እንዲያቋርጡ ጥሪ አቅርቧል።

ጥምረቱ አክሎም እንደ በርካታ ዋና ዋና ዓለም አቀፍ የዜና አውታሮች ሁሉ ኒውዮርክ ታይምስ በጋዛ ላይ ስለሚሰነዘረው ጥቃት ባቀረበው ዘገባ ላይ ከፍተኛ ክትትል ማድረጉን በመግለፅ፣ በርካታ የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች እና ታዛቢዎች በተመሣሣይ ጋዜጣው ለእስራኤል የጦር ወንጀሎች ሽፋን ይሰጣል ማለታቸውን አስታውሷል። (ሚንበር ቲቪ)

በድረ ገጽ ያንብቡ፦ https://minbertv.com/?p=10581

★ ★ ★
Minber TV | Ethio Sat | 11545 | H | 45000
!

ኢትዮጵያ ፍልስጤማዊያንን ለመቀበል ፈቃደኛነቷን ገልፃለች እስራኤል አገዙኝ ብለ ለአሜሪካ ጥያቄ ማቅረቧ ሀገራችን ኢትዮጵያ ከእስራኤል ጋር ምን ያክል እንደተጣበቀች ማሳያ ነው።ከዚህ ቀደምም እ...
19/07/2025

ኢትዮጵያ ፍልስጤማዊያንን ለመቀበል ፈቃደኛነቷን ገልፃለች

እስራኤል አገዙኝ ብለ ለአሜሪካ ጥያቄ ማቅረቧ ሀገራችን ኢትዮጵያ ከእስራኤል ጋር ምን ያክል እንደተጣበቀች ማሳያ ነው።

ከዚህ ቀደምም እንዳየነው የእስራኤል እና የአብይ አህመዷ ኢትዮጵያ ግንኙነት ከወትሮው የተለየ በአሜሪካ ኢቫንጀሊካኖች የሚቀየስ ሀይማኖታዊ ትንቢትንም መሰረት ያደረገ ለኢትዮጵያ ሙስሊሞችም ኦርቶድክሶችም አስጊ የሆነ ግንኙነት ነው።

የኢትዮጵያ ፕሮቴስታንት ሀይማኖት መሪዎች በየጊዜው እየሄዱ እስራኤል ኢምባሲ የሚፀልዩትን ነገር እንደ ቀላል ማየት ወደፊት ዋጋ ያስከፍላል።

የኢትዮጵያ መንግስት በስንት የጦርነትና የችግር ትብታብ ውስጥ የምትማቅቅን የወላለቀች ሀገር እየመራ የእስራኤል የዘር ማፅዳት Ethnic cleansing ዘመቻ አካል መሆኑ በታሪክ የሚያስወቅሰው ነው። ፍልስጤማዊያን ከእርስታቸውና ከመሬታቸው ተነቅለው እንዲሰደዱ የሚደረግ ዘመቻ አካል የሆነ ሁሉ የታሪክ ተጠያቂ ነው። ፍትህ ሲሰፍንም በምድራዊ ህግም ተጠያቂ ነው።

እርግጥ ነው በኢኮኖሚ ቀውስ ማጣፊያ ያጠረው የኢትዮጵያ መንግስት ገንዘብ አገኛለሁ ብሎ ካሰበ እንኳንስ ፍልስጤማዊያንን መቀበልና እስራኤል ጦር ላክልኝ ብትለው ራሱ ወደ ሗላ የሚል አይመስልም።

የኢትዮጵያ መንግስት ፍልስጤማዊያንን እቀበላለሁ ሲል ከአሜሪካ የቢሊዮን ዶላሮችን እርዳታና የባህር በር እንዲኖረው የሚያደርገውን ጥረት እገዛን ሊሻ ይችላል።

እንግዲህ እስራኤል የኢትዮጵያ መንግስት የማሰድዳቸውን ፍልስጤማዊያን ሊቀበለኝ ዝግጁ ነው ብላለች። ውሸት ከሆነ የኢትዮጵያ መንግስት ማስተባበያ ይሰጥ ነበር። እስካሁን አላደረገውም። ወደፊት ሁሉም ሲጠራ የምናየው ይሆናል።

የሾፌሮች አንደበት የአፋር ህዝብና የመንግስት ስም ለማጥፋት የምትጥር ሰው ነው ። በኦሮሚያ በየቀኑ ሽፌሮችን የሚዘረፈ እና ሽፌረ ተፍኖ ከነቤተሰቡ ሚሊዮን ብር ለሚጠይቁ አሸባር ጉደይ አንድ ...
19/07/2025

የሾፌሮች አንደበት የአፋር ህዝብና የመንግስት ስም ለማጥፋት የምትጥር ሰው ነው ።

በኦሮሚያ በየቀኑ ሽፌሮችን የሚዘረፈ እና ሽፌረ ተፍኖ ከነቤተሰቡ ሚሊዮን ብር ለሚጠይቁ አሸባር ጉደይ አንድ ቀን ለሚን አልዘገብቅም? የኢትዮጵያን ዉስጥ ሰላምና ደህንነት ለማስጠበቅ ከአፋር ክልል የተሻለ ክልል የለም ።

Asiya Kamaal
19/07/2025

Asiya Kamaal

19/07/2025

የእስራኤል የስለላ ድርጅት (ሞሳድ) ኃላፊ ዴቪድ ባርኔያ የጋዛ ነዋሪዎችን ወደ #ኢትዮጵያ ለማዘዋወር አሜሪካ ድጋፍ እንድታደርግ የሀገሪቱን ልዩ መልዕክተኛ መጠየቃቸው ተዘግበ።

 ዛሬ ለፍትህና ለእኩልነት የታገለው፤ የዛ ኩሩ ጥቁር ቀን ነው፡፡ እርቅን ሰብኳል፣ ስለሰላምና ፍትህ፣ ስለሰው ልጆች መብት ታግሏል፣ ታሪክ ሰርቷል፣ የሚነበብና የሚተረክ ህያው ታሪክ ሆኖ አር...
19/07/2025


ዛሬ ለፍትህና ለእኩልነት የታገለው፤ የዛ ኩሩ ጥቁር ቀን ነው፡፡ እርቅን ሰብኳል፣ ስለሰላምና ፍትህ፣ ስለሰው ልጆች መብት ታግሏል፣ ታሪክ ሰርቷል፣ የሚነበብና የሚተረክ ህያው ታሪክ ሆኖ አርፏል፡፡

ኔልሰን ማንዴላ የሰው ዘር ሁሉ በአንድነት የሚኖርባትን አዲሲቷን ደቡብ አፍሪካን በእርቅና በወንድማማችነት መንፈስ የፈጠሩ የሰላምና የእርቅ መልዕክተኛ ናቸው፡፡

የማንዴላ የትግል ጉዞ በደቡብ አፍሪካና በኢትዮጵያ መካከል የማይረሳ ግንኙነት እንዲፈጠር ምክንያት ሆኗል፡፡ በፀረ-ቅኝ አገዛዝና በፀረ አፓርታይድ እንቅስቃሴዎች ላይ የተመሰረተው የሁለቱ ሀገራት ግንኙነት የአሁኗ አፍሪካ እንድትመሰረት ፈር ቀዳጅ ሆኖ አልፏል።

ኔልሰን ማንዴላ ነጮች ላደረሱባቸው ግፍና መከራ ምላሻቸው ጥላቻና በቀል አልነበረም፤ ከሁሉም በላይ ሰው የመሆን ክብርና የመንፈስ ልዕልና ጥልቅ ትርጉም ያለው በይቅርታ ውስጥ እንደሆነ ያምናሉ፡፡

የኢትዮጵያ እና ደቡብ አፍሪካ ግንኙነት መነሻው ስር የሰደደ የነፃነት ቁርጠኝነት ጋር የተቆራኘ ነው። እ.አ.አ በ1962 ኔልሰን ማንዴላ በአዲስ አበባ የመጀመሪያውን ዓለማቀፋዊ ንግግራቸውን አድርገዋል፡፡ እንዲሁም የአፍሪካ ብሄራዊ ኮንግረስ ፓራሚሊተሪ ክንፍ የሆነውን ኡምኮንቶ ዊ ሲዝዌን ለማስጀመር ወታደራዊ ስልጠና ወስደዋል።

ይህ ድጋፍ የሀገራቱን የጋራ ባህላዊና ታሪካዊ ትስስርን አጉልቶታል። የሀገራቱ ግንኙነት ከታሪካዊነቱ ባሻገር እየሰፋ ወደ ሁለገብ አጋርነት አድጓል። እ.ኤ.አ. በ1994 ደቡብ አፍሪካ የተካሄደውን ዴሞክራሲያዊ ምርጫ ተከትሎ ሁለቱ ሀገራት ለመጀመሪያ ጊዜ የሁለትዮሽ ግንኙነታቸውን በይፋ ጀመሩ።

ኔልሰን ማንዴላ የኢትዮጵያ ፓስፖርት መያዝን ጨምሮ ከኢትዮጵያ ጋር የነበራቸው ጥልቅ ግንኙነት የሚያሳይ ነው።

በዚህን ወቅት ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነቱ ሁለቱም ሀገራት በአፍሪካ ህብረት ንቁ ተሳትፎ ከማድረግ ባሻገር ለአህጉራዊ ትብብር ያላቸውን ቁርጠኝነት አጽንኦት ሰጥተውበታል። ኢትዮጵያ በፕሪቶሪያ፣ ደቡብ አፍሪካ በአዲስ አበባ ኤምባሲያቸውን ከፍተዋል።

የኢትዮጵያና የደቡብ አፍሪካ ግንኙነት በዲፕሎማሲያዊና ኢኮኖሚያዊ ዘርፍ እያደገ መጥቷል። በተለይም ሀገራቱ እ.ኤ.አ. በመጋቢት ወር 1998 የንግድና ኢኮኖሚ ትብብራቸውን ለማጠናከር የሚያስችል ስምምነት ተፈራርመዋል።

ከ1998 ጀምሮ እስከ አሁን ባለው ጊዜም ኢትዮጵያ ከ60 በላይ ኩባንያዎች ኢንቨስት እንዲያደርጉ ፈቃድ ሰጥታለች።

ኢትዮጵያ እና ደቡብ አፍሪካ የሁለትዮሽ ግንኙነታቸውን ለማጠናከር ያላቸውን ቁርጠኝነት ማሳየት ችለዋል፡፡ በኢትዮጵያ የነበረውን ግጭት በሰላም እንዲቋጭ የፕሪቶሪያውን የሰላም ድግስ አሰናድታለች፡፡

ኢትዮጵያ ብሪክስን መቀላቀሏ በዓለም አቀፍ ደረጃ እያደረገች ላለው ተፅዕኖና ከደቡብ አፍሪካ እና ከሌሎች አባል ሀገራት ጋር ኢኮኖሚያዊና ስትራቴጂካዊ ትብብር ለማድረግ አዲስ መንገድ መፈጠሩን ያሳያል።

ማንዴላ በጉብዝናቸው ወቅት እንደ ሕግ አዋቂነታቸው ለፍትህና ነጻነት ተጉ፤ በዘጠና አምስት ዓመታቸዉ የምድር ሩጫቸዉን ጨረሱ፡፡ ይሁንና በደቡብ አፍሪካውያን ልብ የዘሩት የፍቅርና የእርቅ ዘር ዛሬም ድረስ ማፍራቱን ቀጥሏል፡፡

#ሀገራዊምክክር #ጋዜጣፕላስ #አፍሪካ

S💖A💖W
19/07/2025

S💖A💖W

19/07/2025

ሶሪያ በድጋሜ ድል አድርጋለች!
የመሪዋ የአመራር ብስለት ትእግስትና አርቆ አሳቢነት ፤ የህዝቧ አንድነትና ቱርክን የመሰለች ጠንካራ አጋሯ ለዳግም ድል አብቅተዋታል። ከተጋረጠባት ዳግም የመገነጣጠል ሴራም ተርፋለች።

በአሜሪካና ቱርክ አደራዳሪነት በተደረገው ስምምነት መሰረትም የሶሪያ ጦር ደቡባዊ ሶሪያን ይቆጣጠራል። በእስራኤል የሚደገፉት የድሩዝ ታጣቂዎችም ትጥቃቸውን ያስረክባሉ። ከከባድ እስከ ቀላል መሳሪያዎች ፈትተው መላው ቀጠናውን የሶሪያ ጦርና የደህንነት ሀይሉ ይቆጣጠራል።

የእስራኤል አላማ የነበረው ደቡባዊ ሶሪያን በዱሩዞች አማካኝነት ገንጥሎ ወደ ግዛቷ መቀላቀልና እነርሱ ሲገነጠሉ ደግሞ የኩርድ ገንጣዮችን ከሰሜንና ምስራቅ በኩል መቀስቀስ ነበር። የእስራኤል ኮማንዶዎች ጭምር ከድሩዝ አማፂያን ጎን ተሰልፈው ሲዋጉም ነበር።

የኩርድ ገንጣዮችን እንደማትታገስ ቱርክ ካስጠነቀቀች በሗላ በዚያ በኩል ምንም አይነት ጦርነት አልተነሳም ነበር። የድሩዞችን ደግሞ የሶሪያ ህዝብ ሆ ብሎ በመነሳት የገንጣይ አስገንጣዩን ተልእኮ ማምከን ችሏል።

አሁን የሶሪያ ጦር ወደ ደቡብ መድረስ የለበትም ስትል የየበረቺው እስራኤልም ሳይሳካላት ቀርቷል። የሶሪያ ጦር ትጥቅ ማስፈታት ጀምሯል።

ሶሪያ ጨካኙን አገዛዝ ካስወገደች በሗላ ሶስት ገንጣዮች ናቸው የተጋረጡባት። አንደኛው አለዊያቶች ሲሆኑ ሁለተኛው ድሩዞች ሶስተኛዎቹ ደግሞ የኩርድ ገንጣዮች ነበሩ። አሁን ሶሪያ የቤት ስራዋን እያጠናቀቀች ይመስላል።

የፈራረሰች ሶሪያን በትጥቅ ትግል የተረከበው የአህመድ አልሸርአ በሳል አመራር ሀገሩን በዚህ ልክ ማትረፍ መቻሉ እጅግ የሚደነቅ ነው።
አህመድ ምን ያክል ለመሪነት እንደተሰራም ማሳያ ነው።
አላህ ከፍታንና መጅድን ለሻም ህዝብ ያጎናፅፈው!
ልቅናውን ይመልስለት።

19/07/2025
19/07/2025

Alcamdulillaahi rabbil qaalamiin

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Afar press posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Afar press:

Share