Afar press

Afar press "ጀነት በእናት እግር ስር ናት! "ረሱል ﷺ❤
(1)

𝖢𝖺𝗅𝗐𝖺𝗒 𝗄𝖾𝖾 𝖼𝖾𝗒𝖺𝗁 𝖺𝖽𝖽𝖺𝗍 𝗍𝖺𝗇 𝗊afar u𝗆𝗆𝖺𝗍𝗍𝖺𝗁 𝗑𝗂𝗊𝖺𝖺𝗆𝖺𝗅 𝗑𝗈𝗇𝗀𝗈𝗅𝗈 𝗒𝖺𝗄𝗄𝖾𝖾𝗇𝗂𝗆𝗂𝗁 𝗍akke gicloh gabah agle taallenim kee qokoltaanam ummaan qafar baxal dirki.kinni

31/10/2025

Tamah Diraaba yaanah yanin
30/10/2025

Tamah Diraaba yaanah yanin

የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር ወታደራዊ ዩኒፎረም ለብሰው የሚያሳየው የቅንብር ምስል በሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) የተፈበረከ ነው

/ኢትዮጵያ ቼክ/- በርካታ የፌስቡክ ገጾች እና አካውንቶች የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አወል አርባ የወታደራዊ ዩኒፎረም ለብሰው በኢትዮ-ኤርትራ ድንበር አቅራቢያ እንደተገኙ የሚያሳይ የቅንብር ምስል እያጋሩ ይገኛሉ።

ይህ በስክሪን ቅጂው የሚታየውን የቅንብር ምስል ካጋሩ መካከልም ከ29 ሺህ በላይ ተከታዮች ያሉት እና ‘Sirnaaf Qabsoofna’ የሚል ስም ያለው የፌስቡክ ገጽ ይገኝበታል።

ይህ ገጽ “ከቀይ ባህር 45 ኪሎሜትር ላይ በቡሬ ግንባር!” የሚል ጽሁፍም ከርዕሰ መስተዳድሩ የቅንብር ምስል ጋር አጋርቷል።

ይሁን እንጂ ኢትዮጵያ ቼክ በምስሉ ላይ ባደረገው ማጣራት ምስሉ በሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) የተፈበረከ እንደሆነ አረጋግጧል።

የምስሉን ትክክለኛነት ለማጣራት የጉግል ምርት የሆነውን ‘SynthID Detector’ የተጠቀምን ሲሆን ይህ መገልገያም ምስሉ በሰው ሰራሽ አስተውሎት የተፈበረከ እንደሆነ አመላክቷል።

በሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) የሚፈበረኩ ምስሎች እና ቪዲዮዎች ከጊዜ ወደ ጊዜ እየረቀቁ እና እየተበራከቱ መጥተዋል። እነዚህን አርተፊሻል ይዘቶች በተለያዩ ማህበራዊ ትስስር ገጾች ሲንሸራሸሩ መመልከትም የተለመደ ሆኗል።

ይሁን እንጂ ይህ ቴክኖሎጂ ሀሰተኛ መረጃን ለሚያሰራጩ ግለሰቦች እና ቡድኖች መልካም አጋጣሚን የፈጠረ ሲሆን በርካታ ሰዎችም ለሀሰተኛ እና አሳሳች መረጃዎች ሲጋለጡ ይስተዋላል።

በመሆኑም አጠራጣሪ እና ታማኝ ባልሆኑ ምንጮች የሚጋሩ መረጃዎችን ከማመናችን እና መልሰን ከማጋራታችን በፊት ተገቢዉን ማጣራት እናድርግ።

ኢትዮጵያ ቼክ

 💯👋👍👋👍👍🥀💐🥀🌹🌹Ten Unknown Facts About  Founding: Tesla was founded in 2003 by engineers Martin Eberhard and Marc Tarpennin...
30/10/2025

💯👋👍👋👍👍🥀💐🥀🌹🌹
Ten Unknown Facts About
Founding: Tesla was founded in 2003 by engineers Martin Eberhard and Marc Tarpenning,
not Elon Musk. Musk joined the company as a major investor and became its public face.
Model Naming Quirk: Tesla’s car lineup follows a playful pattern: Model S, 3, X, and Y.
Elon Musk has said it was meant to spell "S3XY," with the number 3 replacing an "E."
Battery Focus: Tesla's breakthrough isn’t just in electric cars but also in battery technology. Tesla has invested heavily in creating
powerful and long-lasting batteries, not only for cars but also for energy storage solutions like Powerwall.
Autopilot and Full Self-Driving: Tesla’s Autopilot is an advanced driver-assistance system, but it’s not fully autonomous. The
company is working on Full Self-Driving (FSD) software, which could eventually enable true autonomous driving.
Gigafactories: Tesla operates massive manufacturing plants known as Gigafactories, located in the U.S., China, and
Germany. These factories are integral to Tesla’s ability to scale production and reduce costs.
SpaceX Connection: Tesla and SpaceX, both run by Elon Musk, share more than just a CEO. The companies collaborate on technology, and
SpaceX’s Falcon Heavy rocket even launched a Tesla Roadster into space as part of a 2018 test flight.
Sustainable Vision: Tesla's mission is to accelerate the world’s transition to sustainable energy.
In addition to electric cars, the company is a leader in solar power and energy storage solutions.
Over-the-Air Updates: Tesla was the first car manufacturer to allow over-the-air software updates, letting owners
download new features and improvements to their cars without visiting a dealership.
AI and Robots: Tesla’s AI Day event introduced Tesla Bot, a humanoid robot designed to handle dangerous or
repetitive tasks, showcasing Musk’s vision for AI and robotics beyond automobiles.
Environmental Impact: Tesla has reduced the overall carbon f

ዶክተር ደሳለኝ ጫኔ በፓርላማ ያነሷቸው ነጥቦች መካከል ሁሌ የእኔን ጥያቄ በጨለምተኝነት ይመለከቱታል ለምን? የሰላም እና የፀፅታ መናጋት ዋና መንስኤው መንግስት ነው።የህሌና እስረኞችን ለምን...
28/10/2025

ዶክተር ደሳለኝ ጫኔ በፓርላማ ያነሷቸው ነጥቦች መካከል

ሁሌ የእኔን ጥያቄ በጨለምተኝነት ይመለከቱታል ለምን?

የሰላም እና የፀፅታ መናጋት ዋና መንስኤው መንግስት ነው።

የህሌና እስረኞችን ለምን አትፈቱም፣ በህግ ማስከበር ስም እስር ለምን አታቆሙም?

መንግስት 10 ድስት ጥዶ አንዱንም አላማሰለውም ፣ ለምን ትኩረት ሰተው የውስጥ ችግሮቻችን አይፈቱም?

በጦርነት ስንት ትውልድ እየበላችሁ ትኖራላችሁ ?

"የኢትዮጵያን ኢኮኖሚያዊ እድገት ለማወቅ አይን፣ አፍንጫ እና ጆሯችሁን ተጠቀሙ" ጠቅላይ ሚኒስትሩ
28/10/2025

"የኢትዮጵያን ኢኮኖሚያዊ እድገት ለማወቅ አይን፣ አፍንጫ እና ጆሯችሁን ተጠቀሙ" ጠቅላይ ሚኒስትሩ

28/10/2025

ቀይ ባህርን በተመለከተ

የቀይ ባህር ጉዳይ ህጋዊ፣ ታሪካዊ፣ መልከዓ ምድራዊና ኢኮኖሚያዊ ጥያቄ ነው ብለን እናምናለን። ይህንን በተረጋጋ መንገድ ማየት ያስፈልጋል። ኢትዮጵያን የቀይ ባህር የማጣት ውሳኔ ማን ወሰነ ብለን ስንፈልግ ተቋማት አልገቡበትም። ይህን የሚያህል የህልውና ጉዳይ ማን እንደወሰነ መጠየቅ ተገቢ ነው። ኢትዮጵያ ተዘግቶባት መኖር አትችልም። ለጎረቤቶቻችን መናገር የምንፈልገው ኢትዮጵያ ስታደግ ለቀጣናውም ልማት ምንጭ ትሆናለች። የምንፈልገው በትብብር ማደግ ነው።

#የጠሚሩምላሾች

"ከቅዳሜ እለት ጀምሮ ከኤርትራ ጋር ውጊያ ገጥመናል  የቀይ ባህር አፋር ዴሞክራሲያዊ ድርጅት አዲስ ኃይል አሰልጥኖ ማስመረቁን ይፋ አድርጓል፡፡በኢትዮጵያ አፋር ክልል የሚንቀሳቀሰው የሻዕቢያ ...
23/10/2025

"ከቅዳሜ እለት ጀምሮ ከኤርትራ ጋር ውጊያ ገጥመናል

የቀይ ባህር አፋር ዴሞክራሲያዊ ድርጅት አዲስ ኃይል አሰልጥኖ ማስመረቁን ይፋ አድርጓል፡፡

በኢትዮጵያ አፋር ክልል የሚንቀሳቀሰው የሻዕቢያ ተቀናቃኝ የቀይ ባህር አፋር ዴሞክራሲያዊ ድርጅት አዲስ ኃይል አሰልጥኖ ማስመረቁን ይፋ አድርጓል፡፡ ሻብያን ለመውጋት የተደራጀው ኃይል መመረቁ የተሰማው ጌታቸው ረዳ እና አምባሳደር ሬድዋን በቡሬ ግንባር በተገኙበት ወቅት ነው፡፡ ከፍተኛ ባለሥልጣናትና ጀነራሎች በቡሬ ግንባር ቅኝነት ባደረጉበት አጋጣሚ፣ የቀይ ባህር አፍር ድርጅት ወታደራዊ አዛዥ ስለ አዲሱ ጦራቸው ሰምሪት መግለጫ አውጥተዋል፡፡ ታጣቂ ኃይሉ ለተከታታይ ሦስት ወራት ያሰለጠናቸውን ኃይል ለስምሪት ዝግጁ ሆኗል ብሏል፡፡ ድርጅቱ ባወጣው መግለጫ የኢሳያስ አፈወርቂን አስተዳደር ለመውጋት የሰለጠነው ኃይል እሰከ መሀል ሀገር ዘለቆ በመግባት ጥቃት መፈጸም የሚችል እንደሆነ ተናግሯል፡፡

የድርጅቱ ወታደራዊ አቅም የፊት ለፊት ውጊያ፣ የሽምቅ ውጊያና ልዩ ኦፕሬሽን መፈጸም እንዲችል ተደርጎ ሰልጥኗል የተባለ ሲሆን፤ በኢሳያስ አፈወርቂ አገዛዝ ተቀምቷል ያለውን የቀይ ባህር አፋር መሬትን ነጻ አወጣለሁ ብሏል፡፡ ወታደራዊ ብቁነቱ ተረጋግጦ ተመርቋል የተባለው የድርጅቱ ኃይል ሻብያን በኃይል ለመገርሰስ የሚያስችል ቁመና አለው ተብሏል፡፡

ድርጅቱ በጀመረው የትጥቅ ትግል የቀይ ባህር አፋር ህዝብ መብት ለማስጠበቅ እና ሙሉ በሙሉ የራስን እድል በራስ የመወሰን መብት ለማረጋገጥ ቁርጠኛ መሆኑን ገልጿል፡፡ የድርጅቱ የራስን በራስ የመወሰን ትግል አስፈላጊ ከሆነ እሰከመገንጠል ይዘልቃል የተባለ ሲሆን፣ ከኢትዮጵያ አፋር ወንድም ሕዝብ ጋርም እተባበራለሁ ብሏል፡፡

የኢትዮጵያ አፋር ሕዝብና መንግሥት የቀይ ባህ አፋርን ሕዝብ ከመፈናቀልና ብሔር ተኮር ጥቃት ለመከላከል ድጋፍ አድርጓል ያለም ሲሆን፤ የአፋር ክልል መንግሥት እና ሕዝብ አድርጎልኛል ላለው ድጋፍ በይፋ አመስግኗል፡፡ ወደፊትም በትብብር መሥራቱን እንደሚቀጥል ጠቁሟል፡፡

የድርጅቱ ሊቀመንበር ኢብራሂም ሀሩን ቀጣዩ ምዕራፍ የድርጅቱን የባህር ኃይል ማቋቋም ነው ብለዋል፡፡ ድርጅቱ አሁን ባለው የፖለቲካ እና ወታደራዊ መስፈርቶች መሰረት የሰለጠነ እና የታጠቀ የባህር ኃይል ለማቋቋም እየሰራ መሆኑን አረጋግጠዋል። ሊቀመንበሩ ለመገልበጥ የሚታገሉትን ሻብያን ከቀይ ባህር አፋር አልፎ ለጎረቤት ሀገራትም ጠንቅ ነው ሲሊ ከሰውታል፡፡ ኢብራሂም የኢሳየስ አስተዳደር ለኤርትራ ህዝብ ብቻ ሳይሆን ለጎረቤት መንግስታት፣ ለቀይ ባህር እና በአፍሪካ ቀንድ ስጋት ሆኗል ሲሉ ነው የወነጀሉት፡፡

የጎረቤት ሀገራት እና የአለም አቀፉ ማኅበረሰብ ይህንን ስጋት ተገንዝበው የኢሳያስ አፈርቂን አስዳደር ለመገርስ የሚታጉ የኤርትራ ኃይሎች እንዲደግፉ ጠይቀዋል። ድርጅቱ የኤርትራን ጭቆና አገዛዝ በጋራ ለመታገል የሚያስችል ግንባር ለመፍጠር ለኤርትራ የፖለቲካ ኃይሎች ጥሪ አቅርቧል፡፡

23/10/2025
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ፖለቲካ ፓርቲዎች የክርክር የተግባር ልምምድ የሚያደርጉበትን መድረክ ማካሄድ ጀመረየኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ፖለቲካ ፓርቲዎች የምርጫ ጊዜ ክርክር የተግባር...
23/10/2025

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ፖለቲካ ፓርቲዎች የክርክር የተግባር ልምምድ የሚያደርጉበትን መድረክ ማካሄድ ጀመረ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ፖለቲካ ፓርቲዎች የምርጫ ጊዜ ክርክር የተግባር ልምምድ የሚያደርጉበትን መድረክ ጥቅምት 11 ቀን 2018 ዓ.ም ማካሄድ ጀመረ። ቦርዱ በ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ረቂቅ የጊዜ ሠሌዳውን አስመልክቶ፤ ከፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር በተወያየ ማግሥት የተጀመረውንና እስከ ጥቅምት 14 ቀን 2018 ዓ.ም የሚቆየውን መድረክ በንግግር የከፈቱት የቦርዱ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ ሲሆኑ፤ በንግግራቸውም የክርክር ልምምዱ የፖለቲካ ፓርቲዎች በ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ፖሊሲዎቻቸውንና ፕሮግራማቸውን ለሕዝብ የሚያቀርቡበትን ሥልት እንዲያዳብሩበት፤ ቦርዱ በቀጣይ በሚያወጣው ፕሮግራምም የፖለቲካ ፓርቲዎቹ ያላቸውን ፕሮግራምና ፖሊሲ ለመራጩ ሕዝብ በመገናኛ ብዙኃን አማራጮች በይፋ ከማቅረባቸው በፊት ልምድ የሚያዳብሩበት ጠቃሚ መድረክ እንደሚሆን ያላቸውን ዕምነት ገልጸዋል።

ቦርዱ ቀደም ሲል ፓርቲዎቹ የምርጫ ጊዜ ክርክር ክኅሎታቸውን ሊያዳብሩ የሚያስችል ሥልጠና የሰጠ ሲሆን፤ በዚኽኛው መድረክም ፓርቲዎቹ ቀደም ሲል በወሰዱት የክኅሎት ማዳበሪያ ሥልጠና ያገኙትን ዕውቀት ተጠቅመው በቀረቡት 16 ርዕሰ ጉዳዮች ላይ በመከራከር የፓርቲዎቻቸውን ዐቋም የሚያንጸባረቁ ሲሆን፤ በየርዕሰ ጉዳዮቹ ላይም ከሁለት እስከ አራት ፓርቲዎች በመድረክ ላይ ወጥተው መከራከሪያቸውን በማቅረብ የመድረኩ ተሣታፊ በሆኑ ተመልካች ፓርቲዎች ሚሥጥራዊ ድምፅ መስጠት እየተካሄደ አሸናፊው እንዲለይ የሚደረግበት መድረክ ነው።

ቦርዱ በቀደመው ዓመት የፖለቲካ ፓርቲዎች በሀገራቸው የዲሞክራሲ ግንባታ ላይ የተሻለ አስተዋፅዖ እንዲኖራቸው ለማስቻል የተለያዩ የዐቅም ግንባታ እና የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠናዎችን መስጠቱ ይታወቃል።

23/10/2025

Riformi caatih Addal yakkeh yan bas

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Afar press posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Afar press:

Share