
26/03/2025
ኢትዮጵያውያንና አፍሪካውያን የሚሳተፉበት ‹‹ግራንድ አፍሪካ ራን›› ስያሜውን በሚመለከተ አስጠነቀቀ
በአሜሪካና በሌሎችም ዓለማት የሚገኙ ኢትዮጵያውያንና አፍሪካውያንን የሚያሳትፈውና መቀመጫውን በአሜሪካ ዋሽንግተን ዲሲ ያደረገው "ግራንድ አፍሪካ ራን›› ስያሜውን (ስሙን) ሌላ ድርጀት (ተቋም) መጠቀም እንደማይችል አስታወቀ፡፡
ተቋሙ እ.ኤ.አ በመጪው ጥቅምት 11 ቀን 2025 በአሜሪካ ዋሽንግተን ዲሲ በሚያካሂደው የአምስት ኪሎ ሜትር የሩጫ ውድድር ላይ ከሚሳተፉ ተወዳዳሪዎች መካከል በዕጣ የ2025 ቶዮታ ኮሮላ መኪና ለመሸለም ዝግጅት ማጠናቀቁን ተናግሯል፡፡
የሩጫው ዋና አዘጋጅ ጋሻው አብዛ (ዶ/ር) ውድድሩን አስመልክቶ ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ ውድድሩ ዘንድሮ ለሰባተኛ ጊዜ በአሜሪካ ዋንሽንግተን ዲሲ የሚካሄድ ሲሆን፣ መርሐ ግብሩ በዋናነት በአሜሪካና በሌሎችም ዓለማት የሚኖሩ ትውልደ ኢትዮጵያውያን ዲያስፖራዎችን ጨምሮ አፍሪካውያንን የሚያሳትፍ ነው፡፡ ፕሮግራሙ ከአንድ ቀን ሩጫነት የበለጠ ፋይዳ እንዳለው ያከሉት ዋና አዘጋጁ፣ በተለያየ የሕይወት አጋጣሚ የማይገናኙ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵውያንን በማቀራረብ ረገድም ጉልህ ድርሻ እየተወጣ ስለመሆኑ ጭምር ተናግረዋል፡፡
ላለፉት ስድስት ዓመታት በዋሽንግተን ዲሲ ሲካሂድ የቆየው ግራንድ አፍሪካ ራን ከሩጫም በላይ ሆኖ ለኢትዮጵያውያን የዲያስፖራ ማኅበረሰብ የመገኛኛ ድልድይ በመሆን፣ እንዲሁም የበጎ አድራጎት ድርጅቶች የገንዘብ ማሰባሰቢያ መድረክ ሆኖ እያገለገለ መሆኑን ታሳቢ በማድረግ፣ ‹‹ቅድሚያ ለማኅበረሰብ›› በሚል መርሐ ግብር የዝግጅቱ አጋር ሆኖ ላለፉት አራት ዓመታት የቆየው አሌክሳንደሪያ ቶዮታ ኩባንያ፣ የ2025 ቶዮታ ኮሮላ ለአንድ ዕድለኛ ተሳታፊ በሽልማት መልክየሚያበረክት ስለመሆኑ ጭምር የውድድሩ ዋና አዘጋጅ ጋሻው (ዶ/ር) ተናግረዋል፡፡
በሌላ በኩል ግራንድ አፍሪካ ራን በሚል ተቀራራቢ ስያሜ ሩጫ ለማዘጋጀት ያሰቡ ተቋማት እንዳሉ ያስታወሱት የውድድሩ ዋና አዘጋጅ ጋሻው (ዶ/ር)፣ ስሙን መጠቀም በሕግ እንደሚያስጠይቅ ተናግረዋል፡፡ በቅርቡ ‹‹ግራንድ ኢትዮ አፍሪካ ራን›› በሚል ስያሜ በኢትዮጵያና በሌሎችም የአፍሪካ አገሮች፣ እንዲሁም ከተባበሩት ዓረብ ኢምሬቶች ጋርበመተባበር የሩጫ ውድድር እንደሚዘጋጅ ዓርብ የካቲት 28 ቀን 2017 ዓ.ም. በስካይ ላይት ሆቴል መግለጫ መሰጠቱ ይታወሳል፡፡
ከግራንድ አፍሪካ ራን የሚለውን ስም በዓለም አቀፍ ደረጃ ለመጠቀም ሕጋዊ ምዝገባና ፈቃድ ያለው