ልዩ ገጽ LIYU PAGE

ልዩ ገጽ  LIYU PAGE በልዮ መልቲሚዲያ እና ኢቨንት አማካኝነት በማህበራዊ ትስስር ድረገጾች በልዮነት ለኢትዮጵያውያን የቀረበ ቀዳሚ የመረጃ ምንጭ ነው።

ኢትዮጵያውያንና አፍሪካውያን የሚሳተፉበት ‹‹ግራንድ አፍሪካ ራን›› ስያሜውን በሚመለከተ አስጠነቀቀበአሜሪካና በሌሎችም ዓለማት የሚገኙ ኢትዮጵያውያንና አፍሪካውያንን የሚያሳትፈውና መቀመጫውን ...
26/03/2025

ኢትዮጵያውያንና አፍሪካውያን የሚሳተፉበት ‹‹ግራንድ አፍሪካ ራን›› ስያሜውን በሚመለከተ አስጠነቀቀ

በአሜሪካና በሌሎችም ዓለማት የሚገኙ ኢትዮጵያውያንና አፍሪካውያንን የሚያሳትፈውና መቀመጫውን በአሜሪካ ዋሽንግተን ዲሲ ያደረገው "ግራንድ አፍሪካ ራን›› ስያሜውን (ስሙን) ሌላ ድርጀት (ተቋም) መጠቀም እንደማይችል አስታወቀ፡፡

ተቋሙ እ.ኤ.አ በመጪው ጥቅምት 11 ቀን 2025 በአሜሪካ ዋሽንግተን ዲሲ በሚያካሂደው የአምስት ኪሎ ሜትር የሩጫ ውድድር ላይ ከሚሳተፉ ተወዳዳሪዎች መካከል በዕጣ የ2025 ቶዮታ ኮሮላ መኪና ለመሸለም ዝግጅት ማጠናቀቁን ተናግሯል፡፡

የሩጫው ዋና አዘጋጅ ጋሻው አብዛ (ዶ/ር) ውድድሩን አስመልክቶ ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ ውድድሩ ዘንድሮ ለሰባተኛ ጊዜ በአሜሪካ ዋንሽንግተን ዲሲ የሚካሄድ ሲሆን፣ መርሐ ግብሩ በዋናነት በአሜሪካና በሌሎችም ዓለማት የሚኖሩ ትውልደ ኢትዮጵያውያን ዲያስፖራዎችን ጨምሮ አፍሪካውያንን የሚያሳትፍ ነው፡፡ ፕሮግራሙ ከአንድ ቀን ሩጫነት የበለጠ ፋይዳ እንዳለው ያከሉት ዋና አዘጋጁ፣ በተለያየ የሕይወት አጋጣሚ የማይገናኙ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵውያንን በማቀራረብ ረገድም ጉልህ ድርሻ እየተወጣ ስለመሆኑ ጭምር ተናግረዋል፡፡

ላለፉት ስድስት ዓመታት በዋሽንግተን ዲሲ ሲካሂድ የቆየው ግራንድ አፍሪካ ራን ከሩጫም በላይ ሆኖ ለኢትዮጵያውያን የዲያስፖራ ማኅበረሰብ የመገኛኛ ድልድይ በመሆን፣ እንዲሁም የበጎ አድራጎት ድርጅቶች የገንዘብ ማሰባሰቢያ መድረክ ሆኖ እያገለገለ መሆኑን ታሳቢ በማድረግ፣ ‹‹ቅድሚያ ለማኅበረሰብ›› በሚል መርሐ ግብር የዝግጅቱ አጋር ሆኖ ላለፉት አራት ዓመታት የቆየው አሌክሳንደሪያ ቶዮታ ኩባንያ፣ የ2025 ቶዮታ ኮሮላ ለአንድ ዕድለኛ ተሳታፊ በሽልማት መልክየሚያበረክት ስለመሆኑ ጭምር የውድድሩ ዋና አዘጋጅ ጋሻው (ዶ/ር) ተናግረዋል፡፡

በሌላ በኩል ግራንድ አፍሪካ ራን በሚል ተቀራራቢ ስያሜ ሩጫ ለማዘጋጀት ያሰቡ ተቋማት እንዳሉ ያስታወሱት የውድድሩ ዋና አዘጋጅ ጋሻው (ዶ/ር)፣ ስሙን መጠቀም በሕግ እንደሚያስጠይቅ ተናግረዋል፡፡ በቅርቡ ‹‹ግራንድ ኢትዮ አፍሪካ ራን›› በሚል ስያሜ በኢትዮጵያና በሌሎችም የአፍሪካ አገሮች፣ እንዲሁም ከተባበሩት ዓረብ ኢምሬቶች ጋርበመተባበር የሩጫ ውድድር እንደሚዘጋጅ ዓርብ የካቲት 28 ቀን 2017 ዓ.ም. በስካይ ላይት ሆቴል መግለጫ መሰጠቱ ይታወሳል፡፡

ከግራንድ አፍሪካ ራን የሚለውን ስም በዓለም አቀፍ ደረጃ ለመጠቀም ሕጋዊ ምዝገባና ፈቃድ ያለው

3ኛው የአፍሪካን ሮቦቲክስ ሻምፒየንሺፕ ውድድር ከሐሙስ ጀምሮ በሳይንስ ሙዚየም ይካሄዳል•  አሸናፊዎች በአሜሪካ በሚካሄደው ዓለማአቀፍ የሮቦቲክስ ውድድር ላይ ይሳተፋሉ 3ኛው ዙር የአፍሪካን ...
08/03/2025

3ኛው የአፍሪካን ሮቦቲክስ ሻምፒየንሺፕ ውድድር
ከሐሙስ ጀምሮ በሳይንስ ሙዚየም ይካሄዳል

• አሸናፊዎች በአሜሪካ በሚካሄደው ዓለማአቀፍ
የሮቦቲክስ ውድድር ላይ ይሳተፋሉ

3ኛው ዙር የአፍሪካን ሮቦቲክስ ሻምፒየንሺፕ ውድድር ከመጋቢት 4 እስከ 6 ቀን 2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ ሳይንስ ሙዚየም እንደሚካሄድ ኢትዮ ሮቦቲክስ አስታወቀ፡፡

ከፊታችን ሐሙስ ጀምሮ ለሦስት ተከታታይ ቀናት በሚካሄደው በዚህ ውድድር የመጀመሪያ ደረጃ፤ የሁለተኛ ደረጃ፣ የኮሌጅና የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች እንደሚወዳደሩ የተገለጸ ሲሆን፤ ውድድሩ በዲዛይኒንግ፤ በኢንጂነሪንግና በአውቶነመስ ኮዲንግ ላይ እንደሚያተኩር ታውቋል፡፡

በውድድሩ አሸናፊ የሚሆኑ ተማሪዎች የዋንጫ ሽልማቶችን የሚያገኙ ሲሆን፤ በኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር የተፈረመ ሰርተፊኬትም ይበረከትላቸዋል ተብሏል፡፡

በዚህ ውድድር በአዲስ አበባ የሚኖሩ አፍሪካውያንም የሚካፈሉ ሲሆን፤ ለፍጻሜ የሚበቁ ተማሪዎች አገራቸውን ወክለው በአሜሪካ በሚካሄደው ዓለምአቀፍ የሮቦቲክስ ውድድር ላይ እንደሚሳተፉ የኢትዮ ሮቦቲክስ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ሰናይክረም መኮንን ገልጸዋል።

ላለፉት 15 ዓመታት የነገዎቹን ኢንጂነሮችና ፕሮግራመሮች የመፍጠር ራዕይ ሰንቆ ሲሰራ የቆየው ማዕከሉ፤ ኢትዮጵያውያን ታዳጊዎች በዓለምአቀፍ የሮቦቲክስ ውድድሮች ላይ እንዲሳተፉና ዓለምአቀፍ ልምድና ተሞክሮ እንዲቀምሱ በማድረግ ረገድ ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል፡፡

ባለፈው ዓመት በቻይና ሻንጋይ በተካሄደው ኢንጆይ ኤአይ ዓለምአቀፍ የሮቦቲክስ ውድድር ላይ 21 ኢትዮጵያውያን ታዳጊዎች ሀገራቸውን ወክለው የተወዳደሩ ሲሆን፤ በውድድሩ ከተሳተፉ 27 የዓለም አገራት 3ኛ ደረጃን ይዘው ማጠናቀቃቸው ይታወሳል፡፡

በተመሳሳይ አምና በአሜሪካ በተካሄደ የዓለም ሮቦቲክስ ሻምፒዮን የተሳተፉ ታዳጊዎች አስደማሚ ውጤት ያስመዘገቡ ሲሆን፤ ይህን ተከትሎም የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር "ታዳጊዎቹ ኢትዮጵያን በዓለም መድረክ ማስጠራት ጀምረዋል" ሲል ዕውቅና ሰጥቷል፡፡

የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ዕውቅናና አድናቆት በመስጠት ብቻ ግን አልተወሰነም፡፡ ኢትዮ ሮቦቲክስ የጀመረውን ታዳጊዎችን በቴክኖሎጂ የማሰልጠንና የማብቃት ሥራን አጠናክሮ እንዲቀጥል ሙሉ ድጋፍ እያደረገ እንደሚገኝ ለማወቅ ተችሏል፡፡

የኢትዮ ሮቦቲክስ መሥራችና ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ሰናይክረም መኮንን እንደሚሉት፤ ማዕከላቸው ታዳጊዎችን ከማሰልጠንና በዓለምአቀፍ ውድድሮች እንዲሳተፉ ዕድሎችን ከማመቻቸት የሚዘልቅ ራዕይን ሰንቋል፡፡

እንደ ቻይናና ሌሎች ያደጉ አገራት ሮቦቲክስ በመደበኛ የትምህርት ሥርዓት ውስጥ እንዲካተት ፍላጎት እንዳላቸው የተናገሩት ዋና ሥራ አስፈጻሚው፤ ለዚያም ዛሬ በትጋት እየሰራን፤ እየታተርን እንገኛለን ብለዋል፡፡

"መስራት ተቸግረናል" ኢትዮ ተሸከርካሪዎች አስመጪ ባለቤቶች ማህበር የጥራት ደረጃ ሰርተፍኬት ምክንያት ሥራ መስራት መቸገራቸውን ለንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር  በደብዳቤ አሳውቀዋል። ኢት...
21/02/2025

"መስራት ተቸግረናል"

ኢትዮ ተሸከርካሪዎች አስመጪ ባለቤቶች ማህበር የጥራት ደረጃ ሰርተፍኬት ምክንያት ሥራ መስራት መቸገራቸውን ለንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር በደብዳቤ አሳውቀዋል።

ኢትዮ ተሸከርካሪዎች አስመጪ ባለቤቶች ማህበር ባደረገው ወቅታዊ ስብሰባ ላይ እንደተነሳው መንግስት እንደ አዲስ ባስቀመጠው የኤሌክትሪክ መኪኖች የጥራት ደረጃ ሰርተፍኬት ምክንያት በአግባቡ መሥራት አልቻልንም። እንደከዚህ ቀደሙ የማህበራችን አባሎች ስራቸውን በቀልጣፋነት ለማከናወን ከመቸገርም በላይ እንደሀገር ጉምሩክ ከመኪና አስመጪዎች የሚጠብቀውን ቀረጥና ታክስ ለማሳካት እና ለመክፈል አዳጋች ሆኖብናል ብለዋል፡፡

በተጨማሪም አባሎቻችን በአንድ ተሽከርካሪ እስከ 200 ዶላር ወጪ እያወጡ ሲሆን በተለይም አገር ውስጥ ለገቡትም እንዲሁም በቅርቡ ለሚያስገቡትም መኪኖች ይህን ክፍያ ለመክፈል የተገደዱ ሲሆን በተለይም ይህንን ሰርተፍኬት ለማሰራት ከሚፈጀው ወራት አንጻር አለአግባብ ለሆነ ከፍተኛ የዲሜሬጅ ወጪ መጋለጣቸውን አንስተዋል፡፡

እነዚህም ወጪዎች በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ የውጭ ምንዛሪ መሆናቸው እንደ ሀገር የሚፈጥረውንም ጫና ከግምት ውስጥ ማስገባት እንደሚያስፈልግ አንስተዋል።

ኢትዮ ተሸከርካሪዎች አስመጪ ባለቤቶች ማህበር ይህ አካሄድ አገርን እንደሚጎዳ እና ቀረጥና ታክስ መሰብሰብ ላይ ትልቅ ችግር ከመፍጠሩም ባሻገር አስመጪዎች ከሰርተፍኬቱ ጋር በተያያዘ የሚያወጡት ወጪ በገቢዎች እንደወጪ ታስቦ አለመያዙ ሌላኛው ማነቆ ሆኖብናል ሲሉ አስታውቀዋል፡፡

አያይዘውም ይህ ሁሉ ዶላር ለጎረቤት አገር መከፈሉ አግባብነት እንደሌለው ተገንዝቦ ሚንስቴር መስሪያ ቤቱ አስፈላጊውን መፍትሄ እንዲያደርግልን እንዲሁም ችግራችንን እንዲፈታልን ዘንድ በአክብሮት እንጠይቃለን ሲሉ (ግልባጭ * ለገንዘብ ሚንስቴር * ለጉምሩክ ኮሚሽን) በማድረግ አስታውቀዋል፡፡

ኢትዮ ተሸከርካሪዎች አስመጪ ባለቤቶች ማህበር በአቤቱታው እንዳስታወቀው የማህበራችን አባሎች አብዛኛዎቹ ሀገራዊ ግዴታቸውን በመወጣት በከፍተኛ ደረጃ ግብር ከፋይ በተደጋጋሚ ተሸላሚ መሆናቸው አውስቷል፡፡

ሐመረ ኖህ ስፔሻሊቲ የጥርስ ህክምና ክሊኒክ በአዲስ አበባ ተከፈተሐመረ ኖህ ስፔሻሊቲ የጥርስ ህክምና ክሊኒክ ዛሬ የካቲት 9 ቀን 2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ መገናኛ አካባቢ በሚገኘው ራሄም ...
16/02/2025

ሐመረ ኖህ ስፔሻሊቲ የጥርስ ህክምና ክሊኒክ በአዲስ አበባ ተከፈተ

ሐመረ ኖህ ስፔሻሊቲ የጥርስ ህክምና ክሊኒክ ዛሬ የካቲት 9 ቀን 2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ መገናኛ አካባቢ በሚገኘው ራሄም ህንፃ ላይ በይፋ ተመርቆ ስራውን መጀመሩን አሳወቀ።

በህክምና ሙያተኞች አማካኝነት የተመሠረተው ክሊኒኩ አቅም የሌላቸውን እና በተለያዩ ሁኔታዎች የጤና እንክብካቤ ማግኘት የማይችሉትን ዜጎች በማገልገል ላይ ትኩረት አድርጎ የተቋቋመ መሆኑን በምረቃው መርሐግብር ላይ ተገልጿል።

ዶክተር ሳሙኤል ሰይፉ የሐመረ ኖህ ስፔሻሊቲ የጥርስ ህክምና ክሊኒክ መስራች እና የአፍ ውስጥ ፣የፊት እና የመንጋጋ ቀዶ ህክምና ስፔሻሊስት ፤እንደገለፁት ክሊኒኩ ዘመናዊ የህክምና መሳሪያዎችን ያሟላ ሲሆን ለህብረተሰቡም ተደራሽ የሆነ አገልግሎት ለመስጠት ዝግጁ መሆኑን እና በቀጣይም በዘርፉ የልህቀት ማዕከል ለማድረግ እንደሚሰራ ገልጸዋል።

በሌላ በኩል የክሊኒኩ መስራች ከሆኑት መካከል አንዱ የሆኑት ዶክተር መለሰ ብዙአየሁ ደግሞ እንደገለፁት
ክሊኒኩ በዘመናዊ መሳሪያዎች መደራጀቱንና በየወሩ በ16ኛው ቀን ነጻ የህክምና አገልግሎት እንዲሁም 50 በመቶ ቅናሽ እንደሚደረግ ገልጸዋል። በተጨማሪም የክሊኒኩ መከፈትን አስመልክቶ ከነገ የካቲት 10 እስከ የካቲት 16 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ ወደክሊኒኩ ለሚመጡ ታካሚዎች በሙሉ የ50 በመቶ ቅናሽ እንደሚደረግ ጨምረው ገልጸዋል።

በመክፈቻው መርሐግብሩ ላይ ፣ በዘርፉ ዕውቅ የሆኑ ባለሙያዎች፣ ታዋቂ ግለሰቦች እና የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች ተገኝተዋል።

500,000.00  ( ግማሽ ሚሊዮን ብር) አበርክተዋል "መቄዶንያን የመደገፍ፣ የመርዳት፣ የበረከት፣ የበጎነት፣ በአረጋውያን የመመረቅ ታላቅ እድል ነው። ስለዚህም 500,000.00 ( ግማሽ ...
08/02/2025

500,000.00 ( ግማሽ ሚሊዮን ብር) አበርክተዋል

"መቄዶንያን የመደገፍ፣ የመርዳት፣ የበረከት፣ የበጎነት፣ በአረጋውያን የመመረቅ ታላቅ እድል ነው። ስለዚህም 500,000.00 ( ግማሽ ሚሊዮን ብር) ለግሰናል" ~ የብላክ ፐርል መስራች እና ዋና ሥራ አስኪያጅ የሆኑት አቶ ብርሃን መሀመድ ሰይድ

አያይዘውም ሁላችንም እንሳተፍ፣ ከበረከቱ እንቋደስ።
❤ ደግ ልባችሁን ይዛችሁ ኑ! - ብለዋል አቶ ብርሃን መሀመድ ሰይድ።

ታሪካዊ ዳራ
ብላክ ፐርል በሰበአዊነት መንገድ

ብላክ ፐርል ከዚህ ቀደም በመቄዶንያ የአረጋውያን እና የአዕምሮ ህሙማን መርጃ ማዕከል የምሳ ግብዣ አደርጓል።

ከተመሠረተ ስምንት አመታትን ያስቆጠረው ብላክ ፐርል በመቄዶንያ የአረጋውያን እና የአዕምሮ ህሙማን መርጃ ማዕከል የድርጅቱን ሠራተኞች በማስተባበር የካቲት 28 ቀን 2016 ዓ.ም ምሳ፤ ማዕድ የማጋራት መርሐግብር ማድረጉ ይታወሳል።

በዚያን ጊዜ ...
አቶ ብርሃን መሀመድ ሰይድ እንደተናገሩት፤ "የብላክ ፐርል ሠራተኞች እና የማኔጅመንት አባላት ብቻ አይደለንም፤ ክቡራት ደንበኞቻችን፤ ደጋግ ልቦችን ይዘን ለበጎ አድራጎት መቄዶኒያ መጥተናል። ለአገር እና ለሕዝብ ከቃል በላይ በተግባር ( አነሰ፤ በዛ ) ሳንል ግዴታችንን ለመወጣት መጥናል። ለአገር እና ለሕዝብ በጎ ሥራ ለማበርከት ከልባችን ❤ ጋር፤ ከደንበኞቻችን ጋር እንቀጥላለን። " ብለዋል።

እንሆ ዛሬ ላይ ቃላቸውን በተግባር አረጋግጠዋል።

ደግ ልባችሁን ይዛችሁ
ኑ ... ፤ ለበጎ አድራጎት ቀጠሮ አትውሰዱ። ዛሬን ለበጎነት ያዉሉ ! - ሲሉ ለአገር እና ለሕዝብ ጥሪ አሰምተዋል።

መቄዶንያ የበጎ አድራጎት ማኅበር በአሁኑ ሰዓት ከ8ሺ በላይ የሚሆኑ ወገኖቻችን በተለይም እራሳቸውን ችለው መንቀሰሳቀስ፣ መመገብ እና መፀዳዳት የማይችሉ አረጋውያንንና አዕምሮ ሕሙማንን ከአዲስ አበባ ጎዳናዎች ላይ በማንሳት የመጠለያ፣ የምግብ፣ የልብስ፣ የሕክምና አገልግሎትና ቤተሰባዊ ፍቅር በመስጠት ደጋፊና ጧሪ የሌላቸው ኢትዮጵያውያንን እየረዳ ይገኛል፡፡

በቅርቡም አዲስ አበባ የሚገኘውን ማዕከል ጨምሮ በኢትዮጽያ ውስጥ የሚገኙ 44 ማዕከላት ከ7,500 በላይ አረጋውያንና አዕምሮ ሕሙማንን ከወደቁበት ጎዳና አንስቶ በማገዝ ላይ ይገኛል።

ዶ/ር ቢኒያም በለጠ መቄዶኒያ የበጎ አድራጎት ማኅበር አዲስ አበባ ሐያት አካባቢ በሚገኘው የማዕከሉ ቅጥርም ጊቢው ውስጥ ዘመናዊ እና ሁለ ገብ ህንጻ በማጠናቀቅ ላይ ሲገኝ ማዕከሉን ህብረተሰቡ እንዲጎበኝ እና ድጋፍ እንዲያደርግ ጥሪውን አስተላልፏል።

የመቄዶኒያ ታላቅ የገቢ ማሰባሰቢያ ስርጭት
ከዛሬ ጀምሮ ይሳተፉ ሲል ጥሪ አቅርቧል።
በ Seifu on EBS YoouTube

ሰው ለመርዳት ሰው መሆን በቂ ነው!

‹‹የክለቦች የባለቤትነት ይዞታ ባልተረጋገጠበት ስለ እግር ኳስ ዕድገት ማሰብ ከባድ ነው›› ጋሻው አብዛ (ዶ/ር)፣ በሰሜን አሜሪካ የታውሰን ዩኒቨርሲቲ ተባባሪ ፕሮፌሰርደረጀ ጠገናውየኢትዮጵያ...
21/01/2025

‹‹የክለቦች የባለቤትነት ይዞታ ባልተረጋገጠበት ስለ እግር ኳስ ዕድገት ማሰብ ከባድ ነው›› ጋሻው አብዛ (ዶ/ር)፣ በሰሜን አሜሪካ የታውሰን ዩኒቨርሲቲ ተባባሪ ፕሮፌሰር

ደረጀ ጠገናው

የኢትዮጵያ እግር ኳስ በተለይም የፕሪሚየር ሊጉ ክለቦች ከመንግሥት ጥገኝነት ተላቀው ኅብረተሰብ አቀፍ ሆነው ራሳቸውን በራሳቸው ማስተዳደር ይችሉ ዘንድ፣ ከኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንና ከኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ አክሲዮን ማኅበር ጋር በመተባበር ከአንድ ዓመት በላይ የፈጀ፣ ባለድርሻ አካላት የተሳተፉበት፣ በማስረጃና መረጃ ላይ የተመሠረተ ጥናት አስጠንተዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት በአሜሪካ ታውሰን ዩኒቨርሲቲ በተባባሪ ፕሮፌሰርነት በማገልገል ላይ ይገኛሉ፡፡ በዋሽንግተን ዲሲ በርካታ ኢትዮጵያውያንና አፍሪካውያን የሚሳተፉበት፣ ከ2011 ዓ.ም. ጀምሮ ለስድስት ተከታታይ ዓመታት በኖቫ ኮኔክሽን ሥር ሆኖ የሚካሄደው ግራንድ አፍሪካ ራንና አፍሪካ ኢምፓክት አዋርድ የተሰኘ በጎ አድራጎት ድርጅት መሥርተዋል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ በጀርመን ሙኒክ ቢዝነስ ስኩል፣ እንዲሁም ኢትዮጵያን ጨምሮ በሌሎችም አገሮች በስፖርት ቢዝነስ ማኔጅመንት ላይ የማማከር ሥራን ጨምሮ ዘርፉን ሊያግዙ የሚችሉ የተለያዩ የምርምር ውጤቶችን ጨምሮ ከ85 በላይ ጥናታዊ ጽሑፎችን አሳትመዋል፡፡ ጋሻው ወደ አሜሪካ ከመጓዛቸው በፊት የታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ምክትል ሥራ አስኪያጅ ነበሩ፡፡ በሰሜን አሜሪካ ዋሽንግተን ዲሲ እያከናወኑት ያለውን የሩጫና የበጎ አድራት ድርጅትን ጨምሮ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ክለቦች መዋቅራዊ ቁመና ዙሪያ ከጥናቱ በመነሳት ደረጀ ጠገናው አነጋግሯቸዋል፡፡

ሪፖርተር፡– ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያን ከለቀቁ በኋላ ‹‹ግራንድ አፍሪካ ራን›› የተሰኘ ሩጫን መነሻ ያደረገ ድርጅት በሰሜን አሜሪካ ዋሽንግተን ዲሲ ላለፉት ስድስት ዓመታት የሩጫ ውድድር አካሂደዋል፡፡ ውጤቱን እንዴት አገኙት?

ዶ/ር ጋሻው፡- ግራንድ አፍሪካ ራን በኖቫ ኮኔክሽን ሥር ሆኖ ለትርፍ ያልተቋቋመ በጎ አድራጎት ድርጅት ሲሆን፣ ከሩጫው ጎን ለጎን በኢትዮጵያ ስፖርቱን ጨምሮ በተለያዩ ዘርፎች ተፅዕኖ ፈጣሪ ለሆኑ ታላላቅ ሰዎች ዕውቅና በመስጠት ላይ የሚገኘው አፍሪካ ኢምፓክ አዋርድ አጠቃሎ የያዘ ነው፡፡ ዓላማው ኢትዮጵያን ጨምሮ ምሥራቅ አፍሪካውያን የሚታወቁበት አትሌቲክስን እንደ መገናኛ መድረክ በመጠቀም፣ በውጭ የሚኖሩ ዳያስፖራ የማኅበረሰብ ክፍሎችን ማገናኘትና ማስተዋወቅ ዋነኛው ነው፡፡ ሁለተኛው በሰሜን አሜሪካ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን የበለጠ ከባህላቸው ጋር ለማቀራረብና ቤተሰባዊ ግንኙነት እንዲፈጠር ለማድረግና በሦስተኛ ደረጃ ተሻጋሪ ለውጥና ተፅዕኖ የፈጠሩ ሰዎችን ስፖርቱን ጨምሮ በተለያዩ ዘርፎች ዕውቅና የሚሰጥበትና የሚከበሩበት መድረክ መፍጠር ነው፡፡ በዚሁ መሠረት ላለፉት ስድስት ዓመታት በተካሄደው ዝግጅት በሩጫውም ሆነ በዕውቅናው ትልቅ ለውጥ አሳይቷል፡፡ በተለይም ኢትዮጵያ ውስጥ ለጋሽ እጆችን ለሚሹ በጎ አድራጎት ድርጅቶች ገንዘብ በማሰባሰቡ ረገድ ተነሳሽነቱና ፍላጎቱ እየጨመረ መጥቷል፡፡ የለጋሽ ድርጅቶች ቁጥር ጨምሯል፡፡ ይህ ሲባል ግን ዕገዛው ባለው ሁኔታ አጥጋቢና በቂ ነው ባይባልም፣ ገንዘብ እየተሰበሰበ ለሚፈለገው አገልግሎት እንዲውል ተደርጓል፣ እየተደረገም ይገኛል፡፡ እስካሁንም መሠረት መብራቴ፣ ሰለሞን ቦጋለና ቻቺ ታደሰን የመሳሰሉ ለሚያግዟቸው በጎ አድጎት ድርጅቶች ዕገዛው ተደርጓል፡፡ በአሜሪካ ለሚኖሩ በተለያዩ ችግሮች ውስጥ ለሚገኙ ኢትዮጵያውያም ተመሳሳይ ድጋፍና ዕገዛም ተደርጓል፡፡

ሪፖርተር፡– አትሌቲክሱን ከማስተዋወቅ አኳያስ ምን ዓይነት ለውጥ አምጥቷል ማለት ይቻላል?

ዶ/ር ጋሻው፡- አትሌቲክሱ ላይ ታዳጊዎችን በማፍራት ረገድ እዚህ ደረጃ ላይ ደርሰናል ማለት ባልችልም፣ ነገር ግን በዚያው በሰሜን አሜሪካ የሚኖሩ ትውልደ ኢትዮጵያውያን ልጆች በየዓመቱ በሚደረገው የሩጫ ውድድር ላይ ቁጥራቸው እየጨመረ መጥቷል፡፡ እንዲያውም አንዳንዶቹ በዚህ ሩጫ ጀምረው በአሁኑ ወቅት በትልልቅ ካምፓኒዎችና ድርጅቶች ታቅፈው በፕሮፌሽናል ደረጃ እየሠሩ ይገኛሉ፡፡ ውድድሩ በተደረገባቸው ዓመታት ታላላቅ ኢትዮጵያውያን ከደራርቱ ቱሉ ጀምሮ ጥሩነሽ ዲባባ፣ ስለሺ ስህን፣ ጉዳፍ ፀጋይና ትዕግሥት አሰፋን የመሳሰሉ አትሌቶች በክብር እንግድነት ስለሚጋበዙ፣ የእነሱን አርዓያነት የሚከተሉ ከሁሉም የአሜሪካ ግዛት በውድድሩ ለመሳተፍ የሚመዘገቡ ቁጥራቸው በከፍተኛ ፍጥነት እየጨመረ መጥቷል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ስፖርቱ ካለው ዘርፈ ብዙ ፋይዳ አኳያ፣ ኢትዮጵያውያን ዳያስፖራ በዓመት አንድ ጊዜ የሚገናኙበት ትልቅ መድረክም ሆኗል፡፡ በዚህም በተለይ ለኢትዮጵያውያን ታሪካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ ፋይዳው በራሱ ትልቅ እየሆነ ነው፡፡ አሁን ላይ እንዲህ ነው ብሎ መናገር ባይቻልም፣ በሆነ ወቅት ግን አሜሪካ ከሚኖሩ ኢትዮጵያውያን የተገኘ ትውልደ ኢትዮጵያዊ በኦሊምፒክ አሊያም በትልልቅ ዓለም አቀፋዊ ውድድሮች ላይ ተሳታፊ ሆኖ የምናይበት ጊዜ ሩቅ እንደማይሆን ካለው ሁኔታ መረዳት ይቻላል፡፡ ይህን ስል ዝም ብዬ ሳይሆን፣ የቀድሞ ሯጮች ከነበሩ ቤተሰቦች ከአቶ ገነት ገብረ ሥላሴ፣ ሙሉጌታ ወንድሙና የሌሎችም ልጆች በአሜሪካ ለሚገኙ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች እያሳዩት ያለው ተሳትፎ የብዙዎችን ቀልብ መግዛት ጀምሯል፡፡ ከእነዚህ ውስጥ አንዳንዶቹ አሜሪካን ወክለው በዓለም አቀፍ የውድድር መድረክ በመካከለኛ ርቀት ውጤታማ የሆኑም አሉ፡፡

ሪፖርተር፡– የሩጫው ስያሜ ‹‹ግራንድ አፍሪካ ራን›› እንደ መሆኑ በመድረኩ ከኢትዮጵያውያን በተጨማሪ የአፍሪካውያን ተሳትፎ እንዴት ይገለጻል?

ዶ/ር ጋሻው፡- በርከት ያሉ አፍሪካውያን ወንድሞቻችን በመድረኩ በሚፈለገው መጠን ለማሳተፍ ብዙ መሥራት ይጠይቃል፡፡ እንደ ስፖርት ቢዝነስ ባለሙያ (ማርኬተር) አንድን ፕሮጀክት ተቋም ለማድረግ ጊዜ ይጠይቃል፡፡ አሁን የእኛ ሥረ መሠረቱን በማስፋት ደንበኞችን ማወቅ፣ ተሳታፊህን ማወቅና መለየት ነው፡፡ በዚህ ደረጃ ከተመለከትነው ምንም እንኳ የሩጫው ስያሜ ግራንድ አፍሪካ የሚል ቢሆንም፣ አሁን በቅርበት የምናወዳድረው ኢትዮጵያውያንን ካልሆነ አፍሪካውያን በቁጥር ደረጃ ያን ያህል ነው፡፡ ዕቅዳችን መጀመሪያ ለአኗኗርም ሆነ ለማኅበራዊ መስተጋብር ቅርበት ያላቸው ማኅበረሰቦቻችን ላይ ያተኮረ እንዲሆን ነው፣ በዚያም ተሳክቶልናል ማለት እችላለሁ፡፡ ባለፈው 2024 ባደረግነው ሩጫ ቁጥራቸው ወደ 300 የሚጠጋ አፍሪካውያን ተሳታፊዎች ነበሩ፡፡ የእኛም ፍላጎት ቀስ እያለ ተፈጥሯዊ ዕድገቱን ጠብቆ ቁጥሩ እያደገ እንዲመጣ ነው፡፡ የሚገርመው ቁጥሩ ተፈጥሯዊ ዕድገቱን ጠብቆ እንዲጨምር በምናደርገው በአንድ ጊዜ ከአቅማችን በላይ እንደሚሆን ካለው ነባራዊ እውነታ መገመት አያዳግትም፡፡
ሪፖርተር፡– የአገር ውስጥ ኩባንያዎችና ድርጅቶች ከኖቫ ኮኔክሽን ጋር በጋራ ለመሥራት ፍላጎት እያሳዩ ነው፡፡ በቅርቡም ከሁለት የአገር ውስጥ ድርጅቶች ጋር አብሮ ለመሥራት ተፈራርማችኋል፡፡ በዚህ ደረጃ ምን ያህል እምነት እየተጣለብን ነው ብለው ያምናሉ?

ዶ/ር ጋሻው፡- ይህ እንደ አንድ የቢዝነስ ባለሙያ የሚነግረኝ፣ ኢትዮጵያ ወስጥ ከተቋማት ጋር በጋራ መሥራት በአገራችን የተለመደው ስፖንሰር ማድረግ ማለት ዕርዳታ እንጂ አብሮ ለማደግ የሚደረግ ስምምነት ተደርጎ አይወሰድም፡፡ በመሆኑም አሁን እየተፈጠረ ያለው የነበረው የተሳሳተ አስተሳሰብ እየተቀየረ፣ ጥቅሙም የጋራ እንደሆነ እምነት እያሳደረ መምጣቱን ነው፡፡ ከኖቫ ኮኔክሽን ጋር አብሮ ለማሠራት የተስማሙት ዳሸን ቢራና ጎፈሬ አብረውን ለረዥም ጊዜ የዘለቁ ናቸው፡፡ በሰሜን አሜሪካ ለሚኖሩ ደንበኞቻቸውም ተደራሽ ሆነዋል፡፡ ሌላው በሰሜን አሜሪካም ሆነ በሌላው ዓለም የሚኖር ኢትዮጵያዊ ሁሉም በልቡ የሚያልመው ኢትዮጵያን ስለሆነ፣ ያንን ታሳቢ በማድረግ የሚፈጸም ስምምነት ጭምር ነው፡፡ ይህ በአገር ቤትም በስፋት ቢለመድ በተለይ ለኢትዮጵያ ስፖርት ዕድገት የሚኖረው ድርሻ ቀላል አይሆንም፡፡

ሪፖርተር፡– ከመደበኛ ሥራዎች በተጨማሪ ሩጫው ላይ እየሠሩ ከመሆኑ አኳያ፣ አገር ቤት የሚገኘውን የኢትዮጵያ አትሌቲክስን በሙያ ደረጃ ለማገዝና ለመደገፍ ጥያቄ ያቀረቡበት፣ አሊያም ከራሱ ከተቋሙ የቀረበልዎት ሐሳብ ይኖር ይሆን?

ዶ/ር ጋሻው፡- ቀደም ሲል ለመግለጽ እንደሞከርኩት የብሔራዊ ፌዴሬሽኑ የቀድሞዋ ፕሬዚዳንት ረዳት ኮሚሽነር ደራርቱ ቱሉና ሌሎችም በቅርበት እንተዋወቃለን፣ እንተጋገዛለን፣ ወዳጆችም ነን፡፡ እንደተባለው አትሌቲክስ የኢትዮጵያውያን ትልቅ ገጸ በረከት ብቻ ሳይሆንም፣ የማንነታችን መገለጫም ነው፡፡ ይህንን ተቋም ለማገዝ ቤታችን ሁሌም ክፍት ነው፡፡ አሁን ላይ ተቋሙ በአዳዲስ አመራሮች ተተክቷል፡፡ ፍላጎቱና ተነሳሽነቱ ካለ በግሌ የምሰስተው ምንም ነገር ሊኖር እንደማይችል ማረጋገጥ እፈልጋለሁ፡፡ አመራሩ በሒደት ከእኛ ጋር አብሮ ለመሥራት፣ በተለይም ማስረጃና መረጃ ላይ የተመሠረተ ሥራ ለመሥራት ዝግጁ ይሆናሉ የሚል እምነት ይኖረኛል፡፡ ስንደርስበት የምንነጋገርበት ይሆናል፡፡ በተለይ ደግሞ ተቋሙን በገቢ ከማጠናከር አኳያ ኢትዮጵያ ውስጥ ብዙ ያልተነካ ሀብት ስላለ አብረን እንደምንሠራ ተስፋ አለኝ፡፡ በሰሜን አሜሪካ በዚህ ደረጃ መግለጽ የምፈልገው አትሌቲክስ፣ ባስኬት ቦል፣ ፉትቦል፣ ቤዝ ቦልን ጨምሮ ካሉት 124 ቡድኖች መካከል 95 በመቶዎቹ ማዘውተሪያዎቻቸው (ስታዲየሞች) መጠሪያቸው፣ የባንክና የተለያዩ ትልልቅ ዓለም አቀፍ ትጥቅ አምራች ኩባንያዎችና ድርጅቶች ናቸው፡፡ በዚህ ደረጃ ወደ ኢትዮጵያ ስንመጣ፣ በግንባታ ላይ የሚገኘውን አደይ አበባ ስታዲየምን ጨምሮ ብዙዎቹ ማዘውተሪያዎች መጠሪያቸው የቢዝነስን ዕሳቤ ከግምት ያስገባ አይደለም፡፡ ይህ የኢትዮጵያን ስፖርት ዕድገት የምንፈልግ ከሆነ መቀየር ያለበት አስተሳሰብ ይመስለኛል፡፡ ለምሳሌ ያህል በሰሜን አሜሪካ ሎስ አንጀለስ ከተማ ውስጥ የሚገኘው ‹‹ቢት ኮይን›› የተሰኘው ኩባንያ ማዘውተሪያዎች (ስታዲየሞች) በስሙ እንዲሰየሙ በሚሊዮን የሚቆጠር ዶላር ነው ለስፖርት ክለቦች አሊያም ቡድኖች የሚከፍለው፡፡ በዚያው በሰሜን አሜሪካ ኢስኮሽያ ባንክ የተሰኘው ተቋም እንዲሁ የስታዲየሙ ስያሜ በስሙ እንዲጠራ በዓመት 40 ሚሊዮን ዶላር እንደሚከፍል አውቃለሁ፡፡ የብዙዎቹ ኮንትራት ትንሹ ዓመት ሲሆን ትልቁ ደግሞ 30 ዓመት ነው፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ በመገንባት ላይ የሚገኘው አደይ አበባ ስታዲየም ከምንለው ‹‹ሲቢኢ›› ስታዲየም ብለን የማንሰይመው ለምንድነው? ይህንን ወደ አትሌቲክሱ ወስደን በገንዘብ ችግር ወደ መሬት ባንክ ከዓመታት በፊት እንዲመለስ የተደረገው የሰንዳፋ አትሌቲክስ መንደር ‹‹ናይኪ›› አሊያም በሌላ በሚታወቅ ካምፓኒ ስም የማንሰይመው ለምድነው? ይህ ብዙ ማሰብ የማይጠይቅ ፊት ለፊት የምናገኘው የአደባባይ እውነታ ነው፡፡

ሪፖርተር፡– ከዚህ በፊት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ላይ አንድ ጥናት አስጠንተው የነበረ መሆኑ ይታወቃል፡፡ የጥናቱ ውጤት ምን ላይ ደርሷል ብለው የሚከታተሉበት ሁኔታ አለ?

ዶ/ር ጋሻው፡- እከታተለዋለሁ፡፡ በመጀመሪያ ደረጃ ለዚያ ጥናት ነገሮችን በማመቻቸት ተነሳሽነቱን ላመቻቹልኝ አካላት ማለትም ለኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን፣ ለኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ አክሲዮን ማኅበርና ክለባት ከፍ ያለ ምሥጋና አለኝ፡፡ በተለይ ሁለቱ ተቋማት ፌዴሬሽኑና ፕሪሚየር ሊጉ ጥናቱ ላይ ተመሥርቶ የዳኞች አስተዳደደር፣ የተጫዋቾች አስተዳደር፣ የአሠልጣኞች፣ እንዲሁም ገቢና ወጪን በሚመለከት ያላቸው የሥልጣን አንድነትና ልዩነት በተለይም ሊጉ ራሱን ችሎ ራሱን በራሱ እንዲያስተዳድር የወሰዱት ተነሳሽነት በጣም የሚገርምና የሚበረታታ ሊያድግ የሚችል ነው፡፡ ሊጉን በሚመለከት የጋሻው ብቻ ሳይሆን፣ በአጠቃላይ የጥናት ቡድኑ በማስረጃና መረጃ ላይ የተመሠረተ ግኝት፣ መሬት ላይ ያለ እውነት ነው፡፡ ከግኝቱ ተነስተው በግኝቱ መፍትሔ ላይ በበቂ ሁኔታ ሄደንበታል ወይ? ጅምር እንደመሆኑ ሁለትና ሦስት ዓመት መጠበቅ ያስፈልጋል የሚል ሐሳብ አለኝ፡፡ ነገር ግን እንደ ሥጋት የምናገረው አሊያም የመንግሥት ትኩረት ያስፈልገዋል የምለው የክለቦች የባለቤትነት ይዞታ ነው፡፡ ይህ የክለቦች የባለቤትነት ይዞታ መፍትሔ እስካላገኘ ድረስ፣ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ዕድገት ሺሕ ጊዜ ቢጠና የትም መድረስ አይችልም፡፡ የክለቦች የባለቤትነት ይዞታ ሲባል ለምሳሌ ሲዳማ፣ ወላይታና ባህር ዳርን ብንወስድ በጀታቸው በሙሉ ለሕዝብ መሠረታዊ ፍጆታ የሚውል ማለትም ለጤና፣ ለትምህርት አሊያም ለመንገድ አገልግሎት የሚውል ነው፡፡ ታዲያ ምን ይሁን ለሚለው ክለቦቹ ራሳቸውን በራሳቸው ማስተዳደር የሚችሉበት ብቃቱም አቅሙም አላቸው፡፡ ምንድነው? ካልከኝ አሁንም ደግሜ ደጋግሜ ልነግርህ የምችለው ምንድነው፣ ተወደደም ተጠላ ክለቦቹ ወደ ግል ይዞታነት በመቀየር ማኅበረሰብ አቀፍ መሆን ይኖርባቸዋል፡፡ በጥናቱ የብዙ አገሮች ተሞክሮ ተወስዶ ለኢትዮጵያ የሚበጀው ነው የተወሰደው፡፡ ማለትም መንግሥት ራሱ የሆነ ድርሻ ይኖረዋል፣ ከዚያም ባለሀብት፣ ኅብረተሰቡና ደጋፊው (የተመዘገበ) ናቸው፡፡ ባለሀብት ሲባል አቪዬሽን አሊያም ቴሌኮም፣ በውጭ የሚኖር ባለሀብት (ዳያስፖራ) አሊያም አገር ውስጥ የሚገኝ ባለሀብት፣ እንደ ድርሻቸው በመቶኛ ተከፋፍሎ የባለቤትነት ድርሻቸውን በሕግ አግባብ ማስቀመጥና ከድርጅቱ አሊያም ከክለቡ ሥራ አስኪያጅ ጀምሮ ተጠያቂነቱም አብሮ እንዲኖር ማድረግ ያስፈልጋል፡፡ ባለፈው ዓመት በጥናቱ ግኝት መሠረት ማኑዋሎችና መመርያዎች ተሠርተው ለሚመለከታቸው ሁሉ ተደራሽ ተደርገዋል፡፡ እንደ አጋጣሚ ሆኖ የተለያዩ ገቢ ማሰባሰብ ላይ፣ ከባህር ዳርና ከፋሲል ከተማ ክለቦች ጋር እነዚህን ማኑዋሎችና መመርያዎች ላይ የመሥራት ዕድሉ ገጥሞኛል፡፡ ብዙም አስቸጋሪ አይደለም፡፡ በሁሉም ዘንድ ፍላጎቱና ተነሳሽነቱ አለ፡፡ ችግሩ ምንድነው ካልከኝ አሁንም የክለቦች የባለቤትነት ይዞታ ገና ስላልተረጋገጠ ዕውን ማድረግ አልቻልንም፡፡ ስለሆነም የባለቤትነት ይዞታው ሊረጋገጥ ይገባል፡፡

ሪፖርተር፡– በጥናቱ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ተሳትፈውበታል ተብሏል፡፡ የባለቤትነት ይዞታ የሚለው የጥናት ግኝቱ አንድ አካል ነው፡፡ ተግባራዊ ማድረግ ያልተቻለው ለምን ይመስልዎታል?

ዶ/ር ጋሻው፡- በግሌ ተጠያቂው አበበ ወይም ከበደ ነው ማለት አልፈልግም፡፡ ነገር ግን ለጥናት ግኝቱ መተግበር ሁሉም በጋራ ሊሠሩበት ይገባል ማለት ግን እወዳለሁ፡፡ ይህን ተግባራዊ ማድረግ ካልተቻለ ቀደም ሲል ለመግለጽ እንደሞከርኩት መፍትሔ ስለሌለው ማለቴ ነው፡፡ ተግባራዊ ከተደረገ ግን የክለቦች ፈቃድ አሰጣጥ መመርያን ጨምሮ ተጫዋቾችና የባለድርሻ አካላት ወርኃዊ ክፍያ እንደ አቅም ለመክፈል ቀላል ይሆናል፡፡ ባለው ሁኔታ ግን የመንግሥትን ገንዘብ ዝም ብሎ መክፈል አሸዋ ላይ ውኃ ከማፍሰስ የተለየ ሊሆን አይችልም፡፡ ምክንያቱም የክለቦች የትኬት (ሜዳ) ገቢ፣ የስፖንሰርሺፕ፣ የስታዲየም ውስጥ የስፖርት አልባሳት (ጀርሲዎች) የሚገኘውን ጨምሮ ከምግብ ሽያጭና ከመሳሰሉት የሚገኙ የገቢ ምንጮች አግባብ ባለው ማኑዋልና መመርያዎች ሊተዳደሩ የሚችሉት ቀደም ሲል ለመናገር እንደሞከርኩት የክለቦች የባለቤትነት ይዞታ መረጋገጥ ይኖርበታል፡፡ ይህ ባልተረጋገጠበት ስለእግር ኳስ ዕድገት ማሰብ ከባድ ነው፡፡

ብራንድ አምባሳደሮቹ ለስለእናት የበጎ አድራጎት ድርጅት ስጦታ አበረከቱ።ስለእናት የበጎ አድራጎት ድርጅት ለችግር የተጋለጡ እና የተጎዱ ህጻናትን እንዲሁም ቤተሰቦቻቸውን ለመታደግ የተቋቋመ ድር...
04/01/2025

ብራንድ አምባሳደሮቹ ለስለእናት የበጎ አድራጎት ድርጅት
ስጦታ አበረከቱ።

ስለእናት የበጎ አድራጎት ድርጅት ለችግር የተጋለጡ እና የተጎዱ ህጻናትን እንዲሁም ቤተሰቦቻቸውን ለመታደግ የተቋቋመ ድርጅት ሲሆን ድርጅቱ ካለበት ወቅታዊ ችግርን በመረዳት በቅርብ ባይሊ የምግብ ማቀነባበሪያ የብራንድ አምባሳደር የሆነው ትንሳኤ ብርሃን እና የጂፒዋይ ማኑፋክቸሪንግ ምርት የሆነው የኢቭ የህጻናት ዳይፐር የብራንድ አምባሳደር አርቲስት መስከረም አበራ በዛሬው እለት ድርጅቱን ጎብኝተዋል።

የስለእናት የበጎ አድራጎት ድርጅት ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ያሬድ አብዱ "ባይሊ የምግብ ማቀነባበሪያ እና የጂፒዋይ ማኑፋክቸሪንግ ምርት የሆነው የኢቭ የህጻናት ዳይፐር የብራንድ አምባሳደሮች ድርጁቱ ውስጥ እየታገዙ የሚገኙ ህጻናትን ለመጎብኘት መምጣታቸው መደሰታቸውን ገልጸው በቀጣይ ስለእናት እየተንቀሳቀሰባቸው የሚገኝባቸውን ዘርፎች በተለያዩ ቅን ግለሰቦች እና ማህበራዊ ሃላፊነታቸውን ከሚወጡ ተቋማት ጋር ድጋፍ በማሰባሰብ የተለያዩ ስራዎች እየሰራ እንደሚገኝ በመግለፅ ካለው የችግሩ ስፋትና ጥልቀት አንፃር ቀጣይነት ያለው ድጋፍ እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል።

በጉብኝቱ ላይ የባይሊ የምግብ ማቀነባበሪያ ምርቶችን ለማስተዋወቅ ብራንድ አምባሳደር የሆነው ወጣቱ ትንሳኤ ብርሃን ስለእናት የበጎ አድራጎት ድርጅት መታገዝ የሚገባው ተቋም እንደሆነ ገልጿል።

የጂፒዋይ ማኑፋክቸሪንግ ምርት የሆነው የኢቭ የህጻናት ዳይፐር የብራንድ አምባሳደር ሁለገቧ አርቲስት መስከረም አበራ የተቋሙ ምርት ከማስተዋወቅ ባሻገር ማኀበራዊ ኃላፊነት ለመወጣት በሚደረገው ጥረት የበኩሏን ድርሻ እንደምታበረክት ገልጻለች።

ሁለቱ ተቋማት የሚያመርታቸውን ምርቶች ለስለእናት የበጎ አድራጎት ድርጅት በስጦታ አበርክተዋል።

የስለእናት የበጎ አድራጎት ድርጅት በቀጣይ ማገዝ ለሚሹ ከስር በተቀመጡ የባንክ ሒሳብ ቁጥሮች ማገዝ ይቻላል።

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፑሽኪን አደባባይ ቅርንጫፍ
📌 1000237880556
ብርሀን ኢንተርናሽናል ባንክ ሳር ቤት ቅርንጫፍ
📌 1601160024989
አቢሲንያ ባንክ አክሲዎን ማህበር ሳር ቤት ቅርንጫፍ
📌 13387583
አንበሳ ኢንተርናሽናል ባንክ ሳር ቤት ቅርንጫፍ
📌 00110086000-66
የኦሮምያ ህብረት ስራ ባንክ ሳር ቤት | ቅርንጫፍ
📌 1000066623681
እናት ባንክ አ.ማ
📌 0161103120220001
ዳሽን ባንክ አማ
📌 0001515959002
ህብረት ባንክ አ.ማ
📌 1071116494046018
ወጋገን ባንክ
📌 0748512511101
አባይ ባንክ አ.ማ
📌 1492113520844013
ደቡብ ግሎባል ባንክ አ.ማ
📌 1012101205951
ቡና ኢንተርናሽናል ባንክ አ.ማ
📌 1119601000427
ንብ ኢንተርናሽናል ባንክ
📌 7000014616794
አዋሽ ኢንተርናሽናል ባንክ
📌 01320243489600

የልጆች አለም አሁን ነው!
15/11/2024

የልጆች አለም አሁን ነው!

የሁላችንም ድጋፍ የሚሻ የመልካም ተግባር ጥሪበኢትዮጵያ አርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ከርስቲያን በምስራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት በመንበረ ጵጵስና ርዕሰ ከተማ ወረዳ የናዝሬት ደብረ ፀሐይ ቅድስት ማርያ...
06/11/2024

የሁላችንም ድጋፍ የሚሻ የመልካም ተግባር ጥሪ

በኢትዮጵያ አርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ከርስቲያን በምስራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት በመንበረ ጵጵስና ርዕሰ ከተማ ወረዳ የናዝሬት ደብረ ፀሐይ ቅድስት ማርያም ካቴድራል ቅጽር ጊቢው ውስጥ በስተሰሜን ባለው ቦታ ላይ G+6 ሁለገብ ሕንፃ ለማስገንባት የዲዛይኑ ሥራ ተጠናቆ የግንባታ ፈቃድ በመውሰድ ሥራውን ለመጀመር በዝግጅት ላይ ይገኛል።

የሕንፃው ግንባታ ዓላማ ገቢ ማስገባት ሲጀምር ከሕንፃ ኪራይ በሚገኘው ገቢ

📌የገጠሪቷን ቤተክርስቲያን የፋይናንስ እጥረት ለመቅረፍ
📌 ረጂ የሌላቸውን አረጋውያንና አቅመ ደካሞችን መርዳት
📌 ወላጅ አልባ ሕፃናትን ለመርዳት
📌 የስብከተ ወንጌል አገልግሎት ስርጭትን በገጠሪቷ ቤተክርስቲያን ለማሳለጥ
📌 የካቴድራሉን መንፈሳዊና ማሕበራዊ አገልግሎት በስፋት ለማሰራጨት እንዲያስችል የታሰበ ሲሆን

ይህንን ባለ6 ወለል ሁለገብ ህንፃ ግንባታን ለማስጀመር የፊታችን ህዳር 7 እስከ ህዳር 10 ቀን 2017 ዓ.ም የሚቆይ ልዩ የገቢ ማሰባሰቢያ መንፈሳዊ ባዛር የተዘጋጀ ሲሆን በመርሐግብሩ ላይ በአዳማ ከተማ እና በሌላው አለም የምትገኙ የቅድስት ቤተክርስቲያን ልማትን የምትደግፉ ሀገር ወዳድ ኢትዮጵያዊያን በዚህ ባዛር ላይ በመገኘት ወይም ካላችሁበት በባንክ አካውንት በማስገባት ድጋፍ እንድታደርጉ በቅድስት ድንግል ማርያም ስም የካቴደራሉ አስተዳደር ይጠይቃል።

ኑ የበረከቱ ተካፋይ ይሁኑ !

"የሰማዩ አምላክ ያከናውንልናል እኛም ባሪያዎቹ ተነስተን እንገነባለን"(ነህ.2:20)

የባንክ አካውንት ቁጥር
👉 ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1000646187005
👉 ዳሸን ባንክ 0014153061011
👉 አቢሲኒያ ባንክ 203151888
👉 አዋሽ ባንክ 013521412262200
👉 ስንቄ ባንክ 1074880231211

ለበለጠ መረጃ

0912226935
0912250077
0911822481

🎯 አብሮነት መሻል ነው!ዶ/ር ጋሻው አብዛ የግራንድ አፍሪካ ረን ዳሬክተር ♦አምስተኛዉ ግራንድ አፍሪካን ረን በዲሲ በመጪዉ ኦክቶበር 12 ይካሄዳል♦በርካታ ኢትዮጵያዊያን ኦሎምፒያኖች እና የዓ...
30/09/2024

🎯 አብሮነት መሻል ነው!
ዶ/ር ጋሻው አብዛ
የግራንድ አፍሪካ ረን ዳሬክተር

♦አምስተኛዉ ግራንድ አፍሪካን ረን በዲሲ በመጪዉ ኦክቶበር 12 ይካሄዳል

♦በርካታ ኢትዮጵያዊያን ኦሎምፒያኖች እና የዓለም ሻምፒዮኖች በዚህ ዝግጅት ላይ በክብር እንግዳነት ይሳተፋሉ።

♦የግራንድ አፍሪካን ረን ባለፉት አምሰት ዓመታት ባዘጋጃቸው ሁነቶች ለተለያዩ የበጎ አድራጎት ድርጅቶች ድጋፍ አድርጓል፡፡

ዶ/ር ጋሻው አብዛ የግራንድ አፍሪካ ረን መሥራችና (CEO)
ከጋዜጣዊ መግለጫቸው ላይ የተወሰደ

***
የ2024 የአፍሪካ ኢምፓክት አዋርድ ተሸላሚዎች ይፋ ሆነዋል

ድምፃዊት አስቴር አወቀ፣ አንጋፋዋ ጋዜጠኛ መአዛ ብሩ፣ እና ሌሎች ሦስት ሴት ኢትዮጵያዊያኖች በአሜሪካ ዋሽንግተን ዲሲ ሊሸለሙ ነው።

አሜሪካ ዋሽንግተን ዲሲ የተመሰረተውና ለትርፍ ያልተቋቋመው ኖቫ ኮኔክሽን የሚያዘጋጀው የ2024 አፍሪካ ኢምፓክት አዋርድ የዘንድሮ የክብር ተሸላሚዎች ታውቀዋል።

ይህ አመታዊ የእውቅና ሽልማት ስነ ስርአት በአሜሪካና በአፍሪካ በሙያቸው ታላቅ ሥራ የሰሩ ግለሰቦችን ለማክበር የተዘጋጀ ነው። በየአመቱ ከስፖርት፣ ከስነ ጥበብና ከስራ ፈጠራ ዘርፎች ለማህበረሰቦቻቸው ላበረከቱት አስተዋፅኦና ለለውጥ ላደረጉት የላቀ ተሳትፎ ከየዘርፉ ተመርጠው የሚሸለሙበት መድረክ ነው።

አፍሪካ ኢምፓክት አዋርድ እስካሁን ለአራት ጊዚያት ተካሂዷል።

እውቅና ከተሰጣቸው ተፅዕኖ ፈጣሪዎች መካከል ደግሞ የሚከተሉት ይገኙበታል፦

📌 2019: ድምፃዊ ቴዎድሮስ ካሳሁን ( ቴዲ አፍሮ )፣ አትሌት ረዳት ኮሚሽነር ደራርቱ ቱሉና ሚስተር ማርክ ጌልፋንድ

📌 2020 - በኮቪድ-19 ምክንያት አልተካሄደም!

📌 2021- አትሌት ጥሩነሽ ዲባባ፣ ድምፃዊ ኤኮንና አቶ በረከት ወልዱ

📌 2022 - አትሌት ቀነኒሳ በቀለ፣ "እረኛዬ" የቴሌቪዥን ድራማ፣ አቶ ሄኖክ ተስፋዬ እና ንግሥት ሰናይ ልኬ

📌 2023 - የዲባባ ቤተሰብ፣ አቶ ግርማ ዋቄ፣ አርቲስት ሙላቱ አስታጥቄና አትሌት ስለሺ ስህን

ዘንድሮም በተለያዩ ዘርፎች አምስት ተፅዕኖ ፈጣሪ ኢትዮጵያዊያንን ለማክበርና እውቅና ለመስጠት ዝግጅቱ ተጠናቋል።

የዚህ አመት ተሸላሚዎች በሙሉ ሴቶች ናቸው።

በስነ ጥበብ ዘርፍ:-
❣️ዝነኛዋ ድምፃዊት አስቴር አወቀ

በጋዜጠኝነት
❣️ አንጋፋዋ ጋዜጠኛ መአዛ ብሩ፣

በስፖርቱ ዘርፍ የማራቶንና የ5000 ሜትር የአለማችን ክብረወሰን ባለቤቶች:-

❣️ ትዕግስት አሰፋ
እና
❣️ ጉዳፍ ፀጋዬ

በቢዝነስ ዘርፍ:-
❣️ ርብቃ ሀይሌ ተሸላሚዎች ይሆናሉ።

በእለቱ የዲሲ፣ ሜሪላንድና ቨርጂኒያ ከፍተኛ ባለስልጣናት፣ ሴናተሮች፣ ከንቲባዎችና ሌሎች ጥሪ የተደረጋላቸው በርካታ እንግዶች ይገኛሉ፤ ተሸላሚዎቹ ከግዛቶቹና ከተማዎቹ ተወካዮች የእውቅና ሰርተፍኬት ይበረከትላቸዋል።

በተጨማሪ ለበጎ አድራጎት ሥራ የሚውል የሙዚቃ ዝግጅት በወጣቷ ድምፃዊት ራሄል ጌቱና በታዋቂው መሳሪያ ተጫዋች ሰላም ስዩም የሚቀርብ ይሆናል።

የ2024 የአፍሪካ ኢምፓክት አዋርድ ስነ ስርአት ሜሪላንድ በሚገኘውና ኢትዮጵያዊያን በባለቤትነት በሚያስተዳድሩት ሜትሮ ፖይንትስ ሆቴል እሁድ ኦክቶበር 13 ቀን 2024 ምሽት በደማቅ ዝግጅት ይካሄዳል።

🎯 አብሮነት መሻል ነው!

Chance to win ❣️♦📌
የ2024 ቶዮታ ኮሮላ መኪናዎን ይውሰዱ

ለውድድሩ የሚመዘገቡ ተሳታፊዎች በሙሉ በእጣ ውስጥ የሚካተቱ ሲሆን፣ እድለኛው አሸናፊ በዝግጅቱ ቀን ማብቂያ ላይ የእጣ ማውጣት ስነ-ስርዓቱ ተከናውኖ በይፋ ይገላጻል።

በዘንድሮው ግራንድ አፍሪካን ረን በዲሲ ሲሳተፉ፣ የ2024 ቶዮታ መኪና ዕጣ የማግኘት ዕድል ይኖርዎታል።❣️♦📌

ለመመዝገብ www.africanrun.com ይጠቀሙ።

የመኪናው ሽልማት፣ ስፖንሰሮቻችን ዳሸን ባንክ እና አሌክዛንደሪያ ቶዮታ በአዘጋጆቹ በኩል ያቀረቡት ነው።

ግራንድ አፍሪካን ረን ለሁሉም ሰው ክፍት ነው - ጀማሪ ሯጭ ይሁኑ፣ ፕሮፌሽናል።

በርምጃ፣ በሶምሶማ ውይም በሩጫ ርቀቱን ሊያጠናቅቁ ይችላሉ።

ዝግጅቱ ከሩጫም በላይ ነው።

ማህበረሰባችን ተሰባስቦ አብሮነታችንን የምናክብርበት ቀን ነው።

ግራንድ አፍሪካን ረን ቀኑ ቀረበ - ኦክቶበር (Oct) 12 ። ይመዝገቡ፣ ከወገንዎ ጋር ቀኑን ያሳልፉ፣ ይዝናኑ፣ ይሸለሙ። ውሱን ቦታዎች ናቸው የቀሩት ቀድመው ይመዝገቡ። ለመመዝገብ www.africanrun.com ይጎብኙ።

African Grand Run - 🇺🇸

ቦታ፦ ዋሽንግተን ዲሲ
ቀን፦ ኦክቶበር 12 ጠዋት 9:00am

በዝግጅቱ ለመታደም ትኬትዎን የሚከተለውን ሊንክ በመከተል ያገኛሉ: https://shorturl.at/YQvrv

For more: Nova Connections, Email: [email protected]; https://www.africanrun.com/impact

***
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) - ሚዲያና ኮሙኒኬሽንስ - በኖቫ ኮኔክሽን የሚዘጋጁ ( የአፍሪካን ኢምፓክት አዋርድ እና የግራንድ አፍሪካን ረን ) ዝግጅቶች የኢትዮጵያ ወኪል ነው።

Getu Temesgen Media & Comminucations
is sole agent in Ethiopia for African Impact Award and Grand African Run events organized by Nova Connection.

#አብሮነትመሻልነው

ለአምስት ቀናት የሚቆይ የቤት ሽያጭ  ምዝገባ ተጀመረ።በተመጣጣኝ ዋጋ ቤት ለመግዛት ፍላጎት ያላቸው ግለሰቦችና ተቋማት የሚሳተፉበት የቤት ሽያጭ ምዝገባ  ከዛሬ ከሚያዝያ16 እስከ ሚያዝያ 20...
26/04/2024

ለአምስት ቀናት የሚቆይ የቤት ሽያጭ ምዝገባ ተጀመረ።

በተመጣጣኝ ዋጋ ቤት ለመግዛት ፍላጎት ያላቸው ግለሰቦችና ተቋማት የሚሳተፉበት የቤት ሽያጭ ምዝገባ ከዛሬ ከሚያዝያ16 እስከ ሚያዝያ 20 ቀን 2016 ዓ.ም ለ5 ቀን በአድዋ ሙዚየም መጀመሩን ኦቪድ ግሩፕ አሳወቀ።

ኦቪድ ግሩፕ «ኦቪድ ገላን ጉራ» የተሰኘ ከተማ በአዲስ አበባ ቦሌ ቡልቡላ አቅራቢያ እየገነባ እንደሆነ የኦቪድ ሪል እስቴት ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ፍሬው በየነ ለሚዲያ ባለሙያዎች በዛሬው እለት በአድዋ ሙዚየም በሰጡት መግለጫ አስታወቁ።

የኦቪድ ገላን ጉራ ከተማ ከቦሌ አየር መንገድ በስምንት ኪሜ ርቀት ላይ ከቦሌ ቡልቡላ ጀርባ 560 ሄክታር መሬት ላይ የሚያርፍ ሲሆን ከ300ሺህ በላይ ነዋሪዎችን ተጠቃሚ የሚያደርጉ 60 ሺህ ቤቶችን የሚኖሩት ሲሆን በቂና ዘመናዊ መሰረተ ልማቶችና የተለያዩ መገልገያዎች የተሟሉለት አለም አቀፍ ስታንዳርድን የሚያሟላ ማራኪ የመኖሪያ የንግድና የመዝናኛ ከተማ ይሆናል ሲሉ አቶ ፍሬው ተናግሯል።

መጋቢት 24 በከንቲባ አዳነች አበቤ በይፋ የመሰረተ ድንጋይ የተቀመጠለት 60 ሺህ ቤቶችን የያዘው የኢትዮጲያ አዲሱ ከተማ ግራውንድ ፍሎሩ ለሰው ልጅ የሚያስፈልጉ መሰረታዊ ነገሮች ሁሉ የተሟሉለት ጂ ፕላስ 30 የሆኑ ህንጻዎች ያሉበት ሲሆን ሆስፒታሎች፣ የአምልኮ ቦታዎች፣ ስቴዲየም፣ የውሃ ፋውንቴኖችና በርካታ የመዝናኛ አማራጮች በስፋትና በጥራት ይገኙበታል ተብሏል።

G+12 የሆኑ 600 ብሎክ ያላቸው 27 ሺህ ቤቶች ስታንዳርድ በሚለው ምድብ ውስጥ ተካተዋል። G+8 የሆኑ በ600 ብሎኮች ውስጥ 24 ሺህ ቤቶችን የያዙትን ደግሞ ዴሉክስ የሚባሉ ሲሆን፣ ፕሪሚየም በሚል ደርጃ ስር በ90 ብሎክ 9ሺህ ቤቶችን ይይዛል። ታውን ሃውስ የሚል ስያሜ የተሰጣቸው G+1 አና G+2 ቤቶችም በከተማው የሚገነቡ እንደሆኑ ተነግሯል።

ኦቪድ ሪል ስቴት ሀላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር በራሱ መሬት ላይ ከሚያለማቸው ቤቶች በተጨማሪ የኦቪድ ገላን ጉራ ፕሮጀክትን ጨምሮ ባጠቃላይ 65 ሺህ ቤቶችን ለማልማት በመስራት ላይ ያለ ሲሆን ከኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስተር ፅህፈት ቤት ጋር የጥምረት ቤትና የጫካ ፕሮጀክትን ጨምሮ በአሁኑ ወቅት 18.5 ቢሊየን ዶላር በላይ የሚያወጡ ፕሮጀክቶችን እያስተዳደረ ይገኛል።

ከነዚህም በተጨማሪ የ60 ሺህ ቤቶች ግንባታ የሚከናወንበት የአዲሱ ኦቪድ ገላን ጉራ ከተማ ፕሮጀክቶችን ጨምሮ ከ4 ሺህ በላይ የቤት ልማት ፕሮጀክቶች ላይ ተሰማርቶ ይገኛል።

አንበሳው ሜታ ተነስቷል !ቢጂአይ ኢትዮጵያ ሜታ አቦ ቢራ ፋብሪካን ለማዘመን ከግማሽ ቢሊየን ብር በላይ ማውጣቱን ገለጸ።ቢጂአይ ኢትጵያ ሜታ አቦ ቢራ ፋብሪካን ከራሱ ጋር ለማዋሃድ የሚያስችለው...
16/02/2023

አንበሳው ሜታ ተነስቷል !

ቢጂአይ ኢትዮጵያ ሜታ አቦ ቢራ ፋብሪካን ለማዘመን ከግማሽ ቢሊየን ብር በላይ ማውጣቱን ገለጸ።

ቢጂአይ ኢትጵያ ሜታ አቦ ቢራ ፋብሪካን ከራሱ ጋር ለማዋሃድ የሚያስችለውን ፍቃድ ባሳለፍነው ወር ማግኘቱን ተከትሎ የሜታ አቦ ቢራ ፋብሪካን እንደገና በማደስና ለማስፋፋት ከ550 ሚሊዮን ብር በላይ መዋዕለ ንዋይ ማፈሰሱን ገለጸ።

በሰበታ ከተማ በሜታ አቦ ቢራ ፋብሪካ ግቢ ውስጥ ዛሬ የካቲት 9 ቀን 2015 ዓ.ም ጠሀት ላይ በተዘጋጀው መርሐ ግብር ላይ የቢጂአይ ኢትዮጵያ ዋና ስራ አስፈፃሚ ሚስተር ሄርቬ ሚልሃድ ጨምሮ ጢሪ የተደረገላቸው ከፍተኛ የክልል እና የፌደራል ባለስልጣኖች በተገኙበት ባለፉት ስድስት ወራት ሜታ አቦ የቢራ ፋብሪካ ዳግም ለሟቋቋም የተከናወኑ ስራዎችን በተመለከት አጭር ገለጻ ቀርቧል።

አዲሱ የቢጂአይ ኢትጵያ ዋና ስራ አስፈፃሚ ሚስተር ሄርቬ ሚልሃድ ባደረጉት ንግግር ቢጂአይ ኢትዮጵያ "የሜታ አቦ ቢራ ፋብሪካን አቅም ለማሳደግ ፣ ስሙን ለማደስና ኩባንያውን ለመንከባከብ፣ እንዲሁም ከሰበታ ከተማ ሕዝብ፣ ከአካባቢው አስተዳደርና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር የጠበቀ ግንኙነት ለመፍጠር የገባውን ቃል በትክክል እንደፈጸምን ለመግለጽ በመቻሌ ደስታ ይሰማኛል" ብለዋል።

ሜታ አቦ ቢራ ፋብሪካ ከ1500 በላይ ለሚሆኑ ሰዎች የሥራ እድል የፈጠረ ሲሆን በወር ከ300,000 ሄከቶ በላይ ሊትር የማምረት አቅም ይኖረዋል።

(ጌች ሐበሻ)
📷Sisay Guzay

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ልዩ ገጽ LIYU PAGE posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to ልዩ ገጽ LIYU PAGE:

Share