Bisratfm101.1

Bisratfm101.1 Bisrat 101.1FM is a radio station established by Oyaya Multimedia PLC based in Addis Abeba, Ethiopia
(1)

ጥር 23-2017 - የእስራኤል ምርኮኞች ቤተሰቦች ኔታንያሁ የተኩስ አቁም ስምምነቱን ማበላሸት የለባቸውም ሲሉ ተናገሩበጋዛ የታገቱ ቤተሰብ ያላቸው እስራኤላውያን የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ...
31/01/2025

ጥር 23-2017 - የእስራኤል ምርኮኞች ቤተሰቦች ኔታንያሁ የተኩስ አቁም ስምምነቱን ማበላሸት የለባቸውም ሲሉ ተናገሩ

በጋዛ የታገቱ ቤተሰብ ያላቸው እስራኤላውያን የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁ የተኩስ አቁም ስምምነቱን እንዳያበላሹ ጥሪ አቅርበዋል፡፡በ+972 መጽሔት ላይ የእስራኤል መንግስትን የሚተቸዉ ዩዳ ኮሄን የተባለዉ ግለሰብ የእስራኤል ወታደር የሆነዉ ልጁ ናምሩድ በጥቅምት 7 የተማረከ ሲሆን እስራኤል በጋዛ ፍልስጤማውያን ላይ የጦር ወንጀል እየፈፀመች ብቻ አይደለም "በእስራኤል ወታደሮች ላይ ወንጀል እየፈፀመች ነው"ሲል ተደምጧል፡፡

"ሁሉም ታጋቾች እንዲመለሱ እፈልጋለሁ" ሲልም አክሏል፡፡ከፍልስጤማውያን ጋር ይበልጥ የተረጋጋ እና ዘላቂ መፍትሄ ላይ መድረስ ተገቢ ነው። ሌላውን ጎን ማየት አለብን። አንዱ ወገን ሲያድግ ሌላኛው ሲሰቃይ ሊሆን አይችልም ። በሌላ በኩል ሐሙስ ዕለት በጋዛ ደቡባዊ ካን ዮኒስ የእስራኤል ምርኮኞችን በርካታ የፍልስጤም ታጠቂ ቡድኖች አሳልፈዉ ለሃማስ መስጠታቸዉ በአካባቢው ባሉ የተቃውሞ ቡድኖች መካከል ያለውን ትብብር እና ግንኙነት ቀጣይነት ያለው መሆኑን የጦርነት ተቆጣጣሪዎች ተናግረዋል ።

የጦርነት ጥናት ኢንስቲትዩት እና Critical Threats ፕሮጀክት (CTP)፣ መቀመጫቸውን አሜሪካ ያደረጉ ሁለት የመከላከያ ትንታኔ ተቋማት፣ የሃማስ ተዋጊዎች፣ የፍልስጤም ተቃዋሚ ኮሚቴ እና የፍልስጤም ሙጃሂዲን ንቅናቄ ሃይሎችን አብረዋቸው እንደነበሩ ያሳያል ሲሉ ተደምጠዋል፡፡ ከእስራኤል ጋር ከ 15 ወራት ጦርነት በኋላ "በተዳከመ ተቋማዊ የማስተባበር ዘዴ ምክንያት ተግዳሮቶች" ሊያጋጥሟቸው በሚችሉበት በዚህ ወቅት በታጠቁት ቡድኖች መካከል ያለው አንድነት አስገራሚ መሆኑ ተገልጿል፡፡

የእስራኤል ማአሪቭ ጋዜጣ በበኩሉ በጋዛ ጦርነት ላይ የእስራኤልን የህዝብ አስተያየት የሚገመግም የዳሰሳ ጥናት አውጥቷል።በአላዛር ምርምር በተካሄደው የሕዝብ አስተያየት መሠረት 57 በመቶ የሚሆኑ እስራኤላውያን የሀገሪቱ የጦርነት ዓላማዎች "ሙሉ በሙሉ አልተሳካም" ሲሉ 32 በመቶ የሚሆኑት "ምንም አልተሳካም" ብለው ያምናሉ፡፡ምላሽ ከሰጡት ሰዎች መካከል አራት በመቶው ብቻ የእስራኤል የጦርነት ኢላማዉን በጋዛ "ሙሉ በሙሉ አሳክቷል" ብለዋል።

በስምኦን ደረጄ

🇪🇹🇪🇹🇪🇹

የብስራትን የተለያዩ ማህበራዊ ገጾች በመቀላቀል፤ ወቅታዊ መረጃዎችን እና ፕሮግራሞችን ይከታተሉ…

Facebook: https://bit.ly/3Hng6Qt
Website: https://www.bisrattv.com/
Telegram: https://t.me/Bisrat101fm
YouTube: https://bit.ly/3zAAOrB
Twitter: https://twitter.com/Bisrat101fm
TikTok: https://bit.ly/

ጥር 23-2017 - አሰልጣኝ መሳይ ተፈሪ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝ ሆነው ለአንድ ዓመት በሚቆይ ውል እንዲቀጥሉ ውሳኔ ተላልፏል። ከህዳር ወር ጀምሮ በጊዜያዊ ዋና አሰልጣኝነት ...
31/01/2025

ጥር 23-2017 - አሰልጣኝ መሳይ ተፈሪ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝ ሆነው ለአንድ ዓመት በሚቆይ ውል እንዲቀጥሉ ውሳኔ ተላልፏል።

ከህዳር ወር ጀምሮ በጊዜያዊ ዋና አሰልጣኝነት እየሰሩ የሚገኙት መሳይ ተፈሪ በዓለም ዋንጫ ማጣርያ ጨዋታዎች የሚያስመዘገቡትን ውጤት መሠረት ተደርጎ ሊታደስ በሚችል የአንድ ዓመት ውል ብሔራዊ ቡድኑን የሚመሩ ይሆናል። አብረዋቸው የሚሰሩ የአሰልጣኝ ቡድን የማዋቀር ኃላፊነትም ተሰጥቷቸዋል።

ዘገባው የኢትዮጲያ እግርኳስ ፌደሬሽን ነው!



የብስራትን የተለያዩ ማህበራዊ ገጾች በመቀላቀል፤ ወቅታዊ መረጃዎችን እና ፕሮግራሞችን ይከታተሉ…

Facebook: https://bit.ly/3Hng6Qt
Website: https://www.bisrattv.com/
Telegram: https://t.me/Bisrat101fm
YouTube: https://bit.ly/3zAAOrB
Twitter: https://twitter.com/Bisrat101fm
TikTok: https://bit.ly/

ጥር  23፤2017 -   በህግ ትፈለጋለህ በማለት አንድን ግለሰብ ያላግባብ የገደሉ ሁለት የቀበሌ አመራሮች በእስራት ተቀጡበደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን አመያ ወረዳ ውስጥ በህግ ትፈለጋለህ በማለት...
31/01/2025

ጥር 23፤2017 - በህግ ትፈለጋለህ በማለት አንድን ግለሰብ ያላግባብ የገደሉ ሁለት የቀበሌ አመራሮች በእስራት ተቀጡ

በደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን አመያ ወረዳ ውስጥ በህግ ትፈለጋለህ በማለት አንድን ግለሰብ አላግባብ የገደሉ ሁለት ግለሰቦች በእስራት መቀጣታቸውን የደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን ፖሊስ መምሪያ አስታዉቋል።

የደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን ፖሊስ መምሪያ የኮሚኒኬሽን ፅህፈት ቤት ሀላፊ ምክትል ኢኒስፔክተር ትግሉ ለገሰ ለብስራት ሬዲዮና ቴሌቪዥን እንደተናገሩት አንደኛ ተከሳሽ አሰፋ ሂርፓሳ፣ሁለተኛ ተከሳሽ ደረጄ ምስጋና የተባሉ የአመያ ወረዳ ባሮ ቀበሌ አመራር አካላት ሰኔ 10 ቀን 2016 ዓ.ም ከቀኑ 10 ሰዐት ላይ አቶ አህመድ ሀሰን የተባሉ ግለሰብ መኖሪያ ቤት በመሄድ መሀመድ ኑር ጀማል የተባለው ግለሰብን በህግ ትፈለጋለህ በማለት ከቤት ጎትተው በማውጣት በያዙት በጦር መሣሪያ ተኩሰው እንደገደሉት በማስረጃ ተረጋግጧል።

ሁለቱ የቀበሌ አመራሮች በታጠቁት ክላሽን ኮቭ የጦር መሣሪያ ተጎጂውን በህግ ትፈለጋለህ በማለት ከወሰዱት በኋላ ከህግ ሊያመልጥ ነው ብለው በሁለት ጥይት ጉዳት አድርሰውበት ህይወቱ እንዲያልፍ አድርገዋል።

ሁለቱ የቀበሌ አመራር አካላት የፈፀሙት ያልተገባ ድርጊት ፖሊስ ማስረጃ በማጣራት የምርመራ መዝገቡን ለአቃቤ ህግ የላከ ሲሆን አቃቤ ህግም ከፖሊስ የተላከውን የምርመራ መዝገብ ተመልክቶ በወንጀለኛ መቅጫ ህግ ቁጥር 539 ንዑስ አንቀፅ 1 እና በ 32 ንዑስ አንቀፅ 1 መሠረት በከባድ የሰው መግደል ወንጀል ክስ መስርቷል፡፡ በአቃቤ ህግ የተመሠረተውን ክስ ሲከታተል የነበረው የደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት አንደኛ ተከሳሽ አሰፋ ሂርፓሳ በ13 ዓመት ፅኑ እስራት ሁለተኛ ተከሳሽ ደረጄ ምስጋናው በ14 ዓመት ፅኑ እስራት እንዲቀጡ የተወሰነባቸው መሆኑን ምክትል ኢኒስፔክተር ትግሉ ለገሰ ጨምረው ገልፀዋል።

በሰመኃር አለባቸዉ

🇪🇹🇪🇹🇪🇹

የብስራትን የተለያዩ ማህበራዊ ገጾች በመቀላቀል፤ ወቅታዊ መረጃዎችን እና ፕሮግራሞችን ይከታተሉ…

Facebook: https://bit.ly/3Hng6Qt
Website: https://www.bisrattv.com/
Telegram: https://t.me/Bisrat101fm
YouTube: https://bit.ly/3zAAOrB
Twitter: https://twitter.com/Bisrat101fm
TikTok: https://bit.ly/

ጥር  23፤2017 -   የፖርቶው የመሰመር ተጫዋች ጋሌኖ በ 50 ሚሊዮን ዮሮ የ ሳውዲአረብያውን ቡድን አል አህሊን ለመቀላቀል መቃረቡ ተነግሯል። በቀጣዮቹ ቀናቶች የህክምና ምርመራውን ለማድ...
31/01/2025

ጥር 23፤2017 - የፖርቶው የመሰመር ተጫዋች ጋሌኖ በ 50 ሚሊዮን ዮሮ የ ሳውዲአረብያውን ቡድን አል አህሊን ለመቀላቀል መቃረቡ ተነግሯል። በቀጣዮቹ ቀናቶች የህክምና ምርመራውን ለማድረግ ወደ ሪያድ አንደሚያመራ ይጠበቃል።

በ መሳይ ተስፋዬ ✍️



የብስራትን የተለያዩ ማህበራዊ ገጾች በመቀላቀል፤ ወቅታዊ መረጃዎችን እና ፕሮግራሞችን ይከታተሉ…

Facebook: https://bit.ly/3Hng6Qt
Website: https://www.bisrattv.com/
Telegram: https://t.me/Bisrat101fm
YouTube: https://bit.ly/3zAAOrB
Twitter: https://twitter.com/Bisrat101fm
TikTok: https://bit.ly/

ጥር  23፤2017 -   የሳውዲአረብያ ቡድኖች በቅርብ ሰአታት ውስጥ በ ባርሴሎናው ተከላካይ አንድርያስ ክርስቴንሰን ላይ ፍላጎት ማሳየታቸው ተሰምቷል። በ መሳይ ተስፋዬ ✍️        የብስ...
31/01/2025

ጥር 23፤2017 - የሳውዲአረብያ ቡድኖች በቅርብ ሰአታት ውስጥ በ ባርሴሎናው ተከላካይ አንድርያስ ክርስቴንሰን ላይ ፍላጎት ማሳየታቸው ተሰምቷል።

በ መሳይ ተስፋዬ ✍️



የብስራትን የተለያዩ ማህበራዊ ገጾች በመቀላቀል፤ ወቅታዊ መረጃዎችን እና ፕሮግራሞችን ይከታተሉ…

Facebook: https://bit.ly/3Hng6Qt
Website: https://www.bisrattv.com/
Telegram: https://t.me/Bisrat101fm
YouTube: https://bit.ly/3zAAOrB
Twitter: https://twitter.com/Bisrat101fm
TikTok: https://bit.ly/

ጥር  23፤2017 -   ማርኮ አሴንሲዮ አስቶን ቪላዎች በፊት መስመራቸው ላይ ኢላማ ካደረጓቸው ተጫዋቾች መሀከል ግንባር ቀደሙ ሲሆን የዝውውር መስኮቱ ሳየዘጋ በፊት ቪላ ፓርክ ሊደረስ አንደ...
31/01/2025

ጥር 23፤2017 - ማርኮ አሴንሲዮ አስቶን ቪላዎች በፊት መስመራቸው ላይ ኢላማ ካደረጓቸው ተጫዋቾች መሀከል ግንባር ቀደሙ ሲሆን የዝውውር መስኮቱ ሳየዘጋ በፊት ቪላ ፓርክ ሊደረስ አንደሚችል እየተነገረ ይገኛል።

በ መሳይ ተስፋዬ ✍️



የብስራትን የተለያዩ ማህበራዊ ገጾች በመቀላቀል፤ ወቅታዊ መረጃዎችን እና ፕሮግራሞችን ይከታተሉ…

Facebook: https://bit.ly/3Hng6Qt
Website: https://www.bisrattv.com/
Telegram: https://t.me/Bisrat101fm
YouTube: https://bit.ly/3zAAOrB
Twitter: https://twitter.com/Bisrat101fm
TikTok: https://bit.ly/

ጥር  23፤2017 -   ቼልሲዎች የ ቦሩሽያ ዶርትሞንዱን ግብ ጠባቂ ኮበልን እንደሚፈልጉ እየተነገረ ይገኛል። ነገር ግን ዝውውሩን ለመፈፀም ከዚህ ወር ይልቅ ክረምት ተመራጭ አንደሚሆን ተሰም...
31/01/2025

ጥር 23፤2017 - ቼልሲዎች የ ቦሩሽያ ዶርትሞንዱን ግብ ጠባቂ ኮበልን እንደሚፈልጉ እየተነገረ ይገኛል። ነገር ግን ዝውውሩን ለመፈፀም ከዚህ ወር ይልቅ ክረምት ተመራጭ አንደሚሆን ተሰምቷል።

በ መሳይ ተስፋዬ ✍️
Via ኢንዲፔንደንት



የብስራትን የተለያዩ ማህበራዊ ገጾች በመቀላቀል፤ ወቅታዊ መረጃዎችን እና ፕሮግራሞችን ይከታተሉ…

Facebook: https://bit.ly/3Hng6Qt
Website: https://www.bisrattv.com/
Telegram: https://t.me/Bisrat101fm
YouTube: https://bit.ly/3zAAOrB
Twitter: https://twitter.com/Bisrat101fm
TikTok: https://bit.ly/

ጥር  23፤2017 -   ባየርን ሊቨርኩሰኖች ማሪዮ ሄርሞሶን ከ ሮማ በ ውሰት ማስፈረማቸው ተረጋግጧል። በ መሳይ ተስፋዬ ✍️        የብስራትን የተለያዩ ማህበራዊ ገጾች በመቀላቀል፤ ወቅ...
31/01/2025

ጥር 23፤2017 - ባየርን ሊቨርኩሰኖች ማሪዮ ሄርሞሶን ከ ሮማ በ ውሰት ማስፈረማቸው ተረጋግጧል።

በ መሳይ ተስፋዬ ✍️



የብስራትን የተለያዩ ማህበራዊ ገጾች በመቀላቀል፤ ወቅታዊ መረጃዎችን እና ፕሮግራሞችን ይከታተሉ…

Facebook: https://bit.ly/3Hng6Qt
Website: https://www.bisrattv.com/
Telegram: https://t.me/Bisrat101fm
YouTube: https://bit.ly/3zAAOrB
Twitter: https://twitter.com/Bisrat101fm
TikTok: https://bit.ly/

ጥር  23፤2017 -   ኤሲ ሚላኖች አሁንም ሳንቲያጎ ሂሚኔዝን ለማስፈረም ጥረት እያደረጉ እንደሆነ ተሰምቷል። ሮሴኔሪዎቹ እንደሚታወቀው ስፓኒያርዱን አጥቂ አልቫሮ ሞራታን ለ ጋላታሳራይ አሳ...
31/01/2025

ጥር 23፤2017 - ኤሲ ሚላኖች አሁንም ሳንቲያጎ ሂሚኔዝን ለማስፈረም ጥረት እያደረጉ እንደሆነ ተሰምቷል። ሮሴኔሪዎቹ እንደሚታወቀው ስፓኒያርዱን አጥቂ አልቫሮ ሞራታን ለ ጋላታሳራይ አሳልፈው ሊሰጡ መቃረባቸው እየተሰማ ይገኛል።

በ መሳይ ተስፋዬ ✍️



የብስራትን የተለያዩ ማህበራዊ ገጾች በመቀላቀል፤ ወቅታዊ መረጃዎችን እና ፕሮግራሞችን ይከታተሉ…

Facebook: https://bit.ly/3Hng6Qt
Website: https://www.bisrattv.com/
Telegram: https://t.me/Bisrat101fm
YouTube: https://bit.ly/3zAAOrB
Twitter: https://twitter.com/Bisrat101fm
TikTok: https://bit.ly/

ጥር  23፤2017 -   ኦሎምፒክ ሊዮኖች በይፋ ፖውሎ ፎንሴስካን በአሰልጣኝነት መቅጠራቸው ተሰምቷል።በ መሳይ ተስፋዬ ✍️        የብስራትን የተለያዩ ማህበራዊ ገጾች በመቀላቀል፤ ወቅታዊ...
31/01/2025

ጥር 23፤2017 - ኦሎምፒክ ሊዮኖች በይፋ ፖውሎ ፎንሴስካን በአሰልጣኝነት መቅጠራቸው ተሰምቷል።

በ መሳይ ተስፋዬ ✍️



የብስራትን የተለያዩ ማህበራዊ ገጾች በመቀላቀል፤ ወቅታዊ መረጃዎችን እና ፕሮግራሞችን ይከታተሉ…

Facebook: https://bit.ly/3Hng6Qt
Website: https://www.bisrattv.com/
Telegram: https://t.me/Bisrat101fm
YouTube: https://bit.ly/3zAAOrB
Twitter: https://twitter.com/Bisrat101fm
TikTok: https://bit.ly/

ጥር  23፤2017 -   ጆርዳን ሄንደርሰን ለ አያክስ የልቀቁኝ ጥሪ በማቅረቡ ፀፀት ውስጥ መግባቱ ተገልጿል። አሁን ላይ እንግሊዛዊው አማካኝ በ አያክስ ቤት ለመቆየት መወሰኑ እየተሰማ ይገኛ...
31/01/2025

ጥር 23፤2017 - ጆርዳን ሄንደርሰን ለ አያክስ የልቀቁኝ ጥሪ በማቅረቡ ፀፀት ውስጥ መግባቱ ተገልጿል። አሁን ላይ እንግሊዛዊው አማካኝ በ አያክስ ቤት ለመቆየት መወሰኑ እየተሰማ ይገኛል። ትላንት አመሻሹን እንደሚታወሰው ሄንደርሰን ሞናኮን ሊቀላቀል መሆኑ ሲነገር ቆይቷል።

በ መሳይ ተስፋዬ ✍️



የብስራትን የተለያዩ ማህበራዊ ገጾች በመቀላቀል፤ ወቅታዊ መረጃዎችን እና ፕሮግራሞችን ይከታተሉ…

Facebook: https://bit.ly/3Hng6Qt
Website: https://www.bisrattv.com/
Telegram: https://t.me/Bisrat101fm
YouTube: https://bit.ly/3zAAOrB
Twitter: https://twitter.com/Bisrat101fm
TikTok: https://bit.ly/

ጥር  23፤2017 -   አስቶን ቪላዎች ሳይጠበቁ ለ ማትያስ ኩንሀ ያልተጠበቀ ዝውውር ሊያደርጉ እንደሚችሉ ዘጋርዲያን በፊት ገፁ ይዞት የወጣው መረጃ አመላክቷል። በ መሳይ ተስፋዬ ✍️    ...
31/01/2025

ጥር 23፤2017 - አስቶን ቪላዎች ሳይጠበቁ ለ ማትያስ ኩንሀ ያልተጠበቀ ዝውውር ሊያደርጉ እንደሚችሉ ዘጋርዲያን በፊት ገፁ ይዞት የወጣው መረጃ አመላክቷል።

በ መሳይ ተስፋዬ ✍️



የብስራትን የተለያዩ ማህበራዊ ገጾች በመቀላቀል፤ ወቅታዊ መረጃዎችን እና ፕሮግራሞችን ይከታተሉ…

Facebook: https://bit.ly/3Hng6Qt
Website: https://www.bisrattv.com/
Telegram: https://t.me/Bisrat101fm
YouTube: https://bit.ly/3zAAOrB
Twitter: https://twitter.com/Bisrat101fm
TikTok: https://bit.ly/

ጥር  23፤2017 -   የአፍሪካ ህብረት በሱዳን የመጨረሻ የፖለቲካ ውይይት እንዲደረግ ጠየቀ የአፍሪካ ህብረት የሱዳን የፖለቲካ ቡድኖች በሀገሪቱ ያለውን ችግር ለመፍታት ያለመ ሰፊ የፖለቲካ...
31/01/2025

ጥር 23፤2017 - የአፍሪካ ህብረት በሱዳን የመጨረሻ የፖለቲካ ውይይት እንዲደረግ ጠየቀ

የአፍሪካ ህብረት የሱዳን የፖለቲካ ቡድኖች በሀገሪቱ ያለውን ችግር ለመፍታት ያለመ ሰፊ የፖለቲካ ውይይት ለመጀመር የመጨረሻ ድርድር እንዲያደርጉ መጋበዙን ምንጮች ገልፀዋል። ምክክሩ የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ እንደተጠናቀቀ በየካቲት ወር አጋማሽ በአዲስ አበባ ይካሄዳል ተብሎ እንደሚጠበቅም ምንጮቹ አክለዋል።

ስብሰባዎቹ ባለፉት ወራት በሱዳን ባለድርሻ አካላት መካከል ሰፊ ውይይት ለማካሄድ ዝግጅት ለማድረግ የተካሄዱ ውይይቶች ውጤትን ለመጨረስ ያለመ ነው። የአፍሪካ ህብረት በተለያዩ የሱዳን ወገኖች መካከል የውይይት መንገድ ለመፍጠር የታለመው ሁሉን አቀፍ የፖለቲካ ሂደት አካል ሆኖ በሐምሌ እና ነሐሴ 2023 ሰፊ ምክክር አድርጓል። የአፍሪካ ህብረት የሱዳን ከፍተኛ የፓናል ቡድን ሃላፊ መሀመድ ኢብን ቻምባስ ግብዣዎች ለተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲዎች መላካቸውን ጉዳዩን የሚያውቁ ምንጮች ለሱዳን ትሪቡን ተናግረዋል።

በነሀሴ ወር በተካሄደው የሁለተኛው ዙር ድርድር ተሳታፊዎች የሲቪል ዲሞክራሲያዊ ኃይሎች ማስተባበሪያ (ታጋዱም)፣ የሱዳን ህዝቦች ነፃ አውጪ ንቅናቄ - ኤስ ፒ ኤልኤም-ኤን በአብደል አዚዝ አል ሂሉ የሚመራው፣ የሱዳን ነፃ አውጪ ንቅናቄ (ኤስኤልኤም) የሚመራው አብደል ዋሂድ መሀመድ ኑር እና የሱዳኑ ባአት ፓርቲ በሐምሌ ወር የመጀመሪያው ዙር ከ20 በላይ ቡድኖች፣ ፓርቲዎች፣ የሲቪክ ማህበራት እና የወጣት ቡድኖች የተሳተፉ ሲሆን አብዛኛዎቹ የሱዳን ጦር ኃይሎችን (SAF) የሚደግፉ ናቸው። እነዚህም በጃፋር አል ሚርጋኒ የሚመራው የዲሞክራሲያዊ ቡድን፣ በቲጃኒ ሲሲ የሚመራው የብሄራዊ ንቅናቄ ቡድን እና በሙባረክ አል-ፋዲል አል-ማህዲ የሚመራው የብሄራዊ ስምምነት ጥምረት ይገኙበታል።

በሚሊዮን ሙሴ

🇪🇹🇪🇹🇪🇹

የብስራትን የተለያዩ ማህበራዊ ገጾች በመቀላቀል፤ ወቅታዊ መረጃዎችን እና ፕሮግራሞችን ይከታተሉ…

Facebook: https://bit.ly/3Hng6Qt
Website: https://www.bisrattv.com/
Telegram: https://t.me/Bisrat101fm
YouTube: https://bit.ly/3zAAOrB
Twitter: https://twitter.com/Bisrat101fm
TikTok: https://bit.ly/

ጥር  23፤2017 -   ሀሰተኛ የብር ኖቶች የሚታተምበት እና የሚባዛበት ማሽን በቁጥጥር ስር ዋለ በደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን በቾ ወረዳ እና ወሊሶ ከተማ በተደረገ ፍተሻ የብር ኖቶች የሚታተም...
31/01/2025

ጥር 23፤2017 - ሀሰተኛ የብር ኖቶች የሚታተምበት እና የሚባዛበት ማሽን በቁጥጥር ስር ዋለ

በደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን በቾ ወረዳ እና ወሊሶ ከተማ በተደረገ ፍተሻ የብር ኖቶች የሚታተምበት እና የሚባዛበት ማሽኖች እንዲሁም ሌሎች ቁሳቁሶች ከሀሰተኛ የገንዘብ ኖት ጋር በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን ፖሊስ መምሪያ ገልጿል።

የደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን ፖሊስ መምሪያ የኮምኒኬሽን ፅህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ትግሉ ለገሰ ለብስራት ሬዲዮና ቴሌቪዥን እንደተናገሩት በደቡብ ምዕራፍ ሸዋ ዞን በቾ ወረዳ ቱሉቦሎ ከተማ ውስጥ ጥር 17 2017 ዓ/ም ከቀኑ 11:30 ላይ በሁለት ግለሰቦች እጅ 43ሺህ 2መቶ ሀሰተኛ ብር መያዙን ገልፀው ይህንን ተከትሎ የስርጭት ምንጭ የት እንደሆነ ፖሊስ ባደረገው የክትትል ስራ በርካታ የሀሰተኛ የብር ኖቶች እና የማተሚያ ቁሳቁሶች በቁጥጥር ስር መዋሉን ገልፀዋል።

በዚህ መሰረትም ፖሊስ ከፍርድ ቤት ባወጣው የፍተሻ ትዕዛዝ መሰረትም በወሊሶ ከተማ ውስጥ አቶ ተስፋዬ አንደቦ በተባሉ ግለሰብ ቤት ውስጥ ሀሰተኛ የብር ኖቶች የሚባዛበት እና የሚታተሙበት የተለያዩ ወረቀቶች እና ቀለሞች በተጨማሪም 75,250 ሀሰተኛ የብር ኖቶች መያዙን ገልፀዋል። በዚ ሀሰተኛ ገንዘብ የማተም እና የማሰራጨት ተግባር ላይ የተሰማሩ አምስት ግለሰቦች በቁጥጥር ስር የዋሉ ሲሆን ከነዚህ ግለሰቦች የተለያዩ ማሽኖች እና ማባዣ ፕሪንተሮች መያዛቸውን ገልፀዋል።

ባለ 2መቶ ሀሰተኛ ኖት ብዛቱ 336 ፣ባለ 1መቶ ሀሰተኛ ኖቶች ብዛቱ 78 እና ባለ 50ብር የብር ኖት ሲሆን በአጠቃላይ 75,250 ሀሰተኛ የብር ኖቶች በቁጥጥር ስር ውለው በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ባለሙያዋች ማሽን በተደረገ ማጣራት ሀሰተኛ የብር ኖት መሆናቸው መረጋገጡን ገልፀዋል።

በሰብል አበበ

🇪🇹🇪🇹🇪🇹

የብስራትን የተለያዩ ማህበራዊ ገጾች በመቀላቀል፤ ወቅታዊ መረጃዎችን እና ፕሮግራሞችን ይከታተሉ…

Facebook: https://bit.ly/3Hng6Qt
Website: https://www.bisrattv.com/
Telegram: https://t.me/Bisrat101fm
YouTube: https://bit.ly/3zAAOrB
Twitter: https://twitter.com/Bisrat101fm
TikTok: https://bit.ly/

ጥር  23፤2017 -   ✍️ጥሎ ማለፍ ለመግባት የሚደረገዉ ጨዋታ ሙሉ ድልድል ይህን ይመስላል።✍️በተፈራ ታመነ        የብስራትን የተለያዩ ማህበራዊ ገጾች በመቀላቀል፤ ወቅታዊ መረጃዎችን...
31/01/2025

ጥር 23፤2017 - ✍️ጥሎ ማለፍ ለመግባት የሚደረገዉ ጨዋታ ሙሉ ድልድል ይህን ይመስላል።

✍️በተፈራ ታመነ



የብስራትን የተለያዩ ማህበራዊ ገጾች በመቀላቀል፤ ወቅታዊ መረጃዎችን እና ፕሮግራሞችን ይከታተሉ…

Facebook: https://bit.ly/3Hng6Qt
Website: https://www.bisrattv.com/
Telegram: https://t.me/Bisrat101fm
YouTube: https://bit.ly/3zAAOrB
Twitter: https://twitter.com/Bisrat101fm
TikTok: https://bit.ly/

ጥር  23፤2017 -   የፊሊፒንስ ምክትል ፕሬዝደንት ሳራ ዱቴርቴ በስልጣን ላይ ባልገዋል በሚል በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች አደባባይ በመዉጣት ከስልጣን እንዲነሱ ጠየቁየፊሊፒንስ ምክትል ፕሬዝዳ...
31/01/2025

ጥር 23፤2017 - የፊሊፒንስ ምክትል ፕሬዝደንት ሳራ ዱቴርቴ በስልጣን ላይ ባልገዋል በሚል በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች አደባባይ በመዉጣት ከስልጣን እንዲነሱ ጠየቁ

የፊሊፒንስ ምክትል ፕሬዝዳንት ሳራ ዱቴርቴ ከስልጣን እንዲነሱ በሺዎች የሚቆጠሩ ተቃዋሚዎች በዋና ከተማዋ በማኒላ ጎዳናዎች ላይ ወጥተዋል።በመዲናዋ የሚገኙ ተቃዋሚዎች ሳራ ዱቴርቴ ከስልጣን እንዲወገዱ የሚጠይቁ ምልክቶችን በመያዝ “አሁኑኑ ሳራን ስልጣን ይልቀቁ!” ብለዋል፡፡ አርብ ጠዋት ላይ አደባባይ የወጡ እና በሰልፉ ላይ የተገኙ ሰዎች ወደ 4,000 የሚጠጉ መሆናቸዉን ፖሊስ ገልጿል፤ ባለስልጣናት 7,400 ሁከት የሚቆጣጠሩ የጸጥታ ኃይሎች መሰማራታቸውን አስታውቋል።

ሳራ ዱተርቴ በፕሬዚዳንት ፈርዲናንድ ማርኮስ ጁኒየር አስተዳደር የትምህርት ፀሐፊ ሆና በማገልገል ላይ በነበረችበት ወቅት የመንግስትን ገንዘብ አላግባብ በመጠቀም እና በሚሊዮኖች የሚቆጠር ዶላሮችን በመመዝበር ሶስት ክስ ቀርቦባቸዋል።የተወካዮች ምክር ቤት አባል የሆኑት ፔርሲቫል ሴንዳና፣ ከክስ አቤቱታዎች አንዱን የሚደግፉ ሲሆን፣ ባልደረቦቻቸዉ በፍጥነት እንዲንቀሳቀሱ ግፊት አድርገዋል። በየእለቱ የእንቅስቃሴ-አልባነት መኖሩን በመተቸት " ሳራ ዱተሬት ስልጣን አላግባብ መጠቀም እና ትንኮሳን በቸልታ መቀበላል" አይኖርብንም ሲሉ ለጋዜጠኞች ተናግረዋል።

ክሱ የሚካሄደው በተወካዮች ምክር ቤት አንድ ሶስተኛው አባላት ድጋፍ ሲያገኝ ብቻ ነው፣ የተከሰሱ ባለስልጣን በሴኔት ሁለት ሶስተኛ ድምጽ ከተሰጠባቸዉ ከስልጣን ሊነሱ ይችላሉ።የፊሊፒንስ ሰዎች እዚህ አሉ፣ ለእውነት እና ለፍትህ ለመቆም ዝግጁ ናቸው። እንዳንሰናከላቸው ፣ ሲሉ ሲንዳና ተናግረዋል፡፡የ 46 ዓመቷ ምክትል ፕሬዝዳንት ፕሬዝዳንት ማርኮስ የስልጣን ተግባራቸውን መወጣት ካልቻሉ በህገ መንግሥታዊ ስርዓት መሰረት የመተካት ሚና ይኖራቸዋል፡፡ ምክትል ፕሬዚዳንቱ የተከሰሱባቸውን ውንጀላዎች ፖለቲካዊ በማለት ውድቅ አድርገዋል።

በስምኦን ደረጄ



የብስራትን የተለያዩ ማህበራዊ ገጾች በመቀላቀል፤ ወቅታዊ መረጃዎችን እና ፕሮግራሞችን ይከታተሉ…

Facebook: https://bit.ly/3Hng6Qt
Website: https://www.bisrattv.com/
Telegram: https://t.me/Bisrat101fm
YouTube: https://bit.ly/3zAAOrB
Twitter: https://twitter.com/Bisrat101fm
TikTok: https://bit.ly/

ጥር  23፤2017 -   ✍️ሩዲገር ስለ ሙሳ ዴምቤሌ ሲናገር ቶተንሃምን አለማክበር ሳይሆን ዴምቤሌ ለምን በትልቅ ክለብ ደረጃ መጨዋት እንዳልቻለ አይገባኝም ምክንያቱም ሁሉም ነገር አለዉ በጣ...
31/01/2025

ጥር 23፤2017 - ✍️ሩዲገር ስለ ሙሳ ዴምቤሌ ሲናገር ቶተንሃምን አለማክበር ሳይሆን ዴምቤሌ ለምን በትልቅ ክለብ ደረጃ መጨዋት እንዳልቻለ አይገባኝም ምክንያቱም ሁሉም ነገር አለዉ በጣም ጠንካራ ክህሎትን የታደለ ተጨዋች ነዉ በማለት ተናግሯል።

✍️በተፈራ ታመነ Via Sky sport



የብስራትን የተለያዩ ማህበራዊ ገጾች በመቀላቀል፤ ወቅታዊ መረጃዎችን እና ፕሮግራሞችን ይከታተሉ…

Facebook: https://bit.ly/3Hng6Qt
Website: https://www.bisrattv.com/
Telegram: https://t.me/Bisrat101fm
YouTube: https://bit.ly/3zAAOrB
Twitter: https://twitter.com/Bisrat101fm
TikTok: https://bit.ly/

ጥር  23፤2017 -   ✍️በአርሰናል በጥብቅ የሚፈለገዉ የ18 ዓመቱ ኖርዊያዊዉ አማካኝ ስቨር ኒፓን እስከ ዉድድር ዓመቱ መጨረሻ በክለቡ ሮዘንበርግ እንደሚቆይ ተነግሯል።✍️በተፈራ ታመነ V...
31/01/2025

ጥር 23፤2017 - ✍️በአርሰናል በጥብቅ የሚፈለገዉ የ18 ዓመቱ ኖርዊያዊዉ አማካኝ ስቨር ኒፓን እስከ ዉድድር ዓመቱ መጨረሻ በክለቡ ሮዘንበርግ እንደሚቆይ ተነግሯል።

✍️በተፈራ ታመነ Via The Athletic



የብስራትን የተለያዩ ማህበራዊ ገጾች በመቀላቀል፤ ወቅታዊ መረጃዎችን እና ፕሮግራሞችን ይከታተሉ…

Facebook: https://bit.ly/3Hng6Qt
Website: https://www.bisrattv.com/
Telegram: https://t.me/Bisrat101fm
YouTube: https://bit.ly/3zAAOrB
Twitter: https://twitter.com/Bisrat101fm
TikTok: https://bit.ly/

Address

Lancha
Addis Ababa
1000

Opening Hours

Monday 06:00 - 00:00
Tuesday 06:00 - 00:00
Wednesday 06:00 - 00:00
Thursday 06:00 - 00:00
Friday 06:00 - 00:00
Saturday 06:00 - 00:00
Sunday 06:00 - 00:00

Telephone

+251904150092

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Bisratfm101.1 posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Bisratfm101.1:

Share