Ethiopian Independent/ሉዓላዊት ኢትዮጵያ

Ethiopian Independent/ሉዓላዊት ኢትዮጵያ fast and real information provide for the audiance

የጨዋታ አሰላለፍ !4:00 ቼልሲ ከ ፒኤስጂ
13/07/2025

የጨዋታ አሰላለፍ !

4:00 ቼልሲ ከ ፒኤስጂ

13/07/2025

በነገራችን ላይ በዛሬው ጫወታ ...
የአርሰናል እና የማንችስተር ዩናይትድ ደጋፊዎች ማንን የሚደግፋ ይመስላችኋል ?🤭

The   Final.
13/07/2025

The Final.

Red and Blue high above New York 🌆🤩Source:- PSG FC official page
13/07/2025

Red and Blue high above New York 🌆🤩

Source:- PSG FC official page

Chelsea fans landing 🛬 soon in America 🇺🇸 for our final game.Source:-From Chelsea official page.
13/07/2025

Chelsea fans landing 🛬 soon in America 🇺🇸 for our final game.

Source:-From Chelsea official page.

🏆
13/07/2025

🏆

ይገምቱ ይሸለሙ 🏆 የቸልሲ እና ፒስጅ ጨዋታ ውጤት ገምተው በትክክል ላወቁ ሶስት ቤተሰቦቻችን ....1ኛ.ቀድሞ የገመተ፣ወጤቱን ያወቀ እና ግብ አስቆጣሪዎቹን ያወቀ ከሆነ=10,000 ብር ይሸለ...
13/07/2025

ይገምቱ ይሸለሙ 🏆


የቸልሲ እና ፒስጅ ጨዋታ ውጤት ገምተው በትክክል ላወቁ ሶስት ቤተሰቦቻችን ....

1ኛ.ቀድሞ የገመተ፣ወጤቱን ያወቀ እና ግብ አስቆጣሪዎቹን ያወቀ ከሆነ=10,000 ብር ይሸለማል

2ኛ. ቀድሞ የገመተ እና ውጤቱን በትክክል የገመተ ከሆነ=7,500 ብር ይሸለማል

3ኛ. ውጤቱን ብቻ በትክክል የገመተ ከሆነ=5,000 ብር የምንሸልምዎ ይሆናል።

የውድድሩ ህጎች ምን ይመስላሉ ?

√ ተሳታፊዎች ግምቶቻቸውን ከዚህ ፖስት ስር ባለው የሀሳብ መስጫ ሳጥን #ብቻ ማስቀመጥ ይኖርባቸዋል።

√ ኤዲት የተደረጉ ምላሾች በፍፁም ተቀባይነት አይኖራቸውም።

√ ግምትዎን መላክ የሚቻለው እስከ 10:30 ሰዓት ብቻ ነው።

🔴 ይነበብ
✍አንድ የቤተሰባችን አባል ለአስር የቤተሰቡ አባሎች ራሱም ማድረግ አለበት።
✍አንድ የቤተሰባችን አባል ግምት ማስቀመጥ የሚችለው #አንዴ ብቻ ነው። ከአንድ ጊዜ በላይ የመለሰ ቤተሰባችን ሽልማት አይደርሰውም።

መልካም ዕድል !

ይሄ መንግስት ምን ሰራ?ብዙዎች ይሄ መንግስት ምን ሰራ? ሲሉ እሰማለሁ። የሰራው ብዙ ይኖራል። ለኔ ግን ከስራዎቹ ሁሉ የሚገዝፍብኝ እቺ እናት የተናገረችው ነው! በዚህ መንግስት ለምነውና፣ ተ...
11/07/2025

ይሄ መንግስት ምን ሰራ?

ብዙዎች ይሄ መንግስት ምን ሰራ? ሲሉ እሰማለሁ። የሰራው ብዙ ይኖራል። ለኔ ግን ከስራዎቹ ሁሉ የሚገዝፍብኝ እቺ እናት የተናገረችው ነው!

በዚህ መንግስት ለምነውና፣ ተሰቃይተው፣ ለልጆቻቸው ሲሉ ማይደረግ ነገር ሁሉ አድርገው ይኖሩ የነበሩ እናቶች አርፈዋል። እፎይ ብለዋል!

በአዲስ አበባ ብቻ ከስድስት መቶ ሺ በላይ ህፃናት በየአመቱ ዩኒፎርምና የትምህርት ቁሳቁስ ተሟልቶላቸው። በቀን ሁለቴ ትምህርት ቤት ውስጥ በነፃ እየተመገቡ በነፃ ይማራሉ። ያለምንም ግብረሰናየረ ድርጅት ድጋፍ ሙሉ ወጪውን የሚሸፍነው መንግስት ነው።

ቁጥሩን ማንም በቀላሉ ማጣራት ይችላል። ከግማሽ ሚሊዮን በላይ የደሃ ልጆች ያለምንም መሳቀቅ ከክፍል ባልንጀሮቻቸው እኩል በቀን ሁለቴ ይመገባሉ። እኩል ዩኒፎርም ይለብሳሉ። እኩል የትምህርት ቁሳቁስ ይሟላላቸዋል። “እናት” አዲስ አበባ ላይ “ልጄን ምን ላብላ?” ማለት ካቆመች አመታት አለፏት። ሙሉ ወጪዋን መንግስት ይሸፍናል።ምእሱ ብቻ አይደለም። ስራ የሌላቸው የተማሪዎቹ እናቶች ደሞዝ እየተከፈላቸው የልጆቻቸውን ምግብ ትምህርት ቤት ውስጥ እንዲሰሩ ተደርጓል።

ጥያቄው .... ስለዚህ አስገራሚና አስደናቂ ተግባር የሚያወራ ገለልተኛ ጋዜጠኛ ወይም አክቲቪስት አይታችሁ ታውቃላችሁ ወይ? መልሱን ለናንተ እያልኩኝ ..... ይሄ ፕሮጀክት ተፈፃሚ እንዲሆን የወሰኑትን ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ፣ መሬት ያወረዱትን የቀድሞ የአዲስ አበባ ከንቲባ ታከለ ኡማ፣ እስካሁኗ ሰአት ድረስ በፊት ከነበረው አስፋፍተውና የበለጠ አጠናክረው በየቀኑ ያለመሰልቸት እየተከታተሉ ያስቀጠሉትን የአዲስ አበባ ከንቲባ ወይዘሮ አዳነች አቤቤና ጠቅላላ አመራሮችን ሁሉ በደሃ እናትና አባቶች ስም እናመሠግናለን!!

BREAKING NEWS Trump announces ‘CEASEFIRE’ between Iran and Israel.
24/06/2025

BREAKING NEWS

Trump announces ‘CEASEFIRE’ between Iran and Israel.

ብሔራዊ ቤተመንግሥት ለጉብኝት ክፍት ተደርጓል።  :- ብሔራዊ ቤተ-መንግስት ሙዚየም ከማክሰኞ በስተቀር ከጠዋት 3 ሰዓት እስከ 11 ሰዓት ለህዝብ እይታ ክፍት ይሆናል ተብሏል።መግቢያው ስንት ...
17/06/2025

ብሔራዊ ቤተመንግሥት ለጉብኝት ክፍት ተደርጓል።

:- ብሔራዊ ቤተ-መንግስት ሙዚየም ከማክሰኞ በስተቀር ከጠዋት 3 ሰዓት እስከ 11 ሰዓት ለህዝብ እይታ ክፍት ይሆናል ተብሏል።

መግቢያው ስንት ነው ?

🎫 መደበኛ ዋጋ 300 ብር

🟡 ልዩ ቲኬት 1ሺህ ብር ነው ተብሏል።

ምን ይዟል ?

🚗 የመኪና ሙዚየም ፣

👑 እዮቤ ልዩ ቤተ-መንግስት ሙዚየም፣

🎁 የቤተ-መንግስት ቋቁሶች እና የተለያያዩ ሀገራት ስጦታዎች ለጉብኝቱ መመቻቸታቸው ተገልጿል።

ምንጭ:- EBC

እንኳን ለ1446ኛው የዒድ አል አድሃ (አረፋ) በዓል አደረሳችሁ!ኢድ ሙባረክ
06/06/2025

እንኳን ለ1446ኛው የዒድ አል አድሃ (አረፋ) በዓል አደረሳችሁ!

ኢድ ሙባረክ

የኢድ ሶላት ተጀምሮ እስከሚጠናቀቅ ለተሽከርካሪ ዝግ የሚሆኑ መንገዶች ይፋ ተደረጉበእስልምና ዕምነት ተከታዮች ዘንድ ነገ ግንቦት 29 ቀን 2017 ዓ/ም የሚከበረው 1 ሺሕ 446ኛው የኢድ አል...
05/06/2025

የኢድ ሶላት ተጀምሮ እስከሚጠናቀቅ ለተሽከርካሪ ዝግ የሚሆኑ መንገዶች ይፋ ተደረጉ

በእስልምና ዕምነት ተከታዮች ዘንድ ነገ ግንቦት 29 ቀን 2017 ዓ/ም የሚከበረው 1 ሺሕ 446ኛው የኢድ አል አድሀ (አረፋ) በዓል ምክንያት በማድረግ በአዲስ አበባ የሚከናወነው የኢድ ሶላት ስነ ስርዓት ተጀምሮ እስከሚጠናቀቅ የተወሰኑ መንገዶች ለተሽከርካሪ ዝግ እንደሚደረጉ የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል፡፡

በመሆኑም የትራፊክ መጨናነቅ እንዳይፈጠር አሽከርካሪዎች ከዚህ በታች የተገለፁት መንገዶች ዝግ መሆናቸውን ተገንዝበው ሌሎች አማራጮችን እንዲጠቀሙ አሳስቧል፡፡

በዚህም መሠረት፡-

• ከመገናኛ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ቅዱስ ኡራኤል አደባባይ ላይ

• ከኦሎምፒያ አደባባይ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ኦሎምፒያ አደባባይ ላይ

• ከጋዜቦ አደባባይ ወደ ደንበል የሚወስደው መንገድ ጋዜቦ አደባባይ ላይ

• ከጎተራ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ አጎና ሲኒማ መስቀለኛ ላይ

• ከጎፋ በአዲሱ መንገድ ወደ ለገሃር መብራት የሚወስደው መንገድ ቅዱስ ቂርቆስ ቤ/ክ መስቀለኛ ላይ

• ከቡልጋሪያ ወደ ሜክሲኮ አደባባይ የሚወስደው መንገድ ላንድ ማርክ ሆስፒታል አካባቢ

• ከሳር ቤት ወደ ሜክሲኮ አደባባይ የሚወስደው መንገድ አፍሪካ ህብረት ትራክ መብራቱ መስቀለኛ ላይ

• ከጦር ኃይሎች በልደታ ከፍተኛ ፍ/ቤት ወደ ለገሃር የሚወስደው መንገድ ከፍተኛ ፍ/ቤትአደባባይ አካባቢ

• ከኑር ህንፃ ወደ ባልቻ ሆስፒታል የሚወስደው መንገድ ኑር ህንፃ መስቀለኛ ላይ

• ከፈረሰኛ መብራት ወደ ጨፌ ሜዳ የሚወስደው መንገድ ጨፌ ሜዳ ትራፊክ መብራት አጠገብ

• ከበርበሬ በረንዳ ወደ አምስተኛ ፖሊስ ጣቢያ የሚወስደው መንገድ በርበሬ በረንዳ አካባቢ

• ከተ/ሃይማኖት በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ወደ ጎማ ቁጠባ ተ/ሃይማኖት አደባባይ

• ከሰንጋ ተራ 40/60 ኮንደሚኒየም ወደ ሠንጋ ተራ መብራት ሰንጋ ተራ 40/60 መስቀለኛ አካባቢ

• ከጌጃ ሰፈር በአምስተኛ ፖሊስ ጣቢያ የሚሄዱ አሽከርካሪዎች ጎማ ቁጠባ አካባቢ

• ከተ/ሃይማኖት አደባባይ ወደ ቴዎድሮስ አደባባይ ተ/ሃይማኖት አደባባይ አካባቢ

• ከሜትሮሎጂ መታጠፊያ ወደ ድሮ EBC የሚወስደው መንገድ ሜትሮሎጂ መታጠፊያ

• ከጎላ ቅዱስ ሚካኤል መስቀለኛ ወደ ኢሚግሬሽን የሚወስደው መንገድ ኢምግሬሽን መስቀለኛ አካባቢ

• ከፒያሳ በቸርችል ጎዳና ወደ ለገሃር የሚወስደው መንገድ ቴዎድሮስ አደባባይ አካባቢ

• ከ ንግድ ማተሚያ ቤት ወደ ፍልውሃ ንግድ ማተሚያ መስቀለኛ መንገዱ አካባቢ

• ከፓርላማ መብራት ወደ ውጭ ጉዳይ ፓርላማ መብራት ላይ

• ከኮንሰን መታጠፊያ ወደ ውጭ ጉዳይ የሚወስደው መንገድ ኮንሰን መታጠፊያ አካባቢ

• ከሴቶች አደባባይ ወደ ካዛንቺስ የሚወስደው መንገድ ሴቶች አደባባይ ላይ መንገዶች ለተሽከርካሪ ዝግ ይሆናሉ ተብሏል፡፡
በተመሳሳይ በአቃቂ ቃሊቲ ክ/ከተማ ዓለም ባንክ መስቀለኛ አካባቢ ከሚከበረው በዓል ጋር ተያይዞ የተወሰኑ መንገዶች ለተሽከርካሪ ዝግ እንደሚደረጉ ተገልጿል፡፡

በዚህም መሠረት፡-
• ከዩኒሳ አደባባይ ወደ በላይ አብ መኪና መገጣጠሚያ የሚወስደው መንገድ

• ከቱሉዲምቱ - ወደ ጨፌ ይርጋ አደባባይ እስከ ዓለም ባንክ መስቀለኛ የሚወስደው መንገድ

እንዲሁም ከፌሮ ድልድይ እስከ ዩኒሳ አደባባይ የሚወስደው መንገድ ከሌሊቱ 10፡00 ጀምሮ ለተሽከርካሪ ዝግ ይሆናል፡፡

ከዚህ በተጨማሪም ዛሬ በበዓሉ ዋዜማ ከምሽት 12፡00 ሰዓት ጀምሮ ከላይ በተጠቀሱት ቦታዎች ላይ ተሽከርካሪዎችን ለአጭርም ይሁን ለረጅም ሠዓት ማቆም የተከለከለ መሆኑ ተገልጿል፡፡

ህብረተሰቡም ከፖሊስ የሚሰጠውን መረጃ ተገንዝቦ የትራፊክ ፖሊስ አባላት በሚጠቁሙት አማራጭ መንገዶች እንዲጠቀም እና ለትራፊክ ፖሊስ አባላት ትዕዛዝ አስፈላጊውን ትብብር እንዲያደርግ የአዲስ አበባ ፖሊስ ጥሪውን አስተላልፏል።

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethiopian Independent/ሉዓላዊት ኢትዮጵያ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share