Ethio Fact Info

Ethio Fact Info ቅንልብ ያላቸው ሁሌም ደስተኞች ናቸው

ዴቪድ ዴህያ ወደ ኦልትራፎርድበማንቼስተር ዩናይትድ ቤት የራሳቸውን ዐሻራ አሳርፈው ካለፉ እና አሁንም ድረስ በኦልድትራፎርድ ከሚናፈቁ ተጫዋች መካከል አንዱ ነው ስፔናዊው ግብ ጠባቂ ዴቪድ ዴህ...
08/08/2025

ዴቪድ ዴህያ ወደ ኦልትራፎርድ

በማንቼስተር ዩናይትድ ቤት የራሳቸውን ዐሻራ አሳርፈው ካለፉ እና አሁንም ድረስ በኦልድትራፎርድ ከሚናፈቁ ተጫዋች መካከል አንዱ ነው ስፔናዊው ግብ ጠባቂ ዴቪድ ዴህያ፡፡

ሰር አሌክስ ፈርጉሰን በ2012/13 የውድድር ዓመት የሊጉን ዋንጫ አሳክተው ከዩናይትድ ጋር ከተለያዩ በኋላ ቡድኑ ደካማ የውድድር ዓመታትን ሲያሳልፍ እሱ በግሉ ምርጥነቱን በተደጋጋሚ አሳይቷል፡፡

ከፈርጉሰን መልቀቅ በኋላ ወደ ኦልድትራፎርድ የመጡ የተለያዩ አሰልጣኞች ቡድኑን ወደ ክብሩ መመለስ ባይችሉም ዴህያ ብቻውን ጨዋታዎችን አሸንፎ የሚወጣ ግብ ጠባቂ ነበር፡፡ ለዚህም የቀድሞ የአርሰናል አሰልጣኝ አርሰን ቬንገር “ግብ ጠባቂ አንድን ጨዋታ ብቻውን አሸንፎ ከወጣ እሱ ዴቪድ ዴህያ ብቻ ነው” ሲሉ ምስክርነታቸውን ሰጥተዋል።

ከዴቪድ ሞዬስ እስከ ሊዊ ቫንሀል፤ ከጆዜ ሞሪኒሆ እስከ ኦሊጉነር ሶልሸር፤ ከራልፍ ራኚክ እስከ ኤሪክ ቴንሀግ ባሉ አሰልጣኞች ስር ማንቼስተር ዩናይትድ በፊት በሚታወቀው ገናናነቱ መቀጠል ባይችልም እሱ ግን ብቻውን ልዩ ነበር፡፡

አሰልጣኝ ኤሪክ ቴንሀግ ለእኔ የአጨዋወት ፍልስፍና ዴህያ አይሆንም በማለት ገፍተው እንዳስወጡት የሚታወስ ሲሆን፤ ዴህያን በማባረር ያመጡት ግብ ጠባቂ አንድሬ ኦናና በየጨዋታው ስህተት የሚሰራ እና በርካታ ጎል የሚቆጠርበት ግብ ጠባቂ ሆኖ ቡድኑን ዋጋ እያስከፈለ ይገኛል፡፡

ይህንንም የተመለከቱ የማንቼስተር ዩናይትድ ደጋፊዎች እሱን መናፈቅ እና በድጋሚ በኦልድትራርድ መመልከት የሁል ጊዜ ምኞታቸው ነው፡፡

የቀያይ ሰይጣኖቹ ደጋፊዎች ዴህያን ቢናፍቁ አያስገርምም፤ ቡድናቸው ማንቼስተር ዩናይትድ ፈርጉሰንን ካጣ በኋላ ባለፉት ዓመታት ጨዋታዎችን ለማሸነፍ በሚቸገረው ቡድን ውስጥ የዴህያ አዳኝ እጆች ከጨዋታው ነጥብ እንዲያገኙ ሚናው የሚተካ አልነበረም፡፡

የድንቅ ችሎታ እና ተሰጥኦ ባለቤቱ ዴህያ በሚቸገረው ዩናይትድ ውስጥ በእሱ ልዩነት ፈጣሪነት ክለቡ ጨዋታዎችን አሸንፎ ሲወጣ መመልከት የተለመደ ነበር፡፡

ዩናይትድን ከለቀቀ በኋላ ለአንድ ውድድር ዓመት ያህል ክለብ አልባ ሆኖ ከቆየ በኋላ ወደ ጣሊያን በመጓዝ ፊዮረንቲናን መቀላቀሉ ይታወሳል፡፡ በተጠናቀቀው የውድድር ዓመት ፊዮረንቲና በጣሊያን ሴሪ ኤ 6ኛ ደረጃን ይዞ እንዲያጠናቅቅ ዴቪድ ዴህያ ትልቁን አስተዋፅኦ አበርክቷል፡፡

እንደተለመደው ሁሉ ስፔናዊው ግብ ጠባቂ ዴቪድ ዴህያ በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ያሳይ የነበረውን ድንቅ እንቅስቃሴ በጣሊያን ሴሪኤ በድጋሚ አሳይቷል፡፡

የማንችስተር ዩናይትድ የቀድሞ ግብ ጠባቂ ዴቪድ ዴህያ 12 ዓመታትን ካሳለፈበት ክለቡ በፈረንጆቹ 2023 በነፃ መልቀቁ የሚታወስ ሲሆን÷ ነገ ወደ ኦልትራፎርድ በመምጣት የቀድሞ ክለቡን በተቃራኒ ይገጥማል፡፡

ዴቪድ ዴህያ የጨዋታው ቀን ከመድረሱ አስቀድሞ ወደ ኦልትራፎርድ መጥቶ እንደሚጫወት በማህበራዊ ትስስር ገጽ ላይ ካሰፈረ በኋላ በኦልድትራፎርድ በጉጉት እየተጠበቀ ይገኛል፡፡

ብሩኖ ፈርናንዴዝ እና ዴቪድ ዴህያ ከነገው ጨዋታ አስቀድሞ በማህበራዊ ትስስር ገፅ በተለዋወጡት መልዕክት፤ ፈርናንዴዝ ጎል እንደማስቆጥርብህ ተስፋ አደርጋለሁ ሲል ዴህያ በበኩሉ እንገናኛለን የሚል ምላሽ ሰጥቶታል፡፡

ነገ 8 ሰዓት ከ45 ላይ ማንቼስተር ዩናይትድ የጣሊያኑን ክለብ ፊዮረንቲናን በሜዳው ኦልድትራርድ ያስተናግዳል፡፡ ምንም እንኳን በእነሱ በኩል ተሰልፎ ባይጫወትም ዩናይትዶች የናፈቃቸውን ውድ ልጃቸውን ዴቪድ ዴህያን በኦልድትራፎርድ ሲጫወት ይመለከቱታል፡፡

ክርስቲያኖ ሮናልዶና ጠቅላይ ሚንስትር ኬር ስታርሜር በዲየጎ ዦታ ህልፈት ሀዘናቸውን ገለጹ በመኪና አደጋ ህይወቱ ያለፈው የሊቨርፑሉ  አጥቂ ዲየጎ ዦታን በተመለከተ ብዙዎች ሀዘናቸውን እየገለጹ...
03/07/2025

ክርስቲያኖ ሮናልዶና ጠቅላይ ሚንስትር ኬር ስታርሜር በዲየጎ ዦታ ህልፈት ሀዘናቸውን ገለጹ

በመኪና አደጋ ህይወቱ ያለፈው የሊቨርፑሉ አጥቂ ዲየጎ ዦታን በተመለከተ ብዙዎች ሀዘናቸውን እየገለጹ ይገኛሉ፡፡

የፖርቹጋል ብሔራዊ ቡድን አምበል ክርስቲያኖ ሮናልዶ ለዦታ ቤተሰቦች፣ ለባለቤቱ ለልጆቹ እና ለአድናቂዎቹ መጽናናትን ተመኝቷል፡፡ የአል ናስሩ አጥቂ ሮናልዶ በብሔራዊ ቡድን ከዦታ ጋር አብሮ ተጫውቷል፡፡

የእንግሊዝ ጠቅላይ ሚንስትር ኬር ስታርሜር በድንገተኛው የፖርቹጋላዊ ተጫዋች ህልፈት ሀዘናቸውን ገልጸዋል፡፡ ተጫዋቾች እንዲሁም ደጋፊዎች የ28 አመቱን ኮከብ ህልፈት ተከትሎ ሀዘናቸውን እየገለጹ ይገኛሉ፡፡ ከታናሽ ወንድሙ ጋር ህይወቱ ያለፈው ዲየጎ ዦታ የሶስት ልጆት አባት ሲሆን በቅርቡ ነበር የተሞሸረው፡፡

ዓለም የጋዛ እልቂትን ሊዘነጋው አይገባም - አንቶኒዮ ጉተሬዝ..........................አለም በጋዛ ያለው ጦርነት እያደረሰው ያለውን እልቂት ሊዘነጋው አይገባም ሲሉ የመንግስታቱ...
29/06/2025

ዓለም የጋዛ እልቂትን ሊዘነጋው አይገባም - አንቶኒዮ ጉተሬዝ..........................

አለም በጋዛ ያለው ጦርነት እያደረሰው ያለውን እልቂት ሊዘነጋው አይገባም ሲሉ የመንግስታቱ ድርጅት ዋና ጸሐፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ ተናገሩ፡፡ በጋዛ እስካሁን 56 ሺህ ገደማ ሰዎች መሞታቸውን መረጃዎች አመላክተዋል፡፡

የንፁሃን ግድያ አሁንም አልቆመም ያሉት የመንግስታቱ ድርጅት ዋና ጸሐፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ ዘላቂ የተኩስ አቁም ስምምነት እንዲደረስ መስራት ያስፈልጋል ብለዋል፡፡

በተለይ በእስራኤል እና ኢራን ግጭት ወቀት ጋዛ ተዘንግቷል ያሉት ዋና ጸሐፊው ይህን ግጭት እልባት ለመስጠት የተሰጠው ትኩረት ጋዛ ላይም መደረግ አለበት ሲሉ ተናግረዋል፡፡

በእስራኤል እና ኢራን መካከል የተደረሰው የተኩስ አቁም ተስፋ የሚሰጥ መሆኑንም ገልፀዋል:: በቀጣይ በጋዛ የተኩስ አቁም ስምምነት እንዲደረስ ብዙ መሰራት አለበት ማለታቸውን ሲጂቲኤን ዘግቧል፡፡

ፕሬዚዳንት ረጀብ ጣይብ ኤርዶኻን እና ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በሔግ ተወያዩ .....................የቱርኪዬው ፕሬዚዳንት ረጀብ ጣይብ ኤርዶኻን እና ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በ...
25/06/2025

ፕሬዚዳንት ረጀብ ጣይብ ኤርዶኻን እና ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በሔግ ተወያዩ .....................

የቱርኪዬው ፕሬዚዳንት ረጀብ ጣይብ ኤርዶኻን እና ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በዘ ሔግ እየተካሄደ ካለው የኔቶ ጉባኤ ጎን ለጎን ተገናኝተው በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይተዋል።

ሁለቱ መሪዎች በትናንትናው ዕለት ባደረጉት ውይይት በቀጣናዊ እና ዓለም አቀፋዊ እንዲሁም የሁለትዮሽ ጉዳዮች ላይ መክረዋል። ፕሬዚዳንት ኦርዶኻን በዚሁ ወቅት በአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ጥረት የተደረሰውን የእስራኤል እና የኢራን የተኩስ አቁም ስምምነት በበጎ እንደተቀበሉት ገልጸዋል።

ፕሬዚዳንቱ ዘላቂ ሰላም እንዲመጣ፣ በጋዛ ያለው ቀውስ እንዲያከትም እና በዩክሬን ጉዳይ ላይ ንግግር እንዲቀጥል መጠየቃቸውን የቱርኪዬ የኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ባወጣው መግለጫ ጠቁሟል። ሀገራቸው በኢነርጂ፣ በኢንቨስትመንት እና በመከላከያ ዘርፍ ከአሜሪካ ጋር በትብብር መሥራት የምትችልባቸው አማራጮች መኖራቸውን ገልጸዋል።

በተለይም በሁለቱ ሀገራት መካከል የሚደረገውን የንግድ ልውውጥ ወደ 100 ቢሊዮን ዶላር ከፍ የማድረግ ዓላማን ለማሳካት የሚያስችል ዕድል እንዳለም መጠቆማቸው ነው የተገለጸው። ሁለቱ ፕሬዚዳንቶች በኔቶ ውስጥ ግንባር ቀደም አጋሮች በመሆን የድርጅቱን የመከላከያ አቅም ማሳደግ አስፈላጊ መሆኑን አስምረውበታል ሲል የዘገበው አናዶሉ ነው።

እስራኤል ለመካከለኛው ምስራቅ ሰላም ትልቁ እንቅፋት ነች ሲሉ ኤርዶጋን ተናገሩ የቱርኩ ፕሬዝዳንት ሬሲፕ ጣይብ ኤርዶጋን እንዳሉት እስራኤል በኢራን ላይ ያደረሰችው ጥቃት ከአሜሪካ ጋር አዲስ ...
21/06/2025

እስራኤል ለመካከለኛው ምስራቅ ሰላም ትልቁ እንቅፋት ነች ሲሉ ኤርዶጋን ተናገሩ

የቱርኩ ፕሬዝዳንት ሬሲፕ ጣይብ ኤርዶጋን እንዳሉት እስራኤል በኢራን ላይ ያደረሰችው ጥቃት ከአሜሪካ ጋር አዲስ ዙር የኒውክሌር ድርድር ቴህራን ከመጀመሩ በፊት በመሆኑ “ድርድሩን ለማበላሸት” ያለመ ነው ብለዋል።

የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በተገኙበት በኢስታንቡል በተካሄደው የዲፕሎማቲክ ኮንፈረንስ ላይ ንግግር ያደረጉት ኤርዶጋን የእስራኤልን “ፍፁም የሽፍታ ድርጊት አወግዛለው በማለት መካከለኛው ምስራቅን ለማተራመስ እየሞከረች ነው ሲሉ ከሰዋል።

የቱርኩ ፕሬዝዳንት የኔታኒያሁ መንግስት ለአካባቢው ሰላም እጅግ በጣም ወሳኝ እንቅፋት መሆኑን እያረጋገጡ ነው" ብለዋል።
አክለውም “የኔታንያሁ መንግስት ሰኔ 13 ላይ ያደረሰው ጥቃት የድርድር ሂደቱን ለማዳከም ያለመ ነው ብለዋል።
እስራኤል ለመካከለኛው ምስራቅ ሰላም ትልቁ እንቅፋት ነች ሲሉ ኤርዶጋን ተናገሩ

የቱርኩ ፕሬዝዳንት ሬሲፕ ጣይብ ኤርዶጋን እንዳሉት እስራኤል በኢራን ላይ ያደረሰችው ጥቃት ከአሜሪካ ጋር አዲስ ዙር የኒውክሌር ድርድር ቴህራን ከመጀመሩ በፊት በመሆኑ “ድርድሩን ለማበላሸት” ያለመ ነው ብለዋል።

የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በተገኙበት በኢስታንቡል በተካሄደው የዲፕሎማቲክ ኮንፈረንስ ላይ ንግግር ያደረጉት ኤርዶጋን የእስራኤልን “ፍፁም የሽፍታ ድርጊት አወግዛለው በማለት መካከለኛው ምስራቅን ለማተራመስ እየሞከረች ነው ሲሉ ከሰዋል።

የቱርኩ ፕሬዝዳንት የኔታኒያሁ መንግስት ለአካባቢው ሰላም እጅግ በጣም ወሳኝ እንቅፋት መሆኑን እያረጋገጡ ነው" ብለዋል።
አክለውም “የኔታንያሁ መንግስት ሰኔ 13 ላይ ያደረሰው ጥቃት የድርድር ሂደቱን ለማዳከም ያለመ ነው ብለዋል።

"ከምስጉን ታዎቂ የቀዶ ህክምና ስፔሻሊስት የተላከ መልዕክት"ውድ የኢትዮጵያ ህዝብ ሆይ: ስራ የምናቆመው:-1. የተሻለ ህክምና እንደሚገባህ ስለምናምን የጤና ስርዓቱ ይሻሻል ብንል ሰሚ ስለአጣ...
12/05/2025

"ከምስጉን ታዎቂ የቀዶ ህክምና ስፔሻሊስት የተላከ መልዕክት

"ውድ የኢትዮጵያ ህዝብ ሆይ: ስራ የምናቆመው:-

1. የተሻለ ህክምና እንደሚገባህ ስለምናምን የጤና ስርዓቱ ይሻሻል ብንል ሰሚ ስለአጣን ነው።

2. ታመህ ወደ ጤና ተቋም ስትሄድ ፊቱ ደስተኛ የሆነና ለማገልገል ዝግጁ የሆነ ሐኪም ታገኝ ዘንድ ነው::

3. መታከም በፈለግህበት ሰዓት ሁሉ ሄደህ ሐኪሙ የለም ሳትባል የሚመለከተውና የተሻለው ባለሞያ ጊዜ ሰጥቶ ያይህ ዘንድ ነው።

4. ማማከር የምትፈልገውን በነፃነት የምታማክርበትና በነፃነት እንደቤትህ የምትቆጥረው ጤና ተቋም ይኖርህ ዘንድ ነው።

ባይሆንማ ኖሮ የጤና ባለሞያው ቢነግድ ማትረፍ ፣ ቢያርስ ማምረት ፣ ቢፈልግ ደግሞ ሀገር ጥሎ የተሻለ ቦታ መሄድ የሚችል እንደሆነ ይታወቃል::

ሀገር ስታድግ ዜጎቿ የተሻለ ኑሮ እንዲኖሩ እንጂ የተገላቢጦሽ የተማሩና ህዝብ የሚያገለግሉ ልጆቿ እንዲራቡ የሚሆኑት በስርዓት ችግር እንጂ በሀገር አቅም ማጣት አይደለም።

ስለዚህ ስለነገው የጤና ስርዓት ስትል አግዘን። ከጎናችንም ሁን። ስርዓቱ ሲስተካከል ደግሞ ሌት ተቀን እንደምናገለግልህ ቃላችን ነው።"
Dr. DEBOL

ቋራ  የቴዎድሮስ አገር ላይ
09/05/2025

ቋራ የቴዎድሮስ አገር ላይ

19/04/2025

ሞገስና ፖለቲከኛ ልደቱ አያሌው

ባለ ንስር ዐይኑ ጎል ቀማሚ - ኬ ዲ ቢ "በኢቲሃድ መግቢያ ሀውልት እንደሚቆምለት እምነቴ ነው" ቁጥሮች አይዋሹም ይባላል፤ በዘጠኝ ዓመት የውሃ ሰማያዊዎቹ ቤት ቆይታው ከሪያን ጊግስ ቀጥሎ በ...
05/04/2025

ባለ ንስር ዐይኑ ጎል ቀማሚ - ኬ ዲ ቢ

"በኢቲሃድ መግቢያ ሀውልት እንደሚቆምለት እምነቴ ነው"

ቁጥሮች አይዋሹም ይባላል፤ በዘጠኝ ዓመት የውሃ ሰማያዊዎቹ ቤት ቆይታው ከሪያን ጊግስ ቀጥሎ በፕሪሚየር ሊጉ ለጎል የሚሆኑ ኳሶችን አመቻችቶ በማቀበል ስሙን በስኬት መዝገብ አስፍሯል።

ጎል ከማይነጥፍበት የማንቸስተር ሲቲ የፊት መስመር ጀርባ በንስር ዐይኑ አሻግሮ በማማተር ኳስን ሲጠበብባት ዓለም የተመለከተው ኮከብ ከቁጥሮችም በላይ መሆኑን አሳይቷል።

የኳስን መዳረሻ እቅጩን በመመተር ለ174 ጎሎች መቆጠር ቀጥተኛ ሚና የነበረው ቤልጂየማዊው አማካይ፥ 106 ጊዜ ኳስን ከመረብ አገናኝቷል። የማንቸስተር ሲቲ የጎል ጠንሳሽ ሆኖ ወደ ኢቲሃድ ከመምጣቱ አስቀድሞ ለቼልሲ ተጫውቷል።

በቤልጅየሙ ጁፒለር ፕሮ ሊግ በጄንክ ክለብ በፈረንጆቹ 2009 የተጀመረው የፕሮፌሽናል እግር ኳስ ህይወቱ በበርካታ ዋንጫዎች ታጅቦ ዘልቋል። በፕሮ ሊጉ ባሳየው ብቃት በቼልሲ ዐይን ውስጥ መግባት የቻለው ቤልጂየማዊው ኮከብ በ2012 የሰማያዊዎቹ ንብረት በመሆን በቀጣዩ ዓመት በወርደር ብሬመን በውሰት አሳልፏል።

ከአንድ ዓመት የውሰት ቆይታ በኋላ በስታምፎርድ ብሪጅ በቂ ዕድል ማግኘት ሳይችል ሌላኛውን የቡንደስሊጋው ክለብ ዎልቭስበርግን ተቀላቀለ።

በጀርመኑ ክለብ የመጀመሪያ አመት ቆይታው 16 ጎሎችን ከማስቆጠር ባለፈ በአንድ የውድድር አመት 21 ለጎል የሚሆኑ ኳሶችን በማቀበል የቡንደስሊጋውን ሪከርድ የግሉ ማድረግ ችሏል።

በአመቱ ባሳየው ድንቅ ብቃት የቡንደስሊጋው የአመቱ ምርጥ ተጫዋች ሽልማትን ተቀዳጅቷል። ከዚያም ወደ እንግሊዝ በመመለስ ከማንቸስተር ሲቲ ጋር በዋንጫዎች ያሸበረቁና በግሉም የጎመራባቸውን ስኬታማ አመታትን አሳልፏል።

በእነዚህ 10 ዓመታት የኢቲሃድ ቆይታው አንድ የቻምፒየንስ ሊግ፣ ስድስት የፕሪሚየር ሊግ፣ 5 የካራባኦና 2 የኤፍ ኤ ዋንጫዎችን ጨምሮ በድምሩ 19 ዋንጫዎችን መሳም ችሏል።

ኬቨን ዲብሮይን በውድድር አመቱ መጨረሻ ከማንቸስተር ሲቲ ጋር እንደሚለያይ ይፋ ማድረጉን ተከትሎ ፔፕ ጋርዲዮላ በሰጡት አስተያየት 'አሳዛኝ ቀን' ሲሉ ተደምጠዋል።

"እሱ በፕሪሚየር ሊጉ ከተመለከትናቸው ታላላቅ ተጫዋቾች መካከል አንዱ ነው፣ በኢቲሃድ መግቢያ ሀውልት እንደሚቆምለት እምነቴ ነው" ሲሉ ፔፕ ስለ ኬቨን ስንብት ሀሳባቸውን ገልጸዋል።

ያለፉት ዓመታት ስኬት ያለ ኬቨን ዲብሮይን የሚታሰብ አይደለም ሲሉም ለነበረው ከፍተኛ አስተዋጽኦ ዕውቅና ሰጥተዋል።

ኬቨን ዴብሮይን በ2019/20 በአንድ የውድድር አመት 20 ለጎል የሚሆኑ ኳሶችን አመቻችቶ በማቀበል በቀድሞው የአርሰናል ኮከብ ቲየሪ ሄንሪ የተያዘውን ሪከርድ መጋራቱ ይታወሳል።

የቀድሞው የፈረንሳይ ብሔራዊ ቡድንና የመድፈኞቹ አጥቂ ቲየሪ ሄንሪ በአንድ ወቅት ስለ ዲብሮይን በሰጠው አስተያየት፥ 'ከሌላ ፕላኔት የመጣ ከአዕምሮ በላይ የሆነ ተጫዋች ነው' ሲል አድናቆቱን ገልጾ ነበር።

በውሃ ሰማያዊው በ17 ቁጥር ማሊያ ወርቃማ ጊዜያትን ያሳለፈው ቤልጂየማዊው ድንቅ አማካይ ከማንቼስተር ሲቲ ጋር ሊለያይ መውጫው በር ላይ ተገኝቷል። ቀጣይ ማረፊያው የት ይሆናል? ዳግም በትልቅ ደረጃ እንመለከተው ይሆን? የእግር ኳሱ ቤተሰብ ጥያቄ ነው።

24/03/2025

ፖለቲካችን አ.ብ.ዷ.ል..!

ያለንበት አሳዛኝ ሁኔታ... እውነታው ይሄ ነው❗️ባሳለፍነው 6 ወራት ውስጥ ብቻ.. ከ330 በላይ ህፃናት በምግብ እጥረት ሞተዋል! የኢትዮጲያ የህብረሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ሪፖርት
09/02/2025

ያለንበት አሳዛኝ ሁኔታ... እውነታው ይሄ ነው❗️

ባሳለፍነው 6 ወራት ውስጥ ብቻ.. ከ330 በላይ ህፃናት በምግብ እጥረት ሞተዋል!
የኢትዮጲያ የህብረሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ሪፖርት

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethio Fact Info posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Ethio Fact Info:

Share