Ethio Fact Info

Ethio Fact Info ቅንልብ ያላቸው ሁሌም ደስተኞች ናቸው
(1)

ታዋቂው የእስልምና ሃይማኖት መምህር ኡስታዝ አህመዲን ጀበል  በምስራቅ አርሲ ዞን በኦርቶዶክስ ክርስትና እምነት ተከታዮች ላይ የደረሰውን ዘግናኝ ጭፍጨፋ፣ እንዲሁም የመኖሪያ ቤቶች እና የቤተ...
03/06/2026

ታዋቂው የእስልምና ሃይማኖት መምህር ኡስታዝ አህመዲን ጀበል በምስራቅ አርሲ ዞን በኦርቶዶክስ ክርስትና እምነት ተከታዮች ላይ የደረሰውን ዘግናኝ ጭፍጨፋ፣ እንዲሁም የመኖሪያ ቤቶች እና የቤተ ክርስቲያን ቃጠሎ አጥብቀው አወገዙ። ኡስታዙ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት ወቅታዊ መልእክት "የንጹሃን ደም መፍሰስ ይብቃ፡ ለዘላቂ ሰላም በጋራ እንምከር!" በማለት ጥሪ አቅርበዋል።

በዚህ መልእክታቸው የፍትህ እጦት ጉዳይን በስፋት ያነሱት ኡስታዝ አህመዲን፣ ባለፉት ዓመታት በንጹሃን ዜጎች፣ በመስጊዶች እና በቤተክርስቲያኖች ላይ ጥቃት ያደረሱ አካላት በህግ ቁጥጥር ስር ውለው ተጠያቂ አለመደረጋቸው እጅግ አሳሳቢ መሆኑን ገልጸዋል። ጥቃቶቹ እየተደጋገሙ ፈጻሚዎቹ ግን ሁልጊዜም "ያልታወቁ" እየተባሉ መፍትሄ አለመገኘቱ፣ ሀገሪቱን ወደ ከፋ አደጋ የሚመራ አካሄድ መሆኑንም በጽኑ አስጠንቅቀዋል።

በተጨማሪም የሰው ልጅ ነፍስ መርከሱ እጅግ አደገኛ መሆኑን የጠቀሱት የሃይማኖት መምህሩ፣ የሰውን ልጅ ህይወት ክቡርነት ከቅዱስ ቁርኣን አል-ማኢዳህ (5:32) ምዕራፍ ዋቢ በማድረግ አስተምረዋል።

በዚህ መለኮታዊ መመሪያ መሰረት አንዲትን ንጹሕ ነፍስ ያለ አግባብ መቅጠፍ መላውን የሰውን ዘር እንደ ማጥፋት የሚቆጠር እጅግ ከባድ ወንጀል መሆኑን አስገንዝበዋል። በአንጻሩ አንዲት ነፍስን ማዳን መላውን የሰው ልጅ እንደማኖር የሚቆጠር ታላቅ ሰብአዊ በጎነት መሆኑን ጠቅሰው፣ ይህ መመሪያ የሰው ልጅን ህይወት ያለምንም የዘር፣ የሃይማኖትና የብሔር ልዩነት ፍጹም የተከበረ መሆኑን እንደሚያሳይ አብራርተዋል።

ይህንን የጥፋት አዙሪት አስቁሞ ዘላቂ መፍትሄ ለማምጣት፣ ማህበረሰቡ ከስሜታዊነት ርቆ ቆም ብሎ ማሰብ፣ ነገሮችን በእርጋታ መመርመር እና በጋራ መምከር እንደሚያስፈልገው ኡስታዝ አህድን አሳስበዋል።

ኡዝታዙ ድርጊቱ ልብን በሀዘን የሚሰብር መሆኑን ጠቅሰው፣ ለሟች ቤተሰቦች እና ለወዳጅ ዘመዶቻቸው መጽናናትን ተመኝተዋል። እውነቱ ወጥቶ የንጹሃን ደም አፍሳሾች የፈጸሙት ወንጀል በምድር ዋጋ አግኝተው ለሌሎች መቀጣጫ እንዲሆኑ፣ ፈጣሪን በጸሎት በመጠየቅ ሀሳባቸውን አጠቃለዋል።

ማን.ዩናይትድ ሊቨርፑልን 3ለ2 በማሸነፍ ወደ ሻምፒዮንስ ሊግ መመለሱን አረጋገጠ።  𝐇𝐄𝐑𝐄 𝐖𝐄 𝐆𝐎! 𝐌𝐀𝐍𝐂𝐇𝐄𝐒𝐓𝐄𝐑 𝐔𝐍𝐈𝐓𝐄𝐃 𝐀𝐑𝐄 𝐁𝐀𝐂𝐊 𝐈𝐍 𝐂𝐇𝐀𝐌𝐏𝐈𝐎𝐍𝐒 𝐋𝐄𝐀𝐆𝐔𝐄 𝐅𝐎𝐑 𝐒𝐄𝐀𝐒...
03/05/2026

ማን.ዩናይትድ ሊቨርፑልን 3ለ2 በማሸነፍ ወደ ሻምፒዮንስ ሊግ መመለሱን አረጋገጠ። 𝐇𝐄𝐑𝐄 𝐖𝐄 𝐆𝐎!
𝐌𝐀𝐍𝐂𝐇𝐄𝐒𝐓𝐄𝐑 𝐔𝐍𝐈𝐓𝐄𝐃 𝐀𝐑𝐄 𝐁𝐀𝐂𝐊 𝐈𝐍 𝐂𝐇𝐀𝐌𝐏𝐈𝐎𝐍𝐒 𝐋𝐄𝐀𝐆𝐔𝐄 𝐅𝐎𝐑 𝐒𝐄𝐀𝐒𝐎𝐍 𝟐𝟔/𝟐𝟕! 🏆

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ለኤርትራ ምላሽ ሰጠኢትዮጵያ አሁን ላይ የባህር በር ያስፈልጋታል ወይስ አያስፈልጋትም የሚለውን መመለስ የምንችለው እኛና እኛ ኢትዮጵያዊያን ብቻ ነን ሲል የውጭ ጉዳይ ሚ...
18/09/2025

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ለኤርትራ ምላሽ ሰጠ

ኢትዮጵያ አሁን ላይ የባህር በር ያስፈልጋታል ወይስ አያስፈልጋትም የሚለውን መመለስ የምንችለው እኛና እኛ ኢትዮጵያዊያን ብቻ ነን ሲል የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡ ሚኒስትር መስሪያ ቤቱ ይህንን የገለጸው በባህር ጥያቄ ላይ በኤርትራ በኩል የሚሰነዘሩ ሀሳቦችን በተመለከተ ማብራሪያ በሰጠበት ወቅት ነው።

የኢፌዴሪ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በዛሬው ዕለት በሰጠው ሳምንታዊ መግለጫ፤ 4 ዋና ዋና ጉዳዮች ላይ ትኩረት አድርጓል። እነርሱም የሕዳሴ ግድብ መመረቅ እና ዲፕሎማሲያዊ አድምታዎቹን፣ ባሳለፍነው ሳምንት የተከናወኑ የአፍሪካ ካሬቢያን ሀገራት እና የአፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤን በተለመለከተ እንዲሁም፤ በቀጣይ ሳምንት በሚከናወነው 80ኛው የተባበሩት መንግሥታት ጉባኤን የተመለከቱ ናቸው።

ቀጣይ ሳምንት በሚካሄደው 80ኛው የተባበሩትን መንግሥታት ድርጅት ጉባኤ መስራች የሆነችው ኢትዮጵያ በዚህ ጉባኤ ተሳታፊ ከሆኑ ሀገራት መካከል ስትሆን፤ ብሔራዊ ጥቅሟቿን ለማስጠበቅ ትሳተፋለች ሲሉም የሚኒስቴሩ ቃል አቀባይ አምባሳደር ነቢያት ጌታቸው ተናግረዋል።

አምባሳደሩ "ከሰሞኑ በተለያዩ መድረኮች የኢትዮጵያ ባለስልጣናት የባህር በርን በተመለከተ እየሰጡት ያለውን አስተያየት አስመልክቶ የኤርትራ መንግሥትን ምላሽ እንዴት ይመለከቱታል?" ተብለው ተጠይቀዋል።

ይህንን ሲመልሱም፤ የባህር በር አስፈላጊነትን በሚመለከት በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ እንዲሁም ከፍተኛ አመራሮች በተደጋጋሚ የተገለጸ ነው ብለዋል።

በተጨማሪም "የባህር በር ለምን እንደሚያስፈልግ የምናውቀው እኛ ኢትዮጵያዊን ብቻ ነን!" ያሉ ሲሆን ለምን እንደሚያስፈልገን በግልፅ አስቀምጠናል" ሲሉም ገልጸዋል። ይህንን ማግኘት የምንችልበት ሰላማዊ፣ ዲፕሎማሲያዊ፣ ፍትሀዊ እና ሕጋዊ መንገድ በተመለከተ ይሆናል ሲሉም አስረድተዋል።

ይህ የባህር በር አስፈላጊነት በተመለከተ በኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን በጎረቤት ሀገራት መሪዎች ጭምር መገለጹን አስረደተዋል። ከሰሞኑ የሶማሊያው ፕሬዝዳት ሀሰን ሼክ መሐመድ በሰጡት ቃል መልልስ ላይ የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ ተገቢነት ያለው ነው ማለታቸው መዘገቡ ይታወሳል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ "ዛሬ የኛ የሆነውን ቀይ ባሕርን መልሶ ለመጠየቅ የሚሰጋ፣ የሚጠራጠር ትውልድ መፈጠሩ የሥነ-ልቦና ስብራት አካል ነው" ማለታቸው ይታወሳል፡፡

ዴቪድ ዴህያ ወደ ኦልትራፎርድበማንቼስተር ዩናይትድ ቤት የራሳቸውን ዐሻራ አሳርፈው ካለፉ እና አሁንም ድረስ በኦልድትራፎርድ ከሚናፈቁ ተጫዋች መካከል አንዱ ነው ስፔናዊው ግብ ጠባቂ ዴቪድ ዴህ...
08/08/2025

ዴቪድ ዴህያ ወደ ኦልትራፎርድ

በማንቼስተር ዩናይትድ ቤት የራሳቸውን ዐሻራ አሳርፈው ካለፉ እና አሁንም ድረስ በኦልድትራፎርድ ከሚናፈቁ ተጫዋች መካከል አንዱ ነው ስፔናዊው ግብ ጠባቂ ዴቪድ ዴህያ፡፡

ሰር አሌክስ ፈርጉሰን በ2012/13 የውድድር ዓመት የሊጉን ዋንጫ አሳክተው ከዩናይትድ ጋር ከተለያዩ በኋላ ቡድኑ ደካማ የውድድር ዓመታትን ሲያሳልፍ እሱ በግሉ ምርጥነቱን በተደጋጋሚ አሳይቷል፡፡

ከፈርጉሰን መልቀቅ በኋላ ወደ ኦልድትራፎርድ የመጡ የተለያዩ አሰልጣኞች ቡድኑን ወደ ክብሩ መመለስ ባይችሉም ዴህያ ብቻውን ጨዋታዎችን አሸንፎ የሚወጣ ግብ ጠባቂ ነበር፡፡ ለዚህም የቀድሞ የአርሰናል አሰልጣኝ አርሰን ቬንገር “ግብ ጠባቂ አንድን ጨዋታ ብቻውን አሸንፎ ከወጣ እሱ ዴቪድ ዴህያ ብቻ ነው” ሲሉ ምስክርነታቸውን ሰጥተዋል።

ከዴቪድ ሞዬስ እስከ ሊዊ ቫንሀል፤ ከጆዜ ሞሪኒሆ እስከ ኦሊጉነር ሶልሸር፤ ከራልፍ ራኚክ እስከ ኤሪክ ቴንሀግ ባሉ አሰልጣኞች ስር ማንቼስተር ዩናይትድ በፊት በሚታወቀው ገናናነቱ መቀጠል ባይችልም እሱ ግን ብቻውን ልዩ ነበር፡፡

አሰልጣኝ ኤሪክ ቴንሀግ ለእኔ የአጨዋወት ፍልስፍና ዴህያ አይሆንም በማለት ገፍተው እንዳስወጡት የሚታወስ ሲሆን፤ ዴህያን በማባረር ያመጡት ግብ ጠባቂ አንድሬ ኦናና በየጨዋታው ስህተት የሚሰራ እና በርካታ ጎል የሚቆጠርበት ግብ ጠባቂ ሆኖ ቡድኑን ዋጋ እያስከፈለ ይገኛል፡፡

ይህንንም የተመለከቱ የማንቼስተር ዩናይትድ ደጋፊዎች እሱን መናፈቅ እና በድጋሚ በኦልድትራርድ መመልከት የሁል ጊዜ ምኞታቸው ነው፡፡

የቀያይ ሰይጣኖቹ ደጋፊዎች ዴህያን ቢናፍቁ አያስገርምም፤ ቡድናቸው ማንቼስተር ዩናይትድ ፈርጉሰንን ካጣ በኋላ ባለፉት ዓመታት ጨዋታዎችን ለማሸነፍ በሚቸገረው ቡድን ውስጥ የዴህያ አዳኝ እጆች ከጨዋታው ነጥብ እንዲያገኙ ሚናው የሚተካ አልነበረም፡፡

የድንቅ ችሎታ እና ተሰጥኦ ባለቤቱ ዴህያ በሚቸገረው ዩናይትድ ውስጥ በእሱ ልዩነት ፈጣሪነት ክለቡ ጨዋታዎችን አሸንፎ ሲወጣ መመልከት የተለመደ ነበር፡፡

ዩናይትድን ከለቀቀ በኋላ ለአንድ ውድድር ዓመት ያህል ክለብ አልባ ሆኖ ከቆየ በኋላ ወደ ጣሊያን በመጓዝ ፊዮረንቲናን መቀላቀሉ ይታወሳል፡፡ በተጠናቀቀው የውድድር ዓመት ፊዮረንቲና በጣሊያን ሴሪ ኤ 6ኛ ደረጃን ይዞ እንዲያጠናቅቅ ዴቪድ ዴህያ ትልቁን አስተዋፅኦ አበርክቷል፡፡

እንደተለመደው ሁሉ ስፔናዊው ግብ ጠባቂ ዴቪድ ዴህያ በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ያሳይ የነበረውን ድንቅ እንቅስቃሴ በጣሊያን ሴሪኤ በድጋሚ አሳይቷል፡፡

የማንችስተር ዩናይትድ የቀድሞ ግብ ጠባቂ ዴቪድ ዴህያ 12 ዓመታትን ካሳለፈበት ክለቡ በፈረንጆቹ 2023 በነፃ መልቀቁ የሚታወስ ሲሆን÷ ነገ ወደ ኦልትራፎርድ በመምጣት የቀድሞ ክለቡን በተቃራኒ ይገጥማል፡፡

ዴቪድ ዴህያ የጨዋታው ቀን ከመድረሱ አስቀድሞ ወደ ኦልትራፎርድ መጥቶ እንደሚጫወት በማህበራዊ ትስስር ገጽ ላይ ካሰፈረ በኋላ በኦልድትራፎርድ በጉጉት እየተጠበቀ ይገኛል፡፡

ብሩኖ ፈርናንዴዝ እና ዴቪድ ዴህያ ከነገው ጨዋታ አስቀድሞ በማህበራዊ ትስስር ገፅ በተለዋወጡት መልዕክት፤ ፈርናንዴዝ ጎል እንደማስቆጥርብህ ተስፋ አደርጋለሁ ሲል ዴህያ በበኩሉ እንገናኛለን የሚል ምላሽ ሰጥቶታል፡፡

ነገ 8 ሰዓት ከ45 ላይ ማንቼስተር ዩናይትድ የጣሊያኑን ክለብ ፊዮረንቲናን በሜዳው ኦልድትራርድ ያስተናግዳል፡፡ ምንም እንኳን በእነሱ በኩል ተሰልፎ ባይጫወትም ዩናይትዶች የናፈቃቸውን ውድ ልጃቸውን ዴቪድ ዴህያን በኦልድትራፎርድ ሲጫወት ይመለከቱታል፡፡

ክርስቲያኖ ሮናልዶና ጠቅላይ ሚንስትር ኬር ስታርሜር በዲየጎ ዦታ ህልፈት ሀዘናቸውን ገለጹ በመኪና አደጋ ህይወቱ ያለፈው የሊቨርፑሉ  አጥቂ ዲየጎ ዦታን በተመለከተ ብዙዎች ሀዘናቸውን እየገለጹ...
03/07/2025

ክርስቲያኖ ሮናልዶና ጠቅላይ ሚንስትር ኬር ስታርሜር በዲየጎ ዦታ ህልፈት ሀዘናቸውን ገለጹ

በመኪና አደጋ ህይወቱ ያለፈው የሊቨርፑሉ አጥቂ ዲየጎ ዦታን በተመለከተ ብዙዎች ሀዘናቸውን እየገለጹ ይገኛሉ፡፡

የፖርቹጋል ብሔራዊ ቡድን አምበል ክርስቲያኖ ሮናልዶ ለዦታ ቤተሰቦች፣ ለባለቤቱ ለልጆቹ እና ለአድናቂዎቹ መጽናናትን ተመኝቷል፡፡ የአል ናስሩ አጥቂ ሮናልዶ በብሔራዊ ቡድን ከዦታ ጋር አብሮ ተጫውቷል፡፡

የእንግሊዝ ጠቅላይ ሚንስትር ኬር ስታርሜር በድንገተኛው የፖርቹጋላዊ ተጫዋች ህልፈት ሀዘናቸውን ገልጸዋል፡፡ ተጫዋቾች እንዲሁም ደጋፊዎች የ28 አመቱን ኮከብ ህልፈት ተከትሎ ሀዘናቸውን እየገለጹ ይገኛሉ፡፡ ከታናሽ ወንድሙ ጋር ህይወቱ ያለፈው ዲየጎ ዦታ የሶስት ልጆት አባት ሲሆን በቅርቡ ነበር የተሞሸረው፡፡

ዓለም የጋዛ እልቂትን ሊዘነጋው አይገባም - አንቶኒዮ ጉተሬዝ..........................አለም በጋዛ ያለው ጦርነት እያደረሰው ያለውን እልቂት ሊዘነጋው አይገባም ሲሉ የመንግስታቱ...
29/06/2025

ዓለም የጋዛ እልቂትን ሊዘነጋው አይገባም - አንቶኒዮ ጉተሬዝ..........................

አለም በጋዛ ያለው ጦርነት እያደረሰው ያለውን እልቂት ሊዘነጋው አይገባም ሲሉ የመንግስታቱ ድርጅት ዋና ጸሐፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ ተናገሩ፡፡ በጋዛ እስካሁን 56 ሺህ ገደማ ሰዎች መሞታቸውን መረጃዎች አመላክተዋል፡፡

የንፁሃን ግድያ አሁንም አልቆመም ያሉት የመንግስታቱ ድርጅት ዋና ጸሐፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ ዘላቂ የተኩስ አቁም ስምምነት እንዲደረስ መስራት ያስፈልጋል ብለዋል፡፡

በተለይ በእስራኤል እና ኢራን ግጭት ወቀት ጋዛ ተዘንግቷል ያሉት ዋና ጸሐፊው ይህን ግጭት እልባት ለመስጠት የተሰጠው ትኩረት ጋዛ ላይም መደረግ አለበት ሲሉ ተናግረዋል፡፡

በእስራኤል እና ኢራን መካከል የተደረሰው የተኩስ አቁም ተስፋ የሚሰጥ መሆኑንም ገልፀዋል:: በቀጣይ በጋዛ የተኩስ አቁም ስምምነት እንዲደረስ ብዙ መሰራት አለበት ማለታቸውን ሲጂቲኤን ዘግቧል፡፡

ፕሬዚዳንት ረጀብ ጣይብ ኤርዶኻን እና ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በሔግ ተወያዩ .....................የቱርኪዬው ፕሬዚዳንት ረጀብ ጣይብ ኤርዶኻን እና ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በ...
25/06/2025

ፕሬዚዳንት ረጀብ ጣይብ ኤርዶኻን እና ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በሔግ ተወያዩ .....................

የቱርኪዬው ፕሬዚዳንት ረጀብ ጣይብ ኤርዶኻን እና ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በዘ ሔግ እየተካሄደ ካለው የኔቶ ጉባኤ ጎን ለጎን ተገናኝተው በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይተዋል።

ሁለቱ መሪዎች በትናንትናው ዕለት ባደረጉት ውይይት በቀጣናዊ እና ዓለም አቀፋዊ እንዲሁም የሁለትዮሽ ጉዳዮች ላይ መክረዋል። ፕሬዚዳንት ኦርዶኻን በዚሁ ወቅት በአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ጥረት የተደረሰውን የእስራኤል እና የኢራን የተኩስ አቁም ስምምነት በበጎ እንደተቀበሉት ገልጸዋል።

ፕሬዚዳንቱ ዘላቂ ሰላም እንዲመጣ፣ በጋዛ ያለው ቀውስ እንዲያከትም እና በዩክሬን ጉዳይ ላይ ንግግር እንዲቀጥል መጠየቃቸውን የቱርኪዬ የኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ባወጣው መግለጫ ጠቁሟል። ሀገራቸው በኢነርጂ፣ በኢንቨስትመንት እና በመከላከያ ዘርፍ ከአሜሪካ ጋር በትብብር መሥራት የምትችልባቸው አማራጮች መኖራቸውን ገልጸዋል።

በተለይም በሁለቱ ሀገራት መካከል የሚደረገውን የንግድ ልውውጥ ወደ 100 ቢሊዮን ዶላር ከፍ የማድረግ ዓላማን ለማሳካት የሚያስችል ዕድል እንዳለም መጠቆማቸው ነው የተገለጸው። ሁለቱ ፕሬዚዳንቶች በኔቶ ውስጥ ግንባር ቀደም አጋሮች በመሆን የድርጅቱን የመከላከያ አቅም ማሳደግ አስፈላጊ መሆኑን አስምረውበታል ሲል የዘገበው አናዶሉ ነው።

እስራኤል ለመካከለኛው ምስራቅ ሰላም ትልቁ እንቅፋት ነች ሲሉ ኤርዶጋን ተናገሩ የቱርኩ ፕሬዝዳንት ሬሲፕ ጣይብ ኤርዶጋን እንዳሉት እስራኤል በኢራን ላይ ያደረሰችው ጥቃት ከአሜሪካ ጋር አዲስ ...
21/06/2025

እስራኤል ለመካከለኛው ምስራቅ ሰላም ትልቁ እንቅፋት ነች ሲሉ ኤርዶጋን ተናገሩ

የቱርኩ ፕሬዝዳንት ሬሲፕ ጣይብ ኤርዶጋን እንዳሉት እስራኤል በኢራን ላይ ያደረሰችው ጥቃት ከአሜሪካ ጋር አዲስ ዙር የኒውክሌር ድርድር ቴህራን ከመጀመሩ በፊት በመሆኑ “ድርድሩን ለማበላሸት” ያለመ ነው ብለዋል።

የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በተገኙበት በኢስታንቡል በተካሄደው የዲፕሎማቲክ ኮንፈረንስ ላይ ንግግር ያደረጉት ኤርዶጋን የእስራኤልን “ፍፁም የሽፍታ ድርጊት አወግዛለው በማለት መካከለኛው ምስራቅን ለማተራመስ እየሞከረች ነው ሲሉ ከሰዋል።

የቱርኩ ፕሬዝዳንት የኔታኒያሁ መንግስት ለአካባቢው ሰላም እጅግ በጣም ወሳኝ እንቅፋት መሆኑን እያረጋገጡ ነው" ብለዋል።
አክለውም “የኔታንያሁ መንግስት ሰኔ 13 ላይ ያደረሰው ጥቃት የድርድር ሂደቱን ለማዳከም ያለመ ነው ብለዋል።
እስራኤል ለመካከለኛው ምስራቅ ሰላም ትልቁ እንቅፋት ነች ሲሉ ኤርዶጋን ተናገሩ

የቱርኩ ፕሬዝዳንት ሬሲፕ ጣይብ ኤርዶጋን እንዳሉት እስራኤል በኢራን ላይ ያደረሰችው ጥቃት ከአሜሪካ ጋር አዲስ ዙር የኒውክሌር ድርድር ቴህራን ከመጀመሩ በፊት በመሆኑ “ድርድሩን ለማበላሸት” ያለመ ነው ብለዋል።

የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በተገኙበት በኢስታንቡል በተካሄደው የዲፕሎማቲክ ኮንፈረንስ ላይ ንግግር ያደረጉት ኤርዶጋን የእስራኤልን “ፍፁም የሽፍታ ድርጊት አወግዛለው በማለት መካከለኛው ምስራቅን ለማተራመስ እየሞከረች ነው ሲሉ ከሰዋል።

የቱርኩ ፕሬዝዳንት የኔታኒያሁ መንግስት ለአካባቢው ሰላም እጅግ በጣም ወሳኝ እንቅፋት መሆኑን እያረጋገጡ ነው" ብለዋል።
አክለውም “የኔታንያሁ መንግስት ሰኔ 13 ላይ ያደረሰው ጥቃት የድርድር ሂደቱን ለማዳከም ያለመ ነው ብለዋል።

"ከምስጉን ታዎቂ የቀዶ ህክምና ስፔሻሊስት የተላከ መልዕክት"ውድ የኢትዮጵያ ህዝብ ሆይ: ስራ የምናቆመው:-1. የተሻለ ህክምና እንደሚገባህ ስለምናምን የጤና ስርዓቱ ይሻሻል ብንል ሰሚ ስለአጣ...
12/05/2025

"ከምስጉን ታዎቂ የቀዶ ህክምና ስፔሻሊስት የተላከ መልዕክት

"ውድ የኢትዮጵያ ህዝብ ሆይ: ስራ የምናቆመው:-

1. የተሻለ ህክምና እንደሚገባህ ስለምናምን የጤና ስርዓቱ ይሻሻል ብንል ሰሚ ስለአጣን ነው።

2. ታመህ ወደ ጤና ተቋም ስትሄድ ፊቱ ደስተኛ የሆነና ለማገልገል ዝግጁ የሆነ ሐኪም ታገኝ ዘንድ ነው::

3. መታከም በፈለግህበት ሰዓት ሁሉ ሄደህ ሐኪሙ የለም ሳትባል የሚመለከተውና የተሻለው ባለሞያ ጊዜ ሰጥቶ ያይህ ዘንድ ነው።

4. ማማከር የምትፈልገውን በነፃነት የምታማክርበትና በነፃነት እንደቤትህ የምትቆጥረው ጤና ተቋም ይኖርህ ዘንድ ነው።

ባይሆንማ ኖሮ የጤና ባለሞያው ቢነግድ ማትረፍ ፣ ቢያርስ ማምረት ፣ ቢፈልግ ደግሞ ሀገር ጥሎ የተሻለ ቦታ መሄድ የሚችል እንደሆነ ይታወቃል::

ሀገር ስታድግ ዜጎቿ የተሻለ ኑሮ እንዲኖሩ እንጂ የተገላቢጦሽ የተማሩና ህዝብ የሚያገለግሉ ልጆቿ እንዲራቡ የሚሆኑት በስርዓት ችግር እንጂ በሀገር አቅም ማጣት አይደለም።

ስለዚህ ስለነገው የጤና ስርዓት ስትል አግዘን። ከጎናችንም ሁን። ስርዓቱ ሲስተካከል ደግሞ ሌት ተቀን እንደምናገለግልህ ቃላችን ነው።"
Dr. DEBOL

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethio Fact Info posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Ethio Fact Info:

Share