Ethio Fact Info

Ethio Fact Info ቅንልብ ያላቸው ሁሌም ደስተኞች ናቸው
(1)

ዓለም የጋዛ እልቂትን ሊዘነጋው አይገባም - አንቶኒዮ ጉተሬዝ..........................አለም በጋዛ ያለው ጦርነት እያደረሰው ያለውን እልቂት ሊዘነጋው አይገባም ሲሉ የመንግስታቱ...
29/06/2025

ዓለም የጋዛ እልቂትን ሊዘነጋው አይገባም - አንቶኒዮ ጉተሬዝ..........................

አለም በጋዛ ያለው ጦርነት እያደረሰው ያለውን እልቂት ሊዘነጋው አይገባም ሲሉ የመንግስታቱ ድርጅት ዋና ጸሐፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ ተናገሩ፡፡ በጋዛ እስካሁን 56 ሺህ ገደማ ሰዎች መሞታቸውን መረጃዎች አመላክተዋል፡፡

የንፁሃን ግድያ አሁንም አልቆመም ያሉት የመንግስታቱ ድርጅት ዋና ጸሐፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ ዘላቂ የተኩስ አቁም ስምምነት እንዲደረስ መስራት ያስፈልጋል ብለዋል፡፡

በተለይ በእስራኤል እና ኢራን ግጭት ወቀት ጋዛ ተዘንግቷል ያሉት ዋና ጸሐፊው ይህን ግጭት እልባት ለመስጠት የተሰጠው ትኩረት ጋዛ ላይም መደረግ አለበት ሲሉ ተናግረዋል፡፡

በእስራኤል እና ኢራን መካከል የተደረሰው የተኩስ አቁም ተስፋ የሚሰጥ መሆኑንም ገልፀዋል:: በቀጣይ በጋዛ የተኩስ አቁም ስምምነት እንዲደረስ ብዙ መሰራት አለበት ማለታቸውን ሲጂቲኤን ዘግቧል፡፡

በእስራኤል ጥቃት ተገደሉ የተባሉ 3 የጦር መሪዎች የኢራን የድል በዓል ላይ ተገኙበእስራኤል ጥቃት ተገደሉ የተባሉ 3 የኢራን ጦር መሪዎች የኢራን የድል በዓልን ከሕዝብ ጋር ሲያከብሩ መታየታቸ...
25/06/2025

በእስራኤል ጥቃት ተገደሉ የተባሉ 3 የጦር መሪዎች የኢራን የድል በዓል ላይ ተገኙ

በእስራኤል ጥቃት ተገደሉ የተባሉ 3 የኢራን ጦር መሪዎች የኢራን የድል በዓልን ከሕዝብ ጋር ሲያከብሩ መታየታቸውን አናዶሉ እና የኢራን የሀገር ውስጥ ብዙኃን መገናኛዎች ዘግበዋል።

እስራኤል ከሰኔ 13 ጀምሮ የኢራን የጦር ጀኔራሎችን መግደሏን ያስታወቀች ሲሆን፤ ሦስቱ የኢራን የጦር መሪዎች በትናንትናው ዕለት ኢራን የድል በዓሏን ስታከብር ከህዝቡ ጋር በመገኘት አክብረዋል ብለዋል ምንጮቹ።

ከዚህ ውስጥ አንዱ የሆኑት የእስላማዊ አብዮታዊ ጥበቃ ኮርፕስ ቁድስ ኃይል አዛዥ ብርጋዴር ጀነራል ኢስማኢል ቃኣኒ በዓሉን ከሕብ ጋር ማክበራቸውን የኢራቅ የሀገር ውስጥ ብዙኃን መገናኛዎች ዘግበዋል።

በኢራን ታስኒም የዜና አገልግሎት የተለጠፈ ቪዲዮ ቃአኒ በዝግጅቱ ላይ ከተሰበሰቡት መካከል አሳይቷል። ኤጄንሲው በኤክስ ላይ ኮማንደር ቃአኒ ዛሬ በተካሄደው የቴህራን የድል በዓል ላይ ይገኛሉ ሲል ተናግሯል።

በዚህ ወር መጀመሪያ ላይ የኒውዮርክ ታይምስ ጋዜጣ ቃአኒ በእስራኤል ጥቃት ከተገደሉት የኢራን ጦር መሪዎች መካከል አንዱ እንደሆኑ ዘግቦ እንደነበር የሚታወስ ነው።

በተመሳሳይ የወቅቱ የመከላከያ ሚኒስትር እና የአየር ኃይል አዛዥ የነበሩ ብርጋዴር ጄኔራል አዚዝ ናስርዛዴህ በሰኔ ወር መጀመሪያ ላይ በመከላከያ ሚኒስቴር ላይ በተፈፀመ የአየር ጥቃት ተገድለዋል ተብለው የነበረ ቢሆንም በሕይወት እንዳሉ እና አሁንም በስልጣን ላይ እንደሚገኙ ተስኒም የዜና ወኪል ዘግቧል።

የአያቶላህ አሊ ኻሚኒ ከፍተኛ አማካሪ እና የደህንነት ዋና አማካሪ አድሚራል አሊ ሻምካኒ እ.ኤ.አ ሰኔ 13 ቀን 2025 በእስራኤል የአየር ጥቃት መሞታቸው ከተነገሩት አንዱ የነበሩ ናቸው።

አድሚራል አሊ ሻምካኒ በድል በዓሉ ላይ በመገኘት የድል በዓሉን አክብረዋል ሲሉ የኢራን የዜና ወኪሎች ዘግበዋል።

ፕሬዚዳንት ረጀብ ጣይብ ኤርዶኻን እና ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በሔግ ተወያዩ .....................የቱርኪዬው ፕሬዚዳንት ረጀብ ጣይብ ኤርዶኻን እና ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በ...
25/06/2025

ፕሬዚዳንት ረጀብ ጣይብ ኤርዶኻን እና ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በሔግ ተወያዩ .....................

የቱርኪዬው ፕሬዚዳንት ረጀብ ጣይብ ኤርዶኻን እና ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በዘ ሔግ እየተካሄደ ካለው የኔቶ ጉባኤ ጎን ለጎን ተገናኝተው በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይተዋል።

ሁለቱ መሪዎች በትናንትናው ዕለት ባደረጉት ውይይት በቀጣናዊ እና ዓለም አቀፋዊ እንዲሁም የሁለትዮሽ ጉዳዮች ላይ መክረዋል። ፕሬዚዳንት ኦርዶኻን በዚሁ ወቅት በአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ጥረት የተደረሰውን የእስራኤል እና የኢራን የተኩስ አቁም ስምምነት በበጎ እንደተቀበሉት ገልጸዋል።

ፕሬዚዳንቱ ዘላቂ ሰላም እንዲመጣ፣ በጋዛ ያለው ቀውስ እንዲያከትም እና በዩክሬን ጉዳይ ላይ ንግግር እንዲቀጥል መጠየቃቸውን የቱርኪዬ የኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ባወጣው መግለጫ ጠቁሟል። ሀገራቸው በኢነርጂ፣ በኢንቨስትመንት እና በመከላከያ ዘርፍ ከአሜሪካ ጋር በትብብር መሥራት የምትችልባቸው አማራጮች መኖራቸውን ገልጸዋል።

በተለይም በሁለቱ ሀገራት መካከል የሚደረገውን የንግድ ልውውጥ ወደ 100 ቢሊዮን ዶላር ከፍ የማድረግ ዓላማን ለማሳካት የሚያስችል ዕድል እንዳለም መጠቆማቸው ነው የተገለጸው። ሁለቱ ፕሬዚዳንቶች በኔቶ ውስጥ ግንባር ቀደም አጋሮች በመሆን የድርጅቱን የመከላከያ አቅም ማሳደግ አስፈላጊ መሆኑን አስምረውበታል ሲል የዘገበው አናዶሉ ነው።

እስራኤል ለመካከለኛው ምስራቅ ሰላም ትልቁ እንቅፋት ነች ሲሉ ኤርዶጋን ተናገሩ የቱርኩ ፕሬዝዳንት ሬሲፕ ጣይብ ኤርዶጋን እንዳሉት እስራኤል በኢራን ላይ ያደረሰችው ጥቃት ከአሜሪካ ጋር አዲስ ...
21/06/2025

እስራኤል ለመካከለኛው ምስራቅ ሰላም ትልቁ እንቅፋት ነች ሲሉ ኤርዶጋን ተናገሩ

የቱርኩ ፕሬዝዳንት ሬሲፕ ጣይብ ኤርዶጋን እንዳሉት እስራኤል በኢራን ላይ ያደረሰችው ጥቃት ከአሜሪካ ጋር አዲስ ዙር የኒውክሌር ድርድር ቴህራን ከመጀመሩ በፊት በመሆኑ “ድርድሩን ለማበላሸት” ያለመ ነው ብለዋል።

የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በተገኙበት በኢስታንቡል በተካሄደው የዲፕሎማቲክ ኮንፈረንስ ላይ ንግግር ያደረጉት ኤርዶጋን የእስራኤልን “ፍፁም የሽፍታ ድርጊት አወግዛለው በማለት መካከለኛው ምስራቅን ለማተራመስ እየሞከረች ነው ሲሉ ከሰዋል።

የቱርኩ ፕሬዝዳንት የኔታኒያሁ መንግስት ለአካባቢው ሰላም እጅግ በጣም ወሳኝ እንቅፋት መሆኑን እያረጋገጡ ነው" ብለዋል።
አክለውም “የኔታንያሁ መንግስት ሰኔ 13 ላይ ያደረሰው ጥቃት የድርድር ሂደቱን ለማዳከም ያለመ ነው ብለዋል።
እስራኤል ለመካከለኛው ምስራቅ ሰላም ትልቁ እንቅፋት ነች ሲሉ ኤርዶጋን ተናገሩ

የቱርኩ ፕሬዝዳንት ሬሲፕ ጣይብ ኤርዶጋን እንዳሉት እስራኤል በኢራን ላይ ያደረሰችው ጥቃት ከአሜሪካ ጋር አዲስ ዙር የኒውክሌር ድርድር ቴህራን ከመጀመሩ በፊት በመሆኑ “ድርድሩን ለማበላሸት” ያለመ ነው ብለዋል።

የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በተገኙበት በኢስታንቡል በተካሄደው የዲፕሎማቲክ ኮንፈረንስ ላይ ንግግር ያደረጉት ኤርዶጋን የእስራኤልን “ፍፁም የሽፍታ ድርጊት አወግዛለው በማለት መካከለኛው ምስራቅን ለማተራመስ እየሞከረች ነው ሲሉ ከሰዋል።

የቱርኩ ፕሬዝዳንት የኔታኒያሁ መንግስት ለአካባቢው ሰላም እጅግ በጣም ወሳኝ እንቅፋት መሆኑን እያረጋገጡ ነው" ብለዋል።
አክለውም “የኔታንያሁ መንግስት ሰኔ 13 ላይ ያደረሰው ጥቃት የድርድር ሂደቱን ለማዳከም ያለመ ነው ብለዋል።

"ከምስጉን ታዎቂ የቀዶ ህክምና ስፔሻሊስት የተላከ መልዕክት"ውድ የኢትዮጵያ ህዝብ ሆይ: ስራ የምናቆመው:-1. የተሻለ ህክምና እንደሚገባህ ስለምናምን የጤና ስርዓቱ ይሻሻል ብንል ሰሚ ስለአጣ...
12/05/2025

"ከምስጉን ታዎቂ የቀዶ ህክምና ስፔሻሊስት የተላከ መልዕክት

"ውድ የኢትዮጵያ ህዝብ ሆይ: ስራ የምናቆመው:-

1. የተሻለ ህክምና እንደሚገባህ ስለምናምን የጤና ስርዓቱ ይሻሻል ብንል ሰሚ ስለአጣን ነው።

2. ታመህ ወደ ጤና ተቋም ስትሄድ ፊቱ ደስተኛ የሆነና ለማገልገል ዝግጁ የሆነ ሐኪም ታገኝ ዘንድ ነው::

3. መታከም በፈለግህበት ሰዓት ሁሉ ሄደህ ሐኪሙ የለም ሳትባል የሚመለከተውና የተሻለው ባለሞያ ጊዜ ሰጥቶ ያይህ ዘንድ ነው።

4. ማማከር የምትፈልገውን በነፃነት የምታማክርበትና በነፃነት እንደቤትህ የምትቆጥረው ጤና ተቋም ይኖርህ ዘንድ ነው።

ባይሆንማ ኖሮ የጤና ባለሞያው ቢነግድ ማትረፍ ፣ ቢያርስ ማምረት ፣ ቢፈልግ ደግሞ ሀገር ጥሎ የተሻለ ቦታ መሄድ የሚችል እንደሆነ ይታወቃል::

ሀገር ስታድግ ዜጎቿ የተሻለ ኑሮ እንዲኖሩ እንጂ የተገላቢጦሽ የተማሩና ህዝብ የሚያገለግሉ ልጆቿ እንዲራቡ የሚሆኑት በስርዓት ችግር እንጂ በሀገር አቅም ማጣት አይደለም።

ስለዚህ ስለነገው የጤና ስርዓት ስትል አግዘን። ከጎናችንም ሁን። ስርዓቱ ሲስተካከል ደግሞ ሌት ተቀን እንደምናገለግልህ ቃላችን ነው።"
Dr. DEBOL

ቋራ  የቴዎድሮስ አገር ላይ
09/05/2025

ቋራ የቴዎድሮስ አገር ላይ

19/04/2025

ሞገስና ፖለቲከኛ ልደቱ አያሌው

ባለ ንስር ዐይኑ ጎል ቀማሚ - ኬ ዲ ቢ "በኢቲሃድ መግቢያ ሀውልት እንደሚቆምለት እምነቴ ነው" ቁጥሮች አይዋሹም ይባላል፤ በዘጠኝ ዓመት የውሃ ሰማያዊዎቹ ቤት ቆይታው ከሪያን ጊግስ ቀጥሎ በ...
05/04/2025

ባለ ንስር ዐይኑ ጎል ቀማሚ - ኬ ዲ ቢ

"በኢቲሃድ መግቢያ ሀውልት እንደሚቆምለት እምነቴ ነው"

ቁጥሮች አይዋሹም ይባላል፤ በዘጠኝ ዓመት የውሃ ሰማያዊዎቹ ቤት ቆይታው ከሪያን ጊግስ ቀጥሎ በፕሪሚየር ሊጉ ለጎል የሚሆኑ ኳሶችን አመቻችቶ በማቀበል ስሙን በስኬት መዝገብ አስፍሯል።

ጎል ከማይነጥፍበት የማንቸስተር ሲቲ የፊት መስመር ጀርባ በንስር ዐይኑ አሻግሮ በማማተር ኳስን ሲጠበብባት ዓለም የተመለከተው ኮከብ ከቁጥሮችም በላይ መሆኑን አሳይቷል።

የኳስን መዳረሻ እቅጩን በመመተር ለ174 ጎሎች መቆጠር ቀጥተኛ ሚና የነበረው ቤልጂየማዊው አማካይ፥ 106 ጊዜ ኳስን ከመረብ አገናኝቷል። የማንቸስተር ሲቲ የጎል ጠንሳሽ ሆኖ ወደ ኢቲሃድ ከመምጣቱ አስቀድሞ ለቼልሲ ተጫውቷል።

በቤልጅየሙ ጁፒለር ፕሮ ሊግ በጄንክ ክለብ በፈረንጆቹ 2009 የተጀመረው የፕሮፌሽናል እግር ኳስ ህይወቱ በበርካታ ዋንጫዎች ታጅቦ ዘልቋል። በፕሮ ሊጉ ባሳየው ብቃት በቼልሲ ዐይን ውስጥ መግባት የቻለው ቤልጂየማዊው ኮከብ በ2012 የሰማያዊዎቹ ንብረት በመሆን በቀጣዩ ዓመት በወርደር ብሬመን በውሰት አሳልፏል።

ከአንድ ዓመት የውሰት ቆይታ በኋላ በስታምፎርድ ብሪጅ በቂ ዕድል ማግኘት ሳይችል ሌላኛውን የቡንደስሊጋው ክለብ ዎልቭስበርግን ተቀላቀለ።

በጀርመኑ ክለብ የመጀመሪያ አመት ቆይታው 16 ጎሎችን ከማስቆጠር ባለፈ በአንድ የውድድር አመት 21 ለጎል የሚሆኑ ኳሶችን በማቀበል የቡንደስሊጋውን ሪከርድ የግሉ ማድረግ ችሏል።

በአመቱ ባሳየው ድንቅ ብቃት የቡንደስሊጋው የአመቱ ምርጥ ተጫዋች ሽልማትን ተቀዳጅቷል። ከዚያም ወደ እንግሊዝ በመመለስ ከማንቸስተር ሲቲ ጋር በዋንጫዎች ያሸበረቁና በግሉም የጎመራባቸውን ስኬታማ አመታትን አሳልፏል።

በእነዚህ 10 ዓመታት የኢቲሃድ ቆይታው አንድ የቻምፒየንስ ሊግ፣ ስድስት የፕሪሚየር ሊግ፣ 5 የካራባኦና 2 የኤፍ ኤ ዋንጫዎችን ጨምሮ በድምሩ 19 ዋንጫዎችን መሳም ችሏል።

ኬቨን ዲብሮይን በውድድር አመቱ መጨረሻ ከማንቸስተር ሲቲ ጋር እንደሚለያይ ይፋ ማድረጉን ተከትሎ ፔፕ ጋርዲዮላ በሰጡት አስተያየት 'አሳዛኝ ቀን' ሲሉ ተደምጠዋል።

"እሱ በፕሪሚየር ሊጉ ከተመለከትናቸው ታላላቅ ተጫዋቾች መካከል አንዱ ነው፣ በኢቲሃድ መግቢያ ሀውልት እንደሚቆምለት እምነቴ ነው" ሲሉ ፔፕ ስለ ኬቨን ስንብት ሀሳባቸውን ገልጸዋል።

ያለፉት ዓመታት ስኬት ያለ ኬቨን ዲብሮይን የሚታሰብ አይደለም ሲሉም ለነበረው ከፍተኛ አስተዋጽኦ ዕውቅና ሰጥተዋል።

ኬቨን ዴብሮይን በ2019/20 በአንድ የውድድር አመት 20 ለጎል የሚሆኑ ኳሶችን አመቻችቶ በማቀበል በቀድሞው የአርሰናል ኮከብ ቲየሪ ሄንሪ የተያዘውን ሪከርድ መጋራቱ ይታወሳል።

የቀድሞው የፈረንሳይ ብሔራዊ ቡድንና የመድፈኞቹ አጥቂ ቲየሪ ሄንሪ በአንድ ወቅት ስለ ዲብሮይን በሰጠው አስተያየት፥ 'ከሌላ ፕላኔት የመጣ ከአዕምሮ በላይ የሆነ ተጫዋች ነው' ሲል አድናቆቱን ገልጾ ነበር።

በውሃ ሰማያዊው በ17 ቁጥር ማሊያ ወርቃማ ጊዜያትን ያሳለፈው ቤልጂየማዊው ድንቅ አማካይ ከማንቼስተር ሲቲ ጋር ሊለያይ መውጫው በር ላይ ተገኝቷል። ቀጣይ ማረፊያው የት ይሆናል? ዳግም በትልቅ ደረጃ እንመለከተው ይሆን? የእግር ኳሱ ቤተሰብ ጥያቄ ነው።

24/03/2025

ፖለቲካችን አ.ብ.ዷ.ል..!

ያለንበት አሳዛኝ ሁኔታ... እውነታው ይሄ ነው❗️ባሳለፍነው 6 ወራት ውስጥ ብቻ.. ከ330 በላይ ህፃናት በምግብ እጥረት ሞተዋል! የኢትዮጲያ የህብረሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ሪፖርት
09/02/2025

ያለንበት አሳዛኝ ሁኔታ... እውነታው ይሄ ነው❗️

ባሳለፍነው 6 ወራት ውስጥ ብቻ.. ከ330 በላይ ህፃናት በምግብ እጥረት ሞተዋል!
የኢትዮጲያ የህብረሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ሪፖርት

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethio Fact Info posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Ethio Fact Info:

Share